Thursday, January 2, 2014

የከተማ አብዮት! – ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

January2/2014

ከሩሲያውያኑ ቦልሼቪክና ሜንሼቪክ አንስቶ፣ የእኛዎቹ ኢህአፓና መኢሶን በፊት-አውራሪነት እስከ ተሳተፉበት ድረስ ያሉ በደም የጨቀዩ አብዮቶች በሙሉ በከተሞች የተካሄዱ ሲሆን፣ አብዛኛው አጋፋሪዎቻቸው ደግሞ ልሂቃኖች እንደነበሩ በጉዳዩ ዙሪያ የተፃፉ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡ ይሁንና እነዚህ አብዮቶች (የተሳኩትም ሆነ የከሸፉት) ሰላማዊውንና ህጋዊውን መንገድ የተከተሉ ባለመሆናቸው ዛሬም ይዘገንናሉ፤ ለወደፊቱም ባልተደገሙ ያሰኛሉ፡፡ ስለምን ቢሉ? ግድግዳው ላይ የተቸከቸከው ፅሁፍ እንዲህ የሚል ምላሽ ያስነብባልና፡- በጭቁን ሕዝብ ስም የብዙሀኑን ቤት አፍርሰዋል፤ ሀገርና ታሪክ ለመቀየር የማይሳናቸው አፍላ ወጣቶችን እርስ በእርስ አጫርሰዋል፤ ‹አንቱ› ሊባሉ የሚችሉ ምሁራንን በአንድ ጀንበር ወደ ትንታግ ነፍሰ-ገዳይነት ቀይረዋል፤ ክስረቱም ከትውልድ ትውልድ የሚተላለፍ ጠባሳ ሆኖ ዛሬ ላይ ደርሷል…

በርግጥም ያ ወቅት መደማመጥ፣ መነጋገር፣ መወያየት፣ መቻቻልን… የመሳሰሉ ምክንያታዊ እሴቶች ህቡዕ ገብተው፤ መጯጯኽ፣ መነቋቆር፣ መፈራረጅ፣ መገዳደል… የገነኑበት ነበር፤ ለዚህም ይመስለኛል ሀገር ሊረከብ የተዘጋጀ አንድ ትውልድ፣ በተኮረጀ ርዕዮተ-ዓለም፣ ባልጠራ ፕሮግራም እቅሉን ስቶ ‹ማርክስ እንደፃፈው›፣ ‹ሌኒን እንዳብራራው›፣ ‹ማኦ እንዳስተማረው›፣ ‹ሆጃ እንደመከረው›… በሚል ጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት ስቶ-በማሳት፣ ሀገር ምድሩን የጦር አውድማ አድርጎ ማለፉ የትላንት የቁጭት ትዝታ የሆነብን፡፡ በአናቱም ዛሬ ‹‹ነፃ አወጣናችሁ›› እያሉ ጃሎታ የሚመቱት የኢህአዴግ መሪዎች ከዚሁ ምንጭ የተቀዱ፣ ግና በቃላት ስንጠቃና በጎሳ ጠባብ አስተሳሰብ የተለዩ የትውልዱና የመንፈሱ ተጋሪ በመሆናቸው፣ የሁነቱ ‹ታሪክ›ነት ለተሰዉት እንጂ፣ ለእነርሱ ‹ሀገር እየመራንበት ነው› የሚሉበት ‹ፖለቲካ› ነውና፣ የነገይቷ የምንወዳት ኢትዮጵያችን መፃኢ ዕድል ገና ከእርስ በእርስ ግጭት ስጋት አለመላቀቁን ያመላክታል፡፡ በዚህ ፅሁፍም የምንዘመርለት የ‹አትነሳም ወይ?› ድምፅ አደገኛውን ስርዓት የመቀየሪያው ጊዜ አሁን በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ግን እነኢህአፓ ተቸንፈው የተሰናበቱበትም ሆነ ኢህአዴግ ድል አድርጎ የመጣበት መንገድ ለዘመኑ መልካም ተሞክሮ ሊሆን ይችላል እንደማለት አይደለም፤ ምክንያቱም በእኔ እምነት የእነርሱ ‹ፋኖ ተሰማራ…› ጊዜው በበየነበት ሙዚየምና የታሪክ ትምህርት ክፍል ውስጥ ብቻ ካልተገደበ ጉዳቱ በቀላሉ የሚጠገን ካለመሆኑም ባለፈ፣ የምንመኘውን ለውጥ ሊያመጣ አይችልምና ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ለትውልዱ ክቡድ ጥያቄ ስኬታማነት መንገድ መሪ አብርሆት መሆን የሚችሉ የደም ግብር ያልጠየቁ፣ ፍፁም ሰላማዊና ህጋዊ በሆነ መንገድ በከተሞች ተካሂደው ሀገርና ህዝብ ያለ ብዙ ኪሳራ በአሸናፊነት የወጡባቸው በርካታ አብነታዊ አብዮቶች (እንደ አረቡ ፀደይም ሆነ እንደ አውሮፓውያኑ ጆርጂያና ዩክሬን ብርቱካናማ-አብዮቶች) መኖራቸው እውነት ነው፤ እንዲሁም በእነርሱ መንፈስ መቀደስ፣ በእነርሱ ፀበል መጠመቅ የአምባገነኑንና የበደለኛውን ሥርዓት እድሜ ለማሳጠር የሚያበረታ ኃይል ማስረፁ እውነት ነው፡፡

ከተማን እንደ ጠላት

የ‹ያ ትውልድ› የጠብ-መንጃ ትንቅንቅን በድል የተሻገረው ኢህአዴግ (ከልቡ አምኖበት ባይሆንም) ይህንን ሁሉ መስዋዕትነት የከፈለው በተለይም ለአርሶ አደሩ ጥቅም መሆኑን በአገኘው አጋጣሚ ሳይናገር አያልፍም፡፡ በግልባጩ ደግሞ የከተማ ነዋሪዎችን ‹ጠላት› አድርጎ በመፈረጅ ሲገነግን ተደጋግሞ ተስተውሏል፤ በርግጥ የዚህ መግፍኤ በብሔር እና በሀይማኖት የከፋፈለውን ሕዝብ፣ በመደብም ለያይቶ የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያ ለማድረግ እና በየአምስት ዓመቱ በሚያካሄደው የይስሙላ ‹ምርጫ› ኮረጆ ገልብጦ ሲያበቃ የፈረደበት ምስኪን አርሶ አደር ‹መርጦኛል› ለሚለው የተለመደ ሰበቡ ‹ይጠቅመኛል› በሚል ለማመቻቸት ‹አዛኝ ቅቤ…› ተቆርቋሪ በመሆኑ ይመስለኛል፡፡ ይህም ሆኖ ድርጅቱ ይህንን የማጭበርበሪያ ስልት በደደቢት በረሃ ራሱ የቀመረው ነው ብሎ ለመከራከር የሚያስችል ገፊ ጭብጥ ይኖራል ብዬ አላስብም፤ ምክንያቱም በአንዳንድ የዓለማችን ሀገራት የፖለቲካውን ኃይል ከጨበጡ በኋላ በሕዝባቸው ላይ ነጋሪት ጎስመው ሞትን ከነዙ፣ ስቃይን ከረጩ እርኩሳን መሪዎች (ፓርቲዎች) ድርሳናት ቃል-በቃል የተገለበጠ መሆኑን የሚያስረግጡ (በስነ-አመክንዮ) የተቀኙ ማሳያዎች ማቅረብ ይቻላልና፤ እንደምሳሌም አንዱን በአዲስ መስመር እንምዘዘው፡-

የ‹ኬመር ሩዥ› መንገድ

በተለምዶ ‹ኬመር ሩዥ› (Khmer Rouge) በመባል የሚታወቀውና አክራሪ ኮምኒስታዊ የገበሬዎች ድርጅት እንደሆነ የሚነገርለት ‹‹Communist Party of Kampuchea /CPK/›› እ.ኤ.አ ከ1975-1979 ዓ.ም ድረስ፣ በወጣት የገበሬ ሠራዊት ታግዞ በካምቦዲያ መንግስታዊ ሥልጣን ተቆናጥጦ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ጨካኝና አፍቃሪ ቻይና የሆነው የፓርቲው ሊቀ-መንበር ፖል ፖትም (Pol Pot)፣ ማኦ ዜዱንግ ‹‹የሀገሬን ኢኮኖሚ ያሳድግልኛል›› በማለት ያረቀቀውንና በግብርና ላይ የሚያተኩረውን ‹‹Great Leap Forward›› ፕሮግራም፣ ‹‹Super Great Leap Forward›› በሚል ተቀጥላ እንደወረደ በመኮረጅ ‹‹ሙሉ የካምቦዲያን ሕዝብ ወደ ‹እርሻ መር-ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ› (Agrarian Society) እቀይራለሁ›› ብሎ ያደረገው ሙከራ ወጪ-ኪሳራን ያወራረደው ሁለት ሚሊዮን ዜጎቹንለህልፈት በመዳረግ እንደ ነበር የታሪክ መፃህፍት ያትታሉ፡፡

ከሁሉም የከፋው ግን ፖል ፖትና ጓዶቹ ‹‹እውነተኛ ዜጋ ገበሬ ብቻ ነው›› በማለት የከተማ ነዋሪዎችን በጠላትነት ከፈረጁ በኋላ ‹‹ማህበረሰባችንን ለማንፃት›› በሚል የቁም-ቅዠት ምዕራባዊ አስተሳሰብ የተንፀባረቀበትን ማንኛውንም ጉዳይ፣ የከተማ ሕይወትን፣ ኃይማኖትን፣ ትምህርትን፣ አንድ ብርም ቢሆን በግል መያዝን… በአዋጅ ማገዳቸው ነበር፤ እንዲሁም ኢምባሴዎችን፣ ጋዜጣና ቴሌቪዥን ጣቢያን ዘግተዋል፤ በሁሉም የሀገሪቱ ከተሞች የሚኖሩ ዜጎችን በማፈናቀል ወደ ገጠር አግዘው፣ በግዳጅ የእርሻ ሥራ ላይ አሰማርተዋል፤ ከዋና ከተማዋ ‹ፈኖሞ ፔንህ› (Phnom Penh) ብቻ ሁለት ሚሊዮን ዜጎች ወደ ገጠር በእግር እንዲጓዙ በመገደዳቸው ሃያ ሺህ የሚሆኑት በጉዞ ላይ ወድቀው እንደወጡ ቀርተዋል፤ ገጠር የደረሱትንም ቢሆን ‹የግድያ ወረዳዎች› እያሉ በሚጠሯቸው የእርሻ ሥራ ላይ አሰማርተው ለአንድ ሰው በነፍስ ወከፍ በየሁለት ቀኑ አንዴ 180 ግራም ሩዝ ብቻ በመስጠት በረሀብ፣ በበሽታ፣ ብስቅየት እና በግድያ እንዲያልቁ አድርጓል፡፡ በመጨረሻም አገዛዙ በቬትናም ጣልቃ ገብነት እ.ኤ.አ በ1979 ዓ.ም በኃይል በመወገዱ፣ ፖል ፖት ከእነተከታዮቹ ሀገሩ ከታይላንድ ወደምትዋሰንበት ጠረፍ አካባቢ በመሸሽ፣ የትጥቅ ትግል እንደአዲስ ጀምሮ ለረዥም ዓመታት ከታገለ በኋላ፣ እ.ኤ.አ በ1997 ዓ.ም እርጅና ተጭኖት በህግ ቁጥጥር ስር በዋለ፣ በዓመቱ ከልብ ጋር በተያያዘ ህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉ ይታወቃል (በነገራችን ላይ ይህ ድርጅት የሽምቅ ውጊያ ከመጀመሩ በፊትም ሆነ በኋላ የተጠናከረበትን ምስጢራዊ መንገድ ጨምሮ የተከተለው ስልት ከሞላ ጎደል ከኢህአፓና ህወሓት አፈጣጠር ትርክት ጋር ተመሳሳይነት አለው)
ኢህአዴግ እንደ ‹ኬመር ሩዥ›

ከሁለት አስርተ ዓመታት የሥልጣን ቆይታም በኋላ፣ የከተማ ነዋሪዎችን በጠላትነት ካሰፈረበት ጥቁር መዝገቡ ላይ መሰረዙ ያልሆነለት ኢህአዴግ ‹እንደ ኬመር ሩዥ ሁሉንም የጭካኔ ተግባራት በአደባባይ ፈፅሟል› ተብሎ ባይወነጀልም፣ ተመሳሳይ ስልቶችን በመኮረጅ በረቀቀ መንገድ አለዝቦ መተግበሩን ግን መካድ አይቻልም፡፡ እንዲሁም የሁለቱ ድርጅቶች ዋነኛ ልዩነት ወደ እንዲህ አይነቱ የጥላቻ ጠርዝ የተገፉበት ምክንያት ይመስለኛል፤ ይኸውም ፈላጭ ቆራጩ ፖል ፖት በከተሜው ላይ የከፋ ቂም የቋጠረበት መነሾ፣ ከገበሬ ቤተሰብ መገኘቱን ጨምሮ፣ ከአስተዳደጉ ጋር በሚያያዙ ‹ህመማቸው-ህመሜ› በሚል ሲባጎ የተቋጠረ ሲሆን፣ መለስና ጓዶቹ ደግሞ የሥልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም በማስላት ብቻ መሆኑ ነው፤ መቼም መሬት የረገጠውን እውነታ ተመልክቶ የሀገሬ አርሶ አደር ከፕሮፓጋንዳ ፍጆታ በዘለለ፣ ከከተሜው የተለየ የመልካም አስተዳደርም ሆነ የመሰረተ-ልማት ተጠቃሚ አለመሆኑን መረዳቱ አዳጋች አይደለም፡፡

የሆነው ሆኖ የኢህአዴግ ‹ፀረ-ከተሜነት› እንዲህ በግላጭ አፍጥጦ የወጣው ከምርጫ 97 በኋላ ነው፤ በወቅቱ ጠቅላይ ሚንስትሩ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርቦ፣ ድርጅቱ በከተሞች መሸነፉን ከገለፀ በኋላ፣ በገጠር ሙሉ በሙሉ ስለተሳካለት መንግስት ለመመስረት የሚያስችል የመራጭ ድምፅ ማግኘቱን አውጇል፤ ይህንንም ተከትሎ ግንባሩን ያልመረጡ የከተማ ነዋሪዎች በተቀነባበረ ሴራ የጥቃት ዒላማ መሆናቸውን የሚያመላክቱ በርካታ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡ በተለይም በድህረ-ምርጫው ከተሜውን ዒላማ ያደረጉ በስራ ላይ የዋሉ አፋኝ ህጎች እና ፖሊሲዎችን ጨምሮ በደባ የተፈፀሙ መንግስታዊ ጥፋቶችን ዘርዘር አድርገን እንያቸው፡፡

መሬትን በተመለከተ የወጣውን የሊዝ አዋጅ በቀዳሚ ምሳሌነት እናንሳው፤ ፓርቲው በ1987 ዓ.ም ባፀደቀው ህገ-መንግስት የመሬት ፖሊሲውን አንዱ ዕማድ አድርጎ በማካተቱ፣ የመንግስት ጭሰኝነትን (Tenants of the state) በገጠሩ ክፍል ሲያሰፍን፣ የመሬት ከፊል ባለቤትነትን ደግሞ ለከተሞች እንዲፈቅድ አድርጎት ነበር፡፡ እናም የግል ይዞታን መሸጥ (መንግስት ለሚፈልጋቸው ‹‹ልማቶች››ም ሆነ በሊዝ ለመቸብቸብ ዜጎችን የማፈናቀል መብት ከማግኘቱ ውጪ) እስከ 97ቱ ድህረ-ምርጫ ድረስ ተፈቅዶ የዘለቀበት ሂደት፣ በዚህ የሊዝ አዋጅ በመሻሩ የተነሳ፣ ነዋሪው መሬት በመሸጥ ሊያገኝ ይችል የነበረው ገቢ ተጨምቆ ወደ መንግስት ካዝና እንዲሻገር ሆኗል፡፡ የዚህን አዋጅ ‹ፖለቲካዊ ንባብ› ውስጥ የምናገኘው ጭብጥ፣ በከፊልም ቢሆን መሬት ላይ የቆመውን የሀብት መሰረት በመናድ፣ የተቃውሞ ኃይሉ የድጋፍ መዕከል እንደሆነ ያመነውን የማህበረሰብ ክፍል ክፉኛ ማድቀቁን ስንረዳ ነው፡፡ አዋጁን እንለጥጠው ካልን ደግሞ ግንባሩ በገጠሩ ያነበረውን የዜጎች የመንግስት ጭሰኝነት በጠመዝማዛ መንገድ፣ በተለይም በአዲስ አበባ የመፈጸም ዕቅዱ አድርገን ልንወስደው እንችላለን፡፡

የኢህአዴግ ከተማንና ከተሜዎችን የመፍራት አባዜ ከጫካ ትግሉ ጋርም በረዥሙ የሚተሳሰር ነው፡፡ በወቅቱ በጥላቻ ከመተያየት አልፎ ደም የተቃባቸው ኢህአፓን መሰል ኃይሎች መሰረታቸው ከተሞች ላይ እንደነበረ ይታወቃል፤ በአናቱም በትግሉ መጠናቀቂያ ዋዜማ እና ማግስት ሊገዛለት ያልቻለው (ማማለሉ ያልተሳካለት) ልብ በተለይ የአዲስ አበቤዎችን ነበር፤ በ1980ዎቹ መጀመሪያም ፓርቲው አንገት ላይ ታንቆ ሊደፋው የነበረው ዋነኛ ጉዳይ፣ ብሔር ተኮር ስርዓቱ ህገ-መንግስታዊ ድጋፍ ሲያገኝና የብሄር ፖለቲካ ብቸኛው የድጋፍም የተቃውሞም ተዋስኦ እንዲሆን መደረጉ ነበር፡፡ ይህንንም ተከትሎ በኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነት መንፈስ ከተገራው የአዲስ አበቤ ብሔር ዘለል ማንነት ጋር እንዲህ በፊት ለፊት መጋጨቱ፣ ከተማይቱን በወረራ የያዛት እስኪመስል ድረስ በጥላቻ እንዲዘምቱበት አነሳስቷል፡፡

ሁለተኛው ምዕራፍ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትን ተከትሎ የመጣው የአሰብ ወደብን ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እንዲካለል የመፈለግ የከተሜዎቹ ግፊት ነው፡፡ ጦርነቱ ሲያበቃና የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ኋላ እንዲያፈገፍጉ ሲገደዱ የነዋሪው ቁጣ ብርቱ እንደነበር እናስታውሳለን፡፡ ይህ እውነትም ሌላኛው ፓርቲውን ቂም ያስቋጠረ ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡ በድህረ-ምርጫ 97 የፀደቀውና አፋኝነቱ በተግባር የተረጋገጠው የሲቪል ማህበረሰቡን የሚመለከተው አዋጅም ‹የብዙዎች ተቋማት ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የወጣ ነው› በማለት ከየአቅጣጫው ይነሳ የነበረውን የተቃውሞ ውግዘት አጣጥሎ፣ በሥራ ላይ ባዋለበት ዓመት በርካታ ተቋማትን ከማፈራረሱ አኳያ፣ መጀመሪያውንም ለእንዲህ አይነቱ ክፉ እርምጃ ታስቦ የተዘጋጀ ነው ወደሚል ጥርዝ ይገፋል፡፡ በተጨማሪም ያለፉትን ሃያ ሁለት ዓመታት ሙሉ በአይኑ መዓት የሚያያቸው ምሁራን፣ የነፃው ፕሬስ አባላት እናበየዘመኑ ከባድ ተግዳሮት የፈጠሩበት የተቃውሞ ስብስቦች ጠንካራ መሰረት በከተማይቱ ውስጥ መሆኑ ጥላቻ እና የጭካኔ እርምጃዎቹን አብዝቶታል፡፡ 

ሌላው አገዛዙ በከተሜዎች (በሸማቾች) ላይ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ የሚያሳዩት፡- ከምርጫው በኋላ ጤናማ ያልሆነ የዋጋ ንረት በከፋ ደረጃ ማሻቀቡ፣ ፍትሃዊ ያልሆኑ የተለያዩ የግብር ህጎች በእንጀራ እና ሽንኩርት ቸርቻሪዎች ላይ ሳይቀር መተግበራቸው ነው፡፡ በተለይም ካለፉት ስምንት ዓመታት ወዲህ የተከሰተው ከፍተኛ የዋጋ ንረት ዋነኛ አባባሽ ኃይል የምግብ ዋጋ መናር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በዚህ የምግብ ዋጋ መናር በዋነኝነት ቋሚ ደሞዝ ተከፋዩ የከተማ ነዋሪው ተጎጂ መሆኑን የስርዓቱ ባለስልጣናትም ይቀበላሉ፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ከሁለት ወራት በፊት በ‹‹አዲስ ዘመን›› መፅሄት የተጠየቀው የፋይናስና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ ‹‹በ2006 ዓ.ም የሚጨመር ደሞዝ አይኖርም›› ከማለቱ ባለፈ ‹‹ነገ ይችን አገር ወደተሻለ የሚያደርስ በጎ መስዋዕትነት ነው›› ሲል በከተሜው መከራ ላይ አላግጧል፡፡ በርግጥ ይህ ሁሉ መዓት ከመውረዱ በፊት በ1998 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ራሱ አቶ መለስ በደቡብ ክልል ወደምትገኘው ይርጋለም ከተማ ድረስ ሄዶ የሙዝ አምራች አርሶ አደሮችን ሰብስቦ ካነጋገረ በኋላ፣ እንዲህ ለፍተው የሚያገኙትን ምርት ለከተሜው በርካሽ መሸጣቸው አግባብ አለመሆኑን ቀስቅሶ ዋጋውን በአራት እጥፍ እንዲጨምሩ በማድረጉ የተፈጠረው የገበያ እጥረት፣ ምንም እንኳ መልሶ አምራቾቹን ሰለባ ቢያደርግም፣ ኩነቱ የጠቅላይ ሚንስትሩን ቀጣይ ዕቅድ የሚያመላከት ነበር፡፡

በከተሞች ውስጥ እየተደረገ ያለው ‹‹የሰፈራ ፕሮግራም››ም (Urban Resettlement) አንዱ ሊነሳ የሚገባው ነጥብ ነው፡፡ በእርግጥ በዚህ ዕቅድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የተሻለ የመኖሪያ ቤቶች ተጠቃሚ እንደሆኑ ማየት እንችል ይሆናል፡፡ ጥያቄው የሚነሳው ግን፣ የአንድ አካባቢ ነዋሪዎችን ከሌሎች የፈረሱ የከተማዎቹ ክፍሎች ከሚመጡት ጋር በአንድ አዳብሎ በኮንዶሙኒየም ቤቶች አጥሮ የማስቀመጡ አንደምታ ላይ ነው፡፡ የዚህ ዕቅድ ክፉ ገፅ የሚገባን በረዥም የአብሮነት መስተጋብር (ሶስት መንግስታትን መሻገር የቻለ የአንድ አካባቢ ነዋሪነት) የተገነባው የጋርዮሽ ፖለቲካው አረዳድ እና የእርስ በእርስ ፍፁም መተማመን፣ 97ን ጨምሮ በተለያዩ ወቅቶች በተነሱ ተቃውሞዎች ወጥ ምላሽ እንዲሰጡ ማደፋፈሩን (አራት ኪሎን የመሳሰሉ አካባቢዎች) አስታውሰን፣ በመልሶ ማስፈሩ ደግሞ የአንዱን አካባቢ ነዋሪ በታትኖ ወደተለያዩ ሳይቶች መውሰዱን ስንመለከት ነው፤ ይህ መራራ እውነታም የገዥዎቻችን ጥላቻ ስር የሰደደ መሆኑን እና የአምባገነናዊ ስርዓቱን ዕድሜ ለማራዘም ያለመ እንደሆነ ይጠቁመናል፡፡

(ስርዓቱ በከተሜዎች ላይ የሰረፀበትን ጥልቅ የጥላቻ ፅንፍ እንዲህ ከተመለከትን፣ የከተማ አብዮት፣ ማኦኢዝም ከሚያዘው ከገጠር ከሚነሳው ብረታዊ ትግል ጋር ያለውን ልዩነት፣ በአረቡ ፀደይ ተሞክሮ በመንተራስ መፈተሹን፤ እንዲሁም የኢህአዴግ ግድፈቶች (Achilles’ heel) የከተማ አብዮትን ለማስነሳት ያላቸውን አስተዋፅኦ፣ በአደባባይ ሊያሰባስቡ የሚችሉ ጥያቄዎች ምን ቢሆኑ የተሻለ ነባራዊውን እውነት ያንፀባርቃሉ… የሚሉትን ጉዳዮች እና መንገዱን ስለሚመሩ የሚችሉትን መልከአ-ቡድኖች ማንነት ሳምንት እመለስበታለሁ)

Discovery of mass grave rocked TPLF warlords and shocked Ethiopians

The Horn Times Newsletter January 1, 2014


Report compiled by Getahune Bekele-South Africa

*Number of exhumed remains rising…























On Tuesday morning 31 December 2013, mortified Army chief-of-staff Gen Samora and Deputy PM D. Mekonen were spotted leaving the third battalion barracks, TPLF’s secret execution site for many years.Ethiopian regime secret execution site

Despite the regime’s massive cover up campaign, intimidation and open threat of secondary mass grave for the accidentally exhumed corpses in order to avoid investigation or to conceal evidence of the mass murder; Ethiopians winced in terror when the news of the discovery of mass grave in Addis Ababa travelled across the vast nation exposing the savagery; atrocities and duplicity of the current ruling minority junta, – largely of Tigre coterie.

The gruesome discovery was made on Friday 27 December and Saturday 28 December 2013, between Sidist- Kilo and Ferensay- legasion areas at Jan-Meda, inside the barracks of the third army battalion when an excavator working for road expansion project pulled out two corpses wrapped in same color blankets and again another four corpses each wrapped in blankets of identical colors.

Eyewitnesses who got to the area and took the photos before the federal police cordoned off the vicinity told reporters that two of the corpses were still in hand-cuffs and one of the victims had his hands tied behind his back.

“I jumped into the ditch driven by emotion and although the remains were dismembered and co-mingled, I have counted four corpses on Saturday, all shot to the base of the skull. That is, as we all know a Bolshevik style execution practiced by the Stalinist TPLF warlords for years. These remains are undoubtedly victims of 22 years of TPLF repression and terror. The blankets, manufactured by the Debre Birhan blanket factory did not lose their original colors and labels. That indicates the executions were not carried out that long ago. ” A retired medical doctor living in Jan-Meda area of Addis Ababa told reporters, sobbing silently.

When contacted by an undercover reporter on January 1, 2014, the Debre Birhan blanket factory’s sales and customer service manager who gave his first name as Negasi, admitted supplying the correctional service authority of Ethiopia with more than 200,000 blankets similar both in color and design to those found in the mass grave in 2005, 2006 and 2007 financial years.
According to Negasi, the factory did so after legally won tenders.

The sales clerk’s admission is a damning proof beyond any reasonable doubt to journalists that the dead tyrant Meles Zenawi’s homicide squad known as the Agazit executed detainees and committed the war crime during the 2005 nation-wide anti TPLF insurrection.

“Well, grim reminders of the Meles Zenawi era, but how many more mass graves are we going to uncover in the coming years in this city purged by Tigre People Liberation Front with unparalleled audacity? It would be the biggest flagrant miscarriage of justice if the ICC chief prosecutor Madam Fatou B let the panicking TPLF warlords off the hook. It is incumbent up on her to send a team of investigators to Addis Ababa without any delay.

“ This blood curdling discovery has exposed the nation’s festering wounds and further complicated the dreadful ethnic fault line created by the ruling Tigre People Liberation Front/TPLF in May 1991. I personally know that then federal police boss; the snarling evil Workeneh Gebeyhu used the third infantry battalion compound as the headquarters of operations in 2005. He quit the post last year and where is he today? The nation is crying for justice.” A political analyst who is following events for the Horn Times from Addis Ababa explained.

“TPLF warlords thought they found a safe spot to store remains of the barbarically executed non-combatant, peaceful protesters. Mass grave right under the nose of the international community and the people of Ethiopia. This crime scene is full of the telltale fingerprints of the dead former ruler Meles Zenawi….” The political analyst added.

In addition, after getting fresh reports about the exhumation of more skeletons on Monday 30 December 2013, the Horn Times’ attempt to get comment from the junta’s top spin-doctor Shimeles Kemal regrettably proved unsuccessful. Moreover, as it is a norm in a totalitarian regime where the flow of information is government controlled, dreading being indicted for war crimes and extermination, not even ordinary federal police officials were willing to comment on this very sensitive matter with far- reaching consequences.

Currently, the army, using corrugated sheet has fenced off the killing spot. The public no longer observes the exhumation; hence, no one knows the exact numbers of corpuses recovered up to so far. According to a journalist the Horn times spoke to minutes before posting this piece, the Jan-Meda neighborhood remains tense with heavily armed federal police and the military manning several roadblocks in the area.

Shell-shocked residents nonetheless, are unanimous in their call on the ICC, the International Criminal Court to investigate the senseless genocide, a result of two decades of tempestuous minority junta rule in Ethiopia.

“Members of IAGS, International Association of Genocide Scholars, must rush to the crime scene to help with recovery and identification of the remains of possibly the 2005 election massacre victims, a dark chapter in our history.” Another resident of the area told the Horn Times reporter asking not to be named for security reasons.

Democracy has been a conglomeration of violence and brutal repression to the long-suffering people of Ethiopia. According to the opinions of several prominent Ethiopians, for the nation to move forward, western powers must disown the genocidal minority junta now and let justice take its course.
infohorntimes@gmail.com

Wednesday, January 1, 2014

በኢትዮጵያ የተወሰኑ የቻይና ኩባንያዎች ከባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ስራ እየከለከሉን ነው ሲሉ 18 የቻይና ኩባንያዎች አመለከቱ

January 1/2014

ሪፖርተር ባወጣው ዘገባ 18 የቻይና ኩባንያዎች ቤጂንግ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በላኩት ደብዳቤ ቀደም ብለው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቻይና ኩባንያዎች ከአንዳንድ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ስራ እንዳናገኝ እንቅፋት ፈጥረዋል ብለዋል።
ኩባንያዎቹ የተሰማሩባቸው መስኮች የኃይል፣ የመስኖ፣ የመንገድና የንፁህ የመጠጥ ውኃ ግንባታዎች መሆናቸውን የዘገበው ጋዜጣው፣ በእነዚህ የመሠረተ ልማት ዘርፎች የተሰማሩት የቻይና ኩባንያዎች የኢትዮጵያ መንግሥት የተወሰኑ ባለሥልጣናት ቀደም ብለው ለገቡ የቻይና ኩባንያዎች ያለ ውድድር ሥራ እንደሚሰጡዋቸው፣ ደካማ የሥራ አፈጻጸም እያለባቸውም አንዱን ሥራ ሳይጨርሱ ተጨማሪ ሥራዎችን በላይ በላዩ ይሰጧቸዋል የሚል ቅሬታቸውን ዘርዝርው ለመንግስት አቅርበዋል።


ጥቂት ነባር የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መንግሥት ገንዘብ የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን የመያዝ እንዲሁም ከቻይና መንግሥት በሚገኝ ብድር የሚገነቡ ፕሮጀክቶችን የመቆጣጠር አዝማሚያ እያሳዩ መምጣታቸውን ጠቅሰዋል።
ነባር ኩባንያዎች ሥራዎችን የሚያገኙት ከተወሰኑ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር በመመሳጠር ነው የሚሉት አዲሶቹ ኩባንያዎች፣ ለሌሎች ኩባንያዎች ክፍት ሳይደረግ በቀላሉ በቢሊዮን የሚቆጠር ዋጋ ያለው ሥራ እንደሚሰጣቸውም ገልጸዋል።
ከኢትዮጵያ መንግሥት አንዳንድ ባለሥልጣናት በተጨማሪ ቻይና ኤምባሲ ውስጥ ቦታ ያላቸው ግለሰቦችም ለተወሰኑ የቻይና ኩባንያዎች እንደሚያዳሉ ያስረዳሉ ሲል ዘገባው ጠቅሷል፡፡
ሌሎቹን በመግፋት የተወሰኑትን የሚተባበሩ በመሆኑ ብዙኃኑ የቻይና ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ማግኘት እንዳይችሉ መደረጉንም በመግለጽ መንግሥት ከፍተኛ ገንዘብ እንዲያጣ ከመደረጉም በላይ፣ ተስፋ የተጣለባቸው ፕሮጀክቶች ደካማ አፈጻጸም ባላቸው ኩባንያዎች እጅ እየወደቁ እንደሚገኙ ተገልጿል።


አዲሶቹ ኩባንያዎች እንደሚሉት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የገቡት አብዛኞቹ የቻይና ኩባንያዎች አነስተኛና መለስተኛ አቅም ያላቸው ናቸው፡፡ ጉዳዩን የቻይናና የኢትዮጵያ መንግሥታት ተረድተው መፍትሔ እንዲሰጧቸው አዲሶቹ ኩባንያዎች ጠይቀዋል።
ዘገባውን ተከትሎ አስተያየታቸውን የጠየቅናቸው የኢኮኖሚ ባለሙያው ዶ/ር ታደሰ ብሩ እንዳሉት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተገነቡ በጥራት ጉድለት ምክንያት ለሚፈርሱት መንገዶችና ህንጻዎች ከቻይና ኩባንዎች በላይ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ናቸው ብለዋል። ዘገባው በከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናትና በቻይና ኩባንያዎች መካከል ያለውን የሙስና ትስስር ያሳያል በማለት ዶ/ር ታደሰ ገልጸዋል

ኢሳት

ቴዲ አፍሮና የቢራው ፖለቲካ (ክንፉ አሰፋ)

January1/2014

በጋዜጠኛ ስህተት የወጣች አንዲት ጽሁፍ ምክንያት 18 ሺህ ፊርማ በኢንተርኔት መሰበሰቡን ሰማን። ጽሁፉን ያሳተመው መጽሄት ስህተቱን አረመ። ይቅርታም ጠየቀ። ዘመቻው ግን እንደቀጠለ ነው። ቴዲ አፍሮ ይንን እንዳልተናገረ መግለጫ ቢሰጥም ጉዳዩ እልባት ሊያገኝ አልቻለም።   ከቶውንም አንድነታችንን የማይፈልጉ ምእራባውያን ጭምር ይህችን ምክንያት በመያዝ ጉዳዩን ማረገብ ጀመሩ። አንድ የዳች ጋዜጣ አጼ ምኒሊክን ከሂትለር ጋር አመሳስሎ በመጻፍ ጋዜጣውን በዚህ ሳምንት አሰራጭቷል! ያለ አንዳች መረጃ። “ለነጮች እጄን አልሰጥም!” ብሎ አድዋ ላይ ስላዋረዳቸው ምኒሊክን ለማንቋሸሽ ምንም መረጃ አያስፈልጋቸውም።

እልፍነሽ ቀኖ የተባለች የኦሮምኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ በአንድ ወቅት በለቀቀችው ነጠላ ዜማ ምክንያት ማእከላዊ እስር ቤት ታስራ ነበር። ምርመራውን የሚያካሂዱት ሰዎች በመጀመርያ የዘፈኑ ግጥም ወደ አማርኛ እንዲተረጎም አደረጉ። በግጥሙ ምንም አይነት የወንጀል ነገር ሲያጡ ግጥሙ “የህግ ትርጉም ይደረግለት” ሲሉ አዘዙ። የህግ ትርጉሙም ብዙ ስላላስኬዳቸው ለግጥሙ የፖለቲካ ትርጉም እንዲሰጠው አደረጉና ሙዚቀኛዋን “ጥፋተኛ ነሽ” ሲሉ ከሰሱ።  የፖለቲካ ትርጉሙ “ይህን ያለችው እንዲህ ለማለት ነው…”  ከማለት ተነስቶ አቀንቃኝዋ በልቧ አስባው ይሆናል የሚለውንም ያካተተ ነበር። በኢትዮጵያ “የፍትህ ሰዎች” የምናስበውንም ያውቁ ኖሯል።

የበደሌ ቢራ አድማ ጠሪዎች ቴዲ አፍሮ በልቡ ያሰበውን የማንበብ ሃይል እንዳላቸው አናውቅም። እሱ ግን የተባለውን ነገር እንዳልተናገረ ገልጾላቸዋል።

አጼ ምኒሊክ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ያከሄዱት ጦርነት “ቅዱስ ጦርነት ነው” ወይንም “አይደለም” የሚለውን ሙግት ለግዜው ወደጎን እንተወው። ምክንያቱም የዚህ ውይይት ውጤጥ የኦሮሞ ህዝብ አሁን ላለበት ችግር የሚፈይደው አንዳች ነገር የለም። የህሊና አይኖቹን ክፍት አድርጎ ለሚመለከት ሁሉ፤ የዛሬው የኦሮሞ ህዝብ ችግር የበዴሌ ቢራን ከመጠጣት እና ካለመጠጣት የላቀ ነው። ለነገሩ እንጂ 90 በመቶ የሚሆነው የኦሮሞ ህዝብ የሚተዳደረው በግብርና፤ ኑሮውም ከእጅ ወደ አፍ በመሆኑ የበደሌ ቢራን የመጠጣት አቅሙም ሆነ እድሉ የለውም። የዚህ ዘመቻ መሪ ተዋንያን የሆነው ጃዋር መሃመድ እንደነገረን ከሆነ ደግሞ 90 በመቶው የኦሮሞ ህዝብ የሙስሊም እምነት ተከታይ ነው። በሙስሊም አልኮል “ሃራም” ነው።

“እስር ቤቱ ሁሉ ኦሮምኛን ይናገራል!” ያለው ማን ነበር? አዎ! የስርዓቱ ቁንጮ የነበረው ስዬ አብርሃ ነው። ስዬ ስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ከርቸሌ ታስረን የነበርን ጋዜጠኞች የእነ ኦቦ ባይራን ጉዳይ እያነሳን በኦነግ ስም በግፍ ለታሰሩት ስንጮህ የዝሆን ጆሮ ነበር የሰጠን።  አቶ ስዬ አብርሃ አይኑ የተከፈተውና ጆሮው ኦሮምኛን መስማት የጀመረው እጆቹ  የኋሊት ታስረው ቃሊቲ ሲወርድ ነበር። በእርግጥ ማየት ማመን ነው። ያየውንና የሰማውን በመመስከሩ ሊመሰገን ይገባዋል። ልብ በሉ። እስረኛው ሳይሆን እስር ቤቱ ነው ኦሮምኛ እየተናገረ ያለው።

ሂዩማን ራይትስ ዋች ሰሞኑን በለቀቀው ዘገባ፤ በኦሮሞ ወገናችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን አስከፊ ስቃይ በድምጽና በምስል ጭምር አሰራጭቷል። ይህንን ስቃይ ለማስቆም የፌስቡክ ታጋዮቹ ስንት ሺህ ፊርማ እንዳሰባሰቡ አልነገሩንም። የበዴሌ ቢራን የኦሮሞ ህዝብ እንዳይጠጣ በ24 ሰዓታት ውስጥ 18 ሺ ፊርማ ተሰብስቧል ብለውናል።

እርግጥ ነው። “ሰብአዊ መብት ይከበር!” የሚል ዘመቻ ከመጀመር ይልቅ “ቢራ አትጠጡ!” ማለቱ ቀላል ሊሆን ይችላል።  በምእራቡ አለም የሚመረተውን ሄነከን ቢራ ራሳቸው እየተጎነጩ  ይህንን ቀጭን ትእዛዝ ሲያስተላልፉ ግን በዚያ ትልቅ ህዝብ ላይ እያሾፉበት መሆኑን የዘነጉት ይመስላል።

የኦሮሞ ልሂቃን ግራ ያጋቡኛል። ይህን ስል ያለምክንያት አይደለም።  በአባ ጅፋር ግዛት ተወልጄ በኦሮሞ ባህል ታንጼ ነው ያደግኩት።  በደሙ ብቻ ‘ኦሮሞ ነኝ’  እያለ ከሚመጻደቀው ይልቅ የኦሮሞን ህዝብ ማንነት ጠንቅቄ አውቀዋለሁ። ቋንቋው፣ ባህሉና ስነልቦናው ውስጡ ሰርጎ ሳይገባ በደሙ ብቻ ራሱን እየለካ ከህልም እና ከቅዠት አለም ውስጥ ገብቶ የኋሊት ከሚራመደው በተሻለ መንገድ።  …    እናም አንድ የኦሮሞ ህዝብ አውቃለሁ።  በቋንቋው፣ በባህሉና በታሪኩ የሚኮራ ህዝብ።  ታታሪና ሰራተኛ ህዝብ።  ከሌላው ጋር ተዋልዶና ተከባብሮ በፍቅር አብሮ የሚኖር ህዝብ።   የኦሮሞ ህዝብ  ከሌላው ወገኑ ጋር በደም ተሳስሯል። ሃቁ ይህ ነው። ግና ፖለቲከኞቹ ከዚህ ህዝብ በሁለት ሺህ ማይልስ ርቀው በምእራቡ አለም በሚሰሩት ስራ ይህንን ትልቅ ህዝብ እጅግ ትንሽ የሚያደርግ መሆኑን ያስተዋሉት አይመስለኝም።

በቅርቡ ሳውዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የጸመችውን ግፍ ለመቃወም በአለም ዙርያ ያለ ኢትዮጵያዊ በጋራ በሚጮህበት ወቅት አንድ እንግዳ ክስተት በኢንተርኔት ላይ ወጥቶ አየን። “ሳውዲ አረቢያ ኦሮሞን አትግደሉ፣ ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ አይደለም፣ ኦሮሞ ወንጀለኛ አይደለም።” የሚል መፈክር የሚያሰሙ ሰዎች ለብቻቸው ሰልፍ ወጡ። እነዚህ ሰዎች የተሰለፉት “ኦሮሞን አትንኩ። ሌሎቹ ግን ወንጀለኞች ስለሆኑ ይገባቸዋል” የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ነበር።  መቼም ከማንም ሰብአዊ ፍጡር እንዲህ አይነት ኢ-ሰብአዊ አባባል አይጠበቅም። ድርጊታቸው ያሳፍራል። አንገትም ያስደፋል። ይህ አሳፋሪ ድርጊት እኔን እንዲህ ካሸማቀቀኝ፤  አፈር ስንፈጭ ያደግነው በኢትዮጵያዊነታቸው የሚኮሮ የኦሮሞ ልጆች ቢያዩት ምን ሊሉ እንደሚችሉ በምናቤ እስል ነበር።  በዚያ ትልቅ ሕዝብ ስም አደባባይ ወጥተው፣ ተግባራቸው ግን ማስተዋል የተሳነው ትንሽ ህዝብ ነበር።  ያንን ኩሩ ህዝብ እንዲህ … እንዲህ እያሉ ሊያሳንሱት አየን።

እ.ኤ.አ. በ1998 ገደማ አቶ ዳዊት ዮሃንስ በሆላንድ ውስጥ ህዝባዊ ስብሰባ ጠርቶ ነበር። ከስብሰባው መሃል አንድ ሰው ከመቅጽበት ተነስቶ ‘ለኦቦ ነጋሶ ጊዳዳ የሚያደርሱልኝ ጥብቅ መልእክት አለኝ’ አለ። ስብሰባውን የሚመራው አቶ ዳዊት ዮሃንስም ሰውዬው ተነስቶ መልእክቱን እንዲናገር ፈቀደለት። ሰውየው ከመቀመጫው ተበሳ።

“ፊንፊኔ መሃል ላይ ያለው የምኒሊክ ሃውልት በአስቸኳይ እንዲነሳ ይንገሩልን!” አለ ፊቱን ቅጭም አድርጎ በኩራት እየተናገረ።  በስብሰባው የነበርን ሰዎች ግን ለተናጋሪው አፈርን። ያሳፈረን ይህንን መልእክት ማስተላለፉ አልነበረም። ሰውየው ሊናገር ከመቀመጫው ሲነሳ ሌላ አንገብጋቢ ጉዳይ ያነሳል ብለን ገምተን ስለነበር እንጂ።  ‘ሰዎች በዘራቸው (በኦሮሞንታቸው) ብቻ የሚታሰሩት፣ የሚሰቃዩትና የሚገደሉት እስከመቼ ነው?’ የሚል መልእክት ነበር የጠበቅነው። ምክንያቱም ወቅቱ በቁጥር 20 ሺህ የሚደርስ የኦሮሞ ተወላጆች የጦር ካምፕ እስረኛ እንዲሆን ካደረጉ በኋላ፤ የኦነግ መሪዎች በባሌ ሳይሆን በቦሌ እየተሸኙ የወጡበት ሰሞን ነበር።  የኦነግ መሪዎች ከህወሃት ጋር በጋራ መስርተውት የነበረውን ቻርተር ረግጠው በመውጣታቸው ምክንያት ኦሮሞው ወገናችን የህይወት መስዋእትነት ጭምር ይከፍል የነበረበት ወቅት።

ዳዊት ዮሃንስም አግባብ ያለው ጥያቄ መሆኑን ከተናገረ በኋላ መልእክቱን ለርእሰ-ብሄሩ እንደሚያደርስ ቃል ገብቶ ሄደ።  መልእክቱን ለዶ/ር ነጋሶ ያድርስ፤ አያድርስ የታወቀ ነገር የለም። ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በዚያን ወቅት የሃገሪቱ ርዕሰ-ብሄር ነበሩ። እንኳንና የተባለውን መልእክት ሊያስፈጽሙ፤  እሳቸውም የዛ ስርዓት ሰለባ ሆነው አየን።

የአጼውን ሃውልት ግን ዛሬ በባቡር ሃዲድ ስራ ምክንያት ከነበረበት ስፍራ እንዲነሳ አድርገውታል።
የተዛባ ታሪክ ይዘን፣  ጥላቻን ብቻ በምናባችን አርግዘን የት እንደምንደርስ አላውቅም። አሁንም በመፍትሄው ላይ ሳይሆን በችግሮቹ ላይ ተወጥረናል።  የምኒሊክ ሃውልት ተነሳም አልተነሳ እንደ እንስሳ ለሚታደነው የኦሮሞ ህዝብ ምን ፋይዳ አለው?  “በእስር ያሉ ወገኖቼ ይፈቱ!” ለማለት እንኳን ሞራል ሳይኖረን አእምሯችንን በአፈ-ታሪክ ብቻ ወጥረን አንዲት ኢንች እንኳን ወደፊት መራመድ እንዳልቻልን ለምን አናስተውልም?
አጼ ምኒሊክ ኢትዮጵያን ግዛት አንድነት ለማስፋፋት ባደረጉት ጦርነት ወንጀል ፈጽመው ከሆነ አጽማቸው ወጥቶ ለፍርድ ይቅረብ ነው የምትሉት?  ወይንስ ይህ ትውልድ የዚያ ወንጀል ውርስ አለበት? ውርስ ካለበትስ ማን ነው ወራሹ? አማራው? ጉራጌው ወይንስ ኦሮሞው?  እንደ ዘረኞች፣ ደም መለካት ካለብን እኚህ መሪ ከአማራም፣ ከኦሮሞም፣ ከጉራጌም ይወለዳሉ። ጠለቅ ብለን ከሄድን ደግሞ ራስ ጎበና ዳጬን በዚያ ስእል ውስጥ እናያለን። ምእራብ እና ደቡብ ኢትዮጵያን በሃይል የያዙና ያስገበሩ የአጼው የጦር መሪ። ራስ ጎበናን ልንጠላቸው እንችል ይሆናል። ኦሮሞነታቸውን ግን ልንክደው አንችልም።   የወንጀል ውርስ በተዋረድ (guilt by association)  ውስጥ ከገባን የኦሮሞን ህዝብም በአእምሯችን ለፈጠርነው ወንጀል ወራሽ ልናደርገው ነው።

የቴዲ አፍሮ “ጥቁር ሰው” አልበም  የሚያሞግሰው ኢትዮጵያን ከወራሪ ጠላት የታደጉትን ጀግኖች ነው። እነ ፊታውራሪ ሃብተጎርጊስ ዲነግዴን እና እነ ባልቻ አባ ነፍሶ። ቴዲ አፍሮ ለነዚህ ጀግኖች ባያቀነቅንላቸውም ከታሪክ መዝገብ ላይ ልንፍቃቸው አንችልም። የታሪክ ተመራማሪዎች ስለነዚህ ጀግኖች የጻፉት አፈ-ታሪክ ወይንም ድርሰት አይደለም። በጀግኖቹ የምንኮራው በዘራቸው ሳይሆን የሰሩት ገድል ነው። በ’ጥቁሩ ሰው’ የተመራው ይህ የጸረ-ቅኝ ግዛት ገድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው አፍሪካና ለጥቁር ህዝቦች ነጻነት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። ይህ ሊዋጥላችሁ የሚገባ እውነታ ነው። በዚያ ገድል የሚያፍሩ ካሉ የራሳቸው ጉዳይ። መላው የአፍሪካ ህዝብ ግን ይኮራበታል። የአለም ጥቁር ህዝብም ሲያስታውሳቸው ይኖራል።
ዘር እየቆጠርን ከሄድን ብዙ የሚጎረብጡ ነገሮችን ልናነሳ ነው። በግዛት ማስፋፋቱ ሂደት ግን አንድ ሃቅ አለ።  ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ህልቀ መሳፍርት ኢትዮጵያዊ አልቋል። ይህ ደግሞ የድንበር መስፋፋት፤ እድገት እና ስልጣኔ ይዞት የሚመጣው ችግር እንጂ አንድን ህዝብ ለመጨረስ ጥናት ተደርጎ የተሰራ እንዳልሆነ ታሪኩን ከስር መሰረቱ ማየቱ ይበጃል። ችግሩ በእኛ ላይ ብቻ ሳይሆን በአያሌ ሃገሮች እንደተከሰተ የታሪክ መዛግብት ይነግሩናል። በ17ኛው ክፍለዘመን የተከሰተው የኢንዱስትሪ አብዮት ሳብያ እንኳን ከሁለተኛው የአለም ጦርነት የማይተናነስ እልቂት ነበር።

አጼ ምኒሊክን ከጀርመኑ ኦቶ ቮን ቢስማርክ ጋር የሚያመሳስሉ ምሁራንም አሉ። እርግጥ ነው ጀርመን  አሁን የያዘችውን ግዛት ቅርጽ እንድትይዝ ያደረገው ፕሩሲያዊው ቢስማርክ ነው። ቢስማርክ የጀርመንን አንድ ታላቅ ኤምፓየር ለመፍጠር አንባገነን፣ ሃይለኛና ጦረኛ መሆን ነበረበት። ታዲያ ይህችን ሃያል ሃገር በመመስረቱ ጀርመኖች አልጠሉትም። ይልቁንም የጀግንነት ስያሜ ለግሰውታል። አያሌ የመታሰቢያ ሃውልቶችንም አቁመውለታል።

ቢስማርክ የህግ ምሁር ነበር። አጼ ምኒሊክ ግን መደበኛም ሆነ ዘመናዊ ትምህርት የተማሩ ሰው አልነበሩም። ከታሪክ እንደምንረዳው በአጼ ልብነድንግል ዘመነ መንግስት፤ የግራኝ አህመድ ወረራን ተከትሎ የነበረውን መከፋፈልና መተላለቅ ለማስቆም መሪዎች ተነሱ።  ሃገርን አንድ የማድረጉን ትግል አጼ ዮሃንስ ጀመሩት፣ አጼ ቴዎድሮስ ቀጠሉበት ከዚያም እምዬ ምኒሊክ ተረከቡት።


አጼ ምኒሊክ ለአመታት በኦነግ ሰዎች ተወግዘዋል። ውግዘቱ አሁንም እታገልለታለው የሚሉትን ህዝብ ችግር ሲፈታው አለየንም። በ1991 ከህወሃት ጋር ጋብቻ ፈጽመው የምኒሊክ ቤተ-መንግስት ሲገቡ ይናገሩት የነበረውን ሁሉ ረሱት። ከቶውንም ያነሱት የነበረው የኦሮሞ ህዝብ የመብት ጉዳይ ሳይሆን የስልጣን ጥያቄ ለመሆኑን አረጋገጡልን።  የሽግግር መንግስቱን ቻርተር ሲያጸድቁ “ኢትዮጵያዊ አይደለንም” የሚለውንም ሳያውቁ ዘንግተውት ነበር። ከገዢው ፓርቲ ጋር የጀመሩት ግዚያዊ ጋብቻ በፍቺ ሲጠናቅቅ የምኒሊክ ጠላትነት መፈክራቸውን እንደገና አነሱት።
የዘር ፖለቲካው ስካር ሞቅ ብሎ በነበረበት በዚያን ወቅት እንደቀልድ ይነገር የነበረ አንድ ቁም ነገር አለ። አንድ የምግብ ቤት በር ላይ በላቲን ፊደል “አማራ መግባት ክልክል ነው!” የሚል ጽሁፍ ሰፍሯል። የጽሁፉ ትርጉም ያልገባው አንድ የአማራ ተወላጅ ጎራ ብሎ ምግብ አዘዘ። አስተናጋጆቹ የሰውየው ድፍረት አስደነገጣቸው። ባለስልጣን ስለመሰላቸው አስተናገደዱት። ዳግም እንዳይመለስም እጥፍ ዋጋ አስከፈሉት። ሰውየው በድጋሚ ሲመጣ ሶስት እጥፍ አስከፈሉት። በሌላ ግዜ ከአምስት ጓደኞቹ ጋር መጥቶ ምግብ አዘዘ። ከተስተናገደ በኋላም አራት እጥፍ ቢል አቀረቡለት።  በዚህ ግዜ ቲፕም ጨምሮ ሰጣቸው።  የሆቴሉ ባለቤት በነጋታው “አማራ መግባት ክልክል ነው!” የሚለውን ጽሁፍ አንስቶ “ኦሮሞ መግባት ክልክል ነው!” በሚል ቀየረው።

በአሁኑ ዘመን ከበድ አለ እንጂ፣ ሰዎችን በጎሳ አደራጅቶ ከማሳደም የቀለለ ትግል የለም። ደም ከውሃ ይወፍራል እንዲሉ፤ ሰዎች በጋራ የሚጋሩትን ነገር እያነሱ ስነልቦናዊ ዘመቻ ማድረግ ስኬት ሊኖረው ይችላል። ዘለቄታ ግን አይኖረውም። የዘር ፖለቲካ ልክ እንደ ስካር ነው። ይሞቃል ከዚያም ይበርዳል። በርግጥ በሞቅታ ግዜ የሚፈጠረው አደጋ ቀላል ላይሆን ይችላል። እ.ኤ.አ. በ1993 በምስራቅና በምእራብ ኢትዮጵያ የተፈጸመው አሰቃቂ ወንጀል ለዚህ ዋቢ ነው። የኦነግ ልሂቃን የ19ኛውን ክፍለ ዘመን ጉዳይ እየደጋገሙ ያነሱልናል።  በ21ኛው ክፍለ ዘመን በራሳቸው እጅ የተፈጸመው ግድያ ግን በብሄራዊ ቴሌቭዥን ጭምር እንድናየው ተደርጓል።  ነብሰ-ጡር ሴቶች በጩቤ ሆዳቸውን እየተሰነጠቁ ሲገደሉ አየን። ነብስ ያላወቁ ሕጻናትና የ90 አመት አዛውንት ጭምር ከተራራ ላይ እየተወረወሩ ሲጣሉም የአይን ምስክሮች ነን። እነዚህ ሰዎች የምናስታውሰው ይህን በመሰለ ወንጀል ብቻ አይደለም። ድርጊቱ የቂምና የቁርሾ አሻራ ጥሎ አልፏል።

ይህ ሁሉ በደል በዘመናችን ተፈጸመ። በዳዮቹ ግን አሁንም በቀልን አርግዘው ይጓዛሉ።

የበደሌ ቢራን አለመጠጣት የኦሮሞን ችግር የሚፈታ ከሆነ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ቢራውን መጠጣት ያቁም። የአኖሌን ሃውልት መሰራት ለኦሮሞ ህዝብ ፍትህ የሚያመጣ ከሆነ ደግሞ፤ ሃውልቱ በየከተማው ይገንባ። ግና ይህ ሃውልት ለመጭው ትውልድ ጥሎት የሚያልፈው ቂምና በቀልን እንጂ፤  ለሚታገሉለት ህዝብ የፍትህ ጥያቄ ዋስትናው ምን እንደሆነ ልንረዳው አልቻልንም።  አሁን ያለው ትውልድ ያልፋል። ከዚህ ትውልድ በኋላ ለሚወለዱት ልጆች ጥለንላቸው የምናልፈው ቅርስ ጥላቻ፣ ቂም እና በቀል ብቻ ይሆናል።

ከዘመናችን ታላቅ ሰው ከኔልሰን ማንዴላ አንድ ነገር እንማር። ማንዴላ የደቡብ አፍሪካን ብቻ ሳይሆን የአለምን ፖለቲካ የለወጠ የፖለቲካ ነብይ ነው። ይህንን ሲያደርግ የፖለቲካ ፎርሙላ አልነበረውም። ክፉን ነገር በበጎ ለማሸነፍ ወሰነ። ጥላቻን በፍቅር ለወጠ። ልክ እንደ ክርስቶስ፣ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ብሎ በፍቅር አሸነፋቸው። ታሪክ ሰርቶ አለፈ። ስሙም ከመቃብር በላይ ለዘልአለሙ ይኖራል።

ዶ/ር ነጋሶ ከፓርቲ ፖለቲካ ለመሰናበት ከጫፍ ደርሰዋል

Janaury1/2014


በታሪክ ትምህርት ከጀርመን ሀገር በፒኤችዲ በላቀ እውቀት የተመረቁት፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ከተማሪዎች ንቅናቄ፣ በኦነግ፣ በኦህዴድ/ኢህአዴግ እና በአንድነት/መድረክ የፖለቲካ ቆይታ ያደረጉት፣ በግል ስብዕናቸው በገዢውም በተቃዋሚውም አባላት ከበሬታንና ተወዳጅነትን ያተረፉት የ70 ዓመት ዕድሜ ባለፀጋ የሆኑት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከፓርቲ ፖለቲካ ለመሰናበት ከጫፍ ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ።
ዶ/ር ነጋሶ ለሁለት ዓመት በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን (አንድነት) የምርጫ ጊዜያቸውን በማጠናቀቅም ኃላፊነታቸውን ለተተኪያቸው ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው አስረክበዋል። የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝደንት ከገዢው ፓርቲ ጋር በሃሳብ ከተለዩ በኋላ ለእምነታቸው በርካታ ውጣ ውረድን ማሳለፋቸው ይታወቃል። ባለፈው ቅዳሜና እሁድ ፓርቲው አዲስ አበባ ውስጥ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤው መጠናቀቂያ ላይ በፓርቲው ለነበራቸው ገምቢና አዎንታዊ ቆይታ ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
ዶ/ር ነጋሶ ፓርቲው በቅርቡ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚለው ሕዝባዊ ንቅናቄ በቀዳሚነት በመሳተፍ አባላት ሲታሰሩ በመታሰር ጭምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማድረግ ተወዳጅነትና ተደናቂነትን አትርፈዋል።
ይሁን እንጂ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ወደተቃዋሚው ጎራ በመቀላቀል ሲጀመር የስድስት ፓርቲዎች አሁን ደግሞ የአራት ፓርቲዎች ግንባር የሆነውን “መድረክ” እውን እንዲሆን በርካታ ጥረት አድርገዋል። ነገር ግን ጥረታቸው በብዙሃኑ የአንድነት አባላትን ያሳመነ ባለመሆኑና ውትወታቸው ሚዛን ባለመድፋቱ በ1993 ዓ.ም ከገዢው ፓርቲ ጋር ገጥሟቸው ከነበረው የኀሳብ ልዩነት ጋር ሊቀራረብ የሚችል የኀሳብ ልዩነት አጋጥሟቸዋል።
የኀሳብ ልዩነቱ በዶ/ር ነጋሶ በኩል መድረክ “በግንባር” አደረጃጀት መቀጠል ሲፈልጉ ብዙሃኑ የአንድነት አባላት ግን በሦስት ወር ውስጥ አንድነት ከመድረክ ጋር ያለውን ግንኙነት ላይ እልባት እንዲሰጥ፣ ውህደትም ቅድሚያ እንዲሰጠው የሚል ውሳኔ በፓርቲው የጠቅላላ ጉባኤ በኩል አሳልፏል።
“በብዙሃን የኀሳብ የበላይነት እገዛለሁ” የሚሉት ዶ/ር ነጋሶ፤ መድረክ በግንባርነት መቀጠሉ ይጠቅማል በሚል የፀና አቋም መያዛቸውን ለሰንደቅ ጋዜጣ አረጋግጠዋል። የእሳቸው ኀሳብ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሚያጣ መሆኑንም ሲያረጋግጡ ከአንድነት ፓርቲ እንደሚለቁና ከእንግዲህ እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ በፓርቲ ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ እንደማያደርጉ፣ በግል ተሳትፎአቸው ድምፃቸውን በልዩ ልዩ መንገድ እያሰሙ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

“በግንባር” እና በ“ውህደት” መካከል የሚዋልለው የኢንጂነሩ ሹመትና የዶ/ሩ ሽኝት

January1/2013


አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከተመሠረተ በኋላ ሦስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ሰሞኑን አካሂዷል። ፓርቲው “የቅንጅት ወራሽ” በሚል መርህ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳን ሊቀመንበር በማድረግ ጉዞውን ከጀመረ በኋላ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፏል። በ2002ቱ ሀገር አቀፍ ምርጫ ዋዜማ የቀድሞው የሕወሓት ከፍተኛ አመራርና የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ስዬ አብርሃንና የቀድሞ የኢፌድሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን በአመራር አሳትፎ ጉዞውን ቀጥሏል።

ፓርቲው ሁለቱን ታዋቂ ግለሰቦች በአመራር ደረጃ ካሳተፈ በኋላ ፓርቲው ለሁለት የመከፈል አደጋውን በመቀነስ ህልውናውን አስጠብቆ ዘልቋል። ምንም እንኳ በወቅቱ “መርህ ይከበር” ብለው በፓርቲው መጠነኛ የፕሮግራም ለውጥ ላይ ጥያቄ ያነሱ አካላት በዚህ ወቅት “ሰማያዊ” በሚል መጠሪያ ፓርቲ መመስረታቸውም የሚታይ ሐቅ ነው። በዛን ጊዜ የተቀሰቀሰው የፖለቲካ አለመግባባት አሁን በተጨባጭ ሁለት ፓርቲ እንዲኖር ማድረጉም መሬት የረገጠ እውነታ ነው።
በአንድነት የውጣ ውረድ የፖለቲካ ሂደት ውስጥ በምርጫ 2002 ዓ.ም ዋዜማ “መድረክ” መፈጠሩም ይታወቃል። አንዳንድ የአንድነት ፓርቲ አባላት መድረክ የአንድነት የጦስ ዶሮ አድርገው ያዩታል። ያም ሆኖ ኢህአዴግ 99.6 በመቶ ውጤት እንዳገኘ በገለፀበት “ምርጫ 2002” መድረክ የተሻለ ተፎካካሪ እንደነበር አይዘነጋም።
ብዙዎች “ባልተጠናቀቀ ፕሮግራም” ወደ ምርጫ ገብቷል፤ የብሔርና ሕብረብሔር በአንድ አጣምሯል፣ በመሬት ፖሊሲ፣ በፌዴራሊዝምና በሃገሪቱ ሌሎች ወሳኝ ጥያቄዎች ላይ የጋራ መግባባት አልደረሰም በማለት የሰላ ትችት ቢያቀርቡበትም ባለፉት ሁለት ዓመታት መድረክ ግን ከተራ ቅንጅት ወደ ግንባር ለማደግ ችሏል። ይሁን እንጂ መድረክ ወደ “ግንባር” ማደጉ ያላጠገባቸው በርካታዎች ናቸው።
ከሰሞኑ በአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ከተነሱ አጀንዳዎች መካከልም የመድረክ በተለይም የፓርቲ የውህደት ጉዳይ አንዱ ነው። ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ዋዜማ ስለ ውህደት የማሰባቸው ጉዳይ የተለመደ ነው። በዚህ አሁን ባለንበት ጊዜም የ2007ቱ የምርጫ ዋዜማ የውህደት ድምጾች ከየአቅጣጫው እየተደመጡ ነው።
በአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የፓርቲው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው የበርካታ ፓርቲዎችን ስም በመጥራት “የእንዋሃድ” ጥሪ አሰምተዋል። ከሁሉም በላይ ቀደም ሲል አቶ ልደቱ አያሌው ሲመሩት የነበሩትን ኢዴፓ እና ውህደት አስፈላጊ ነው ብሎ ለማያምነው ሰማያዊ ፓርቲ ጭምር ጥሪ አድርገዋል። ይህ ጥሪ ለአንዳንዶች “እንዳያማህ ጥራው እንዳይበላህ ግፋው” ቢመስልም ኢንጂነር ግዛቸው ግን የውህደት ሃዋርያ ሆነው ቀርበዋል።
ውህደትን በተመለከተ የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በሦስት ወራት ውስጥ እልባት እንዲሰጠው መወሰኑም ታውቋል። አሁን በውህደት ጠረጴዛ ላይ የተቀመጡ በርካታ የውህደት ሰነዶች አሉ። የውህደት ሰነዶቹ በአፋጣኝ ተግባራዊ እንዲሆኑ “አዲሱ” የአንድነት ሊቀመንበር እጅ ላይ ወድቀዋል።
አንድነት ፓርቲ ባዘጋጀው የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ መሠረት ፓርቲዎችን ማሰባሰብ አንዱ አላማው ነው። “ማሰባሰብ” የሚለው ቃል በግልፅ “ማዋሃድ” የሚለውን ባይተካም ፓርቲው የተበታተኑ ፓርቲዎችን በአንድ ላይ እንዲሆኑ ማድረጉ ጤናማ አካሄድ እንደሆነ የሚስማሙ ብዙዎች ናቸው። በዚህም መነሻ ባለፉት ወራት ውስጥ በርካታ የውህደት ጥያቄዎች ወደ አንድነት ፓርቲ እያመሩ ነው።
ከሁለት ዓመት በፊት በዲአፍሪክ ሆቴል በተካሄደው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ “የፖለቲካ ኃይሌ ተሟጦ አልቋል” በማለት ከፖለቲካው መድረክ የተገለሉት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ውስብስቡን የውህደት ማመልከቻ የመመርመር ታሪካዊ ኃላፊነት የወደቀባቸው ይመስላል። ኢንጂነር ግዛቸው የወጣቶች ሚና መጉላት እንዳለበት ደጋግመው ቢገልፁም፤ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ፓርቲው በእጃቸው ላይ እንዲወድቅ ሆኗል። አንድነት ፓርቲን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች የኢንጂነር ግዛቸውን በድጋሚ ወደ አመራር መምጣት ከተገነዘቡ በኋላ “ፓርቲው ወደ ፊት ተራመደ ወይስ ወደኋላ” ብለው እንዲጠይቁም አድርጓቸዋል። አንዳንዶች ደግሞ የኢንጂነሩን መመረጥ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ካምፕ የአመራር ንጥፈት ማሳያ አድርገውታል።
በሌላ በኩል የኢህአዴግ ፋሽን የሆነው “መተካካት” በተቃዋሚው ጎራ ውጤታማ እንዳልሆነም የሚገልፁ አልጠፉም። በተመሳሳይ መንገድ የእነ አቶ አዲሱ ለገሰን ወደ አመራር መመለስ በማየት በገዢውም ሆነ በተቃዋሚ ጎራ “መተካካት” ሳይሆን በስልጣን “መመላለስ” አድርገው የተገነዘቡም ይመስላል።
የሀገሪቱን ፖለቲካ በትውልድ መነፅር የሚለኩ ወገኖች ዛሬም ቢሆን “የ60ዎቹ ትውልድ” የሀገሪቱን የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተቆጣጥሯል የሚል ቅሬታ እየተደመጠ ነው። አንድነትም ቢሆን የወጣት አመራር በማጣቱና በመቸገሩ በኢንጂነር ግዛቸው ስር መጠለሉን እንደመረጠና አማራጭም እንዳጣ በመግለፅ በማሳያነት የሚያቀርቡ አሉ።
በሌላ በኩል አንድነት ፓርቲ ኢንጂነር ግዛቸውን በሊቀመንበርነት ቢመረጡም ፓርቲውን በበላይነት በሚመራው የስራ አስፈፃሚ አባላት (ካቢኔ) መካከል 60 በመቶ ወጣቶች እንዲሆኑ መወሰኑ አሁንም የአንድነት ፓርቲ በወጣቶች የሚመራ ፓርቲ ነው ወደሚል ስሜት የሚያደሉ ወገኖች እንዲበራከቱ መንገድ ጠርጓል።
በአጠቃላይ ፓርቲው በወጣቶች ከመመራቱም ጋር በተያያዘ “ቅንጅትና ግንባር” እያሉ ትግሉን ከማስታመም ባለፈ የተበታተነውን የፓርቲዎች ኃይል በውህደት አማካኝነት ለማሰባሰብ ከፍተኛ ወኔ የተንፀባረቀበት ጉባዔ ነበር።
ይሁን እንጂ የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ግን የውህደት ሂደት ላይ ጥያቄ አንስተዋል። ከጉባኤው በኋላ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደተናገሩት በአንድነት ፓርቲ የሁለት ዓመት የሊቀመንበርነት ዘመናቸው አልሰራሁም ብለው ከሚቆጫቸው ጉዳዮች መካከል የመድረክና የአንድነት ግንኙነት አለመጠናከር አንዱ ነው። ዶ/ር ነጋሶ በፓርቲው የአመራር ዘመናቸው መድረክ ወደ “ግንባር” ማደጉ ተስፋ የሰጣቸውና ተገቢም የፖለቲካ እርምጃ እንደነበር ይገልፃሉ። ውህደቱ ግን ገና 
በአንፃሩ የሰሞኑ የአንድነት ጉባኤን ተከትሎ ለፓርቲዎቹ የተደረገው የውህደት ጥሪ በመርህ ደረጃ ተቀባይነት ያለው ጥሪ ቢሆንም ከተቀመጠው ጊዜና ካሉት አስቸጋሪ ሁኔታዎች አንፃር ተግባራዊነቱ ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ነው ዶ/ር ነጋሶ የገለፁት። አዲሱ የአንድነት ሊቀመንበር ኢዴፓን ጨምሮ ለሁሉም ፓርቲዎች የውህደት ጥሪ ያስተላለፉበት መነሻ “ጊዜ አጠፋን” ከሚል ስሜት እንደሆነ የሚጠቅሱት ዶ/ር ነጋሶ “የእኔ አቋም ከአራቱ የፓርቲዎች የትብብር አይነቶች “ውህደት” የሚለው ላይ ጥያቄ አለኝ። በተለይ የመድረክና የአንድነት ግንኙነት ላይ ለጊዜው የሚያዋጣው መድረክ “ግንባር” ነው ብለዋል።
“ከፓርቲዎች ጋር የተለያዩ ሕብረቶች መፍጠር ይቻላል። በተለይም በምርጫ በሰብአዊ መብት፣ በሕግ የበላይነት ትብብር መፍጠር ያስኬዳል። ከዚህ አለፍ ሲሉ ጠንካራ መዋቅራዊ ግንኙነት በማድረግ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን እንደ ኢህአዴግ ግንባር ፈጥረው መሄድ ይችላሉ። ይህንን ደረጃ ካለፉ ደግሞ ወደ ውህደት ይሄዳሉ” ብለዋል።
ከዚህ አንፃር ባለፉት ሁለት ዓመታት የእሳቸው አመራር በሁለት መንገድ ውጤታማ እንዳልነበረ አምነዋል። አንደኛውና ዋነኛው የመድረክ/አንድነት ግንኙነት ላይ ከልብ ሆኖ ያለመስራት ችግር ነው። በዚህ ረገድ አንድነት ጨምሮ የመድረክ አባል ፓርቲዎች በተናጠል ከራሳቸው ፕሮግራም ባለፈ የጋራ ፕሮግራም ለሆነው የመድረክ ፕሮግራም በኩል ጠንካራ ስራ አልተሰራም ብለዋል። ከዚህ አኳያ ብዙ ጭቅጭቆች ስለነበሩ ውጤታማ እንዳልሆኑም ገልፀዋል።
በዶ/ር ነጋሶ እምነት የመድረክና የአንድነት ፕሮግራምን በማስፈፀም በኩል መንታ ኀሳብ መኖሩ ውጤማ እንዳይኮን መሰናክል መፍጠሩን ነው የገለፁት፤ ለዚህ ደግሞ ኃላፊነቱን የሚወስደው “የእገሌ ድርጅት ነው” ማለት አስቸጋሪ እንደሆነ ነው የሚገልፁት። “በአንዳንድ ድርጅቶች አንድነትን ጨምሮ የጋራውን ፕሮግራም በአግባቡ አልተሰራም። ሌሎቹም በዚያው መጠን የመድረክ ፕሮግራም በቆራጥነት አላስፈፀሙም” ብለዋል።
በሁለተኛ ደረጃ ውጤታማ ያልሆኑበት የስራ አፈፃፀም ፓርቲው ባዘጋጀው የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ሰነድ መሠረት በህዝብ ግንኙነት በኩል በርካታ ስራዎች ቢሰሩም የምርጫ ማኒፌስቶ በማዘጋጀት በኩል ብዙ ርቀት አለመኬዱን እንዲሁም በስትራቴጂክ እቅዱ መሠረት ሻዶ ካቢኔ እና ፓርላማ እናቋቁማለን የሚል እቅድ ብንይዝም አልተሳካልንም ብለዋል። በውጤት ረገድ ፓርቲው አዲስ እይታ እንዲኖረው በማድረግና “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የሚለው የሕዝብ ንቅናቄ አርኪ ተግባር እንደሆነም ሳይገልፁ አላለፉም።
የአንድነትና መድረክ ግንኙነት በተመለከተም በስልጣን ዘመናቸው ግንኙነቱ በሙሉ ልብ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ያልተቆጠበ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ገልፀዋል። በፓርቲውም ውስጥ ከመድረክ ጋር በገባነው የቃል ኪዳን ውል መሠረት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ሲወተውቱ ቢቆዩም በኢንጂነር ግዛቸው በኩል ጉልህ ሆኖ የወጣው “ግንባር አንፈልግም” የሚለው ጉዳይ የእሳቸው ውትወታ የተሳካ እንዳልነበር፣ የጠቆመ አጋጣሚ ነው ብለዋል።
“እኔ ወደ አንድነት የመጣሁት በመድረክ ምክንያት ነው። አንድነት መድረክ ውስጥ ስገባ ፕሮግራሙ ከተስማማኝ በአንድነት በኩል መድረክን ለማገልገል ነው። አሁን ግን ኢንጂነር ግዛቸው ውህደት ብለዋል። በእኔ እምነት ቃል በገባነው መሠረት መድረክ በግንባር ካልቀጠለ እኔ ከአንድነት ጋር የለሁም” የሚሉት ዶ/ር ነጋሶ የ“ግንባር” አደረጃጀት በአሁኑ ወቅት ለሁሉም ፓርቲዎች ጠቃሚ ነው። ውህደት በችኮላ ሳይሆን በሂደት የሚመጣ ነው ብለዋል።
ሌላው ዶ/ር ነጋሶ የአንድነት ፓርቲ ሆነው በተመረጡት ወቅት “አንድነት ፓርቲን ወደ ኦሮምያ ክልል ያሰርፃሉ” የሚለው አስተያየት በመጀመሪያ በአስተያየቱ እንደማይስማሙ የገለፁት ዶ/ር ነጋሶ፤ እሳቸው ሲሰሩ የነበሩት በሁሉም ክልሎች እንደነበር አስረድተዋል። በእሳቸው የአመራር ቆይታም እሳቸው የኦሮሞ ተወላጅ ስለሆኑ ወደ አንድነት አመራር የመጡት የኦሮሞን ሕዝብ ለመሳብ ነው የሚለው አመለካከት የተሳሳተ ነው ብለዋል።
በእሳቸው የአመራር ዘመን ከገዢው ፓርቲ ጋር ድርድር አለመደረጉን በተመለከተም የሚያስቆጫቸው ጉዳይ እንዳለ ዶ/ር ነጋሶ ተጠይቀው፤ የኢህአዴግ አቋም አስቸጋሪ መሆኑን፣ የፖለቲካ ተፈጥሮአዊ ባህሪ መወያየት ቢሆንም የውይይት በሩ መዘጋቱ እንደሚያሳዝናቸው ገልፀዋል። “እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ፓርቲ መነጋገር መርሃችን ነበር። ጭብጨባ የሚያምረው በሁለት እጅ ነው። በአንድ እጅ ማጨብጨብ አይቻልም። አሁንም ሆነ ወደፊት በዚህች ሀገር ዴሞክራሲያዊ ሂደት እንዲጎለብት የውይይት መድረክ ክፍት መሆን አለበት። ይሁን እንጂ ኢህአዴግ ለድርድር ዝግጁ አለመሆኑ ያሳዝናል። ይህንንም በተመለከተ አንድ ሰው ሊቀመንበር ስለሆነ ብቻ አያሳካውም። ጥረቱ የጋራ ስለሆነ ኢህአዴግ ድርድርን ባለመቀበሉ ባዝንም በግሌ ግን የሚቆጨኝ የለም” ብለዋል።
በመጨረሻም በመድረክና በአንድነት መካከል ያለው ግንኙነት “ግንባር” የማይሆን ከሆነና እሳቸው ከአንድነት ጋር የሚለያዩ ከሆነ ያሳለፉት ጊዜ እንደባከነ ይቆጠር ይሆን ወይ? ለሚለው ጥያቄም “የሚቆጨኝ ነገር የለም። ጉዳዩ የትግል ጉዳይ ነው። ህሊናን የማይነካ፣ በመርህ ጉዳይና በእምነት ጉዳይ ልዩነት እስከሌለ አብሮ መስራት ይቻላል። የእምነትና ህሊናን የሚነኩ ጉዳዮች ከተቻለ ለማሳመን ካልሆነ በሰላም መለያየት ነው። ይህንን በምልበት ጊዜ ለምን “ውህደት” የሚል አቋም ያዙ ብዬ ሰዎችን መውቀስ አልፈልግም። በተፈጥሮዬም የሰዎችን አቋም አከብራለሁ። የራሴን አመለካከት ለማስረፅ የምሄደውን ርቀት ያህል የሌሎችን አቋም አልጋፋም” ሲሉ ዶ/ር ነጋሶ መልሰዋል።
እንደሚጠበቀው ከአንድነት ፓርቲ ጋር የኀሳብ ልዩነት ከተፈጠረ ቀሪው ህይወታቸው ምን ሊሆን እንደሚችል የተጠየቁት ዶ/ር ነጋሶ በማናቸውም ጉዳይ ላይ እስከህይወት ፍፃሜአቸው ኀሳባቸውን በመስጠት፣ በሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲጎለብትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና ማኅበራዊ ፍትህ ላይ በማናቸውም መልኩ ድምፄን እያሰማሁ እቀጥላለሁ ብለዋል። “ነገር ግን በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ወይም ሕገ-ደንብ ተግባር ውስጥ ገብቼ የፓርቲ ፖለቲካን ለማራመድ ፍላጎት የለኝም። በቀጣይም ሁሉም ፓርቲዎች ሁሉን በሚያይ ዓይን እቀጥላለሁ” ሲሉ አጠቃለዋል።


አራት የፌዴራል ፖሊስ አባላት በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው ታሰሩ

Janaury1/2014
በቂም በቀል ተነሳስተውና አስበው፤ አንድን ሰው በእንጨት ዱላ ደብደበው ገድለዋል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተባቸው አራት የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በ6 ዓመት ከ7 ወራት እና በ5 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት በትናንትናው ዕለት የቅጣት ውሳኔ ሰጠ።
አንደኛ ተከሳሽ ምክትል ሳጅን ብሩክ ሽፈራው፣ ሁለተኛ ተከሳሽ ኮንስታብል ኃይላይ አርአያ፣ ሶስተኛ ተከሳሽ ኮንስታብል ፀጋዬ ወ/አረጋይ እና አራተኛ ተከሳሽ ሆነው የቀረቡት ኮንስታብል ታዬ ጭንዲን የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ የመሰረተባቸው ክስ ሁለት ሲሆን፤ በ1ኛው ክስ ስር አንደኛ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበው ዝርዝር፣ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ሰውን ለመግደል አስበው ሰኔ 2 ቀን 2004 ዓ.ም በግምት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 09/14 ልዩ ቦታው ጎፋ ማዞሪያ አካባቢ ጨካኝነታቸውን በሚያሳይ ሁኔታ 1ኛ ተከሳሽ ምክትል ሳጅን ብሩክ ሽፈራው ሟች ሃሚድ ወዳጆን በእንጨት ዱላ ጭንቅላቱን እና ጀርባውን ደጋግሞ ሲመታው፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችም የሟችን ጭንቅላት በዱላ በመምታት ጉዳት እንዲደርስበት ከማድረጋቸውም በተጨማሪ ራሱን በመከላከል በማይችልበት ሁኔታ በመግደላቸው በፈፀሙት ከባድ የሰው መግደል ወንጀል ተከሰዋል ይላል።
የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ በ2ኛ ክስ ዝርዝር ስር የጠቀሰው አራተኛ ተከሳሽ ኮንስታብል ታዬ ጭንዲን ሲሆን፤ ኮንስታብሉ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያሉትን ተከሳሾች ለመርዳት አስቦ ከላይ በክሱ የተጠቀሰው ድርጊት ሲፈጸም የሟች ሀሚድ ወዳጆ ሶስት ጓደኞች ለመገላገል ሲሉ የታጠቀውን ክላሽ በመደገን እንዳይገላግሉ የከለከላቸው በመሆኑ በፈፀመው አባሪ በመሆን ከባድ የሰው መግደል ወንጀል ተከሷል ሲል ያትታል።
በዐቃቤ ሕግ የቅጣት ማክበጃነት የቀረበው ተከሳሾቹ የፖሊስ አባል ሆነው ህግና አሰራርን እያወቁ ተቃራኒ በሆነ መንገድ ወንጀል መፈፀማቸውና በግብረ አበርነት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት መፈፀማቸው የወንጀሉን ከባድነት ያሳያል ብሏል። ተከሳሾቹ በበኩላቸው እንደቅጣት ማቅለያ ያቀረቡት ሀሳብ ከዚህ ቀደም የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው መሆኑንና የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች መሆናቸውን ሲሆን ፍርድ ቤቱም የሁለቱንም ወገኖች ሀሳብ ተቀብሎ መርምሯል።
የግራቀኙን የክስ ክርክር ሲያደምጥ የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት አራቱንም የፌዴራል ፖሊስ አባላት በፈፀሙት ወንጀል ጥፋተኛ ናቸው ያለ ሲሆን፤ በትናንትናው ዕለት (ታህሳስ 22 ቀን 2006 ዓ.ም) ደግሞ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾችን በ6 ዓመት ከ7 ወር ፅኑ እስራት ሲቀጣ 3ኛ እና 4ኛ ተከሳሾችን በ5ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል።


እ.ኤ.አ የ2013 ዓመት የኢትዮጵያ የአቦሸማኔው (ወጣቱ ትውልድ) መነሳሳት ሲገመገም፣

January 1/2014

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

እ.ኤ.አ በጃንዋሪ 2013 “እ.ኤ.አ 2013 የኢትዮጵያ የአቦሸማኔው ትውልድ ዓመት ይሆናል“ በማለት ትንበያ ሰጥቸ ነበር፡፡ እንዲህ ስልም ቃል
ገብቸ ነበር፣ “የኢትዮጵያ ወጣቶች ለፍትህና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሚያደርጉትን ትግል ለመደገፍ እና ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እንዲል የእራሴን ሙሉ አስተዋጽኦ እንደማደርግ እንዲሁም ትግሉ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገር ወጣቱ ትውልድ እንዲነሳሳ ሳደፋፍር ነበር፡፡” በዚህም መሰረት ጀግኖቹ ወጣቶች ትግላቸውን ቀጥለው ከፍ ወዳለ ደረጃ ላይ አድርሰውታል፡፡ ለወጣቶቹ እንዲህ በማለትም ተማጽኘ ነበር፣ “ብዙዎቹን ወጣቶች፣ ለመድረስ፣ ለማስተማር እና የበለጠ ግንዛቤ እንዲያገኙ ጥረት አድርጉ፡፡” ከዚህ አንጻር ቃሌን ሙሉ በሙሉ በማክበር ስኬታማ ስራ በመሰራቱ የተሰማኝን ኩራት ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡

እ.ኤ.አ ዴሴምበር 2013 በአሜሪካ በአርሊንግተን ከተማ ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከይልቃል ጌትነት ጋር በመገናኘቴ ታላቅ ደስታ እና ክብር የተሰማኝ ሲሆን ለወደፊትም ከኢትዮጵያ የአቦሸማኔው (ወጣቱ ትውልድ) ጋር ያለኝን የትግል አጋርነት በጽናት እንደምቀጥል ቃል ገብቻለሁ፡፡
እ.ኤ.አ በዴሴምበር 2013 የአቦ-ጉማሬው (የወጣቱ እና የቀድሞው ትውልድ) ትውልድ በሰላማዊ ትግሉ ሂደት በንቃት ከሚሳተፈው ከኢትዮጵያ አቦሸማኔ ትውልድ ጋር ያለውን የትግል አጋርነት ይፋ አድርጓል፡፡ እንዲህ ብዬ ተናግሬም ነበር፣ “የአቦ-ጉማሬው ትውልድ አባል መሆኔ በኩራት እንድሞላ አድርጎኛል፡፡” በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የአቦ-ጉማሬ ትውልድን “የመፍጠር” አስፈላጊነት ከምንም በላይ ተቀዳሚ ተግባር ሆኖ ተገኝቷል፡፡ የአቦ-ጉማሬው ትውልድ በአፈጣጠሩ የጉማሬው (የቀድሞው ትውልድ) አባል ሲሆን በተግባራዊ ድርጊቱ ግን እንደ አቦሸማኔው (ወጣቱ ትውልድ) የሚያስብ፣ አቦሸማኔውን የሚመስል እና እንደ አቦሸማኔው ሁሉ የክንውን ድርጊቶችን የሚፈጽም የማህበረሰብ ክፍል ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የአቦ-ጉማሬው ትውልድ የጉማሬውን (የቀድሞውን ትውልድ) ድክመቶች በሚገባ የተረዳ እና እነዚህን ግድፈቶች በማስወገድ የወጣቱን ትግል ወደ ላቀ የእድገት ምዕራፍ ለማሸጋገር በአንድ ዓላማ ለአንድ ዓላማ የሚሰራ የህብረተሰብ አካል ነው፡፡

የአቦ-ጉማሬው ትውልዶች ድልድይ ገንቢዎች ናቸው፡፡ ወጣቱን ከቀዳሚው ትውልድ የሚያገናኙ ጠንካራ የትውልድ ድልድዮችን የሚገነቡ ናቸውና፡፡ ህዝቦችን በዴሞክራሲ፣ በነጻነት እና በሰብአዊ መብት ጥበቃ የሚያስተሳስሩ ድልድዮችን ይገነባሉና፡፡ በትውልድ ቦታቸው እና አካባቢያቸው ተጠርንፈው የተያዙ ህዝቦችን የሚያገናኙ እና ጥልቅ የጎሳ ሸለቆዎችን ሰንጥቀው የሚያቋርጡ ድልድዮችን  የሚገነቡ ናቸውና፡፡ በቋንቋ፣ በኃይማኖት እና በክልል ተነጣጥለው የተቀመጡ ህዝቦችን የሚያገናኙ ድልድዮችን ይገነባሉና፡፡ ደኃውን ከሀብታም የሚያገናኙ ድልድዮችን የሚገነቡ ናቸውና፡፡ ብሄራዊ ዕርቅ ለማውረድ እና የብሄራዊ አንድነትን ለማምጣት ህዝቦችን የሚያገናኙ ድልድዮችን የሚገነቡ ናቸውና፡፡ በአገር ቤት ውስጥ ያሉትን ወጣቶች በውጭ አገር ከሚኖሩት የዲያስፖራ ወጣቶች ጋር የሚያገናኙ ድልድዮችን ይገነባሉና፡፡

በእ.ኤ.አ 2013፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች የእራሳቸውን የኃይማኖት ጉዳይ እራሳቸው በሚፈልጉበት መልክ ማስተዳደር እንዲችሉ እና በእምነታቸው ላይ የሚካሄደውን የመንግስት ጣልቃገብነት በመቃወም በሰላማዊ ሰልፍ ብሶታቸውን በመግለጻቸው ብቻ በገዥው አካል ብዙሀን መገናኛ ዘዴዎች ረበየለሽ እና ግዙፍ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ተካሂዶባቸዋል፣ በታጠቁ ኃይሎች በዘፈቀደ ከህግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርገዋል፣ በየማጎሪያ እስር ቤቶችም እንዲጋዙ ተደርገዋል፡፡ ሀገር በቀል የእስልምና አክራሪዎች እና አሸባሪዎች “የኃይማኖት ጦርነት” በማወጅ በኢትዮጵያ ውስጥ የእስላም መንግስት ማቋቋም ይፈልጋሉ በሚል ሰበብ በህዝብ ዘንድ ለማጋለጥ በማሰብ ገዥው አካል “ጅሃዳዊ ሃራካት” (“የኃይማኖት ጦርነት እንቅስቃሴ“ የሚል ርዕስ በመስጠት ለአንድ ሰዓት የዘለቀ “ዘገባዊ ፊልም” አዘጋጅቶ በአየር ላይ አውሏል፡፡ ያ የሞራል ዝቅጠት የተንጸባረቀበት፣ ሆን ተብሎ ዜጎችን ለማጥቃት በማለም እና ለምንም የማይጠቅም እርባናየለሽ ዘገባዊ ፊልም ለህዝብ በማሳየት የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች በናይጀሪያ በመንቀሳቀስ በህዝብ ላይ ጅምላ ፍጅት በማድረስ ላይ የሚገኘው ቦኮ ሃራም የተባለው ጽንፈኛ እስላማዊ አክራሪ ድርጅት ተከታዮች እና የአልቃይዳ ታዛዦች እና አሸባሪዎች ናቸው በማለት ወጣቶቹን ከህዝብ ነጥሎ ለማሳየት የታለመ ነበር፡፡ ያንን አስቀያሚ እና መቅንየለሽ ዘገባዊ ፊልም በጣም አድርጌ እኮንነዋለሁ፡፡ ምክንያቱም “ውሸቶች ታጭቀውበታል፣ ዓይን ያወጡ ደረቅ ውሸቶች፣ የተወገዙ ውሸቶች እና ሞራለቢስ ቅጥፈቶች፡፡ ‘ጅሃዳዊ ሃራካት’ የእነዚህ የአራት ቀጥፈቶች ጥቅል አንድ መጠሪያ ስም ነው::”

በእ.ኤ.አ የ2013 የእኔን ልዩ ጀግኖች አክብሪያለሁ፡፡ ለጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ለጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ልዩ ክብር እሰጣለሁ፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሁለቱ ጋዜጠኞች በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ኢትዮጵያ በአምባገነኑ ገዥ አካል እየታሰሩ፣ እየተሰቃዩ፣ ከህግ አግባብ ውጭ ብይን እየተሰጠባቸው፣ እና የማስፈራሪያ ውርጅብኝ እየተፈጸመባቸው ለሚገኙት ወጣት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ቋሚ ተምሳሌት በመሆናቸው ነው፡፡ እነዚህ ጋዜጠኞች ለእኔ ልዩ ናቸው፣ ምክንያቱም በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ፣ በአሁኑ ጊዜ ከአምባገነኖች ጋር እተካሄደ ያለውን ትግል እና የኢትዮጵያ ወጣቶች ለነጻነት የሚያደርጉትን ተጋድሎ የሚወክሉ የወጣቱ ቀንዲል በመሆናቸው ነው፡፡ እውነትን እና ትክክለኛውን መርህ ከመያዝ በስተቀር ሌላ ምንም ዓይነት የሚዋጉበት ነገር የላቸውም፡፡ ቅጥፈትን እና ውሸትን በእውነት ጎራዴ ድል ያደርጋሉ፡፡ ብዕርን ብቻ በመታጠቅ ተስፋ ማጣትን በተስፋ፣ ፍርሀትን በድፍረት፣ ቁጣን በምክንያታዊነት፣ እብሪትን በክብር፣ ድንቁርናን በዕውቀት፣ ታጋሽየለሽነትን በትዕግስት፣ ጭቆናን በትግል፣ ጥርጣሬን በመተማመን፣ እና ጭካኔን በሩህሩህነት ይዋጋሉ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ እነዚህ ጋዜጠኞች በስልጣን ላይ ላሉት እና ስልጣናቸውን ለታዕይታ ለሚያወሉ፣ ስልጣንን አላግባብ ለሚጠቀሙ፣ ስልጣናቸውን ከተሰጣቸው ስልጣን በላይ ለሚያውሉ እና ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ በሙስና ለሚዘፈቁ ባለስልጣናት ትኩረት በመስጠት ፊት ለፊት በመግጠም እውነት እውነቱን እስከ አፍንጫቸው ድረስ ይነግሯቸዋል፡፡

እ.ኤ.አ በ2013 በኢትዮጵያ ጥልቀት እና ስፋትን በመያዝ ተንሰራፍቶ የሚገኘውን አስደንጋጩን ሙስና ዓለም ተመልክቷል፡፡ ሙስናው በየትኛውም ኢከኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዘርፍ ላይ ተንሰራፍቶ ይገኛል- በኮንስትራክሽን፣ በቴሌኮሙኒኬሽን፣ በመሬት፣ በጤና፣ በፍትህ፣ እና በትምህርት፡፡ በትምህርት ላይ የሚፈጸም ሙስና ምናልባትም በጣም የአውዳሚነት ባህሪ ይኖረዋል፣ ምክንያቱም በወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ላይ ጠንከር ያለ አሉታዊ ተጽዕኖ ስለሚያስከትል ነው፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ትምህርትን አስመልክቶ እንዲህ ብለዋል፣ “ትምህርት ዓለምን ለመለወጥ የምትጠቀምበት ጠንካራ መሳሪያ ነው፡፡“ በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል ግን ድንቁርና ለውጥን ለመከላከል እና በስልጣን ኮርቻ ላይ ተፈናጥጦ ለመኖር የሚያገለግል ጠንካራ መሳሪያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ገዥው አካል የተሳሳተ መረጃ በመስጠት፣ የውሸት መረጃ በመጋት፣ የማሳሳቻ ለውጥ በማቅረብ፣ አቅጣጫቸውን የሳቱ ሀሳቦችን በማሰራጨት፣ ጊዜ ያለፈባቸውን መፈክሮች እና ካለፉት ዘመናት የመከኑ ቀኖናዎችን በመምዘዝ እና ለወጣቱ በማቅረብ የሀሰት የፕፓጋንዳ ዳቦ በማስገመጥ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያን ደንቆሮ ንጉሶች፣ ንግስቶች፣ ልዑላን እና ልዕልቶች የነገሱባት “የደንቆሮዎች ግዛት” እንድትሆን አድርገዋታል፡፡ የትምህርት ሙስና የወደፊቱን ወጣት ትውልድ እድል ይሰርቃል፡፡ እውቀትን ለማግኘት፣ ህይወታቸውን ለመለወጥ፣እና የአገራቸውን ዕጣፈንታ ለመወሰን የሚያገለግሏቸውን ዕድሎች በመዝጋት ለዘላለም የዕውቀት እና የምሁርነት ሽባ አድርጓቸው ይቀራል፡፡ ማልኮም ኤክስ በውል እንዳጤኑት፣ “ያለ ትምህርት በዚህች ዓለም ላይ የትም መሄድ አይቻልም” ብለዋል፡፡ በዚህ በወጥመድ በተያዘ እና ቁጥጥር ባለበት ዓለም እና ሙስና በተንሰራፋበት የትምህርት ስርዓት የኢትዮጵያ ወጣቶች የትም መሄድ ይችላሉን?

እ.ኤ.አ በዴሴምበር 2013 አጋማሽ የኢትዮጵያ ወጣቶች ቃልኪዳናቸውን አድሰዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ ያሉ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ የኃይማኖት ነጻነት እንዲከበር፣ ሰብአዊ መብቶች እንዲጠበቁ እና የህገ መንግስት እና ህዝባዊ ተጠያቂነት መኖርን በመጠየቅ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በአገሪቱ ማዕከል በሆነችው በአዲስ አበባ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡ በወጣቱ ስራ አጥነት፣ በዋጋ ግሽበት እና በተንሰራፋው ሙስና ላይ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ገዥውን አካል ጠይቋል፡፡ እኔ በዚህ ሁኔታ በጣም ተመስጫለሁ፡፡ “በኢትዮጵያ ወጣቶች ረዥሙ የነጻነት እና የክብር ጉዞ ተጀምሯል፡፡ በጣም ቆንጆ ነገር ነው፡፡ በጣም ቆንጆ ነገር ነው፣ ምክንያቱም ሰላማዊ ነው፡፡ በጣም ቆንጆ ነገር ነው፣ ምክንያቱም የአንዲት አገር ኢትዮጵያ ውድ ልጆች እርስ በእርሳቸው በመዋደድ እና በአገር ፍቅር ስሜት ሆ ብለው በአንድነት ሆነው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ እያሉ ሲጮሁ ነበር፣ “ከዚህ በኋላ ምንም ዓይነት ትዕግስት የለንም! ለውጥ እንፈልጋለን!”

በሰማያዊ የአቦሸማኔ (ወጣቱ ትውልድ) መነሳሳት ጊዜ የኢትዮጵያ ወጣት የህብረተሰብ ክፍል የለማ ምናባዊ አስተሳሰቡን በመጠቀም አዲስ ልዩ የሆነ ለውጥ በኢትዮጵያ ሀገሩ ለማምጣት እየተነሳ ነው በማለት የክርክር ጭብጤን ሳቀርብ ነበር፡፡ ወጣቶቹ አዲሲቷን የጀግኖች ሀገር የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ያልማሉ፡፡ በዘር ክፍፍል ላይ የተመሰረተችውን፣ በጎሳ አፍቅሮ የተዋቀረችውን፣ የኃይማኖት ጽንፈኝነት እና አፍቅሮ ዘረኝነትን አካታ የተመሰረተችውን አሮጊቷን ኢትዮጵያ አይፈልጉም፡፡ የጾታ እኩልነት እንዲሰፍን ይፈልጋሉ፡፡ በድፍረትም እንዲህ በማለት እጠይቃለሁ፣ “ወጣቶቹ የራሳቸው የሆነች ኢትዮጵያ ለምን አትኖራቸውም? የእኛ የእራሳችን የሆነች ኢትዮጵያ አለችን፣ ወጣቶቹ የራሳቸው ኢትዮጵያ እንድትኖራቸው ጊዜው አሁን አይደለምን?”

እ.ኤ.አ በሳመር 2013 ፕሬዚዳንት ኦባማ አፍሪካን በጎበኙበት ጊዜ የኢትዮጵያን ወጣት የህብረተሰብ ክፍል በስፋት ለመድረስ ስል በማዘጋጃቸው ትችቶቼ ላይ ተጨማሪ ፈጠራ ለመጨመር በማሰብ ሁለት “ፍላሽ ድራማ” (ትያተር) ጭውውቶችን አካትቼ ነበር፡፡ በዚያ ጽሁፌ ላይ የተጠቀሱት ሁለቱ ተዋሃኒዎች ኦባማ ለምን “ወደ አፍሪካ እንደመጡ” በእርግጠኝነት የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ የንግግራቸው ዳህራ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ዱማ፡ አሃ! ኦባማ ወደ ትውልድ አሁጉሩ ወደ አፍሪካ ተመልሶ መጣ፣ ጥሩ ነው ሹዲ
ሹዲ፡ የለም፣ ከአፍሪካውያን ጋር ለመነጋገር ነው የመጣው
ዱማ፡ ለመነጋገር?  ጣፋጭ ንግግር? ጠንካራ ንግግር? ትንሽ ንግግር? የሰላም ንግግር?
የጦርነት ንግግር? የሚተገበር ንግግር? ንግግር ብቻ?  የስሜት ንግግር? ትርጉመቢስ ንግግር?
ርካሽ ንግግር? ገንዘብ ይናገራል… ንግግር፣ ንግግር፣ ንግግር…?

ከኦባማ የአፍሪካ ጉብኝት በኋላ ሁለቱ ወጣት ተዋሃኒዎች የእራሳቸውን ዳኝነት ሰጡ፣
ሹዲ፡ ኦባማ መጡ እና ሄዱ…
ዱማ፡ ኦባማ መጡ እና አዩ፣ ግን ምን አሸነፉ? አገኙ?
ሹዲ፡ ኦባማ መጡ፡፡ አዩ፡፡ ተመልሰው ሄዱ፡፡

በእ.ኤ.አ 2013 ፕሬዚዳንት ኦባማ “አፍሪካን ማጠናከር” በሚል ለጀመሩት ተነሳሽነት የአፍሪካን ወጣቶች ለማጠናከር የእራሴን ጠቃሚ ምክሮች ልለግሳቸው ሞክሬ  ነበር፡፡ “አፍሪካን ከማጠናከራቸው” በፊት ወጣቱን እንዲያጠናክሩት፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ አፍሪካ የኃይል (ኤሌትርክ) ችግር እንዳለባት እንደሚያውቁ እና ለዚህ ችግር መወገድም አጋር እንደሚሆኑ የተናገሩትን ንግግር እኔም እስማማለሁ፡፡ አፍሪካ በኃይል ስልጣን ከሚባልጉ፣ በኃይል ስልጣናቸውን አላግባብ ከሚጠቀሙ፣ በኃይል ስልጣናቸውን እና ኃላፊነታቸውን ከሚያደበላልቁ እና በኃይል ስልጣናቸውን ትክክል በማስመሰል አላግባብ ከሚጠቀሙ ሌባ መሪዎች ፕሬዚዳንት ኦባማ በእርግጥም አፍሪካን ባለ ኃይሎች እያጠናከሩ ነው፡፡ ጥያቄው አፍሪካን ከማጠናከሩ ላይ አይደለም፣ ነገር ግን አሜሪካ በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በእየዓመቱ በእርዳታ፣ በብድር እና በቴክኒክ እገዛ ሰበብ ኃያላን አምባገነን አፍሪካውያን ገዥዎች ኪስ እያጨቀች ኃይል የሌላቸውን የአፍረካ ህዝቦች እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል ከማወቁ ላይ ነው፡፡ ኦባማ አፍሪካውያንን ማጠናከር ከፈለጉ ተራ አፍሪካውያን ህዝቦችን ስልጣናቸውን አላግባብ ከሚጠቀሙ እና በስልጣን ከሚባልጉ አምባገነን ገዥዎች መዳፍ በመጠበቅ የማጠናከር ስራውን መጀመር ይችላሉ፡፡ የፖለቲካ ስልጣኑን ይዘው የወጣቱ እምቅ ኃይል ጎልቶ እንዳይወጣ እንቅፋት የሚሆኑበትን እንዲሁም ብዝበዛ እና ስልጣንን አላግባብ መጠቀምን በማስቆም የወጣቱን ኃይል ማጠናከር አለባቸው፡፡ በየዓመቱ የሚለገሰውን በቢሊዮን የሚቆጠር የዶላር ዕርዳታ የአፍሪካ የሌባአምባገነኖችን ኃይል በመቀነስ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠረውን የአፍሪካ ወጣቶችን ኃይል ማጠናከር ይኖርባቸዋል፡፡

አ.ኤ.አ በማርች 1963 የተካሄደውን የአሜሪካ የሲቪል መብቶች እንቅስቃሴን የመሩትን ወጣቶች 50ኛ ዓመት በዓል በዋሽንግተን ዲሲ አክብሪያለሁ፡፡ በ26 ዓመታቸው የአሜሪካንን የሲቪል መብቶች እንቅስቃሴ የጀመሩትን እና ፍቅር የነገሰበት ማህበረሰብን ለመመስረት ማርቲን ሉተር ኪንግ “በህብረተሰቡ ህይወት የይዘት ለውጥ እንዲሁም በኑሮው የመጠን ለውጥ“ በሚያመጡት ነገሮች ልዩ ትኩረት ሰጥተው ሲታገሉ ነበር፡፡ የማርቲን ሉተር “ፍቅር የነገሰበት ማህበረሰብ” ከዘረኝነት፣ ከድህነት እና ከጦረኝነት ነጻ የሆነ ማህበረሰብ ነው፡፡ ፍቅር እና ፍትህ የነገሰበት ማህበረሰብ በእትማማቾች እና በወንድማማቾች ፍቅር እና መተሳሰብ መርሆዎች ላይ በመመስረት ለህይወት ትርጉም የሚሰጥ ነው፡፡ ማርቲን ሉተር ኪንግ እንዲህ ብለዋል፣ “የዘመናችን ዋና የፖለቲካ እና የሞራል ጥያቄዎች መልስ ሰላማዊ ትግል ነው፡ ጭቆናን እና ኃይልን በሰላማዊ መንገድ ለማስወገድ ጭቆንና እና ኃይልን አለመጠቀም የሰው ልጅ ፍላጎት መሆን አለበት፡፡ የሰው ልጅ በቀልን፣ ኃይልን እና አሉታዊ የአጻፋ ምላሽ የመስጠት መንገዶችን በማስወገድ በሰዎች መካከል ያሉትን ግጭቶች በሰላም መፍታት አለበት፡፡ እንግዲህ የዚህ ሁሉ መሰረቱ ፍቅር ነው፡፡”  ሲሉ ማርቲን ሉተር ኪንግ ተናግረዋል::

እ.ኤ.አ በ2013 “የኢትዮጵያ ወጣቶች ህዳሴ” እውን እንዲሆን ጥሪ አቅርቢያለሁ፡፡ እንዲህ በማለት የክርክር ጭብጤን አቀርባለሁ፡፡ በኢትዮጵያ እውነተኛ “ተሀድሶ”, “እንደገና የመወለድ” ወይም “እንደገና የመፈጠር” ዓይነት ዕድል እንዲመጣ ከተፈለገ ሊመጣ የሚችለው በወጣቱ ደም፣ ላብ እና እንባ ብቻ እንጅ በአምባገነኖች ወይም በእነርሱ አፈቀላጤዎች ከሚፈበረክ የውሸት ፕሮፓጋንዳ አይደለም፡፡ ሀገሪቱን ወደ ኢኮኖሚ ተሀድሶ ለመምራት የጦሩ ጫፍ ኢትዮጵያውያን/ት ወጣቶች ናቸው:: ኢኮኖሚዉን የሚንቀሳቀሱት ኢትዮጵያውያን/ት ወጣት ኢንተርፕሪነሮች መሆን እንዳለባቸው፡፡ ወጣት ኢትዮጵያውያን/ት ምሁራን የዕውቀት ኃይል ሽግግርን በግንባርቀደምትነት መምራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ወጣት የኢትዮጵያ ሳይንቲስቶች እና ኢንጅነሮች አገሪቱ እራሷን እንድትችል እና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነቷም እንዲጎለብት ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ወጣት የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ወጣቶች የፍትህን ጎራዴ መታጠቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ወጣት የኢትዮጵያ መሪዎች ጠንካራ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ለውጥ አራማጆች በመሆን የ21ኛው ክፍለ ዘመን የተከበረች እና ኩሩ ኢትየጵያን መመስረት አለባቸው፡፡

እ.ኤ.አ በ2013 በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ወጣት ስደተኛ ሰራተኞች ለአስደንጋጭ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተዳርገዋል፡፡ የሳውዲ ፖሊሶች፣ የደህንነት ሰራተኞች እና ዘራፊዎች ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን በመንገድ ላይ በማደን የመደብደብ፣ የማሰቃየት እና አንዳንድ ጊዜም የመግደል ወንጀሎችን ፈጽመውባቸዋል፡፡ የሳውዲ ፖሊሶች ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን ሲያሰቃዩ የሚያሳዬውን የቪዲዮ ክሊፕ መመልከት ለህሊና የሚሰቀጥጥ ነገር ነው፡፡ የሳውዲ አረቢያ ፖሊሶች እና የደህንነት ኃይሎች ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን በየመንገዶች ላይ ሲያሳድዱ፣ ሲያጠቁ እና ሲገድሉ የሚያሳየው የቪዲዮ ክሊፕ ትርምስ በሰው ልጆች ዘር ላይ የተፈጸመ የሰብአዊ መብት ወንጀል ዋና ማረጋገጫ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል “የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር” “የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣኖች በህገወጥ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች ላይ ያሳለፉትን ውሳኔ እና ህገወጥ ኢትዮጵያውያንን/ትን ወደ ሀገራቸው በመመለሱ ፖሊሲ ላይ ኢትዮጵያ ያላትን አክብሮት ትገልጻለች፡፡” በማለት በሳውዲ አረቢያ ያለው ገዥ አካል በስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ለፈጸመው የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እንዲህ ሲሉም አክለዋል፣ “አገሮች በጦርነት ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ህገወጥ ናቸው የሚሏቸውን ዜጎች እንደዚህ ያለ ወደ አገራቸው የመመለስ ፈጣን እርምጃ ቢወስዱ ህዝብም ሊቀበለው እና ሊረዳው ይችላል፣ ሆኖም ግን በሰላማዊ ጊዜ እንደዚህ አይደረግም” በማለት የሳውዲ አረቢ ገዥ አካል በኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ የፈጸመውን ሁኔታ ገልጸዋል፡፡ በሌላ አገላለጽ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ሰራተኞች ለተፈጸሙባቸው የመብት እረገጣዎች እራሳቸውን ተጠያቂ ማድረግ አለባቸው ማለት ነው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለጥንቱን አባባል “የሚያጎርስህን እጅ በፍጹም አትንከስ” አዲስ ትርጉም ሰጥተውታል፡፡

የእኔን አፍሪካዊ ጀግና ታላቁን ኔልሰን ማንዴላን ደህና ይሁኑ ብዬ የምሰናበትበት ጊዜ ነበር፡፡ ኔልሰን ማንዴላን በፍጹም ላገኛቸው አልቻልኩም፣ ባገኛቸው እንዴት ደስ ባለኝ! ለማግኘት የምፈልገው ደግሞ በዓለም ላይ እጅግ ከተከበሩት ሰው ጋር ተገናኝቸ ነበር በማለት ለስሜቴ ክብር ለመስጠት አይደለም፣ ነገር ግን ለአፍሪካውያን ክብርን፣ ኩራትን እና ሞገስን ላጎናጸፉት እኒያን ጀግና ኔልሰን ማንዴላን በዚህ አጋጣሚ አመሰግናለሁ የምትለዋን ቃል በትህትና ለማቅረብ እንጅ፡፡

ኔልሰን ማንዴላ ድልድይ ቀያሽ ነበሩ፡፡ ዘርን፣ ጎሳን እና የህብረተሰብ መደብን የሚያገናኙ ድልድዮችን ገንብተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ እሳት አጥፊ ነበሩ፡፡ በዘር እና በጎሳ ጥላቻ ተቀጣጥሎ የነበረውን ቤት እሳት በማጥፋት በደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ እውነት እና ዕርቅ እንዲሰፍን አድርገዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ መንገድ ቀያሽ ነበሩ፡፡ በረዥሙ ጉዞ ወደ ነጻነት የሚያደርሱ በስም “ደግነት” እና  “ዕርቅ” የሚባሉ ሁለት መንገዶችን በመገንባት የተናገሩትን በተግባር አሳይተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ የህንጻ ንድፍ ነዳፊ/architect ነበሩ፡፡ በአፓርታይድ አመድ ላይ በብዙሃን ዘር ዴሞክራሲ የተዋበውን ማማ ገንብተዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ የልዩ ተሰጥኦ ባለቤት ነበሩ፡፡ ከባርኔጣ ላይ ጥቁር እና ነጭ እርግቦችን በአንድ ጊዜ በመልቀቅ በነጻነታቸው ተንፈላስሰው እንዲበሩ አድርገዋል፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ለዘላለም የሚኖር የለውጥ ሐዋርያ ነበሩ፡፡ ጥላቻን በፍቅር፣ ፍርሃትን በወኔ፣ ጥርጣሬን በእምነት፣ ታጋሽየለሽነትን በትዕግስት፣ ቁጣን በመግባባት፣ ጥላቻን በስምምነት፣ እና ቅሌትን በክብር የሚለውጡ ነበሩ፡፡

የማንዴላን መልዕክት ለኢትዮጵያውያን/ት ወጣቶች አስተላልፌአለሁ፡፡ “ፍቅር የነገሰበትን የኢትዮጵያን ማህበረሰብ ለመመስረት ደግ ነገርን አድርጉ፣ ይቅርታን እና እርቅን አውርዱ፡፡ የስኬት ቃልኪዳን ባይኖርም ሞክሩ፣ ውድቀት እንዳለ ብታውቁም ሞክሩ፣ ጥርጣሬ ያለ እና እርግጠኝነት የጎደለ መሆኑን ብታውቁም ሞክሩ፡፡ ደክማችሁ እና መቀጠል የማትችሉ መሆኑን ብታውቅም እንኳ ሞክሩ፡፡ ተስፋ በማይኖርበት ጊዜም ሞክሩ፡፡ ዓላማችሁን ካሳካችሁህ በኋላም ቢሆን ሞክሩ፡፡ ማንዴላ እንደሞከሩት ሁሉ ሞክሩ፡፡”

እ.ኤ.አ በ2013 የሰማያዊ ፓርቲ አስረጅ ምስክርነት ሆኘ ቀርቢያለሁ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ሰማያዊ ፓርቲን የምደግፍበት ምክንያት ከወጣቶች፣ በወጣቶች፣ ለወጣቶች፣ የተቋቋመ የፖለቲካ ፓርቲ ስለሆነ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የአብዛኛውን የኢትዮጵያን ህብረተሰብ ፍላጎት እና ጥቅም ሊወክል የሚችል ፓርቲ ስለሆነ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከኢትዮጵያ ህዝብ ከ35 ዓመት የዕድሜ ክልል በታች ያለው የህብረተሰብ ክፍል 70 በመቶውን ይሸፍናል፡፡

በአሁኑ ጊዜም የኢትዮጵያ ወጣቶች ለዴሞክራሲ፣ ለህግ ልዕልና፣ ለነጻነት እና ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ሲባል የደም፣ የላብ እና የእንባ መስዕዋትነት በመክፈል ላይ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ምርጡ እና ብሩህ አዕምሮ ያለው ወጣት እየተቀጣ፣ ፍርደገምድል ፍርድ እየተበየነበት፣ እየታሰረ፣ እና ጸጥ እረጭ ብሎ እንዲገዛ እየተደረገ ነው፡፡ ከእነዚህ የወጣት ዝርዝር የመጀመሪያው እረድፍ ላይ የሚገኙት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ እስክንድር ነጋ፣ አንዷለም አራጌ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ በቀለ ገርባ፣ አቡበካር አህመድ፣ ውብሸት ታዬ፣ ኦልባና ሌሊሳ፣ አህመዲን ጀቤል፣ አህመድ ሙስጣፋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ በቅርቡ ከህይወት የተለየው የኔሰው ገብሬ እና ሌሎች ለቁጥር የሚያታክቱ ትንታግ የኢትዮጵያ ወጣቶች ናቸው፡፡ “የሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄን” የኢትዮጵያ ወጣቶች ለእራሳቸው እና ለወደፊቱ ትውልድ የሚተላለፍ ህልማቸውን እና ሀሳቦቻቸውን የሚተገብር ድርጅታዊ ተቋም አድርጌ እወስወደዋለሁ፡፡ ዝምታውን ከዚህ በኋላ እናቁም እና “ከሰማያዊ ፓርቲ ንቅናቄ” ጎን በመሰለፍ ድጋፋችንን እንድንሰጥ ለሁሉም ህዝቦች ተማጽዕኖዬን አቀርባለሁ፡፡

የኢትዮጵያ ወጣቶች፡ ከተኛችሁበት እንቅልፍ በመንቃት እንደ አንበሳ በመነሳት እና እንደ አቦሸማኔ በመወርወር “ውዲቱን ኢትዮጵያ” ገንቡ፣

በኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2013 የአቦሸማኔዎች ትውልድ ዓመት ዋና የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ያለፈው ከድንቁርና፣ ከጎሳ ጥላቻ፣ ከዘር አድልኦ እና ከጾታ ኢፍትሀዊነት የጸዳች “ውዲቷን ኢትዮጵያ” ተገንብታ የማየትን ህልም ወጣቶቹ በፍጹም በፍጹም እንዳያቆሙ የሚለው ነው፡፡ ዓመቱ የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች የስኬት ዓመት ነው ማለት እችላለሁ፣ ሆኖም ግን ስራዎቻቸው ገና ሙሉ በሙሉ አልተከናወኑም፡፡ ከፊታቸው ገና ረዥም እና አስቸጋሪ ጉዞ ይጠብቃቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወጣቶች ከመጨረሻው ግባቸው ከመድረሳቸው በፊት በጣም አደገኛ የሆኑ ሸለቆዎችን የማቋረጥ፣ ድንጋያማ እና ቀጥ ያሉ ተራራዎችን የመውጣት፣ እና  ጎርፍ የሞላው ወንዞችን የመሻገር ተግባራትን ማለፍ ይጠብቃቸዋል፡፡ ጉዟቸውን በድፍረት እንዲቀጥሉ እማጸናለሁ፡፡ እ.ኤ.አ በ1819 የእንግሊዝ ሙሰኛ፣ ጨካኝ እና ቀጣይነት ያለው የአምባገነን አገዛዝ ጥቃትን በመቋቋም በሰላማዊ ትግሉ ሲፋለሙ ለነበሩ ወጣቶች ድጋፍ ይሆን ዘንድ ፔርሲ ባይሸ ሸሌይ የቋጠሯቸውን ስንኞች እንድያጣጥሙ እጋብዛቸዋለሁ፣
ታላቅ ስብሰባ ይደረግ፣
በታልቅ ግነዛቤ፣
በነጠሩ ቃላቶችም አውጁ፣
አምላክ ነጻ አድርጎ ፈጥሯችዋልና፣

አምባገነኖቹም ከደፈሩ፣
ከማሀላችሁ ታጥቀው በፈረሳቸው ይጋልቡ
ይውጉ ይቁረጡ ይጨፍጭፉ
እንደልባቸው ያርጉ፡፡

በታጠፉ እጆች እና አተኩረው በሚያዩ ዓይኖች፣
አለቅንጣት ፍርሃት አለመገረም፣
ሲገድሉ ሲያርዱ ልብ በሏቸው፣
ቁጣቸው እስኪበርድላቸው፡፡

ከዚያም ከእንቅልፋቸው እንደነቁ አንበሶች ተነሱ፣
በቁጥር የለሽ ብዛታቸሁ፣
በንቅልፍ የጣሉባችሁን የእስር ሰንሰለቶች እንደጤዛ አራግፏቸው፣
እናንተ ሺ ናቸሁ፣ እነርሱ ግን ጥቂት፡፡

የኢትዮጵያ ወጣቶች፡ እንደ አንበሶች ተነሱእንደ አቦሸማኔዎች ተሰንዘሩ!

ታህሳስ 22 ቀን 2006 .

ስለ ዳግማዊ ምንሊክ የ” ኒዎርክ ታይምስ ” ጋዜጣ (ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር) የዛሬ 96 አመት የፃፈው ፅሁፍ ለአሁኑ ትውልድ ታሪካዊ ማስረጃ ነው

January1/2014


ጉዳያችን የተሰኘው ብሎግ ያቀረበውን ጡመራ  እንዲህ አቅርበንላችኋል ፣ ጉዳያችን ብሎግን ከልብ እናመሰግናለን 

ዳግማዊ አፄ ምንሊክ ፎቶ 

ኢትዮጵያ በየዘመኗ በሕልውናዋ ላይ የተቃጣባት የመበታተን አደጋን ያለፈችበት መንገድ የጦርነት መንገድ ብቻ አይደለም።ሆኖም ግን ከነበሩን የግጭት ታሪኮች በዘለለ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩ እና በሕዝብ ዘንድም የተወደዱ  መሪዎች ነበሩን።ከእነኝህ ውስጥ ዳግማዊ ምንሊክ አንዱ ነበሩ። አፄ ምንሊክ ሀገር የማስተዳደር ጥበብን የተማሩት በአፄ ቴዎድሮስ እጅ ሆነው እድገታቸውን በንጉሡ ቤተመንግስት ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።ንጉሡ የቀደሙ አባቶቻቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ዮሐንስ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ አላማቸው እውን እንዲሆን ያደረጉ እድለኛ ንጉስም ናቸው።
አፄ ምንሊክ ኢትዮጵያን አንድ ከማድረግ አልፈው እስከ ኬንያ፣ሱዳን እና ሱማልያ ግዛት ድረስ ዘልቀው ገብተው በቅኝ ግዛት ይማቅቁ የነበሩ ህዝቦችን ነፃ ያወጣሉ የሚል ስጋት የነበረባቸው  እና በወቅቱ በእነኚሁ የጎረቤት ሃገራት  ላይ የጥቅም ፍላጎት የነበራቸው የአውሮፓ ሃገራት በብርቱ ተፈታትነዋቸው ነበር።በመሆኑም አዲስ የድንበር ውል ከኢትዮጵያ ጋር የመፈራረም ፍላጎት ከእንግሊዝ፣ፈረንሳይ እና ኢጣልያ በኩል ጥያቄ መነጻቱን የወቅቱ የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ።
ዛሬ ዛሬ በምንሊክ ላይ ታሪካዊ መሰረት የሌላቸው ቀድሞ አፄ ምንሊክ የቅኝ ግዛት ጥማታቸውን በገቱባቸው እና ቂም በያዙ ፀሐፊዎች የተፃፉ ናቸው ብለው ከሚነግሩን አስገራሚ ''የታሪክ'' ፅሁፎች ውስጥ ''በምኒሊክ ዘመን እስከ አስር ሚልዮን ኦሮሞዎች አለቁ'' የሚል ፅሁፍ በአንዳንድ የማህበራዊ ድህረ ገፆች ተለቀው ሲነበቡ መመልከት  አስገራሚ የሰሞኑ ክስተት ነው።በፖለቲካው አለም በቂ ርዕዮተ አለምም ሆነ ፖለቲካዊ ፍልስፍና የጠፋባቸው አንዳንድ ወገኖች ''ትርፋማ'' ብለው ያሰቡት የዘር ፖለቲካ በኢትዮጵያውያን መካከል መዝራት እና ከመቶ አመት በፊት  የሆነውን የታሪክ ክስተት የአሁኑን ትውልድ በመውቀስ ትኩረት ለማግኘት ሲታትሩ መመልከት የዘመኑ አስቂኝ ተውኔት ነው።ዳግማዊ ምንሊክ ገና ብዙ የሚጠና ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ወታደራዊ ክህሎት ባለቤት ለመሆናቸው በወቅቱ ከወጡት የዓለማችን ድንቅ ጋዜጦች አንዱ የ ኒውዮርክ ታይምስን እትም መመልከት ይበቃል።
ከእዚህ በታች በሚገኘው የኒውዮርክ ታይምስ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሕዝብ ብዛትን 7,000,000 (ሰባት ሚልዮን) መሆኑን ያስቀምጣል። እዚህ ላይ አንዳንድ እራሳቸውን የታሪክ ምሁራን ነን በሚል ባልተጨበጠ ይልቁንም በምኒሊክ የቅኝ ግዛት ህልማቸው ከተደናቀፈባቸው ቂመኛ ፀሐፊዎች አነበብን የሚሉት እና የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ያማለሉ መስሏቸው  ''ምንሊክ 10 ሚልዮን ኦሮሞ ገደሉ'' እያሉ ኢትዮጵያ ከነበራት የህዝብ ብዛት (7 ሚልዮን) በላይ  ቁጥር ሲጠሩ እፍረት አልተሰማቸውም።
''ማን ያውራ የነበረ'' እንዲሉ የኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ ጋዜጣው አዲስ አበባ በነበረ  በልዩ ዘጋቢው አማካይነት ስለንጉሡ እና ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታ ፅፎ ነበር።ጋዜጣው  አፄ ምንሊክ እና አስተዳደራቸውን ከገለፀበት አረፍተ ነገር  ውስጥ እነኝህ ይጠቀሳሉ  -
- ኢትዮጵያን ወደ ህገመንግስታዊ የንጉሥ አስተዳደር ለመቀየር ሂደት ላይ መሆኗን፣
- የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 7 ሚልዮን መሆኑን፣
- አፄ ምንሊክ ንጉሰ ነገስት ሲሆኑ ጦርነት የነበረው የአፄ ዮሐንስ ተተኪ  እሳቸው መሆናቸውን ካልተቀበሉት ጋር ብቻ እንደ ነበር፣
- የአውሮፓውያንን ስልጣኔ ወደሀገራቸው ለማምጣት የባርያ ንግድን ከመዋጋታቸውም በላይ ነፃ ትምህርት ዕድል ዜጎች እንዲያገኙ መሰረት መጣላቸውን፣
- ምንሊክ እራሱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ሰው መሆናቸውን። ከችሎታዎቻቸው መካከል  ዲፕሎማት፣የፋይናንስ ባለሙያ እና  ወታደር የሚሉት እንደሚጠቀሱ እና
- እንደ ዲፕሎማት እና ወታደር የጣልያንን ወረራ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ያደረጉበት ጥበብ መሆኑን፣
የሚሉ ይገኙበታል።የጋዜጣውን ሙሉ ፅሁፍ ከእዚህ በታች ያለውን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ።

 የኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይክፈቱ።

Published: November 7, 1909 Copyright © The New York Times

http://query.nytimes.com/mem/archive-free/pdf res=F50A12F63A5A15738DDDAE0894D9415B898CF1D3

የ“ኢትዮ ምህዳር” ዋና አዘጋጅ እንደገና ተከሰሰ

December 31/2013

የኢትዮ ምህዳር ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ፤ ከንግድ አሰራርና ሸማቾች ባለስልጣን ጋር በተገናኘ ሐሙስ እለት ማዕከላዊ ምርመራ ድረስ ተጠርቶ ቃል እንዲሰጥ ተደረገ፡፡ በባለስልጣኑ ለፖሊስ ያመለከተው፣ ህዳር 23 ቀን 2006 ዓ.ም “የንግድ አሰራርና ሸማቾች ባለስልጣን ቅሬታ ቀረበበት” በሚል ርእስ በጋዜጣው ላይ ባወጣው ዜና ሳቢያ እንደሆነ ጋዜጠኛ ጌታቸው ተናግሯል፡፡ 

የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ቢሯችን ድረስ መጥተው የዜና ጥቆማ ሲሰጡን፤ መስሪያ ቤቱ ዘመድ አዝማድ በሙስና የሚሰባሰቡበት ሆኗል በማለት የጽሑፍና የቃል መረጃ አቅርበውልናል የሚለው ጋዜጠኛ ጌታቸው፤ ጋዜጠኛ ልከን ስራ አስኪያጁን ለማነጋገር ብንሞክርም ሳይሳካ ወደ ህዝብ ግንኙነት ክፍል እንድንሄድ ነው የነገረን ብሏል፡፡ እዚያም ቢሆን ጥያቄዎቻችሁ ኢሜይል አድርጉልኝና መልስ እሰጣለሁ ብሎ እንደዘገየብንና እንዳልተሳካልን አካተን ዜናውን ሰርተነዋል ብሏል ጋዜጠኛው፡፡

 በ15 ቀኑ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን በኩል ቅሬታ ሲደርሰን፤ ቅሬታ ካለው እናስተናግዳለን ብለን መልስ ሰጥተናል ያለው ጋዜጠኛ ጌታቸው፤ ሐሙስ እለት ወደ ማእከላዊ ምርመራ ተጠርቼ ቃሌን እንድሰጥ ከተደረግሁ በኋላ በዋስትና ተለቅቄያለሁ ብሏል፡፡ “ኢትዮ ምህዳር” ጋዜጠኞች በአዋሳ ዩኒቨርሲቲ ክስ ቀርቦባቸው በቀጠሮ ቀን ለመከራከር በተጓዙበት አጋጣሚ በስራ ባልደረባቸው ላይ አደጋ እንደደረሰባቸው ይታወሳል፡፡ ለሁለት ቀናት በለገጣፎ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደነበረም አዘጋጁ ተናግሯል፡፡


ባለትዳሯን ከሌላ ወንድ ጋር ስትሳሳሚ ፎቶ አንስቼሻለሁ፤ይህንንም ፎቶ በፌስቡክ አለቀዋለሁ ብሎ አስፈራቷል በሚል ክስ የታሰረው አርቲስት ዳንኤል በዋስ ተፈታ

january 1/2014

አንዲት ባለትዳር ሴትን ከሌላ ወንድ ጋር ስትሳሳሚ ፎቶ አንስቼሻለሁ ይህንንም ፎቶ በፌስ ቡክ አለቀዋለሁ ብሎ በስልክና በአካል አስፈራርቷል በሚል ክስ ተመስርቶበት የታሰረው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ፍርድ ቤት ቀርቦ በዋስ መለቀቁን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ ገለጹ።

ከዚህ በፊት በነበረው የዜና እወጃችን አርቲስት ዳንኤል ተገኝ መታሰሩን የዘገብን ሲሆን ዜናውን ተከታትለን እንደምንዘግብ ቃል በገባነው መሠረት ዛሬ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጉዳዩን በቅርበት ሲከታትሉ ነበር የዋሉት። አርቲስቱ “ወንድ ጋር ስትሳሳሚ ፎቶ አንስቼሻለሁ ይህንንም ፎቶ በፌስ ቡክ አለቀዋለሁ ብሎ በስልክና በአካል አስፈራርቷል” በሚል ከቀረበበት ክስ በተጨማሪ ከዚህችው ወ/ሮ ፊልም እሰራለሁ ብሎ 500 ሺ ብር እንደተቀበለና በማጭበርበር ክስ ቀርቦበት እንደነበር ይታወሳል።

ዘጋቢዎቻችን አርቲስት ዳንኤል ክስ በዋስ ስለመፈታቱ እንጂ ለፍርድ ቤቱ ስንት እንዳስያዘ የጠቀሱት የለም። ሆኖም ግን አርቲስቱ ሌላ ቀጠሮ ተሰጥቶት ዋስትና አስይዞ ተፈቷል።

ዘ-ሐበሻ

ኢትዩጵያ ህጻናትን ወደ ውጭ በጉዲፈቻ ስም በመላክ ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኑዋና መረጃዎች አመለከቱ

December 31/2013
ታህሳስ ፳፪( ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ የወጡ መረጃዎች እንዳሳዩት በአፍሪካ ባለፉት 6 ዓመታት በጉዲፈቻ ስም ወደ ውጭ ከተላኩት 34 ሺ 342 ህጻናት ውስጥ 63 በመቶ ወይም 21 ሺ 365 ሰዎችን በመላክ ቀዳሚ ናት።

በሃገሪቱ በሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ፈቃድ የተሰጣቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ጉዳይ አስፈፃሚ የጉዲፊቻ ደላሎች ተበራክተዋል፡፡ በአብዛኛው ለጉዲፈቻ በሚቀርቡ ህፃናት የህይዎት ታሪክ ላይ የሚጻፈው ” ተጥለው የተገኙ ወይም ወላጆቻቸውን  በህይዎት ያጡ ” የሚል በመሆኑ በልጆቹ ህይወት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አለው።

የሴቶች እና ህፃናት ሚኒስቴር የሆኑት ወ/ሮ ዘነቡ መንግስት ህጻናቱን ወደ ውጭ ለማላክ ለፍርድ ቤት የሚያስከፍለው 25 ብር ብቻ መሆኑን ይናገሩ እንጅ፣ የጉዲፈቻ አሳዳጊዎች፣ አንድ ህጻን ለማግኘት እስከ 20 ሺ ዶላር እንደሚከፍሉ ይናገራሉ፡፡

የደቡብ ክልል የሴቶች እና ህፃናት ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ  በህፃናት የሚነግዱ አካላት በርካታ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ ኢትዩጵያ ያወጣችው አማራጭ የህፃናት መመሪያ በራሱ ሙሉ አለመሆኑንና ለችግሩ መባባስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉንም ይገልፃሉ፡፡ በርካታ የፖሊስ እና የመንግስት አካላት ” ህጻናት ወደ ውጪ ቢሄዱ ይለወጣሉ” የሚል አመለካከት መያዛቸው ስህተት ነው የሚሉት ሃላፊዋ፣ በደቡብ ክልል እንደወጡ የቀሩ ልጆችን የሚጠብቁ እናቶች ዛሬም መንግስትን እያማረሩ ነው ፡፡

ኢቲቪ በቅርቡ ባቀረበው ዘገባ 832 ህጻናት በየአመቱ ከኢትዮጵያ ይወጣሉ ብሎአል። ይሁን እንጅ ከፌደራል መደበኛ ፍርድ ቤት የተገኘ መረጃ እንደሚያሳየው በ2005 ብቻ 2 ሺ 201 ህጻናት ከአገር እንዲወጡ ፈቃድ ተሰጥቷል።
ከአፍሪካ ሀገራ ላይቤራ እና ዛምቢያ ጉዲፊቻን በማገድ ለህጻናቱ በቂ እንክብካቤ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል። በኢትዮጵያ ጉዲፈቻ ለመጀመርያ ጊዜ የሕግ ከለላ የተሰጠው በ1952 ዓ.ም. በወጣው የፍትሐ ብሔር ሕግ ነው፡፡