Thursday, December 5, 2013

የካርቱም ድራማ፡ እነ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሕዝቡን ስብሰባ ጠርተው እነርሱ ቀሩ

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ
(ከካርቱም የተላከልኝ መረጃ ነው፤ እንዳለ ለጥፌዋለሁ።) ትላንት ማክሰኞ (ህዳር 24, 2006 ዓም) በኢትዮጵያ ስዓት አቖጣጠር ልክ ከ10:00ጀምሮ ለተለያዩ የማህበራት አመራሮችና እድሮች ዛሬ ሮብ ለሚደረግ ስብሰባ ሰዉ እንዲጠሩ መልዕኽት ተላለፈ። መልዕክቱ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለች የሚመሩትና ሌሎች ሚንስትሮች የሚገኙበት በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ5:00 የሚጀመር ስብሰባስላል ከየማህብራችሁ 200 ሰዉ እንድትጋብዙ የሚል በስልክ መደወል ተጀመረ።

 በተሰጠዉ መምሪያ መሰረት ሁሉም አመራሮች ወደ አባሎቻቸዉ መደወል ያዙ። በአካል ያገኙትም ለሌላዉ እንዲናገር ወሬው ድፍን ካርቱም እንዲዳረስ አደረጉ። የሚገርመዉ ከሃይለማሪያም ደሳለኝ ውጭ ሌሎች ሚኒስትሮች ከባለፈዉ ዓርብ ጀምሮ መግባት ጀምረዋል። እስከ ትላንትና ቀን ሁሉም በየመጡበት ፊና የተለያዩ ስራዎች ሲያከናዉኑ ቆይተዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደግሞ ትላንት ማክሰኞ ምሽት ላይ ካርቱም ገቡ። አይነጋ የለ ለሊቱ ነጋ። በካርቱም የሚገኙው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስትገባ የመጀመሪያዉ በር ስታልፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ/ማህበረሰብ/ ሬስቶራንት አለ ከዛ አልፎ ሌላ ሁለተኛ በር ልዩ ፍተሻ የሚደረግበት አልፎ ኤምባሲዉ ትገባለህ። hailemariam and samora በዚህ መስረት ስብሰባዉ ዛሬ ሮብ ይደረጋል ተብሎ የኮሚኒቲዉ ሰራተኞች ሁሉም ከጥዋቱ 2:00 ስራ ገብተዉ ግቢዉን ሲያፀዱ ዉለዉ ረፋድ ላይ በኢትዮጵያ ስዓት አቆጣጠር 6:00 ዛሬ ስራ ስለሌለ ወደ ቤታችሁ ሂዱ ተባሉ። ጊዜዉ እየገፋ ነዉ ስዓቱ እየተቃረበ ነዉ። ስብሰባዉ በማህበረሰቡ ውስጥ በሚገኙዉ መናፈሻ ይደረጋል ተብሎ ሲጠበቅ ነበር። ምክንያቱ ሁሌም የተለያዩ ፖለቲካዊ ና ሃይማኖታዊ በዓላት የሚደረጉት በዚሁ አከባቢ ነበር። ዛሬ ግን ሌላ ነገር ተደረገ። ለታዳሚዉ የሚሆኑ ወንበሮች በኤምባሲው ግቢ ዉስጥ በለችሁ ትንሽ ሚዳና ዛፎች ስር ተደረደሩ።

 ስዓቱ ገፋ ኤምባሲዉ ውስጥ የሚገኙ ሰራተኞ ከዉትረዉ ለየት ባለ አለባበስ ግማሾች ሱፍ በከራቫታ ግማሾቹ ደግሞ ነጭ ቲሸርት በክራቫታ ለብሰዉ ውር ውር ማለት ጀመሩ። የደህንነት ሰዎች ግቢዉን ሁሉ መመርመር ጀመሩ። የተወሰኑ የፀጥታ ሰዎች ከተመደቡ በኋላ ልክ በኢትዮጵያ ስዓት አቆጣጠር 10:30 ወደ ውስጥ መግባት ተጀመረ። ህዝቡ ቀስ ያለ መምጣት ጀመረ። ኤምባሲዉም ሆነ የኮሚኒቲ ሬስቶራንቱ በሱዳን ፖሊሶች ተከቧል። የመጀመሪያዉ በር ፍተሻ ላይ ሰዉ በማህበሩ ወይ በእድሩ እየተጠየቀ ሞቫይሉን በትልቅ ፌስታል ዉስጥ በማስቀመጥ ተፈትሾ ባዶ እጁን ወደ ግቢዉን ይገባል። ከዛም በተጨማሪ የኤምባሲዉ መግቢያ ሁለተኛ በር ጋር ድጋሜ ተፈትሾ ወደ ውስጥ ይገባል። በስተግራ ወደ ተዘጋጁት ወንበሮች ሁሉ ገብቶ ቦታ ቦታዉን መያዝ ይጀምራል። እንድህ እንዲህ እየተባለ እስከ 12:00 በኢትዮጵያ አቆጣጠር ሁሉም ገብቶ ቁጭ ይላል። ሌላዉ የሚገርመዉ ትዕይንት ደግሞ የገዛ ኢምባሲያችን ህንፃ ላይ ተራ ፖሊሶች ወጥተዉ አከባቢዉን እየቃኙ ጠበቃዉን ተያይዘዉታል። በተጨማሪም በኤምባሲዉ ዙርያ በሚገኙት ህንፃዎች የተለያዩ ፖሊሶች ተመደቡ።

 በተለይ ከኤምባሲዉ አጠገቢ በሚገኝ ሲንድያን ሆቴል አከባቢ ትንሽ እንግዶች በመስኮት ወጣ ገባ ሲሉ በፖሊሶች አርፈዉ እንዲቀመጡ ተነገራቸዉና ተደበቁ። ህዝቡ ተሰብስቦ ዝምታ ሰፍነዋል። መድረክ አከባቢ ለሚኒስትሮችና የተወሰኑ ዲፕሎማቶች ተብሎ 15 ቪ ኣይ ፒ ወንበሮች ተቀምጠዋል። ከነሱም አለፍ ብሎ ሶስት ጠቅላይ ሚኒስትሩና የመድረኩ መሪዎች ይቀመጡባቸዋል ተብለዉ ከነ ጠሬጲዛና ማይክሮፎን የተዘጋጁተዉ ነበሩ። ሁሉም የእንግዶችን መምጣት መጠባበቅ ጀመረ። አንዴ የኤምባሲዉ ደህንነቶች ወደዚህ ወደዚያ ይላሉ። ምንም የማያዉቁ የሱዳን ቦዲጋርዶች /አጃቢዎች/ ገብተዉ ወደዚ ወደዚያ ይላሉ። በመሃል ከተሰበሰበዉ ህዝብ 3 ኤርትራዉያን ተይዘዉ እንዲወጡ ተደረጉ። አሁን ስዓቱ ሄደ ልክ 1:30 ሆነ። እንግዶች አሁንም አልመጡም። 

ሁኔታዉ ያላማራቸዉ የኤምባሲዉ ዲፕሎማቶች ግራ ተጋቡ። በዚህ መሃል የአምባሳደር አባዲ ዘሞ አማካሪ የሆኑት ወ/ሮ ፍረወይኒ እና የኤምባሲዉ ፋይናንስና አስተዳደር አቶ ቀለሙ የሃይለማርያምንና የመድረክ መሪዎች ወንበር ያዙ። ወ/*ሮ ፍረወይኒ ትንሽ ማይክሮፎኑን መታመታ በማድረግ “ሚኒስትሮቹ ወደዚህ አገር የመጡት ዋና አላማ ከሱዳን መንግስት ጋር በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ነበር የመጡት። ለዚህም ጉዳይ ዛሬ ጥዋት በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2:00 ወደ ገዳሪፍ /የሱዳን ሌላዉ ከተማ / ሄደዋል። የሄዱበት አላማ ደግሞ የሱዳን መንግስት ከኢትዮጵያ የ200 ኪሎዋት የኤሌትሪክ ሃይል ለመዉሰድ ለማስወረቅ ነዉ። እዛ ዉለዉ ከዛ በኋላ በሱዳን ወደ ሚሰራዉ መርሃዊ በተባለዉ ቦታ ያለዉ ትልቁ ግድብ ለመጎብኘት ሄደዋል። የዛሬዉ ፕሮግራም እነሱ በፈለጉት መስረት ከህዝቡ ጋር መገናኘት እንፈልጋለን ይህንን ስዓት ያዙልን ብለዉን ነዉ ስንጠብቃቸዉ የዋልነዉ። እስከ ቅርብ ስዓት ድረስ ስንደዉልላቸዉ ነበር። እንደሚመጡ ነግረዉን ነበር። አሁን ከትንሽ ደቂቃዎች በፊት ግን በኢትዮጵያ መንግስት ስም ህዝቡን ይህንን ያህል ስዓት ስላስቆየነዉ ይቅርታ ጠይቁልን ብለዋል። እኔም የመንግስት አካል ስለሆንኩኝ ይቅርታዉ እያስተላለፍኩ ነዉ” ሲሉ ተስብሳቢዉ የተወሰነ ማለትም 10% ሲያጨበጭብ 90% ማጉረምረምና በስሜት መናገር ጀመረ። 

በዚህ መሃል ፍረወይኒ ንግግርዋን በመቀጠል ይቅርታ ነገ ደሞ ወደ ፈረንሳይ ይበራሉ ስለዚህ 80 ሚሊዮን ህዝብ ሃላፊነት ተሸክመዉ እየዞሩ ነው ስለዚ ምናልባት ለመናገር የምትፈልጉት ነገር ካላችሁ አንድ ሁለት ሰዉ እድል ልስጥ ትላለች። በዚህ ግዜ የመጀመሪያ እጅ አዉጥቶ ዕድል የተሰጠዉ ሼክ ዳዉድ የአማራ ልማት ማህበር ሊቀመንበር እንዲሁም በባለፈዉ ዓመት በሱዳን የኮሚኒቲው ወክሎ ከሌላ አገራት የዲያስፖራ አካላት ጋር በመሆን የህዳሴን ግድብን ጎብኝቶ የመጣ ሰዉ ነዉ። ሼክ ዳዉድ ሲናገር ፥- እኔ በበኲሌ ይህ ይቅርታ በምንም ታአምር አልቀበለዉም ብሎ ሲናገር ህዝቡን ሁሉ አጨበጨበ ንግግሩን በመቀጠል , በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም እና ዶ/ር ቴድሮስ አድሐኖም አለመምጣታቸዉ ለማመኑ በሚያስቸግር ሁኔታ ከብዶኛል፡ ይህ ንቀት ነዉ። የሰዉ አገር 200 ሜጋ ዋት ሃይል እሰጡ እየረዱ የኛ ችግር አልታይ ብሎዋቸዉ ነዉ ወይ በጣም በጣም ያሳዝናል። 

መንግስታችን የሰዉ አገር ፀጥታ እያስከበረ የኛን መብት ማስከብር አለመቻሉ ጉልበት ስላጣ አይመስለኝም በጣም በጣም አዝኛለሁኝ በመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፊት ለመጠየቅ ከያዝኩዋቸዉ ጥያቄዎች አንዱ በቅርቡ እምዱርማን ተብሎ በካርቱም በሚገኙዉ ሰፈር ሰሙኑን አንድ ማዚን የሚባል የሱዳን ጦር መሪ የኢትዮጵያ መንግስት ፍቃድ ሰጥቶኛል እያለ ወረቀት እያሳየ ሰዎች ከቤታቸዉ እያስወጣ ወደ እስርቤት እየወረወረ ነዉ። ይህ ለምን ይሆናል። ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ጭብጨባ በዛ በመቀጠል መኪ ያተባለ የጉራጌ ልማት ማህበር ሊቀ መንበር ሲናገር ችግሩ የኛ ነዉ ሌላ ጊዜ ወደ ኢምባሲ አንመጣም ባለስልጣን ሲመጣ ግን እንዲህ ለምን እንመጣለን ለምን በማህበር አትደራጁም ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ህዝቡ ማጉረምረም እና አንዳንዶችን መሳደብ ጀመሩ። ጩሆት ሆነ በዚህ ማሃል ወ/ሮ ፍረወይኒ እንዲህ ቀጠለች “ ጠላ ቤት አይደለም ኤምባሲ ነዉ እንደፈለጋችሁት አትጭሁ ስነስርዕእት ስነስርዓት እንደማመጥ። መኪ ያለዉን ትክክል ነዉ። እስቲ እንነጋገር በእዉነት እናንተ በአገራችሁ ከፍቶዋችሁ ነዉ የመጣችሁ? ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ መጥፎ ስለሆነች ነው ወይ? በማለት ህዝቡን ለማግባባት ብትሞክርም ህዝቡ ማጉረምረሙ ቀጠለ በመጨረሻም ስብሰባዉ ያለፍሬ በይቅርታ ተበተነ። የሚገርመዉ ሰዉ ሲገባ ሞቫይል በፊስታል ነበር የተሰበሰበዉ። ከስብሰባዉ ሁሉ ሲወጣ ሌላ ግርግር ሆነ። ሁሉም እስኪወጣ ድረስ 2:30 ሆነ፡ ድራማዉ በእንዲህ ተጠቃለለ:: 

‹‹መለስ ዛሬ የለም፡፡ አዲስ ጊዜ ነው፡፡ ደስ ብሎኛል፤ ቪዛዬም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተሰጥቶኛል፡፡››...አና ጎሜዝ

Decenber 5/2013

የሸፈተው የአና ጎሜዝ ልብ?!

‹‹መለስ ዛሬ የለም፡፡ አዲስ ጊዜ ነው፡፡ ደስ ብሎኛል፤ ቪዛዬም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተሰጥቶኛል፡፡››...
(… Meles has gone! This is a new timing. I am pleased I was granted visa without preconditions.)
ይህንን ያሉት በምርጫ በ1997 የአውሮፓ ኅብረት ምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ሆነው የመጡት ሚስስ አና ጎሜዝ ሰሞኑን ከአዲስ ስታንዳርድ መጽሔት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው፡፡
የአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ መሰንበቻውን ካስተናግደችው ጉባኤዎች መካከል የአፍሪካ ካሪቢያን፣ የፓስፊክና አውሮፓ የጋራ የፓርላማ ስብሰባ አንዱ ነበር፡፡ ጉባኤው የመንግሥት ሚዲያ ቀልብ ይሳብ እንጂ የሕዝቡን ቀልብ የሳበው ግን ሌላ ነው፡፡ ሪፖርተርን ጨምሮ የግሉን ሚዲያና የሕዝቡን ቀልብ የሳበው የሚስስ አና ጎሜዝ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ነው፡፡ 
ከዘጠኝ ዓመት በፊት ከመንግሥት ጋር የተወዛገቡት የአና ጎሜዝ መምጣት የበለጠ አስገራሚ ያደረገው እሳቸው በዚሁ ጉባኤ በአዲስ አበባ መገኘታቸው ብቻ አይመስልም፡፡ እሳቸው በአባልነታቸው የሚታወቁበት አውሮፓ ኅብረት ፓርላማ ለኢትዮጵያ 5.5 ቢሊዮን ብር በዕርዳታ መልክ መለገሱን ኢቲቪ ዘግቧል፡፡ በአመዛኙ የምርጫ 97ን ተከትሎ የፖለቲካ ምህዳሩ መጥበቡን ቢናገሩም፤ ከአንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ግልጽ ውይይት ማድረጋቸውና አዲስ የለውጥ ነፋስ አየሁ ማለታቸውም ሌላው አነጋጋሪ አጀንዳ ሆኗል፡፡ 
አና ጎሜዝና ምርጫ 97
ኢትዮጵያ ከደርግ ውድቀት በኋላ ቢያንስ በመርህ ደረጃ የሕዝብ ይሁንታ የሚረጋገጥበት ሕዝባዊ ሥልጣን በምርጫ የሚያዝበት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ታውጇል፡፡ ኢሕአዴግ አብዛኛው የፓርላማ መቀመጫውን በምርጫ ስም (ገለልተኛ ታዛቢዎች እንደሚሉት) መቆጣጠር ይዞት የመጣው ባህል፣ በሦስተኛው ዙር የ1997ቱ አገራዊ ምርጫ ተሰብሮ ነበር፡፡ በወቅቱ እንደ አሸን የፈሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁለት አውራ ጥምረቶች (ኅብረትና ቅንጅት) በመፍጠር ገዥውን ፓርቲ ኢሕአዴግ በሰላማዊ መንገድ መፈታተን ችለው ነበር፡፡ ኋላ ኋላ ጉዳዩ ላይ ጥናት ያካሄዱት ምሁራን እንደሚሉት በሙያ ሥነ ምግባር ጉድለት ምክንያት፣ የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት አደገኛነቱ የሚያመዝን ቢሆንም፣ የግል ሚዲያው በአገሪቱ ታሪክ ተጠናክሮ የመጣበት ወቅትም ነበር፡፡ መንግሥት የሰነዘራቸው ከፍተኛ ትችቶች ሳይዘነጉም የአገር በቀልና የውጭ ሲቪክ ማኅበራትም በፖለቲካው የላቀ ሚናቸውን ተጫውተዋል፡፡  
ይኸው የ97ቱ ምርጫ በአንዳንድ የኅብረተሰብ ክፍል ላይ የራሱ የሆነ የማይረሳ መጥፎ ጠባሳ ጥሎ አልፏል፡፡ በመንግሥትና በተቃዋሚዎች ግንኙነት ላይ ያስከተለው ሕመምም አሁንም ድረስ አልተፈወሰም፡፡ ምርጫውን ተከትሎ ለተፈጠረው ቀውስም፣ በዋና ተዋናዮቹ ሁለቱ ወገኖች ብቻ የተወሰነ አልነበረም፡፡ 
ኢሕአዴግ እንደሚለው፣ አንዳንድ የፖለቲካ ሰዎች የራሳቸው የፖለቲካ አጀንዳ ይዘው የተንቀሳቀሱ የ‹‹ኒዮሊበራል›› ኃይሎች በገንዘብም ሆነ በሞራል ጫና ለመፍጠር ክፍተቱን ተጠቅመው ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ይህ በማናቸውም አገሮች የሚፈጠር ቀውስ ለውጭ ኃይሎች በር መክፈቱ ግን በኢትዮጵያም በሌሎች አገሮችም እንግዳ አይደለም፡፡ በምርጫም ሽፋንም ሆነ በኃይል በመፈንቅለ መንግሥት፣ በተለይ ምዕራባውያን ኃይሎች የማይፈልጉትን አካል ለመጣልና የሚፈልጉትን ወገን ደግሞ ለማንገሥ ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ጣልቃ ገብነት ከማድረግ አይቦዝኑም፡፡ የሚያስከትለው ውጤት ከአገር አገር ይለይ እንጂ፣ በተለይ በድሀ አፍሪካ አገሮች የእነዚህ ኃይሎች እጅ ረዘም ያለ ነበር፡፡ ዋና አጀንዳቸው ባይሆንም ለዲሞክራሲ መስፋፋት ምንም ዓይነት ፋይዳ አይኖራቸውም ግን አይባልም፡፡ 
ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ ስማቸው በቀላሉ ከሕዝብ አእምሮ ከማይጠፋው ጥቂት የፖለቲካ ሰዎች እኩል የሚታየው፣ የውጭ ሰዎች ግንባር ቀደሙ ደግሞ የሚስስ አና ጎሜዝ ነው፡፡ ለዚህም ይሆናል ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተደረገው ዓለም አቀፍ ጉባኤና ከአውሮፓ ኅብረት ከፍተኛ ዕርዳታም በላይ፣ የብዙዎችን ቀልብ የሳበ የሚመስለው፡፡ ወይዘሮዋ በአሁኑ ወቅት በተለይ የአዲስ አበባን ነዋሪዎች ቀልብ የሳቡት ከምርጫው ቀውስ ዘጠኝ ዓመት በኋላ ወደ ከተማይቱ ሲመጡ ለመጀመርያ ጊዜ በመሆኑ ብቻ አይመስልም፡፡ ያሳዩት የአቋም ለውጥ ጭምር እንጂ፡፡ 
የአና ጎሜዝ ልብ ዛሬ ወዴት ነው?
ከሁለት ዓመት እስር በኋላ በይቅርታ የተፈቱ የቅንጅት አመራሮች፣ የሚዲያና የሲቪክ ማኅበራት የፖለቲካ አራማጆችም፣ በምርጫው ወቅት ያሳዩትን ጉልበት ይዘው መቀጠል አልቻሉም፡፡ በተቃዋሚዎች ላይ ተስፋ የቆረጡት ግን የአሜሪካ መንግሥት (ቀጥሎ የመጣው የኦባማ አስተዳደር) እና የአውሮፓ ኅብረት ብቻ አልነበሩም፡፡ በምርጫ ውጤት እንደታየው፣ መራጩ ሕዝብ በተቃዋሚዎች ላይ ተስፋ መቁረጡን በግልጽ አሳይቷል፡፡ ማሳያው በ1997 ምርጫ መቶ በመቶ ቅንጅትን የመረጠው የአዲስ አበባው ሕዝብ፣ ከአንድ ወንበር በስተቀር በ2002 ዓ.ም. ኢሕአዴግን መርጧል፡፡ የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት፣ የፖለቲካ ቁርጠኝነት የትግል ጽናት የላቸውም ብሎ ተስፋ የቆረጠባቸው የተቃዋሚዎች አመራሮች ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ተንቀሳቅሰናል›› በሚል ይቅርታ መጠየቃቸው ብቻም አይመስልም፡፡ መሪዎቹ ከእስር ከወጡ በኋላ በሁለት እግሩ መቆም የሚችል ድርጅት ይዘው መቀጠል አለመቻላቸውም ጭምር ነው፡፡ ይህንን በማድረግ ምትክ፣ በመካከላቸው በተፈጠረው አለመግባባት ወደተራ ድብድብ እስከመግባት የደረሱ ነበሩ፡፡ መንግሥት ይህንን ክስተት ለፕሮፖጋንዳ በስፋት ተጠቅሞት ነበር፡፡ 
በቅርቡ አዲስ አበባ የመጡት አና ጎሜዝ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው ግልጽ የሆነ ውይይት ማድረጋቸው ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ከተቃዋሚዎች ጋር ምንም ንግግር አለማድረጋቸው ይነገራል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ድንገተኛ ሕልፈት አገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ሽግግር እንድታደርግ እንደ መልካም አጋጣሚ የተመለከቱት አና ጎሜዝ፣ በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መሠረታዊ የሆነ ለውጥ ለማየት የጓጉ ይመስላሉ፡፡ 
በዚሁ ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፣ ‹‹አዲስ ነፋስ አለ›› ያሉት መንግሥት ለእሳቸው ያለምንም መንገላታትና እንቅፋት ቪዛ ስለሰጣቸው የአወንታዊው ለውጥ ምልከታቸው ቀዳሚ ነው፡፡ አሁንም ከ97 በኋላ የፖለቲካ ምህዳሩን በተመለከተ ችግሮች መኖራቸው አስረግጠው የተናገሩት አና ጎሜዝ፣ በአጠቃላይ ግን አገሪቱ በተለየና አዲስ አመራር ውስጥ መሆኗን ይናገራሉ፡፡ ያዩዋቸው ለውጦች ምን ምን እንደሚያካትቱ በዝርዝር ባያስረዱም፡፡ አንድ ትልቅ ለውጥ የተመለከቱት የሶሻል ሚዲያ መስፋፋት ሲሆን፣ ያንንም ከመንግሥት ቁጥጥር በላይ በመሆኑ ነው ይላሉ፡፡ በሙሰኞች ላይ የተወሰደ ዕርምጃም አድንቀዋል፡፡ ‹‹በኢትዮጵያ ላይ እኔ ምንም የኢኮኖሚ ሆነ ምንም ግላዊ ፍላጎት የለኝም›› የሚሉት አና ጎሜዝ፣ አንዳንድ ባለሥልጣናት በግልጽ ለመነጋገር መፍቀዳቸውንም እንደ ለውጥ ሳይመለከቱት አልቀሩም፡፡ ‹‹እኔን ለመስማት መፈለጋቸው ራሱ ጥሩ ይመስለኛል›› ብለዋል፡፡ ‹‹በሽብርተኝነት የታሠሩት ጋዜጠኞች እንጂ አሸባሪዎች አይደሉም›› ለሚለው ሙግታቸው ማስረጃ እንዲያቀርቡ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ‹‹ጋዜጠኞች መሆናቸውን ነው የማውቀው›› ከማለት ውጪ የማቀርበው ማስረጃም የለኝም ብለዋል፡፡ 
በወቅቱ ከቅንጅት አመራሮች አንዱ የነበሩት ዶክተር ኃይሉ አርአያ፣ የአና ጎሜዝን መምጣት በበጎ ጎን አይተውታል፡፡ ‹‹መቀራረቡ በእኔ በኩል ገንቢ ነገር ነው፤››  የሚሉት ዶክተር ኃይሉ፣ ‹‹በአገሪቱ ተለውጧል ያሉትን ነገር ግን እሳቸው ብቻ ናቸው የሚያውቁት፡፡ እሳቸው በወቅቱ ይዘውት ከነበረው አቋም አሁን ምንም የተለወጠ ነገር አላየሁም፡፡ አቋማቸውን የሚያስለውጥ መሠረታዊ ለውጥ አላየሁም፤›› ብለዋል፡፡ ዶክተር ኃይሉ እንደሚሉት፣ በአገሪቱ እሳቸውም የማይክዱት ልማት እየመጣ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ‹‹ከዚያ ውጪ ግን በፖለቲካ መስክ ምንም የመጣ ለውጥ የለም፡፡ ቪዛ ስለተሰጣቸው ብቻ አዲስ ለውጥ አለ ማለት ግን አግባብ አይደለም፤›› ይላሉ፡፡ 
የቀድሞ አምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶ በበኩላቸው በ1997 ዓ.ም. በካምፓላ (ኡጋንዳ) አምባሳደር የነበሩ ቢሆንም ጉዳዩን በቅርበት ይከታተሉ እንደነበር ይናገራሉ፡፡ አና ጎሜዝ በወቅቱ በኢትዮጵያ ላይ የያዙት አቋም የግላቸው እንዳልነበር በአጠቃላይ የምዕራባውያን መንግሥታት አቋም እንደነበር ይናገራሉ፡፡ በተለይ ደግሞ፣ ኒዮሊበራሊዝምን አክርረው የሚቃወሙት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስን እንደ ‹‹የወገብ ቅማል›› አድርገው ነበር የሚያዩዋቸው ብለዋል፡፡ በወቅቱ ከኢትዮጵያ የተባረሩት አራት የውጭ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችም የተቃውሞ እንቅስቃሴውን በገንዘብ ሲደግፉ እንደነበር ለአብነት ይጠቅሳሉ፡፡ አና ጎሜዝ ብቻም ሳይሆኑ እነ ክርስቶፈር ክላፋም፣ ክሪስ ቦርና የኤችአር 2003 ሕግ አርቃቂ ዶናልድ ፐይን የመሳሰሉትም በተመሳሳይ ይጠቅሳሉ፡፡ እሳቸውም እንደ ዶክተር ኃይሉ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ አቋም የሚያስለውጥ ምንም የተለወጠ ነገር የለም፤›› በሚለው ሐሳብ ይስማማሉ፡፡ 
አና ጎሜዝ ከመንግሥት ጋር መታረቅ የፈለጉበት ምክንያት ግን ‹‹ታክቲክ›› እንደሚሆን በመገመት፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ላይ ያለው አቋም መለወጡን ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ይገምታሉ፡፡ ‹‹ከወደቀ ጋር መሆን ማን ይፈልጋል?›› በማለት፡፡ ‹‹አሁን በ60 ዲግሪ አቋማቸው ተለውጧል ያሉት አምባሳደር ተስፋዬ፣ ግለሰቦች የራሳቸው ሚና ቢኖራቸውም ያው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የተዉት ፖሊሲና ርዕዮተ ዓለም እየተተገበረ ስለሆነ ምንም አቋም የሚያስለውጥ ነገር የለም፤›› ይላሉ፡፡ ‹‹ስህተታቸውን አምነው፣ ለውጡ ከልብ ተቀብለውት ከሆነ ግን መልካሙን እመኝላቸዋለሁ›› ብለዋል፡፡ 
በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሰላምና ልማት ተቋም ተመራማሪው አቶ አቤል አባተ በበኩላቸው፣ ‹‹የአና ጎሜዝ መለሳለስ ከአውሮፓ ውስጥ የደረሰባቸው መገለል ውጤት ነው፤›› ይላሉ፡፡ ከ1997 ምርጫ በኋላ የኢሕአዴግ መጠናከርና መንግሥት በልማት ላይ ያሳያቸው ተጨባጭ ዕድገቶች የተቺዎቹን አፍ እየዘጋለት እንደሆነ በመግለጽ፡፡ ለዚህም ከአቶ መለስ ሕልፈት በኋላ ምንም ዓይነት የፖሊሲም ሆነ የስትራቴጂ ለውጥ ባልታየበት የአና ጎሜዝ መለሳለስ ጥሩ ማሳያ ነው ብለውታል፡፡ 
‹‹ቀደም ሲል ከተቃዋሚ አመራሮች ጋር የነበራቸው መጥፎ ስም ለማደስ ፈልገው ይሆናል፡፡ ለአቋማቸው መለወጥ ዋነኛ ምክንያት ግን መገለላቸውና በአውሮፓ ኅብረት ውስጥ ምንም ዓይነት ተሰሚነትና ተአማኒነት ማጣታቸው ነው፡፡›› 
የባከኑ ስምንት ዓመታት
አና ጎሜዝ ሰሞኑን እዚሁ አዲስ አበባ እስከታዩ ድረስ፣ በተገኙ አጋጣሚዎች በሙሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ሲከሱ፣ ሲወነጅሉና ሲያጣጥሉ ቆይተዋል፡፡ 
ከይቅርታ ጠያቂዎቹ መካከል ወደ አሜሪካና አውሮፓ የገቡ አንዳንድ አመራሮች ከውጭ በመሆን ከእነ ሚስስ አና ጎሜዝና ዶናልድ ፔይን (ከሦስት ዓመት በፊት ሕይወታቸው ያለፈው) ጋር በመሆን ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡ መንግሥትን በኃይል ለመጣል ከዳያስፖራ ድጋፍ እያሰባሰበ የሚገኘውና በመንግሥት በአሸባሪነት የተፈረጀው ግንቦት ሰባት ሊቀመንበሩ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ (በአገር ክህደት ክስ በሌሉበት ሞት የተፈረደባቸው) ጋር በቅርበት ሲሠሩ ከቆዩት መካከል፣ አሁን ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ‹‹ግልፅ›› ውይይት ማድረጋቸውን የሚናገሩት ሚስስ አና ጎሜዝ ናቸው፡፡ በአውሮፓ ኅብረት አስተባባሪነት ኢትዮጵያን በሚመለከቱ መድረኮች፣ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ የተለያዩ ተቃውሞአቸውን እንዲገልጹም ከማመቻቸት ባሻገር ራሳቸው በተለያዩ ወቅቶች ኅብረቱ በኢትዮጵያ ላይ እንዲጨክን ድምፃቸውን ሲያሰሙ ኑረዋል፡፡ በኢትዮጵያ በሽብርተኝነት ክስ ተፈርዶባቸው በእስር የሚገኙት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣ መንግሥት ያፀደቃቸውን ሕጎች እንዲከልስ፣ ኅብረቱ ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ዕርዳታም ሆነ ብድር እንዲያቋርጥ በተለያዩ መንገዶች ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ የእሳቸው ጥረት፣ በአጠቃላይ የአውሮፓ ኅብረትና አባል አገሮች ሥልጣን ላይ ባለው መንግሥት ዕውቅና እንዲነፍጉ የሚጠይቅ ነው፡፡ ከዚያም አልፈው ወይዘሮዋ፣ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ባለው የድንበር ግጭትም ጭምር አስተያየት የሚሰጡ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሄጉ ፍርደ ገምድል ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲያደርግ ለዚህም ኅብረቱ ጫና እንዲፈጥር ይጠይቃሉ፡፡ 
በተለይ አምና መጋቢት ወር ላይ ለኅብረቱ ባቀረቡት ስሞታ፣ የአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የሆኑት ጆሴ ማኑኤል ባሮሶ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝን በሚያነጋግሩዋቸው ወቅት፣ አገሪቱ ‹‹የፖለቲካ›› እስረኞቿን በአስቸኳይ እንድትፈታ የድንበር ውሳኔው በአስቸኳይ እንዲተገበርና በሶማሊያ የምታደርገውን ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት እንድታቆም ጫና እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ‹‹በእርግጥ እሳቸው ማምጣት የሚችሉት ለውጥ እምብዛም ነው›› ያሉዋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያምንም የሥልጣን ሽግግር እንዲያደርጉ ፕሬዚዳንቱ ጫና ይፈጥሩ ዘንድ ተማጽነው ነበር፡፡ አውሮፓ ኅብረት ምርጫ 97ን ተከትሎ ያደረገው ለውጥ ካለ፣ ለአገሪቱ የሚሰጠው ዕርዳታ በመንግሥት በኩል መሆኑ ቀርቶ በፕሮጀክቶች አማካይነት በቀጥታ ለዜጎች እንዲውል ማድረጉ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ በሶማሊያም ጉዳይ ሆነ በአካባቢው ደኅንነትና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ዙርያ በጋራ ሲሠራ ቆይቷል፡፡ ይህ ግን ለአና ጎሜዝ ፍፁም ተቀባይነት የለውም፡፡ ኅብረቱ በኢትዮጵያ ላይ የሚከተለው ፖሊሲ እስካሁንም አይዋጥላቸውም፡፡
በመጀመርያ አካባቢ የአውሮፓ ኅብረት በተለይ ደግሞ የኅብረቱ ዋና አከርካሪ ከሆኑት አባል አገሮች ግንባር ቀደም ከሆኑት መካከል እንግሊዝ በኢትዮጵያ ላይ የዕርዳታና ብድር ለኢትዮጵያ መንግሥት በቀጥታ እንዳይሰጥ በመከልከል የተሳካላት ቢመስልም የኋላ ኋላ ነገሮች እየተቀየሩ መጥተዋል፡፡ የአውሮፓ ኅብረትም ሆነ የአሜሪካ መንግሥት፣ ተስፋ የጣለባቸው ተቃዋሚዎችና ‹‹አክቲቪስቶች›› ወደ እስር ቤት በመግባታቸው ተፅዕኖዋቸው እየቀጨጨ በመሄዱ የውጭ ኃይሎችም ተስፋ እየቆረጡ መጥተዋል፡፡ ወይዘሮዋም ‹‹አይዟችሁ›› ሲሉዋቸው የነበሩ አመራሮችን ከእስር አላዳኑዋቸውም፡፡ 
እንደ የፖለቲካ ተመራማሪዎች ትንተና፣ በአገሪቱ የተፈጠረው የፖለቲካ ቀውስና መንግሥት የሰጠው አሉታዊ ምላሽ፣ የአገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ጉዞን ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ምክንያት ቢሆንም፣ የውጭ ኃይሎች ግን ተስፋ የተጣለውን ያህል ተቃዋሚዎች የዲሞክራሲ ጉዞውንም የሚታደጉ አልነበሩም፡፡ ከውጭ ተፅዕኖ በአንጻራዊነት ነፃ መሆኑን የሚያምነው ኢሕአዴግም ሊቀመንበሩ አቶ መለስም፣ ክፍተቱን ተጠቅመው በኢትዮጵያ ላይ እጃቸውን የሰደዱ ኃይሎች በቀላሉ መቋቋም ችለዋል፡፡ 
የአና ጎሜዝ ድምዳሜና መዘዙ
የመለስ ዜናዊ አጠቃላይ ትንተና የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በ1997ቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ላይ ሐቀኛ ሪፖርት አላቀረበም የሚል ነው፡፡ በተለይ የምርጫ ታዛቢ ቡድኑን በመሩት ፖርቱጋላዊቷ አና ጎሜዝ ላይ ጠንከር ያለ ተቃውሞን ከመሰንዘር ባሻገር ዘለፋ አከል አነጋገሮችን ተጠቅመዋል፡፡ በኢትዮጵያን ሔራልድ ጋዜጣ ለመጀመርያ ጊዜ በስማቸው ባወጡት ጽሑፍ ቡድኑ በሪፖርቱ ያካተታቸው ጥሬ ሐቆች ያሉት ቢሆንም፣ ድምዳሜው ሁሉ መሠረታዊ ችግር ያለበት መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡ በሪፖርቱ በተካተቱ የምርጫ ጣቢያዎች ሁሉ ተስተዋሉ የተባሉትን ችግሮች በዝርዝር በማስታወስ ለችግሮቹ መንስዔ የሆኑትንና ሪፖርቱ በውል ያላጤናቸውን ነገሮች በመዘርዘር የሪፖርቱን ኢ-ሚዛናዊነት ያስቀምጣሉ፡፡ በተለይ በቡድን መሪዋ ላይ ካነሷቸው አበይት ነጥቦች መካከል ግለሰቧ የምርጫውን ሒደት ከመታዘብና ከመዘገብ ኃላፊነት አልፈው በድህረ ምርጫው በተነሱት ያለመግባባት ጥያቄዎች የመፍትሔ ሐሳብ ጠቋሚ ሆነው ቀርበዋል የሚል ነው፡፡ አና ጎሜዝ በሪፖርታቸው ምርጫው በተቃዋሚዎች አሸናፊነት መጠናቀቁን ገልጸው የተጋረጠውን አደጋ መመለስ የሚቻለው መንግሥትና ተቃዋሚዎች ወደ ጥምር መንግሥት የሚያመራቸውን የጋራ ስምምነት ማድረግ ሲችሉ እንደሆነ የሚገልጽ ንድፈ ሐሳብ ነበራቸው፡፡ 
በእነዚህና በሌሎችም ተጨማሪ ጉዳዮች የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹በሪፖርቱ ያልተካተተ ነገር ግን የሪፖርቱ ችግር ምንጭ›› ያሉት አና ጎሜዝን የሚሸነቁጡ ንግግሮችንና ዘለፋዎችን ሰንዝረዋል፡፡ በምላሻቸው ማጠናቀቂያ ላይ የቡድን መሪዋን የመፍትሔ ሐሳብ ላቅርብ ባይነትን በነገር ሲወጉ ‹‹የተከበሩት ወይዘሮዋ ከምርጫው ጋር ተያያዥነት የለውም ብለው እንጂ ዘንድሮ ስላገኘነው ጥሩ የዝናብ መጠንም አስተያየት መስጠት ይችሉ ነበር፤›› ሲሉ መልሰዋል፡፡ 
ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ምላሽ የብዙዎችን ቀልብ የሳበው በጽሑፋቸው መጨረሻ ያሰፈሩት፣ ‹‹What’s love got to do with it›› የታዋቂዋ አፍሪካ አሜሪካዊት ዘፋኝ ቲና ተርነር ዘፈን ወይዘሮዋን ሸንቆጥ ማድረጋቸው ነበር፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ጽሑፍ እስካሁን በወይዘሮዋ ላይ ያሳደረው ተፅዕኖ ከፍተኛ ይመስላል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ኅልፈት ያደረባቸውን ስሜት እስከመግለጽ ደርሰዋል፡፡ 
አና ጎሜዝ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ በእጅጉ መበሳጨታቸውን በመግለጽ ‹‹ከተቃዋሚዎች የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገልኝና ሌላ ሌላ አስመስለው ነው የገለጹኝ፡፡ በጣም ምርጥ ጭንቅላት ያለው ሰው ቢሆንም የሰው ሐሳብ የማምታታት ችሎታ የነበረው መሪ ነው፤›› ሲሉ ነው የገለጿቸው፡፡ 
ቪዛ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ማግኘታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መሞት ያገናኙት አና ጎሜዝ የብሔር ጉዳይም ማንሳታቸው በኢትየጵያ ስላዩት መሻሻል እንዲነግሩት ለጠየቃቸው አዲስ ስታንዳርድ መጽሔት፣ በሰጡት ምላሽ ‹‹አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሚናውን ለመጫወት ቀላል አይሆንም፡፡ በውስጣቸው የሥልጣን ሽኩቻ እንደነበርም አውቃለሁ፤ እሱ ከትግራይ አይደለማ፡፡ የተሰጠኝን ቪዛ ትልቅ ትርጉም እሰጠዋለሁ፤›› ብለዋል፡፡ 

Amnesty urges gov’t to free Eskinder Nega


December 5,2013.

Rights group launches a global appeal for the release of journalist sentenced to 18 years on terrorism charges.

(Al Jazeera) Rights group Amnesty International has issued a global appeal for the release from prison of an award-winning journalist in Ethiopia.

Amnesty on Wednesday said it was trying to raise awareness of the case of Eskinder Nega as part of a campaign called “Write for Rights.”

Eskinder, in prison since 2011, is serving an 18-year sentence on terrorism charges.

Amnesty says the journalist was a “thorn in the side of the Ethiopian authorities” for making speeches and writing articles critical of the government.

Eskinder’s wife, Serkalem Fasil, who was arrested with him but later released, and who now lives in the US, said her husband was arrested for being a journalist and for repeatedly criticising the government.

Ethiopian government spokesman, Shimelis Kemal, said Eskinder was not convicted for his criticism of the government but because he was running a clandestine ‘terrorist’ organisation.

According to the Committee to Protect Journalists, Ethiopia has the second highest number of journalists imprisoned in Africa and is the eighth biggest jailer of journalists in the world..

US urged to tighten message on human rights abuses

December 5, 2013

AFP – Human rights activists Wednesday urged the US government to be more consistent in its approach toward repressive regimes, warning that muddled responses sent the wrong message to democracy campaigners.
Deportation of Ethiopian Refugees from Norway
Torture and abuse at the hands of Ethiopian government officials…
America’s over-arching focus on security concerns and the fight against terrorism is obscuring the need to hold governments accountable for rights abuses, activists said at the start of a two-day seminar organized by the Washington-based group Human Rights First.
One delegate, Nadine Wahab, said US policy after the coup in Egypt, including a partial freeze in military aid which has halted delivery of large weapons systems but does not bar other arms, was part of the problem.
“When funding… continues to go to the weapons that attack and create human rights violations, like tear gas and bullets, but you hold the F-16s, the message that’s going to these governments and going to human rights defenders is that human rights is not important,” said Wahab, an expert with the Cairo Institute for Human Rights Studies.
Wahab also challenged the US administration’s policy of not cutting off all military aid to Egypt — a decision based on the need to ensure the army can fight militants in the Sinai peninsula and help maintain regional stability — after the ouster of Mohamed Morsi, Egypt’s first elected president, in July.
“One of the things that the United States really needs to do is look at its counter-terrorism narrative, look at how security is thought of within a domestic policy and an international policy and see whether security and stability is human rights? Or whether security and stability is guns and more weapons?” said Wahab.
UN special rapporteur on the rights to freedom of peaceful assembly, Maina Kiai, agreed saying the United States needed to treat all governments the same way.
“It’s very difficult to understand why the US government treats Ethiopia when it attacks human rights defenders differently from how the US treats Zimbabwe. Or how the US treats Egypt as opposed to Bahrain,” he said.
“Once you start seeing these differences they start sending a message across the world that actually the US wants to pick and choose where it wants to defend human rights.”
Ethiopia is one of the largest recipients of US aid in Africa, yet in 2009 it passed a law on non-government organizations which activists slammed as a bid by the government — in power for 21 years — to wipe out any civil society.
The legislation has largely passed without comment and US Secretary of State John Kerry made a high-profile visit to the country in May to attend an African Union summit.
The “US supporting a despotic government like the Ethiopian government is essentially creating destabilization in the Horn of Africa and Ethiopia,” warned Yalemzewd Bekele Mulat, an Ethiopian lawyer and activist.

የሳውዲ አረቢያው ቀውስ መከሰት ለኢትዮጵያውያን/ት ዲያስፖራ=በፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ

December 5, 2013 
የሳውዲ አረቢያው ቀውስ መከሰት ለኢትዮጵያውያን/ት ዲያስፖራ ፍቅርና አንድነት ትምህርት ሰጥቶ ይሆን? በአረብ አገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሠራተኞች ላይ የሚደረገው ህገወጥ የማሰቃየት እርምጃ በአስቸኳይ ይቁም! በአሁኑ ወቅት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ በሪያድና በአዲስ አበባ ከተሞች ባሉ ገዥ አካሎች እየተፈጸመ ያለው የሰብአዊ መብት እረገጣ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ ለጉዳዩ ልዩ የሆነ ትኩረት እንዲሰጡትና ለወገኖቻቸው የማያቋርጥ ድጋፍ እንዲያደርጉ ምቹ አጋጣሚን ፈጥሯል፡፡

ባለፉት በርካታ ሳምንታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ እየተፈጸመ ባለው አስደንጋጭ የሰብአዊ መብት እረገጣ የቪዲዮ ምስል መታየት መጀመሩን ተከትሎከአውስትራሊያ እስከ አሜሪካ ባሉ በአስር ሺዎች በሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ዲያስፖራ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ ቁጣ እና የልብ ስብራት በማስከተሉ ምክንያት በየአካባቢያቸው ባሉ የሳውዲ አረቢያ ቆንስላዎችና የዲፕሎማሲ ማዕከላት በሮች ላይ ፊት ለፊት በመሰለፍ በግንባር በመግጠም ባሳዩት ቆራጥ ኢትዮጵያዊ የተቃውሞ ወኔ የመብት ረጋጮችን የሳውዲ አረቢያ ገዥ ባለስልጣኖች በማሸማቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከ6 – 7 ሺ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን/ት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ከሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት የሳውዲ አረቢያ ገዥ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ እየፈጸመ ያለውን ህገወጥ እርምጃና የሰብአዊ መብት እረገጣ በአስቸኳይ እንዲያቆም በመጠየቅ በሳውዲ አረቢያ ከሚገኙ ወገኖቻቸው ጋር የማያቋርጥ ትብብርና ወገናዊ ድጋፍ እንደሚያደርጉ በአደባባይ በግልጽ አሳይተዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ከአትላንታ እስከ ሲያትል ከተሞች በመሰለፍ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡ ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ በአውሮፓ የተለያዩ ከተሞች በመውጣት ሰላማዊ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡

 የሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዎች በየደረሱባቸው ቦታዎች ሁሉ ባነሮችን በመያዝ ድምጻቸውን ከፍ በማድረግ “ሳውዲ አረቢያ ሃፍረተኛ! ሃፍረተኛ! ሃፍረተኛ! “ሳውዲ አረቢያ ሃፍረተኛ!” በማለት ተቃዎሟቸውን አሰምተዋል፡፡ በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ እየተደረገ ያለው የሰብአዊ መብት እረገጣና ህገወጥ አያያዝ በአስተማማኝ መረጃ ላይ ተደግፎ የቀረበ በመሆኑ ሊካድ የሚችል ጉዳይ አይሆንም፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች/Human Rights Watch እ.ኤ.አ ዴሴምበር 1/2013 ባወጣው ዘገባ መሰረት “የሳውዲ አረቢያ መንግስት በግዛት ክልሉ ውስጥ በሚኖሩ የውጭ አገር ሠራተኞች ላይ የኃይል እርምጃን በመውሰድ በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞችን የአካል ጉዳት ሰለባ እንዲሆኑ አደርጓል፣አንዳንዶችንም ገድሏል፣ ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉትን ኢትዮጵያውያን/ት ደግሞ ያለበቂ ምግብና መጠለያ አቅርቦት በጊዚያዊ የእስር ቤት ማዕከሎች አጉሮ ይገኛል“ በማለት በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያውያን/ት ዲያስፖራ ማህበረሰብ በወገኖቹ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በመመልከት በተግባር እያሳየ ያለውን ንዴትና ቁጣ ሶስት ዋና ዋና ነገሮች በትክክል ይገልጹታል፡፡ 1ኛ) የሳውዲ አረቢያ የመንገድ ላይ ዘራፊዎች እና የፖሊስ ሌቦች እንዲሁም ህገወጦች ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሠራተኛ ዜጎችን ከየቤታቸው በማስወጣት በየመንገዱ በመጎተት በቃላት ለመግለጽ በሚያስቸግር መልኩ ጭካኔና አረመኔነት በተመላበት ሁኔታ ሲደበድቡ፣ ሲዘርፉና ሲያስሩ በመታየታቸው፣ 2ኛ) የሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል የእራሱ ፖሊሶችና ሁከት ፈጣሪዎች በእብሪት ተነሳስተው በኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ ያለምንም ማቋረጥ ጥቃት ሲሰነዝሩ እያየ ምንም ነገር ሳያደርግ በማንአለብኝነት መመልከቱ፣ 3ኛ) በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ከመሰሉ ገዥ የሳወዲ አረቢያ አካል ጋር በመሞዳሞድ የገንዘብ እርዳታ ስለሚያገኝ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ደካማነትና የእግር ላሽነት ባህሪ በግልጽና በዓለም የአደባባይ መድረክ ላይ በማሳየት ላይ በመገኘቱ የሚሉት ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ እና በአትዮጵያ ያለው ገዥ አካል በስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ በሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል እየደረሰ ባለው የሰብአዊ መብት እረገጣና ህገወጥ አያያዝ ሁለት የማይገናኙና ተጻራሪ የሆኑ ምላሾን ሲያንጸባርቁ ይታያሉ፡፡ በአንድ በኩል በውጭ አገር ያለው የዲያስፖራ ማህበረሰብ በሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ስደተኛ ሠራተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ እየደረሰ ባለው መከራ እና ስቃይ ከወገኖቹ ጎን በጽናት ሲቆም በተጻራሪው ገዥው በአዲስ አበባ የሚገኘው አካል ደግሞ ጠንከር ያለ መግለጫ ከማውጣት ወደኋላ ያፈገፍጋል፣ እንደ አሉሚኒየም ብረት ወደኋላ ይለመጣል፣ የሳውዲን ገዥ አካልን ጫማ ለመላስ ወደ ተረከዙ ያጎነብሳል፣ እንዲሁም አምባገነኑን አረብ ይቅርታ ይጠይቃል፡፡ በአጭሩ ሎሌነቱን በይፋ አሳይቷል!፡፡ ከወባ ትንኝ ተመራማሪነት በፍጥነት ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት የተሸሙትና እ.ኤ.አ ከ2015 አገራዊ “ምርጫ” በኋላ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ ይጠቀልላሉ ተብለው የሚጠበቁት ቴዎድሮስ አድሃኖም የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣኖችን ውሳኔ እና ህገወጥ ስደተኞችን የማባረር ፖሊሲያቸውን ኢትዮጵያ እንደምታከብር በድፍረት ለብዙሃን መገናኛ ይፋ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ በተደረገው የዜጎች ህገወጥ አያያዝ ስሜታቸው የተጎዳ መሆኑን ለሳውዲ አረቢያው አምባሳደር በቀልድ መልክ ገልጸው ይደልዎ ብለዋል፡፡ በዲፕሎማሲያዊ በእራስ መተማመን መልክ አድሃኖም “ይህ ተቀባይነት የለውም” ብለዋል፡፡

እርሳቸውና ገዥው አካል ነገሮችን ሁሉ በቁጥጥራቸው ስር እንዳደረጉ በሚመስል መልኩ አድሃኖም “ዜጎቻችንን ለመቀበል ሙሉ በሙሉ ዝግጅታችንን ያጠናቀቅን መሆናችንን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ“ በማለት የምጸት ጩኸት አሰምተዋል፡፡ ማዘናቸውን የገለጹበት ሁኔታ ከልብ ያልሆነ፣ ለታይታ እና ለይስሙላ የተደረገ፣ የባለስልጣንነት ሞገስ የሌለውና እርባናየለሽ ነበር፡፡ እንዴት አንድ በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ የተቀመጠ ባለስልጣን የእራሱን ዜጎች ለሚያዋርድ የሌላ አገር ፖሊሲ “ክብር” ይሰጣል? እንዴት አንድ ሰው የአንድን በባዕድ አገር የሚኖሩ ወንድሞችና እህቶች አስገድዶ የሚድፍር፣ የሚገድል፣ ሰውነትን የሚበጣጥስ፣ የሚያሰቃይና ተጠርጣሪ ነው በማለት ያለፍርድ የሚገድል ኃይል በእራሱ አስተሳሰብ በመመራት “ተቀባይነት የለውም” የሚለውን ትርጉምየለሽ የዲፖሎማሲ ቃል ይመርጣል? እንዴት አንድ ሰው በትክክለኛው የዲፕሎማሲያዊ ንዴትና ቁጣ ኖሮት በህጋዊ መንገድ ጉዳዩን ለመከታተል ሳይሞክር “ስሜቴ ተጎድቷል” እንዲሁም “አዝኛለሁ” ሊል ይችላል? ስዕል የአንድ ሺ ቃላትን ያህል የመናገር ኃይል ያለው መሆኑ ሀቅ ነው፡፡ የሳውዲ አረቢያዎች የሰብአዊ መብት እረገጣ የቪዲዮ ምስሎች የዲያስፖራውን ቁጣ የመቀስቀስ ኃይል ነበራቸው፡፡

 በቀላሉ ሊታይ የማይገባው እውነታ በሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል በኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች ላይ የተፈጸመው አሳንሶ የማየት፣ የማዋረድ፣ ማሰቃየትና ሰብአዊ መብትን መርገጥ በተመሳሳይ መልኩ በተራው ኢትዮጵያውያን/ት ላይ በኢትዮጵያው ገዥ አካል ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሲፈጸም ቆይቷል፡፡ የአድሃኖም ገዥው አካል ነጻውን ፕሬስ በማሽመድመድ ተንሰራፍቶ የሚገኘውን የሰብአዊ መብት እረገጣ ከህዝብ ዕይታ ለመደበቅ ያደረገው ጥረት በአብዛኛው ስኬታማ ቢሆንም ሁሉንም ደብቆ ለማስቀረት ግን አልተቻለውም፡፡ ብዙ አስደንጋጭ የፎቶግራፍ ምስሎች በማስረጃነት ቀርበዋል፣ እነዚህም የፎቶግራፍ ምስሎች የሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ከፈጸመው የሰብአዊ መብት እረገጣ የበለጠ የኢትዮጵያ ገዥ አካል በተራ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች ላይ የፈጸመው አስደንጋጭ የሰብአዊ መብት እረገጣ ፎቶግራፍ የበለጠ አስደንጋጭ ነው፡፡ በሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል በኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ በኖቬምበር 2013 የተፈጸመው የሰብአዊ መብት እረገጣ በኢትዮጵያ ገዥው አካል በተራ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ በኦክቶበር 2013፣ በኖቬምበር 2012፣ በዴሴምበር 2011፣ ወዘተ በተመሳሳይ መልኩ ተፈጽሟል፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ገዥው አካል እስረኞችን ከህግ አግባብ ውጭ አስገድዶ የእምነት ቃል እንዲሰጡ ያደረገውን ሂዩማን ራይትስ ዎች በዘገባው “በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ማዕከላዊ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት እስረኞች በማያቋርጥ ሁኔታ በጥፊ ይጠናገራሉ፣ በእርግጫ ይደበደባሉ፣ በቦክስ ይነረታሉ፣ በዱላና በጠብመንጃ ሰደፍ ይደበደባሉ፡፡ ጥቂቶቹ በሚያሰቃይ ሁኔታ እጆቻቸውን ከኩማዎቻቸው ላይ በማንጠልጠል፣ ወይም ደግሞ እጆቻቸውን ከጭንቅላታቸው በላይ ከፍ አድርገው በማቆም ማሰርና ለብዙ ጊዜ እየተደበደቡ እንዲቆዩ ማድረግ“ አካቶ አቅርቦታል፡፡ ዋናው ከክስተቱ የተማርኩበት አጋጣሚ፣ የነቃና የተበሳጨ ህዝብን መመልከት፣ እውነት ለመናገር ለእኔ አሁን ባለው የሳውዲ አረቢያ ሁኔታ ዋናው “የተማርኩበት አጋጣሚ” ብዬ የምወስደው አብዛኛው የዲያስፖራ ማህበረሰብ በዚህች አጭር ጊዜ ውስጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሰባስቦ ተቃውሞውን በመግለጽ እረገድ ውጤታማ መሆኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ በዚህ አይነት ቀልጣፋ በሆነ መልክ፣ ኃይልና አስደናቂ ፍላጎት ስልታዊ በሆነ መልክ ዓለም አቀፍ የቁጣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ አይችልም የሚለውን የቀድሞ እምነቴን እንድሰርዝ አድርጎኛል፡፡ በእርግጠኝነት ለመናገር ይህ ድርጊት ለእኔ “ይበል” የሚያሰኝ ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ አይቻለሁ፣ ከተለመዱት የመብት ተሟጋቾች በስተቀር አብዛኛው ለእኔ ዝምተኛ ብቻ ሳይሆን የተኛም ጭምር መስሎ ይታየኝ ነበር፡፡ ነገር ግን እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2013 በሚያስደንቅ ሁኔታ ግዙፉን የኢትዮጵያን ዲያስፖራ በንቃት ሲሳተፍ ተመልክቻለሁ፡፡ ወንዶች ሴቶች፣ ወጣቶችና አዛውንቶች በሳውዲ አረቢያ በወንድሞቻቸውና በእህቶቻቸው ላይ የሚፈጸመውን ስቃይና የሰብአዊ መብት ጥሰት በመቃወም በመቶዎችና በሺዎች በመሆን እየወጡ ከጎናቸው ተሰልፈዋል፡፡ ይህን ግዙፍ ዲያስፖራ እንዲነቃ ያደረገው ምንድን ነው? እርግጠኛ አይደለሁም፡፡

በአሁኑ ጊዜ ትልቁ ስጋቴ በሳውዲ ያለው ቀውስ ካበቃ በኋላ ይህ ግዙፍ የዲያስፖራ ማህበረሰብ ተመልሶ ይተኛ ይሆን የሚለው ነው፡፡ የሁላችንም ትምህርታዊ አጋጣሚዎች፣ የኢትዮጵያ ስደተኛ ሰራተኛ በሳውዲ አረቢያ ገዥ አካል በደርሰባቸው የሰብአዊ መብት እረገጣና ማሰቃየት የኢትዮጵያ ገዥው አካል ጆሮ ዳባ ልበስ ማለቱ ልዩ የሆኑ ትምህርታዊ አጋጣሚዎችን በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ሰጥቷል የሚል እምነት አለኝ፡፡ “ትምህርታዊ አጋጣሚ” የሚለውን ሀረግ ለብዙሀን ትምህርት፣ ለህዝቦች መነሳሳትና ለግለሰቦች በንቃት መሳተፍን ሊያመጣ የሚያስችል በታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ዋጋ ያለው ልዩ ድርጊት በማለት ተርጉሜዋለሁ፡፡ ከዚህ በመቀጠል የሚቀርቡትን ጥቂት የማስተማሪያ እና የመማሪያ ትምህርቶች የትርጉም ቅርጽ ከግንዛቤ በማስገባት ማስተላለፍ የምፈልገው ዋናው መልዕክት ቀውስ በደረሰ ጊዜ ብቻ የሚወረወር ምላሽ ነጻነትን፣ ዴሞክራሲን ለመጎናፀፍ እና በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብትን ለማስከበር ስኬታማ እና ለድል የሚያበቃ ስሌት አይደለም፡፡ በሳውዲ አረቢያ እንደደረሰው ቀውስ ሁሉ በሌሎችም ትክክል ናቸው ብለን በምናምንባቸው ጉዳዮች ሁሉ ልዩ የሆነ ዓለምአቃፋዊ ትብብር፣ ወንድማማችነት፣ እህትማማችነት እና መነሳሳትን በተረጋጋ ሁኔታ ማንጸባረቅ ይጠበቅብናል፡፡ በሳወዲ አረቢያ ቀውስ ምክንያት የታየውን የመነሳሳት “አዚም” ደግመንና ደጋግመን ማሳየት ይኖርብናል፡፡ ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን/ት በቋሚነት ለሰብአዊ መብት መከበር መሟገትና መንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡ በኢትዮጵያውያን/ት ዲያስፖራ መነጽር መመልከት፣ ተራ ንግግር እራሳችንን ከስሜታዊነት፣ ግንፍልተኝነት እና ከቀውስ ለመውጣትና የእራሳችንን እጣ ፈንታ እራሳችን ወሳኝ እንድንሆን ሰላማዊ ሽግግር ለማድረግ “የኢትዮጵያ ዲያስፖራ መስታወት” ምናባዊ ቅርጽ የሚል ላስተዋውቅ፡፡ የነቃውን ግዙፍ የዲያስፖራ ማህበረሰብ ለዘለቄታው እንደነቃ ለዘላለሙ ጠንቃቃ ተመልካች ሆኖ አንዲቀጥል ልዩ ስትራቴጂ መንደፍ ያስፈልጋል፡፡ በኢትዮጵያ ዲያስፖራ ያሉ ችግሮችና ጉዳዮች ምን ምን እንደሆኑ እናውቃለን፣ ጥቂቶች በጣም ቀላል ነገሮች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ መፍትሄ ለማግኘት የበለጠ አስቸጋሪዎች ናቸው፡፡ በግልጽ በመተማመን እና በመወያየት ችግሮችን ካልፈታናቸው በስተቀር ታላቁን የነቃ የዲያስፖራ እንቅስቃሴ ወደኋላ በመመለስ እንዲተኛ ማድረግ ያስችላሉ፡፡ ከአንድ ቀውስ ወደሌላ ቀውስ መሸጋገር እኔ በበኩሌ ያመኛል፣ ይደክመኛልም፡፡ የዲያስፖራው ማህበረሰብ እርስ በእርስ እንዲዋደድ፣እንዲደራጅ፣ እንዲታደስ እና ለውጤት እንዲንቀሳቀስ ማድረግ አለብን፡፡ ከእራሳችን እና ከእያንዳንዳችን ጋር ንግግሮች ያስፈልጉናል፡፡ “በኢትዮጵያ ዲያስፖራ መስታወት” እመለከታለሁ፡፡ ንግግር ለማድረግ መስታወቱን ከግድግዳው ጋር እሰቅለዋለሁ፡፡ እኔን ወደኋል ይመለከተኝ እና እንዲህ ይላል፣ ሁላችሁም ማድረግ ትጀምራላችሁ ነገር ግን አትጨርሱትም፡፡ መስታወቱ እንዲህ በማለት ያስታውሰናል፣ “በቅርቡ በህይወት የተለዩት የኢትዮጵያ ገዥ አካል መሪ እንዲህ ብለው ነበር ’የአትዮጵያ ዲያስፖራዎች ብዙ ነገሮችን ይጀምራሉ፣ የጀመሩትን ግን በፍጹም አይጨርሱትም፣ ታዲያ ስህተት ተናግረዋልን?’” ጥያቄውን ላለመመለስ ቃላትን ለመፈለግ እሞክራለሁ፡፡ “እውነት ለመናገር ብዙ ብዙ ነገሮችን እንጀምራለን፣ ነገር ግን በጣም ጥቂቶችን ብቻ ለውጤት እናበቃለን፣ ከእኔ የግል ተሞክሮ ማስረጃ ማቅረብ እችላለሁ፣ እ.ኤ.አ ከ2005 ጀምሮ የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት አጠባበቅ ትግል በንቃት ስቀላቀል ያየኋቸው፣ የሰማኋቸው፣ በአንድ ወይም በሌላ መልኩ የተሳተፍኩባቸው፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ ወይም የአድቮኬሲ ቡድኖች፣ ግብረ ኃይሎች፣ ኮንፈረንሶች፣ ፎረሞች፣ የምክክርና የውይይት ቡድኖች፣ ቴሌኮንፈረንሶችና የግል ስብሰባዎች፣ ወርክሾፖች፣ ስምምነቶች፣ የአካዳሚክ ሴሚናሮች እና ሲምፖዜሞች ናቸው፡፡ ከእነዚህ ሁሉ አንዱም ፍሬ አፍርቷል ብየ ለመናገር አልደፍርም“:: ወዲያዉኑ እራሴን በፍጥነት አርማለሁ፡፡ “አንድን ነገር በግማሽ አሳክተናል፣ በአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ኤችአር/HR 23ን ማን ይረሳዋል (ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እና ተጠያቂነት ድንጋጌ)፣ አዎ! ያ ታላቅ ትምህርታዊ አጋጣሚ ነበር፡፡ ያ የህግ ሰነድ በቅርቡ በህይወት ለተለዩት ጠቅላይ ሚኒስትር የእራስ ምታት፣ የልብ ስብራት፣ የሆድ ቁርጠት፣ የጀርባ ውጋት፣ የጥርስ ቁርጥማት እና የጆሮ ህመም ሆኖባቸው ነበር! ኤችአር 2003 የተለያየ አመለካከት የነበራቸውን የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ወደ አንድ እንዲመጡና ተቀራርበው ዓላማቸውን በጋራ እንዲያሳኩ ለማድረግ አስችሎ ነበር:: መስታወቱ አቁአረጠኝ፡ “እንዲህ ነው እንጂ! ሁላችሁም አንድ ሁሉን አቀፍ የሆነ ጠንካራ መሰረት ያለው የሰብአዊ መብት ተሟጋች የዲያስፖራ ማህበረሰብ ድርጅት ማቋቋም ትችላላችሁ፡፡ ከሁሉም በላይ ለማሰቃየት፣ ከህግ ውጭ ለሚፈጸም ግድያ፣ በዘፈቀደ በቁጥጥር ስር ማዋል እና እስራቶች፣ ድብደባዎች እና ለምርጫ ድምጽ ስርቆት የተለየ ትኩረት በመስጠት የማያምን ማን አለ?” ግልጽ የሆነውን መልስ ላለመስጠት ወሰንኩ፡፡ አንድ ነገር ስንጀምር ወደ ስኬታማነት ልናመጣው ይገባል ወይም ደግሞ የፈለገውን ጊዜ ቢውስድም እየሞከርነው መቀጠል ይኖርብናል፡፡ ሁልጊዜ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ሁላችሁም አንድን ነገር ለመቃወም በንዴት በስሜታዊነት ትነሳላችሁ፡፡መስታወቱ እንዲህ ሲል ይጠይቃል፣ “በኢትየጵያ ያለው ታማኝነት የጎደለው ገዥው አካል አንድ ነገር ሲያደርግ ወይም ሳያደርግ ሲቀር ሁላችሁም ሁልጊዜ በንዴትና በስሜታዊነት ምላሽ ለመስጠት የምትሞክሩት ለምንድን ነው?“ በፍጥነት የሳውዲ አረቢያን ሁኔታ ሃሳብ መጣብኝ፡፡ “ስሜታዊነት መሆን ምንም ስህተት የለበትም፡፡ ሰው መሆንና ስሜታዊ አለመሆን ማለት ሮቦት መሆን ማለት ነው፡፡ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በሳውዲ አረቢያ ከሰው በወረደ መልክ ግፍ ሲፈጸምባቸው እያየን እና እየሰማን ለምንድን ነው የማንናደደውና ከቁጥጥር ውጭ የማንሆነው?“ መስታወቱ በጥንቃቄ መጠየቁን ይቀጥላል፣ “ከተነፈስክ በሁላ ንዴት ሲበርድልህ የሚተርፍህ ምንድን ነው? ተስፋ መቁረጥ፣ በጣም ስሜታዊ መሆን፣ ማዘን? ኃይል የለሽነት፣ ተስፋቢስነት፣ ምንም ነገር ያለማድረግ ሁኔታ ውስጥ ልትገባ ትችላለህን? ወይም ደግሞ እንደገና ለመደራጀትና ወሳኝ እርምጃ ለመውሰድ ያለ የሌለ የፈጠራ ኃይልህን ትጠቀማለህ? እራሴን በመነቅነቅ ሀሳቤን አንጸባርቃለሁ፡፡ “ምንጊዜም ቢሆን ንዴት በመጨረሻው ተፈጻሚነት እንዳይኖርና ሽባ ሆኖ ያስቀራል፡፡ በምንናደድበት ጊዜ የምናባክነው ኃይል ወደ ረዥሙና ቀጣይነት ስላለው የአድቮኬሲ እና ድርጊት በአወንታዊነት ማዋል አለብን::” ንዴታችን ለምክንያታዊነት፣ በስሌትና በጥቅል ታስቦበት ለሚሰራ ተግባር መንገድ መስጠት አለበት፡፡ ሁልጊዜ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ሁላችሁም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ቀውሶችን የመቃወም ዝንባሌ ታሳያላችሁ፣ ነገር ግን ከእነዚህ ያላነሰ ጠቀሜታ ላላቸው ሆኖም ግን ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑትን ችላ ትላላችሁ:: መስታወቱ እንዲህ ይላል፣ “ባለፈው ዓመት በርካታ አስደንጋጭ ቀውሶች በግልጽ ለመውጣታቸው ምስክር ናችሁ፡፡ በኢትዮጵያ ገዥ አካል በሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት ላይ ሰብአዊ መብት መርገጥና ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲፈጸምባቸው ነበር፡፡ ጥንታዊውንና የተከበረውን የኢትዮጵያን የኃይማኖት መሬት የዋልድባን ገዳም ዓይን ባወጣ መልኩ ገዥው አካል ለውጭ የሸንኮራ አገዳ አልሚዎች ማስረከቡ ይታወሳል:: በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን ከሚኖሩበት አካባቢ በኃይል በማፈናቀል የዘር ማጽዳት ዘመቻ መፈጸሙ ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው::” መስታወቱ ቀጥሏል፣ “በርካታ ዝቅተኛ ገጽታ ያላቸው ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ የአውዳሚነት ባህሪ ያላቸው እየተከናወኑ ያሉ ቀውሶች አሉ፣ የገዥው አካል “የሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ እድገት” ማስመዝገብ ፕሮፓጋንዳ ቢኖርም በአሁኑ ጊዜ ወደ አስር ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን/ት በረሀብና ቸነፈር የህይወት አጣብቂኝ መካከል ወድቀዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ1970ዎቹና በመጀመሪያዎቹ 1980ዎቹ እንደነበሩት ዓመታት ዓይነት ረሀብ የማይታየው በዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታ ምክንያት ነው፡፡ በጎረቤት አገሮች እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ስደተኛ ኢትዮያውያን/ት ቁጥር በየዓመቱ በመቶዎችና በሺዎች እየጨመር በመሄድ ላይ ይገኛል፣ በትምህርትና በጤናው ዘርፍ ቀውሶች ይታያሉ፡፡ የሙስና ቀውስ እና ሌሎችም ይገኛሉ፡፡ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ጥራት ደካማ መሆን እና የአገልግሎቱ እጥረትም ይታያል፣ ይህም በወጣቶች ስብዕና ላይ ትልቅ የሰብአዊ መብት እረገጣ ተብሎ ሊመደብ ይችላል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች በተሳሳተ አስተዳደር እየተመሩ ነው፣ የፖለቲካ ተቋማት እየሆኑና የገዥው ፓርቲ ታማኞች የሙስና ስልጠና አካባቢዎች እየተደረጉ ነው::

” በገፍ መቃወም ያለብን ትልቅ ገጽታ ያላቸውን ቀውሶች ብቻ ሳይሆን ትንሽ ገጽታ ያላቸውን ጭምርም መሆን አለበት፡፡ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ሁላችሁም በሚባል መልኩ ሁልጊዜ ደካማ የመከላከል ጨዋታ ታደርጋላችሁ::መስታወቱ እንዲህ ይገልጻል፣ “በዲያስፖራው ያላችሁ ሁላችሁም መንግስት የሚሰራውን ሁልጊዜ ትቃወማላችሁ፣ የማይሰራውን ግን በጣም ጥቂት ብቻ ትይዛላችሁ:: በቅርቡ በህይወት የተለዩት የገዥው አካል መሪ ይህንን ደካማ ጎን እንደ በሰይፍነት የመጠቀም ጉብዝና ነበራቸው:: እና እናንተ በሙሉ ለአገራችሁ እርባና ያለው ነገር ስትሰሩ አትታዩም፣ እሳቸው የህዝብን የትኩረት አቅጣጫ ለማስቀየር ሲሉ አንድ አስደንጋጭ የሆነ ነገር ሲያደርጉ ወይም ሲናገሩ እናንተ ለዚያ ምላሽ ለመስጠት ስትሽከረከሩ ትወጡ ትወርዱ ነበር፣ ይህንም አይተው በዚያ ጭራቃዊ ፈገግታቸው ይመለከቱ ነበር::” ለመስታወቱ እንዲህ በማለት ለመግለጽ እሞክራለሁ፣ “እኒያ ሰው ጨካኝ በመሆናቸው ጎበዝ ነበሩ፣ እሳቸው ዋና የነገር አጧዥ፣ የተንኮል ንድፍ አውጭ፣ ታማኝነት የሚጎድላቸው እና የብልጥነት ሴራ የሚሰሩ ነበሩ፡፡ ምርጫ አልነበረንም::” መስታወቱ ይሄን አስተያየት ችላ አለው:: “አሁንም የእርሳቸው ጋሻጃግሬዎች በእርሳቸው ፈለግ እንደዚያው እንደተለመደው የማይረባ ድርጊታቸውን እንዲቀጥሉ ትፈቅዳለህ?“ እኔ መልስ የለኝም፣ ጥያቄው እንዳልሰማ ለማስመሰል እሞክራለሁ፣ ለእራሴ ቀስ ብየ እናገራለሁ፣ “ምንም ዓይነት ቡድን ጠንካራ የመከላከያ መስመር ሳይኖረው ለድል አይበቃም“:: ጠንካራ የዲያስፖራ ቡድኖችን መፍጠርና ጠንካራ የመከላከል ጨዋዎችን ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ሁላችሁም ትኩረት ይጎድላችኋል፣ መስታወቱ እንዲህ ይላል፣”ሁላችሁም ከአንድ ጉዳይ ወደ ሌላ ዝውውር ለማድረግ ትኩረትና ተስፋ ይጎድላችኋል፣ የቀውስ ሁኔታዎችን በንዴት ምላሽ ለመስጠት ስትሞክሩ ይህ ሁኔታ ደግሞ በጣም ረዥም በሆነ ምንም ነገር ያለመስራት ወሰንተኛ የሆነ ቸልተኝነት ያስከተላል::” እራሴን እጠይቃለሁ፣ “ያ የሚሆነው ለምንድን ነው?“ ድርጅትና አመራር ሳይኖር አንድ ጉዳይ ላይ ትኩረት ማድረግ አስቸጋሪ ሊሆን ይችላልን? ለምንድን ነው ግልጽና ጠንካራ የአድቮኬሲና የድርጊት አጀንዳ የማይኖረን?” ለመስታወቱ እነግረዋለሁ፣ “ትኩረት ያጥረናል ምክንያቱም ግልጽ ራዕይ የለንም፣ ራዕይ ያጥረናል ምክንያቱም ቁርጠኝነት ያጥረናል፣ ቁርጠኝነት ያጥረናል ምክንያቱም በእራሳችን በራስ መተማመን እና በክርክር ጭብጦቻችን ላይ እምነት ያጥረናል፡፡“ እዚህ ላይ የአፍሪካን የጥንት አባባል በመዋስ፣ “ወደየት እንደምትሄድ ካላወቅህ ማንኛውም መንገድ እዚያ ያደርስሀል፡፡“ አብዛኞቻችሁ ቆሞ ተመልካች ናችሁ፣ መስታወቱ እንዲህ ይላል፣ “አብዛኞቻችሁ ከጎዳና ዳር ቆሞ ማየትን ትመርጣላችሁ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከጎን ሆነው ትችት መሰንዘርን ይመርጣሉ፡፡“ አቋረጥኩ፡፡ “ዋናው ዘዴ የተመልካቾችን ምዕናብ ለማጎልበት፣ ለእነሱ ተስፋ ለመስጠትና ለማጠናከር፣ እውቀት እና በሰብአዊ መብት ጥበቃ ላይ በእራስ የመተማመን ጠቀሜታ ለማጎልበት ነው፣ በዚህም መሰረት ከተመልካችነት ወደ ሰብአዊ መብት ተሟጋችነት ይቀየራሉ፡፡“

 መስታወቱ ስሜትን እንዲህ በማለት ያነሳሳል፣ “ሰብአዊ መብት የተመልካች እስፖርት አይደለም፣ ሰብአዊ መብት የቡድን ስራ ነው፡፡ እያንዳንዱ ሰው በሜዳው ውስጥ ነው፣ እያንዳንዱ ሰው የሚጫወተው ድርሻ ይኖረዋል እና ትልቅ ግብ ማስመዝገብ ይኖርበታል፡፡“ ከታች ጀምረን ማነሳሳትና ማንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡ እናንተ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት በሙሉ የሲቪክ ማህበረሰብ የድርጊት ዘመቻ መመስረት አለባችሁ፣ መስታወቱ እንዲህ በአንክሮ ያስጠነቅቃል፣ “እናንተ ሁላችሁም ለድል የሚያበቃችሁን መንገድ በመከተል በተለየ ሁኔታ ለመስራት፣ ቅድሚያ ዝግጅት በማድረግ ለመስራት፣ ከስሜታዊነት ነጻ ሆኖ ለመስራት መብቃት አለባችሁ፡፡“ እናንተ ሁላችሁንም ማስተማር፣ ማንቀሳቀስ፣ ማደራጀትና ማጠናከር የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ለጋራ ጥረት ማብቃት አለባችሁ፡፡ እናንተ ሁላችሁም የሰቪክ ማህበረሰቡ ጋር በመሆን ዘመቻውን በቀልጣፋነት ማካሄድ አለባችሁ፣ ለሲቪክ ማህበረሰቡ እንቅስቃሴ ህበረተሰቡን በኮሚቴ፣ በጎ ፈቃደኞችን በመመልመል፣ ለወርክሾፖች አመራር በመስጠት፣ ከታች ጀምሮ ያለውን እያንዳንዱን ዜጋ ለማጠናከር እና በንቃት ለማሳተፍ በቴሌቪዥንና ሬዲ ፕሮግራሞች ላይ ትኩረት በመስጠት መስራት ያስፈልጋል፡፡ የሲቪክ ማህበረሰቡ ከታች ጀምሮ በሙሉ እንዲሳተፍ! እናንተ ሁላችሁም በሌሎች ላይ ስድቦችን በመወርወር ጊዜ ማባከን፣ መስታወቱ እንዲህ ይላል፣ “እናንተ ሁላችሁም ገዥውን አካል በማውገዝ እና ዘለፋዎችን በመወርወር ብዙውን ጊዚያችሁን በከንቱ ታባክናላችሁ፣ ሁላችሁም አታገኙትም፣ የዱሮ አባባል በመዋስ፣ ’ከአሳማ ጋር (ወይም ከሌባ) ከጭቃ ውስጥ ትግል አትግጠም‘ አሳማው (ወይም ሌባው) ሲደሰት አንተ ቆሻሻ ትሆናለህ:: ወሮ በላን በጭቃ ጅራፍ በዝልፍያ መስተካከል አይቻልም::” ምላሽ ለመስጠት ፈጠንኩ፡፡ “አንድ ሰው አካፋን አካፋ ማለት አለበት፡፡

“ መስታወቱ እንዲህ በማለት ምክር ይለግሳል፣ “ስለዚህ አንዴ ጥራው እና ተንቀሳቀሱ፣ አስታውስ! ወደ ዴሞክራሲ ወይም ወደ ነጻነት በስድብ አትደርስም፡፡”” መስማማቴን ለመገልጽ እራሴን ነቀነቅሁ፡፡ “የእውነት ወንጭፎችን እና ቀስቶችን ታጥቀን መዋጋት አለብን፣ በእውነት ጋሻዎች መመከት አለብን፣ ከመብት እረጋጭ ኃይሎች ነጻ ሆነን በነጻነት ለመናገር፣ ለመዘመር፣ ትልቁን ጉዞ መጓዝ አለብን፡፡“ እውነትን ተናገር እንጅ የሰብአዊ መብት እረጋጭ ኃይሎችን አትሳደብ፡፡ እናንተ ሁላችሁም በክፍል ውስጥ ላለው ዝሆን ትኩረት ስጡ፣ መስታወቱ እንዲህ ይላል፣ “እነሱን ለመረዳት ሳይሆን በሌሎች ሰዎች ጫማዎች ለመጓዝ ሞክር (ምክንያቱም“እነሱን ለመረዳት መሞከር ጊዜ ማጥፋት ነው) ነገር ግን የእነርሱን ፍርሃት ለመረዳት እና የድብቅ እንባ ማፍሰስ ለመገንዘብ ሞክር፣ እነሱ አደጋዎች ጭካኔ የተሞላባቸው እና ህሊና የሌላቸው ናቸው፣ ነገር ግን ፍርሃት አልባዎች አይደሉም፡፡ በፍርሃት ይኖራሉ፣ ነገር ግን መሰረተቢስ ፍርሃቶች አይደሉም፣ የእነርሱ ፍርሃት በጫካው ውስጥ በማታ አያነደደ እንደሚያበራው ነብር ሁሉ ተመሳሳይ ናቸው፡፡” ይላል ዊሊያም ብሌክ፡፡ “የቸርቺል ኬኔዲ የፍርሃት ተቃርኖ’ በሚሉት ወጥመድ ተይዘዋል፣ አምባገነኖች ደፍረው ወጥተውው በማይጋልቧቸው ነብሮች ከወዲያ ወዲህ ይላሉ፣ እና ነብሮቹ ተርበዋል”፣ ቸርችል ያስጠነቅቃሉ፡፡ ፕሬዚዳንት ጆን ኬኔዲ ለማስታወስ “በጥንት ጊዜ በሞኝነት በነብሮች ጀርባ ላይ በመቀመጥ ኃይልን ለማግኘት ይፈልጉ የነበሩ አምባገነኖች በነብሮቹ ሆድ ውስጥ ገብተዋል፣ በሌላ አባባል “በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ የሚከለክሉ እነሱ በአመጽ መወገዳቸው የማይቀር ነው፡፡“ መስታወቱ ቀጠለ፣ “አምባገነኖች እርግጠኛ እና እብሪተኛ ይመስላሉ፣ ነገር ግን ይህ ሁሉን አቀፍ የሆነ ፍርሃታቸውን ለመሸፈን ሲሉ የሚያደርጉትና ከዕለታት በአንዱ ቀን እነርሱ ከታች ለወደቁ ጭቁኖች እነርሱ በፈጠሩት ገሀነም አነርሱ ስልጣናቸውን በኃይል ተነጥቀው ወደ መቀመቅ መውረዳቸው የማይቀር ነው፡፡“ መስታወቱን እጠይቀዋለሁ፣ “አምባገነኖች ቀን በቀን ይኖራሉ ብለህ መናገር ትችላለህ? ነገ ድረስ ለመቆየት አምባገነኖች ዛሬ ሁሉን ነገር ያደርጋሉ፣ ነገ ከነገ ወዲያም እና ከዚያ ወዲያም ቀን በቀን ነው የሚኖሩት?“ መስታወቱ እንዲህ ያስተካክለዋል፣ “በፍጹም፡፡ አምባገነኖች ሰዓት በሰዓት፣ ደቂቃ በደቂቃ፣ ሰከንድ በሰከንድ በፍርሃት ተውጠው ነው የሚኖሩት፣“ የተራቡ ነብሮች? የነቁ ግዙፎች ነብሮች! እናንተ ሁላችሁም ብቻችሁን ልትሰሩት አትችሉም፣ ከመሄድህ በፊት የመጨረሻዋን ቃል መስታወቱ እንዲህ ይናገራል፣ “እናንተ ሁላችሁም ብቻችሁን ልትሰሩት አትችሉም፣ እናንተ ሁላችሁም ጓደኞች መፈለግና ከእነርሱ ጋር ተባብራችሁ በጋራ ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡” ማሰብ ጀመርኩ፣ “ስንቶቻችን ነን ለእኛ ምርጥ ጓደኞች ጓደኞች የሆን? ስንቶቻችን ነን የሂዩማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ዘላለማዊ መጠበቂያ አባል የሆንነው? ስንቶቻችን ነን የሲ ፒ ጄ የጋዜጠኞች ተከራካሪ ድርጅት መብራቱን በቃሊቲ እስር ቤት ላይ በማነጣጠር እነ አስክንድር ነጋ፣ ውብእሸት ታየ እና ሌሎች በህገወጥ መንገድ ታስረው ለሚገኙት አባል የሆንነው? ብቻችንን ልንሰራው የምንችለው ጉዳይ አይደለም፡፡

ስንቶቻችን ነን ባህላዊውን የህብረተሰብ ቡድኖች እና የኢትዮጵያን የአካባቢ ጥፋት ለመከላከል ብለው ልዩ ስራዎችን ዓለም አቀፍ ወንዞች በፍትሀዊነት እንዲያገለግሉ የሚታገሉትን ዜጎች የምናደንቅ? በዓለም አቀፍ እና በአገር ውስጥ ከሚሰሩ የመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞች ጓደኛ አለን? በድንገት በአምሮዬ ጥያቄ መጣ፡፡ ለምንድን ነው እነ ሲኤን ኤን፣ቢቢሲ፣ ኤቢሲ፣ ሲቢኤስ፣ አልጃዚራ፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ኤልኤ ታይምስ፣… የእኛን ሰላማዊ ተቃውሞዎች ለህዝብ ይፋ የሚያደርጉት?“ ከእነርሱ ጋር ጓደኝነት ስላልመሰረትን ነው? ብቻችንን ልንሰራው የምንችለው ጉዳይ አይደለም፡፡ አብረን ለምንሰራው ሁሉ ሰማይ ወሰናችን ሊሆን አይችልም! መስታወት፣ መስታወት በ…. “የኢትዮጵያ ዲያስፖራ መስታወት” እውነቱን ወይም ደግሞ ውሸቱን ሊነግረን ይችላል፡፡ ምናልባት በመስታወቱ ውስጥ ማየት የምፈልገውን አይቼ ይሆናል፣ ምናልባት መስተዋቱም እኔ በመስታወቱ ላይ እንዲታይ ያስቀመጥኩትን አንጸባርቆ ይሆናል፣ ምናልባት መስታወቱ ሁሉም መልሶች ያሉት ወይም የሌሉት ይሆናል፣ ምናልባት መስተዋቱ የእኔ ህሊና ይሆናል፣ በእርግጥ በበየእለቱ በመስታወቱ ስመለከት የምጠይቀው፣ “በግድግዳው ላይ ያለህው መስታወት የነቃው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ከዚህ በኋላ ምን ማድረግ ይኖርበታል? ወደፊት ይቀጥላ … ለአንባቢዎች ማስታወሻ፣ “ከኢትዮጵያ ዲያስፖራ መስታወት ንግግሮች“ ልዩ በተከታታይነት የሚወጡ ትችቶች ናቸው፣ወደፊት በየጊዜው በሚስቡ ክስተቶችና ድርጊቶች ላይ ትኩረት በማድረግ እንደምጽፍ እገምታለሁ፡፡ ማስተማሪያና መማሪያ በሚሆኑ ድርጊቶችለመምህር ፈልጎ ማውጣት መቻሉ በአጣቃላይ የሚያስደንቅ አይሆንም፡፡ 12/4/2013

‹‹ጥቅም›› ላይ ሳይውል የመሸጋገሪያ ድልድይ ፈረሰ

December 5/2013
የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን አራት ኪሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ወደ ጆሊ ባር...
፣ ኮጆሊ ባር ወደ አራት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ለመሸጋገርያ የሚያገለግል የብረት መሰላል መሥራቱ ይታወሳል፡፡ ባለሥልጣኑ ይህንን መሸጋገሪያ መሰላል የሠራው፣ በአካባቢው የሚተላለፈው የሕዝብ ብዛት ከሌሎች አካባቢዎች የበዛ ስለሆነ፣ የትራፊክ መጨናነቅና በየቀኑ በተሽከርካሪ አደጋ እየተቀጠፈ ያለውን የሰው ሕይወት (ምንም በተባሉት ቦታዎች እስካሁን የከፋ አደጋ ባይደርስም) ለመታደግ በሚል መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ባለሥልጣኑ ሦስተኛ መሸጋገሪያ ድልድይ የሠራው ፒያሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ወደ ራስ መኰንን፣ ወደ አዲሱ ገበያና ወደ አፍንጮ በር (ውቤ በረሃ) በሚወስደው አደባባይ ላይ ነው፡፡
ይህ መሰላል አቀማመጡ ወይም የተሠራበት አቅጣጫ ለተጠቃሚው አመች ባለመሆኑ፣ አብዛኛውን ጊዜ ሲጠቀሙበት የሚስተዋሉት የጐዳና ተዳዳሪዎች ናቸው፡፡ በአካባቢው የሚኖሩት የጐዳና ተዳዳሪዎችም በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጥር ሥር የሚያድሩና በልመና ላይ የተሰማሩ ሲሆኑ፣ መሰላሉን መፀዳጃ በማድረጋቸው፣ መተላለፊያነቱ ቀርቶ የበሽታ ማስተላለፊያ እስከመሆን ደርሶ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ከአራት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ያሠራው የፒያሳው የመተላለፊያ መሰላል በአካባቢው በሚገነባው የቀላል ባቡር ተርሚናል ምክንያት ሰሞኑን እንዲፈርስ ተደርጓል፡፡ የተሠራበት ጊዜ ቅርብ መሆኑን የሚያስታውሱ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ‹‹አስተዳደሩ የሚመራው በዕቅድና በፕሮግራም ከሆነ፣ ቀላል የባቡር መስመር በቅርብ እንደሚሠራ እያወቀ በዚህን ያህል ወጪ ለምን አሠራው?›› በማለት በትዝብት እየጠየቁ ይገኛሉ፡፡   ‹‹ጥቅም›› ላይ ሳይውል የፈረሰው መሸጋገሪያ

Ginbot 7’s Response to EPRDF’s Request for “Negotiation”

December 5, 2013
The authoritarian system that has been built by the Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Front (EPRDF) is in apparent crisis. It is now evident that panic and nervousness within EPRDF is increasing with the passing of each day, and there is ample evidence that indicates towards this major behavioural shift within the ruling EPRDF party. For example, the sudden death of its leader, the ever increasing popular resistance inside and outside the country, and the customary uneasiness of the regime as national elections approach are some of the main indicators. The long-standing political behaviour the EPRDF regime demonstrates that whenever EPRDF is cornered or finds itself in a crisis situation, it uses negotiation as a quick way out or crisis management tool. We believe EPRDF’s most recent call for “negotiation” is not different from its established political behaviour.
Ginbot 7: Movement for Justice, Freedom and Democracy has repeatedly affirmed its strong allegiance towards a democratic change in Ethiopia in a peaceful way through dialogs, discussions, and negotiations. It is EPRDF’s stubbornness and arrogance that pushed Ginbot 7 to look for alternative means and strategies of fighting for justice, freedom and democracy.
The Executive Committee of Ginbot 7 has thoroughly deliberated on EPRDF’s call for “negotiation”. The committee has concluded that this issue concerns the Ethiopian people as a whole, not just Ginbot 7 as a movement. Ginbot 7 strongly believes that the negotiation and its outcome has direct impact on the struggle for freedom and democracy that the Ethiopian people have already waged, and the sacrifices that they are paying. Therefore, Ginbot 7 has decided to exploit the convenience of this opportunity to reiterate its position on negotiation in general, and EPRDF’s current call for negotiation in particular.
1. On negotiated change
As we have repeatedly made it very clear to the Ethiopian people, our primary choice or the most preferred way of struggling for democratic change in Ethiopia is through peaceful dialogs and constructive round table discussions. It is the arrogance of the EPRDF, and particularly its use of force to settle political differences that forced us to look for alternative strategies. G7 has made it clear, time and again, that if the choice presented to us is between living in tyranny and fighting for our liberty, our choice always is dying in dignity while fighting for liberty. We deeply believe in these sacred values, and it is this fundamental principle that attracts our members in Ethiopia and all over the world.
Our principal standpoint on negotiations has two aspects. The first has to do with the process itself. We are always open for a meaningful negotiation to settle political problems. The second has to do with the expected outcome of such an exercise. The outcome of the negotiations should lead to the establishment of a genuine democracy at the minimum possible cost. Ginbot 7 is not interested in negotiations that will jeopardise the aspiration of the Ethiopian people for justice and democracy. We welcome negotiations that can insure sovereignty of the Ethiopian people to decide and shape their destiny through free and democratic process. We cannot negotiate against our principles and the will of the Ethiopian people.
Therefore:
  1. Full recognition of the sovereign power of the Ethiopian people and laying the foundation for a democratic political dispensation should be the ultimate outcome of any and all negotiations. This being the primary goal, there might be several other valuable goals that come in the process, such as the immediate release of all political prisoners. However, other goals, valuable as they may be, cannot substitute the primary goal of establishing a genuine democratic dispensation. The primacy of the will of the Ethiopian people is not negotiable. Ginbot 7 shall not negotiate with EPRDF, or any other force for that matter, unless it accepts this primary objective.
  2. Such negotiations should be conducted not only between EPRDF and Ginbot 7; but with all other stakeholders – political and civic organisations—. EPRDF’s preference to negotiate with individual organisation emanates from a short sighted tactical calculation; it does not show that it seeks long term sustainable solution to the multifaceted challenges facing the country. There is no democracy that is good for one organisation only. All efforts to establish a democratic order should include other political and civic organisations in Ethiopia. Deciding who should run the country, or who should get how much power are not the principal objectives of such a negotiation. The negotiation should be how to empower people to elect their own leaders in a free and fair election and ensure the basic rights of citizens. The issue should not be power grab but starting a genuine process that will establish an acceptable, just and democratic system of governance in Ethiopia.
  3. As explained above, this is a national issue and cannot be conducted behind closed doors. There is no reason why it should be kept secret from the Ethiopian people.
2. Confidence building measures to ensure that past mistakes are not repeated
Based on our past experience in negotiating with EPRDF, which emanate from lack of sincerity on the part of the EPRDF, negotiations should take the opponent’s behaviours into account. Negotiating with an untrustworthy entity requires a different approach to that conducted with a credible negotiating partner. The later requires a set of precautions to ensure that there is a good faith effort to negotiate as well as a rigorous mechanism of verification and implementation to avoid backsliding. In the absence of such precautionary measures, the negotiation cannot be expected to be fruitful.
This is not the first time that EPRDF sought negotiation. So far, we do not know a single instance when EPRDF faithfully implemented agreements reached at negotiations. Rather, we have observed time and again that it in fact cherishes violating negotiations as bravery and cleverness. Nothing is more important to EPRDF than clinging on to power. It hasn’t shown any willingness in the past to sacrifice even a fraction of its power for the long-term benefits of the country.
We, in Ginbot 7, do have first-hand experience with EPRDF’s bogus negotiations. We cannot allow this to repeat itself.
Therefore, we need to make sure that the following actions are taken by the EPRDF government as a confidence building measure and as an indicator of its genuine interest in finding a negotiated solution to the country’s multifaceted political problems:
  1. All political prisoners, journalists, human right activists should be released. This should include those who are detained in secrete prisons;
  2. Intimidating people, especially members of the opposition political parties should stop immediately. The rights of every Ethiopian should be respected and protected;
  3. All politically motivated verdicts of the Kangaroo courts should be nullified. Files that are currently active should be dropped;
  4. All repressive laws that are aimed at terrorising and silencing people should be annulled;
  5. Negotiations should be conducted in the presence of third party mediators. All the process should be filed and kept in hands of the independent mediators. The negotiation place itself should be negotiated. The whole process should be open to the Ethiopian people.
If EPRDF is not willing to take these actions, we would not believe that it has any genuine interests in any negotiated settlement. Until then, Ginbot 7 and other democratic forces will continue their struggle in line with their respective strategies. Ginbot 7 will not be distracted by a negotiation proposal and process that lack substance towards tackling and resolving the longstanding challenges facing Ethiopia and in line with the aspiration of the Ethiopian people for a genuine and democratic change.
December 2, 2013
The Executive Committee
Ginbot7: Movement for Justice, Freedom and Democracy.

ኢትዮጵያን በሙስና ከሚታወቁ የዓለም አገሮች ተርታ ያሰለፈው ሪፖርት ይፋ ሆነ

December 5, 2013 

corruption index



ትናንት ኅዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም. በመላው ዓለም ይፋ የሆነው የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ተቋም የሙስና አመላካች ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ከሙስና ጽዱነት ተርታ ውጭ ከሆኑና በሙስና ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ከሚፈረጁ አገሮች አንዷ ሆና መገኘቷን ይፋ አደረገ፡፡
ሪፖርቱ በሚከተለው የሙስና መለኪያ ሚዛን መሠረት፣ ከሙስና ጽዱ የሚባሉ አገሮች ከዘጠና እስከ መቶ ነጠብ የሚያገኙት ናቸው፡፡ በአንፃሩ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል፣ የሙስና ጎሬ ሆነዋል ተብለው የሚታሰቡ አገሮች ደግሞ ከመለኪያው ከ50 በመቶ በታች የሚያስመዘግቡት ናቸው፡፡ በመንግሥት ተቋሞች ውስጥ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል ተብለው ከተለዩት ውስጥ ኢትዮጵያ 33 ከመቶ የመለኪያውን ነጥብ በማስመዝገብ ከከፍተኛ ሙስኞች ተርታ እንደምትሰለፍ የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ከ177 አገሮች ውስጥ 111ኛውን ደረጃ መያዟም በሪፖርቱ ይፋ ሆኗል፡፡
ኢትዮጵያን ጨምሮ መላው አገሮች ለሙስና ተጋላጭነት ከሚለኩባቸው መመዘኛዎች መካከል፣ የፕሬስ ነፃነት፣ የተጠያቂነትና የሰዎች የመደመጥ መብት፣ የፍትሕ አካላት ከተፅዕኖ ነፃ መሆን፣ የሕግ የበላይነት፣ የሰብዓዊ ልማት መለኪያና ሌሎችም ጠቋሚዎች እንደሚካተቱ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በድረ ገጹ ይፋ አመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በፕሬስ ነፃነት ከ179 አገሮች 127 ደረጃን በመያዝ የፕሬስ ነፃነት ከሌሉባቸው አገሮች ተርታ ትመደባለች፡፡ በፍትሕ አካላት ነፃነትና ከተፅዕኖ ውጭ ካልሆኑ አገሮች መካከል አንዷ ስትሆን ከ142 አገሮች ውስጥም 93ኛ መሆኗ ይፋ የተደረገው ዓምና ነበር፡፡
ተቋሙ 177 አገሮችን በሙስና እንደሚጠረጠሩበት ደረጃቸው በመመዘን ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሐራ በታች ከሚገኙ አገሮች 90 ከመቶው ለሙስና በሚያስጠረጥራቸው ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሆነው አግኝቷቸዋል፡፡ ቦትስዋና ከሰሐራ በታች አገሮች ዝቅተኛ የሙስና ወንጀል የሚፈጸምባት ስትሆን፣ ሶማሊያ ከሁሉም አገሮች በታች በመሆን ሙስና የተንሰራፋባት ተብላለች፡፡ በዓለም ላይ ከ177ቱ ውስጥ 69 ከመቶ አገሮች ከፍተኛ የሙስና መናኸሪዎች መሆናቸውን ሪፖርቱ ያረጋግጣል፡፡
ከሰሐራ በታች የሚገኙትን አገሮች በሙሰኝነት ተፈርጀው የሚመሩት የምሥራቅ አውሮፓና እስያ አገሮች ሲሆኑ፣ 95 ከመቶ በላይ አገሮች ከፍተኛ ሙሰኞች ሆነው ተመዝግበዋል፡፡
በዓለም ላይ ከፍተኛ ሙስና ከተንሰራፋባቸው አሥር አገሮች ስድስቱ ከሰሐራ በታች አፍሪካ ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ (ሪፖርተር)

Wednesday, December 4, 2013

ሳውድ አረቢያ የውጭ ዜጎችን ማስወጣቱዋን እንደምትቀጥል አስታወቀች

december 4/2013

ህዳር (ሃያ አምስ)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-ካለፈው ወር ጀምሮ ህጋዊ ወረቀት የላቸውም በሚል የውጭ ዜጎችን ማባረር የቀጠለችው ሳውድ አረቢያ፣ ከአለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድርጅት ትችት ቢደርስባትም፣ ዜጎችን ማስወጣት እንደምትቀጥል አስታውቃለች። አረብ ኒውስ እስካሁን በተወሰደው እርምጃ 126 ሺ ሰዎች ከአገሪቱ መውጣታቸውን ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ 90 ሺ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው መግባታቸውን ገልጸዋል።

አረብ ኒውስ አንድ ባለስልጣንን ጠቅሶ እንደዘገበው ውጭ ዜጎችን የማስወጣት እርምጃው ተጠናክሮ ይቀጥላል። ኢትዮጵያውያን በአለማቀፍ መድረኮች ያሰሙትን ተቃውሞ ተከትሎ የሳውዲ የጸጥታ ሀይሎች በኢትዮጵያውያን ላይ የሚወስዱትን እርምጃ ቢቀንሱም፣ አሁንም ግን ከ40 ሺ ያላነሱ እስረኞች በእየሰር ቤቶች ወንጀለኞች ተብለው ታስረው እንደሚገኙ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን በአረብኛ የሚታተሙ ጋዜጦችን በመጥቀስ ተናግረዋል። አረብ ኒውስ ዛሬ ባወጣው ዘገባ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ ከወጡ በሁዋላ ወንጅል በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል ብሎአል።
ሂማውን ራይትስ ወች ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያውያንን ለማስወጣት ያቀደው የሳውዲ መንግስት፣ እርምጃ ከመውሰዱ ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ ” ኢትዮጵያውያንን የሚያጥላላ ዘገባዎችን ያሰራጭ እንደነበር መጥቀሱ ይታወቃል። የሳውዲ ጋዜጦች ኢትዮጵያውያንን ማጥላላት መቀጠላቸው የሳውዲ መንግስት በሂደት ለሚወስደው እርምጃ ጋዜጦቹ ከአሁኑ መከላከያ እያዘጋጁለት ነው በማለት በሳውዲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል።
አሁንም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወረቀት የላቸውም በሚል እንደሚባረሩ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የሳውዲ መንግስት የምህረት አዋጁን ሊያራዝም ይችላል በሚል ወደ አገር ለመመለስ እአመነቱ እንደሆን ያነጋገርናቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል። ይሁን እንጅ በተለይም በጅዳ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ተመሳሳይ ከአገር የማስወጣት ዘመቻ ሊካሄድ እንደሚችል የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በጂዳ ሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ሳይዘናጉ አጋጣሚውን በመጠቀም ቶሎ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ያነጋገርናቸው ሰዎች መክረዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደ አገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያውያን ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውንም የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።  መንግስት ይህን ያክል ህዝብ በአንድ ጊዜ ለመቀበል አቅም እንደሌላው እየገለጠ ይገኛል።

ማምሻውን በሹክሹክታ የደረሰኝ ብርቱ መረጃ !

December 4/2013

ነቢዩ ሲራክ ke Saudi Arabia
መልዕክቱን አስቀድሜ ዝርዝሩን ላስቀጥል ልቤ ፈቀደ ! ሹክሹክታው የመልዕክቱ አደራረስ እንጅ መልዕክቱ የተጨበጠ እውነት ነው እናም ስሙኝ ... !
ይድረስ ለወገኖቸ ... ህጋዊ መኖርያ ሰንድ ስሌላችሁ ወደ መጠለያ ለመግባት ፈልጋችሁ እስካሁን እድሉን ያላገኛችሁ ወገኖቸ ሆይ! እነሆ ተራችሁ ደርሷል ! በተለምዶ ፖሊስ ለማያዝ ሰው በሚሰባሰብበት በሸረፍያ ድልድይ ስር በመሄድ እዚያው ብትሰባሰቡ በሁለት ቀናት ውስጥ አውቶቡስ እየመጣ ወደ ሽሜሲ መጠለያ እንደሚወስዳችሁ ከአንድ ብርቱ ውስጥ አዋቂ ወዳጀ በሹክሹክታ መረጃ ደርሶኛል! ሽሜሲ እንደደረሳችሁ ወደ መጠለያው ሳትገቡ አሻራ በማድረግ በአንድ ቀን ልዩነት ወደ ሃገር ቤት የምትገቡበት መንገድ መዘርጋቱንና ይህንንም ለማሳለጥ የመጠለያው ሃላፊዎች ፣ የፖስፖርት ክፍል (የጀዋዛት) ሃላፊዎችና ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች ከጅዳ ቆንስል ከፍተኛ ሃላፊዎች ጋር መክረው ዘክረው ውሳኔ መተላለፉ ብርቱ መረጃ ከብርቱው ውስጥ አዋቂ ወዳጀ መረጃው ማምሻውን በስልክ አቀብሎኛል !
መረጃውን ያቀበለኝን አረብ ወዳጀ ለተጠቀሱት መረጃዎች ቅርብ ነው ። እናም መረጃውን አቀብሎኝ ሲጨርስ በራሴ ላይ የሚጉላላውን ጥያቄ አነሳሁና ... ለምን ነዋሪው በጅዳ ቆንስል ተሰብስቦ እንዲሄድ አይደረግም? ስል ጠየቅኩት " እሱን እርሳው! በአካባቢው የኢትዮጵያ ቆንስልን ጨምሮ የተለያዩ ዲፕሎማሲ መስሪያ ቤቶችን በአካባቢው ይገኘኛሉ ። ትልቁ የንጉስ ፉሃድ ሆስፒታል ትምህርት ቤቶችና በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል በቆንስላችሁ አካባቢ ምንም እንቅስቃሴ ሊኖር አይፈቀድም! አሁን መውጣት ለሚፈልጉ ብቸኛው አማራጭ ሸረፍያ ብቻ ነው ። እዚያ በመሔድ የአካባቢውን ጸጥታ ሳይረብሹ በረጋ መንፈስ መሰባሰብ ከቻሉ ቢበዛ በ24 ሰአት ውስጥ መሰባሰባቸው ሲታወቅ አውቶቡሶች መጥተው ይወስዷችኋል! አውቶቡስ ላይ እንዳሉ የመጓጓዣ ሰነድና አሻራ እንዲሰጡ ይደረጋል ! በመጡበት አውቶቡስ በመጠለያው ሳይውሉ ሳይድሩ በተዘጋጀው አውሮፕላን ወደ ሃገራቸው ይላካሉ ! ሌላው
የመጠለያ እንግልቱን ፈርተው በራሳቸው ቲኬት መሄድ ለሚፈልጉትም አሁን የሚፈሩት ችግር የለም ። ለቲኬት ገንዘብ አይክሰሩ ፣ ቲኬት በራሳችሁ ከሚቆርጡ ገንዘባቸውን ቆጥበው ሸረፍያ አውቶቡስ ሲመጣ ጠብቀው ተዘጋጅተው ከሄዱ በአንድ ቀን ሰንድ ተሰርቶላቸውና ቲኬት ተቆርጦላቸው ወደ ሃገር ቤት መግባት ይችላሉ ። ይህ ማለት ደግሞ ገንዘብ ቆጠቡ ማለት ነው! ግን በአየር መንገድ በቤተሰብ መሸኘት ከፈለጉ የራሳቸው ምርጫ ነው ። " ሲል የማይዋሸው ብርቱ ወዳጀ የሰጠኝ መረጃ ውሃ የሚያነሳ ምክር ጭምር ነው!
ጥያቄየን ቀጠልኩ ...ከሁለት ቀናት በፊት በአልጋ ወራሹ ልዑል ሰልማን በመሩት የምክር ቤት ስብሰባ ላይ " ህገወጦችን በማስወጣቱ ረገድ እርምጃውነሰ አጠናክረን ፣ እንቀጥላለን " የሚለውን ጠንከር ያለ መግለጫ አነሳስቸ ፣ ብዙ ነዋሪዎች " ህጉ ይሻሻላል ፣ የምህረት አዋጁ ለአመት ተራዝሟል ! " በሚል ወደ ሃገር ቤት መግባትን አለመፈለግ እንደተጋጨብኝ አጫወትኩት ... ቀጠልኩና በዚህ ዙሪያስ ምን ትላለህ? ስል ወዳጀን የብዙዎቻችሁን ጥቃቄ ጠየቅኩት! ያማይዋሽ የማይቀጥፈው ፣ ብርቱው የመረጃ ምንጨ ፈገግ እንደማት ብሎ መለሰልኝ " ልብ ያለው ልብ ቢል ይሻላል ፣ ዘንድሮ አምናና ካች አምና አይደለም ፣ ሰአቱ ሳይልቅ በተከፈተው መንገድ የወጡ የታደሉ ነው የሚሆኑት! የምክር ቤቱን መግለጫ ሰምተሃል ፣ እኔም ውስጥ ውስጡን እየሆነ ያለውን ገላልጨ አልነግርህም ፣ ህገ ወጥ ሆኖ ፣ ያልተሟላ ሰነድ ይዞ እንደ ቀድሞው " ህግ ይሻሻላል፣ ምህረት አለ !" የሚለውን ተወው! አመነኝ! ያ ጊዜ አሁን አይደገምም!
ልብ ያለው ልብ ይበል ፣ ጓዙን ሸካክፎ ዛሬ በመጣው እድል ተጠቅሞ ወደ ሃገሩ በሰላም ቢገባ ይሻለዋል። ይህ ላልሆነና ተደብቄ ጊዜውን አለወፋለሁ ለሚል ፍርድ ነው! መቀጮውን ከፍሎ በእስር ማቅቆ እንደሚሄድ አትጠራጠር ! ይህ ብርቱ ህግ ነው ፣ ህጉን ለማስፈጸም መንግሰት ከፍተኛ ገንዘብ እያወጣ ነው ፣ ሁሉመ ሆኖ ያለወጣ ሰውዋጋውን ከፋይራሱ ነው የሚሆነው! " ሲል ቀርጥ አድርጎ የሚያውቀውን መረጃ አካፍሎኛል!
በሽሜሲ መካ መጠለያ እና በመዲና ወደ ሃገራቸው ለመመለስ የጠየቁት በአብዛኛው በያዝነው ሳምንት ወደ ሃገር ቤት መሸኘታቸውን ተጨባጭ መረጃ ደረስኝ መባቻ ወዳጀ ውስጥ አዋቂው ያለኝን ሰምታችኋል። የጅዳ ከተማ ያሉ ወገኖች ተራውየእናንተ ነው ፣ ተዘጋጁ ፣ አማራጫችሁን እናንተው ታውቃላችሁ! ወገኖቸ ሆይ ! ጆሮ ያለው ይህን ሹክሹክታ ይስማ !
መረጃው እንደደረሰኝ ከአደጋ ጊዜ ከተቋቋመው ኮሚቴ አንዳንድ አባላት ጋር በሸረፍያ የሚሰበሰበው ነዋሪ ሊረዳ የሚችልበትን መንገድ ተወያይቻለሁ! ዝርዝሩን እና የምክክሩን መድረሻ እናዎጋለን! እስከዚያው ምከሩ ! አትውጡ እንዳልኳችሁ ውጡ ያልኩት ተጨበጭ መረጃን ይዠ እንደሁ ግን እመኑኝ !
የግርጌ ማስታዎሻ :
ወዳጆች ከላይ ሹክ ያልኳችሁን መረጃ የሚያጠናክሩ መረጃዎች ማምሻውን ለእኛ መንግስት ሃላፊዎች እና ለወገን ወገን ደራሽ ኮሚቴ የህዝብ ግንኙነት ባልደረቦች መድረሱን ሰምቻለሁ! እናም መረጃውን በሰፊው በማሰራጨት ግንዛቤ እንሰጥ ዘንድ እማጸናችኋለሁ ! እባካችሁ share "ሸር" በማድረግ እንደጋገፍ !
እስኪ እሱ ያቅናው !

በመርካቶ ከፍተኛ ቃጠሎ ተከሰተ::

December 4/2013
በአዲስ አበባ መርካቶ የተነሳው የ እሳት ቃጠሎን ይህ ዜና ለዘ-ሐበሻ እከደረሰበት ሰዓት ድረስ የከተማዋ የ እሳት አደጋ ሊቆጣጠረው አለመቻሉን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ አስታወቁ። ዘጋቢዎቻችን እንዳሉት መሃል መርካቶ ከከምዕራብ ሆቴል ወደ በርበሬ በረንዳ በሚወስደው መንገድ ወይም በተለምዶው ቦምብ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተነሳ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ከፍተኛ ንብረት እየወደመ ነው። በዛው አካባቢ በሚገኙት ሜትሮ ሆቴል. ሐረር ዳቦ ቤት፣ ዓለም ሽንሽንና ጌጣጌጥ መሸጫ መደብሮች በዚህ ቃጠሎ የተጠቁ ሲሆን ከአንድ ሰዓት በላይ በፈጀው የእሳት ማጥፋት ሥራ ቃጠሎውን ሊቆጣጠሩት አለመቻላቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ይህ በ እንዲህ እንዳለ ትናንት ማክሰኞ በትራንስፎርመር መቃጠል ምክንያት 70 ዎርክሾፖች በ06 ቀበሌ (ኢንዱስትሪ ዞን) በእሳት ቃጠሎ መውደማቸውን አብረሃ ደስታ ከመቀሌ መዘገቡን ዘ-ሐበሻ ላይ አስነብበን ነበር። ዛሬም አብርሃ ከመቀሌ እንደጻፈው “ዛሬ ሮብ ሌሊት ደግሞ በዓዲ ሐቂ ገበያ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደርሶ ብዙ ንግድ ቤቶች ወድመዋል። በተመሳሳይ አጋጣሚ ዛሬ ሮብ ጠዋት በዓዲሹምድሑን ሰፈር በእሳት ቃጠሎ አደጋ ንብረት ወድመዋል።” ብሏል።
አብርሃ ‘መቐሌ በሁለት ቀናት ዉስጥ በሦስት አቅጣጫዎች (ሰሜን፣ ምዕራብና ደቡብ) የእሳት አደጋ ሰለባ ሆናለች። የማክሰኞው አደጋ በትራንስፎርመር መቃጠል ምክንያት ሲሆን የዛሬው የዓዲ ሐቂና የዓዲሹምድሑን ቃጠሎ መንስ ኤ ግን እስካሁን በትክክል አልታወቀም።” የደረሰበትን መረጃ በፌስቡክ ገጹ አካፍሏል።
አብርሃ የመቀሌውን ዜና ከዘገበ በኋላ በአንዳንድ ሰዎች የተሰጠውን አስተያየት ሲተች “መቐለ በ18 ሰዓታት ዉስጥ ሦስት የእሳት ቃጠሎ አደጋዎች አስተናግዳለች (06፣ ዓዲሐቂና ዓዲሹምድሑን)። ህዝብ ተጨንቀዋል፣ አዝነዋል፣ ተገርመዋል። ባለስልጣናቱ ግን ምንም ዓይነት ቅድመ ጥንቃቄ ለማድረግ እንኳን ዝግጁ አይመስሉም። ካድሬዎቹም አደጋው ከመከላከል ይልቅ ‘ንብረት ወደመ’ ስንል ‘ቃላት ተሳሳቱ’ እያሉ ያሸፉብናል። በመቐለ ከተማ በወደመው ንብረት ለማዘን ስለ እሳት አደጋው መስማት በቂ ነው። ስለ ቃላት አመራረጥ ማተኮር ግን ጥሩ አይመስለኝም። ምክንያቱም ጥረታችን ፅሑፍ መፃፍ ሳይሆን ስለ ደረሰው አደጋ መረጃ መስጠት ነው።” ብሏል።
(ዘ-ሐበሻ)


 

የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት የአፄ ምኒልክ 100ኛ አመት መታሰብያ በዓል እንዳይከበር ፍቃድ ከለከለ

December 4, 2013
የሰማያዊ ፓርቲ የአፄ ምኒልክ 100ኛ አመትን በተለያዩ ዝግጅቶች አስቦ ለመዋል በጃንሜዳ የመሰብሰብ ፍቃድ እንዲሰጠው ጥያቄ አቅርቦ ነበር፣ ይሁንና መንግስት ጥያቄውን ተልካሻ ምክንያቶችን በመደርደር ውድቅ ማድረጉን የሚገልጽ ደብዳቤ ለሰማያዊ ፓርቲ ልኳል።

የፊታችን ታህሳስ 3 የእምዬ ምኒልክን 100ኛ እረፍት በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት እንደሚዘክር የታወቀ ነዉ፡፡ በፕሮግራሙ ላይም በርካታከሀገር ዉስጥና ከዉጪ ሀገር ምሁራን ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ይገኛሉ ተብሉ ይጠበቃል፡፡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ሰማያዊ ፓርቲ ለዝግጅቱ በሚያስፈልጉ ጉዳዩች ላይ ስራ እየሰራ ይገኛል! በስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ አዋጅ መሰረትም ስብሰባ እንደሚያደርግ ለስብሰባና ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ደብዳቤ በትናንትናዉ እለት ያስገባ ሲሆን ዘሬ በደብዳቤ የተመለሰዉ መልስ እጅጉን አስቂኝና አጠያያቂ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡
በደብዳቤዉ ላይ ለምታደርጉት ስብሰባ እዉቅና ልነሳጥችሁ አንችልም ምክንያቱም የፖሊስ ጥባቃ መመደብ አንችልም የሚል ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ደግሞ የፅፈት ቤቱ ሀላፊ ተብዬዉ አቶ አሰግድ በንቀት ደግሞ ማናችሁና ምኒልክ ምናምን የምትሉት ደግሞ ምኒልክ ማነዉ በሚል በእብሪት የመለሰዉ መልስ ነበር፡፡
እንኳን ድንኳን ጥሎ ለመሰብሰብ ይቅርና ጎዳና ሙሉ ህዝብ በመላበት የሩጫ የሰልፍ መሰል የገዢዉ ፓርቲ መልካም ፈቃድ ያገኙ ፕሮግራሞች ከህዝቡ እኩል ፌደራል ፖሊስ ለጥበቃ እንደሚታዘዝላቸዉ እየታወቀ ፤ በሌላ መልኩም በድፍረት እንወጣለን ብለን በተለያየ ምክንያት በተጠሩ ሰልፎች ላይ ለድብደባ የሚላከው ቁጥር ስፍር የሌለዉ የፀጥታ ሀይል አሁን ምን ቢውጠው ነዉ የጥበቃ የሚሆን የሰዉ ሀይል ልናስተባብር አንችልም ስለዚህ ዝግጅታችሁን እዉቅና አንሰጠዉም መባሉ??? ይህ ከእብሪት በላይ ምን ሊሆን ይችላል!!!?
ያም ሆነ ይህ ዝግጅቱ በታቀደለት ምልኩ እንደሚፈፀም በተለመደ ቁርጠኝነት ላይ ነን! ሲፈልጉ ለጥበቃ የከለከሉትን ሀይል ለድብደባ ይላኩት!!! እኛ የምንዘክራቸዉ ፍርሃት ካልፈጠረባቸዉ ሞተዉም መንፈሳቸዉ ካልተለየን እምቢ ባይ አባቶቻችን ተወልደናል፡፡
ድል ለኢትየጵያ ህዝብ!!!
Semayawi party, Addis Ababa

“መንግሥት ከግንቦት ሰባት ጋር ለመደራደር ያቀረበው ጥያቄ የለም” Ethiopian government did not request to negotiate with Ginbot 7

December 4/2013

(በሰንደቅ ጋዜጣ) “መንግሥት ከግንቦት ሰባት ጋር ለመደራደር ያቀረበው ጥያቄ የለም” Ethiopian government did not request to negotiate with Ginbot 7
በኢትዮጵያ ፓርላማ በአሸባሪነት የተፈረጀው የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፤ ኢህአዴግ ለደርድር ጥያቄ አቅርቦልኛል በሚል እያናፈሰ ያለው መሰረተ ቢስ የፈጠራ ወሬ መሆኑን አቶ ሽመልስ ከማል የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አስታወቁ።
ግንቦት 7፤ ህዳር 23 ቀን 2006 ዓ.ም በኢሳት ቴሌቪዥን በኩል ባወጣው መግለጫ ይፋ እንዳደረገው ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በሁለት ወር ጊዜያት ውስጥ ለሶስት ጊዜያት ያህል የእንደራደር ጥያቄ አቅርቦልኛል ብሏል። ንቅናቄው ለእንደራደር ጥያቄው ምላሽ በሚል ባሰፈረው ሐተታ የኢህአዴግ የእስካሁኑ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት ውጥረት ሲበዛበትና መዉጪያና መግቢያዉ ሲጠፋዉ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችን “እንወያይ፣ እንደራደር” በማለት ለውጥረት ማስተንፈሻ ጊዜ ይገዛል ካለ በኋላ ስማቸው ባልተገለጸ መልዕክተኞች በኩል ደርሶኛል ያለውን “የእንደራደር” ጥያቄ ንቅናቄው በዋናነት ያየው ኢህአዴግ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም እየሞከረ ነው በማለት ለድርድሩ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጧል።
አቶ ሽመልስ ከማል ግን በመንግስት በኩልም ሆነ በገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ በኩል ለግንቦት 7 የቀረበ እንደራደር ጥያቄ እንደሌለ አረጋግጠው መንግስት ቢፈልግ ጌታው እያለ ከተላላኪው ጋር ምን ያደራድረዋል ሲሉ ጠይቀዋል። ይህ የእነዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ቅጥፈት መሆኑን ጠቅሰው “በዚህ መንገድ እያሞኙ ገንዘብ መሰብሰብ ለምደዋል፤ ይህም ውሽት ለዚሁ ተግባር የተፈበረከ ነው” ብለዋል። ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ሁኔታ ድጎማና ድጋፍ ለሚሰጧቸው አካላት ሒሳብ ለማወራረድ ድል አድርገን ልንገባ ነው በማለት ሲቀጥፉ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሽመልስ ይህ ዓይነቱ አካሄድ በባዶ ሜዳ ራስን አግዝፎ ለማየት ከመመኘት የሚመነጭ ቅዥት ነው ብለውታል።

ዝምታችን በቃ!! የምናውቀው ብቻችን እጣ ፈንታችን ሰንጎነጫት ነው፡፡ በጣም እጅግ በጣም ከመሸ! ዝም ስንል እናልቃለን! ……

December 4/2013

‹‹መጀመሪያ በ‹‹አማራው›› ላይ መጡ ምንም አልተናገርኩም ምክንያቱም ‹‹አማራ›› አልነበርኩም፡፡ ቀጥለው ‹‹በኦሮሞ›› ላይ መጡ ምንም አላልኩም ምክንያቱም ‹‹ኦሮሞ›› አልነበርኩም፡፡ በመቀጠል ‹‹በሶማሊው፣ በጋምቤላው፣በትግሬው….ላይ መጡበት ምንም አልተናገርኩም ምክንያቱም ከአንዳቸውም አልነበርኩም ከዚህ በመቀጠል በሙስሊሙ ላይ መጡ አሁንም ምንም አላልኩም ምክንያቱም ሙስሊም አልነበርኩም በመቀጠል በክርስቲያኖቹ ላይ መጡ ምንም አልተናገርኩም ምክንያቱም ክርስቲያን አልነበርኩም በስተመጨረሻ በእኔ ላይ መጡብኝ አሁን ለእኔ የሚቆምልኝ ማንም አልቀረም፡፡ ብቻዬን ነኝ!››
ይህ በናዚዎች ስር የነበረው ህዝብ ታሪክ ነው፡፡ በአምባገነኖች ስር ያለና የነበረ ህዝብ ታሪክ ነው፡፡ የእኛው የኢትዮጵያውያን የወቅቱ ችግር ነው፡፡ኒይሞለር በአንደኛው የዓለም ጦርነት የተሳተፈና የናዚ ቀንደኛ ደጋፊ የነበር የፕሮቴስታንት ፓስተር ነበር፡፡ ጨፍጫፊው ናዚ ለጀርመናውያን እቆማለሁ ቢልም በሀሳብ የተለዩትን ጀርመናዊያን ላይ ግን ጠንካራ ብትሩን አሳርፎባቸዋል፡፡ እናም ኮሚኒስት፣ ሶሻሊስት፣ ቤተ እስራኤላዊያን፣ የሰራተኛ ማህበራት….ሌላም ሌላም ከናዚ አስተሳሰብ የሚቃረኑት በሙሉ በየተራ እርምጃ ተወሰደባቸው፡፡ በዛ ዘመን አንዱ ላይ እርምጃ ሲወሰድ ሌላው ዝም በማለቱ ናዚዎች የሚፈልጉትን ሁሉ በግፍ ጨፍጭፈዋል፣ አስረዋል፣ አሰቃይተዋል፡፡
በዚህ ወቅት የፕሮቴስታንቱ ፓስተር ማርቲን ኒይሞለር የሂትለርና የናዚ ደጋፊ ነበር፡፡ ምክንያቱም ኮሚኒስት፣ ሶሻሊስት፣ ቤተ እስራኤላዊያን፣ የሰራተኛ ማህበራት… የሚባሉት መካከል ብዙዎቹ ከፕሮቴስታንት ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው እንደ ጠላት አይቷቸዋል፡፡ ፓስተሩ ሂትለር ኮሚኒስቶቹን ሲያዝር፣ ሲገድል፣ ሲያግዝ ‹‹እግዚያብሄር አይወደውም፣ እነሱም ጀርመናውያን ናቸው፣ ይቅር ተባባሉ፣ ተቀራረቡ›› ከማለት ይልቅ እግዚያብሄር የማይወደውን እግፍ በአይኑ እያየ ዝምታን መረጠ፡፡
ናዚ ያልዳሰሰው የህብረተሰብ ክፍል፣ ካድሬ ለማድረግ ያልጣረው ጀርመናዊ፣ ከጎኑ ለማሰለፍ ያልሞከረው መሪ አልነበረምና በስተመጨረሻ ወደ እምነት ተቋማት ማምራቱ የግድ ነበር፡፡ እናም ፕሮቴትታንትም ቤተ ክርስቲያንም ከመጽሃፍ ቅዱስ ይልቅ የናዚን ‹‹ዶክትሪን›› እንድትቀበል ተገደደች፡፡ ልክ እንደኛው ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ማለት ነው፡፡ ናዚን አድንቆ የገባውን ካድሬ ‹‹የእምነት አባት›› እነ ሂትለር እጃቸውን ዘርግተው ተቀበሉት፡፡ በእምነታችን ጣልቃ ሊገባብን አይገባም ያሉት ግን አይቀጡ ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ማርቲን ኒይሞለር የናዚን ‹‹ዶክትሪን‹‹ አልቀበልም ካሉት ‹‹አባቶች‹‹ መካከል አንዱ ነበር፡፡ ናዚ ሲያሰቃያቸው ዝም ብሎ ያያቸው ቤተ እስራኤላዊያን፣ ኮሚኒስቶች፣ ሶሻሊስቶች፣ የንግዱ ማህበራት…..የደረሰባቸው እጣ ፈንታ አሁን እሱ ጋ ደርሳለች፡፡ ከሌሎቹ ጋር ባለመተባበሩ ብቻውን ቀረ፡፡ ናዚዎች አስረው ሲያሰቃዩት ኖረው የተፈታው ጥምር ጦሩ ከአሸነፈ በኋላ ነው፡፡ ሆኖም ይህ ፓስተር ከስቃዩ በኋላ በእጅጉ ተጸጽቷል፡፡ እ.ኤ.አ እስከ 1984 ድረስ ስለ ሰላም ሰብኳል፡፡ ይህ ሰው ከሚታወቅባቸው መካከል ዝምታ አንድ በአንድ እንደሚያስጨርስ በእስር ዘመኑ የተናገረውና መግቢያየ ላይ ወደ እኛው ሁኔታ አጠጋግቼ የጠቀስኩት ወርቃማ አባባል ነው፡፡ እሱ ቃል በቃል ያለው እንዲህ ነበር፡፡
‹‹First they came for the communists, and I didn't speak out because I wasn't a communist. Then they came for the socialists, and I didn't speak out because I wasn't a socialist. Then they came for the trade unionists, and I didn't speak out because I wasn't a trade unionist. Then they came for me and there was no one left to speak for me.››
ይህ አባባል ከሌላ ብሄር፣ እምነት ወይንም ሌላ ማንነት ውስጥ ነኝ ብሎ በሌሎች ላይ የሚደረጉትን ጥቃቶች በቸልታ ለሚያልፍ አሊያም ከላይ የተጠቀሱት ‹‹ማንነቶች›› ውስጥም ሆኖ ግድ ለማይሰጠው ሰው ሁሉ የሚያገለግል ነው፡፡ በሌሎች ላይ የሚደረግን በዝምታ ሲያልፍ ኖሮ በስተመጨረሻ አብሮት የሚቆም አጥቶ በብቸኝነት ለሚጨቆን ሁሉ የተነገረ ነው፡፡
በእኛ አገር በአንዱ ቋንቋ ተናጋሪ ላይ ችግር ሲደርስ ሌላኛው ዝምታን ይመርጣል፡፡በእምነትም ቢሆን ተመሳሳይ ነው፡፡ ሙስሊሙ ሲነካ፣ ኦርቶዶክሱ ስለ መርህ፣ ስለመብት አብሮ አይጮህም፡፡ ሙስሊሙ፣ ፕሮቴስታንቱምና ካቶሊኩም የሚያደርገው ተመሳሳይ ነው፡፡ በተቃዋሚዎቻችን ሰፈር ደግሞ ይብሳል፡፡
በአገራችን ከሚነገሩት አሉታዊ አባባሎች መካከል ዝምታን የሚያበረታቱት በግንባር ቀደምነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ሌሎች በሚደርስባቸው ችግር ይቅርና በራሳችን ጉዳይ ዝምታን በመምረጥ ኢትዮጵያውያን ባህላችን አድርገነዋል፡፡ ዝምታ ወርቅ ነው፣ ዝም አይነቅዝም፣ ዝም ባለ አፍ ዝንብ አይገባበትም፣ ዝምን ማን ወሰደው፣ ብንናገር እናልቃለን…. እና በርካቶች ዝምታን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ ከመናገር ይልቅ ዝምታን የሚመርጠው ይህ ባህላችን ‹‹መቻል!›› የሚባል ቃልንም በምሳሌነት፣ በስምነትና በሌላም መልኩ በስፋት ይጠቀምበታል፡፡ ገዳይ ባህል!
የጀርመኑ ፓስተር የናዚ ቀንደኛ ደጋፊ ነበር፡፡ መጨረሻ ግን የሂትለር ዱላ ያመራው ወደሱው ነው፡፡ እንዲያውም ስቃዩን በወጉ የሚያይለት፣ ለዚህ ስቃዩ የሚቆረቆርለት አላገኘም፡፡ ደጋፊ፣ ካድሬ…..ም ቢሆን ስለ አንድ ብሄር፣ እምነት፣ ቋንቋ፣ ሙያ፣ አሊያም ስለ ራሱ ከዚህም ወረድ ሲል ፈርቶ ዝም ቢል የመጨረሻው መዓት እሱ ላይ ማረፉ የማይቀር ነው፡፡ የአሁኑን ጨምሮ ከገዥው ጋር የተሰለፉ ፖለቲከኞች፣ ካድሬዎች፣ ደጋፊዎችና ሌሎች አካላትም በስተመጨረሻ በትሩ ያረፈው እራሳቸው ላይ ነው፡፡
በቃ! የዝምታችን አባዜ ይህ ነው ትርፉ፡፡ ልክ እንደዚያ ቄስ፣ ልክ እንደኛ ፖለቲከኞች፣ ልክ እንደአገራችን የእምነት ተቋማት፣ እንደ ማህበራት፣ ምሁራን፣ ልክ የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች የተለመደ ተግባር ዝምታ፣ ‹‹ምን አገባኝ!››፣ የፖለቲካ እሳትነት ብቻችን ያስበላናል፡፡ አስበልቶናልም፡፡ ማንም ስቃያችን ሳያይልን፣ ማንም ሳይጮህልን፣ ማንም ሳይቆምልን ያስፈጀናል፡፡ ያስጨርሰናል፡፡ ዝምታ ከወርቅ ይልቅ እንደሚያበሰብስ፣ እንደሚነቅዝና እንደሚያነቅዝ የምናውቀው ብቻችን እጣ ፈንታችን ሰንጎነጫት ነው፡፡ በጣም እጅግ በጣም ከመሸ!
ሚኒልክ ሳልሳዊ