Tuesday, December 3, 2013

በጅጅጋ የሚታየው ስረአት አልባነት ተባብሷል

December 3/2013


ህዳር (ሃያ አራ)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በጅጅጋ በማንኛውም ሰአት ዜጎች ቤታቸው በጸጥታ ሀይሎች ይፈታሻል። የጸጥታ ሀይሎችም ከሞባይል ስልክ ጀምሮ እስከ ላፕቶፕ እንዲሁም ገንዘብ ይወስዳሉ። የቀበሌ መታወቂያዎችን ሳይዙ ከሄዱ ደግሞ ተጠርጥረው ይያዛሉ። የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚሉት ጅጅጋ ለኢትዮጵያውያን ከሳውድ አረቢያ በላይ የስቃይ መሬት ሆናለች ።

አንድንድ ምንጮች እንደሚሉት ችግሩን የተወሳሰበ ያደረገው አልሸባብ  በጅጅጋው ፕሬዝዳንት የግል ሞባይል ላይ የብሄር ብሄረሰቦች በአል በከተማዋ የሚከበር ከሆነ  እርምጃ እንደሚወስድ መሀላ ያለበት የዛቻ ኤስ ኤም ኤስ መላኩን ተከትሎ
ከፍተኛ ፍተሻ በየጎዳናው እየተደረገ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት አለህ በሚል አንድ የጅጅጋ ነዋሪ ጫካ ተወስዶ  ሲደበድቡት በድንገት በመሞቱ ለቤተሰቡ 50 ሺ ብር ካሳ ተሰጥቶ ሬሳው ከከተማ ውጭ እንዲቀበር ተደርጓል፡፡  ከአልሸባብ ጋር በተያያዘም አንዲት ወጣት ሴት ከአካባቢው ተወስዳ ማእከላዊ ታስራ መደፈሩዋም ታውቋል፡፡

ህዳር 29 የሚከበረውን  የብሄር ብሄረሰቦች ቀን  እንዲሳተፉ የተጋበዙ አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የካቢኔ አባላት በጸጥታና ደህንነት ምክንያት ለመሄድ አለመፈለጋቸውንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።  ይህንን ተከትሎም ከፍተኛ ባለስልጣኖች ለካቢኔ አባላት ጠንካራ ደብዳቤ በመጻፍ በስፍራው እንዲገኙ እያዘዙ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ  በኢ.ፌ.ዳ.ሪ. የፌዳሬሽን ምክር ቤት እና በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልላዊ መንግሥት ትብብር 8ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አከባበር ለውይይት የቀረበ በሚል ርእስ የተዘጋጀው ጽሁፍ ለኢሳት አስቀድሞ የደረሰው ሲሆን  በጽሁፉ ውስጥ ስለክልሉ ታሪክ አነጋጋሪ የሆኑ ጉዳዮች መካተታቸውን ተመልክቷል።

በጽሁፉ ውስጥ “የአቢሲንያ መኳንንት ወደ በረሃው የሚወርዱት ሊያጋጥም የሚችለውን የወባ በሽታ በሚክስ ደረጃ ፈጣንና ትርፋማ የከብት ዘረፋ ለማድረግ ብቻ ነው፡፡” ለምሳሌ ሽፍቶችን በማጥፋት ስም የአፄ ምኒሌክ ጦር አባላት በ1902 እ.ኤ.አ. ከ50ሺ በላይ የእንስሳት ሀብት ከማኅበረሰቡ ተዘርፎ በጅጅጋ በኩል ወደ ሀረር እንዲላክ ተደርጓል፡፡ ” ይላል።

በኀይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥትም የክልሉ ሕዝቦች እንደ ሌሎች የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በሀገሪቷ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ተገለው የቆዩበት ጊዛ ነበር ካለ በሁዋላ፣ የጭቆና ቀንበራቸውን በመጫንና ሕዝቡን ለመቆጣጠር ጥቂት ለሆዲቸው ለኖሩ የጎሳ መሪዎች የተወሰነ ጊዚያዊ ጥቅም በመስጠትና በማታለል ይንቀሳቀሱ ነበር ብለዋል፡፡ የኢጣሊያ ወራሪ ኀይል ኢትዮጵያን ቅኝ ለመግዛት በሚያደርገው ዝግጅት የተደናገጡት አፄ ኀይለስላሴ በመጀመርያ ጊዜ የክልሉን ታዋቂ ግለሰቦችና የጎሳ መሪዎች ሀረር ላይና በመቀጠል በቀብሪደሀር ከተማ በመሰብሰብ የክልሉ ሕዝብ ሀገሪቷን ከወራሪው ኀይሌ እንዲከላከል ጠይቀው ነበር ጽሁፉ ያመለክታል፡፡ጽሁፉ በኢህአዴግ ዘመን ለክልሉ የተሻለ እድል መምጣቱንም ያትታል።

Woyane – bringing the war to America

December 3, 2013
by Yilma Bekele 
Things come apart so easily when they have been held together with lies.’ Is what comes to mind when we see the behavior of the Ethiopian government and its response to the Ethiopian tragedy taking place in the Kingdom of Saudi Arabia.
Lies have been told to cover up previous lies that it has become a Public Relations War instead of unfolding human catastrophe. Catastrophe is a very loaded word but it explains what we know to have happened to our people in that closed kingdom. Thanks to todays technology of Internet and Mobile communications we are witnessing what could happen when cowards take charge. They could strip you of your humanity and throw you into a no man’s land between Saudi and Yemen like a piece of garbage.
Ethiopians working in the Kingdom of Saudi Arabia
We Ethiopians are beyond shock. All those that witnessed YouTube videos, digital photographs and interviews with the frightened and lost cannot but feel the agony of these young people. There are plenty of outsiders that are willing to stand with us against injustice. We need all the help we can get. A little part of the deal is that we have to start to do the job ourselves and then they would help us. It always works better that way.
Ethiopians in their hundreds of thousands travel out of the country to work. In the tens of thousands more leave thru the porous boarders and travel all over the world without papers. The last week we have been focusing on those in Saudi Arabia that found themselves stranded with no place to go. Refer to the link to read morehttp://www.tikuranbesa.com/the-kingdom-from-hell-and-ethiopians/
The Saudi Kingdom gave a seven month amnesty period for foreigners to get their paper in order or leave. November 3rd was the deadline. It is estimated that ‘nearly a million Bangladeshis, Indians, Filipinos, Nepalis, Pakistanis and Yemenis left before the end of amnesty period.
The Ethiopian Government knew of the Saudi decision to deport undocumented people and it is fully aware of the thousands of its citizens that migrate to the Middle East without paper. It chose to ignore the problem for seven months. The Ministry of Pimping that sends thousands of citizens like any export Item and the Ministry of Foreign Affairs under Dr. Tedros Adhanom and all his Embassy and Conciliates decided to be quiet about it wishing it would go away.
The Saudi regime started rounding up undocumented workers November 4th and they had their first Ethiopian victim on November 5th. It became open season on hunting illegals’ by Saudi Security forces and vigilantes. (http://www.ethiopianreview.net/index/ )
The Diaspora that always keep one eye on Ethiopia started their protest movement right around this time. No Saudi Embassy was safe from our outrage. The Ethiopian people heard the bad news due to the relentless coverage by ESAT and our independent web sites. Initially the Ethiopian government tried to blame alarmist Diaspora for the bad news. But nothing could stay hidden in this day and age.
First they tried to ignore the impending disaster. Then they tried to find a scapegoat. Unable to deflect the news of the horrible situation they decided to use the good old trick of lying, disinformation and empty bravado to cover their impotence. Here in entirety is a speech given by the foreign Minister in front of some African meeting in Addis Abeba on November 18th three weeks into the tragedy.
“As you know from Saudi Arabia you know although it is not just deporting Ethiopians only but are deporting other citizens they call illegal and from Ethiopian side three were killed during the crackdown and not only that thousands are in camps we are trying to make it as smooth as possible because if Saudi Arabia says they are illegal we don’t mind they have homes to come to (applause) and we have already started the operation. Our command post is working and well and we have already received hundreds we are expecting tens of thousands and I would like to reassure you that we are ready to receive our fellow citizens home (applause) I had the last ten days because in family planning as we had been saying be careful girls and women I had heard straight from camps from women who are crying for help there is nothing moving than that. I am so saddened I am really depressed that is why I was not going to actually come here asking Dr. keste if he could excuse me because it is almost round the clock crisis management since this issue started but in the name of global solidarity even if we have to deport illegal we can do it smoothly because this is not a war situation it may be accepted when nations are at war to deport like this in a rapid fashion people could understand but not in peaceful situation we could have arranged it together to make the smooth transfer because as I said earlier we are ready to have our citizens so I am sorry to start with this it is something that has been bugging me for some time now ….. “
It is easy to see why things keep going wrong in our country. There is something missing in the picture. We are lacking some major ingredient that our country is made from. How did we survive as a nation state for hundreds of years? How exactly did our country stayed free while all around us were colonized by powerful European powers? It is not that we had a formidable military force or a well-developed economy. What we had was ‘that free leave me alone spirit’ and wise leaders surrounded by skilled diplomats. That is what we are missing today.
Emperor Tewodros committed suicide rather than be taken prisoner by the British force thereby denying them the reason to stay.  Emperor Minilik played the English, French, Russians even Italians like a Masinko and won at Adwa. Emperor Haile Selassie spoke at the league of nations where he said those fateful words ‘’it is us today, it will be you tomorrow.’ Accompanied by PM Aklilu Haptewold and Foreign Minister Ketema Yifru His Majesty played a central role in establishing the Organization of Africa Unity and getting Addis Abeba to be the Headquarter. Those are our accomplishments of the last one hundred fifty years.
Who is filling those shoes today? It is obvious Dr. Tedros is not a diplomat or has not been given the training and skill set to be an effective diplomat. Those dis jointed statements cannot be made by a seasoned diplomat or by someone speaking on behalf of eighty million people.
The puppet Prime Minster was not allowed to acknowledge the crisis and was seen standing for a photo opportunity with Gulf Arabs while stretching his hands for alms in the middle of this affront to people and country. Some say the TPLF party was displaying the leadership potential of the Foreign Minister preparing him for promotion. Based on his performance it looks like they picked a good time to show his short comings. He got his position not due to his ability but solely due his ethnicity.
The Ethiopian government is used to telling all kinds of tall tales to its citizens due to its monopoly of the mass Media including Print, Television, Radio, Phone, Internet and a spy in every neighborhood. But when the crisis attracts international attention this kind of ‘deception’ or ‘evading the truth’ does not work. Dr. Tedros was sent out to put lipstick on a pig. He failed miserably.
How is the Diaspora handling this cowardly attack by the Arabs against a people that have not done them any harm except do their most menial and dangerous jobs? We went out in every city that has any number of Ethiopian exiles to protest this atrocity. It was headlined by our relentless media and discussed in every coffee shop.How is the Diaspora handling this cowardly attack by the Arabs
It is definitely a good thing that thousands of miles from home that we still feel a strong affinity to people and country. The anger was genuine and the pain was deeply felt by all. We are a unique people that the love for our homeland seems to have been engrained in our DNA if that at all is possible. I went out on a protest in San Francisco with about five hundred of my people and felt genuinely invigorated.
I also noticed something unique during this protest which I have not come across before. The protest call was scheduled to happen on Monday and I received a text message with the pic of the post card on Saturday. I have heard that there was a tele conference called to organize a protest and I was surprised by the speed they were working. It was not that group. The Post card does not have a contact number or a web address. ‘Ethiopian Community and Cultural center in Oakland’ is mentioned as a sponsor but no one seems to know who they are. Some people were confused by the proximity of the name to the real ‘Ethiopian Center’ they know and are familiar with. I was also surprised by the sameness of all the post cards printed in North America. It is obvious it was designed by the same person or group. The use of shocking images, the color combination and the title are a giveaway.
What was most surprising was the sheer number of post cards and the speed they spread in the community. Every Ethiopian and Eritrean center including Orthodox Churches, Mosques and Evangelical Churches were covered. There is nothing like having frightened and blackmailed cadres to do your menial job.
Someone called for a protest and there was nothing to do but go out and give a hand. I was very curious. Slowly people started to show up. It is as if we were all told to bring the real Ethiopian flag with us. A few ladies were wearing it as a head scarf while some had it around their neck. The men were wearing it on their hats, as a T shirt while a few were carrying the mother of all Ethiopian Flags about twenty feet long. One hour into the event no one that claims responsibility has shown up but our number was increasing by the minute. Around 12 PM a few young people showed up with megaphone and we started congregating around the loud device.
The speech being given by the still unknown organizers was laying the ground for our slogans. The target was to be Saudi Arabia and our beef with them was regarding the treatment of our people. What was said repeatedly was since this is strictly about ‘human rights’ thus no ‘politics’ should be allowed to contaminate the atmosphere. Mentioning the role of the Ethiopian government was a cause to boo. At long last things were beginning to make sense. The haste in organizing this fake protest was becoming clearer by the minute.
Why would anyone want to circumvent this noble cause most of us went out to show solidarity with our people is a valid question? The majority that showed up were genuinely concerned about the condition of their people and with good Ethiopian heart they came out to express their deeply felt sadness. Unfortunately it is sad to see a very small number that were used to squander this golden opportunity that could have been used for greater good. Why? What would they benefit?
The answer is intertwined with the nature of the government in power and how they have managed to use greed as a weapon. Up until now Woyane has used its sympathizers to silently infiltrate and create chaos from within. The two favorite recipients of this were the Political Party support groups and our Church. It is sad to see our community being taken over or made a subsidiary of TPLF. This occasion was the crowning moment of all that work. Our people at home are faced with an overwhelming and cruel force that terrorizes their daily life and today some in the Diaspora are economic prisoners to be called upon to serve their master in times like this.
I was in complete awe watching the protest march from the side by the actions of the masterful operators at work. The way they played the crowed reminded me of Jimmy Hendricks on Guitar, Mulatu Astatke on keyboard, Shambel on Masinko, Tilahune, Teddy with Gigi as vocalists – they were that good.
What was achieved is a good question. As a diaspora activist I learnt never to discount the ingenuity of Woyane as an enemy. This fifth column (http://en.wikipedia.org/wiki/Fifth_column ) they unveiled took a long time to build. All the registration for land, the requirement of personal documents including finger print was part of the process. Today every city and town has its own kebele rep just like in mother Ethiopia. For us it was a wake up moment and for Woyane it was a champagne time.
One thing for certain is that their action was a betrayal of our people and country. Our protests are not random noises but a thought of calculated acts to achieve a certain gain. Regarding our current problem in the Middle East our aim was:
  • Stop the abuse immediately while we search for lasting solution.
  • Organize some kind of entity to research and offer options.
  • Work with the UN, Red Cross and other organizations to look for safe locations for the political refugees and resettle those who want to return to Ethiopia.
  • Put pressure on the Ethiopian government to allow political freedom.
The interference by the Woyane regime and the Banda like work by our own friends, family and neighbors sabotaged all this important work. The problem is still with us. Despite the lie by the Ethiopian government there are still tens of thousands stranded in Saudi Arabia and dumped in Yemen. Those that called for this quick response are nowhere to be seen today. Their job is done, after all it was never about stopping the atrocity but it was all about shielding the regime. Check out the protest in your city and notice that there is no follow up work or any attempt to continue the work till the problem is solved. What the regime wanted was for us to go out and vent our displeasure on the Arabs and go home and that was the end of the matter.
Our work is still not done. We should go back and start from scratch and re organizes our response. We have learnt a lesson. Woyane has arrived in America in full force. The sleeper agents, the morally deficient characters they have recruited, the economically challenged cheap Hodams they have bought are not going to be a push over. Afraid to be unmasked they would try any means to saw dissent amongst us. It is time to recognize the shifting situation in our movement and act accordingly.
Our people still are not comfortable asking questions, digging deep and researching before making a decision. Our culture does not encourage curiosity and we abhor reading, learning and referring to experts. The last weak we saw all our weaknesses when we saw people following like cattle and afraid to even ask who is in charge here and who elected you to that position. We should never follow without asking by whom and for what. Like we shouldn’t sign a paper without reading it first we should never follow someone without knowing what the game plan is all about. It is time to fight back intelligently not emotionally.
“Things come apart so easily when they have been held together with lies.”
― Dorothy AllisonBastard Out of Carolina

ወያኔን አትንኩ የሳውዲ መንግስትን ተቃወሙ፣ ከመረቁ አቅርቡልኝ ከሥጋው ጾመኛ ነኝ

December 3, 2013
አዜብ ጌታቸው

ማቆሚያ ያጣው የክህደት – እርከን

የሳውዲ መንግስት በወገኖቻችን ላይ የፈጸመው ግፍና ኢ.ሰባዊ ተግባራት በመላው አለም የሚገኘውን ኢትዮጵያዊ ሁሉ አስቆጥቷል! አስቆጭቷል!።

ይህ በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው ግፍና በደል ብሄራዊ ውርደት እንጂ ተራ-ወንጀል አይደለም፡: ብሄራዊ ውርደት ደግሞ የደም- እዳ ነው!። በደም ሥሮቹ ዋሻ ኢትዮጵያዊ ደም የሚሹለከለክበት ዜጋ ሁሉ ይህን የደም-እዳ ሊጋራ ተፈጥሮ ግድ ይለዋል። ግድ የማይለው ካለ፦ እሱ አንድም ከተፈጥሮ እዝ ውጭ ነው። አልያም ኢትዮጵያዊ አይደለም። ከተፈጥሮ እዝ ውጭ የሆነ ፍጡር ሊኖር እንደማይችል ከግንዛቤ በማስገባት፤ ለግዜው ኢትዮጵያዊ አይደለም የሚለውን ይዘን እንጓዝ።

በህውሃት አስኳልነት የሚንቀሳቀሰው የወያኔ መንግስት እንደ መንግስት ላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ግዚያት የሃገርን ህልውና የሚቧጥጡ ፤ የሕዝብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ፤ እንደ ግለሰብም የግለሰብ መብትን የገሰሱ እጅግ በርካታ ጥፋቶችን በጥናት ሲያከናውን ቆይቷል። የወያኔ መንግስት በህዝብ ላይ ቂም የሚይዝ ጉደኛ መንግስት ነው። የወያኔ መንግስት የሚያስተዳድረውን አገርና ሕዝብ የሚጠላ! ከዚህ በፊት በሃገራት ታሪክ ያልታየ ወደፊትም ሊታይ የማይችል የአለማችን ብርቅዬ  መንግስት ነው።

ወያኔ ይህን አደረገ ሲባል ሁሌ እንደነቃለን /SURPRISE/። ከዚህ በላይ ምንም አይነት ክህደት ሊፈጽሙ አይችሉም ብለን ስንደመድም እነሱ ግን የክህደታቸውን ደረጃ ከፍ አድርገው ያስደንቁናል/SURPRISE/
ድንበር ቆርሰው ለጎርቤት አገር ሰጥተው አስደነቁን/ SURPRISE/። ከዚህ በላይ ምን ሊመጣ ነው? ከዚህ በላይስ ምን ሊያደርጉ ይችላሉ? ብለን የድንበር መሬት ቆርሶ ለባዕድ መስጠት ማለት ከክህደቶች ሁሉ የከፋ የክህደት ጣራ ነው ስንል ደመደምን። ወያኔ ደግሞ የለም ይህ የመጨረሻው ክህደት አይደለም ። የድንበር መሬቱ ሲገርማችሁ እትብታችሁ የተቀበረበትን የመሃል አገር መሬታችሁንም ለውጭ ኢንቨስተር እንሸጣለን። እናንተንም አፈናቅለን ከነልጆቻችችሁ ጎዳና  እንጥላለን አሉና ስንቱን ጎጆ አፍርሰው ስንቱን አባ-ወራ ለጎዳና አዳሪነት ዳርገው አስደነቁን /SURPRISE/።

ቀጠሉም፦ የክህደት እርከናቸውን ብቻ ሳይሆን አድማሱንም አሰፉት። ከዓለማዊ (በህዝብና በሃገር ላይ ከሚፈጽሙት) ክህደት ወደ መንፈሳዊ ክህደት ተሸጋገሩ። የሃገር ቅርስ እያላችሁ የምትመጻደቁበትን ገዳም አርሰን ሸንኮራ እንዘራለን አሉ፡፡ የሙስሊሙን ወገን እውነተኛ መንፈሳዊ መሪዎች አባረው አብዮታዊ ዲሞክራት መሪዎችን አስቀመጡ።

መንፈሳዊው ክህደት ግን እንደ ዓለማዊው ክህደት እዳው ገብስ አልሆነላቸውም። መናንያኑ በሱባኤና በጸሎት ለአንድዬ ፋክስ ላኩ፤ ሼኮቹም በሰላት አላህን ምን እስክንሆን ነው የምትጠብቀው? አሉ። አንድዬ/አላህ ከብርሃን ፍጥነት በቀደም መልስ ሰጠ፡፤ ከሸንኮራውም ሆነ ከስኳሩ ቀድሞ “የህውሃቱ አንድዬ”ይሟሟ ዘንድ ማዘዣ ጻፈ!።ያም ግን የክህደታቸው እርከን መጨረሻ አልሆነም።

አሁን በቅርቡ ደግሞ የሳውዲ አረቢያ መንግስት በወገኖቻችን ላይ ግፍና በደል በፈጸመበት ቅጽበት  “የሳውዲ መንግስት ስደተኞቹን ማባረር መብቱ ነው” በማለት የክህደት እርከናቸውን ከፍ አድርገው አስደነቁን።/SURPRISE/
ነገ ደግሞ ከዚህ የባሰ ምን አይነት ክህደት ፈጽመው እንደሚያስደንቁን ማሰብም መገመትም የሚከብድ ይመስለኛል። እውነት! እውነት! እላችኋለሁ! እነሱ ግን እኛ ለማሰብና ለመገመት እንኳ የሚያዳግተንን ቀጣዩን የክህደት እርከን በማንጠብቀው ፍጥነት በተግባር ፈጽመው ዳግም ያስደንቁናል።

ይህ ሂደት ደግሞ እነሱ እስካልጠፉ ካልጠፉ ወይም ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር እስካልጠፋች ቀጣይ ነው። የኛ ጫንቃ መሸከሙ ይክበደው እንጂ የነሱ የክህደት እርከን ከፍ እያለ መሄዱ አይቀርም።ፕሮፌሰር መስፍን የክህደት ቁልቁለት ያሉትን ልብ ይሏል።ለእኔ ግን የክህደት ዳግት …እየሆነ ነው።

ወደ ሁለተኛው የጽሁፌ ክፍል ልግባ፡ በሣውዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻን ላይ የተፈጸመው ግፍና አረመኔያዊ ተግባር ያስቆጣው በተለያዩ አገራት የሚገኝ ኢትዮጵያዊ በሚገኝበት ሃገር የሳውዲ ኤንባሲ እየተገኘ ተቃውሞውን በምሬት ገልጿል። በኔ እይታ ይህ በመላው አለም የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ያሰማው ተቃውሞ ከዚህ በፊት በየትኛውም አገር ዜጋ በዚህ መጠንና ርብርብ የተደረገ አይመስለኝም። የምዕራቡ አለም ታላላቅ ሚዲያዎች ለጉዳዩ በቂ ሽፋን ሰጥተውት ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያዊያኑ ተቃውሞ ምን ያህል የአለማችን መነጋገሪያ ሆኖ በሰነበተ ነበር። ያም ሆነ ይህ በቂ ሽፋን ተሰጠውም አልተሰጠው የኢትዮጵያኑ ድምጽ ከፍ ብሎ ተሰምቷል።ውጤትም አስገኝቷል።

የሳውዲን መንግስት በመቃወም ረገድ ኢትዮጵያዊው ሁሉ አንድ ሆኖ ቆሟል። ለምን ቢባል ብሄራዊ ውርደት ነውና ! ብሄራዊ ውርደት ደግሞ ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት የደም እዳ በመሆኑ ኢትዮጵያዊ  ሁሉ ስሜቱ ሊነካ ግድ ብሏል።
ይህ ብሄራዊ ውርደት ያስቆጨው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ቁጣውን በሳውዲ መንግስት ላይ ብቻ አልገደበም። የአረብና የምዕራባዊያን ሎሌነቱን በተደጋጋሚ ባረጋገጠው የወያኔ መንግስት ላይ ጭምር እንጂ።ለምን ካልን? ይህ ብሄራዊ ውርደት እንዲፈጸም ምክንያት የሆነው ሃገርና ሕዝብ ጠሉ የወያኔ መንግስት በመሆኑ የሚል ነው መልሱ።

በተለያዩ ጸሃፍትና ሚዲያዎች ሲገለጽ የነበረውን መደጋጋም ባይሆንብኝ በሳውዲ የሚገኙ የበርካታ ሃገራት ዜጎች በሳውዲ መንግስት የተሰጠው የ7 ወር ግዜ ሳይጠናቀቅ ዜጎቻቸውን ወደ ሃገራቸው በመመለስ ከዚህ መሰሉ ችግር ታድገዋቸዋል። የወያኔ ባለስልጣናት ግን በተቃራኒው የኢትዮጵያዊያኑን ህገ-ወጥነት በመመስከር የተፈጸመውን ግፍ የተጋነነ እያሉ ሰነበቱ። በመሆኑም የኢትዮጵያኑ ቁጣ ከሳውዲ ባላነሰ በወያኔ መንግስት ላይ በረታ።ይህ ብቻ አይደለም፤ ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ሳውዲ ኤንባሲ የጠራውን የተቃውሞ ሰልፍ የአጋዚ ታጣቂዎች በዘግናኝ ቅጥቀጣ በመበተን የወያኔ መንግስት በሳውዲ የተፈጸመብን ግፍ ተባባሪ መሆኑን አረጋገጠ። ይህም ደግሞ ኢትዮጵያዊያኑ በወያኔ መንግስት ላይ የሚያሰሙትን ቁጣ አጠናከረው።

ይህ በእንዲህ እያለ ተቃዋሚውን ኢትዮጵያዊ የተቀላቀሉ የወያኔ ካድሬዎችና ቅልቦች የሳውዲን መንግስት እንጂ ወያኔን መቃወም ትክክል አይደለም። ወያኔን አትንኩ ሳውዲን ብቻ ተቃወሙ በማለት ከመረቁ አቅርቡልኝ ከሥጋው ጾመኛ ነኝ ሲሉ እንደሰነበቱም ተመልክተናል።

እንደኔ እንደኔ እነዚህ ወገኖች የሳውዲ መንግስትን ለምን እንደሚቃወሙም የገባቸው አይደሉም። የማድረግ እንጂ የማሰብ ሃላፊነት ስላልተሰጣቸው አንዳንዴ የሚያደርጉትና የሚናገሩት ነገር ሲቃረን እንኳ አያስተውሉም።

ይህ ብሄራዊ ውርደት አለም አቀፍ መልክ መያዙ ወይም በውጭ መንግስት መፈጸሙ እንጂ ልዩ ያደረገው፤ የወያኔ  መንግስት በሃገር ውስጥ ባለው ዜጋና በሃገሪቷ ላይ ተደጋጋሚ ሃገርና ህዝብ አዋራጅ ተግባር ፈጽሟል።
እነዚህ የወያኔ ቅልቦች፦ በደል፤ ግፍና ግድያ ድንበር ዘለል እስካልሆነ ድረስ በሃገር ውስጥ በተፈጸመ ግድያና ክህደት ላይ ተቃውሞ ሊቀርብበት አይገባም እያሉ እንደሆነ የተረዱ አልመሰለኝም።

እነዚህ የወያኔ ቅልቦች፦ የሚያገባን ከሪያድና ከጅዳ የተባረረው ኢትዮጵያዊ ጉዳይ እንጂ  ከጉራ ፋርዳ በግዴታ የተፈናቀለው ኢትዮጵያዊ ጉዳይ የኛ ጉዳይ አይደለም እያሉ እንደሆነ የገባቸው አይመስለኝም።
እነዚህ የወያኔ ቅልቦች፦ የሚያንገበግበን በሪያድ ጎረምሶች የተደፈሩት እህቶቻችን ጉዳይ እንጂ በወያኔ ታጣቂዎች የተደፈሩት የተቃዋሚ ድርጅት አባላት ጉዳይ አያገባንም። ይህም ሲያንሳቸው ነው እያሉ እንደሆነ ያወቁ አልመሰለኝም። ለነገሩ የተሰጣቸው ሃላፊነት የማድረግ እንጂ የማሰብ አይደለምና ሊረዱም፤ ሊገባቸውም ሆነ ሊያውቁም አይችሉም።

ለነኚህ ወገኖች ላመላክት የምሻው (ማንበብ ከተፈቀደላቸው) የሳውዲ መንግስት እነሱ አትንኩብን ከሚሉት ከወያኔ መንግስት ምን ያህል የተሻለ መሆኑን ነው።
  • በመጀመሪያ ደረጃ እኛ በሳውዲ መንግስት ላይ የተቆጣነው ወገኖቻችንን ከሳውዲ እንዲወጡ በማዘዙ አይደለም። የሳውዲ መንግስት ያንን ማድረጉ መብቱ ነው።  ቁጣና ተቃዉሟችን ትእዛዙን በአግባቡና ሰባዊ በሆነ መልክ ባለመፈጸሙ ነው፡፡ እንደሰማነው ደግሞ የሳውዲ መንግስት ስደተኞችን የሚያስወጣው ለዜጎቹ ስራ ዕድል ለመክፈት ነው፡፤ በአንጻሩ የወያኔ መንግስት ዜጎቹን ወልደው ከብደው ከኖሩበት ሃገር የሚያፈናቅለው ለውጭ ሃብታሞች የስራ ዕድል ለመስጠት ነው። ልብ ካላቸሁ ልዩነቱን ልብ በሉ ።የሳውዲ መንግስት ለዜጎቹ ሲል ስደተኛን አባረረ።ወያኔ ለውጭ ባለሃብት ሲል ዜጎቹን አፈናቀለ አሰደደ።

  • ሴቶቻችን ላይ የመድፈር ወንጀል የፈጸሙት የሳውዲ ጎረምሶች እንጂ የሳውዲ መንግስት ፖሊሶችና ታጣቂዎች አይደሉም። ሃገር ውስጥ ባሉ በተቃዋሚ ድርጅት አባላት ላይ የመድፈር ወንጀል የሚፈጽሙት ግን መንግስት  ደሞዝ የሚከፍላቸው የስርአቱ አካሎች ናቸው።  ! ተደብቃችሁም ቢሆን ይህንንም አስቡ።
በቅርቡ ተክሌ የተባሉ አንድ ጸሃፊ ከወደ ካናዳ “…ሰልፋችንን ልንቀማ …” በሚል ርዕስ ለንባብ ያቀረቡት ጽሁፍም ይህንኑ የወያኔ ቅልቦች “የወያኔ መንግስት አይነካብን” ግርግር በስፋት ተመልክቷል። አቶ ተክሌ ስጋት አላቸው። ሰልፋንም ይቀሙናል የሚል።በርግጥም አንዳንድ ቦታ ተስክቶላቸዋል ተብሏል።ስኬት በምን እንደሚለካ ግልጽ ባይሆንም…በበኩሌ የአቶ ተክሌን ስጋት እጋራለሁም አልጋራምም።

የአቶ ተክሌን ስጋት እጋራለሁ

የወያኔ መንግስት ዲያስፖራውን ለመበተን ከፍተኛ ባጀት መድቦ በተለይ ወጣቶችን በልዩ ልዩ ጥቅማጥቅም በመደለል ወደ ሃገር ቤት ጠርቶ ስልጠና ሰጥቶ ሊያሰማራ መሆኑን ከሰማሁበት ቅጽበት ጀምሮ ይህ መንግስት እድሜው ካላጠረ መጪው ግዜ አስፈሪ መሆኑ ታይቶኛል።የኢትዮጵያዊነትን እሴቶች በአግባቡ ለመረዳት እድሉና አጋጣሚው (exposure) ያልነበረው በውጭው አለም ያደገ ትውልድ የወያኔ መንግስት እነኚህን እሴቶች ለማጥፋት የሚሄድበትን መንገድና ተንኮል እንዲረዳ አይጠበቅበትም። መኖሩን ስለማያውቀው ነገር መጥፋት ሊያውቅ አይችልምና።ይህን ክፍል እንደ አውቆ አጥፊዎቹ ጎልማሳና አዛውንት የወያኔ ቅልቦች ልንኮንነውም ሆነ በጥፋተኝነት ልንጠይቀውም ይከብደናል።

የወያኔ መንግስት እንኳን በውጭው አለም ለሚገኝ ወጣት ትውልድ ቀርቶ በሃገር የሚገኘውንም ወጣት በግሎባ ላይዜሽን ጥራዝ ነጠቅ ፍልስፍና በውጭው አለም ባህል፤ ሙዚቃ፤ አልባሳት፤ ፊልሞችና በመሳሰሉት ግሳንግሶች እያጠመደው እንደሆነ እያየነው ነው።በመሆኑም በተለይ በወጣቶቻችን ላይ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት ይገባናል እላለሁ። በወጣቶች ጀርባ የሚንቀሳቀሱ ተባዮችን በማጋለጥ ወጣቱን ማንነቱን የማያውቅ ዜጋ ከመሆን ልንታደገው ይገባል። ይህ ወያኔን ከመቃወም እንቅስቃሴ ባላነሰ በትኩረት ሊሰራበት የሚገባ ተግባር ነው።የአቶ ተክሌን ስጋት የምጋራውም በዚህ ምክንያት ነው።

የአቶ ተክሌን ስጋት አልጋራም

የአቶ ተክሌን ስጋት የማልጋራው ደግሞ በአንድና አንድ ምክንያት ብቻ ነው። የወያኔ መንግስት ምንም እንኳ ከፍተኛ በጀት መድቦ ከዚህ ቀደም በነበረበት የጥንካሬ መሰረት ላይ ተመልሶ ለመቀመጥ እየተንደፋደፈ መሆኑ እውነት ቢሆንም ከውስጡ በተከሰቱና ከውጭም ባሉ ችግሮች እንደ አንጋሬ ተወጥሮ የሚገኝበት ወቅት ነው። በሚከተላቸው የተሣቱና የሃገሪቷን አቅም ያላገናዛቡ ፖሊሲዎች ምክንያት የተከሰተው የኑሮ ውድነት ከአጋዚ ሰራዊት ሰደፍ በበለጠ ህዝቡን እየደቆሰው ነው። ሙስሊሙ፤ ክርስቲያኑ፤ ገበሬው፤ የዩኒቨርሲቲ ተማሪው፤ መምህራኑ፤ ሰራዊቱ ….ሁሉም ውስጥ ቁስል አለ።ሁሉም ፍትኑን መድሃኒት ይሻል። መደሃኒቱ ደግሞ ወያኔን ማስወገድ ነው። ወያኔ እንደ መንግስት ደግፈው ያቆሙትን ምሶሶዎች አጥቷል፡፤ ከዚህ አንጻር የወያኔ ደጋፊዎች እንኳን የኛን ሰልፍ ለመንጠቅ ቀርቶ ራሳቸውም ከወያኔ ጓዳ ጓዛቸውን ጠቅልለው እብስ የሚሉበት ግዜ ሩቅ የሚሆን አይመስለኝም።

በዚህ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተመርኩዤ የአቶ ተክሌን ስጋት  ስቃኘው ከኛ ይልቅ ወይኔ ነው መስጋት ያለበት ባይ ነኝ።

ይህን ስል ግን እጃችንን አጣጥፈን እየተመለከትን ወያኔ እንደ ባሉን ከሰማይ ወርዶ እግራችን ስር ፈንድቶ ይጠፋል በሚል ግብዝነት አይደለም። እንዲያውም ከመቼውም ግዜ በበለጠና በተለየ መልክ መንቀሳቀስና መስራትን የሚጠይቅ የታሪክ አጋጣሚ ላይ እንደምንገኝ አጽንኦት ሰጥቼ መግለጽ እሻለሁ።ምክንያቴም፦ የወያኔ መንግስት ከፍተኛው ስጋት የዲያስፖራው እንቅስቃሴ መሆኑ ግልጽ ነው። በመሆኑም የሚጨብጠው የሚይዘው ያጣው የወያኔ መንግስት ከፍተኛ በጀት የመደበበት ዲያስፖራውን የማዳከም የመበተን ከተቻለም የመቆጣጠር ፕሮጀክት በርካታ ወገኖችን ሊያነሆልል ስለሚችል ይህን እድል እንዳያገኝ በተደራጀ መልክ ልንቀሳቀስ ይገባልና ነው።

ምን ማድረግ ይገባናል?

ከዚህ በፊት የነበረው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በዘፈቀደ የሚከናወን፤ በአብዛኛው የወያኔ መንግስት ለሚፈጽመው ኢሰባዊና ኢ.ዲሞክራሲያዊ ተግባራት የተቃውሞ ምላሽ መስጠትን ብቻ ያለመ ነው። አለፍ ሲልም የወያኔ የግፍ በትር ያረፈባቸውን ተጎጂ ዜጎች በገንዘብና በሞራል መርዳት ነው። አልያም በተቃዋሚነት ቆመው የሚታገሉ የተደራጁ ወገኖችን መርዳት ነው።  ይህ ብቻ ደግሞ የወያኔን መንግስት አውርዶ የምንናፍቀውን ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመገንባት የሚደረገውን ትግል ከግብ አያደርስም።

ከዚህ በኋላ በውጭው አለም ያለው የወያኔን መንግስት ብሄራዊ ጥፋት ለማስቆም የሚታገል ኢትዮጵያዊ ሁሉ! ሕዝባዊና አካባቢያዊ ድርጅት መፍጠር ይገባዋል፡፤ይህ ህዝባዊ ድርጅት ፡ ኢትዮጵያን እንታደግ የሚል አንድና ግልጽ አላማን ያማከለ የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅትን ፕሮግራምና አቋም በተለይ የማይቀበል ወይም በተለይ የማይነቅፍ የፖለቲካ ድርጅት አባል የሆነው ያልሆነው በጸረ ወያኔ አቋሙ ብቻ ተመዝኖ የሚቀላቀልበት ሆኖ ተጠሪነቱም በዛው በተቋቋመበት ሃገር ላለው ኢትዮጵያዊ ብቻ የሆነ አደረጃጀት መከተል ይገባል።

እስካሁን ትግላችንን የጎዳው እርስ በርስ መጠራጠርና አልያም ግዴለሽነት በመሆኑ ይህ አዲስ አደረጃጀት ከምንም ነገር በፊት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ፍጹም በሆነ መቀራረብና መተማመን ላይ የተመሰረተ አባላት ሊያከብሩት የሚገባ የዲሲፒሊንና የአሰራር ደንብ  አውጥቶ ተግባራዊ ማድረግ ነው።
ይህ ህዝባዊ ድርጅት አደረጃጀቱ እንደ እድርና ማህበር ሁሉ ሕዝባዊ መልክ ኖሮት እንቅስቃሴው ግን እንደ ፖለቲካ ድርጅት ልዩ ልዩ ንኡሳን ኮሚቴዎች የያዘ ሊሆን ይችላል።

ለምሳሌም የመረጃ  ክፍል፤ የዲሲፒሊንና ሥነ ስርአት ክፍል፤ የመድረክ ዝግጅት ክፍል፤ የፋይናንስ ክፍል፤ የአባላት ምልመላ ክፍልና ሌሎችም እንደአካባቢው ሁኔታ ሊኖሩ የሚገባቸው ክፍሎችን ማካተት ይችላል።

የመረጃ ክፍሉ፤  በአባላት መካከል የነቃ የመረጃ ልውውጥ የሚደረግበትን መንገድ እያመቻቸ በአካባቢው ያሉ የወያኔ ጀሌዎችን  ለይቶ በማወቅ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ተከታትሎ የማጋለጥ ሚና ይጫወታል።

የዲሲፒሊን ክፍሉም በአባላት ቸልተኝነት የሚፈጠሩ ስህተትና ጥፋቶችን በአግባቡ በማረም የህዝባዊ ድርጅቱን ውስጠ ደንብ ተግባራዊነት ያረጋግጣል። መተማመን እንዲሰፍንና አባላት ለህገ ደንቡ ተገዢ እንዲሆኑ ያደርጋል።
የቅስቀሳና መድረክ ዝግጅት ክፍሉም የወቅቱ ሁኔታን አስመልክቶ ልዩ ልዩ መድረኮችን በማዘጋጀትና በማመቻቸት የአባላትን ሁለንተናዊ ግንዛቤ የሚያበለጽጉ ስራዎችን ይሰራል።ሌሎቹም ንዑሳን ክፍሎች እንደዛው የተሰጣቸውን ሃላፊነት ይመራሉ።
አደረጃጀቱ በተለይ በህቡ ቢሆን ጠቀሜታው የጎላ ይሆናል። ምክንያቱም በወያኔ ጀሌዎች የሚደረግን እንቅስቃሴ ለማክሸፍም ሆነ በየአካባቢው የሚኖሩ እንደ ቸርች ኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የስፖርት ኮሚቴ የወጣቶች ኮሚቴ ፤ የሴቶች ኮሚቴ፤ የመሳሰሉትን ተቋማት ድምጽ ሳይሰማ ያለ ችግር መቆጣጠር ያስችለናል።

ይህ እንግዲህ ቀጣይ እንቅስቃሴያችንን በመንደፍ ረገድ እንደ መነሻ የቀረበ ሃሳብ ሲሆን፡፤ በጽሁፌ ላመላክተው የፈለኩት አብይ ጉዳይ ግን ከዚህ ቀደም ስናደርገው የነበረው የትርፍ ግዜ የዘፈቀደ “ሲያመች ብቻ” አይነት እንቅስቃሴ የትም እንደማያደርሰንና በአፋጣኝም ተቀራርበን ተማምነንና ተግተን የምንሰራበትን መንገድና ዘዴ መፈለግ እንዳለብን ነው። ይህን ማድረግ ካልቻልን የወያኔን ዘላለማዊ መንግስትነት የኛንም ዘላለማዊ ተቃዋሚነት ተቀብለን ሲገሉ እያለቀስን፤ ሲያስሩ እንዲፈቱ እየጠየቅን፤ ሲያፈናቅሉ ተፈናቃዩን እየረዳን፤ …. የራሳችንንም የሀገራችንንም መጨረሻ መጠበቅ ነው……
azebgeta@gmail.com

የኢህአዴግ የድርድር ጥያቄና የግል እይታዬ – ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

December 3/2013

አንድ፣ ኢሳት ፣ ኢህአዴግን እና ግንቦት7ትን የተመለከተ ዘገባ ካቀረበ በሁዋላ አንዳንዶች ዜናውን ሲጠራጠሩት ተመልክቻለሁ፣ ያሽሟጠጡም አልታጡም። መጠራጠርም፣ ማሽሟጠጥም የሰውልጅ ባህሪ በመሆኑ አልገረመኝም። ትንሽ የገረመኝ አንዳንድ “ጋዜጠኞች” መረጃውን ካገኙ በሁዋላ በራሳቸው መንገድ አጣርተው ሀቁን ማውጣት ሲችሉ እነሱም እንደሌላው መልሱን በማንኪያ እንዲቀርብላቸው መፈለጋቸው ነው። ጋዜጠኛ “ጥቆማ” ከተሰጠው ተመራምሮ፣ የምርምር ስራውን ይጽፋል እንጅ እንደ አንባቢ መልሱ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብለት አይጠብቅም፣ ጥያቄ መጠየቅማ ማንም ይጠይቃል፣ ጋዜጠኛን ጋዜጠኛ ወይም ተመራማሪ የሚያደርገው ለጠየቀው ጥያቄ ላይ ታች ብሎ መልስ ማቅረብ ወይም በአሰባሰባቸው መረጃዎች ላይ ተንተርሶ ትንተና መስጠት ሲችል ነው ( በሁለተኛው መስፈርት መሰረት ተመስገን ደሳለኝን እና በእስር ላይ የሚገኘው ውብሸት ታየን አደንቃለሁ)።

ሁለት፣ ዜናውን እንደሰማሁ መጀመሪያ የመጣልኝ ጥያቄ “እና ምን ያስገርማል?” የሚለው እንጅ፣ “ድርድሩ የተጠየቀው መቼና በእነማን በኩል ነው?” የሚለው አልነበረም። የአለም የፖለቲካ ታሪክ በግጭትና በድርድር የተሞላ ነው። “ድርጅቶች ይጋጫሉ፣ ይደራደራሉ፣ ምን ያስገርማል?”፣ በፖለቲካ ትግል” በመቃብሬ ላይ ..” የሚባል ነገር የለም። “ለምን ሰበር ዜና ሆነ ታዲያ?’ እንዳትሉኝ፣ ሰበር ዜና ማለት አስገራሚ የሆነ ዜና ማለት አይደለም ።
ሶስት፣ ቀጥሎ የመጣልኝ ጥያቄ “ኢህአዴግ ከግንቦት7 ጋር መደራደር ለምን ፈለገ?” የሚለው ነው። ይህን ጥያቄ ለመመለስ ” የፖለቲካ ድርጅቶች የእንደራደር ጥያቄ የሚያቀርቡት መቼ ነው?” የሚለውን ማየት ነበረብኝ። የፖለቲካ ድርጅቶች በአብዛኛው ለድርድር የሚቀመጡት ህልውናቸውን ለማቆየት ወይም ተደራድሮ የሚገኝ ጥቅም ሳይደራደሩ ከሚገኝ ጥቅም ( ጉዳት) የተሻለ ሆኖ ሲያገኙት ነው። በዚህ ንድፈሀሳብ ላይ ተመስርቶ ኢህአዴግ እና ግንቦት7 አሁን ያሉበትን ቁመና መፈተሽ ይገባል። ኢህአዴግ ከመለስ በሁዋላ ኢህአዴግ አለመሆኑ ይታወቃል።ሊቀመንበሩ ድርጅቱን ይዞ ለመቀጠል ተቸግሯል፣ (ምናልባትም በቅርቡ ይፋ የሚሆኑ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከፍተኛ የገንዘብ ችግር አጋጥሞታል)፣ የ ህዝቡ ልብ እንደሸፈተ አውቋል፣ ወጣቱ ለውጥ እንደሚፈለግ ተረድቷል፣ ሰራዊቱ የሚተማመንበት ሀይል እስኪያገኝ እንጅ እንደሚከዳው ተገንዝቧል። በአጠቃላይ መጪው ጊዜ ለኢህአዴግ ብሩህ አለመሆኑን ግንባሩ ጠንቅቆ ያውቃል። በዚህ አደጋ ውስጥ ሆኖ ጊዜ ለመግዛትና ድርጅቱን ለማጠናከር የድርድር ጥያቄ ቢያቀርብ አይገርምም።
ግንቦት7 ለኢህዴግ “አጣዳፊ ጠላት” (immediate threat) ሆኗል እያልኩ አይደለም፣ ነገር ግን እምቅ ጠላት ( potential threat) መሆኑን አልጠራጠርም ። አንድ ድርጅት ለሌላው ድርጅት አጣዳፊ ጠላት የሚሆነው ፣ አሁን ባለበት ሁኔታ፣ ከተቃራኒው ድርጅት የበለጠ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የሀይል ሚዛን ሲኖረው ነው። ግንቦት7 ኢህአዴግን ዛሬውኑ ለማስወገድ አይችልም ምክንያቱም ከኢህአዴግ የሚበልጥ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ ሀይል የለውምና ፤ ነገር ግን በጊዜ ሂደት እንደሚያስወግደው መገመት ይቻላል፣ ከመለስ በሁዋላ ያለውን ሁኔታ ብታጠኑ የኢህአዴግ የሀይል ሚዛን ወደ ታች እየወረደ፣ በአንጻራዊ መልኩ የግንቦት 7 የሃይል ሚዛን ደግሞ ወደ ላይ እየወጣ ነው፣ የ ግንቦት7 መሪዎች በዚህ አመት የሀይል ጥቃት እንደሚጀመሩ አስታውቀዋል፣ በዚህ አመት ቀርቶ በሚቀጥሉት 3 አመታት ጥቃት ከፈጸሙ እያደጉ መሆኑን የሚያሳይ ነው ( 4 ፓይለቶች መክዳታቸውንም አንዘንጋ)። የፖለቲካ ሳይንቲስቶች እንደሚሉት ሁለት አይነት ሀይል አለ። አንዱ መቺው ሀይል ( hard power) ሲሆን ሌላው ደግሞ መለስተኛው ሀይል ( soft power) ነው። መቺው ሀይል የሚባለው ወታደራዊው ሀይል ነው። በዚህ በኩል ኢህአዴግ ከግንቦት7 በብዙ እጅ የሚልቅ ጉልበት አለው። ነገር ግን ግንቦት7ትም በዚያው ጎዳና እየተጓዘ መሆኑን መርሳት የለብንም።
መለስተኛ ሀይል (soft power) የሚባለው ደግሞ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያዎችን፣ ጥራት ያለው የሰው ሀይልን ( መሪም ተከታይም)፣ ህዝባዊ ድጋፍ ፣ የካፒታል አቅም ፣ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት የመሳሰሉትን ያካትታል። ግንቦት7 በዚህ በኩል ከፍተኛ ጉልበት መገንባቱን መመስከር ይችላል። ከኢህአዴግ ተመጣጣኝ የሆነ ካፒታል ባይኖረውም፣ ከሌሎች ድርጅቶች የተሻለ ካፒታል( ገንዘብ)እንደሚኖረው ከስራዎቹ መገመት ይቻላል ። የተማሩ ሰዎችን በመያዝ በኩልም፣ ከኢህአዴግ ቢበልጥ እንጅ አያንስም። በፕሮጋንዳውና በህዝብ ድጋፍ በኩልም እንዲሁ። እንዲያውም የግንቦት7 የፕሮፓጋንዳ ማሽኖች ከኢህአዴግ የተሻሉ ለመሆናቸው ብዙ አስረጅ አይጠይቅም፣ የግንቦት7 ራዲዮና ዌብሳይት እስከዛሬ ሳያቋርጥ እየሰራ ነው፣ ጠንካራ የፓልቶክ ደጋፊዎችም አሉት። ኢህአዴግ ራሱ የሚሰራላቸው ፕሮፓጋንዳም ቀላል አይደለም። ኢህአዴግ ቢያንስ በውጭ ያለውን ድጋፉን፣ በተለይም ለጀመራቸው የአባይ እና ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ገንዘብ ለመለመን ሲል ግንቦት7ን ለድርድር ቢጠይቀው አይገርምም። ኢሳት የግንቦት7 ነው ብሎ ስለሚያስብም፣ ኢሳትን እንዲያስቆምለት ልደራደርህ ቢል አሁንም አይገርምም። (በኢሳት ላይ እንኳ ቀልድ የለም፣ መደራደር ከፈለገ ከኢሳት ጋር እንጅ ከግንቦት7 ጋር ሊሆን አይችልም፣ ምክንያቱም ግንቦት7 ስለኢሳት ምንም የሚያገባው ነገር የለምና፣ ከኢሳት ጋር ድርድር ከተጀመረም ለኢሳት የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ዙሪያ እንጅ፣ ከስራው ጋር የተያያዘ እንደማይሆን መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ)
አራት፣ ኢህአዴግ ከግንቦት7 ጋር ብቻ ነው ወይ ድርድር የመረጠው? እኔ ባለኝ መረጃ ኢህአዴግ በእነ ፕ/ር ኤፍሬም ይስሀቅ በኩል ላለፉት 4 ወራት ከእነ አቶ ሌንጮ ለታ ድርጅት ጋር ሲነጋገር ነበር። ይህን ጠንቅቄ አውቃለሁ። ከኦብነግ ጋርም እንዲሁ ተደጋጋሚ የድርድር ጥያቄዎች ቀርበዋል። እነዚህ ድርጅቶች በፓርላማ “አሸባሪ” የተባሉ ናቸው። እና ለግንቦት7 ጥያቄ ቢያቀርብ ምን ይደንቃል? ፖለቲካ እኮ ፊት ለፊት የምትናገርውና በውስጥ የምታደርገው የተለየ ነው። That is politics. በነገራችን ላይ ” አንደኛው የአለም ጦርነት የተጀመረው በድብቅ በሚካሄድ ፖለቲካ የተነሳ ነው” ተባለና ፖለቲካ ግልጽነት እንዲኖረው ተብሎ አዲስ አስተሳሰብ ለረጅም ጊዜ ተራመደ። ፖለቲካ ግን ዛሬም ፊትና ጀርባ እንደያዘ ቀጥሎአል።
አምስት፣ “ጥያቄው በእነማን በኩል ቀረበ?’ የሚለውንም ለራሴ አንስቻለሁ። የድርጅቱ መሪዎች መልሱን ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፣ ነገር ግን የራሴን ግምቶች አስፍሬአለሁ። አንድ፣ በቅርቡ በእነአቦይ ስብሀት የተመራ ቡድን አሜሪካ ከርሞ ሄዷል። ሁለት፣ ፕ/ር ኤፍሬም አሜሪካ ከርመዋል፣ ኦነጎችን ለማስታረቅም ላይ ታች ሲሉ ከርመዋል። ሶስት፣ በቅርቡ የአውሮፓ እና የካረቢያን አገሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፣ ብዙ ዲፐሎማቶችም አዲስ አበባ ነበሩ። አራት፣ ኖርዌይና ሆላንድ ሁሌም ተቃዋሚዎችን ለማቀራረብ ይሰራሉ። ይዋል ይደር እንጅ ትክክለኛውን መልስ እናገኛለን። መልሱ ግን ከጠቀስኳቸው ሰዎች ወይም አገሮች በአንዱ ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ። የእንደራደሩ ጥያቄ ለመቅረቡ ግን መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ። እስከዛው እንደ ጋዜጠኛ መላ ምት በማስቀመጥ ምርምራችን መቀጠሉ ተገቢ ነው።
ስድስት፣ ግንቦት7 ለምን ይህን ድርድር ይፋ ማድረግ ፈለገ? ኢህአዴግ አስቀድሞ በኢቲቪ ” ከግንቦት7 ጋር ሲያደርግ የነበረው ድርድር ከሸፈ” ብሎ መግለጫ ቢሰጥ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስቡት? የግንቦት7 ደጋፊዎች የድርጅቱን መሪዎች በጥሩ አይን የሚያዩዋቸው አይመስለኝም፤ ግንቦት7ትም ውስጥ አለመተማመን ይፈጠርና ድርጅቱን ከሁለት ሊከፍለው ይችል እንደነበር መገመት ይቻላል፣ ዲሞክራሲያዊ ነኝ የሚል ድርጅት ከአባሎቹና ከህዝቡ የሚደብቀው ነገር መኖር የለበትም። ግንቦት7 በመግለጫው “ድርድር መደረግ ካለበት ከሁሉም ድርጅቶች ጋር ነው፣ ሁሉንም ነገር ግልጽ እናደርጋለን የምንደብቀው የለንም” ብሎአል። ትክክል ነው። እውነተኛ ድርድር ሲጀመር ለጊዜው ይፋ የማይወጡ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ፣ ድርድር ተጠየቅሁ ብሎ መግለጫ መስጠቱ ግን የሚገርም አይመስለኝም። ግንቦት7 መረጃውን ከኢህአዴግ ቀድሞ ይፋ ማድረጉ ድርጅቱን ከመከፋፈል ማዳን ብቻ ሳይሆን ንቅናቄው ከኢህአዴግን አንድ እርምጃ ቀድሞ የ ሚያስብ መሆኑን ለማሳየትም ጠቅሞታል።
በአገር ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞች በኢህአዴግ በኩል ያለውን መልስ ይዘውልን እንደሚቀርቡ ተስፋ እናድርግ።

ሳውዲ አረቢያ ጎዳና ላይ የኢትዮጵያውያን ደም ብቻ ነው የሚፈሰው

December 3/2013

ሳውዲ አረቢያ ጎዳና ላይ የኢትዮጵያውያን ደም ብቻ ነው የሚፈሰው፡፡ የሚያለቅሱትም ኢትዮጵያውያን ሆነዋል፡፡ ኦጋዴን ታነባለች፤ ጋንቤላ ውስጥ ተወላጆቹ ለአረቦቹ እትብታቸው የተቀበረበትን መሬት ትተው እየሸሹ ነው፡፡ በኦነግ ስም መታሰር አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ቀድሞ የታሰሩትንም ማዕከላዊ፣ ዝዋይ፣ቃሊቲ….እየማቀቁ ነው፡፡ ከየ አካባቢው ኢትዮጵያውያን መሬታችሁ አይደለም ተብለው ያፈሩትን ተነጥቀው እየተባረሩ ነው፡፡ ሙስሊሞቹ ታስረዋል፡፡ መስጊድ ውስጥ ፖሊስ ገብቷል፡፡ ገዳማት ለሸንኮር አገዳ ተከልለዋል፡፡ ወጣቱ ስራ አጥቷል፡፡ ተቃዋሚዎችና ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪዎች›› ተብለው እየተሰቃዩ ነው፡፡ ህገ መንግስቱን ጠቅሶ መብትን ማስከበር ያስደበድባል፡፡ ያሳስራል፡፡
ኢትዮጵያ እንዲህ ሆነች፡፡ እምነት ምኑም ባይሆን በኢኮኖሚው ያስለቅሱታል፡፡ ከእነሱው ተጠግቶ ለኢኮኖሚው ግድ ባይኖረው በእምነቱ ይመጡበታል፡፡ ይህንም ቢሆን ‹‹ዝም›› ብሎ ቢያልፍ እህቱ ሳውዲ ውስጥ ተደፍራ ስትሞት ‹‹ህገ ወጥ ስለነበረች ነው›› ይሉታል፡፡ ለዚህ ሰቆቃ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ይደበደባል፡፡ ይታሰራል፡፡ ብቻ በአንድም ሆነ በሌላ ኢትዮጵያ ታነባለች፡፡ የሚያሳዝነው ግን እንዲህ እያነባች መጨፈሯ ነው፡፡
አንድ የአማርኛ ፊልም ላይ ነው፡፡ ተዋናዮቹ ‹‹ጥሮ ግሮ›› የሚለውን ቃል ወደ እንግሊዘኛ ለመተርጎም ሞክረው መጣር መጋር በኢትዮጵያ እንጅ ሌላ አገር እንደሌለ አምነው ይተውታል፡፡ እንደ እኔ ኢትዮጵያ እያነባች የምትዳንስ ብቸኛዋ አገር ትመስለኛለች፡፡ እያነቡ እስክስታ የእኛው ብቻ መገለጫ ይመስለኛል፡፡ ሰቆቃ ተለይቷት የማታውቀው አገር እያረረች ትስቃለች፣ እያነባች እስክስታውን ታስነካዋለች፡፡ ይህ የሚደረገው በገዥዎቿ ትዕዛዝ ቢሆንም የሚያለቅሱትም የሚዳንሱትም ግን ምስኪኖቹ ህዝቦቿ ናቸው፡፡
በአሁኑ ወቅት ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ለህዳር 29 ዳንስ እየተለማመዱ ነው፡፡ ይህ ሁሉ በሆነበት ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› የሚባሉት በተድላና በደስታ እንደሚኖሩ ሲነገር ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን እየራጠራለሁ፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ህቡዕ ይሆኑብኛል፡፡ መቼም ብሄር ብረሰቦችና ህዝቦች የሚባሉት ሳውዲ፣ ኦጋዴን፣ ጉራፈርዳ፣ ነቀምት፣ አዲስ አበባ……ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰቃዩትን ውጭ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ሳውዲ ውስጥ እህቱ የሞተችበት እንባውን በቅጡ ሳይጠራርግ ይጨፍራል፡፡ መሬቱን የተነጠቀው፣ ወንዱሙ የታሰረበት፣ ከክልል የተባረረ…..እርር ድብን እያለም ቢሆን በትዕዛዝ እስክስታውን ይመታል፡፡ እያረረ ይስቃል፡፡
ህዳር 29ኝም ሆኑ ሌሎቹ በዓላት ለእኔ እንደዚህ ናቸው፡፡ ቋንቋህ ተከብሮልሃል ተብሎ መብቱን በአፍ መፍቻው መናገር ሳይጀምር ሰቆቃ የደረሰበት ህዝብ፣ የብሄርን መብት ተከብሮልሃል ተብሎ ከስም ያላለፈ ጥቅም ያላገኘ ‹‹ብሄርና ብሄረሰብ›› ከልቡ የሚያከብረው በዓል ሊሆን አይችልም፡፡ አዎ ህዳር 29 መብገኛ፣ እያረሩ የሚጨፈርበት፣ ህገ መንግስታዊ መብት ከጭፈራና ማስመሰል ያለለፈበት እያረሩ የሚስቁበት ቀን ነው፡፡

የምስራቅ ኢትዮጵያ ፖለቲካ (ተመስገን ደሳለኝ)

December 3/2013

…አውሮፕላኑ ቅዳሜ ጠዋት ሶስት ሰዓት ላይ ድሬዳዋ አየር ማረፊያ ደርሶ ከተርሚናሉ ስወጣ፣ ተጠራጥሬ ሰዓቴን ተመለከትኩ፤ የድሬ የጠዋት ፀሐይ ከተለመደው ንዳዷ ጋር የአዲስ አበባን የቀትር መራራ ፀሀይን ታስከነዳለች፤ እናም አጥበርባሪ ጨረሯን ያለምህረት ስትለቅብኝ፣ ጓደኛዬ መኪና ይዞ እቦታው እስኪደርስ መጠበቁ በገዛ ፍቃድ መለብለብ ስለመሰለኝ፣ በቀጥታ ከተደረደሩት ታክሲዎች አንዱን ይዤ ወደ ከዚራ አመራሁ፤ ድሬ የሄድኩት በዋናነት ከማህበራዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ምክንያት በመሆኑ ሊቀበለኝ የተዘጋጀውን ጓደኛዬን ደውዬ ከማውቃቸው የአንዱን ሆቴል ስም ጠቅሼ እዚያ እንድንገናኝ ነገርኩት፡፡
የሆቴሉ ፍተሻ ከወትሮው ጠንከር፣ ጠጠር ያለ በመሆኑ ትዕግስትን ይፈትናል፡፡ እንዲህም ሆኖ ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ማረፊያ ክፍሎች በሙሉ መያዛቸው ተነግሮን ቀኝ ኋላ ለመዞር ተገደድን፤ ይሄኔም ነው የጓደኛዬ ፊት ልውጥውጥ ሲል ያስተዋልኩት፤ ጭንቅላቴን በማነቃነቅ በምልክት ምን እንደተፈጠረ ጠየኩት፤ ለአፍታ አመንትቶ ከፊት ለፊታችን በግምት አስር ሜትር ርቀት ላይ ወደቆሙ ሁለት ሰዎች ጠቆመኝ፤ ልብ ብዬ አየኋቸው፤ ሁለቱንም ከዚህ ቀደም አይቻቸው አላውቅም፤ ደግሞም በዙሪያችን ከሚርመሰመሱ ሰዎች የተለየ ምንም አይነት ሁኔታ ላስተውልባቸው አልቻልኩም፤ እናም ወደ ጓደኛዬ ዞሬ በግርታ ግንባሬን ቋጥሬ ጥያቄ በተሞላ ዓይን አተኮርኩበት፤ ጓደኛዬም ከሁኔታዬ እንዳልገባኝ ተረድቶ ከሹክሹክታም ዝቅ ባለ ድምፅ ‹‹ደህንነቶች ናቸው፣ እየተከታተሉህ ነው›› አለኝ፤ ቢሆኑስ ታዲያ!? በግዴለሽነት ትከሻዬን እየሰበቅሁ ‹‹ለራሳቸው ጉዳይ መጥተው ሊሆን ይችላል›› ብዬው ወደ ሌላ ሆቴል አቀናን፤ እዛም የተለቀቀ ክፍል አለመኖሩ ተነግሮን ፊታችንን ከእንግዳ መቀበያው ‹‹ዴስክ›› ዘወር ስናደርግ እነዛ ‹ደህንንቶች› ቆመው ተመለከትኳቸው፡፡ አሁን ከልምዴ በመነሳት ክትትል ሊሆን እንደሚችል ለማመን በተቃረበ ጥርጣሬ ተውጬ ሌላ ሆቴል ደርሰን ክፍል ጠየቅን፤ በለስ ቀናንና የሆቴሉን መስፈርት አሟልቼ ሳበቃ ጓደኛዬን ቡና ቤቱ ውስጥ እንዲጠብቀኝ አድርጌ፣ ክፍሉን ከተረከብኩ በኋላ ሻንጣዬን አስቀምጬ፣ ገላዬን ተለቃልቄ፣ ልብስ ቀይሬ ደረጃውን መውረድ እንደጀመርኩ ከሰዎቹ ጋር ፊት ለፊት ተገጣጠምኩ፡፡ የጭንቅላት ሰላምታ ሰጥቼ አለፍኳቸው፤ ምላሽ የለም፤ ፈገግ አልኩ፡፡ ከወዲሁ የሰሞኑ ምስራቅ ኢትዮጵያ አክራሞቴ ምን ሊመስል እንደሚችል አሰብኩና፣ በልጅነቴ ከሰፈር ማቲዎች ጋር የምንጫወተውን የአኩኩሉ ድብብቆሽ አስታውሼ፣ በድጋሚ ለራሴ ፈገግኩ፡፡
ገና ከአዲስ አበባ ስነሳ ማህበራዊ ጉዳዬን ስጨርስ የድሬዳዋ፣ ሐረር እና ሶማሌ ክልልን ወቅታዊ የፖለቲካ ትኩሳት ለማዳመጥ ለተጨማሪ ስድስት ቀናት የሚያቆይ ፕሮግራም አስቀድሜ ይዤ ነበር፤ ከአራት ቀን ቆይታ በኋላም ቀጥታ ወደዚሁ ስራዬ ነበር የገባሁት፡፡ ለጉዳዩ ትኩረት እንድሰጥ ያደረገኝ በቅርቡ ሐረር ከተማ ውስጥ በተከበረው ‹‹የዓለም የመቻቻል ቀን›› ላይ በክልሉ የተንሰራፋው መድልዎና የሐብሊ ተፅዕኖ ተደብቆ፣ ፍትሐዊ አስተዳደር የሰፈነ ለማስመሰል መሞከሩ፤ እንዲሁም ህዳር 29 ቀን በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅጅጋ (ጅግጅጋ) የሚከበረውን ‹ስምንተኛው የብሔር ብሔረሰብ ቀን›ን አስመልክቶ አካባቢውን ከዋጠው ስጋት በተቃራኒው መንግስት እየነዛ ያለው የሀሰት ፕሮፓጋንዳን ከተጨባጩ እውነታ ጋር ለመፈተሽ ፍላጎት አድሮብኝ ነው፡፡
ፊታችሁን ወደ ምስራቅ…
ምስራቅ ኢትዮጵያ ከሀገሪቱ የ3ሺ ዓመት ታሪክ ዕኩሌታውን ሰላምና መረጋጋት የተሳነው ከመሆኑም በላይ፣ ለማዕከላዊ መንግስት የስጋት ምንጭ ሆኖ ነው ዛሬ ድረስ የቀጠለው፡፡ ከአቶማን ተርኪሽ ወታደሮች እስከ አል-ሸባብ ሰርጎ ገቦች ድረስ መተላለፊያ ‹‹ኮሪደር›› ሆኖ አገልግሏል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ ሶማሊያውያን የዘር ግንድ ከጐረቤት ሀገራት ሶማሊያና ጅቡቲ ጋር የሚተሳሰር መሆኑና የሃይማኖትና የኢኮኖሚ ምንጭም ተመሳሳይነት አካባቢውን በበቂ ደረጃ ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እንዳደረገው የፖለቲካ ተንታኞች ያምናሉ፤ ነዋሪዎቹ በቀላሉ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ የሚኖሩ መሆናቸውም ሌላው ችግር እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ ቅኝ ገዥዎቹ የአውሮፓ ሀገራት በበኩላቸው አካባቢውን ‹ፍሬንች ሶማሌ ላንድ›፣ ‹ብሪታኒያ ሶማሌ ላንድ› እና ‹ኢታሊያ ሶማሌ ላንድ› በሚል ከፋፍለው ማስተዳደራቸው፣ ከሶማሊያ ነፃነትም በኋላ የሞቃዲሾን ቤተ-መንግስት የተቆጣጠሩ ገዢዎች ‹ታላቋን ሶማሊያ እንመሰርታለን› በሚል ቀቢፀ ተስፋ ከአንድም ሶስቴ የኢትዮጵያን ወሰን ተሻግረው የኃይል ወረራ መፈፀማቸው የአካባቢውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶት ነበር፤ ከዚያም ባሻገር የዚያድባሬ ሶማሊያ መፈራረስም የቀጠናውን ሠላምና ፀጥታ ከድጡ ወደ ማጡ አድርጎታል፡፡
በዚህ ሁሉ ከባቢያዊ ውጥረት እየታመሰ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ በአንድነት በሐረርጌ ክፍለ ሀገር ስር ሲተዳደር የቆየው የምስራቁ የሀገራችን ክፍል፣ ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ ባነበረው ‹‹ፌደራሊዝም›› በሶስት ሊከፈል ችሏል፤ ‹‹የሶማሌ እና ሐረር ክልል›› እንዲሁም ‹‹የድሬዳዋ አስተዳደር›› በሚል፡፡ ይህ ሁኔታም ከዚህ ቀደም በውጭ ተፅዕኖ ይተራመስ የነበረውን ‹ጂኦ-ፖለቲክስ› ብሔር ተኮር ለሆነ ተጨማሪ አዲስ ቁርቁስ አጋለጠው፡፡ በአናቱም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ ኦጋዴን፣ ጎዴ፣ ደጋሀቡር፣ ቀለፎን የመሳሰሉ ከተሞች ክልሉን ‹እንገነጥላለን› የሚሉት የኦጋዴን ብሔራዊ ግንባር ታጣቂዎች መርመስመሻ መሆናቸው አካባቢውን የስጋት ቀጠና አድርጎታል፤ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ድሬዳዋ ላይ ያነጋገርኳቸውና በሽግግር መንግስቱ ወቅት የአስተዳደሩ አባል የነበሩ አቶ ኡስማን (ለዚህ ፅሁፍ ስማቸው የተቀየረ) ‹‹የዚህ ሁሉ ተጠያቂ ለጣልቃ ገብነቱ ያልተመቹትን የአካባቢው ልሂቃን ‹ለወረራ የመጡ የዚያድባሬ መኮንኖች› እያለ አሸማቅቆ ከፖለቲካው ገፍቶ በማስወጣት ክልሉን ዛሬ ላለው ደካማ አስተዳደር የዳረገው ኢህአዴግ ነው›› ይላሉ፡፡ በግልባጩ የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ ካሳ ተክለብርሃን የተገፉት ሰዎች ኢትዮጵያዊ አለመሆናቸውን ለ‹‹ዘመን›› መፅሄት የገለፀው እንዲህ በማለት ነበር፡-
‹‹ሶማሊያ የፈራረሰበት ወቅት ስለነበር በጣም ትላልቅ የሶማሊያ ተፈናቃዮች የሰፈሩባቸው ካምፖች ነበሩ፡፡ እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ አንዱ የስደተኞች ካምፕ የነበረባት አገር ነበረች፡፡ በተለይ አርትሼክ አካባቢና ሌሎች አካባቢዎችም ትልልቅ ካምፖች ነበሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የመጡ የዚያኛው ሶማሊያ መኮንኖች፣ ሲቪል ሰራተኞች ኢንጂነሮችና ፓይለቶች ነበሩ፤ በአካል ያገኘናቸው የምናውቃቸው እነዚህ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ጋር የሚለያቸው ነገር ስላልነበረ በአብዛኛው በስደተኛነት ከመጡ በኋላ የአካባቢውን የፖለቲካ ስልጣኑንም ያደራጁት እነሱ ነበሩ፡፡ አንዱ ትዝ የሚለኝ ይሄ ነው፡፡ ይሄንን የኢህአዴግ ሰራዊትና ከላይ የሄደው የኢትዮጵያ ሰራዊት ሊለየው አይችልም ብቻ ሳይሆን ያ የመጣውን እንዳለ የሚያቅፍ ሁኔታ ነው የነበረው በአካባቢው፡፡ ስለዚህ ለረጅም ጊዜ ያ ኃይል ነው እንግዲህ አዲስ በተፈጠረው አጋጣሚ የታላቋ ሶማሊያን አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሶማሊያ ላይ ለመዝራት ትልቅ ጥረት ያደረገው››
ይህ ክርክር በራሱ ኢህአዴግ ‹‹ፊታችሁን ወደተረጋጋችው ምስራቅ ኢትዮጵያ (ሶማሊ ክልል) መልሱ›› ያለበት አውድ የተለመደው የቅጥፈት ፕሮፓጋንዳ እንጂ አካባቢው የጦርነት ወረዳን ያህል የሚያሰጋ መሆኑን ያመላክታል ፡፡ እናም ከአርቲስቶች እና ጋዜጠኞች እስከ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ፊት-አውራሪነት የተካሄደው የጉብኝት ፕሮግራም፣ መንግስት ምንም እንኳ የህዝቦችን አንድነት ‹የማጥበቅ ዕቅድ› የሚል የዳቦ ስም ቢሰጠውም፣ ‹ሶማሌ ክልል ፍፁም ሰላም ነው› የሚል የሀሰት ፕሮፓጋንዳን ለመንዛት መሆኑን ለመረዳት በአካባቢው ያለውን የፀጥታ አጠባበቅ ብቻ መመልከቱ በቂ ይመስለኛል፡፡
የቦምባስ ዕገታ
ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ‹‹ሕገ-መንግስታችን ለህዳሴያችን›› በሚል መሪ ቃል የሚከበረው ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች ቀን›› በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅጅጋ በመሆኑ በአካባቢው ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት ለመለካት ረቡዕ ህዳር 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ወፍ ጭጭ ሳይል ነበር ድሬዳዋን ለቅቄ ወደ ሐረር ጉዞዬን የተያያዝኩት፡፡ ይህንን ሰዓት የመረጥኩት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አዲስ አበባ ላይ እንኳ ጋብ እየለ የመጣውን የደህንነት ሰራተኞች ክትትል ድሬዳዋ ላይ በየደረስኩበት ሲያንዣብብብኝ፣ በማስተዋሌ፣ ምናልባት ከዕይታ ውጪ መንቀሳቀስ ብችል በሚል እሳቤ ነበር፡፡ መኪናው ከአንድ ቀን በፊት የተከራየሁትና ድሬ ውስጥ ያልተጠቀምኩበት በመሆኑ፣ በስጋት የሚንጠውን የደንገጎ አቀበትም ሆነ ጥንታዊቷን ሐረር ከተማ አቋርጠን እስክናልፍ አንዳች ችግር አላጋጠመንም፡፡ ይሁንና ከሐረር በግምት 80 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በሶማሊያ ክልል የምትገኘው ቦምባስ ከተማ ደርሰን ጥቂት እንደተጓዝን፣ መኪናውን ዳር አስይዞ እንዲያቆም አንድ የትራፊክ ፖሊስ ለሹፌሩ የእጅ ምልክት አሳየው፤ ይሄኔም ነው ድሬ ላይ እንደ ተሰወርኩባቸው እርግጠኛ ሆኜ በልቤ ከሳቅኩባቸው ሁለቱ ሰላዮቼ ጋር ፊት ለፊት የተፋጠጥነው፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ስሜን ጠርተው አነጋገሩኝ፤ እኔም ከምንም ነገር በፊት መታወቂያቸውን እንዲያሳዩኝ ጠየቅኩ፤ ሳያቅማሙ አሳዩኝ፤ ወዲያውኑም የአፍ መፍቻ ቋንቋው አማርኛ እንዳልሆነ የአነጋገር ዘዬው በግልፅ የሚያስታውቀው አንደኛው የደህንነት አባል፣ ከዚህ በላይ ጉዞውን መቀጠል እንደማልችልና በቀጥታ ወደ ድሬዳዋ መመለሱ እንደሚጠቅመኝ ሊነግረኝ ሞከረ፡፡ ከመገረሜ ብዛት ንግግሩን ለመረዳት ጥቂት ሰከንዶች ፈጅተውብኝ ነበር፡፡ መቼም ይህ ሰው ቀልደኛ መሆን አለበት! አለዛ በገዛ ሀገሬ የት ድረስ መሄድ ወይንም የት ቦታ ጉዞዬን መግታት እንዳለብኝ ሊወስንልኝ ባልደፈረ ነበር፤ ሆኖም ንዴቴን ዋጥ አድርጌ ምን ማለት እንደፈለገ እንዲያስረዳኝ በትህትና ጠየኩት… ይኼኔ ጓደኛው ጣልቃ ገባና ወደ ጅግጅጋ ለመሄድ ማሰቤን እንደደረሱበትና ወደ ከተማው እንድገባ እንደማይፈቅዱልኝ ቆጣና ኮስተር ብሎ አሳወቀኝ፡፡ እኔም ፈርጠም ብዬ እዚህ ድረስ መጥቼ ጅጅጋ ሳልደርስ እንደማልመለስ ቁርጡን ነገርኳቸው፡፡ ቃለ-ምልልሱ እየከረረ ሲሄድ ማስፈራራቱን ወደ ሹፌሩ አዞሩትና በብርቱ ያዋክቡት ያዙ፤ ይህ ድርጊታቸው ያልጠበቅኩት በመሆኑና የሹፌሩንም ምላሽ አለማወቄ መጠነኛ ድንጋጤ አጫረብኝ፡፡ እንደገመትኩትም ሁኔታውን በፍርሃት ተውጦ ይከታተል የነበረው ሹፌር ትንሽ እንኳ ሳያንገራግር መኪናውን ቆስቁሶ ወደ ሐረር አዞረው፡፡
‹‹ምን ሆነሃል?›› አልኩት በንዴት ጮኽ ብዬ፡፡
‹‹ወንድሜ እኔ ቤተሰብ የማስተዳድር ሰው ነኝ፡፡››

Monday, December 2, 2013

Are Medias infected by Woyane disease or simply jiving?

December 2, 2013

Bravery is a trait that is much needed in Media-journalism than any other occupation. Confronting tyranny with bare hand not only require bravery but, principled stand on public interest. When Eskider Nega  and Reyot Alem and many more before them face-off ethnic tyranny that cause so much pain and suffering bare hand on the battle ground there is no whatsoever excuses for anyone in a distance places to decompose their responsibility to the people and stand tall
Every week I glance through all Ethiopian online Medias to catch up with what is happening to my people and country. Beside ESAT and a few online Medias as my primary source of daily news, I take a pick over the rest not so kosher sites to see how far they drift to divert the burning issue of our people for whatever reason they do it.EPRDF/TPLF hiding the truth
Naturally, no one have much expectation from the official TPLF’s pimps for doing the job they are paid to recycle rubbish everyday of the year.  After all they accepted they can’t rise up out of rubbish recycling business. I can understand the motivation to take the low road and to remain down there for too long. But, the real problems are the rest of Medias that claim to be free but drift allover the map aimlessly; distracting the struggle to rid the ethnic tyranny we are condemned under.
After observing the online Medias for extended period I came to conclusion that, either they are infected with Woyane disease or simply jiving us on their responsibility. It could also be their ambition clouding their mind to use Media as a vehicle to achieve their other agenda.
First thing is First
When it comes to real Media, for that matter political party or civic organization the ultimate measure is how intensely they go after things that are important for the public interest. And, what is important is not what tyranny claim it did or does to jive the public to stay uninvited.
Therefore, if people are under tyrannical rule like we Ethiopians are, Free Media duty is to go after the brazen ruling regime that is killing and robbing our people. Likewise, if people are under democratic rule like Americans are, it is to go after the elected representatives to see if they are doing the job they elected to do or goofing around to fill their pocket book with corruption.
It might sound too idealistic for some of our contemporary elites that made public interest an academic or ideological exercise to generate paper in abandoning our people for tyranny or foreign perks they can put their hands on. But, many brave souls stood firm for the public interest and made it possible for their people to live free of tyranny.  Ethiopians have our own brave souls on the frontline that paid and paying with their lives and limbs as a vanguard of the people’s interest. If only we all back them up to free us from tyranny.
Unfortunately, those that can’t tell the difference between public interest and petty interest became noxious in society to prolong the life of tyranny. Therefore, in tyranny ruled nation like Ethiopia there is absolutely noting better for any Media, political party or organization as important as going after tyranny until it unconditionally surrenders for the people will.
Thus, when one observe reports, news pieces or anything that resemble recycled rubbish that shouldn’t belong in any self-respecting ‘Free Media’ we can’t help but say it isn’t kosher and make sure it never get away.
What isn’t KOSHER?
The very meaning of ‘Free Media’ is to be the adversary of tyranny period. In other word, the first and only priority of Free Media is to be the vanguard of the public interest. Thus, rejecting anything tyranny isn’t only a duty but the guiding principle that drives Free Media. Therefore, entertaining direct and indirect rubbish coming out of tyranny isn’t only kosher but, in bad taste; if not a crime against the public interest.
Let’s take few examples of not so kosher way of massaging rubbish and presenting it as worthy news.  Content sourced from tyranny via a third party or unverifiable sources’ with off the wall story and the untimely content that distract from the pressing issue are some of the  substandard news to qualify for Free Media reporting that doesn’t worth the ink and space wasted on it.
For example ‘India can partner Ethiopia in space technology’ by IANS (Indo-AsianNews Service).
It says
‘Addis Ababa, Nov 28 (IANS) With Ethiopia launching a new space programme last month, India can have a promising partnership with Africa in this frontier technology, India’s outgoing ambassador here has said’
It goes on to say… can…should…would… with absolutely no verifiable value worthy of news. It is also tacky for a Media to provide a personal Gmail contact; ‘Hadra Ahmed can be reached at hadraahmed@gmail.com (It isn’t clear Hadra works for Ethiomedia or IANS where the news suppose to originate)
Another one is from AFP titled ‘Over 50,000 illegal Ethiopian workers sent home from Saudi Arabia’  quoting the Ethiopian Foreign Ministry.
It says,
ADDIS ABABA (AFP) – Ethiopia has flown home over 50,000 citizens in Saudi Arabia after a crackdown against illegal immigrants in the oil-rich state, the foreign ministry said Wednesday.
Strangely, the Foreign Ministry’s website doesn’t claim 50,000 returned but estimate the total numbers to be between 50 to 80 thousands.
But, given the urgency of the crises in Saudi Arabia and knowing what the brazen Woyane regime is capable, the last thing Ethiopians expect from ‘Free Media’ is what a departing Indian diplomat’s wild imagination on space exploration may be or worthy news from the regime’s sources. For that we have Reporter and Addis Fortune or more like Mis-Reporter and Mis-Fortune
What possible value could water down reporting and unverifiable sourced news serves the public interest?
If the message is to say the regime is doing its job repatriating migrant workers or Ethiopia under Woyane is advancing in space technology to send satellite or space crew to the orbit just because some foreigner said so, it is a deliration of duty that wouldn’t be expected ‘Free Media’ based in the free world.
Another example of not kosher news is from Tadias Magazine titled NYC Ethiopians Make Presence Felt at the Saudi Mission to the United Nations
By Tadias Staff on Wednesday, November 20th, 2013
‘New York (TADIAS) — Ethiopians in New York made their presence felt outside the Permanent Mission of Saudi Arabia to the United Nations on Monday, November 18th.’
The water down report that supposed to cover a demonstration titled it ‘Ethiopians make their presence felt’ and picked a featured picture of one woman out of the 100s at its disposal. It added ‘diverse crowd included members of the Caribbean and other African communities joining fellow Ethiopians’ and completely ignored the 100s of report to the role of the ruling Ethiopian regime that was also the target of the demonstration all over the world. It also failed to interview the demonstrators as one would expect from ‘Free Media”.
Is it possible Media can be more than water down report or cut-and-paste flyby news coming from every direction that suit someone’s wishes, imagination, fantasies and illusions?  If that isn’t the case, how is it people waste valuable time and misuse technology that can be better used for the ‘real thing’ intended? Better yet, what is the use of Free Media if it isn’t to squeeze tyranny and its riffraff that live-off the sweat and blood of the people?
Seriously, what would make full grown adults with all the opportunities the free world offers them (knowledge, freedom, technology, access…) without contributing a penny to make it turn around and reduce such privilege to undermine the very people and country that struggle for the same privilege?
Could it be fear, corruption or lack of confidence that rattle their mind to make them a walking danger for public interest?
Personally, when it comes guarding the public interest I don’t see much effort in most Ethiopian online Medias.  The two examples are not isolated incidence. Opinion aside, wouldn’t it be nice for Medias to do investigative reporting on what is important to our people? Say for example, why the brazen regime is wasting public money to buy telescope (‘explore space’) when it couldn’t put up temporary shelter on earth to Ethiopian migrant workers it trafficked in the Middle East and claim to repatriate? How it is a country under Woyane where having an e-mail is a luxury buying telescope turned into exploring space worthy of  news?
Better yet, couldn’t it be more productive if Free Medias goes, say after EFFORT and its army of corrupt merchants-of-death that is robbing the country blind so that the money can be recovered and used for public good? What about confronting the self-declared ethnic Apartheid regime to surrender for democracy? I mean; the real things that make a difference.
On the more urgent issue of the suffering of our people, how come the ‘Free Media’ not looking into the estimated 400 ‘employment agencies’ permitted by the regime’s Labor Ministry to traffic humans in the name of job opportunity? Are these agencies TPLF owned business enterprises in human trafficking? Questions and more question …investigation and more investigation in public interest.
I almost gave up on most of Ethiopian online Medias until ESAT showed up and changed the Media landscape. The very existence of ESAT– rattling tyranny to see the screaming of its stooges and apologists by itself is priceless. When we add what ESAT does to educate us it is worth billions of dollars of free lessons. In fact, the messengers of tyranny and poverty should contribute double for being freed from recycling rubbish.
While we are at it, I recommend establishing The ESAT Foundation and give at least 10% of our income and to allow us to leave our Estate for the Foundation. After all, as we are obligated to give for spiritual reasons, what could be a better cause than freeing our mind from rubbish propaganda?
In conclusion, if you call yourself ‘Free Media’ and happen to neglect your responsibility Ethiopians are watching. The day of impunity is closing faster than you think. Shape-up-or-ship-out is the message that would ring more and more frequently.
As the struggle for democracy intensifies, the responsibility of Free Media is noting more than to stand guard for public interest. If you are not up to it, say so and do what you do best.
Freedom from tyranny is coming; there is no way around it. The question for one-and-all of us is ‘to-be-or-not-to-be’ on the right side of history. When it comes to the Media, it is ‘‘to-be-or-not-to-be’ free in defending the public interest from tyranny and its riffraff. Whichever sides of history we choose determine our fate. For sure, there is no glory to be on the side of tyranny. It is the last place a self respecting person chooses.
The article is dedicated to our suffering people under the medieval kingdoms of Arabia and at the hand of the self-declared ethnic regime of Ethiopia.

የወያኔ አገዛዝ በመልዕክተኞቹ በኩል ላቀረበው የ“እንደራደር” ጥያቄ ከግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ምላሽ

December 2/2013
ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የገነባዉ ሥርዓት በከፍተኛ ችግሮች የተወጠረ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የመሪው ሞት በወያኔ መሀል ያስከተለው ቀውስ፤ የሕዝብ ሁለገብ ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበት መሄድ የፈጠረበት ስጋት እና ምርጫ በደረሰ ቁጥር የሚደርስበት ጭንቀት መጨመር ተደማምረው ውጥረቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እያደረሱት መሆኑን የሚያሳዩ በቂ ምልክቶች አሉ። የእስካሁኑ ተሞክሮዓችን እንደሚያሳየው ወያኔ ውጥረት ሲበዛበትና መዉጪያና መግቢያዉ ሲጠፋዉ ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችን “እንወያይ፣ እንደራደር” በማለት ለውጥረት ማስተንፈሻ ጊዜ የሚገዛ መሆኑን ነው። ሰሞኑን በወያኔ አገዛዝ መልዕክተኞች በኩል የደረሰንን “የእንደራደር” ጥያቄ ንቅናቄያችን በዋናነት ያየው ወያኔ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም እየሞከረ መሆኑን ነው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘው ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በሰላማዊ መንገድ በሚደረግ ትግልና በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረጉ ዉይይቶች ቢመጣ የግንቦት 7 ምርጫ መሆኑን ንቅናቄያችን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። ግንቦት 7ን ሁለገብ ትግል ውስጥ እንዲገባ ያስገደደው የወያኔ እምቢተኝነትና እብሪት ብቻ ነው።
የግንቦት 7 ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰሞኑ የወያኔ የእንደራደር መልዕክት እንደደረሰው በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ባጠቃላይ እንጂ ግንቦት 7ን ብቻ የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነ ከድምዳሜ ላይ ደርሷል። ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ከሚያደርገው ትግልና እየከፈለ ካለው መስዕዋትነት ጋር በቀጥታ ግንኙነት አለው። በመሆኑም፤ ለቀረበልን ጥያቄ ግልጽ መልስና፤ ድርድር ስለሚባለው ጉዳይም ያለንን አቋም ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከተው የኢትዮጵያ ሕዝብና የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ ለማቅረብ የሚያስችል ተጨማሪ አጋጣሚ አድርገን ወስደነዋል። በዚህም መሠረት ለቀረበልን ጥያቄ የሰጠነዉን መልስና አቋማችንን በድርጅታችን ድረ ገጽ ላይና በሌሎች መገናኛ ብዙሀን በኩል በይፋ ለመግለጽ ወስነናል።
በድርድር ስለሚመጣ ለውጥ ያለን የመርህ አመለካከት:
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንዳደረግነው ድርጅታችን ከምሥረታው ጀምሮ የትግል ስልቱን ሲወስን እምነቱ አድርጎ የተነሳው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በሀገራችን በሰላማዊ መንገድና በድርድር ቢመጣ በእጅጉ የሚፈልገውና የሚመኘው መሆኑን ነው:: ድርጅታችንን ወደ ሁለንተናዊ ትግል የገፋው በመግቢያው ላይ እንደገለጽነው የወያኔ እብሪት ብቻ ነው:: የቀረበልን ምርጫ በባርነትና በውርደት መኖር ወይም ለነፃነት እየታገልን መሞት ቢሆን ኖሮ ንቅናቄያችን የሚመረጠው ምን ግዜም ለነፃነትና ለአገር አንድነት ታግሎ በክብር መሞት መሆኑን በተደጋጋሚ ለሕዝብ ግልጽ አድርገናል። ይህ የማይናወጥ አቋማችን ደግሞ ለይምሰል የተቀመጠ አቋም ሳይሆን ከልባችን የምናምንበትና ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አባላቶቻችንን ያሰባሰብንበት አቋም ነው። ዛሬ በትግሉ ግንባር የምንንቀሳቀሰውና ወደ ግባችን የሚወስደንን ተጨባጭ እርምጃዎች እየወሰድን ያለነውም በዚሁ አቋማችን ዙሪያ ነዉ።
ይህ አቋማችንና እምነታችን በአንድ ላይ ጎን ለጎን የሚሄዱ ሁለት መርሆችን አጣምሮ የያዘ ነዉ። አንደኛው፣ ሂደትን በሚመለከት ሁሌም ለድርድር ክፍት መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ፣ ይህ የድርድር ሂደት እንዲያው ለለበጣ የሚደረግ ሳይሆን ወደሚፈለገው ነጻነት በአነስተኛ መስዕዋትነት ሊያደርስ ይችል ከሆነ በሩን ላለመዝጋት እንጂ፣ በምንም አይነት ዋና ውጤቱን፤ ማለትም ኢትዮጵያን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሀገር ማድረግን፤ የሚቀይር ወይንም ከዚያ ያነሰ ውጤትን ለመቀበል መፍቀድን ፈጽሞ የማያመለክት መሆኑን ነው::
በእኛ በኩል ድርድሩን አስፈላጊና ጠቃሚ የሚያደርጉት መነሻ የፖለቲካ እሳቤዎችም ከእነኝሁ ሁለት መንታ ገጽታዎች የሚመነጩ ናቸው:: በድርድር ለሚገኝ ፍትሀዊና እውነተኛ ውጤት ክፍት መሆናችንን ሁሌም እናሳያለን፤ ነገር ግን ይህን የምናደርገው የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባትን ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚጠይቀውን ማንኛውንም መስዋዕትነት መከፈል አለበት የሚለውን መሠረታዊ የአካሄድ መርህ በመመርኮዝ እንጂ መርሀችንን ለድርድር ለማቅረብ እንዳልሆነ በግልጽ መታወቅ ይኖርበታል::
ስለዚህም:
ሀ)    የድርድሩ ውጤት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ያረጋገጠ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በአስቸኳይ እውን ማድረግ መሆን ይኖርበታል:: ይህ ዋናው ግብ ሆኖ ከዚህ በመለስ የሚኖሩ በሂደት የሚገኙ አነስተኛ ግቦች ሊኖሩ ይችላሉ (ለምሳሌ የፖለቲካ እስረኞች ማስፈታት…ወዘተ):: ሆኖም በምንም አይነት ለእነኝህ መለስተኛ ግቦች ተብሎ ዋናውን ግብ የሚያሳጣ ወይንም ጊዜውን ያላግባብ የሚያስረዝም ድርድር፣ ድርድር ነው ብሎ ድርጅታችን አይቀበልም። ስለዚህም ዋናው የድርጅታችን ዓላማና ግብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ፣ በፍጹም ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም:: በሥልጣን ላይ ባለው ኃይል በኩል ወደዚህ ግብ ለመድረስ ቁርጠኝነቱ በሌለበት ሁኔታ በሚደረግ ማንኛውም አይነት ድርድር ውስጥ ግንቦት 7 አይሳተፍም::
ለ)  በግንቦት 7 እምነት ማንኛውም ድርድር ወያኔ ከግንቦት 7 ጋር በተናጠል የሚያደረገው ሳይሆን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሁሉንም የፖለቲካ ኃይሎች ያካተተ መሆን ይኖርበታል:: ድርጅቶችን በተናጠል እየለያዩ “እንደራደር” ማለት በራሱ ጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ስሌትን የያዘ እሳቤ እንጂ፣ በዘላቂነት አገሪቱን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ አገር ለማድረግ መፈለግን አያመለክትም:: ለአንድ ድርጅት ለብቻው የሚመጣ ወይም የሚጠቅም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የለም:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመፍጠር ፍላጎት ያለው ድርድር በአገሪቱ ያሉትን የተለያዩ የፖለቲካም ሆነ የሲቪክ ኃይሎችን ያካተተና ያመኑበት መሆን ይኖርበታል:: የሚደረገው ድርድርም ማን በስልጣን ላይ ይውጣ ወይንም የፖለቲካ ስልጣንን ባሉት ኃይሎች መሀከል እንዴት እናከፋፍለው የሚል የስልጣን ቅርምት ድርድር ሳይሆን፤ ሕጋዊና የሕዝቡን የሥልጣን ሉዓላዊነት ባረጋገጠ ሁኔታ የፖለቲካ ስልጣን እንዴት እንደሚያዝ ፍትሀዊ የሆነ ሂደትን ለማስጀመር የሚደረግ ድርድር መሆን አለበት::
ሐ) ቀደም ብለን እንደጠቀስነው ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አንድን ድርጅት ወይንም የፖለቲካ ድርጅቶችን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ነው:: ይህ እስከሆነ ድረስ እንዲህ አይነት ድርድር ከሕዝቡ በተደበቀ ሁኔታ በሚስጥር የሚካሄድበት ምንም ምክንያት የለም::
2)   ከዚህ በፊት ከወያኔ ጋር ከተደረጉ ድርድሮች ያገኘናቸው ተመክሮዎችና ከዚህ በመነሳት ወደፊት በሚደረጉ ምንም አይነት ድርድሮች እንዳይደገሙ ለመጠበቂያ የሚሆኑ ከአሁኑ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች
ከማንኛውም ወገን ጋር የሚደረግ ድርድር የተደራዳሪዎቹ ምንነት፤ ውስጣዊ ባህርያቸውን፤ ከተለምዶ ተግባራቸው ያላቸውን ተአማኒነትና ወደዚህኛው ድርድር ያመጣቸውን ምክንያቶች በበቂ ከመገንዘብ ጋር ተያይዞ የሚታይ ጉዳይ ነው:: ቃሉን አክባሪና ተዓማኒ ከሆነ ሰው ጋር የሚደረግ ድርድርና ያለፈው ታሪኩ ምንም አይነት የተዓማኒነት ባህርይ ከማያሳይ ቡድን ጋር የሚደረግ ድርድርም ሆነ ለድርድሩ የሚደረግ ዝግጅት ለየቅል ናቸው:: ይህ ማለት ግን ተዓማኒነት ካለው ኃይል ጋር ብቻ ነው ድርድር የሚካሄደው ማለት አይደለም:: በፍጹም ተዓማኒ ካልሆነ ኃይል ጋር የሚደረግ ማንኛውም ድርድር ግን ድርድሩ በእርግጥም ተግባራዊ ሊሆን የሚችል መሆኑን የሚያሳዩ ጠንካራ መጠበቂያዎች (System of Verification) እንዲሁም ግልጽ የመተግበሪያ ሥርዓቶች (Implementation Mechanism) ሲደረጉለት ብቻ ነው ከምር ሊወሰድ የሚችለው:: ከዚህም ባሻገር ግን መጀመሪያውኑ ወደ ድርድር የሚመጣው ለጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ሳይሆን በእዉነተኛ መንፈስ ከድርድር የሚመጣውን ውጤት በመፈለግ መሆኑን የሚያሳዩ “የመተማመኛ” ምልክቶች ሲያሳይ ነው በእርግጥም ወደ ድርድር የመጣው ከልቡ ድርድሩንና ከድርድሩ የሚመጣዉን ዉጤት ፈልጎ መሆኑን ለማመን የሚያስችለው::
ወያኔ ከተቀናቃኝ ወገኖች ጋር “ድርድር” ሲያደርግ የመጀመሪያ ጊዜዉ አይደለም:: እኛ እስከምናውቀው ድረስ ምናልባት በኃይል ይበልጡኛል ብሎ ከሚያምናቸው ወገኖች ጋር ካልሆነ በስተቀር፣ በረሃ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ በማንኛውም ጊዜ ለቃሉ ታማኝ፤ ለመርሁ እውነተኛ፤ ለደረሰበት ስምምነት ተገዢ ሆኖ አያውቅም:: ይልቁንም ሶስተኛ አደራዳሪ ወገኖችን በሚያሸማቅቅና በሚያሳፍር መልኩ ውሸትን እንደ አዋቂነት፤ ማጭበርበርን እንደ ብልጠት፤ የተስማማበትን በገሀድ ማፍረስን እንደ የአመራር ብልሀት አድርጎ የሚያይ፤ ምንም እፍረትና ጨዋነት የሚባል ነገር ያልፈጠረበት እኩይ ኃይል ነው:: ከራሱ የድርጅት ጥቅምና በስልጣን ከሚገኝ የዝርፊያ ሀብት ማካበት ባሻገር፤ ለአገር ዘላቂ ጥቅም ብሎ የራሱን ጥቅም አሳልፎ የሚወስደው ምንም እርምጃ እንደሌለ በተግባር በተደጋጋሚ ያረጋገጠልን ኃይል ነው:: በግንቦት 7 ውስጥ ያለን ወገኖች ይህንን የወያኔ ባህርይ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ ሌሎች ጽፈውት ያነበብነው ሳይሆን፣ እራሳችን በተግባር በተሳትፈንበት ሂደት ያገኘነው ጥልቅ ግንዛቤ ነው:: ይህንን ደግሞ በአንድ አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን ከድርጅቱ ታሪክ ጋር የተጣበቀ፤ በአመራር አባላቱ ላይ እንደ ግል ባህርይ የሰረጸ መሆኑን እስክንገነዘብ ድረስ በተደጋጋሚ የተመለከትነው ነው:: ስለዚህም ከዚህ ኃይል በኩል የሚመጣን የ “እንደራደር” ጥያቄ ከዚህ በፊት እንዳደረገው ለገባበት የፖለቲካ ውጥረት ማስተንፈሻ፣ ለውሸት ፕሮፓጋንዳው መጠቀሚያ፤ ለጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ መሰብሰቢያ፤ የዴሞክራሲ ታጋዮችን ትጥቅ ማስፈቺያና ወኔ መስለቢያ አድርጎ እንዲጠቀምበት በፍጹም አንፈቅድለትም:: ስለዚህም ከላይ በመርህ ደረጃ ከጠቀስናቸው ሶስት ጉዳዮች በተጨማሪ ምንም ዓይነት ድርድር ከመደረጉ በፊት ወያኔ ጉዳዩን ከምር የወሰደው መሆኑን የሚያሳዩ “የመተማመኛ” እርምጃዎች መውሰድ አለበት ብለን እናምናለን::
እነኝህም፣
ሀ)  ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች፤ ጋዜጠኞች፤ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት:: ይህ ደግሞ በግልጽ     የሚታወቁ እስረኞችን ብቻ ሳይሆን በድብቅ የተቋቋሙ ማጎሪያና ማሰቃያ ቤቶች ያሉትን ሁሉ ማጠቃለል አለበት።
ለ)  በሕዝብ በተለይ በተቃዎሚ ኃይሎች ላይ ወያኔ በየቀኑ እያካሄደ ያለውን ወከባና እንግልት ባስቸኳይ ማቆም፣ ሰብዓዊና የዜግነት መብታቸውን ማክበር አለበት።
ሐ)   በፖለቲካ ምክንያት ከዚህ በፊት የተወሰዱ ሁሉም ዓይነት ፍርድ ተብዮ ውሳኔዎች እንዲሻሩ ማድረግ፤ በሂደት ላይ ያሉ ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ምንም አይነት ክሶችን ማቋረጥ አለበት።
መ)   ሕዝብን በፍርሃትና በስጋት ለማቆየት ሆነ ተብለው የወጡ አፋኝ ህጎችን በአስቸኳይ ማንሳት አለበት።
ሠ)   ማንኛውም ድርድር ገለልተኛ የሆኑ ሶስተኛ ወገኖች ባሉበት፤ የድርድሩ ሂደት በምስልና በድምጽ ተቀርጾ በገለልተኛ ወገኖች እጅ ብቻ የሚቀመጥ፣ የድርድሩ ቦታም የተደራዳሪ ወገኖች በጋራ በሚስማሙበት ቦታ መሆኑን መቀበልና ይህንንም በግልጽ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ አለበት።
እነኝህ ከላይ ያስቀመጥናቸው በወያኔ በኩል የሚወሰዱ “የመተማመኛ” እርምጃዎች ለተቃዋሚዎች ተብሎ የሚወሰዱ እርምጃዎች አይደሉም:: ወያኔ እነዚህን እርምጃዎች ለመውሰድ ቁርጠኝነት ሳይኖረው ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት የሚደረግ ድርድር ላይ ከምር ይሳተፋል ብለን ማመን በፍጹም ስለማንችል ነው ::
እስከዚያው ድረስ ግን ግንቦት 7ም ሆነ ሌሎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት በቁርጠኝነት የምንታገል ኃይሎች፣ ወያኔ እነኝህን የመተማመኛ እርምጃዎች እስኪወስድና ቀደም ብለው በተቀመጡት መርሆች መሠረት በሚደረግ ድርድር በተግባር ሊመነዘር የሚችል ስምምነት፣ አልፎም ለምንም አይነት ማጭበርበርና መንሸራተት እድል የማይሰጥ ጠንካራ መጠበቂያዎች መኖራቸው እስኪረጋገጥ ድረስ፣ የጀመርነውን ትግል ይበልጥ አጠናክረን የምንገፋበት እንጂ በምንም አይነት ለአንድ አፍታም ቢሆን በድርድር ስም የማንዘናጋ መሆኑን አበክረን እናስታውቃለን::
የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ፣
ኅዳር 23፣ 2006 ዓ:ም

አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤ ክፍል ሁለት (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም )

December 2, 2013
አበሻ ድግስ ይወዳል፤ ድግስ የሚወደው መብላትና ማብላት ስለሚወድ ነው፤ ለመብላት የአበሻ ምክንያቱ ብዙ ነው፤ ልጅ ተወለደ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ክርስትና ተነሣ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ አገባ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ሞተ ብሎ መብላት ነው፤ አበሻ ሰው ቀብሮ ሲመለስ በንፍሮ ይጀምርና ቀስ በቀስ ወደሌላው ይተላለፋል።
Prof. Mesfin Woldemariam
Prof. Mesfin Woldemariam
ሃይማኖትም ቢሆን ለመብላት ካልሆነ የነፍሱ ጉዳይማ በጣም ሩቅ ነው፤ ሕያዋን ለነገሥታት፣ ሙታን ለካህናት ይገብራሉ፤ በሚለው መመሪያ መሠረት
ግብር መቀበል ያለ ነው፤ ክርስቶስ ተወለደ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ተጠመቀ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ሞተና ተቀበረ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ተነሣ መብላት ነው፤ ማርያም አረገች መብላት ነው።
ማኅበርም የሚጠጣው (የሚበላው ለማለት ነው፤) ለመብላት ነው፤ አምላክ በተለያዩ ስሞቹ፣ ቅድስት ማርያም በተለያዩ ስሞችዋ፣ መላእክት፣ ቅዱሳን፣ ሰማዕታት ሁሉ ለመብላትና ለማብላት ያገለግላሉ፤ ወደመንግሥተ ሰማያት ለመግባት አማላጅ ሊሆኑ የሚችሉ ሁሉ ማኅበር ለመብላት ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ፤ የሌሎች አገሮች ክርስቲያኖች በመብል አይመለሱም፤ ገበያቸው በጠገራ ብር ነው፤ ስለዚህም አብሮ መብላት ብሎ ነገር የለም።
አበሻ የሚበላው የመጣውን ሲቀበል ብቻ አይደለም፤ የሚሄደውን ሲሰናበትም መብላት ይወዳል፤ ሞትም ቢሆን ለመብላት ምክንያት ነው፤ ቀብር ብሎ እዝን እያቀረቡ መብላት ነው፤ ሠልስት ብሎ መብላት ነው፤ ለሰባት መብላት ነው፤ ለዓርባው መብላት ነው፤ የሙት-ዓመት ደግሶ መብላት ነው፤ በቀብር ላይም ቢሆን ለቅሶውም ‹‹ሆዴ! ሆዴ!›› ነው።
ለአበሻ ጾምም ቢሆን ለመብላት ነው፤ የጾም ትልቁ ምሥጢሩ ምግብ እንዲናፍቅ ለማድረግ ነው፤ የፍስኩ የተትረፈረፈ ምግብና ጥጋብ ባይኖር ማን ይጾማል? የለየላቸው ጠጪዎች በሁዳዴ መለኪያውንና ብርጭቆውን አርግፍ አድርገው የሚተውት ሲፈሰክ በናፍቆት ዊስኪውንና ቢራውን ለመጋት ነውኮ! ይህ ባይሆን አንድ ጊዜ ሞጣ ያየሁትየበግ ሌባ ለምን ይጦም ነበር? ታሪኩ እንዲህ ነው፤ በሞጣ አውሮጵላን ማረፊያ አንድ የበግ ቆዳ የያዘ ሰውዬ በፖሊሶች ይጠበቃል፤ እንደሰማሁት በግ ሰርቆ ጫካ ይወስድና ቆዳውን ገፎ ለመሸጥ ወደገበያ ሲሄድ ተይዞ ነው፤ የሁዳዴ ጾም ስለነበረ ሥጋውን ለማይጾሙ አውሬዎች ጫካ ውስጥ ጥሎ ነው! አሁን ይህ ሰውዬ የሚጾመው ሲፈሰክ ደህና አድርጎ በናፍቆት ለመብላት ካልሆነ ለሌላ ለምንድን ነው ሊባል ነው?
ሥራም ቢሆን ለመብል ነው፤ ከመኝታው ሲነሣ ጀምሮ እስኪተኛ ቢበላ ደስታውን አይችለውም፤ለገና፣ ለፋሲካ፣ ለእንቁጣጣሽና ለመስቀል ለገናና ለፋሲካ፣ ለእንቁጣጣሽና ለመስቀልም ከሌሊት ጀምሮ ከአንዱ ቤት አንዱ ቤት እየተዘዋወሩ በመብላት ቀኑ ያልፍ የለም እንዴ! በእውነት አበሻ መብላት የሚወደውን ያህል ማብላትም ይወዳል፤ ስሞት! ስቀበር! አፈር ስገባ! … ወዘተ. እየተባባለ የጠገበውን ሰው በቁንጣን እንዲሰቃይ ማድረግ የአበሻ ልዩ የፍቅር መግለጫ ነው! መጎራረስም አለ፤ ፍቅርና ጉርሻ ሲያስጨንቅ ነው እየተባለ ፍቅርና ሆድን ያያይዛል፤ አነጋገሩ አበሻ ለመብላት ያለውን እንጂ ፍቅርን አይገልጽም፤ ማሰጨነቅንና ፍቅርን ምን አገናኛቸው! አበሻ ሌላም ተረት አለው፤ የወለዱትን ካልሳሙለትና የሠሩትን ካልበሉለት ደስ አይለውም ይባላል፤ የልጅ ፍቅር ከምግብ ፍቅር ጋር ተስተካክሎ የቀረበ ይመስላል፤ ደሞም ብቻውን የበላ ብቻውን ይሞታል፤ ይላል፤ ጉድ ነው! ሲሞትም ተከተሉኝ የሚል ይመስላል!! ለነገሩማ ፍቅርምኮ አበሻ ዘንድ ምግብ ነው፤ ሆዴ! አንጀቴ! ጎንደሬዎች ሲያሳምሩት ደግሞ ራቴዋ! ይሉታል።
ዛሬ ዛሬ አበሻ ከማብላት ይልቅ ማጠጣት ይወዳል፤ እስቲ ሰዎች ሰብሰብ ብለው በሚጠጡበት ቦታ ብቅ በሉ፤ ያቺን የፈረደባትን ጉበት ለማቃጠል በአቦ፣ በሥላሴ የማይል የለም፤ ቸገረኝ ብሎ ገንዘብ የሚጠይቅ አይምጣ እንጂ ለማብላትና ለማጠጣት፣ ለአንድ ጥሪኝ ፈሳሽ አበሻ ቸር ነው፤ በላኤ ሰብስ በማርያም ስም አንድ ጥሪኝ ውሀ ሰጥቶ አይደለም እንዴ የበላው ሰው ሁሉ የተሰረዘለት? አበሻ በሆድ አይጨክንም።
ለአበሻ ምግብ ክቡር ነው፤ ስለዚህም ምንም ነገር ሲበላ ተቀምጦ ነው፤ ፈረንጅ ቂሉ በየመንገዱ እንደመጋዣ ያመነዥካል፤ በየመንገዱ ማመንዠክ ምግቡን ማዋረድ ነው፤ ከዚያም በላይ ቆመው ሲበሉ ወደጉልበት ይወርዳል ይላል፤ ለአበሻ ጨጉዋራና ጉልበት በቀጥታ የተገናኙ ናቸው፤ ሳይንሱ የሚለው ሌላ ቢሆንም አበሻ አበሻ ምን ቸገረው?
ለመሆኑ ከሆድ ጋር ያልተያያዘ ነገር አበሻ ምን አለው? ነገርን በሆድህ ያዘው ምን ማለት ነው? ነገርን ማብላላት የማሰብ ምትክ መሆኑ ነው፤ ልጆች ሆነን አይጥ አበላሁት እንል ነበር፤ አሸነፍሁት ለማለት ነው፤ ዛሬም ቢሆን ቁማርተኞች በላሁ-ተበላሁ ይባላሉ፤ አይጥ ከማብላት ገንዘብ ወደማብላት ተለወጠ እንጂ ከሆድ አልወጣም፤
አበሻ በሆዱ የማይዘው ምን ነገር አለ? ፍቅርም፣ ጥላቻም በሆድ ነው፤ ቂምም በሆድ ነው፤ ምኞትም ፍላጎትም በሆድ ነው፤ ተስፋም በሆድ ነው፤ መጥኔ ይስጠው የአበሻ ሆድ! ሁሉን ከተናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል፤ አይ የአበሻ ሆድ! የነገር ስልቻ ከመሆኑ በላይ ነገር አልቆበት ‹‹ነገር እንዳይርበው(!)›› ጥንቃቄ ማድረግ አለበት! የአበሻ ሆድ እህል ቢያጣና ከእህል ባዶ ቢሆንም ከነገር ባዶ መሆን የለበትም፤ እህል ቢጠፋም ነገር አይጥፋ!
የአበሻና የሆድ ነገር በዚህ አያበቃም፤ አበሻ ሲያመው ቡዳ በልቶት ነው፤ ቆንጆውን ሁሉ ቡዳ ይበላዋል፤ ልብ በሉ ለአበሻ በዓይንም ይበላል ማለት ነው! አንዳንዴም ሲያመው መድኃኒቱ ምግብ ነው፤ ለሆድ ቁርጠት ብላበት፤ አበሻ ሲሞትም ለቅሶው ሁሉ ስለሆድ ነው፤ ‹‹የኔ ሆድ፣ ሆዴ እንዴት ይቻለው! ፋሲካን የት ልፈስክ?››
እስከናካቴው ‹‹ሆድ›› የሚባል ቃል ከአበሻ ቋንቋ ፈጽሞ ቢሰረዝ ቋንቋው ብቻ ሳይሆን አበሻም ጉድ ይፈላበታል፤ አእምሮ፣ ኅሊና የሚባሉትን ቃላት አበሻ አያውቃቸውም፤ ተግባራቸውንም ሁሉ ለሆድ ሰጥቶታል።