Wednesday, November 27, 2013

የግንቦት7 እና አክራሪ የእስልምና ሀይሎች በኢህአዴግ አባላት ስም ፓርላማውን በመቆጣጠር ኢህአዴግን ሊጎዱት ይችላል ሲሉ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ተናገሩ

November 26/2013
ህዳር ፲፯(አስ ሰባት )ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ይህን የተናገሩት ” በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደው የፖለቲካ እንቅስቃሴ የመንግስት ቀጣዩ የምርጫ ፈተና” በሚል ርእስ ለኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ባቀረቡት ጽሁፍ ነው።
ኢሳት የሚኒስትሩን  ሙሉ ንግግር የያዘ ሰነድ የደረሰው ሲሆን፣ በሰነዱ ግርጌ ላይ ” ለመደበኛ አባላት የማይነገር፣ ለከፍተኛ አመራሮች ብቻ” የሚል ተጽፎበት ይታያል።  በዚህ ርእስ ስር ደግሞ ” ቀጣዩ የምክር ቤት አባላት ምርጫ የግንቦት ሰባት እና አክራሪ እስልምና ሀይሎችን የሚያስቀጥሉ አባላት ወንበሩ በኢህአዴግ አባላት ስም ሊነጠቅ ይችላል። ” ብሎአል። ሚኒስትሩ ለዚህ አስተሳሰባቸው የምርጫ 97ትን ሁኔታ እንደማጠቃሻ ተጠቅመዋል። ” የ97 የቅንጅት አሸናፊት አካሄድ ስልት ማለትም የተቃዋሚ አባላት ሁነው በህቡእ ተደራጅተው በኢህአዴግ የአባላትን ካርድ ሙሉ በሙሉ ፓርቲውን ሊጎዱት ይችላሉ” ሲሉ ሚኒስትሩ ጽፈዋል።
ሚኒስትሩ በዚህ ጽሁፋቸው፣ ቅንጅት በ97 ምርጫ ማሸነፉን እንዲሁም የኢህአዴግ አባላት ሆነው ለቅንጅት በውስጥ ይሰሩ የነበሩ ሰዎች እንደነበሩ ጠቅሰዋል። በክርስትና እና በእስልምና ሀይማኖት ሽፋን የሚካሄደውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሚኒሰትሩ በዝርዝር አቅርበዋል።
በክርስትና ሀይማኖት በኩል ” መንግስት በሃይማኖት አባቶች ሹመት ላይ እጁን ያስገባል፤ የዋልድባ ገዳም ተደፈረ፤ አልፎ አልፎ በአጋጣሚ ቤተክርስታያን ባለበት አካባቢ ከድርቅ ጋር ተያይዞ በሚነሳ ቃጠሎ ሆነ ተብሎ እንደተደረገ ማስወራት፤ ይህን የሚያግዝ የውጭ ሚዲያ መኖር ኢሳት በቀዳሚኒት ፣ የደርግ ስርዓት ደጋፊዎች የሆኑት ቪኦኤ በቀጣይነተወ የሚያራግቡት አካሄደ ጉዳዩን ትኩረት እንዲያገኝ ” ማድረጉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የሙስሊሙ እንቅስቃሴንም በተመለከተ ሚኒሰትሩ ሲገልጹ”  ከቅንጅት እስከ ህብረት፣ ከቪኦኤ እስከ ቲቪ አፍሪካ፣ ከጀርመን ድምጽ እስከ ቢላል ሬዲዮ፣ ከጅሃዳዊ ሀረካት እስከ ግንቦት ሰባት፣ ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዓለም አቀፍ እስከ መድረክ እስከ ስደተኛው ሲኖዶስ ያሉ ሀይሎች በተናጠልና በህብረት” ተሳትፈውበታል ብለዋል።
የሙስሊሙ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ፍጥነት በመዳከም ሂደት ውስጥ የገባው በቡድኑ ቀንደኛ መሪዎች ላይ ህጋዊ ስርአቱን ተከትሎ የእስራት እርምጃ ከተወሰደ በሁዋላ ነው ብለዋል።
በሃይማኖት ሽፋን የሚካሄዱ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውለው አድረው እየተጋለጡና እየተዳከሙ መሄዳቸው ባይቀርም ባለፉት ሁለት ዓመታት ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን በሀይል ለመፈታተን ከሞከሩት የሁከት ሀይሎች ዋነኞቹ ነበሩ ማለት ይቻላል ብለዋል ሚኒሰትሩ።
“በሃይማኖት ስም የሚካሄደውን ንግድ ውጤታማ እንዲሆን በማድረግ ረገድ  የድህነት መንሰራፋትና የመልካም አስተዳደር  እጦት ወይም ጉድለት ተጠቃሽ ናቸው” የሚሉት ዶ/ር ሽፈራው በተለይ ከድህነትና ኋላቀርነት መውጫውን ትክክለኛ መንገድ የሚያመላክት መሪ ድርጅት በሌለበት ፣ በሃይማኖት ሽፋን የሚነግዱ የፖለቲካ ሀይሎች አንዱን በሌላው ላይ ማነሳሳት የፅድቅ መንገድ እንደሆነ አስመስለው በማቅረብ ዜጐችን ወደጥፋት ይመራሉ” ብለዋል።
መሪ ድርጅቱም ኖሮ በአመራርም ሆነ በአባላት ደረጃ በአንድ በኩል ከፀረ ድህነትና ኋላቀርነት ትግሉ ላይ ጽናትና ብቃት ያለው አመራር መስጠት ካልተቻለ፣ በሌላ በኩል ደግም የፓርቲና የመንግስት መሪዎች ስራቸውን ከየትኛውም ሃይማኖት ገለልተኛ በሆነ መንገድና ሁሉን ሃይማኖቶች እኩል በሚያስተናግድ አግባብ ካልፈፀሙ ይኸው ችግር ተባብሶ መቀጠሉ አይቀርም ሲሉ ዶ/ር ሽፈራው አስጠንቅቀዋል።
አሁንም ድህነትና ኋላቀርነት በመኖሩ፣ በፓርቲና በመንግስት አመራራችን የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች በመኖራቸውና የእምነት ጉዳይ ለሚዛናዊ አስተሳሰብ ያለው ተጋላጭነት ዝቅተኛ በመሆኑ አልፎ አልፎ የተካረረ ፍጥጫ እያጋጠመ መሆኑንም ሚኒስተሩ በጽሁፋቸው አብራርተዋል።
ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ለኢህአዴግ ባለስልጣናት ያቀረቡትን ሙሉ ጽሁፍ በድረገጻችን መመልከት የምትችሉ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።
በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደው የፖለቲካ እንቅስቃሴ የመንግስት ቀጣዩ የምርጫ ፈተና
ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም
ህዳር 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ
1. በክርስትና ሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደው የፖለቲካ እንቅስቃሴና ቀጣይ አዝማሚያዎቹ፣
  በክርስትና ሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደው እንቅስቃሴ በዋነኛነት ኢትዮጵያ የክርስትና ሃይማኖት የበላይነት ሊኖርባት ይገባል በሚል ኋላቀርና ዘመን የሻረው አስተሳሰብና ሀይል የሚመራ ነው፡፡
  በዚህ መሠረት ይህ ኋላቀር ሀይል መነሻና መድረሻውን የክርስትና ሃይማይማኖትን  የበላይነት አድርጐ ይህን ሊያረጋግጡልኝ ይችላሉ የሚላቸውን መፈክሮች ጐላ አድርጐ ያሰማል፡፡
  በዚህ ረገድ “ኢትዮጵያ የክርስትና ደሴት ነች”፣ “አንድ አገር አንድ ሃይማኖት” የሚሉ መፈክሮቹ የአስተሳሰቡን ጭብጥ የሚያሳዩ ናቸው፡፡
 በዚህ ሀይል አስተሳሰብ መሠረት አገራችን በርካታ ሃይማኖቶችን ያስተናገደችና በማስተናገድ ላይ የምትገኝ አገር መሆኗ ቀርቶ የክርስቲያን ደሴት ብቻ ተደርጋ ትቀርባለች፡፡
  እራሱ አንድ አገር አንድ ሃይማኖት የሚለው አስተሳሰብም በተመሳሳይ መልኩ በኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ሃይማኖት ብቻ እንዳለ ወይም ሊኖር እንደሚገባ የሚሰብክ ኋላቀር የፀረ እኩልነት አስተሳሰብ ነው፡፡
  እነዚህ ሀይሎች አንደንዶቹ የሃይማኖት ጉዳይ ህብረተሰቡን በቀላሉ ሊያደናግርልን ይችላል ብለው የሚያምኑ ተቃዋሚ የፖለቲካ ሀይሎች ሲሆኑ
  ከፊሎቹ ደግሞ ከሃይማኖት አኳያ የኦርቶዶክስ እምነት መንግስታዊ ሃይማኖት መሆኑ ቀርቶ ከሌሎች ሃይማኖቶች በእኩልነት የሚታይና የሚከበር መሆኑን ያልተቀበሉ በትላንቱ ዓለም የሚኖሩ ሀይሎች ናቸው፡፡
  የፖለቲካ ሀይሎቹ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የክርስትና ሀይማኖትን መጠለያ በማድረግ የተለያዩ ቀስቃሽና ስሜትን የሚኮረኩሩ የፈጠራ አጀንዳዎችን ለማራገብ የሚሞክሩ ናቸው፡፡
ለምሳሌ፡- መንግስት በሃይማኖት አባቶች ሹመት ላይ እጁን ያስገባል፤ የዋልድባ ገዳም ተደፈረ፤ አልፎ አልፎ በአጋጣሚ ቤተክርስታያን ባለበት አካባቢ ከድርቅ ጋር ተያይዞ በሚነሳ ቃጠሎ ሆነ ተብሎ እንደተደረገ ማስወራት፤ ይህን የሚያግዝ የውጭ ሚዲያ መኖር ኢሳት በቀዳሚኒት እና ቪኦኤ /የደርግ ስርዓት ደጋፊዎች/ የሚያራግቡት አካሄደ ጉዳዩን ትኩረት እንዲያገኝ አድርግውታል፡፡ ፤
  በራሳቸው ፖለቲካዊ መስፈርት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና ሀላፊዎች መሾምና መሻር የሚፈልጉ ተቃዋሚ ሀይሎች በተለይም ደግሞ በውጭ የሚገኙ ተቃዋሚ ሀይሎች የራሳቸውን ሰው አዘጋጅተው ለማስመረጥ ብዙ ጥረት አድርገዋል፡፡
  በዛሬማ ሸለቆ አካባቢ የስኳር ልማቱ የሚካሄደው በጣም ዝቅተኛና ቆላ ላይ ሲሆን፤ የዋልድባ ገዳም መሬት ደግም በደጋና ወይናደጋ ቦታዎች ላይ የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሃቁ ይህ ሆኖ ሳለ በገዳሙና በስኳር ማሳው መካከል ያለውን ከፍተኛ የመልክዓምድር ልዩነት በቅርቡ ለማያውቁ የክርስትና ምዕመናን ሁሉ ገዳሙ ተደፈረ የሚለው ቃል እልህና የቁጣ ስሜት ይፈጥርባቸዋል ብሎ በማመን ሰፊ ዘመቻ ሲካሄድበት ከርሟል፡፡
  የዚህ ዘመቻ ፊታውራሪዎች በአሜሪካን ድምጽ ሬዲዮ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ የቀድሞ የኢህአፓዎችና የቅንጅት ትርፍራፊዎች ናቸው፡፡
 በአንድ ወቅት በምዕራብ ኢትዮጵያ ጅማ አካባቢ በኻዋርጃ ስም የሚታወቁ አክራሪዎች በክርስቲያኖች ላይ ያደረሱትን ግድያ መጠጊያ በማድረግ “ክርስቲያኖች እየተጨፈጨፉ ነው ስለዚህም አፀፋው ሊመለስ ይገባዋል” በሚል ቅኝት መንቀሳቀስ ጀምረው ነበር፡፡
 አልፎ አልፎ እንደምናየውም ከድርቅ ጋር በተያያዘ ምክንያት በሚነሳ ቃጠሎ አንድ ቤተ ክርስትያን ወይም ገዳም ባለበት አካባቢ በአጋጣሚ ቃጠሎ ከተነሳ ይህንኑ ሆን ተብሎና በክርስትና ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሲባል እንደተደረገ አስመስሎ የማቅረብ፣
  እንዲሁም ለቤተ ክርስትያን መስሪያ ተብሎ ባልተሰጠ ቦታ የቤተክርስትያን ግንባታ መጀመርና ህገ ወጥ ግንባታ እንዲቆም ሲጠየቅ በክርስትና ሃይማኖት ላይ ተዘመተ ብሎ የእኩልነት ጥያቄ ማንሳት አዘውትረው የሚጠቀሙባቸው ስልቶች ናቸው፡፡
 ከመንግስትና ድርጅት ሀላፊዎች ውጭ ባሉ የተሳሳተ አስተሳሰብ ባላቸው ዜጐች የሚራመዱት እነዚህ ኋላቀርና ፀረ እኩልነት አስተሳሰቦች እንደተጠበቁ ሆኖ ሃይማኖታዊ አዝማሚያ ባልተለያቸውና በመንግስታዊ ሀፊነትና በእምነታቸው መካከል ያለውን ልዩነት በውል መገንዘብ የተሳናቸው ሀላፊዎች ደግሞ የየራሳቸውን ስህተት ሲሰሩ ማስተዋል የተለመደ ነው፡፡
 በአጠቃላይ ሲታይ ወቅታዊና ለፖለቲካ ንግድ የሚያመች እንዲህ አይነት አጀንዳ ሲፈጠር አጋጣሚውን ለመጠቀም ምን ጊዜም ወደ ኋላ አይሉም፡፡
 በክርስትና ስምና ሽፋን የሚነግዱ ፖለቲከኞች አነዚህን የመሳሰሉ መሠረተ ቢስ አጀንዳዎችን በመቅረጽና በማራገብ ክርስትና ሃይማኖት ተከብሮና ተቻችሎ በሚኖርባት አዲሲቷ ኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ክብርና ሞገሱን የተገፈፈ አስመስለው ያቀርባሉ፡፡
  ለእምነቱ ክብርና ሞገስ የሌላቸው ራሳቸው በሃይማኖቱ ሽፋን የፖለቲካ ንግድ የሚያካሂዱት
  ሀይሎች መሆናቸውን ደብቀው መንግስትና ስርዓቱን በመሰረተ ቢስ ወንጀል ይከሳሉ፡፡
2. በእስልምና ሀይማኖት ሽፋን የሚካሄደው የፖለቲካ እንቅስቃሴና ቀጣይ አዝማሚያዎቹ፤ 
በክርስትና ሀይማኖት ሽፋን ከሚካሄደው እንቅስቃሴ ባልተናነሰ ይልቁንም አልፎ አልፎ በራሱ ባህሪ ከዚያም በከፋ ሁኔታ በእስልምና ሀይማኖት ስም ሚካሄድ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚታይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
  እንቅስቃሴው ውስጥ ውስጡን ሲካሄድ ቆይቶ ከቅርብ አመታት ወዲህ አክራሪነትን ለመታገል እንቅስቃሴ ሲጀመር ነው በግልጽ ፀረ ህገመንግስታዊ መልክ ይዞ መታየት የጀመረው፡፡
  ከ20 ዓመታት በፊት በጨቋኙ ስርዓት ይደርስባቸው ከነበረው ግፍና በደል በዲሞክራሲያዊ ትግል ተላቀው የሃይማኖታቸውን እኩልነት ባስከበሩባት አዲሲቷ ኢትዮጵያ የሃይማኖት የበላይነትን በማስፈን ቅኝትና ከሌሎች ሃይማኖት ተከታይ ወንድሞቻቸው ጋር በመቻቻልና በእኩልነት የመኖር እድልን በሚዘጋ ሁኔታ የሚንቀሳቀሱ አክራሪ ዝንባሌዎች መታየት ጀምረዋል፡፡
  እነዚህ አክራሪ እንቅስቃሴዎች በዋኛነት ከሰሜን አፍሪካና ከመካከለኛው ምስራቅ አገሮች አክራሪ ሀይሎች የመነጩ፤ በአንድ በኩል የእስልምናን የበላይነት በአካባያችን ለማስፈን የሚካሄደው እቅድ ማስፈጸሚያ፤ በሌላ በኩል በሃይማኖቱ በሚነግዱ ግለሰቦችና ቡድኖች በሃገሪቱ የተፈጠረውን የእኩልነት ስርዓት በመፃረር የበላይነትን ለማሰፈን የሚካሄደው እንቅስቃሴ መገለጫዎች ናቸው፡፡
  በእነዚህ  አክራሪ አስተሳሰቦች የሚመሩ ጽንፈኞች መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ በመገንዘብ በሀይማኖት ሽፋን የዜጐችን ሰብዓዊ መብቶች የሚረግጡ በርካታ አስነዋሪ ተግባራትን ፈጽመዋል፡፡ ነባር መስጊዶችን አቃጥለዋል፣ ነባርና ኢትዮጵያዊ መሠረት አላቸው የሚሏቸውን የሃይማኖት መጽሃፍት አቃጥለዋል፡፡
  ይህን በመቃወም ለማስቆም የሞከሩ ዜጐችና የሃይማኖት ትምህርት ቤቶችንና መስጊዶችን የአመራር ቦታዎች በጉልበት ነጥቀዋል፣ ይህን የተቃወሙ ዜጐችን ሁሉ ከቤት ንብረታቸው አፈናቅለዋል፡፡ ይህ ከሞላ ጐደል አክራሪዎቹ በደረሱባቸው ቦታዎች ሁሉ የተካሄደ ነው፡፡
  የመጀመሪያው ሙከራ ያነጣጠረው በኢትዮጵያ ያሉ ብዙዎቹ ነባር ሃይማኖቶች ሁሉ መሠረታቸው መካከለኛው ምስራቅ መሆኑ እየታወቀ መንግስት አህባሽ የሚባል ሃይማኖት ከውጭ አመጣብን የሚለው መከራከሪያ ውሃ የማይቋጥር ቢሆንም መንግስት ይህኛውን ወይም ያኛውን ሃይማኖት ከዚህኛው ወይም ከዚያኛው አገር በብድር የሚያመጣበት ምክንያትም ሆነ ሎጂክ አልነበረውም፣ የለውምም፡፡ ሃቁ ይህ ሆኖ ሳለ በውጭ ገንዘብ ድጐማ የሚንቀሳቀሱት እነዚህ ሀይሎች ባላቸው አቅመ ሁሉ በመታገዝ
  መንግስት አህባሽ የሚባል የውጭ እምነት አምጥቶ /በሃጂ አብዲላሂ መምህርነት የተስፋፋውን/ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ሊጭንበት እየተንቀሳቀሰ ነው የሚል መሠረተ ቢስ ጉዳዮችን እያመጡ መንግስት በሃይማኖታችን ጉዳይ ጣልቃ ገባ ብለው ሲከሱ ሰንብተዋል፡፡ ቀላል ያልሆነ የህብረተሰብ ክፍል በተለይም ወጣት አደናግረዋል፡፡
 የአስተምህሮ መሰረታቸው ብቻ ሳይሆን የየፋይናንስ ምንጫቸውም የውጭ ሀይል ለዚያውም በጣም በቅርቡ የምናውቀው መካከለኛው ምስራቅ በሆነበት ሁኔታ መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ ገብነት ለመክሰስ የሚያስችላቸው ሞራላዊ ብቃት እንዴት ሊጐናፀፉ ቻሉ?
  ገንዘብን በመጠቀም ነባሩን የሱፊ እምነት ለመገለባበጥ ያደረጉት ጥረትና በተወሰነ ደረጃ ያገኙት ውጤት የልብ ልብ ስለሰጣቸው ብቻ ራሳቸውን ምሉዕ በኩልሄ አገር በቀል ሌላውን ደግሞ መጤ ለማስመሰል እስከመሞከር ደርሰዋል፡፡
 ደግነቱ በዚህች ዴሞክራሲያዊት ምድር አገር በቀል መሆን ወይም አለመሆን እምነትን ለማስተማር ቦታ የሌለው መሆኑ እንጅ አገር በቀል ያልሆነ እምነት ሁሉ ኢትዮጵያ ውስጥ ቦታ ሊኖረው አይገባም ቢባል ማን ይቀራል፤
  ነገር ግን አዲሱቱ ኢትዮጵያ የሃይማኖት መለኪያዋ የዜጐች ምርጫ መሆን አለመሆኑ ነው፡፡ መሠረቱ ኢትዮጵያዊ፣ አፍሪካዊ ወይም የሌላ ዓለም መሆን አለመሆኑ አይደለምና ከመካከለኛው ምስራቅ አንዳንድ አገሮች በቅርቡ የገቡትን ሌሎች አስተምህሮዎች ያልከለከለችውን ያክል አህባሽም ሆነ ሌላ አስተምህሮ የዜጐች ምርጫ እስከሆነ ድረስ እንዳይገባ የምትከለክልበት አንዳችም ምክንያት አልነበረም፡፡
 በዚህ ጉዳይ ላይ መንግስት ጉዳዩን አቃሎ በመመልከት ሰፊና አጥጋቢ ማብራሪያ ባለመስጠቱ ግን አክራሪዎቹ ፈቃጅና ከልካይ ሆነው አህባሽ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት የለበትም የሚል አስተምህሯቸው የብዙዎቹን ወጣት ሙስሊሞች አዕምሮ እንዲበርዝ እድል አገኘ፡፡
  ሌላው መጠቀሚያ ሊያደርጉት የሞከሩት                                                                                                                                                                                                                                                                                                         እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ ነበር፡፡
 መንግስት ከት/ቤቱ የፈለገው ሃይማኖትና ፖለቲካ የተነጣጠሉ መሆናቸውን በመቀበል ከማናቸውም አይነት የፖለቲካ አስተምህሮ በፀዳ አኳኋን ተግባሩን እንዲፈጽም ብቻ ነው፡፡
  ተቋሙ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን አክብሮ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ለማንም ተጠያቂነት በሌላቸው ወገኖች እየተመራ ከሃይማኖታዊ ጉዳዮች በራቁና ለአክራሪዎች በተመቹ አጀንዳዎች ተጠምዶ ጊዜውን ሲያሳልፍ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም ይህንኑ መነሻ በማድረግ ድርጅቱ በእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሚመራና ተጠያቂነት ያለበት ተቋም እንዲሆን ተደርጓል፡፡
 የሙስሊሙ ማህበረሰብ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቶችን እንደ አዲስ መርጦ ማደራጀት እንደሚፈልግ ግልጽ ነበር – ከየአቅጣጫው በሚነሱ ጥያቄዎች፡፡ በዚህመ ሠረት ምክር ቤቶቹ በአፋጣኝ በሚካሄድ ምርጫ እንዲዋቀሩ ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡ ይህ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ህገ መንግስታዊ መብት በመሆኑ መንግስት ይህንኑ ተቀብሎ፤ ምክር ቤቶቹ ለዚህ የህዝብ ጥያቄ አወንታዊ ምላሽ እንዲሰጡ ከእርሱ የሚጠበቀውን ምክር ለግሷል፡፡ ምክር ቤቶቹ በአፋጣኝ በሚካሄድ ምርጫ እንዲዋቀሩ የማድረጉን ዴሞክራሲይዊ አሰራርም ደግፏል፡፡
  ልክ መንግስት ጣልቃ እንደገባና ያለሙስሊሙ ህዝብ ፍላጐት  መራጮች በላዩ ላይ እንደተጫኑበት በማስመሰል ሲቀሰቅሱ ከቆዩ በኋላ ከዚህ ታላቅ የዴሞክራሲ ተግባር አቋርጠው ወጡ፡፡
በውጤቱም ህዝቡ ከአክራሪነት የፀዱ የሚላቸውን ሰዎች መምረጡን አረጋግጧል፡፡ ነገር ግን ይህ ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ መካሄዱ ያንገሸገሻቸው አክራሪ ሀይሎች ገና ከምርጫው ዋዜማ ጀምሮ ይህንኑ ለመቃወም ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡
  ድምፃችን ይሰማ በማለት አርብ አርብ በአንዋር መስጊድና አልፎ አልፎም በሌሎች መስጊዶች ከመንግስት ጋር በከፍተኛ ደረጃ ሲፋጠጡ ከርመዋል፡፡
  ከውጭ ሚዲያዎች ጋር በተቀናጀ አኳኋን በእስልምና ሃይማኖት ላይ ጥቃት የደረሰ በማስመሰል ለማነሳሳት ብዙ ጥረት አድርገዋል፡፡
  በፖሊስና ፀጥታ አስከባሪ ሀይሎች ትዕግስት ወደ መካረርና ግጭት እንዳይመራ ተደረገ እንጂ ከሞላ ጐደል ለአንድ ዓመት ተኩል ያክል አክራሪዎቹ መንግስትን ወደ ግጭትና ደም መፋሰስ ለማስገባት ያላደረጉት ጥረት አልነበረም፡፡
  በአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ ስብሰባ ወቅት ያልተፈቀደ የሚሊዮን ሰዎች ሰልፍ ለማድረግና የአዲስ አበባን መንገዶች በመዘጋጋት አደጋ ለመፍጠር ሙከራ አድርገው ነበር፡፡ እንደዚሁም ባለፈው ክረምት አንድ ሌሊት ላይ ከቢላል መስጊድ በመነሳት አዲስ አበባ ከተማን ለማተራመስ ሞክረው ነበር፡፡
  እራሱን ጀሃዳዊ ሃረካት በሚል ስያሜ ለማስተዋወቅ ጥረት ያደረግ ከነበረ የአሸባሪዎች ድርጅት ጋር በመቀናት የአንዋር መስጊዱንም ሆነ ሌሎች መሰል የነውጥ ሙከራዎች በሽፋንነት መጠቀም መርጠው ነበር፡፡
  ይህም ሆኖ መንግስት ረጀም ጊዜ ወስዶ ባካሄደው ጥናትና በሰበሰባቸው ማስረጃዎች ላይ በመመስረት በቡድኑ ቀንደኛ መሪዎች ላይ ህጋዊ ስርዓቱን ተከትሎ የእስራት እርምጃ ወስዷል፡፡
  ከዚህ ጊዜ በኋላ ነው ንቅናቄው በከፍተኛ ፍጥነት በመዳከም ሂደት ውስጥ የገባው፡፡
  በሌላ በኩል ደግም ሃይማኖትን በሽፋንነት ለመጠቀም የሞከረው ይኸው ሀይል በተለይ በውጭ ከሚገኙ ደጋፊዎቹ ጋር በመቀናጀት አሉ የተባሉትን ፀረ ኢትዮጵያ ሚዲያዎች ከመጠቀሙም ባሻገር ከግንቦት 7 እስክ ስደተኛው ሲኖዶስ ባለ የትምክህት ሀይሎች ለመደገፍና ብርቱ ጥረት አድርጓል፡፡ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል ፈሊጥ እርስ በእርስ ተሳስረውና ተደጋግፈው ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡
  በማጠቃለል ሲታይ በሃይማኖት ሽፋን የሚካሄዱ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውለው አድረው እየተጋለጡና እየተዳከሙ መሄዳቸው ባይቀርም ባለፉት ሁለት ዓመታት ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን በሀይል ለመፈታተን ከሞከሩት የሁከት ሀይሎች ዋነኞቹ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡
  በሀይማኖት ሽፋን የሚካሄደው እንቅስቃሴ በጽንፈኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች በቀጥታ ከተደረገው የነውጥ ማነሳሰት በእጅጉ የላቀ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
  ምንም እንኳን ነውጠኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከ97 ውድቀታቸው በኋላ በተመሳሳይ ደረጃ ወደሚገለጽ የጐዳና ላይ ነውጥ ለማምራት በከፍተኛ ደረጃ እየተቸገሩ ቢሆኑም በሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደውን እንቅስቃሴ በመደገፍና ነዳጅ በማርከፍከፍ ለማቀጣጠል ያደረጉትን ጥረት ጨምሮ የወቅቱ ፀረ ህገ መንግስታዊ ንቅናቄ መገለጫ የሃይማኖት ልባስ ይዞ የሚካሄደው እንቅስቃሴ ነው ማለት ይቻላል፡፡
  በሃይማኖት ሽፋን ለመንቀሳቀስ የተመረጠበትን ዋነኛና ደጋፊ ምክንያቶች መለየትና ከዚህም አኳያ መሠረታዊ መፍትሄ ማበጀት ይገባል፡፡
3. ሃይማኖትን በሽፋንነት ለመጠቀም የተመረጠባቸው ምክንያቶች፣
  ሃይማኖትን በሽፋንነት በመጠቀም የፖለቲካ እንቅስቃሴውን ማካሄድ የመረጡት ሀይሎች የተለያየ መጠሪያ ያላቸው ነገር ግን በመሰረቱ የትምክህት ወይም የጠባብነት መፈክሮችን አንግበው ለመፋለም የሞከሩ የፖለቲካ ሀይሎች እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
  ከቅንጅት እስከ ህብረት፣ ከቪኦኤ እስከ ቲቪ አፍሪካ፣ ከጀርመን ድምጽ እስከ ቢላል ሬዲዮ፣ ከጀሃዳዊ ሃረካት እስከ ግንቦት ሰባት፣ ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዓለም አቀፍ እስከ መድረክ እስከ ስደተኛው ሲኖዶስ ወዘተ ያሉ ሀይሎች በተናጠልና በህብረት የተሳተፉበት ነው፡፡
  ሁሉም ያነገቡትን ዓላማ በተለያዩ ፀረ ህገ መንግስታዊ ስልቶች በመታገዝ ለማስፈፀም ሞክረው የከሸፈባቸው ሀይሎች ናቸው፡፡
  እነዚህ አላማቸውን በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ በማራመድ ለስኬት መብቃት ያቃታቸው ድርጅቶችና ሀይሎች ከፍ ሲል እንደተመለከትነው የፖለቲካ ዓላማቸውን በሃይማኖት ሽፋን ማራመድ የመረጡት ይህ ስልት ምን ዓይነት እድል ቢሰጣቸው ነው ብሎ ጥያቄ ማንሳትና ጉዳዩን መመርመር በዚሁ ዙሪያ በቀጣይነት መካሄድ ያለበትን ትግል በትክክል ለመወሰን አስፈላጊ ነው፡፡
  በድሃና ኋላቀር ህብረተሰብ ውስጥ በእምነት ጉዳይ ዜጐችን ብዥታ ውሰጥ መክተት ይህን ስልት ለመረጡ ወገኖች በቀላሉ ያለመጋለጥ እድል ያጐናጽፈናል፡፡ ከዚህም አለፍ ሲል ለድል ያበቃናል ብለው ማመናቸው ነው፡፡
  የእምነት ጉዳይ ለሚዛናዊ አስተሳሰብ ያለው ተጋላጭነት በተነፃፃሪ አነስተኛ ከመሆኑ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
  በሃይማኖት ለሚመራ ሰው ወደ ማንኛውም ድርጊት ለማምራት ማመን ብቻውን በቂ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡
  “በእምነትህ የመጣ ነው” ተብሎ የቀረበለትን ጉዳይ ያለማንገራገር ተቀብሎ ወደ ድርጊት ማምራት በብዙ የሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
  ስለሆነም ይህ አካሄድ በሃይማኖታቸው ቀናዒ የሆኑ ሰዎች በሃይማኖት ሽፋን የሚራመዱ የፖለቲካ አጀንዳዎች ሰለባ ለማድረግ የተሻለ እድል ይፈጥርልናል በማለት ነው፡፡
  በበለፀገው ዓለምም በአሸባሪነትም ሆነ በፀረ አሸባሪነት ጐራ ተሰልፈው የሚፋለሙ ሀይሎች ሃይማኖታዊ ጥሪ በማስተላለፍ የፖለቲካ ዓላማቸውን በሃይማኖት ግጭት መልክ ሲያስኬዱ ማየት የተለመደ ነው፡፡
  የትኛውንም ጎራ በመሠረተ ቢስ እምነት ነክ ውንጀላዎች በቀላሉ በስሜት በማነሳሳት ሌላውን እንዲገጥሙ ማድረግ ይቻላል ተብሎ ይታመናል፡፡
በመሆኑም የከሰሩ ፖለቲከኞች ሁሉ ሃይማኖትን በሽፋንነት በመጠቀም መንቀሳቀሳቸው የእምነት ጉዳይ ለሚዛናዊ አስተሳሰብ ያለው ተጋላጭነት በተነፃፃሪ አነስተኛ ከመሆኑ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
  በሃይማኖት ስም የሚካሄደውን ንግድ ውጤታማ እንዲሆን በማድረግ ረገድ አጋዥ ሚና የሚጫወቱ ችግሮች ደግሞ ይኖራሉ፡፡ በዚህ ረገድ የድህነት መንሰራፋትና የመልካም አስተዳደር  እጦት ወይም ጉድለት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
  በተጨባጭ እንደሚታየው በበለፀገና ሰርቶ የመጠቀም እድል በሰፋበት ማህበረሰብ ውስጥ ለጽንፈኝነት መሠረት የሚሆን ተስፋ መቁረጥ አይገኝም፡፡ ሰርቶ መክበርና ማደግ ስለሚቻል ለተስፋ መቁረጥ ምክንያት የሚሆን ችግር አይኖርም፡፡
  መልካም አስተዳደር በሰፈነበት ሁኔታ ዜጐችና ህዝቦች በደስታና በስምምነት ይኖራሉ፡፡ በአንፃሩ ድህነትና ኋላቀርነት በተስፋፋበት ህብረተሰብ ውስጥ ተስፋ መቁረጥ ያይላል፡፡ ዜጐች የምድራዊ ኑሯቸውን ከሲኦል ያልተለየ አድርገው በመውሰድ በሃይማኖት ስም ለሚቀርቧቸው ሃሳዊ መሲሆች ሁሉ አመኔታቸውን ሊሰጡ ይገደዳሉ፡፡ ኢትዩጵያ በመጭው ምርጫ ፈተና ይሆንብናል፡፡
  በተለይ ከድህነትና ኋላቀርነት መውጫውን ትክክለኛ መንገድ የሚያመላክት መሪ ድርጅት በሌለበት በሃይማኖት ሽፋን የሚነግዱ የፖለቲካ ሀይሎች አንዱን በሌላው ላይ ማነሳሳት የፅድቅ መንገድ እንደሆነ አስመስለው በማቅረብ ዜጐችን ወደጥፋት ይመራሉ፡፡
  መሪ ድርጅቱም ኖሮ በአመራርም ሆነ በአባላት ደረጃ በአንድ በኩል ከፀረ ድህነትና ኋላቀርነት ትግሉ ላይ ጽናትና ብቃት ያለው አመራር መስጠት ካልተቻለ፣ በሌላ በኩል ደግም የፓርቲና የመንግስት መሪዎች ስራቸውን ከየትኛውም ሃይማኖት ገለልተኛ በሆነ መንገድና ሁሉን ሃይማኖቶች እኩል በሚያስተናግድ አግባብ ካልፈፀሙ ይኸው ችግር ተባብሶ መቀጠሉ አይቀርም፡፡
  ከዚህ አኳያ ሲታይ ድህነትና ኋላቀርነነት እንዲሁም እነዚህን ለማስወገድ የሚያስችል ብቃት ያለው አመራር እጦት የፖለቲካ ጽንፈኝነትና የሃይማኖት አክራሪነት የሚስፋፋባቸው ለም አፈሮች ብቻ ሳይሆኑ በሃይማኖት ሽፋን የሚነግዱ ፖለቲከኞችም እንደመልካም አጋጣሚ የሚመለከቷቸው ናቸው፡፡
  በመሆኑም እነዚህን ችግሮች በመፍታት በሃይማኖት ሽፋን ለሚነግዱ ፖለቲከኞች መንቀሳቀሻ አድማሱን ማጥበብ እጅግ ተፈላጊ ሆኖ ይገኛል፡
IV. በሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደውን የፖለቲካ ንግድ በአስተማማኝ ደረጃ ለማሸነፍ ምን እንስራ?
  ከፍ ሲል እንደገለጽነው ፈጣንና ህዝብ የሢቀምበት ለውጥና ብዝሃነነትን በአግባባ የማስተናገድ ችሎታተ የያለው ህብረተሰብ በመፈጠሩሪ ምክንያት በሀይማኖት ሽፋንም ሆነ በግላጭ ሲካሄድ የቆየው ጽንፈኛ እንቅስቃሴ የህዝብ ይሁንታን ሊያገኘ ባለመቻሉ ትርጉም ያለው ሁከትና ብጥብጥን ለመቀስቀስ ሳይቻለው ቆይቷል፡፡
 ይህ መሠረታዊ ሃቅ አንደተጠበቀ ሆኖ አሁንም ድህነትና ኋላቀርነት በመኖሩ፣ በፓርቲና በመንግስት አመራራችን የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች በመኖራቸውና የእምነት ጉዳይ ለሚዛናዊ አስተሳሰብ ያለው ተጋላጭነት ዝቅተኛ በመሆኑ አልፎ አልፎ የተካረረ ፍጥጫ የሚያጋጥመን ሆኖ ቆይቷል፡፡
 ይህ ፍጥጫ በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሞላ ጐደል ሁሉንም ተፋላሚ ሀይሎች በሁለት ጐራ ከፍሎ ያፋጠጠ ሆኖ ከርሟል፡፡
  ምንም እንኳን ችግሩ ለጊዜውም ቢሆን በመንግስት ታጋሽነትና አርቆ አስተዋይነት እንዲሁም በሰላም ወዳዱ ህዝብ ብርቱ ትግል የከሸፈም ቢሆን ለችግሩ መቀስቀስ ምክንያት የሆኑት ጉዳዮች በሙሉ ዛሬም በተጨባጭ ይገኛሉና ይህንን ታሳቢ ያደረገ የመፍትሄ ሃሳብ ማመላከት ተገቢ ይሆናል፡፡
1. ፀረ- ድህነትና ፀረ-ኋላቀርነት ትግላችንን እናፋፍም፣
  በድህነት የተጐዳ ህብረተሰብ ሁሌም በምሬት ውስጥ የሚኖርና ከዚህ ችግር የሚያላቅቀው ትክክለኛ አማራጭ ካልቀረበለት በስተቀር በሌሎች ጽንፈኛና መሰረተ ቢስ አማራጮች ሊማለል የሚችል ነው፡፡
  በተለይ ደግም በምድራዊው ህይወቱ ያላለፈለትን ህዝብ በሰማይ ቤት ያልፍልሃልና ማንኛውንም ጽንፈኛ አቋም ተግባራዊ አድርግ ለሚሉ አይነት ቅስቀሳዎች ተጋላጭ ይሆናል፡፡
 ኋላቀርነትም እንደዚሁ አንድን ህብረተሰብ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር እድል በመንፈግ ለተስፋ መቁረጥና ጽንፈኝነት ሊዳርገው ይችላል፡፡
  ምሬቱ የከፋና ተስፍ የቆረጠ ህዝብ ባለበት ሁሉ ጽንፈኝነት ሲስፋፋ የምንመለከተው በዚህ ምክንያት ነው፡፡
  ይህ አዲስ ግኝት ሳይሆን ድርጅታችን ቀደም ሲል ጀምሮ የተገነዘብነውና ለመፍትሄውም የታገለለት ጉዳይ ነው፡፡
 ድርጅታችንና በርሱም የሚመራው ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ድህነትና ኋላቀርነት ጽንፈኝነትንና፣ ፀረ እኩልነት የሆኑ የትምክህትና ጠባብነት አዝማሚያዎችን ወዘተ ሊሸከም የሚችል ለም አፈር መሆኑን ታሳቢ በማድረግ በድህነትና ኋላቀርነት ላይ ጦርነት ካወጀ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡
 ፈጣንና ብዙሃኑ ህዝቦች የሚቀጠሙበትን ልማት አስፋፍቷል፡፡
  መሠረተ ሰፊና አሳታፊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ገንብቷል፡፡ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ቀጣይ ትግል አካሂዶ በመስኩ ከፍተኛ ድሎችን አስመዝግቧል፡፡
  ይህም በመሆኑ ዛሬ አገራችን ከመቼውም ጊዜ በተለየ ሁኔታ በፈጣንና ህዝብ በሚጠቀምበት ዴሞክራሲያዊ የእድገት አቅጣጫ እየገሰገሰች ትገኛለት፡፡
  እድገታችን ፈጣንና መሰረተ ሰፊ በመሆኑም የህዝቡን ተስፋ አለምልሟል፡፡
  ዴሞክራሲያችን ብዝሃነትን በማወቅና በማክበር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ በህዝቦች መካከል ፍቅርን መከባበርና መቻቻልን አጐልብቷል፡፡
  የእርስ በርስ መናቆርና ከዚህም ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችል ተስፋ መቁረጥ መሰረት ተንዷል፡፡ ብዙ አገሮች በቀለም አብዮቶች ሲናጡና ከቀውስ ወደ ቀውስ ሲረማመዱ በአገራችን ሰላምና መረጋጋት እንደሰፈነ የቀጠለው በዚህ ምክንያት ነው፡፡
2. ወጣቱን ከስራ አጥነትና ተስፋ መቁረጥ እንታደግ?
 አብዛኛውን ጊዜ በስሜት የሚያነሳሱ ጉዳዮች በቀላሉ ተጽዕኖ የሚያሳርፉት በወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ላይ ነው፡፡
  በተለይ ወጣቱ ለስራ አጥነት፣ ጥራት ለሌለው ትምህርት፣ ከተደራጀ ፖለቲካዊ ተሳትፎ መገለልና ለመልከም አስተዳደር የሚያመች ሁኔታ ባልገጠመው ወቅት ስሜት ቀስቃሽ የሆኑ አቀራረቦች በደካማ ጐኑ ለመግባት የተሻለ እድል ያገኛሉ፡፡
  በአገራችን በተለይ ከ97 ዓ/ም ድህረ ምርጫ ቀውስ በመማር የወጣቱን የልማትና የተጠቃሚነት፣ የመልካም አስተዳደርና የተሳትፎ ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት ያደረግነውና የተሳካ ውጤት ያገኘነውም በመሰረቱ ለስራ አጥነትና ለተስፋ መቁረጥ የተጋለጠ ወጣት ሊኖርበት የሚችለውን ተጋላጭነት በማስወገድ ንቁ የአገር ገንቢ ለማድረግ ነው፡፡
  ወጣቱ ያለበትን የመነሻ ካፒታል ችግር በከፊልና የራሱን ተሳትፎ ባረጋገጠ አኳኋን ልንቀርፍለት፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታዎችን ገንብተን በማቅረብ ለልማታዊ ጥረቱ የተሻለ ሁኔታ ልናመቻችለት ይገባናል፡፡
  በገጠርም በግብርናና ከግብርና ውጭ በሚካሄዱ ልማታዊ ሰራዎች ተሳትፎውንና ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ ይገባናል፡፡
  ከዚህ ጐን ለጐን ወጣቱ ትውልድ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በሚካሄደው ትግል ዋነኛ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ ተጠናከሮ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡
 ይህ ሲሆን ብቻ ነው ወጣቱ ሚዛናዊ አስተሳሰብ እንዲይዝ ለማድረግ የምናደርገውን አስተምህሮ በቅን ልቦና ተመልክቶ ሊቀበል የሚችለው፡፡
3. የመንግስትና ፓርቲ አመራርን ሃይማኖታዊ ገለልተኝነት እናጠናክር፣
  ህዝቡ ለመብቱና ለጥቅሙ የሚያደርገውን ትግል በትክክለኛ መስመር ለመምራት የተነሳው ድርጅታችንም ሆነ ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስታችን የብሄርና የሃይማኖት ልዩነት ሳያደርግ አላማውን የተቀበሉና መንግስታዊ ተልዕኮን ለመፈፀም ዝግጁ የሆኑ ታጋዮችንም ያሰባስባል፡፡
  ይህም በመሆኑ ድርጅታችንም ሆነ ልማታዊ መንግስታችን የተለያዩ እምነቶች ተከታዮች የሚሳተፉባቸው ተቋማት እንዲሆኑ አድርጓቸዋል፡፡
  ይህ መሠረታዊ የግል እምነትን የማክበርና የማስከበር ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ ድርጅታዊ አመራርን የማረጋገጥም ሆነ መንግስታዊ አገልግሎትን የመስጠት ጉዳይ ከሃይማኖት /ከራስህም እምነት ጭምር/ ገለልተኛ በሆነ መንገድ መካሄዱን ማረጋገጥ ይገባል፡፡
 ዜጐችና የተለያዩ እምነት ተከታዮች ከድርጅት የሚያገኙት አመራርና ከመንግስት የሚያገኙት አገልግሎት በእኩልነት ከሀይማኖት ገለልተኛ በሆነ መንገድ ሊፈፀም ይገባዋል፡፡
  በየደረጃው የሚገኙ ሀላፊዎች ከዚህ አኳያ በተጨባጭ ከሚፈፀሙ ገለልተኝነትን ለድርድር ከሚያቀርቡ ስህተቶች መጽዳታቸውን ማረጋገጥ ይገባል፡፡
4. የህገ መንግስታዊና ሚዛናዊ አስተሳሰብ ትምህርትን ማስፋፋት፣
 ሆን ብለውና እያወቁ በሀይማኖት ሽፋን የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ጥረት የሚያደርጉ ወገኖችን ከተሳሳተ አቅጣጫቸው በትምህርት መመለስ አይቻልም፡፡
  እነዚህ ጥቅማቸውን በጥገኛ ወይም የኪራይ ሰብሳቢ መንገድ ለማሳካት የሚንቀሳቀሱና ለዚህም የቆረጡ ናቸው፡፡
  ስለሆነም ተጋልጠው የፖለቲካ ተፅዕኖ የማሳረፍ አቅማቸው እንዲዳከምና የማታ ማታ ደግሞ ተነጥለው ወደ ዳርቻ እንዲገፉ /marginalized/ ማድረግ ብቻ የሚጠይቁ ወይም የሚፈልጉ ናቸው፡፡ ስለሆነም ስለህገ መንግስታዊና ሚዛናዊ አስተሳሰብ አስተምህሮ ስናነሳ ለእነዚህ እንደማይሆን በመገንዘብ ጭምር ነው፡፡
  ህገ መንግስታዊና የሚዛናዊ አስተሳሰብ ትምህርት ከማንም በላይ የሚያስፈልገውና የሚጠቅመው ከልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ሂደቱ ተጠቃሚ ለሆኑት ብዙሃን ህዝቦች ነው፡፡
  ስለሆነም ለራሳችን ማህበራዊ መሰረቶች በህገ መንግስታዊ ስርዓታችን ላይ ግልጽነት፣ እምነትና ስርዓቱን ከአደጋ የመጠበቅ ቁርጠኝነት እንዲያዳብሩ የሚያግዝ ትምህርት ልንሰጥ ይገባናል፡፡
  እያንዳንዱ ዜጋ በማንኛውም ጉዳይ ላይ አቋም ከመውሰዱ በፊት ለምን? ለማንና መቼ? እንዴትና የት? ወዘተ የሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን በማንሳት መመርምር እንደሚገባው ማስተማር ይገባናል፡፡
  እነዚህን ጥያቄዎች በማንሳት የህዝብንና የአገርን ጥቅም የሚጐዳን ማናቸውም ጉዳይ መቃወም፣ የሚጠቅመን ጉዳይ ደግሞ መደገፈ እንዳሚገባ ማስተማር ይገባል፡፡
  ሌላው ሰው አድርጐታል በማለትና በመንጋ ቅኝት በመመራት አቋም መውሰድ እንደማይገባ ይልቁንም አያንዳንዱ ሰው ራሱን ችሎና በህሊናው አመዛዝኖ አቋም መውሰድ እንዳለበት ማስተማር ይገባናል፡፡
 በአንድ በኩል ከእያንዳንዱ ሚዛናዊ አቋምና ተግባር በሌላ በኩል ደግሞ ከእያንዲንዱ ሚዛናዊነት የጐደለው አስተሳሰብና ተግባር ተፈላጊውን ትምህርት መስጠትና የሚዛናዊ አስተሳሰብን የበላይነት ማረጋገጥ ይገባናል፡፡
5. በሃይማኖት ሽፋን የሚነግዱትን ሀይሎች በቀጣይነት ማጋለጥና መሰረት ማሳጣት፣
ü እነዚህ ተግባራት በትክክል ከተፈፀሙ አክራሪነትንና ጽንፈኝንት ከማሸነፍ አኳያ ረጅም ርቀት እንደሚወስዱን አያጠያይቅም፡፡ ይህም ሆኖ ብቻቸውን በቂ ናቸው ሊባሉ የሚችሉ አይደሉም፡፡ በሃይማኖት ሽፋን የሚነግዱ ጽንፈኞችን ሁሉ በማጋለጥ ትግል ሊደገፉ የሚገባቸው ናቸው፡፡ ከዚህ ትግል ውጭ የምናገኛቸው ውጤት ምሉዕነት ሊኖረው የሚችል አይደለም፡፡
  ህዝቡ ህይወቱን በሚመለከቱ መሠረታዊ ጉዳያች ላይ ሁሉ ብቁ፣ ዝርዝርና ወቅታዊ መረጃ እንዲኖረው ማድረግ ነው፡፡
  የመንግስትን እቅዶችና አፈፃፀም እንዲሁም በአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችና መልካም አጋጣሚዎችን የሚመለከት መረጃ ለህዝቡ በፍጥነትና በግልጽ ማቅረብ ይገባናል፡፡
  ከዚህ አኳያ በየመስሪያ ቤቱና በየድርጅት ጽ/ቤቱ ያሉትን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊዎች አደረጃጀቶች በብቃት ማንቀሳቀስ ይጠበቅብናል፡፡
  ይህን የማጋለጥና መሠረታቸውን የመናድ ስራ እየሰራን አስፈላጊ ሆኖ በተገኘበት ደረጃና መጠን ደግም ህጋዊ እርምጃ መውሰድ ይገባናል፡፡
  እነዚህን በተናጠልና በድምር በመፈፀም በሃይማኖት ሽፋን የሚካሄዱ አፍራሽና አክራሪ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን በተሟላ አኳኋን አይሳነንም፡፡
ለመደበኛ አባላት የማይነገር ፤ ለከፍተኛ አመራሮች ብቻ
ቀጣዩ የምክር ቤት አባላት ምርጫ የግንቦት ሰባት አና አክራሪ እስልምና ሃይሎችን የሚያስቀጥሉ አባላት ወንብሩ በኢህአዴግ አባላት ስም ሊነጠቅ ይችላል፡፡
  የ97 የቅንጅት አሸናፊነት አካሄድ ስልት ማለትም የተቃዋሚ አባለት ሁነው በህቡእ ተደረጅተው በኢህአዴግ የአባላትንት ካርድ ሙሉ በሙሉ ፓርቲው ሊጎዱት ይችላሉ፡፡ 

Tuesday, November 26, 2013

EU Member of Parliament Ana Gomes in Addis Ababa

November 26, 2013
Ana Gomes, known for publicly criticising Ethiopia following the 2005 government crackdown
Serious talk! EU Member of Parliament Ana Gomes, known for publicly criticising Ethiopia following the 2005 government crackdown, which claimed over 200 lives, in a seemingly serious discussion during lunch break with Ethiopian MP and Speaker of the House Abadulla Gemeda in Addis Ababa, November 25, 2013. ANDUALEM SISAY | NATION MEDIA GROUP
The 26th European Union (EU) and African Caribbean Pacific (ACP) Joint Parliamentary Assembly (JPA) opened in Addis Ababa, Ethiopia Monday morning.
The assembly is expected to debate several issues, ranging from use of natural resources to fiscal reform and redistribution of wealth and decentralised cooperation.
The gathering is also expected to discuss respect for the rule of law and the role of an impartial and independent judiciary and South-South and triangular cooperation.
The assembly that will be concluded on Wednesday, has no decision-making powers.
However, it allows elected representatives of ACP countries to address their concerns directly to the EU Commission and be updated on the negotiations on trade deal, such as the Cotonou Agreement.
“There is an ample room for more enhanced partnership in many areas of interest to both sides,” said Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, while opening the assembly.
“But in a large sense, this relationship should not in any way be based on the rather obsolete assumption that one side is the ultimate provider and the other perennial receiver of resources whatever the object of the relationship might be – economic or political.”
JPA comprises 78 members of parliament and 12 vice-presidents from both sides (EU and ACP).
The assembly is expected to be concluded after discussing social and environmental impacts of pastoralism on ACP countries on the last day.
JPA meets twice a year, once in the EU, traditionally in the country holding the presidency of the Council of the EU and once in an ACP country, determined by the group of ACP countries.
Source: AFRICA REVIEW

Monday, November 25, 2013

“ኦሮሞዎች ኢትዮጵያውያን አይደለንም”የሚለውን መፈክር ማሰማት- ምን ማለት ነው?

November 25/2013

እኛ ኦሮሞዎች ኢትዮጵያውያን አይደለንም”የሚሉ ኦሮሞዎች እንዳሉ አውቃለሁ። ይህን አቋም የሚያራምዱት ከአጠቃላይ የኦሮሞ ህዝብ ውስጥ ምን ያህል ፐርሰንቱን እንደሚወክሉ ግን መረጃው የለኝም። በፖለቲካ ፓርቲ ደረጃ አንድኛው የኦነግ ክንፍ ከኢትዮጵያ የተለየችን ኦሮሚያ የመፍጠር ዓለማ ሰንቆ ሲንቀሳቀስ፤ ሌለኛው ደግሞ “መፍትሔው ሁላችንም በእኩልነትና በፍትህ የምንኖርባትን ኢትዮጵያ እውን ማድረግ ነው” ብሎ ማወጁን ከሁለት ዓመት በፊት ሰምቻለሁ። ይህ ብቻ ሳይሆን በነ ፕሮፌሰር መረራ የሚመራው ኦብኮ( ልብ በሉ ኦብኮ በ 1997ቱ ምርጫ ወቅት ከቅንጂት ቀጥሎ በተናጠል በርካታ የፓርላማ መቀመጫዎችን ያሸነፈና በኦሮሞ ህዝብ ንድ ተቀባይነቱን ያስመሰከረ ፓርቲ ነው) ፣ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ የተመሰረተው ኦፌዲንና ሌሎችም የኦሮሞ ፓርቲዎች- ከነባሩ ኦነግ የተለየ አቋም እንደሚያራምዱ እና ዲሞክራሲ፣ ፍትህና እኩልነት በሰፈነባት ኢትዮጵያ ውስጥ የ ኦሮሞን ህዝብ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥ ውጪ ሌላ የተሻለ አማራጭ እንደሌለ አውጀው እየተንቀሳቀሱ ነው። በ ያ ላይ ጥርስ የሌለው አንበሳ የሆነው የኢህአዴጉ- ኦህዴድም አለ። በኢትዮጵያ ጉዳይ ከ ኦነግ የተለየ አቋም የሚያራምዱት እኚህ ሁሉ ፓርቲዎች ይነስም ይብሳም የየራሳቸው ደጋፊዎች አሏቸው።

ከዚህ አንፃር ከታች በቪዲዮው የሚታዩት ሰልፈኞች እንደ ኦነግነታቸው፦”ሳዑዲ ዐረቢያ የኦሮሞ ህዝብን መግደል አቁሚ!”የሚል መፈክር ማሰማት መብታቸው ነው። “ኦሮሞዎችኢትዮጵያውያን አይደለንም!” የሚለው ግን የተሣሳተ እንዲሁም ከሞራልን ከህሊና አኳያ ተገቢ ያልሆነ ነው።

አዎ! ሰልፈኞቹ፦”እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም” ማለት ይችላሉ። በነፕሮፌሰር መረራ ፣ በነ ኦቦ ቡልቻ ደመቅሳ እና በሌሎችም በርካታ ኦሮሞዎች ጉዳይ ግን ህዝበ ውሳኔ ማሳለፍ አይችሉም። በየትኛው ውክልናቸው ነው ስለ አጠቃላዩ የ ኦሮሞ ህዝብ ውሳኔ የሚያሳልፉት በኢትዮጵያዊነታቸው የማይደራደሩ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊነታቸውን ጥያቄ ምልክት ውስጥ የማያስገቡ እልፍ ኦሮሞዎችን ባቀፈች አገር ላይ ፦”ኦሮሞዎች ኢትዮጵያውያን አይደለንም!” ብሎ ያለ ውክልና ማወጅ አይቻልም። “እኛ የኦነግ አባላት ኢትዮጵያዊ አይደለንም!”ማለት ግን መብት ነው። ይቻላል።

ሌላው ያሳነኝ ነገር የዚህ ሰልፍ ዓላማ በሳዑዲ በስደተኞች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስቃይና ግድያ እንዲቆም ለመጠየቅ ነው። ይህ ከሆነ እንደ ኦነግ አስተሣሰብስ ቢሆን ፦“ሳዑዲ ዐረቢያ የኦሮሞ ህዝብን መግደል አቁሚ!” የሚለው አይበቃም ነበር ወይ? “ በዝህ አስከፊ ሁኔታና ሁሉም ስለሁሉም እየጮኸ ባለበት ወቅት “ኦሮሞዎች ኢትዮጵያውያን አይደለንም”የሚለውን መፈክር ማሰማት- ምን ማለት ነው? ‘ሳዑዲ ኢትዮጵያውያንን መምታት ትችየለሽ’ ማለት አይመስልም ወይ? አረ እየተስተዋለ!
Dereje Habtewold

ተዋርደን አንቀርም!!!

November 25/201
ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር፡፡መቸም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር፡፡ህጉ የሚለው ግን ማስፈቀድ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡በተቃራኒው መንግስት በተለያዩ ጉዳዮች ሳቢያ በእለቱ ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ከለላ መስጠት የማይችልበት ሁኔታ ከገጠመው ሰልፉን ለጠራው አካል ችግሩን ገልጾ ቀኑ እንዲተላለፍለት ይጠይቃል፡፡

በመሆኑም ይህን መሰል ጥያቄ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ለፓርቲያችን ባለመቅረቡ በሙሉ ልብ ቅድመ-ዝግጅት ማድረጉን ተያያዝን፡፡
ሁሌም ቢሆን መንግስት ሰበብ ፈልጎ ሊወነጅለንና ከመስመር ሊያስወጣን እንደሚፈልግ በሚገባ እናውቃለንና በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ሳይቀር ጥንቃቄ እናደርጋለን፡፡ለሚመለከተው መስሪያ ቤት ባሳወቅን በአስራ ሁለት ሰአታት ውስጥ ምላሽ ስላልመጣ ሙሉ በሙሉ ህጋዊነታችንን አረጋግጠናል ማለት ነው፣እነሱ ደግሞ ጠብ-መንጃ በእጃቸው አለና የፈለጉትን ሁሉ ማድረግ ይችላል፡፡
አቶ ሽመልስ ከማል ለሚዲያወች የሰጡትን ፍጹም ከእውነት የራቀ ውንጀላና ሰበብ አዳምጨዋለው፡፡ “ሰላማዊ ሰልፉን ያገድንበት ምክንያት ጸረ-አረብ መፈክሮች ስለነበሩ ነው“ብለዋል፡፡መጀመሪያ ደረጃ ሰልፉ ገና ከግቢው ፈቅ ሳይል ነው ያፈኑት፣ሆኖም የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም አንድ በአንድ እየሆንን ወደ ሰላማዊ ሰልፉ መዳረሻ ለመሄድ ስንሞክር የተወሰኑ አመራሮችን አራት ኪሎ አካባቢ ያዙን፣እነሱ ቀድሞውኑ ሰልፉ እንዳይካሄድ ስለወሰኑ ነው እንጅ ትንሽ እንኳ ተንቀሳቅሶ የሰልፉን ባህሪ ለመገምገም ምንም እድል አልሰጡንም፡፡
ለምሳሌ ሰልፉን እንደምናደርግ ይፋ ባደረግን ማግስት ከራዲዮ ፋና ተደውሎ አንዳንድ ጥያቄዎች ተጠይቄ ነበር፡፡በቃለ-መጠይቁ ሰላማው ሰልፉ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰውን በደል በመቃወም እንደምናደርግ ተናግረናል፡፡ጋዜጠኛው ለሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች መልዕክት ካለ ብሎ በጠየቀኝ ወቅት የሳውዲ አረቢያ ሰንደቅ አላማ ላይ ያለው ምልክትና ጽሁፍ ሀይማኖትን የሚመለከት በመሆኑ ዜጎች በስሜታዊነት ባንዲራ እንዳያቃጥሉ፣እነሱ ቢያዋርዱንም እኛ ግን ክብር ያለን ዜጎች ስለሆንን ተቃውሟችንን ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ማካሄድ እንዳለብን ተናግሬ ነበር፡፡ከሰላማዊ ሰልፉ በፊት በዚህና በተለያየ መንገድ በማያሻማ ሁኔታ መልዕክት ባስተላልፍም እነሱ ግን ይህን በመቁረጥ አላስተላለፉትም፡፡እነዚህና ሌሎች ምክንያቶች ሲደመሩ የአቶ ሽመልስ ከማል ንግግር ነጭ ውሸት መሆኑን ያስገነዝባል፡፡
ሁለተኛ የአንድ ሀገር መንግስት ዜጎቹ እየተደፈሩ፣በማጎሪያ ካምፕ በረሀብና በውሃ ጥም፣ሌላው ቢቀር መጸዳጃ ቤት እንኳ ተከልክለው ፍጹም ከሰውነት ክብራቸው ወርደው እየተበደሉ፣እየተገደሉ ባለበት ወቅት ገና ለገና ተቃዋሚ ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ላይ በሚንጸባረቅ ጥላቻና ተቃውሞ የዲፕሎማሲ ግንኙነቴ ይበላሽብኛል ብለን መናገር እንችላለን?ሌላው ይቅር አንድ ክፉና ደጉን የለየ ሰው የሚያስበው ጤነኛ ሃሳብ ነው ማለትስ ይቻላል?
ከእገዳው ባሻገር የሚደንቀው ነገር ደግሞ በፓርቲያችን አመራሮችና አባላት ላይ የተደረገው ድብደባ ነው፣የሆነ ማስተላለፍ የፈለጉት ነገር ያለ ይመስላል፡፡የጭካኔያቸውን መጠን እንድናውቅ የሚደበድቡት አቅመ-ደካሞችን፣ሽማግሌወችንና ሴቶችን እየመረጡ በፍጹም አረመኔነት ነበር፡፡ይህን ተግባራቸውን ስመለከት የደረሱበትን የዝቅጠት ደረጃ መታዘብ ችያለው፡፡ከፖለቲካ ልዩነትም፣ከአምባገነንነትም በላይ ሰወቹ እንደታመሙ ነው ለመረዳት የቻልኩት፣ስር የሰደደ የቁስ ሰቀቀንና የስልጣን ጥም የተጣባቸው፣ለዚያ ሲሉም የትኛውንም አይነት ውርደት ለመቀበል የቆረጡና የሞራል ልዕልናቸውን ሙሉ በሙሉ ያጡ ሰዎች ናቸው፡፡ስነ-ልቦናቸው ክፉኛ ተቃውሷል እንጂ ሀገር እመራለው የሚል ቡድን እንዲህ ያለ ተግባር ይፈጽማል ለማለት እቸገራለው፡፡በአባላቶቻችን ላይ ክፍኛ ድብደባ ተፈጽሟል፣እስከዛሬም እግሮቻቸው መራመድ የማያስችላቸው፣የሚያነክሱ ሰዎች አሉ፡፡እውነት ለመናገር ይሄ እብደት ነው፡፡አንዲት እራሷን መከላከል የማትችል ሴትን ለሶስት መደብደብን ከዚህ በተሸለ ልገልጸው አልችልም፡፡
አንድ ማስገንዘብ የምፈልገው ነገር ለኛ ዋነው ጉዳይ የዜጎቹ ህጋዊነት ወይም ህጋዊ ያለመሆን ጉዳይ አይደለም፡፡በምንም አይነት መንገድ ሴቶች እየተደፈሩ፣ወንዶች በየስርቻው እንደ ውሻ ተቀጥቅጠው እየተገደሉ እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች ታጉረው ይህን ሁሉ መከራ መቀበላቸውን ልንታገሰው፣ወይም ከህጋዊነት አንጻር እየተራቀቅን ልንመለከተው አንችልም፣ስለ ህግም ከተወራ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ጭፍጨፋው ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ባላቸው ላይ ጭምር ሲፈጸም እንደነበር አምኗል፡፡
ባለንበት የግሎባላይዜሽን ዘመን የአንዱ ሀገር ዜጋ ካለ ሀገሩ መገኘት አገር ይያዝ የሚያስብል አይደለም፡፡መውጣት ካለባቸው ጊዜ በመስጠት፣ከመንግስታቸው ጋር በመነጋገር በዘዴ ነገሩን መከዎን እየተቻለ አንድ ሀገርና መንግስት በሰዎች ላይ እንዲህ የጭካኔ ጥግ የሆነን አቋም ይዘው መንቀሳቀሳቸው ፍጹም ኢ-ሰብአዊነት ነው፡፡
ለኢትዮጵያውያን እንዲህ ያለ አስከፊ ጊዜ የለም፣እውነቱን ለመናገር ለአገዛዙ ሰዎች የነበረኝ ጭላንጭል ተስፋም አፈር ተደፍቶባታል፣እንዲህ ግልጽ የሆነ ጭፍጨፋ እየደረሰብን እንኳ በድፍረት ለመናገር አልፈለጉም፡፡ስለ ኢትዮጵያውያን መገደል ለማውራት ሲፈልጉ ሌላ ሀገር ይጠቅሱና እነሱም እኮ እየተገደሉ ነው ይላሉ፣ወገን ከምንለው የማህበረሰባችን አካል ይሄን መስማቱ ከጥቃቱ ይበልጥ ያማል፡፡
ለምሳሌ ኢቲቪ ስጉዳዩ ሲያወራ ህገ ውጥ ሊባል የሚችል ድርጊት ተፈጽሟል በማለት ነው፡፡ተመልከቱ! እንዴት ያለ ባዕድነት ነው?ኢትዮጵያውያን በድህነትም ውስጥ እንኳ ለክብራችን የመሞት ባህሪ አለን፣ይሄ ከቀደሙት አንጡራ ኢትዮጵያውያን የወረስነውና ዛሬም ያለን ሀብታችን ነው፡፡
ትናንት ፍየል ጠባቂ የነበረ በረኸኛ ይህን ክብራችንን ገፍፎ እንደውሻ ቀጥቅጦ ስርቻ ሲጥለን ያልተቆጣ መንግስት ኢትዮጵያዊ ነው?ከዜጎቹ የወጣና ለህዝቡ የቆመ እውነተኛ መንግስት ከዚህ የበለጠ የሚቆጣበት ጉዳይ ከወዴት ይመጣል?
እውነተኛ መንግስት ቢሆን ኖሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሳውዲ ካምፓኒዎችን በሰአታት ውስጥ ማባረር፣ኢምባሲውን ዘግቶ አምባሳደሩን ማሰናበትን የመሳሰሉ ውሳኔዎችን ያሳልፉ ነበር፡፡የሆነው ግን በተቃራኒው ነው፣የድፕሎማሲ ግንኙነቴ ሊበላሽ ይችላል ብሎ እኛ ድምጻችን እንዳናሰማ ደበደበን፣አፈነን፡፡በግልጽ እንደሚታየው የጥቅም ትስስሩ ነው አፋቸውን ያዘጋቸው፣ይህች ጥቅማቸው እንዳትቋረጥ በዜጎች ህይዎት መደራደርን መርጠዋል፡፡
ስነ ልቦናቸው የተቃወሰ በመሆኑና ተራ ስስታሞች በመሆናቸው እንጂ ኢንቨስትመንትም ሆነ ዲፕሎማሲ ግብአትነታቸው ለሰው ልጅ ነው፣እንደ አህያ ሲያፈጋ ከርሞ ሬሳቸውን ለላከ መንግስት እንዴት ተመጣጣኝ ምላሽ ለመመለስ ይገዳል?እንዴት እንደ ኢትዮጵያ ያለች ታሪካዊትና ለአፍሪካ የነጻነትና የኩራት ተምሳሌት የሆነች ሀገርን እየመሩ እንዴት ትናንት የነዳጅ ዘይት ባቆማቸው እረኞች ስትዋረድ ዝም ይላሉ?!::
እንዴት!
በዜጎች ህይወት የተደራደረው አገዛዝ ማለፉ አይቀርም፣ለዚህ ጥርጥር የለኝም፡፡ታሪክ ለመጥቀስ ብዙ ርቀት መሄድ አያስፈልግኝም፡፡የቅርብ የሰሜን አፍሪካ አምባገነኖች የከፋ ፍጻሜ አለና፡፡ኢትዮጵያውያን ፍቅርም ጸብም እናውቃለን፣ሳውዲወችም የፈጸሙትን ግፍ ማወራረዳቸው አይቀርም፡፡በዚህ ክፉ ጊዜ ስለስብአዊ መብት ቆመናል የሚሉ አለም አቀፍ ተቋማት ዝምታን መምረጣቸው እውነተኝነታቸውን ለመመርመር ጥሩ እድል ይሰጠናል፡፡
መንግስት ቢኖረን ኖሮ ይሄ ሁሉ ውርደት ይፈጸምብን ነበር ብየ አላስብም፡፡በዚህ ሰአት ርዕሰ-መንግስት ብሆን ኖሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትልቅ ድርጅት እንደመሆኑ፣ወደየትኛውም ሀገር የሚደረገውን ጉዞ አቋርጨ ዜጎቸን ማስወጣትን አስቀድም ነበር፡፡ያሄ ጥቂት ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ሊያመጣብን ቢችልም ከከፋው የዜጎች ስቃይ ጋር ግን በአንድ ሚዛን ላይ አይቀመጥም፡፡የአደጋ መከላከያና ዝግጁነት ኮሚሽን የሚባል ድርጅት አለ፡፡በዜጎቻችን ላይ ጎርፍና ድርቅ ሲመጣ ብቻ ነው የሚንቀሳቀሰው? ይሄም ሰው ሰራሽ አደጋ ነው ሙሉ ሀይሉን ወደዚህ አዙሮ ሊንቀሳቀስ ይገባው ነበር፡፡
እርግጥ ነው ባቀድነው መሰረት ሰላማዊ ሰልፉ ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዳይሆን አድርገውታል፡፡ጩኸቱ ግን ይቀጥላል……ባለን አቅም ሁሉ አፈናውንም፣ወከባውንም ተቋቁመን ለዜጎቻችንና ለኢትዮጵያዊነት እንታገላለን፡፡
አገዛዙ ይሄን ሰላማዊ ሰልፍ ሲያፍን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንድ መልእክት አስተላልፏል፣ይህን መልእክት እንዲያስትላልፍ ማስገደዳችንም ለኛ ትልቅ ስኬት ነው፡፡የሳውዲ መንግስት ያሻውን ያደርግ ዘንድ የፈቀድኩት እኔ ነኝ፣በመሆኑም እሱን በመቃወም ግንኙነቴን አታበላሹ ብሎ እርምጃ በመውሰዱ ህዝቡ የነገሩ ቁልፍ የት እንዳለ፣የአጥቂወቹ በራስ መተማመን ምን ላይ እንደቆመ በጠራ ሁኔታ ለመመልከት እንዲችል ሆኗል፡፡
ይሄ ሁሉ ነገር እየተፈጸመ የተስተዋለ አንድ ነገር አለ፡፡የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዝምታ እውነተኛ ማንነታቸው፣እውነተኛ በአገዛዙ ውስጥ ያላቸውን ቦታ ያሳየን ክስተት ነው፡፡እንደሚታወቀው እሳቸው በኢህአዲግ እንጂ በኢትዮጵያ ህዝብ የተመረጡ አይደሉም፡፡ኢህአዲግ የሚናገረው ከሌለ እርሳቸው የሚሉት አይኖርም፡፡እንደ አንድ ሀገርና ህዝብ መሪ ግን የመኮነንም ሆነ የማጽናናት ቃል ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ባሉበት ቦታ ያስቀመጣቸው ህወሀት ነው፤ድርጅቱ ደግሞ ይሄን አቋም አልወሰደም፡፡ስለዚህ እንደሚቆጣቸው ስለሚያውቁ ዝምታን መረጡ፣ቸልታንም አስበለጡ፡፡በሀገርም ሆነ በግለሰብ ደረጃ ከዚህ በላይ ሽንፈት ያለ አይመስለኝም፡፡
(ይህ ጽሁፍ በፋክት መጽሄት ተስተናግዷል፣ነገር ግን መጽሄቱ ላልደረሳቸው ሰዎች ይደርስ ዘንድ እዚህ ለማስተናገድ ወደድኩ፡፡)

Sunday, November 24, 2013

SMNE urges Minister Tedros Adhanom to take swift and comprehensive action

November 24, 2013

SMNE urges Minister Tedros Adhanom to take swift and comprehensive action in addressing the shameful treatment and humiliation of Ethiopian migrant workers in the Kingdom of Saudi Arabia (KSA) and other countries in the Middle East.

An open letter to Minister of Foreign Affairs
Dr. Tedros Adhanom Ghebreyesus
Minister of Foreign Affairs
Federal Democratic Republic of Ethiopia
Addis Ababa, Ethiopia
Dear Minister Tedros Adhanom:
I am writing this letter to you as your Ethiopian brother who shares the same beautiful country despite the fact we hold to significantly different political views. As the executive director of the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE), a social justice organization that stands for the well being of all our diverse Ethiopians, I am not here to please you or anyone else, but instead I am here to urge you, the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) and the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) to take swift and comprehensive action in addressing the shameful treatment and humiliation of Ethiopian migrant workers in the Kingdom of Saudi Arabia (KSA) and other countries in the Middle East.
Whether or not Ethiopians agree with you or whether or not they believe that the TPLF/EPRDF is representative of the people does not make a difference in this because you are the ones now in charge. You may not agree with what I will be saying, but I feel the moral obligation to speak forthrightly about what I believe to be true; if you consider me to be in error at any point, I am accountable for whatever I say. The humiliation and shameful mistreatment of the Ethiopians that is going on now is not only felt by those Ethiopians experiencing it physically, but it is also felt by all Ethiopians wherever they are, whether or not they are TPLF/EPRDF supporters, members of an opposition group or completely non-political.
This has been proven in the last weeks as tens of thousands of Ethiopians from more than 30 countries and 80 cities throughout the world have come out and continue to come out with one unified message: “Stop the mistreatment of Ethiopians in Saudi Arabia.”The suffering of our people in Saudi Arabia carries our name with it, putting all of us, including you and the TPLF/EPRDF, in the same box even if we do not agree on many other things.
This is not a problem to be solved or funded by the World Bank, United Nations, other countries, international organizations, the Ethiopian Diaspora or the Ethiopian opposition. Only the TPLF/EPRDF has the capacity and clear responsibility to deal with the magnitude and scope of this massive human tragedy of our people. Current efforts are not enough! Ethiopians all over the world are outraged by what is ensuing at the hands of a country supposed to be a friend of Ethiopia. It is intolerable.
My first question: where is Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn? The man who is supposed to be the leader of Ethiopia has failed to say anything about this? Why? In any other country where leaders are elected by the people, such silence in the face of such immense suffering would be considered dereliction of the prime minister’s primary duty to protect the citizens of the country and would be reason to resign.
Some are saying it is an indication of the EPRDF’s plan to replace him with yourself. If true, why such political maneuvering when it comes to such a critical issue? We strongly hope the reported sympathy you show for these Ethiopians in harm’s way is genuine and not simply a part of damage control for the benefit of the EPRDF or about enhancing one’s own personal image for future political aspirations.
In the speech you gave before the Third International Family Planning Conference in Addis Ababa on November 16, 2013, you focused almost exclusively on the plight of Ethiopians in Saudi Arabia; but in fact, the problem of Ethiopians is worldwide, especially in the Middle East where so many are suffering.
Why is there not a reaction from the EPRDF to the plight of Ethiopians in many other places? Why have we not seen this kind of caring coming from you or others in the EPRDF over the last few years as these stories of abuse came out? What has the EPRDF done to stop it?
Those Ethiopians in the Diaspora and within the country with access to the international media have heard heartbreaking stories about the mistreatment of Ethiopian domestic maids and other migrant workers in many parts of the Middle East. Like most other Arab countries, Saudi Arabia uses the kafala system where those Ethiopians entering the country with a one-way ticket must give up their passports and other identification papers at the airport. These are the very documents needed to obtain exit visas, required by law before one can leave the country; yet, many never see their passports and papers again.
Saudi authorities claimed to provide a 7-month amnesty period to undocumented workers before being deported, but it is impossible to obtain such a visa without proving their legal status. That requires a passport. In cases where Ethiopians did have such documents in their possession, it often has not made any difference as they still have been rounded up and mistreated. (See our previous press release for more detailshttp://www.solidaritymovement.org/downloads/131111-SMNE-Calls-on-ERPDF-to-Protect-Ethiopians-in-Saudi-Arabia.pdf) Ethiopians on the ground predict difficulty in rapidly returning Ethiopians to their home country; believing it will prove to be an administrative nightmare, taking many months, unless there is a relaxation of regulations in Saudi Arabia and the utmost of cooperation between them, employment agencies, the Ethiopian Embassy, the Ethiopian government and other institutions involved.
We both know that one of the reasons this crisis is so mammoth is because it did not start two weeks, two months, or two years ago. The influx of Ethiopians to the Middle East started nearly six years ago, but the flood of Ethiopian refugees and migrant workers was birthed out of the oppressive policies of the TPLF/EPRDF and the exclusion of most Ethiopians from equal opportunities reserved for party supporters. Under other circumstances, these workers would have remained to live and work in their home country; however, so many of our people are so desperate with the lack of food, opportunity, hope and life in Ethiopia that even if they were warned about inhumane working conditions and abusive treatment in the Middle Eastern countries like Saudi Arabia, they ignored them.
 Large billboards paid for by employment agencies throughout Addis Ababa, other cities and even in the countryside advertised to attract more innocent and unwitting recruits. Yet, many quickly became entrapped in situations where they were regularly beaten, raped or overworked but could not escape because of those papers and laws that prohibited them from changing employers. What has the EPRDF done in response to the daily or weekly accounts of Ethiopians committing suicide or losing their minds—even after recently hearing that 90% of those in hospitals for mental breakdowns were Ethiopian women?
Why did you, (the Minister of Foreign Affairs) not stop these employment agencies from continuing to recruit these young people when you heard these accounts? Instead, tens of thousands of workers were sent off to this plight on a monthly basis. Last year, according to your own government website, 160,000 domestic workers sought employment in the Middle East, most through employment agencies within our own country. Who is making a profit from the hardship, blood and humiliation of our people? Why was there not a crackdown months or years ago? 
If this were taking place in a country where people keep their elected officials accountable and where the rule of law is enforced, individuals in positions like your own, would have been fired or would have resigned because of the moral shame of it.
In your talk you said you could not even sleep because of the mistreatment of Ethiopians while the EPRDF’s security forces cracked down on innocent Ethiopians rallying in front of the Saudi Embassy in Addis Ababa who were only protesting the same mistreatment of their people as were you. Why are you sleepless for those being beaten, arrested and tortured in Saudi Arabia and not for those beaten, arrested and tortured in Addis Ababa? Is the pain our people feel different when it is committed by Saudi police rather than by the EPRDF police? Does it really matter who is doing it? It is the people of Ethiopia you are to represent; but instead, the EPRDF is brutally violent with Ethiopians who were rallying for the same cause you claimed to care about. Should you not have rather joined together with them in their protest instead?
On the other hand, when it comes to the horrible abuse, rape and mistreatment of our people, we Ethiopians have forgotten our differences. We are Ethiopians and above all, we are human beings created in the image of God. He knows who we are and hates injustice, oppression and the exploitation of the vulnerable. Yet, one Saudi Arabian posed a very good question. He asked, “Before you curse us and dehumanize us, tell your own government to treat you decently?”
Regardless of how Ethiopians are treated either by Saudis or by the EPRDF, we know who we are. We are a people created, gifted and loved by God. It is our Creator who gave us this land of Ethiopia to call our own. Why is our land drying up to our own people? What has happened to the heart and soul of Ethiopia? The situation in Saudi Arabia is alarming but the real crisis is in our own country? Is the ruling regime of TPLF/EPRDF ready to do something about it? We recognize that you and your ethnic group are in power for now, but for what gain if it is at the expense of others? How hard must one get before the impetus for change comes sincerely from softened hearts towards the pain and suffering of others?
We are not interested in words and pretenses but in a transformational change that will embrace a New Ethiopia for all our children—yours, mine and our peoples’—the present and coming generations. Suppressing the truth or simply putting small bandages on a critically wounded nation will only galvanize increasing numbers of Ethiopians to demand sustainable remedies to this systemic illness we face in our country.
In light of this, on behalf of these voiceless and oppressed Ethiopians in Saudi Arabia, I call on you to take immediate and comprehensive action by bringing back all Ethiopians wanting to return to their motherland, whether documented or undocumented and whether they are in Saudi Arabia by choice, through deception, as a result of human or sexual trafficking or by any other means. It should not matter now. It is your responsibility and that of the regime you serve to bring our people back like any nation would do that cares about its nationals. Any who want to come home should be brought, even if there are no jobs for them in Ethiopia. It is better to become a beggar with dignity than to live in a place where they are unwanted, mistreated and dehumanized.
Never have Ethiopians been more united. Groups of all kinds and sorts, including pro-TPLF/ERPDF groups, are standing up for the victims—knowing they are “us.” Who cares about what kind of flag is being waved?  This is about other human beings. This is about our people. These Ethiopians are not checking out the ethnicity, religion, political view or background of those being mistreated to see if they match their own before being outraged about the Ethiopian man beaten to death on the streets of Jeddah or the Ethiopian woman gang-raped by a mob of civilian thugs. Instead they are seen simply as Ethiopians. No human being, including other migrant workers from other countries, should be treated in that way and Ethiopians know this. Their hearts are breaking in response to the cries of our people.
This is an opportunity for the EPRDF to act for the good of all of us. It is a second-chance to show who you are. It is an opening that is fragile and fleeting. It can be used rightly or wrongly; in a timely and earnest fashion or missed entirely through failing to act or acting in pretense.
As you may already know, the SMNE (http://www.solidaritymovement.org) is based on the principles of putting humanity before ethnicity or any other differences and that no one is free until all are free because when a society values and cares for its people, it builds the foundation for healthier, more harmonious and more prosperous communities, villages and nations. What Ethiopians have experienced on-the-ground under the TPLF/EPRDF regime you represent is a system which has exercised political and ethnic-based favoritism to the exclusion of the majority.
Despite the EPRDF’s many laws, institutions, pretenses and public assertions to the contrary, the disillusioned and desperate lives of Ethiopians attest to the facts. The acclaimed double-digit economy still leaves the majority in such poverty that they are leaving the country and becoming the victims of modern slavery in wealthy Arab countries. Addressing these issues would be part of a long-term solution to the flood of Ethiopians refugees to not only the Middle East, but to all sides of the globe where their suffering is not new.
Many report that the Ethiopian Embassy in Saudi Arabia has been unresponsive to their pleas for help and have even turned away young women who have bruises on their bodies and faces from mistreatment. The Ethiopian Embassy in Saudi Arabia was closed for three days this past week and finally reopened. Why in the midst of this crisis? Stories from the ground in Saudi Arabia have emerged substantiating the alleged illegal connections between employment agencies in Ethiopia, Ethiopian Embassies and traffickers, not only in the Middle East but in other countries, like South Africa, as well. How can this mounting crisis be solved without pursuing a thorough investigation of these practices? The EPRDF must hold accountable any of those Ethiopians who are making money out of the suffering of these people through illegal actions. Now the Saudis have reportedly dumped off thousands of Ethiopians at the border of Yemen with no supplies or means of survival. What will you do for them? Will you be sleepless for those in Yemen, Dubai, the United Arab Emirates, Lebanon and beyond?
You have spoken of your commitment to bringing these people home and have claimed that 10,000 people were repatriated by November 20, 2013 and that 19,428 were repatriated to Ethiopia by 10:00 PM, Ethiopian time, on November 22, 2013. This appeared on your Twitter account. People at the airport in Addis Ababa say they have not seen many people coming in let alone these huge numbers.
How could they come in these numbers without being noticed? Which airline are you using for transport and which kind(s) of plane? How many passengers per plane and why have Ethiopians not seen a flood of arrivals from Saudi Arabia? How will you deal with the high level of skepticism among Ethiopians who would like to challenge you on these enormous figures even while hoping you are speaking the truth?
However, the credibility of the EPRDF is in question. To bring that many people (19,000) in the last few days will have required more than 22 flights on an Airbus, the largest of all planes, with the maximum passengers allowed—853. However, most airbuses are set up to only accommodate an average of 480-490 according to Wikipedia’s website on Boeing’s Airbus [i]. Most other planes will only take 400 or fewer passengers. The video coverage of you at the airport with the incoming migrant workers shows no more than 100 people with you at the airport. If this is a scam it is only another humiliation to the world that these numbers have been so grossly inflated. Why is the media not covering this?
The task of repatriation is not an easy one and if your office and the TEPRDF are genuine in carrying this out, Ethiopians will exercise patience and you will earn of the respect of many; however, even then, the EPRDF must look at root causes and long-term solutions if this situation is going to improve and not blow up again sometime and somewhere else. This will entail a much longer discussion in the future;however, for today’s problem, I, on behalf of the SMNE and the Ethiopian people who have asked for help, will offer the following recommendations:
Recommendations:
  1. The EPRDF should find a way to send multiple planes or ships to bring people back home as soon as possible, even if it means subsidizing Ethiopian Airlines and others to accomplish this large task. The EPRDF should also find the means to utilize large ships that could have the capacity to transport four to five thousand passengers at a time as a means to ship the people across the Red Sea, at least to Djibouti where buses could bring them to Addis Ababa or other destinations. 
  1. The EPRDF should negotiate with Saudi Arabian officials to cut down on red tape linked to the kafala system and other administrative challenges that obstruct the swift repatriation of our people due to their current suffering. The problems inherent to a system that immediately confiscates passports and other identification documents belonging to migrant workers upon entry into the country should be quickly overcome due to the massive task on hand and the unfair predicament of Ethiopians whose paperwork is not accessible through no fault of their own.
  1. The EPRDF should ask the Ethiopian-Saudi Arabian billionaire, Sheikh Mohammed Hussein Al Amoudi, to help finance the transportation of these people; not only because it is the right thing to do, but because this man is half Ethiopian—his mother is an Ethiopian and his father is Saudi. He could use not only his money but also his influence as a Saudi to tell the Saudi kingdom to treat Ethiopians with respect and dignity. Why has he not come out in outrage regarding the beating, torture and rape of these people? The young Ethiopian woman, suffering in the hands of Saudi men, could have been his Ethiopian mother. He has made a good amount of his billions in Ethiopia and so now it is his turn to give back. This is his chance to show if he wants to continue his business in the New Ethiopia.
  1. Due to the lack of trust in the TPLF/EPRDF, an independent group, which is not connected to the TPLF/EPRDF, like the International Organization for Migration (IOM) or human rights groups, should observe the process and the results. Let them document what is going for accuracy. It will increase your credibility if it is not a whitewashed report. We all agree that the EPRDF should repatriate Ethiopians, but are highly suspect of the numbers. You say the government is working on this 24 hours a day, but in this atmosphere of mistrust, verification of the facts on the ground is necessary to be believed. Why does the camera not go to those shelters?
  1. If the EPRDF is genuine in carrying out its mandate, these efforts should not stop with Saudi Arabia but should include other Ethiopians experiencing similar difficulties in Yemen, Lebanon, Dubai, Libya, UAE, or other places, especially those using the kafala system.
  1. Numerous reports of corrupt practices on the part of Ethiopian employment agencies and staff at Ethiopian Embassies in Saudi Arabia and other places point to the complicity of some in the trafficking and what has become the modern slavery of our people. Allegations that the TPLF/EPRDF has turned a blind eye to what may be endemic organized crime should be thoroughly investigated and any found guilty should be held accountable. Reports that are numerous and credible alleging that criminal enterprises are being conducted behind the scene in Ethiopian embassies throughout the world, including in Europe, should not be overlooked but investigated.
  1. Remove all billboards and other forms of recruitment and assignment of migrant workers to the Middle East until further investigation ascertains that it is safe for our people.
  2. If the Saudis continue to do this to our people in their country, you have the power to evict Saudi investors who are capitalizing on our resources, particularly where the peoples’ rights have been violated and where the landor resources of Ethiopians have been illegally confiscated with little or no benefit to the people of Ethiopia.
To the Kingdom of Saudi Arabia and its people, our Saudi Arabian neighbors:
We ask you to desist from any mistreatment of Ethiopian migrant workers in your country and to facilitate the process of their return, particularly in regards to the provision of exit visas. If they are unwanted in the KSA, their own country should receive them swiftly.
We also recognize these actions by the KSA to be in direct violation to the directions given by the Prophet Muhammad, revered and honored by many of our fellow Ethiopians, which explicitly prohibited any of his disciples from ever committing such acts against those who gave not only refuge to his followers, but hospitality.
To the people of Saudi Arabia:
We recognize that these draconian policies being carried out in the Kingdom of Saudi Arabia by its officials and some civilians do not reflect the attitudes, behavior and spirit of many wonderful Saudi Arabians who may be as outraged as are we. We continue to seek good relations with all who uphold the dignity and respect of all people, regardless of whether we share the same ethnicity, religion, culture or viewpoint for we believe humanity should come before ethnicity.  Our Creator endowed all of us with worth.
Minister Tedros Adhanom:
The failure of the Ministry of Foreign Affairs and the TPLF/EPRDF to care for our own people is why we are dealing with this tragedy now. There are many other countries in Africa that are as poor or even poorer than Ethiopia, but you do not hear the horror that their people are facing like what we hear from Ethiopians.
To revive the soul of our beautiful country of Ethiopia again will only come as God helps us to soften our hearts towards others, resulting in the restoration of justice, forgiveness, and the embracing of each other. We seek a country where the value of human life is not judged by whether one is a child of the elite, the wealthy or the favored ethnic group running the country but because one is human and Ethiopian.
I await your response and hope you will swiftly act on this.
Sincerely yours,
Obang Metho, Executive Director of the SMNE
On behalf of the SMNE and Ethiopians suffering in Saudi Arabia and throughout the world
910- 17th St. NW, Suite 419
Washington, DC 20006 USA

“የኢትዮጵያ ህዝብ ለውጥ ፈልጓል፤ ግን ለውጡን የሚሸከምለት ፓርቲ ይፈልጋል”

“የኢትዮጵያ ህዝብ ለውጥ ፈልጓል፤  ግን ለውጡን የሚሸከምለት ፓርቲ ይፈልጋል”November 24/2013

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በቅርቡ ከአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ጋር ውህደት፣ ከሌሎች 10 ፓርቲዎች ጋር ቅንጅት ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ሲሆን ፓርቲው ከረጅም አመታት በኋላ የፕሬዚዳንት ለውጥም አድርጓል፡፡

 ከአዲሱ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ ጋር ፓርቲው ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር እየፈጠረ ስላለው ውህደት እና ቅንጅት እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤ በፓርቲው ጽ/ቤት ተገኝቶ አነጋግሯቸዋል፡፡
ከ“መድረክ” ጋር ያለው ጥያቄ “አንድነት” ሊፈታው የሚገባው ነው ፓርቲያችን ግራ የተጋባ አይደለም መኢአድ በሀገሪቱ ካሉ ፓርቲዎች ጠንካራው ነው ህዝቡ እውነተኛውንና ውሸታሙን መለየት አለበት::
ከ“አንድነት” ፓርቲ ጋር ውህደት ለመፈፀም የጀመራችሁት ውይይት ምን ላይ ደረሰ? ውህደቱንስ በዚህን ወቅት መፈፀሙ ለምን አስፈለገ?
ህዝባችንን ካለበት ችግርና የሰብአዊ መብት ጥሰት ነፃ ለማውጣት የጋራ አላማ ያላቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች በአንድ ላይ መስራት ወሣኝነት አለው ብለን እናምናለን፡፡ ተለያይቶ ድምጽ ከመሻማት ይልቅ አንድ ላይ ሆኖ ሃብትንም ሆነ ሌላ ሌላውን አቀናጅቶ መንቀሳቀስ ጠቃሚ ነው፡፡ በህዝቡም ላይ በራስ መተማመንን ፈጥሮ ሃይል ያለው “ሊመራኝ የሚችል ፓርቲ አለኝ” ብሎ እንዲያምን አንድ መሆን ወሳኝ ነው ብለን እናምናለን፡፡ እኔ አሁን ባለው ደረጃ ማለት የምችለው፣ አንድነትና መኢአድ ለመዋሃድ ድርድር እያደረጉ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን መግለጫ ለመስጠት ያስቸግረኛል፡፡ ምክንያቱም ሂደቱ በራሱ ኮሚቴ የሚመራ ነው፡፡ ኮሚቴው ማንም ሰው በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ መስጠት አይችልም የሚል ፕሮቶኮል ፈርሟል፡፡ የየፓርቲዎቹ ባለስልጣናትም ሆኑ ተደራዳሪዎች መግለጫ መስጠት አይችሉም፡፡

 ከአንድነት ጋር ውይይት ጀምረናል ብላችኋል፣ አንድነት ደግሞ የመድረክ ግንባር አባል ነው፣ እናንተ ደግሞ መድረክን እንደማትፈልጉት በተደጋጋሚ ገልፃችኋል፡፡ ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል?

መኢአድ በኢትዮጵያ አንድነት ጥላ ስር ለመሄድ ከማይፈልጉ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመንቀሳቀስ ይቸገራል፡፡ የመኢአድ አወቃቀሩም ሆነ አላማው ሁሉም ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ጥላ ስር መንቀሳቀስ አለባቸው የሚል ነው፡፡ በጐሣም ተደራጅተው በኢትዮጵያ ጥላ ስር ሆነን “አንዲት ሉአላዊት ኢትዮጵያ” በሚለው ስር አብረን እንሄዳለን ካሉ አብሮ ለመስራት ችግር የለውም፡፡

 ስለዚህ አንድነት በመድረክ ስር ሆኖ እንዴት ይሆናል የሚለው የራሱ የአንድነት ጉዳይ ነው፤ የመኢአድ ጉዳይ አይደለም፡፡ መኢአድ እና አንድነት እየተደራደሩ ነው፤ ሁለቱም ተመሳሳይ ፕሮግራም፣ አላማ፣ ደንብ ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን ከመድረክ ጋር ያለውን ጥያቄ አንድነት ሊፈታው የሚገባው ጥያቄ ነው እንጂ የመኢአድ አይደለም፡፡ ይሄ የድርድሩም አካል ነው፡፡
ውህደቱን ስትፈጽሙ አመራሩስ እንዴት ነው የሚደራጀው?

እንግዲህ እንደነገርኩህ በዚህ ላይ መግለጫ ለመስጠት ያስቸግረኛል፡፡ ተደራዳሪዎች ስላሉ ይሄ ነው ብሎ ለማለት ፕሮቶኮሉ ያስረኛል፤ ነገር ግን ውህደት ከተካሄደ ውህደት የሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ ይፈፀማሉ ማለት ነው፡፡ ለዚህ ካለአመራሩ ይሄ ይሆናል ማለት አልችልም፡፡
መኢአድ ከሌሎች ፓርቲዎች የሚለየው በምንድነው?

ፓርቲያችን ተመሳሳይ ደንብ እና አላማ ካላቸው ፓርቲዎች የሚለይበት አንደኛ፣ ህብረ ብሔራዊ መሆኑ ነው፡፡ የመኢአድ እምነት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በኢትዮጵያ፣ ጥላ ስር ሆኖ የእያንዳንዱ ዜጋ መብት ሲከበር፣ የሁሉም ዜጋ መብት ይከበራል ብሎ ያምናል እንጂ የአንድ ጐሣ መብት ሲከበር የጐሣው አባላት መብት ይከበራል ብሎ አያምንም። አሁን ለምሣሌ ገዢው ፓርቲ ውስጥ ያለው የብአዴን መብት ሲከበር፣ የእያንዳንዱ አማራ መብት ተከበረ ማለት አይደለም፡፡ የኦህዴድም በተመሳሳይ፤ ሌላው መኢአድ የሚመራው በሊበራል ዲሞክራሲ አስተሳሰብ ነው፤ ይሄ ከሌላው የሚለየን ይመስለኛል። ሌላው የምንለይበት ፓርቲያችን ግዙፍ የሆነ አደረጃጀት ያለው ነው፡፡ በመላው ሃገሪቱ በሚገኘው እያንዳንዱ ቀበሌ መኢአድ አለ፡፡
በአራቱም ማዕዘናት ቢኬድ መኢአድ የሌለበት ቀበሌ የለም፡፡ እንዲሁም ፓርቲው የእያንዳንዱ ብሔር ጥንቅር ውጤት ነው፡፡
ምናልባት የብሔር ተዋጽኦው ሲነሣ እርስዎ ከሚሉት በተቃራኒ የአማራው ሚና የሚጐላበት እንዲያም ሲል አመራሩ እና ማዕከላዊ ኮሚቴው ለሰሜን ሸዋ አካባቢ ተወላጆች ብቻ የተሰጠ ነው የሚል ወቀሳ ይቀርብበታል…

እዚህ ላይ አሁን የመኢአድን አመራር ጥንቅር ያየህ እንደሆነ ከአማራው፣ ከጐፋው፣ ከወላይታው ያለበት ነው፡፡ ለምሣሌ የፓርቲውን ምክትል ተቀዳሚ ሊቀመንበር ብንወስድ ከጐፋ ነው፣ የመኢአድን የስራ አስፈፃሚ ብትወስድ ኦሮሞች አሉ፤ ለምሣሌ ብሩ ደሲሣ ከአሶሳ አለ፣ ገለቱ ኤጀርሣም አለ፡፡ ስለዚህ ይሄ የጠላት ወሬ ነው። መኢአድን ለማዳከም የሚነዛ አሉባልታ ነው። አማራው ከሌላው ብሔር የበለጠ በዚህ ፓርቲ ውስጥ ተሳትፎ የለውም፡፡ ለምሣሌ የአባላት ጥንቅርን የወሰድን እንደሆን በሰሜን ካለው አባል የበለጠ በደቡብ ነው ያለው፡፡ ከ39 በመቶ በላይ በደቡብ አካባቢ ያሉ ናቸው፡፡ ከሰሜን ሸዋ የመጡ ናቸው የሚባለው የሰሜን ሸዋ ህዝብ ወይም በዚያ የሚገኝ የአማራ ተወላጅ እንዳጋጣሚ ሆኖ አማራው ይገደል በነበረ ጊዜ ፕ/ር አስራት ፓርቲውን ይመሩ ነበር፡፡ ይህ ማለት ግን አመራሩ በጠቅላላ ከሰሜን ሸዋ ነበረ ለማለት አይቻልም። እሣቸው እንደ ፕሬዚዳንት ከሰሜን ሸዋ ይሁኑ እንጂ ከተለያዩ የአማራ ክፍሎች የተውጣጣ የስራ አስፈፃሚ መዋቅር ነበር፡፡ ፕ/ር አስራት፤ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅትን ሲያቋቁሙ የአማራው ወይም የአንድ ብሔር ፓርቲ አድርገው ለማቋቋም አልነበረም ፍላጐታቸው፤ ነገር ግን ይገደልና ይሰደድ የነበረውን አማራ ከጥቃቱ ለመከላከል ያህል ያቋቋሙት ነው፡፡ በወቅቱ ለጊዜው አማራው ላይ የሚደርሰውን ጥቃት እንከላከልና ኋላ ላይ ህብረ ብሔራዊ ሆኖ ሁሉንም ብሔሮች አሣትፎ ይቀጥል የሚል መርህ ነበራቸው፡፡ በዚህ መርህ አሁን ካለበት ደረጃ ደርሷል፡፡ አማራው በዚህ ውስጥ በምንም ሁኔታ የበላይነት የለውም፤ ይሄ የጠላት ወሬ ነው፡፡

 ከዚህ ቀደም ከመድረክ ጋር አብረን አንሰራም ብላችሁ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ 10 ፓርቲዎች ያሉበት ቅንጅት በመኢአድ ጉልህ ሚና እየተፈጠረ ነው ያለው፡፡ ከዚህ ፓርቲዎች አብዛኞቹ የጐሳ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ከመድረክ ጋር አብሮ አያስጉዘንም ያላችሁበት አጀንዳን ወደ ጐን ትታችሁ አሁን እንዴት ከነዚህ ፓርቲዎች ጋር ለመቀናጀት መረጣችሁ?

ትክክል ነው እነዚህ ድርጅቶች የጐሳ ናቸው። ኢህአዴግ ኢትዮጵያን በጐሳ ሲሸነሽን እነዚህ ፓርቲዎች በጐሳቸው… ተደራጅተው ነው፤ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ፓርቲዎቹ የጐሣ ቢሆኑም በኢትዮጵያ ጥላ ስር ሆነን እንታገላለን ያሉ ናቸው። ስለዚህ ፓርቲዎቹ በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር መሆንን የሚሹ ናቸው፡፡ የጐሣ/ብሔር/ ፖለቲካ እንደማያዋጣ አምናለሁ፤ በኢትዮጵያ ጥላ ስር ሆነን ከመኢአድ ጋር እንታገላለን ስላሉ ነው የተቀበልነው፡፡ እንግዲህ የነበሩት 33 ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ከ33ቱ አብዛኞቹ በጐሣችን ብቻ ነው የምንታገለው ስላሉ አማራጫቸውን ይዘው ሄደዋል፡፡ በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ሆነን እንታገላለን ያሉት መኢአድ እንዲያታግላቸው ወደዚህ መጥተዋል፡፡ እዚህ ላይ ግልጽ መሆን ያለበት ከመጡት ውስጥ 70 በመቶ የሚሆኑት የብሔር /ጐሣ/ ድርጅቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ህብረ ብሔራዊ ናቸው፡፡

 ከመድረክ ስብስብ ጋር ያላችሁ መሠረታዊ ቅራኔ ምንድን ነው? ከስብስቡ ውስጥ በኢትዮጵያዊነት አያምኑም ብላችሁ የምትጠቅሷቸው ፓርቲዎች አሉ እንዴ?

በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ካለማመን ባሻገርም በአንዳንድ ፖሊሲያችንም እኮ እንለያያለን፡፡ ለምሣሌ በመሬት ጉዳይ፤ መኢአድ መሬት የህዝብ ነው፤ መንግስት ሊያዝበት አይችልም ብሎ ነው የሚያምነው፡፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ጥሪት ሊኖረው ይገባል ብሎ ያምናል፡፡ ዜጐች መሬት ተከራይተው ሊኖሩ አይገባም፤ ይሄ የመኢአድ ፖሊሲ ነው፡፡ ነገር ግን የሌሎቹ የመድረክ አባላት ፕሮግራም በዚህ አያምንም፤ የኢህአዴግን ነው ይዘው የሚሄዱት፤ በነገራችን ላይ አንዳንዶቹ ኢህአዴግ ዲሞክራሲያዊ ስላልሆነ ነው እንጂ በፖሊሲ ደረጃ አንለይም ባይ ናቸው፡፡
መድረክ ውስጥ እንደዚያ የሚሉ ድርጅቶች አሉ?

አዎ! በሚገባ

 የአስሩን ፓርቲዎች ፖሊሲና ፕሮግራም ካስቀመጡልን ነጥቦች አንፃር በሚገባ መርምራችኋል ማለት ነው?

መቶ በመቶ በሚገባ አጥርተን መርምረናል፣ ፕሮግራማቸውን አንብበን እና ተናበን ነው ይሄን ያደረግነው፡፡
በ1997 ስለተፈጠረው ቅንጅት አመሰራረትና ውድቀት ብዙ ተብሏል፡፡ የአሁኑን ቅንጅት ከፈረሰው ቅንጅት ምንድን ነው የሚለየው?
ቅንጅት ስንል ያው ቅንጅት ነው፡፡ አይለያይም። እያንዳንዱ ፓርቲ የራሱን ህልውና ጠብቆ ነገር ግን የሚመጣው ችግርና አደጋ በአንድ ላይ እንታገላለን ብሎ የሚያምን ነው፡፡ ስለዚህ አንድ ላይ ተጨፍልቆ አንድ እንደመሆን አይታሰብም፡፡ በ1997ም እያንዳንዱ ፓርቲ በዚህ አይነት ሁኔታ ራሱን የቻለ ነበር፡፡

 ግን በአንድ ፕሮግራምና በአንድ የመወዳደሪያ ምልክት ነበር ለምርጫው የቀረበው…

ይሄም ልዩነት አይኖረውም፤ እንደዚያው ነው። ነገር ግን የአሁኑ በየክልሉ ያሉት ፓርቲዎች ቢሮ ካላቸው እንደ ግንኙነት መድረክነት ያገለግላል፤ በየክልሉ በቀላሉ ተደራሽ መሆን ይቻላል፡፡ ከዚያ በተረፈ ከ97 ዓ.ም ቅንጅት ልዩነት የለውም፡፡

 ወደ አንድነት ድርድሩ እንመለስና የ97 ቅንጅት ሲፈርስ መኢአድ ህልውናውን ጠብቆ ሲጓዝ “አንድነት” ደግሞ የመኢአድ አባላት የነበሩትን ጨምሮ በቅንጅቱ መፍረስ ቁጭት ባደረባቸው ፖለቲከኞች የተቋቋመ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ያን ጊዜ በአንድነት መጓዝ ያልቻላችሁ አካላት ዛሬ ምን ታይቷችሁ ነው አንድ ካልሆንን እያላችሁ ያለው?

መቼም አንድ ላይ ስትሠራ ትጋጫለህ ትኮራረፋለህ፣ የሃሣብ ልዩነት ይፈጠራል። እያንዳንዱ አመራር ልዩነት ይኖረዋል፡፡ ይሄ እንግዲህ ያለ ነው፡፡ ችግራችን ምንድነው ልዩነት ሲመጣ የግለሰቦች ፀብ ነው ነጥሮ የወጣው፤ ነገር ግን ይሄ መሆን የለበትም፡፡ ግለሰቡን ሣይሆን ከተቃወምንም ሃሳቡን ነው መቃወም ያለብን። ኢትዮጵያውያን የሚጐደለን ይሄ ይመስለኛል። ስለዚህ እንዳልከው አንድነትን የመሠረቱት ብዙዎቹ ሰዎች ከዚህ አኩርፈው የሄዱ ናቸው። ያኔ በተለያዩ ምክንያቶች ሄደዋል፡፡ አሁን ግን ከስህተቶቻችን ተምረን አብረን ጠንክረንና ተባብረን እንሠራለን። አንድ ጊዜ ተጣልተናልና መልሰን አብረን መስራት አንችልም የሚል እምነት አይኖረንም፡፡ እየተጋጨንም ዞረን ደግሞ ስህተታችንን አምነንና ተማምነን መስራት ምንም ማለት አይደለም፡፡ ለወደፊትም አለመግባባቶች ቢኖሩ በዚህ መልኩ እየተማመኑና እየተወያዩ መሄዱ ይቀጥላል የሚል እምነት ነው ያለኝ እና ከዚህ አንፃር ቢታይ መልካም ነው፡፡

 በየጊዜው ፓርቲዎች መድረክ፣ ትብብር፣ ህብረት፣ ቅንጅት እያሉ በጋራ እየተሰባሰቡ ሲወድቁ ሲነሱ የኢትዮጵያ ህዝብ ታዝቧል፡፡ መኢአድም የዚህ ሂደት አንዱ አካል ነው፡፡ ለወደፊትስ ፓርቲያችሁ በዚህ ሁኔታ እስከየት ድረስ ነው ሊጓዝ የሚችለው?

እንግዲህ ባለፉት 22 አመታት የፓርቲዎች ስብስብ አንድ ሲሆን ሲለው ደግሞ ሲፈርስ ኖሯል፡፡ እንደ እኔ አመለካከት ይሄ የሆነው ሁሉም ነገር በግለሰቦች ፍላጐት ላይ የተመሠረተ ስለነበረ ነው፡፡ ይሄ ኢትዮጵያንም ሆነ ዜጐቿን የጐዳ ትልቁ በደል ነው፡፡ አንዳንዱ የፓርቲ አመራር ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ቆሜያለሁ ካለ፣ ራሱን ለዚያ አላማ መሸጥ አለበት፡፡ ግቡ ወይም የሩቅ አላማው ኢትዮጵያውያንን ነፃ ማውጣት ወይም በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ሠፍኖ ማየት መሆን አለበት። ግን በዚህች ሀገር እስካሁን ሲደረግ የቆየው እኔ ሊቀመንበር ካልሆንኩ፣ የኔ ፓርቲ የበላይ ካልሆነ ሲባል ነው፡፡ ከዚህ አንፃር አሁንም ቢሆን መኢአድ ሊያደርግ የሚችለው የጋራ ትግል አስፈላጊነትን ያምናል፤ ስለዚህ እስከቻለው ድረስ ከአላማው ጋር ከሚስማሙት ጋር አብሮ ይሠራል፡፡ ይህ መሆኑ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ አንደኛ ድምጽ አይሻሙም፤ በሁለተኛ ደረጃ በህዝቡ ላይ በራስ የመተማመን ስሜትን መፍጠር ይቻላል። አለኝታ የሚሆን ፓርቲ አለኝ ብሎ እንዲያምን ይገደዳል፡፡ ደካማና የተነጣጠለ ፓርቲ ሆነው ካያቸው ግን ህዝቡ እምነት ሊጥልባቸው ይቸገራል እና መኢአድ አሁንም| ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸው ድርጅቶች ጋር አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ ነው፤ ግን ይሄ የሚሆነው በቅንነት፣ በእውነተኛነት ኢትዮጵያን እያሰበ ከሚመጣ አካል ጋር ነው፡፡ ሸር ይዞ ከሚመጣ ጋር ግን ለመስራት ይቸገራል፡፡

 መኢአድ ራሱ አንዴ ሲቀናጅ፣ ሲዋሃድ፣ ሲተባበር ሲያሻው ደግሞ ቅንጅቱና ውህደቱን ሲያፈርስ የኖረ ፓርቲ ነው፤ አሁንም በዚህ አዙሪት ውስጥ መሆኑን ያዩ ወገኖች ፓርቲው ግራ የተጋባ ነው ሲሉም ይደመጣል…

ፓርቲያችን ግራ የተጋባ አይደለም፡፡ ግልጽ አላማ ግልጽ የሆነ ፕሮግራምና ደንብ ያለው ፓርቲ ነው። ፓርቲው ህብረ ብሔራዊ፣ ብዙ አባላትና ደጋፊዎች በውጭም በሀገር ውስጥም ያለው በመልካም አመራር የሚመራ ፓርቲ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን አምነው ከሚመጡ ፓርቲዎች ጋር ለመስራት መኢአድ ዝግጁ ነው፤ ነገር ግን የሚመጡትን ፓርቲዎች ለመምራት የሚሞክር ሳይሆን አብሮ የሚሰራ ነው፡፡

 በየክልሉ ያሉ ቢሮዎቻችሁ እየተዘጉባችሁ እንደሆነ ስትገልፁ ከርማችኋል፡፡ ከነዚህ ክልላዊ እና ጐሣዊ ፓርቲዎች ጋር ለመቀናጀት የወሰናችሁበት ሚስጥር ምናልባት ዳግም ለመጠናከር አስባችሁ ይሆን?

ይሄም ዝም ብሎ ግምታዊ አስተያየት ነው እንጂ ፓርቲው አሁን በየትም ቦታ ብትሄድ ቢሮ አለው ወይም መዋቅር አለው፡፡ እንደተባለው በተለያዩ ጫናዎች ምክንያት በተለይ የወረዳዎቹ ቢሮዎች ተዘግተው ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ መኢአድን ብቻ ሣይሆን ሌሎችንም ጐድቷቸዋል፡፡ ስለዚህ አሁን መኢአድ በሃገሪቱ ካሉ ፓርቲዎች ጠንካራው ነው ብል ስህተት አይደለም። በሀገር ውስጥም በውጭም ያሉ ደጋፊዎቻችን ለፓርቲው መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ ነው። እዚህ ያለው አመራርም የተዘጉ ቢሮዎችን ለማስከፈት ጥረት እያደረገ ነው። እስከ 2007 ድረስ ሙሉ ለሙሉ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ቢሮ ይኖረናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ይህን ካልኹ፣ አሁን የኢትዮጵያ ህዝብ፤ “አንድ ላይ ካልተባበራችሁ፣ ካልሠራችሁ ለትግሉ አስቸጋሪ ነው” በሚል ህብረት እንድንፈጥር እየጠየቀ ነው፡፡ ስለዚህ መኢአድ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወደ አንድ መጥቶ፣ ጠንካራ ፖለቲካ ፓርቲ ተፈጥሮ፣ መወዳደር አለባቸው እንጂ መቶ ደካማ ፓርቲዎች ዝም ብለው መጮህ የለባቸውም የሚል እምነት አለው፡፡ ከዚህ አንፃር ነው እንጂ እኛ ድክመት ኖሮብን በእነሱ ለመሸፈን አይደለም፡፡ እነሱ ብዙም ይዘው የሚመጡት ነገር የለም፡፡

 መኢአድ ከሌላው የተሻለ ሰፊ ህዝባዊ መሠረት ካለውና አደረጃጀቱም ጠንካራ ከሆነ በምርጫ ወቅት ለምን ተፎካካሪ ሊሆን አልቻለም?
ፓርቲው እየታገለ ያለው እሱ ብቻ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን ነው፡፡ እንደተባለው ፓርቲው ጠንካራ መሠረት ያለው ቢሆንም ከገዢው ፓርቲ የሚደርስበት ጫናም በዚያው ልክ የሰፋ ነው። አባላቱ ንብረታቸውን ይነጠቃሉ፣ ይታሰራሉ፣ ይደበደባሉ፤ ሰዎች የፓርቲው አባል ስለሆኑ ብቻ የተለየ ጥቃት ይደርስባቸዋል፡፡ እንደነዚህ አይነት ተጽእኖዎች ደግሞ ሊያራምዱ አይችሉም፡፡ በሌላ መንገድ ገዥው ፓርቲ የራሱን የደህንነት አባላት እና ካድሬዎች በየፓርቲዎቹ ውስጥ ሰግስጐ ያስገባል፡፡ በዚህም በፓርቲ ውስጥ መናወጥ ይፈጥርና የፓርቲውን አመራር ያዳክማል፡፡ ይሄ በማዕከል ብቻ ሳይሆን በዞንና በወረዳም ጭምር የሚደረግ ነው፡፡ እንደነዚህ አይነት ተጽእኖዎች ናቸው ከፍተኛ ችግር የፈጠሩት፡፡ ህዝቡም መወጣት ያለበትን ሃላፊነት መወጣት አለበት፡፡ እውነተኛውንና ውሸታሙን መለየት መቻል አለበት፤ ዳር ሆኖ መመልከቱ አይጠቅምም፡፡

 ተቃዋሚዎች ለመዳከማቸው ገዢውን ፓርቲ ተጠያቂ ያደርጋሉ፤ ገዥው ፓርቲ ደግሞ ጠንካራ ተቃዋሚዎች ባለመኖራቸው ሸክሜ በዝቷል እያለ ነው…

እዚህ ላይ ሁለት ነገር ነው የሚታየኝ፡፡ አንደኛ አቶ መለስም በህይወት በነበሩ ጊዜ የተናገሩት ነው፡፡ ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ ቢመጣ ሩቅ መንገድ ሄደን እንቀበለዋለን ተብሎ ነበር፡፡ ነገር ግን ቅንጅት ተፈጥሮ ጠንካራ ፓርቲ ሲመጣ በጥይት ግንባሩን ነው ያሉት። ይሄ አባባል እንግዲህ ፖለቲከኞቻችን ለይስሙላ የሚጠቀሙት መሆኑን አረጋጋጭ ነው፡፡ “እንዳይበላ ግፋው እንዳያማህ ጥራው” አይነት ነገር ነው፡፡ አሁንም አቶ ኃይለማርያም የተናገሩትን ሰምቸዋለሁ “ሌሎቹ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሃላፊነትን መሸከም ስላልቻሉ የሃገሪቱ ሸክም ሁሉ ኢህአዴግ ላይ ወድቋል።
ተበራቱ” የሚል ነው፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ኢህአዴግ ምንም አይነት ሃላፊነት ሊሸከም የሚችል ፓርቲ ነው ብዬ አላምንም፡፡ ለምን? የኢትዮጵያን ህዝብ ሰብአዊ መብት እየጣሰ ያለ ፓርቲ፣ ሃላፊነት እሸከማለሁ ቢል አይታመንም፡፡

 በሁለተኛ ደረጃ የኢትዮጵያን ህዝብ አዎንታ የተቀበለ ፓርቲ አይደለም፡፡ በሃይል፣ በመሳሪያ ስልጣን የያዘ ፓርቲ ነው፡፡ እኔ የማዝነው አቶ ኃይለ ማርያም በጣም ክርስቲያን ናቸው ይባላል፤ ግን በእዚህ አይነት ጉዳይ ላይ የሚናገሩት ነገር ከእምነታቸው ይቃረንብኛል፡፡ እነሱ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ያቁሙና ከዚያ በኋላ ጠንካራ ተቃዋሚ ካጡ ይሄን ነገር ሊናገሩ ይችላሉ፡፡

 መኢአድን ጨምሮ ብዙዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በግለሰብ አውራዎች ላይ የተመሠረቱ ሆነው ይታያሉ። ከፕሮግራምና አላማቸው ይልቅ ፕሬዚዳንቶቻቸው ጐልተው ይወጣሉ፡፡ የሚሆነው ለምን ይመስልዎታል?

በእርግጥ ይሄ ነገር መሆን የሌለበት ነው፡፡ አመራር ብቻ አይደለም፤ አባላትም በሁሉም ነገር ላይ ተሣትፎአቸው መጠየቅ አለበት፡፡ የእነሱ ተሣትፎ ከሌለበት የኔ ነው የሚሉት ነገር ሊኖር አይችልም። በመጀመሪያ ደረጃ አባላቱ የኔ ነው ሊሉ የሚችሉት ፓርቲው አሣታፊ ሲሆን ነው፤ ስለዚህ እንደነዚህ አይነት ነገሮች በቀጣይ ሊታረሙ የሚገቡ ናቸው፡፡ አመራሩና አባላቱ የውስጥ እኩል ተሣትፎ ሊኖራቸው ይገባል። አንድ ሰው አንድ ፓርቲ ሊሆን አይገባም። የእከሌ ፓርቲ ሊባል አይገባም፡፡ መኢአድ ያንን ለማድረግ እየሰራ ነው፡፡ በአደረጃጀቱም ትልቁን ስልጣን የሚሰጠው ከታች ላለው ነው፡፡ የፓርቲ አመራሮች ራሳቸውን ለአባላቱ ተገዢ ካላደረጉ፣ ነገ ለሚመሩት የኢትዮጵያ ህዝብ ተገዢ ሊሆኑ አይችሉም።

 የ2007 ምርጫ እየተቃረበ ነው፡፡ መኢአድ ከምርጫው ምንድን ነው የሚጠብቀው?
እኛ ስራችንን እየሰራን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ አዎንታውን ከሰጠን ስልጣን ለመያዝ ከመጓዝ የሚያግደን ነገር የለም፣ ነገር ግን የመጫወቻ ሜዳው በትክክለኛው መንገድ ካልሄደ የኢትዮጵያን ህዝብ ልናማው አንችልም፡፡

 እኛንም ህዝቡ ሊያማን አይገባም፤ ማማት ያለበት ገዢውን ፓርቲ ነው፡፡ በጥይት በዱላ እየደበደበ አባላቶች እንዳይሳተፉ የሚያደርግ ከሆነ፣ በምርጫ ወቅት ካርድ እየሰረዘ አሽነፍኩ የሚል ከሆነ፣ በምርጫ ወቅት ታዛቢዎቻችንን እየደበደበ፣ በመድሃኒት እያሠከረ እያስተኛ የሚዘርፍ ከሆነ መታማት ያለበት ገዢው ፓርቲ ነው፡፡ መኢአድ በ2007፤ መቶ በመቶ አሸንፋለሁ ብሎ እየተራመደ ነው ያለው፤ ይሄን ደግሞ እርግጠኞች ነን። ለምን ካልን አሁን የኢትዮጵያ ህዝብ ለውጥ ፈልጓል፤ ግን ለውጡን የሚሸከምለት ፓርቲ ይፈልጋል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ዛሬ በብዙ መልኩ መብቱ ተጥሷል። የሃገሪቱን የኢኮኖሚ ትሩፋት መጠቀም ተስኖታል፡፡ የቀን ሠራተኛው፣ ብሎኬት ሠራተኛው፣ ዶሮ አርቢው ሣይቀር ከውጭ እየመጣ ነው፡፡ የሀገሪቱ ዜጋ መጠቀም አልቻለም፡፡

Saturday, November 23, 2013

የመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች በአዛዦቻቸው ላይ ውጥረት ፈጥረውል::

November 23/2013
ጄኔራል አበባው ታደሰን እና የብኣዴን መኮንኖችን ያገለለ ስብሰባ መካሄዱ ጥያቄ አስነስቷል::



በወያኔ የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ውጥረት መፈተሩን ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ተሰምቷል:: በወታደራዊ ጥቅማ ጥቅም እና በህገመንግሥቱ ዙሪአ ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ አካል መጥፋቱ እና ዝም መባሉ ዉስጥ ውስጡን እየተብላላ ያለው የመኮንኖቹ ጥያቄ እንዳይፈነዳ የተሰጋ ሲሆን ከፈነዳ ሰራዊት ለሶስት ቦታ እንደሚከፈል ለምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

መኮንኖቹ በትምህርት በስራ እና በማእረግ እድገት በቤተሰብ እንክብካቤ በደሞዝ ጭማሪ እና በሕገመንግስታዊ የህዝብ መብቶች ዙሪያ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ወታደራዊ ጥቅማ ጥቅሞች ለአንድ ብሄር አባላት ብቻ ተመድበው እየተሰራባቸው ነው ከተማ ውስጥ ታጥቀው የመሸጉ እና ህዝብን እያጠቁ የሚገኙት የአንድ ብሄር አባላት ናቸው እንዱሁም ከሃገራዊ ጥቅም ይልቅ የፓርቲ ጥቅም እየተስተዋለ ነው:ወታደሩ የጦር ሳይንስን እና ዲሲፕሊን በጎደለው መልኩ እየተስተዳደረ ነው በሰራዊቱ እና በሃገሪቱ ሁሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን ሽፋን እና ማዘናጊያ በማድረግ የሙስና እና የዘረፋ መስፋፋት መልስ ሊያገኝ ይገባዋል ጄኔራል መኮንኖች አላቸው የተባለው ንብረት ይጣራ በሃገሪቱ የፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች ሊመለሱ ይገባል የሚሉ እና ተመሳሳይነት ያላቸውን ጥያቄዎች ማንሳታቸው ታውቋል::የመከላከያ አባላቱ በኑሮ ውድነት እና በተቃዋሚዎች ህገመንግስታዊ መብቶች ላይ ያነሱት ጥያቄ አዛዦቹን ያስደነገጠ ከመሆኑም በላይ በአንድ ብሄር ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እስከመቼ የሚለውም ጥያቄ መመለስ አለበት በሚል የእግር እሳት እየሆነባቸው ነው::

ይህ ከዚህ ቀደም የተጀመረው እና አሁንም በሰሜን እዝ እና በምስራቅ እዝ የተከሰተው የሰራዊቱ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እና የጥቅማ ጥቅም አቤቱታ በመላው ሃገሪቱ ተስፋፍቶ በሁሉም የሰራዊት እዞች ውስጥ ጥያቄው መነሳቱን ምንጮቹ አመልክተዋል::በተለያዩ ጊዜያት እየተንከባለለ የመጣው ይህ የሰራዊቱ አቤቱታ እጅግ አደገኛ አዝማሚያ እያሳየ ሲሆን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እንዲወገድ እና ህገመንግስታዊ መብቶች እንዲከበሩ ጥያቄዎች ገፍተው መምጣታቸው ሲታወቅ ከፍተኛ የሕወሓት ጄኔራሎች በየቀኑ ካለማቋረጥ ምስጢራዊ ስብሰባዎችን እያደረጉ ከመሆኑም በላይ ከየእዙ የሚመጣላቸው ሪፖርት መፍታት የሚቻልበትን ጉዳይ እየተወያየ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጮቹ ገልጸው ነበር::

ሌ/ጄ ሳሞራ የኑስ ጡረታ ወቶ በምትኩ የብኣዴን ሜ/ጄ አበባው ይተካሉ ሲባል ወያኔ በድንገት የመለስ የቅርብ ሰው የነበሩትን እና በአንድ ወቅት የአማር ክልል አቶ አያሌው ጎበዜን ላንቻ አከባቢ በመኖሪያ ቤታቸው ለ3 ወር አግተው ሲያሰቃዩ የነበሩት ሌ/ጄ ዮሃንስ ገብረመስቀልን በማእረግ ሾሞ ሳሞራ የኑስን ለመተካት የሚያደርገውን ሩጫ የብኣዴን አባላት መቃወማቸውን ተከትሎ ጄኔራል አባባውን ጨምሮ የብኣዴን መኮንኖችን ያገለለ የሕወሃት አባላት የሆኑ ጄኔራሎች ብቻ የተሳተፉበት በትግሪኛ የተመራ ስብሰባ መደረጉን ውስጥ አዋቂ ምንጮቹ ተናግረዋል::በስብሰባው ላይ ቀሪ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች እና የመምሪያ ሃላፊዎች ለምን አልተሳተፉም የሚል ጥያቄ ከአንድ ስማቸው ካልተጠቀሰ ብርጋዴር ጄኔራል መነሳቱን ምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ይህ ስብሰባ ዋና አትኩሮቱ የነበረው በብሄር አደና ላይ ሲሆን እንደ ምንጮቹ መረጃ በአማራ እና በኦሮሞ መኮንኖች እየተመራ ያለውን የለውጥ ጥያቄ በማክሸፉ ዙሪያ እንደነበር እና አሁንም በስፋት የሕወሓትን የፓርቲ አቋም የሚቀበሉ እና የጥቅም ተጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለመሾም የታቀደ ሲሆን እንዲሁም ከፖለስ ሰራዊት በከፍተኛ የማእረግ ሹመት ወደ ጦር ሰራዊቱ ለማምጣት የታሰበ ሲሆን በወታደራዊ ደህንነት ዙሪያ ሌላ ተጨማሪ ሰልጣኞችን ከፖሊስ ወስዶ በማሰልጠን ወደ ሰራዊት ማዘዋወር የሚሉ ውይይቶች ተካሂደውበታል:: አሁንም ስብሰባው የቀጠለ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን እንለቃለን::


ምንሊክ ሳልሳዊ :

ወቅታዊ ችግሮቻችን የራሳችን መንግሥት ባለቤቶች እንድንሆን ይበልጥ ሊያበረቱን ይገባል!

November 22/2013
በወያኔ አረመኔያዊ አገዛዝ ሳቢያ ከሀገራቸውና ከትውልድ ቀያቸው ተፈናቅለው በዐረቡ ዓለም በተለይም በሳዑዲ ዐረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ ሰሞኑን እየደረሰ የሚገኘውን ዘግናኝ ሰቆቃና ግድያ በመሪር ስሜትና በንቃት እየተከታልን ነው። አበው “ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳው አይቀበለውም” እንዲሉ እነዚህ ወገኖቻችን በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ‹የሀገራቸው መንግሥት ነው› የሚባልለት የወያኔው መንግሥት እንኳንስ በባዕድ ሀገር በሚገዛው ሀገርም ውስጥ የሚያካሂደውን የመብት ገፈፋና ሕዝቤ በሚለው ዜጋ ላይ በዘር እየከፋፈለ የሚያራምደውን የግፍ አገዛዝ ዐረቦቹም ሆኑ ቀሪው ዓለም ያውቁታል። በመሆኑም ለነዚህ ምሥኪን ዜጎች የሚጮኽላቸውም ሆነ ለመብታቸው መከበር የሚቆረቆርላቸው አንድም መንግሥታዊ አካል እንደሌለ ከበፊት የተገነዘቡት እውነታ ነው። በወገኖቻችን ላይ ይህን ሁሉ ሰማይና ምድር የማይችሉት የግፍ ቁልል እነዚህ የዐረብ መንግሥታት የፀጥታ ኃይሎች ሲከምሩባቸው ማንም ዝምባቸውን እሽ የሚል ወይም ጠንከር ባሉ ቃላት እንኳን ተቃውሞ የሚያቀርብ አካል እንደማይር ያውቃሉ። ለዚህም ነው ታላላቅ የሚዲያ አውታሮች ሳይቀሩ ሀገሪቷንና ሕዝን በመናቅ በዝምታቸው መግፋትን የወደዱት። ይህ ነገር ከሃይማኖትም ይሁን ከቀለም፣ ከዘርና ከፖለቲካዊ እሳቤዎች አኳያ የሰው ልጅ ተፈጥሮን ባሕርይና የሀገራትንና የመንግሥታትን ተጻራሪ ድርብ አቋሞችን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።
 “ሰው ለሰው የሚጨነቀው፣ ምን ዓይነት ሰው ሲጎዳ ወይም ምን ዓይነት ሕዝብና የትኛው ሀገር ችግር ላይ ሲወድቅ/ሲወድቁ ይሆን?” በሚል ከፍተኛ ፍልስፍና ውስጥ የሚያስባ ልዩ አጋጣሚ ፈጥሯል። በእውኑ ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ሕዝብ በበለፀጉ ሀገሮች የአንድ ንጉሥ-ንግሥት ንብረት ከሆነች ውሻ ያንሳሉን? ንግሥት ኤልሣቤጥ የሚወዷት የቤት ድመት ወይም የንጉሥ አብደላ የቤተ መንግሥት ውሻ ቢሞቱ ሲኤንኤንንና ቢቢሲን የመሳሰሉ ላለው የሚያሽቃብጡ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት የመክፈቻ ዜናቸው እንደሚያደርጓቸው አይጠረጠርም። ወትሮም ብሂሉ “ላለው ይጨመርለታል” ነውና። እንደዚህ ያለው አካሄድ በውነቱ ቅስምን የሚሰብርና ከ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሰለጠነ የሚባል ማኅበረሰብ የሚጠበቅ አልነበረም።
በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ እየተደረገ ያለው ሰቅጣጭ የሕይወት ገጠመኝ በሌሎች ሀገራት ሕዝቦች ላይ ቢደረግ ኖሮ በአሁኑ ወቅት ዓለማችን ከዳር እዳር በተቃወሰች ነበር። በዚህ ዘመን እንደኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የተዋረደ የለም፤ ለዚህ ያበቃንም ይበልጡን በየምንሄድባቸው አካባቢዎች ያሉ መንግሥታት ብቻ ሳይሆኑ እቤታችን ያለው እሾህ፣ እዚያው ኢትዮጵያችን ውስጥ በአራት ከሎ ቤተ መንግሥት የመሸገውና በመላዋ ሀገራችን እንደመዥገር የተጣበቀው ወያኔ ነው። ስለዚህ ዋናው ጠላታችን ቤታችን ውስጥ ሁሉንም ነገር ተቆጣጥሮ ለመከራና እንግልት የዳረገን ወያኔ እንጂ ከዚህ ክፉ አውሬ የጭራቆች ቡድን ቀድሞ በኃላፊነት የሚጠየቅ ሊኖር አይገባም። እርግጥ ነው – በችግራቸው ጊዜ በጥሩ እንግዳ ተቀባይነት ከደረስንላቸው ወገኖች ይህን መሰል ግፍና ስቃይ ማየትና መስማት ዕንቆቅልሽ መሆኑ አይቀርም።
የአንድ ሀገር ዜጎች በተለያዩ ምክንያቶች በፍቅርም ይሁን በጠብ፣ በሥራና ለሥራም ይሁን በስደትና በጦር ምርኮኝነት ከሀገራቸው ወጥተው በሌሎች ግዛቶች የሚገኙበት ሁኔታ በተለይ በዚህ ዘመን በስፋት ይስተዋላል። በዚህን ጊዜ ባሉን ዓለም አቀፍ ሕግጋት መሠረት የዜጎች እንቅስቀሰሴና ዝውውር የዲፕሎማሲን መስመር በጠበቀ ሁኔታ ይከናወናል እንጂ እንዲህ እንደሰሞኑ አንዱ በሌላው ላይ ኢሰብኣዊ ድርጊትን አይፈጽምም። “በዚህን ጊዜ ውስጥ ሀገራችንን ለቃችሁ ውጡ፤ ካልወጣችሁ እንዲህና እንዲህ የመሰለ ችግር ይደርስባችኋል” ተብሎ ማሰጠንቀቂያ ይሰጣል እንጂ ድንገት ከመሬት ተነስቶ የሌሎች ሀገራት ዜጎችን ላልተጠበቀ ኢሰብኣዊ ድርጊት ማጋለጥ ሰብኣዊም ሃይማኖታዊም መደላድል የሌለው ዐይን ያወጣ ወንጀል ነው።
የአሁኑን የኢትዮጵያ መንግሥት ተብዬውን ዓይነት ሳይሆን ሁነኛ የሕዝብ አገልጋይ መንግሥታት ባሉባቸው ሀገራት ውስጥ ብዙ አስገራሚ ግን ተገቢና የሚጠበቅ መንግሥታዊ ፈጥኖ ደራሽነትንና ከአደጋ ታዳጊነትን ማየታችን በጣም የተለመደ ነው። ብዙ አብነቶችን መጥቀስ ቢቻልም የቅርብ ጊዜውን የሻሊትን ጉዳይ ብቻ ማውሳት በቂ ነው።
ሻሊት እሥራኤላዊ ወጣት ወታደር ነበር። ቀደም ሲል በሀገራዊ ግዳጅ ላይ እያለ በፍልስጥኤማውያን ይያዝና ሥውር ቦታ ይታሰራል። በሁለቱ ወገኖች መካከል ብዙ ጊዜ የወሰደ ድርድር ይካሄዳል። የአንድ ዜጋ ጉዳይ መላ እሥራኤላውያንን ማወዛገቡን ይቀጥላል። በመጨረሻም ከአንድ ሺህ በላይ እሥረኛ በአንድ ሻሊት አስፈትተው ፍልስጥኤሞች ይህን ወጣት ወታደር ይለቁታል። ለሀገርና ለሕዝብ ተቆርቋሪ መንግሥት ማለት እንደዚህ ነው። እሥራኤል ሕይወት ያለውን ዜጋዋን ብቻም ሣይሆን ለአንድ በጦርነት ለተሰዋና በጠላት ቁጥጥር ሥር የሚገኝ በድን ዜጋዋ ሕይወት ባላቸው በርካታ ምርኮኞች የምትለውጥ ለዜጎቿ ስሱ የሆነች ሀገር መሆንዋን ከበፊትም የምናውቀው ነው። በዘመናችን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በማድረግ ለዜጎች መብት መከበር ከመታገል አንጻር ሣይሆን በየትም ሥፍራ የሚኖሩ ዜጎች ለሀገር ውርደትና ለአጠቃላዩ የሕዝቡ ኅልውና ማክተም ሌት ከቀን ተግቶ በመሥራት አኳያ ከወያኔ መንግሥት ሌላ በዓለም ሌላ ሀገር ሊኖር እንደማይችል በልበ ሙሉነት መወራረድ ይቻላል። እኛ ላይ እሳት ነው የጣለብን።
“ጽድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ” እንዲሉ እኛ ኢትዮጵያውያን እንደእሥራኤል ያለ ለዜጋው እንስፍስፍ መንግሥት ማግኘቱ ቀርቶብን በዚህን ዓይነት አደጋ የበዛበት ወቅት የዜጎቹ ደኅንነት ካልተጠበ የዲፕሎማሲና የንግድ ግንኙነቶቹን እንደሚያቋርጥ ለማስመሰልም ቢሆን በማስፈራራት ለጨፍጫፊው መንግሥትና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት አቤት የሚል መንግሥት ቢኖረን ምንኛ በታደልን ነበር። ወያኔ ግን ተፈጥሮው እንደነዛው እንደጨፍጫፊዎቹ በመሆኑ እዚህ ግባ የሚባል ውኃ የማያነሣ ሰበብ በመስጠት ዜጎች እየተጨፈጨፉ ባሉበት ሁኔታ ሚዲያዎቹ ሁሉ በአሸሸገዳሜ ዘፈን ተሞልተው በሀገር ሰላም የተለመደ የማደንቆሪያ ልማታዊ ተብዬ ፕሮፓጋንዳውን በስፋት ቀጥሎበት ይታያል። ይህም በጣም ያሳዝናል።
ወያኔ ራሱ ህጋዊ መንግሥት የሆነ ይመስል ከሀገር የሚሰደዱ ዜጎችን ከህግ መስመር ውጪ ነው የወጡትና አያገባኝም በሚል ማደናገሪያ ከመንግሥታዊ ኃላፊነቱ እየሸሸ ነው። በመሠረቱ ቀድሞ መምጣት ያለበት ዜግነት እንጂ ሕግ አይደለም። ሰው የሠራው ሕግ በተፈጥሮ ከተገኝ ሰው መቅደም የለበትም። እንኳንስ ለዜጎቹ ምንም ነገር ካላሟላ ጨቋኝ መንግሥት ይቅርና ሁሉም ነገር ከተመቻቸላቸው ያደጉ ሀገሮችም ሳይቀር ከመንግሥታቸው በመቃረን ጭምር ሰዎች በተለያዬ ምክንያት ከሀገራቸው ይወጣሉ። ለምሳሌ ስኖውደን የተባለው አሜሪካዊ በቅርቡ ከሀገሩ ሸፍቶ በራሽያ ውስጥ ይገኛል። በዚህ ሰው ላይ ማንም አካል ተነስቶ ኢሰብኣዊ ድርጊት ቢፈጽምበት የአሜሪካ መንግሥት ራሱ እንደተዋረደ ይቆጥሩታልና ያ ስኖውደንን የሚያንገላታ አካል የዚህችን ልዕለ ኃያል የሆነች ሀገር ጡንቻ ይቀምሳል እንጂ “ከእኛ ጋር ተጣልቶና አስቀይሞን ስለወጣ እንኳን የእጁን አገኘ!” ከሚል የመሠሪዎች ቂም በቀለኝነት በመነሣት አሜሪካውያኑ እጃቸውን አጣጥፈው አይቀመጡም። ወያኔ ግን ተፈጥሮው በቂምና በበቀል የታጀለ በመሆኑ የሣዑዲን መንግሥት እንዲያውም በባለውለታነት እስካሁን ከሰጣቸው ሰፋፊ እርሻዎች በተጨማሪ ሌላ ትላልቅ መሬቶችን በሽልማት ሳይሰጣቸው አይቀርም። ይህ መንግሥት በሀገር ውስጥም በሰው ግዛትም እየገባ ዜጎቹን የሚጨፈጭፍ በመሆኑ ለዜጎች የሚቆረቆር ተፈጥሮ በጭራሽ የለውም። መባጽዮን ጃተኒን በሰላም በተቀመጠበት ኬንያ ውስጥ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮቹን አሰማርቶ ያሰገደለ ወያኔ ለዜጎች ይቆረቆራል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ሰሞኑንም የግንቦት ሰባትን ሕዝባዊ ኃይል አመራር ለማስገደል እበላ ባይ ወንጀለኞችን አስርጎ ከፍተኛ የነፍስ ማጥፋት ወንጀል ሙከራ ያደረገ የባለጌዎች መንግሥት ራሱ ገፍቶ ያወጣቸውን ዜጎች ደኅንነት ለማስጠበቅ ከወዳጆቹና ከዓላማው አራማጆች የዐረብ መንግሥታት ጋር ይቀያየማል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው። ለሕዝብና ለሀገር ውርደትና አጠቃላይ የሞራልም ሆነ የማኅበራዊ ዕሤቶች ውድቀት የቆመን አካል ደግ ነገር እንዲያደርግ መጠበቅ የወያኔን ሥረ መሠረትና የተፈጥሮ ባሕርይ በቅጡ አለመገንዘብ ነው። መፍትሔው ግን በያንዳንዳችን እጅ ውስጥ ነው።
እንደግንቦት ሰባት ያለው አማራጭ አንድና አንድ ብቻ ነው። ይሄውም ይህን የዜገች ፀር የሆነ የወንበዴ መንግሥት በሁሉም ሥልቶች ተረባርቦ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ ነው። ይህ ሲሆን ነው ዜጎቻችን በሚሄዱበት ቦታ ሁሉ አንገታቸውን ቀና አድርገው እንዲሄዱ የሚያስችላቸውን የኔ ነው የሚሉት ሕዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መንግሥት ማቆም የሚቻለው። ያኔ ነው ኢትዮጵያ ከተቀበረችበት ተነስታ በዜጎቿ የጋራ ምክክርና ስምምነት በአዲስ ጠንካራ መሠረት ላይ የሚገነባ ሁሉንም እኩል የሚያይ፤ ለሁሉም እኩል መኩሪያ የሚሆን መንግሥት ሊመሠረት የሚችለው። ያኔ ነው የሀገራችንን የሰውና የተፈጥሮ ሀብት ለሀገራችን በማዋል ድህነትንና ስደትን በተባበረ ክንዳችን የምንገታው። ያኔ ነው ሀብታችን በግለሰቦች እየተመዘበረ ለጥቂቶች መንደላቀቂያ መሆኑ የሚቀረውና ለሕዝቡና ለሀገሪቱ ዕድገት የሚውለው። ያኔ ነው በዓለም የተበተነው የተማረ የሰው ኃይላችንና በብዙ ዕውቀትና የሕይወት ልምድ የዳበረው ዜጋችን ወደ ሀገሩ መጥቶ ሀገር ቤት ካለው ኃይል ጋር በመተባበር ኢትዮጵያችንን ከገባችበት አረንቋ የሚያወጣትና ትንሣኤዋም በአዲስ መልክ የሚታወጀው። ለዚህ ሁሉ ተጨባጭ ምኞት እውንነት ደግሞ ሁላችን እጅ ለእጅ ተያይዘን ይህን የበሰበሰና የፈራረሰ ግን በቅርጹ ሲታይ ሕይወት ያለው የሚመስል የወሮበሎች መንግሥት በጋራ ትግል ከነሰንኮፉ ፈንቅለን ልንጥለው ይገባል። ዋናው የችግራችን ሁሉ መባቀያ አዲስ አበባ ላይ ቁጭ ብሎ መንስኤውን ትተን በውጤቶች ላይ ብቻ ማዘኑና መቆዘሙ እንዲሁም ባልተቋረጠ የሀዘን ድባብ ውስጥ ተቀምጦ ማንባቱ ዋጋ የለውም። የኛን ሥራ ወደጎን ትተን ወያኔ በሚፈጥራቸው አፍራሽ ተግባራትና ውጤታቸው ዝንትዓለሙን ማላዘኑ የነሱን ዕድሜ ከማራዘም ውጪ ለኛ የሚተርፍ አወንታዊ ፋይዳ የለውም። ከተባበርን የዚህ መንግሥት ዕድሜ ከሣምንታት አይረዝምም፤ ካልተባበርንና አንዳችን የአንዳችንን ጉድጓድ በመቆፈር ተግባር ከተጠመድን ወያኔ በጀመረው መንገድ ቀጥሎ ሀገራችን በለዬለት ሁኔታ ከዓለም ካርታ እንድትሰረዝ ፈቃደኞች ሆነናል ማለት ነው። ምርጫው የኛው ነው።
በመጨረሻም በሰሞኑ የወገኖቻችን ዕልቂት ምክንያት በቀጥታም ይሁን በተዛዋሪ የወያኔው ግፈኛ አገዛዝ ሰለባ የሆኑ ወገኖቻችንን ነፍስ ይማር እንላለን፤ ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ውርደቱና ታሪካዊ አንድምታው አሉታዊ ጥላውን ለሚያሳርፍበት ለመላው ሕዝባችንም መጽናናትን እንመኛለን።