Friday, August 23, 2013

ከአዲስ አበባ ወደ ወልዲያ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ተገልብጦ በርካታ ሰዎች ሞቱ

ነሃሴ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአዲስ አበባ ወደ ወልድያ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ አውቶቡስ ደሴ አካባቢ ሲደርስ በመገልበጡ የ21 ሰዎች ህይወት ጠፋ፣ የዛሬውን ጨምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 66 ደርሶአል።
የአደጋው  መንስኤ ጥራት የሌለው የአስፓልት መንገድ በጎርፍ በመቆረጡ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የወልድያ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ለኢሳት እንደገለጸው ደግሞ የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ ባሙያዎች ከደሴ በመላካቸው መረጃው ተጣርቶ እስከሚቀርብ ድረስ አስተያየት ለመስጠት አይቻልም ብሎአል።
ይህን ዜና እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ሾፌሩን ጨምሮ የ3 ሰዎች አስከሬን በጎርፍ በመወሰዱ ለማግኘት አልተቻለም። የተወሰኑ አስከሬኖች ወደ ቀወጃ፣ ቆቦ፣ ወልድያና ሳንቃ ተልከው የቀብር ስነስርአታቸው ተፈጽሟል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአካባቢው የሚጥለው ዝናም የአስፓልት መንገዶችን እየጎመደ ጉዳት ማድረሱን  ነዋሪዎች ይናገራሉ። መንገዶቹ የውሀ ፍሳሽ የሌላቸው በመሆኑ በቀላሉ ለአደጋ እንደሚዳረጉ እነዚሁ ነዋሪዎች ይገልጻሉ።
ከሁለት ቀናት በፊት በአምባሰል ወረዳ አንድ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በጎርፍ በመወሰዷ የ15 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወቃል። በጉዳዩ ዙሪያ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣንን ባለስልጣናት ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

በአንዋር መስጂድ ፖሊስ ሙስሊም ሴቶች ላይ ከፍተኛ ድብደባ ፈጸመ! ጁምአ

August 23, 2013
ድምፃችን ይሰማ

ጭንቅላታቸው የተፈነከተና ደም ይፈሳቸው የነበሩ ሴቶች ታይተዋል!

Ethiopian Musilms
ጥቂት የማይባሉ እናቶችና እህቶች ሰላታቸውን ሳይሰግዱ ወደ ቤታቸው ለመመለስ ተገደዋል!
ዛሬ የጅምአን ሰላት ለመስገድ በተገኙ እናቶች ላይ ፖሊስ ድብደባ መፈጸሙ ታወቀ፡፡ በመርካቶ አንዋር መስጂድ የዛሬውን የጁምአ ሰላት ለመፈጸም የተገኙ በርካታ እናቶችና እህቶች በፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድብደባ ተፈጸመባቸው፡፡ እነዚሁ ለጸሎት የተሰባሰቡ እናቶች ድብደባ የተፈጸመባቸው ከመስጂዱ ግቢ ውጪ አንጥፋችሁ መስገድ አትችሉም በሚል ነው፡፡

ታላቁ አንዋር መስጂድና ሌሎችም መስጂዶች በጁምአ እለት የሚመጣውን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ማስተናገድ ስለሚሳናቸውና ስለሚሞሉ ህብረተሰቡ ውጪ አንጥፎ መስገዱ ባለፉት 15 ዓመታት የተለመደና የሚታወቅ ሀቅ ቢሆንም በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ ብሄራዊ ጭቆናን እያሰፈነ ያለው መንግስት ሙስሊሞችን በሁሉም አቅጣጫ ለማጥቃት በማለም የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር በተለይም ሴቶች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ቀጥሎበታል፡፡

በዛሬው ድብደባ ጭንቅላታቸው የተፈነከተና ደም ይፈሳቸው የነበሩ ሴቶች እንደነበሩ የታወቀ ሲሆን ጥቂት የማይባሉ እናቶችና እህቶች ሰላታቸውን ሳይሰግዱ ወደ ቤታቸው ለመመለስ ተገደዋል፡፡ መንግስት የሃይማኖት አክራሪነትን እታገላለሁ በሚል ስም በሙስሊሙ ላይ ብሔራዊ ጭቆና በማስፈን ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ ጭቆና ዒላዎችም ልክ ዛሬ እንደታየው አረጋውያን እናቶችና እህቶች ሆነዋል፡፡

የእምነት ነጻነትን አክብሪያለሁ እያለ ደጋግሞ በሚዲያ የሚናገረው መንግስት በሕገ መንግስቱ የተቀመጡትን የእምነት ነጻነት መብቶች በመጣስ ሙስሊሙ ላይ ከፍተኛ በደል በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡ ሙስሊሙ ህብረተሰብ የራሱ የእምት ተቋም እንዳይኖረው ከማድረግ አንስቶ አዲስ እምነት በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ በኃይል መጫን፣ የሙስሊሙን ማህበረሰብ መሪዎች ማሰርና ማሰቃየት፣ የመብት ጥያቄ ያነሱ ሰላማዊና ያልታጠቁ ዜጎችን መግደል፣ መስጂዶችን ማሸግ፣ ኢማሞችን ያለ ሕዝቡ ፍላጎት ከስራቸው ማፈናቀልና በራሱ ፍላጎት መንግስታዊ ኢማሞችን መተካት እና ሌሎችም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሊፈጸሙ የማይችሉ ተግባራትን መንግስት ያለ ምንም ሀፍረት ሲፈጽም ቆይቷል፡፡

አሁን ደግሞ በክልሎች ሲካሄድ እንደነበረው ሁሉ ሙስሊሙን ሕብረተሰብ ከሰላት ለማቀብና ለማሸማቀቅ ለመስገድ ወደ መስጂድ የሄዱ ሙስሊሞችን ለጸሎት በተቀመጡበት ድብደባ ሲፈጸምባቸው እየተመለከትን ነው፡፡ የዚህ አይነቱ ተግባር በኢትዮጵያ ታሪክ ቢያንስ ባለፉት 90 ዓመታት እንኳ ያልታየ ድርጊት የእምነት ነጻነት በሕገ መንግስት ደረጃ በተደነገበት በዚህ ወቅት እየተፈጸመ መሆኑ ሙስሊሙ ህብረተሰብ የመንግስትን አላማና ግብ በአንክሮ አንዲያጤነው የሚጋብዝ ነው፡፡ ባለፈው ዓመት በደሴ ሸዋ በር መስጂድ መስጂድ የሞላባቸው የከተማው ሙስሊሞች ውጪ አንጥፋችሁ ሰግዳቹሀል በሚል ፖሊስ ከፍተኛ ጥቃት ሰንዝሮ በርካቶችን ለእስርና አሰቃቂ ድብዳባ መዳረጉ ይታወሳል፡፡

መንግስት መሰል ሁኔታዎችን ኹከት ለመፍጠር የሚጠቀምባቸው በመሆኑ ሁኔታዎችን በትእግስት ከማሳለፍ በዘለለ ድርጊቱ ሲፈጸም ፎቶ ግራፍና ቪዲዮ ማንሳት ሊዘነጋ የማይገባ ተግባር መሆኑን ማስታወስ ያሻል፡፡

Top UDJP Official Nebiyou Bazezew in critical condition after assault

August 23, 2013
The Horn Times Newsletter August 22, 2013
by Getahune Berkeley-South Africa


UDJP tour bus mobbed by its diehard supporters in Fiche. (Pic minilik Salsawi)

UDJP tour bus mobbed by its diehard supporters in Fiche. (Pic minilik Salsawi)
Drunk with ethnocentric tyranny, the Ethiopian ruling minority junta under the leadership of Prime Minister Hailemariam Desalegn is continuing its crack down on opposition groups with devastating cruelty and mercilessness.

Currently, the inept and abusive regime and its cadres are focusing on the opposition party UDJP’s nationwide campaign for change under the banner of “millions of voices for change.”

According to Finotenetsanet weekly Amharic tabloid, as part of the naked assault on freedom of association, UDJP Addis Ababa zone executive committee member Nebiyou Bazezew Wubalem, 42, and colleague Messay Teke were severely assaulted and robbed by more than sixteen TPLF cadres in the town of Fiche; about 45 km north of the capital while on campaign to mobilize the local youth for Saturday 25 August 2013 peaceful march.

The incident took place yesterday 21 August 2013 at 9pm local time.
The injured duo have arrived in Addis Ababa this morning, 22 August for further medical attention and UDJP acted swiftly and decisively by sending another strong team to the town of Fiche.
The town’s deputy security chief, Haileeyesus Beyene, spearheaded yesterday’s well-coordinated attack and robbery on UDJP members.

“Nebioyu Bazezew Woubalem became a target before even going to the town of Fiche after his recent interview with you guys (the free media in exile). I spoke to him today at 12 o’clock and despite the ordeal he is in good spirit and raring to go. His injuries are not life threatening but he was in critical condition earlier. We all hope and pray that he will be back to work soon.” A close friend of the brutally mauled UDJP stalwart Ato Nebiyou Bazezew who requested anonymity told the Horn Times from Addis Ababa.

infohorntimes@gmail.com

የፍራቻ ፖለቲካ እና የፖለቲካ ፍራቻ -እውነቱ እና ፍርሃቱ

by Minelik S
የፍራቻ ፖለቲካ እና የፖለቲካ ፍራቻ -እውነቱ እና ፍርሃቱ በፍቃዱ ዘ ሃይሉ
የፍራቻ ፖለቲካ እና የፖለቲካ ፍራቻ - ጥንድ በኢትዮጵያ መሪዎችና ሕዝቦች መሀል የተጋረጡ የጦር መሳሪያዎች ናቸው፡፡ ሕዝቡ ካልፈራ ፖለቲከኞቹ የፍራቻ ፖለቲካ ይጫወታሉ፣ ፖለቲከኞቹ የፍራቻ ፖለቲካ ካልተጫወቱ ሕዝቡ ፖለቲካን ይፈራል፡፡ የሁለቱም ውጤት አንድ ነው፤ ውጤቱም ሕዝቡ መሪዎቹን የሚያስከፋ ነገር መናገርም ሆነ መተግበር ይፈራል፡፡

የፍራቻ ፖለቲካ፤ በገዢው እና ተቃዋሚዎቹ
ጥንት፣ ወትሮም ንጉሥ የማይከሰስ በመሆኑ መንግስታት ሕዝቦቻቸውን ማስፈራራታቸው የደንብ ያህል ነበር፡፡ ‹‹የተማረ ይምራን›› መባል ከተጀመረበት እና ደርግ የንጉሡን መንበር ከተረከበበት ጊዜ ወዲህም ግን ‹‹ደንቡ›› አልቆመም፡፡ ደርግ ‹‹አብዮቱን›› ሊቀለብሱ የሚንቀሳቀሱትን በሙሉ እንደማይምራቸው በሕዝብ ፊት ምሎ ዘመተባቸው፡፡ አብዮቱን ከሚቀለብሱት እንዳንዱ ላለመሆን የፈራ በሙሉ የኢሠፓ አባል ሆኖ በወንድሙ ላይ ዘመተ፡፡ ቀሪው ‹‹መሀል መስፈር›› የፈለገውም፣ ከፍራቻው’ጋ እንደተሟገተ 17 ዓመታት ኖረ፡፡
ኢሕአዴግ ቀርቶ የፍራቻ ፖለቲካ የቀረ ከመሰለ በኋላ ግን መልኩን ቀይሮ መጣ፡፡ አብዮቱን መቀልበስ፣ ሕገመንግስቱን መቀልበስ በሚል ተተካ፡፡ መንግስት የተቃወመውን ሁሉ በሆነ ስም በመፈረጅ ስለሚወነጅል፣ ላለመፈረጅ የሚሰጋው ሁሉ ወደወጣበት ምሽግ ተመልሶ ገባ፡፡ ‹‹ፖለቲካ እና ኮረንቲ›› የሚለው አባባል የተፈጠረው ያኔ ነው፡፡
የፍራቻ ፖለቲካን፣ ኢሕአዴግ በሌላም አካሔድ ይጫወትበታል፡፡ እንደገዢው ፓርቲ ዲስኩር ከሆነ፣ ኢሕአዴግ ከወረደ ወይም ተቃዋሚዎች ወደስልጣን ከወጡ የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ/ነፃነት ተዳፍኖ ይቀራል፣ የሃይማኖቶች እኩልነት አደጋ ላይ ይወድቃል፣ ልማቱ ይደናቀፋል… ወዘተ፣ ወዘተ፡፡
የዚህኑ ግልባጭ ተቃዋሚዎችም ይጠቀሙበታል፡፡ ኢሕአዴግ ካልወረደ ብሔር ብሔረሰቦች እርስ በእርሳቸው ይባላሉ፣ የኢትዮጵያ አንድነት እመቃብር ይወርዳል፣ ሃይማኖተኞች ጽንፈኛ ይሆናሉ፣ ኢኮኖሚው ተጣምሞ ይቀራል… ወዘተ፣ ወዘተ፡፡ ሙግቶቹ እውነትነት ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ነገር ግን የፖለቲካዊ ጫወታም ሆነ የምጣኔ ሃብታዊ ትንታኔ እና ትንቢት ለማይገባው ምስኪን ግን ያኛው ከመጣ፣ ይሄኛው ከወረደ ወይም ያኛው ካልመጣ ይሄኛው ከሰነበተ ነገሩ ሁሉ ምስቅልቅሉ ወጥቶ፣ ሕዝቦች ሁሉ አደጋ ላይ ወድቀው…በሚል ፍርሃት ሙሉ ራዕይ ታቅፎ ይቀራል፡፡ ለሁሉም እንደመፍትሄ የሚቆጥረው ደግሞ ሽሽት /ስደትን/ ነው፡፡
የፖለቲካ ፍራቻ፤ በተመልካቹ ሕዝብ
የ2011 Legatum Prosperity Index፤ ኢትዮጵያን ከ110 አገሮች ጋር አወዳድሮ በብልፅግናዋ 108ኛ ባስቀመጠበት ሪፖርቱ Safety & Security ንዑስ ዘርፍም 106ተኛ ይበቃሻል ለማለት ያበቃውን ምክንያት ሲዘረዝር፣ “The Ethiopian government has been known to engage in political violence and, globally, Ethiopia is the country where expression of political views is perceived by the population to be most restricted. This may be contributing to the rate of flight of professionals, intellectuals, and political dissidents, which is among the 20 highest rates in the world.” (‹‹የኢትዮጵያ መንግስት በፖለቲካዊ አመጾች ላይ እጁን በማስገባት ይታወቃል፣ በዓለምአቀፍ ደረጃም ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አመለካከትን ማንፀባረቅ በጣም የተገደበባት አገር ተደርጋ በዜጎቿ ትታሰባለች፤ ይህ ምናልባትም፣ ከዓለማችን ችግሩ የከፋባቸው 20 አገራት መካከል ኢትዮጵያን ላሰለፋት፥ የባለሙያዎች፣ ምሁራን እና ፖለቲከኞች ስደት መንስኤ ሳይሆን አይቀርም፡፡››) ብሏል፡፡
Personal Freedom ብሎ በሰየመው ንዑስ ዘርፍም ኢትዮጵያ ውራ (110ኛ) ሆናለች፡፡ ሲዘረዝረውም እንዲህ ብሎ ነው፤ “Ethiopia ranks among the bottom 10 countries for citizens’ freedoms in expression, belief, association, and personal autonomy.” (‹‹ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ሐሳብን፣ እምነትን፣ ማሕበርን፣ እና የመግለፅ ነፃነት፣ እና የግል አቋምን ለማንፀባረቅ ከማይመቹ የዓለማችን 10 አገሮች ተርታ ትሰለፋለች፡፡››)
ሐሳብን ለመግለፅ ካለመቻል ጀርባ ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን የማይገልፁት/ለመግለጽ የሚፈሩት ፖለቲካዊ አመለካከታቸውን ብቻ አይደለም ሃይማኖታዊ፣ ፆታዊ ጉዳዮቻቸውንም ጭምር ነው፡፡ ለዚህ አንዱ አስተዋፅዖ አዋጪ ‹‹የመቻቻል ምሳሌ›› የሚባለው ነገር ግን ‹‹መቻቻልን›› በጥያቄ ምልክት ውስጥ ያስቀመጠው ባሕላችን ነው፡፡ ‹‹መቻቻል›› በአገራችን አናሳው ብዙሐኑን ሲችል በሚል እሳቤ ተውጦ መክረሙ አጨቃጫቂ አይደለም፡፡ ስለዚህ አፈንጋጭ አመለካከቶች እውነታ ቢኖራቸውም እንኳን ተቀባይነት አይኖራቸውም፣ ሌላው ቀርቶ አፈንጋጭ አሳቢው ከሐሳቡ’ጋ ተግባብቶ እንዳይኖር ዱላ ይበዛበታል፡፡ ይህ ባሕል የወለደው ፍራቻ ፖለቲካዊ አስተሳሰብን የማንፀባረቅ፣ አንፀባርቆ ተቀባይነት የማጣት ፍራቻን ይወልዳል፡፡
ሕዝባችን ይፈራል፣ እንዲፈራም ታሪኩ ያስገድደዋል፤ ነገር ግን የሚፈራው በብትር የሚቀጣውን መንግስት ብቻ ሳይሆን በቃላት እና በማግለል የሚቀጣውን የራሱን ማኅበረሰብም ጭምር ነው፡፡ በዚህም የራሱን ሐሳብ ለራሱ አፍኖ በማለፍ ለአገሪቱ ለውጥ የሚበጁ በርካታ አማራጭ ሐሳቦችን አፍኖ ገድሏል፡፡ ይህንን ዓይነቱን ሕዝባዊ ፍራቻ አምባገነን መንግስታት ይፈልጉታል፣ እንዲለመልም እንጂ እንዲኮሰምን አያደርጉም፡፡ ለአምባገነን መንግስታት፣ ፍርሃት ከሰራዊቱ ይልቅ ሕዝቡን ከተቃውሞ ያቅብላቸዋል፡፡
በአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ደፋር ጋዜጠኞች፣ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች እና አፈንጋጭ ሃይማኖተኞች ሲገደሉ ነበር፣ እየታሰሩ እና እየተሳደዱ ነው፡፡ ይህ እውነታ ግን ከሕዝባዊው የፍራቻ አድማስ የበለጠ አይደለም፡፡ በግሌ የኢሕአዴግ መንግስትን ካጠነከሩት ጉዳዮች መካከል የሕዝቡ ፍራቻውን ከእውነተኛው ስጋት (risk) በላይ ማግነን እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ ለዚህም ነው ይህንን መጻፌ!
"መፍራት ያለብን ብቸኛው ነገር ፍርሃትን እራሱን ነው" እንዲሉ ፍራንክሊን ዲ. ሩዝቬልት፣ ፍርሃታችንን እንፍራው፡፡

ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ ወደ ሃገሯ ለመመለስ በተዘጋጀችበት ወቅት እራሷን በገመድ አንቃ ገደለች

በትላንትናው እለት በሳኡዲ አረቢያ አስደንጋጭ የሆነ ትእይንት ተፈጥሮአል ፡ይሄውም በቤት ሰራተኝነት ለሁለት አመት አገልግሎት ወደ ሳኡዲ አረቢያ ሄዳ ሁለት አመቷን አጠናቃ ወደ ሃገሯ ለመመለስ ጊዜዋን በጨረሰችበት ወቅት እና እንዲሁም አሰሪዎቿ የሰራተኝነት ቪዛዋን ፣የጊዜ ገደቡን እንዲጨርስ አድርገው ጨርሰውላት ለመሄድ በተዘጋጀችበት ወቅት እራሷን ለማጥፋት በመወሰን በመኝታ ቤቷ በመግባት በገመድ እርሳሷን አጥፍታለች ሲሉ አሰሪዎቿ ለመገናና ብዙሃኖች ተናግረዋል ::
 
ምን እንደነካት አናውቅም እኛንም አስገርሞናል አስደንግጦናል ለሁለት አመታት ከእኛ ጋር ስትሰራ ምንም ችግር የለባትም ያለ ጊዜ ገደቡ የቪዛዋን ጉዳይ ጨርሰን በጠየቀችን መሰረት ልንሸኛት ሁላችንም በተዘጋጀንበት ሰአት እርሷን አጥፍታለች ያሉት አሰሪዋ ከሚኖሩበት ደቡባዊ ሳኡዲ አረቢያ ከሃሚስት ሙሽህቲ ከተማ አካባቢ ነው ።እስካሁን የማንነቷ ጉዳይ አልታወቀም !

Thursday, August 22, 2013

Anti-terrorism decree: Born from power thirst

by Reeyot Alemu, Ethiopia

The article has been translated from the Amharic original for the International Women Media Foundation. The author,

a columnist for the now-defunct Ethiopian newspaper Feteh, is currently serving a 5-year prison sentence in Addis Ababa on bogus terrorism charges. The International Women’s Media Foundation honored Alemu with its 2012 Courage in Journalism Award last year, and in May 2013, the UNESCO recognized her “commitment to freedom of expression” with its Guillermo Cano World Press Freedom Prize.

Many questions cross my mind when I look at the “‘Anti-Terrorism Decree” and its application. Why does this decree have paragraphs that violate human rights? Why does it prosecute innocent citizens who have no ties to terrorism or terrorist organizations? I ask myself. In order to answer these questions one needs to look at the reasons behind the creation of such a decree, and so I did.

Why was the anti-terrorism decree written? One needn’t look too far to realize that the ruling party, EPRDF, didn’t create these anti-terrorism laws because it faced a real threat. You only need to look at the individuals who are either facing such charges, or have already been found guilty under this decree. Members of the opposition party who have denounced human rights violations and have peacefully called for the replacement of the current regime by a more democratic one,

freethinkers who dared ask stern questions to officials at locally organized discussion forums, leaders of the Muslim community who refused to dilute and redraft their religious beliefs to appease the government’s stance on religion, and ourselves, members of the free press who performed their duty as voices of the people have been the main victims of this anti-terrorist decree.

This proves that the real purpose of this decree is to enable the current regime to comfortably rule without any criticism, opposition, or competition. These actions are not creations of the EPRDF, instead they are old tried and true methods copied from other brutal regimes. It is very well known that colonial regimes of the past found it convenient to label the freedom fighters that refused to kneel as “terrorists.” And today, the EPRDF travels this same colonial path by stuffing its prisons with its own citizens and punishing those of us who have refused to give up our human and citizenship dignity.

What is to be done? Stopping the gross human rights violations that the EPRDF is committing under the guise of the anti-terrorism decree requires a lot of work. The current anti-terrorism decree will have to be replaced by a more appropriate one. Even with such changes, as long as the judicial system leans in favor of the EPRDF such arrests will continue. For, those of us who are currently imprisoned would have been found “not guilty” had we been judged fairly, even under the current anti-terrorism decree. As such, demonstrations and movements aimed at this decree, and more importantly at the ruling EPRDF who seeks to illegally use it, shall be strengthened and continued.

The reason I strongly believe that these protests should primarily be aimed at the ruling party is because it is the source of the wrongful application of this law and other innumerable Ethiopian problems. We have observed with disgust the length this regime will travel to protect its grip on power, and its rule. In other words, the actions of the EPRDF are based on motives that are tied to ethnicity, power hunger, and unjust prosperity among others. In Arthur Gordon’s words “If one’s motives are wrong, nothing can be right.” Because of this, nothing good can be expected from the EPRDF.

Therefore our only option for change remains a modern and peaceful struggle wherein we should be prepared to provide the needed sacrifices. As we embark on this journey to transform the system, there are many related issues that we should consider. We should deeply consider all the challenges set forth by the ruling party whether they are the ethnic, religious, ideological, or the interest based divisive elements it nourishes. We shall learn how to unite our many fronts of struggle into one.

Looking forward, it is the role of any responsible citizen, and especially that of the opposition parties and related groups, to think of and discuss  the nature of the system that shall proceed the current one. For as long as we accomplish these required duties, and stay  firm in our convictions, a Bright Day will not be too far.

ለእምነት ነፃነት የምናደርገውን ትግል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለዜግነት ክብር እና ለሀገር ነፃነት ከምናደርገው ትግል ጋር እናቀናጅ!!!


       
ትንሽነቱ በፈጠረበት ስጋት ምክንያት ሁሉንም ነገር ካልተቆጣጠረ በጉልበት የያዘውን ሥልጣን የሚያጣ የሚመስለው እና በዚህም ሳቢያ ሁሉም ነገር ውስጥ እጁን የሚነክረው ወያኔ ራሱን በገዢነት ከሾመበት እለት ጀምሮ የሃይማኖት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር እንደተጋ ነው። በእኛ በኢትዮጵያዊነት ዳተኝነት ታግዞም ትጋቱ ውጤት እያስገኘለት ነው።

ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክህነትን ከፓትሪያርክ ጀምሮ እስከ ደብር አለቆች ድረስ ያለው መንፈሳዊ ሹመት ተቆጣጥሯል። አሁን የቀየረው የቤተክርስቲያኒቷን ሃይማኖታዊ ቀኖናን መቀየር ነው። ወያኔ በሥልጣን ላይ ከቆየ ይህንንም ከማድረግ የማይመለስ መሆኑን በእስልምና እምነት ላይ ተግባራዊ እያደረገ ካለው መገንዘብ ይቻላል።

ልክ እንደ ክርስትናው ሁሉ ወያኔ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን (መጅሊስ) በራሱ ካድሬዎች ሞልቶት ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮታል። እስልምና ላይ ግን የሃይማኖት ተቋማትን ከመቆጣጠር አልፎ በቀኖና ጉዳይ በመግባት የራሱን “ምርጥ እስልምና” እያስተዋወቀ ነው። ዛሬ በሙስሊሞች ላይ የመጣው ነገ በክርስቲያኖችም ላይ የሚመጣውን አመላካች ነው።

እርግጥ ነው ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች የወያኔን ጥቃት በፀጋ አልተቀበሉትም። ሁሉም በየራሳቸው መንገድ የወያኔን ሁሉን-ጠቅላይ አገዛዝ እየተቃወሙትና እየታገሉት ነው። ዛሬ የወያኔ ጥቃት የደረሰበት ደረጃ ግን የሁለቱን ሃይማኖቶች አማኖችን ኅብረት የሚጠይቅ ሆኗል። ወያኔ ደግሞ በበኩሉ ይህ መከባበርና መተባበር እንዳይኖር ጥረት እያደረገ ነው።

የሁለቱም ትላልቅ ሃይማኖቶች ምዕመናን ለእምነታቸውና ለእምነት ተቋሞቻቸው ነፃነት በሚታገሉበት በአሁኑ ሰዓት “ጅራፍ እራሱ ገርፎ ራሱ ይጮህ” እንዲሉ ወያኔ ድምፃቸውን ቀምቶ በደሉን ለማጠናከር እየተጠቀመበት ነው። እፍረት ያልፈጠረባቸው የወያኔ ሹማምንት “መንግሥት በእምነታችን ጉዳይ ጣልቃ አይግባብን” እያሉ አቤት የሚሉትን ምዕመናንን “በፓለቲካ ጉዳይ ጣልቃ ገባችሁ፤ ይህ ደግሞ በኛ ሕግ ክልክል ነው” እያለ ይከሳቸዋል።

“ሃይማኖት በመንግሥት፤ መንግሥትም በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ አይገቡም” የሚለውን ሰፊ ተቀባይነት ያለው መርህ ወያኔ መሠሪ በሆነ ተንኮሉ “ሃይማኖት በፓለቲካ፤ ፓለቲካም በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገቡም” ወደሚል እጅግ አደገኛ መርህ እየቀየረው ነው።

“በሃይማኖትና መንግሥት” እና “በሃይማኖትና ፓለቲካ” መካከል ያለው ግዙፍ ልዩነት ለአብዛኛው ምዕመን ግልጽ አይደለም በሚል ግብዝነት ነገሮችን በማጣመም ምዕመናንን በማደናገር ለፍረጃ ያመቻቻቸዋል።

አዎ ሃይማኖትና መንግሥት መለያየት አለባቸው። ኢትዮጵያዊ ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች እየጠየቁ ያለውም ወያኔ ይህንን መርህ እንዲያከብር ነው። “ወያኔ ሆይ!!! በሃይማኖታችን ጉዳይ ጣልቃ አትግባብን!” እያሉት ነው።

ሃይማኖትና ፓለቲካ ግን በብዙ ክሮች የተቆላለፉ ነገሮች ናቸው። ለሃይማኖት ነፃነት መከራከር ራሱ ፓለቲካ ነው። ለሰብዓዊ መብቶች መከበር መከራከርም ትልቅ ፓለቲካ ነው። የሁለቱ ሃይማኖቶች አማኞች ይከባበሩ፤ ይተባበሩ ማለትም ፓለቲካ ነው። ይህ እንዳይፈጠር ነው ወያኔ ሃይማኖትና ፓለቲካ እሳትና ጭድ አድርጎ ሊስላቸው የሚዳዳው።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ኢትዮጵያዊያን ምዕመናን በሃይማኖትና ፓለቲካ አንድነትና ልዩነት ላይ የጠራ አቋም መያዛቸው ትግላችን ያግዛል ብሎ ያምናል።

ሃይማኖትና መንግሥት መለያየታቸው ተገቢ ነው። ሃይማኖትና ፓለቲካ ግን አንድ ባይሆኑም በብዙ መንገዶች የሚደጋገፉ ናቸው። ሃይማኖቶች ለእምነት ነፃነት፣ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለዜግነት ክብር፣ ለሀገር ነፃነት እና መሰል ጉዳዮች በግንባር ቀደም መታገል ይኖርባቸዋል። በታሪካችን ውስጥ ታቦቶች ጦር ሜዳዎች ዘምተው አርበኞችን አበረታተዋል። ይህ ዛሬም ሊደረግ የሚገባው የተቀደሰ ተግባር ነው።

በዛሬ የአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ሃይማኖትና የሃይማኖት ተቋማትን ከወያኔ መዳፍ ማውጣት ሀገርን ከወያኔ መዳፍ ከማዳን ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ጉዳይ ሆኗል። ስለሆነም ለሃይማኖት ነፃነት የምናደርገው ትግል ለሀገራችንም የምናደርገው ትግል አካል ነው።
ወያኔ በሃይማኖቶቻችን፣ በሀገራችን ብሎ በራሳችን ላይ የመጣ እኩይ ኃይል ነው።

ስለሆነም፣ ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለሃይማኖት ነፃነት የምናደርገውን ትግል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለዜግነት ክብር እና ለሀገር ነፃነት ከምናደርገው ትግል ጋር እንድናቀናጅ ወገናዊ ጥሪ ያደርጋል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ሰላሳ ሶስቱ ፓርቲዎች -ሰማያዊ ፓርቲን ከፓርቲዎች የትብብር መድረክ አሰናበቱ።

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የ33ቱ ፓርቲዎች የትብብር መድረክ -ሰማያዊ ፓርቲን ያሰናበተው፤የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ሰሞኑን ለ ሰንደቅ ጋዜጣ የሰጡት ቃለምልልስ የሌሎች ፓርቲዎችን ክብር የነፈገ ነው በሚል ነው።

በዚህም መሰረት ፓርቲዎቹ ባደረጉት ስብሰባ ሰማያዊ ፓርቲ ከስብስቡ እንዲወጣ መወሰናቸውን የቪኦኤ ዘገባ ያስረዳል።
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፀሀፊ አቶ ተስፋዬ ታሪኩ ውሳኔው የተላለፈው ባለፈው እሁድ በተካሄደ አስቸኳይ ስብሰባ እንደሆነ  ገልጸዋል።

አቶ ይልቃል ለሰንደቅ በሰጡት ቃለ ምልልስ በዚህች አገር ከሰማያዊ ፓርቲ ውጪ ሌላ ተቃዋሚ ፓርቲ አለ ብለው እንደማያምኑ መገለፃቸው ይታወሳል።

“ገዥው ፓርቲና ምርጫ ቦርድ የሰጡንን ዕውቅና ሳይቀር አቶ ይልቃል ነስተውናል”ያሉት የመኢአድ ፀሀፊ፤ህዝቡ በፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ እምነት እንዳያድርበት ደባ ስለፈጸሙ፤ ድርጊታቸውን እንዲያርም ጊዜ ቢሰጣቸውም ሊያርሙ ስላለረቻሉ፤ ይባስ ብለውም ያንኑ ሃሳባቸውን ፡”የኛ ፕሬስ”በተሰኘ ጋዜጣ ላይ በማንፀባረቃቸው እና አቋሙ የ እርሳቸው ብቻ ሳይሆን የፓርቲያቸው ጭምር እንደሆነ በመረጋገጡ ከስብስቡ እንዲሰናበቱ ወስነናል ብለዋል።

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ይልቃል በበኩላቸው “የሰጠሁት አስተያየትና ያንፀባረቅኩት ሃሳብ አዲስ አይደለም፤ እውነትም    ነው”ብለዋል።

እስካሁን ሌሎች ፓርቲዎች የከፈሉትን መስዋዕትነት እርሳቸውና ፓርቲያቸው እንደሚያደንቁ ለቪኦኤ የተናገሩት አቶ ይልቃል፤ይሁንና ተቃዋሚዎች በአሁኑ ጊዜ የህዝብን የለውጥ ጥያቄ ለመመለስ በሚያስችል ጥንካሬና አቋም ላይ አለመሆናቸውን ገልጸዋል።
“እኔ ስህተተኛ ብሆን ደስታዬ ነበር”ያሉት አቶ ይልቃል፤”እነዚህ ፓርቲዎች ነን እንደሚሉት ቢሆኑ እኔና ጓደኞቼ ሰማያዊ ፓርቲን አፍርሰን ወደየሌሎች ፓርቲዎች እንገባለን፤ወይም ወደየቤታችን እንሄዳለን”ብለዋል።

“ግን እውነቱ ሌላ ነው። የኢትዮጵያን ችግር መጋፈጥ አለብን ካልን እውነቱን ማድበስበስ የለብንም” በማለት ቀደም ሲል በሰጡት አስተያዬት እንደሚያምኑ በድጋሚ አረጋግጠዋል።

32 suspected of organizing protests in Kucha fired

ESAT News  August 22, 2013

Thirty-two people that were suspected of organizing the opposition and protests in Kucha Woreda, Selam Ber town, Gamogofa Zone of Southern Ethiopia, have been fired from their jobs. Among whom are 2 prosecutors, 2 judges, 1 court registrar and a police officer. Eight others have left their jobs and fled to other regions. Sixteen more people have been arrested in the past weeks alone.

Over 40 people, who include people that were detained since last month, had appeared in Court yesterday and were given another appointment to August 30, 2013. Worried that the tensions might turn into violence, 60 elders of the Woreda have travelled to Addis Abeba to speak to Federal government officials yesterday. A month ago, some elders that had travelled to Addis Abeba on a similar mission have been detained. Masebo Madalcho, investor and prominent elder of the area, has been detained three days ago.

Over 160 Bajaj motorcycles, suspected of serving as information conduits between the districts, are still seized by the police. ESAT has learnt that the elders that travelled to Addis Abeba will warn the Federal government officials that the local community will take its own measures unless the government stops evicting civil servants and detaining people, which the government will be responsible for.

The Unity for Democracy and Justice Party (UDJ) had called on the government to immediately find solutions to the “rights and identity” questions of the residents of Kucha Woreda.

ESAT’s attempt to speak to Ethiopian government officials on the issue was unsuccessful.

አሳ ጐርጓሪ ዘንዶ ያወጣል (ክፍል ፭)

ugust 22, 2013

ናደዉ፦ከዋሽንግተን ዲሲ
የወያኔ ጉጅሌዎችን ስዉር አጀንዳ ፅሁፍ ከዚህ ሆድ አደር ተላላኪ ታሪክ በኋላ ወደ ሌሎቹ እዘምታለሁ፤በማህበር ተጠርንፈዉ እስከሚመጡልኝ ወይም እስከሚመጡብኝ ድረስ ማጋለጤ በሰፊዉ ይቀጥላል፧ለጠላቴ አልተኛም እንደ በትናቸዉ/ፍርሻው ስንሻዉ የታች አርማጭሆ ልጅ መሆኔ ቀረ?!
ምርጫዉ ስንሻዉ ወይም ብዙዎች የዲሲና አካባቢዉ ነዋሪዎች እንደሚጠሩት በትናቸዉ/ፍርሻው ስንሻዉ ባለፈዉ እሁድ ደግሞ አዲስ የጥላቻና የጋጠወጥ ስድብ ከረጢቱን ዘረገፈዉ፣ አዎ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በሚገኙት በሙስሊሙ ሕብረተሰብ መሪ በፈርስቲ ኢጂራ ፕሬዘዳንት በሼክ ነጂብ ላይ፧ በወያኔ ጉጅሌ በጀት በሚተዳደረዉ ወናፍ መንደርተኛ ራዲዮኑ እሳቸዉን ብቻ ሳይሆን ባለቤታቸዉንና የሙስሊሙን ሕብረተሰብ የድምፃችን ይሰማ እንቅስቃሴም ጭምር፥እንደወያኔ አስተዳዳሪዎቹ ሁሉ እሱም ሲሳደብ ዉሎ አደረ ፧ተወካያቸዉ መሆኑም አይደል?!መሽቶ ነጋ በቅዳሜ ማታና በእሁድ ቀን ፕሮግራሞቹ፤እኔም በዚህ ባንዳ ዙርያ በተከታታይ ለማወጣቸዉ ፅሁፎቼ ስል አለፍ አለፍ አድርጌ መቅረፀ ድምፄን ይዤ መከታተሌ አልቀረም፧ሚስቴና ልጆቼን ተደብቄ በሌሉበት መሆኑ ይታወቅልኝ !ምክንያት፥የዚህን ተሳዳቢ ሰዉዬ ቱማታ ላለመስማት ቤቱን ጥለንልህ እንዉጣ የሚለዉ ብስጭታቸዉ ስላሳሰበኝ ብቻ !!
ለእለቱ ለስድብ ኢላማነት የተመረጡትን እኝህን የሀይማኖት መሪ እንዲህ አለ፦ በአክብሮት ዘለፋዬን እርስዎም ባለቤትዎም የሀይማኖትዎም ተከታዮች በጥሞና ያዳምጡኝ ብሎ የራዲዮን ፕሮግራሙን ጀመረ፣የተለመደዉን የጥላቻ ስድብ ዉርጅብኝ በይሉኝታ ቢስና ፀያፍ ቃላቶቹ ለቀቀዉ አዎ እሱ ማንን ፈርቶ?!
ዛሬ ገና ለዚህ ተከታታይ ፅሁፌ ተገቢና ትክክለኛ ርእስ መስጠቴን አረጋገጥኩ። አሳ ጐርጓሪ ዘንዶ ያወጣል። ያልኩትን፧ በትምህርተ ጥቅስ አስቀመጥኩት፤ ለምን እንዲህ አልክ ብትሉኝ መልሴ እንደሚከተለዉ ይሆናል፧! እኚህ ሰዉ ስለዚህ መሰሪ የደርግ ካድሬ ብዙ ምስጢር እንደሚያዉቁ ስለማዉቅ ብቻ ሳይሆን ዛሬ የሚያዉቁት ነገር ምናልባትም ላለፉት አስርተ አመታት ለዋሽንግተን ነዋሪ ኢትዮጵያዉያን ያልተናገሩትን የደራሽ ግብረሃይል ምስጢር የሚያጋልጡበት ወቅት አሁን በመሆኑ ነዉ። ሳይቸግረዉ የነካካቸዉ ይመስለኛል፧ያዉም የሞራል ህልዉናን በሚፈታተን መልኩ፥ለዚህ ወስላታ የመልስ ምት አያስፈልገዉ ብለዉ ነዉ ሃጂ?! ነገሩ እንዲህ ነዉ በክፍል አንድና ሁለት ላይ በግልፅ እንዳሠፈርኩት የዛሬ አስር አመት አካባቢ አገራችን ኢትዮጵያ በከፍተኛ ረሀብና ድርቅ በተጠቃችበትና አላፊነት የጎደለዉ የህወሀት ዘረኛ አምባገነን አገዛዝም ሁኔታዉን ለመደበቅ በሚድበሰበስበት በዚያን ወቅት የዓለም አቀፍ የዜና ማሰራጫዎች ሁኔታዉን ገሀድ ማዉጣታቸዉ እርግጥ ነዉ። በወገኖቻችን ላይ ደርሶ የነበረዉ አስከፊ ሁኔታ ወያኔን ከመታገል ጎን ለጎን ለተጎዱት ወገኖች በአፋጣኝ መድረስ ጊዜዉ ግድ ይል ነበር። በዚህም መሰረት በዳያስፓራ የሚገኙት አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን ትልቅ ድርሻ አበርክተዋል በዋሽንግተንና አካባቢዉም በተመሳሳይ መልኩ ከተጎጂ ወገኖቻቸዉ ጎን ለመቆም መንቀሳቀሳቸዉ አልቀረም። ይህንኑ የወገን ጥሪ ምላሽ ለመስጠት ሲባል በተቋቋመዉ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ግብረሃይል ዉስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ በማድረግ ከሁለት መቶ ሽህ ዶላር በላይ ተሰበሰበ የተሰበሰበዉንም ገንዘብ ደራሽ ግብረሃይል የሚል ስያሜ ለተሰጠዉ ኮሚቴ በአደራ በአደራ አስረከበና ዉጤቱን መጠባበቅ ጀመረ። በጊዜዉ ከኮሚቴዉ አባላት ዉስጥ በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት የኢትዮጵያዊነት ራዲዮኑ ጓድ ምርጫዉ ስንሻዉ፤የሀገር ፍቅር ራዲዮኑ ባንዳዉ ንጉሴ ወልደማርያም፤የፈርስቲ ኢጅራዉ ፕሬዘዳንት ሃጂ ነጂብና ሲስተር እማዋይሽ ነበሩ። ተወካዮቹ በአካል ተገኝተዉ ለተጎጂ ወገኖቻችን አስፈላጊዉን ቁሳቁስ ገዝተዉ አንዲሰጡ የሕዝብ አደራ ተቀበሉ ፧አደራዉን ግን በሉት።
እንዲህ ሆነላችሁ የተከበራችሁ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ፧ የኮሚቴዉ ተወካዮች አዲስ አበባ ቦሌ አለምአቀፍ አዉሮፕላን ማረፊያ እንደደረሱ በወያኔ ካድሬዎችና ሰላዮች ታጅበዉ ወደተዘጋጀላቸዉ ሸራተን ሆቴል አመሩ፧ ከተለያዩ ባለስልጣኖችም የምስጋናና የእንኳን ደህና መጣችሁ ስልኮች አቃጨሉላቸዉ የኰሚቴዉ መሪ የነበረዉ ሆድ አደር ተላላኪዉ ንጉሤ ወልደማርያም ከመመሪያ ጋር በእለቱ በሆቴል ክፍሉ ዉስጥ የወያኔ አባልነት ፎርም መሙላቱን የከብት ሕክምና ባለሙያዋ ባለቤቱ ታወራለች። በተያዘላቸዉ ምርጥ ክፍል አርፈዉ ለጥቂት ቀናት በከተመዉ ዉስጥ ከተዝናኑ በኋላ ፧ከየአቅጣጫዉ ከአገር ዉስጥም ሆነ ከዉጭ አገር በተጎጂዎች ስም በሚጎርፍለት ገንዘብ የሰከረዉ ወያኔ መልእክተኞቹን በቴሌቪዥን መስታወት ለጥቂት ደቂቃዎች ከሌሎች ለጋሾች ጋር ቀርበዉ ሁለት መቶ ሽህ የኢትዮጵያ ብር በጊዜዉ የወያኔ የአደጋ መከላከል ኰሚሽን ኮሚሽነር ለነበሩት ለአቶ ስምኦን መቻሌ ያስረክቡና በሌላ የክህደት ፕሮግራም ለመገናኘት ተማምለዉ ይለያያሉ። ከመሐል አንድ እህታችን ብቻ በነገሩ ግራ በመጋባት ይህንን የህዝብ አደራ በልነትን ታወግዛለች ወደ አሜሪካ ስትመለስ ለማጋለጥም ለራሷ ቃል ትገባና ዋሽንግተን በገቡ ማግስት ጀምሮ በተለያዩ ራዲዮኖች እየቀረበች ወገኖቼ የረሀብተኛዉ የእርዳታ ገንዘብ ተበላ እያለች መጮህዋን ትቀጥላለች ፧ቀሪ የኰሚቴ አባላትን ጨምሮ በአማላጅ ሁኔታዉ ይፋ እንዲወጣ ታስጠይቃለች ነገር ግን የሚሰማት ጠፋ ። አንድ እለት ብቻ ጓድ በትናቸዉ ስንሻዉ ከሕብረተሰቡ ዛቻና ማስፈራርያ ሲበዛበት በራሱ ራዲዮ ላይ ወጥቶ ሃምሣ ሽህ ዶላር ብቻ መቅረቱንና ይህም ገንዘብ ወደፊት የሕዝብ ዉሳኔ ያገኛል ብሎ ለፈፈ፤ከዚያ ቀናት ሳምንታትን ሳምንታት ወራትን ወራት አመታትን አስቆጠሩ እነሆ ዛሬ አስርተ አመቱ ተቆጠረ ነገሩ የተረሳ ከሀዲ ቀማኞቹም ለይቶላቸዉ ወያኔ በፍርፋሪ ከጎኑ በግልፅና በስዉር አሰልፏቸዉ በሚመፀወቱት የራዲዮን የአየር ሰአት እንደገና ይሰድቡናል ያላግጡብናል፣ ገንዘቡንና ጊዜዉን የተበላዉ ነዋሪም አፈር ብላ ብሎ ተራግሞ ወደ ቤቱ ገባ ብዙዎች ግን በተለያዩ ቦታዎች የነዚህን ከሀዲዎች ፀያፍ ተግባር ዛሬም ያስታዉሳሉ። ይህ የህዝብ ገንዘብ ነዉ ያለንበት አገር ደግሞ የህግ የበላይነት ይከበራል የተበላዉ በረሀብ ለተጎዱ ወገኖች የተዋጣ ገንዘብ ነዉ የፈለገዉ ያህል ጊዜ ቢቆይም ጉዳዩን በሕግ ፊት ማቅረብ ይቻላልና የህግ ባለሞያ ኢትዮጵያዉያንን ነገሩን እንዲመረምሩት በዚህ አጋጣሚ አሳስባለሁ!
አሁንም በቅርቡ በዚያ በዘራፊዎቹ ንኡስ ኰሚቴ ዉስጥ የነበሩ አዛዉንትን አግኝቼ ሳነሳባቸዉ ነገሩ እንደዉስጥ እግር እሳት ያንገበግበኛል አሉ ወንጀለኞቹን እነ በትናቸዉ ስንሻዉን ዛሬም ምርር ብለዉ በፊቴ ተራገሙ በተጨማሪም እንዲህ አሉኝ በዚያን ወቅት ተጨንቄ ሃጂ ነጂብም ዘንድ ሄጄ እዉነቱን ለሕዝቡ ንገሩ ብዬ ብጠይቀዉ ዳግም አጠገቡ እንዳልደርስ አባረረኝ አሉና ሁኔታዉን ጊዜ እንዳመቻቸዉ የሚያዉቁትን ሁሉ በተገኘዉ ሚዲያ ገሃድ እንደሚያደርጉት ገለፁልኝና ተሰነባበትን።
በመጨረሻ ማሳሰብ የምወደዉ ሃጂ ነጅብ የሚያዉቁትን ይንገሩንና እርስዎም ከሕሊና ወቀሳ ይገላገሉ፣በብዙ ሀይማኖቶች ሲነገር የምንሰማዉ፦ ሌባና ሌባ ሲሰረቅ አይቶ እንዳላየ የሆነ ፧የሁለቱም ወንጀል አንድ ነዉ ይባል የለ?!እና እነዚህ ወሮበሎች ስለዘረፉት ገንዘብ የሚያውቁትን ይንገሩን እግረመንገድዎንም ከሃሜቱ ነፃ ይዉጡ እያልኩ ነዉ። ወቅቱም አሁን ነዉና!!!
የጓድ በትናቸዉ ስንሻዉ ጉድ መቸም ቢጎለጎል አያልቅም እኔም አንዴ ጀምሬዋለሁና የማዉቃቸዉንና የሚደርሱኝን መረጃዎች በሙሉ እሄድባቸዋለሁ አዲስ አበባ አፍንጮ በር አካባቢ ለምትኖረዉ የድሮ ጓደኛዪ ምሥራቅ ስንሻዉ ከባለቤትዋ ከታጋይ ተክሌ አጋበዝ ጋር ሆና የወንድምዋን ጉድ እንድታየዉና ይህንን ፅሁፍ እንድትፈትሸዉ ሰሞኑን ሳልደዉልላት አልቀርም።
ይህን ማስታወሻ ስፅፍ ዶክተር ታዬ ወልደሰማያትና አቶ ብርሃነ መዋ ትዝ አይሉኝ መሰላችሁ!?በነገራችን ላይ ሁለቱንም ወንድሞቼን እጅግ አድርጌ አከብራቸዋለሁ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዉስጥ ቀላል የማይባል አስተዋፅዖ ማበርከታቸዉ እውነት ነው። ዛሬ ግን ወደ ፓለቲካዉ መድረክ ዳግም ላይመለሱ ከአንደበታቸዉ ብዙዎቻችን ሰማን። የሚገርማችሁ ደግሞ ሁለቱም በአንድ ወቅት በቅንጅት መፍረስ ማግስት መሆኑ ነዉ፧ ለዚህ ትልቁና ዋናዉ ተከሳሽ ጓድ በትናቸዉ ስንሻዉ መሆኑ አይደንቅም። የቅንጅት አመራሮች በእስር ላይ በነበሩበት ግዜ እዚህ የነበሩት የቅንጅት የድጋፍ ኮሚቴ አባላት መከፋፈል ጀመሩ የኰሚቴው ሰብሳቢ የነበሩት ሻለቃ ዮሴፍ በእስር ላይ ከሚገኙት የቅንጅት ፕሬዘዳንት ከኢንጅነር ሃይሉ ሻወል የኰሚቴ አባላቶች ሹም ሽር በፊርማቸዉ አረጋግጠዉ ላኩ ተባለ አሰራሩ ማእከላዊነት ያልጠበቀ ነዉ ይሄ የንጉሣዊ ሹመት አይነት ነዉና አንቀበልም የሚል አካል ተፈጠረ የነብርሃነ መዋ ቡድን፧ ከስር ቤት ሾልኮ መጣ በተባለዉ የሹመት ዝርዝር ዉስጥ በዚያ የፓርቲ ስብስብ ዉስጥ ያልነበሩት የዶክተር ታየ ወልደሰማያት ስም የመሪነቱን ቦታ ይዞ ቀረበ ይህንን ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያራግቡት ሃላፊነቱን በበላይነት አንዲመራዉ ደጎስ ካለ የገንዘብ ጉርሻ ጋር ጓድ ምርጫዉ ስንሻዉ ተረከበ ረዳት ሆድአደር አፍራሾችም ተመደቡለት ረዳቶቹ ደግሞ ከኛ ወዲያ ትግል ላሳር የሚሉ የትግል ዘመናቸዉን ሻማ በማብራት ብቻ የሚደክሙ የዲሲ ፋኖዎችና በታኞች ተሳካላቸዉ በአጭር ጊዜ የአገሪቱን ሕዝብ አንድ አድርጎ ወያኔን ያርበደበደዉን ብዙ ዜጎች በጠራራ ፀሐይ ዉድና ተተኪ የማይገኝለትን ዉድ ሕይወታቸዉን የገበሩለትን የፓለቲካ ንቅናቄ ጠልፈዉ ጣሉት አሽመደመዱት። አዎ ምርጫዉ ስንሻዉ፧እነ ሻለቃ ዮሴፍንና ታዋቂዉን ስመ ጥር የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ማኖ አስነካቸዉ ሸወዳቸዉ በግርግርም ከፍተኛ ገንዘብ ተበላ ቅንጅትም ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ከጨዋታ ዉጪ ሆነ ተበተነ የበትናቸዉ ስንሻዉ አለቆች ከበሮአቸዉን ደለቁ ከሕዝባዊዉ ማእበል ተጠራርጎ ከመጥፋት ዳኑ፧ ያን ሁሉ ወንጀል ፈፅመዉ ዛሬም እነምርጫዉ አሉ!አሁንም ኢንጅነር ሐይሉን እነ ብርሃነ መዋንም ጨምሮ ሁሉንም ባልተገራዉ ግልብ ንግግሩ ሙልጭ አድርጎ እያወረዳቸዉ ነዉ።ዛሬ በዚህ ባንዳ ምክንያት ብዙ ጠንካራ ሰዎችን አጥተናል አሁንም ዘለፋዉን ቀጥሏል።
መቸም በበትናቸዉ ስንሻዉ ዘለፋና ዝርፊያ ቆሽቱ ያልተቃጠለ አንጀቱ ያላረረ የለምና የዚህ ካድሬ ተጠቂዎች ለዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ብዙ መረጃዎች አደርሰዉታል፧ብዙዎቹ ይበሳጫሉ እንዲህ ያለ ኢትዮጵያዊ የለም ያስብላሉ ተግባራቶቹ ግን እዉነቶች ናቸዉ። እና አኔ እያልኩ ያለሁት ስም ለማጥፋት ለመጠፋፋት ሳይሆን አካሄድህ አስነዋሪ ነዉ ብሎ እሱነቱንና ወልጋዳ አካሄዱን ለራሱ እንደመስታወት አሳይቶ ወደወገኖቹ ለመመለስ ነዉ እንጂ ከተላላኪ ሆድ አደሮች ጋር ይሄን ያህል ግዜ ማባከን ባላስፈለገም ነበር ምናልባት ወደቀልቢያዉ ቢመለስ ብዬ እንጂ!!
ትናንት አንድ ወዳጄ አንድ አባት በዚህ አጉራ ዘለል ካድሬ የሆኑትን ልንገራችሁና የዛሬዉን ፅሁፊን ላብቃ በአንድ ወቅት ለከፈተዉ ቤተክርስትያን በደመወዝ እንዲያገለግሉት አንድ አባት ከምስጢራተ ቤተክርስትያንና ቅዱሳን መጽሐፍቶች ጋር ከአገር ቤት ያስመጣቸዋል በሚኖርበት አካባቢ ነዋሪዎች ቪላ ዉስጥ የምትገኝ አንድ ጠባብ ክፍል ይከራይላቸውና ይገባሉ ቄሱም በየወሩ ከሚሰጣቸዉ ደመወዝ ለቤቱ ኪራይ እየቀነሰ ቀሪዉን ሲሰጣቸዉ ይከርማል የሰዉየዉ ግልብ ባህርይ ባይመቻቸዉም ሌላ መጠጊያ ስለሌላቸዉ ረዘም ላለ ጊዜ እንደተቀመጡ እንባ እየተናነቃቸዉ ይናገራሉ አነጋገራቸዉ ሁኔታቸዉ በዚህ በመጦርያ እድሜያቸዉ ስደተኝነታቸዉና ሁኔታቸዉ እጅግ አሳዝኖኝ መንፈሴ እየተሸበረ ስላስቸገረኝ ንግግራቸዉን ቶሎ እንዲጨርሱ በመመኘት ከዚያ በኋላስ አልኳቸዉ ከዚያ በኋላማ ልጄ አሉ አንገታቸዉን አቀርቅረዉ መሬቱን በያዙት ረጅም ጃንጥላ ጫፍ እየቆረቆሩ ፦አንድ ቀን ትንሽ አመም አርጎኝ እቤት ዋልኩ ያለወትሮየ ቤት መዋሌን የተመለከቱት የቤቱ ባለቤቶች ሊጠይቁኝ መጡ እህል ዉሃም ሰጡኝና በደንብ ሳይሻለኝ እንዳልነሳ ሲመክሩኝ አይ እዚህ አገር ወጪዉ መች ያስተኛል አልኳቸዉ ሴትየዋም ሳቅ ብለዉ አይ አባ እርስዎ ደግሞ ምን ወጪ አለብዎት ለምግቡም ቢሆን አያስቡ አሉኝ እኔም ለሆዴ እንኳ ግድ የለኝም የቤት ኪራዩን ማን ይከፍልልኛል ስላቸዉ የምን የቤት ኪራይ ነዉ የሚያወሩት እኛ ሁኔታዎን አይተን ምርቃትዎ ይበቃናል ብለን ገንዘብ ተቀብለዉ አናዉቅም አሉኝ እኔም በየወሩ ከደመዜ ላይ እንደሚቆርጥብኝ ነገርኳቸዉና ከዚያን አለት ጀምሮ አይኑን አያሳየኝ ብዬ ለአምላኬ አልቅሼ ቀረሁ አሉኝ። አይገርምም ወገኖቼ?!
እነዚህን የመሳሰሉ አሳፋሪ ብዙ ተግባሮቹን ብዙ ትሰማላችሁ እዚህ አካባቢ ጎራ ብትሉ፤ከዚህ ነዉረኛ የወያኔ ተላላኪ የምንረዳው አንድ ነገር አለ ይኸዉም አምባገነኑና ጨካኑ የህወሀት ስርአት በዙርያው የሚኮለኩላቸዉ ፍርፋሪ ለቃቃሚዎች ምንአይነት ከርሳሞችና ምግባረ ብልሹዎች እንደሆኑ ነዉ።
ክፍል ፮ ይቀጥላል

Wednesday, August 21, 2013

Ethiopia’s Muslim Activists Pave a Path for Nonviolent Political Activism

August 21, 2013
by Terrence Lyons, Briefing
 World Politics Review


The embarrassing Interview of Deputy PM Haile Mariam DesalegnA year after Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn came to power following the death of longtime leader Meles Zenawi in August 2012, the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) remains firmly in control. It has continued to govern through a collective leadership that includes three deputy prime ministers from the Amhara, Tigray and Oromo wings of the coalition; Hailemariam hails from the Southern People’s Party. Party discipline and coherence has held, although the lead-up to elections in 2015 may reveal destabilizing fissures. But while older opposition parties and armed movements have been marginalized, a social movement of Ethiopian Muslims is an important new development.

Rapid economic growth has been key to Ethiopia’s stability. The economy grew by more than 10 percent annually over the past decade, and while growth has slowed down it remains higher than the African average. Recent data, however, suggest that earnings from coffee and gold, Ethiopia’s two largest sources of export revenues, have declined. The World Bank also raised concerns that Ethiopia’s boom has relied too heavily upon public investment and that sustained growth will require a significant increase in private investment.

The political opposition to the EPRDF—currently divided into camps based on whether they subscribe to ethno-national or pan-Ethiopian goals and whether they operate in exile or have remained in the country—has struggled to find channels to influence Ethiopian politics. After competitive elections in 2005 and the subsequent crisis that led to the arrest of much of the opposition leadership and the collapse of the main opposition coalitions, the regime effectively criminalized dissent. Restrictions on independent media and civil society limit the ability of Ethiopians to mobilize outside of the structures of the ruling party. The EPRDF’s dominance was evident in local elections this year, in which it and its affiliated parties won all but one seat nationwide.

As a result, opposition political parties that challenged the regime in 2005 now play virtually no role in national politics. The Semayawi, or Blue, party organized a notable demonstration in June and has some following among the youth, but its potential to challenge the regime is limited. Berhanu Nega, a politician who had considerable influence in 2005, is now operating in exile without a significant presence in the country. Repression and the use of anti-terrorism laws, as well as weak structures and leadership, limit the opposition’s ability to operate within Ethiopia.

Meanwhile, several groups, notably the Oromo Liberation Front (OLF) and the Ogaden National Liberation Front (ONLF), remain engaged in protracted armed struggles, but Addis Ababa has effectively managed these military challenges. Oromo nationalism remains potent, but the OLF leadership is divided and discredited. Promising talks between the ONLF and Addis Ababa collapsed in October 2012, but there are officials on both sides that see advantages from a negotiated settlement. The government would like to end the war in order to concentrate on development of the region’s natural gas and other resources. Some Ogadenis recognize that they are unlikely to win the military contest and wish to end the ferocious counterinsurgency campaign in the region. But reaching a durable agreement, a recent International Crisis Group report accurately notes, will require “unprecedented concessions from both sides.”

Finally, the ongoing demonstrations by Ethiopian Muslims, who make up approximately 40 percent of the country, provide an important model of politics outside of the ruling party that relies upon neither armed struggle nor the strategies of electoral competition on a hopelessly lopsided playing field. The demonstrations began 18 months ago to protest government interference in Islamic affairs and the regime’s links to the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council. The movement has been extraordinarily disciplined and nonviolent and has succeeded in part by focusing on a specific set of issues. Demonstrations have been held after Friday prayers in Addis Ababa but also notably in other towns across Ethiopia.

Muslim activists emphasize that they are operating within the framework of the Ethiopian constitution and that they are not seeking to overthrow the regime. The Ethiopian government, in contrast, has consistently claimed that the protests were organized by extremists bankrolled from overseas and seeking to establish an Islamist state. More recently Addis Ababa has identified neighboring Eritrea as the source of this alleged external support. The movement’s leadership was arrested July 2012 and charged with terrorism in October.

Earlier this month there were clashes between Ethiopian security forces and Muslims reportedly following the arrests of three local imams in Kofele, a town in the Oromo region. A heavy police presence and arrests in Addis Ababa following the Eid al-Fitr ceremonies celebrating the end of Ramadan on Aug. 8 further raised the temperature and tensions. Government spokesman Shimeles Kemal alleged that the arrests were of “Salafist elements who tried to create disturbances.”
Despite the government’s arrests and condemnations, the Ethiopian Muslim demonstrators have shown that sustained, nonviolent political activism is possible in Ethiopia. What is not clear,

however, is the movement’s future. Many leaders in the older ethno-nationalist movements, including those with large Muslim constituencies, such as the Oromo and Somali, view the multiethnic nature of the movement with trepidation. Others, including leaders in the Semayawi party, view it as a vehicle to advance pan-Ethiopian political ideas. Some Muslim activists propose a strategy of sustained low-level protest that avoids confrontation and recognize that a quick victory is impossible.

 To move more assertively would spark a military crackdown, and the movement’s leadership is likely to lose control if there is violence. The key dynamics to watch in the lead-up to elections in 2015 are therefore competition within the ruling party and the potential for the Ethiopian Muslim movement to create new space for political activism.

Terrence Lyons is associate professor of Conflict Analysis and Resolution and co-director of the Center for Global Studies, George Mason University.

‘እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል’ – ልንዋጋው የሚገባ አህያዊ ብሂል! – By Nasrudin Ousman

በኢሕአዴግ የሚመራው መንግሥት በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች መካከል የእርስ በርስ ጥርጣሬና ጥላቻ ለመፍጠር፣ ከተሳካም የሃይማኖት ግጭት ለመቀስቀስ በተለያዩ አቅጣጫዎች በጣም አደገኛና መርዘኛ የሆነ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከፍቷል፡፡ “እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል” በሚል አህያዊ ብሂል ላይ የተመሠረተውን ይህንን እርኩስ ዘመቻ፣ ለዚህች አገር ህዝቦች ሰላምና ፍቅርን የሚመኝ ኢትዮጵያዊ በሙሉ አጥብቆ ሊዋጋው ይገባል፡፡ …
እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ያነሳናቸውና ተገቢ ምላሽ ያገኙ ዘንድ በሰላማዊ መንገድ የምንታገልላቸው ጥያቄዎች፣ መንግሥት በሃይማኖታችን ላይ የቃጣውን ዓይን ያወጣ ጣልቃ ገብነት መነሻ አድርገው የተነሱ እንጂ ድንገት ከመሬት ላይ የበቀሉ አይደሉም፡፡ [ከቶውኑ ድንገት ከመሬት ላይ የበቀሉ ጥያቄዎች የድፍን አገሪቱን ሙስሊሞች በአንድ መንፈስ በጋራ ሊያነቃንቁ ይቻላቸዋልን? ይህ የማይመስል ነገር ነው፡፡]
… መንግሥት ከ1987 አጋማሽ አንስቶ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ላይ ያሻውን ሰው ሲሾም እና ተቋሙን በካድሬዎቹ ሲያሽከረከር እየታዘብን በዝምታ አሳልፈናል፡፡ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለህዝበ ሙስሊሙ ምንም የረባ መንፈሳዊም ሆነ ማኅበራዊ አገልግሎት የመስጠት ብቃት እንደሌለው፣ በህዝበ ሙስሊሙ ስም በተቋሙ የሚንቀሳቀስ የህዝብ እና የአገር ሀብት በአሳፋሪ ሁኔታ በግለሰቦች ሲመዘበር፣ በሐጅና ዑምራ ጉዞ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ ከፍተኛ ብዝበዛ (ዝርፊያ) ሲፈፀም፣ የአርባ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ተቋም የሠፈር ዕድር እንኳ ለመምራት በማይበቁ መደዴ ግለሰቦች ሲመራ … ልባችን በሐዘን እየደማም ብዙ ዓመታትን በዝምታ አሳልፈናል፡፡ ይህ ሁሉ ሲኾን፣ ከዚህ የተቋማችን አሳዛኝ ገፅታ ጀርባ የኢሕአዴግ እጅ እንዳለ ሳናውቅ ቀርተን አልነበረም፡፡ … መንግሥትን “በቃህ!” ለማለት የተገደድንበት ሁኔታ የተከሰተው ኢሕአዴግ ይህንኑ ተቋማችንን መሣርያ በማድረግ በአዲስ አስተምህሮ ሊያጠምቀን መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ ማድረግ ከጀመረበት ከሐምሌ 2003 ወዲህ ነው፡፡ [… ይህ በስፋት የሚታወቅ በመሆኑ እዚያ ላይ ሀተታ አላበዛም፡፡]
የሰላም ዘቦች እሥር እና ግልብ “ፀረ-አክራሪነት”
እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ባይኖረን ኖሮ፣ እንደ ተቋም አልባነታችን ከዓመታት በፊት ወደ አስከፊ የጥፋት መንገዶች ለመነዳት በተዳረግን ነበር፡፡ በእርግጥም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መሪ አልባ ሁነው በቆዩባቸው ባለፉት አሥራ ዘጠኝ ዓመታት የሃይማኖት ጽንፈኝነት እና ነውጠኝነት ሊስፋፉ የሚችሉባቸው ብዙ ክፍተቶች ነበሩ፡፡ እነዚህን ክፍተቶች የደፈናቸው የነቀዘው መጅሊስ ሳይሆን፣ ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ውስጥ የበቀሉ በሳል አንጋፋና ወጣት የሃይማኖቱ ምሁራን ናቸው፡፡ በተለያዩ መድረኮች፣ እንዲሁም የትምህርትና መረጃ ማሰራጫ አውታሮች (መጻሕፍት፣ መጽሔት፣ ሲዲ፣ ወዘተ.) በሃይማኖት መቻቻልና ከሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች ጋር አብሮ በመኗኗር፣ የጎረቤትን ሐቅ (መብት) በመጠበቅ አስፈላጊነት፣ የጽንፈኛ አስተምህሮቶችን ጉድፍ እና አሉታዊ ገፅታ በማጋለጥ እነዚህ ወጣት እና አንጋፋ ምሁራን ሙስሊሙን ማኅበረሰብ በትጋት አስተምረዋል፡፡ እነዚህ አንጋፋና ወጣት የሃይማኖቱ ምሁራን በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 27 የተደነገገውን “የሃይማኖት፣ የእምነትና የአስተሳሰብ ነፃነት” በመጠቀም ለኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ህይወት መበልፀግ፣ እንዲሁም ህዝበ ሙስሊሙ ከሌሎች ሃይማኖት ተከታዮች ጋር በሰላም፣ በፍቅር እና በመከባበር የመኖር እሴትን በጥልቀት ተገንዝቦ ይህን እሴቱን እንዲንከባከብ በማስተማር ባይተጉ ኖሮ ኢትዮጵያዊው ሙስሊም በተለያዩ ኃይሎች ተፅዕኖ ውሉ በማይታወቅ አቅጣጫ የዕውር ድንብር በተጓዘና በተጋለበ ነበር፡፡ በእርግጥም የኢሕአዴግ መንግሥት ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ በኩል የሃይማኖት ጽንፈኝነት የሚያሰጋው ቢሆን ኖሮ፣ በኢትዮጵያዊው ሙስሊም ማኅበረሰብ ውስጥ የሰላምንና የአብሮ መኖር እሴቶችን ያሰረፁትን እነዚህን ድንቅ የማኅበረሰቡ አባላት (የሃይማኖት ምሁራን) በአጋርነት በማሰለፍ ስጋቱን በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስወግድ ውጤታማ ሥራ መሥራት በቻለ ነበር፡፡
የሁከት ናፍቆት
እጅግ የሚያሳዝነውና በአሁኑ ወቅት በገሃድ የሚታየው ግን፣ የኢሕአዴግ መንግሥት ፍላጎት በአገሪቱ ላይ ሰላምንና የህዝቦች አንድነትን ማስፈን አለመሆኑ ነው፡፡ ኢሕአዴግ የአገር ሰላምን እና የህዝቦችን በሰላም አብሮ የመኖር ትሩፋት በጽናት ሲሰብኩ የኖሩ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ወጣትና አንጋፋ የሃይማኖት ምሁራንን ዘብጥያ የወረወረው ከሰላም ፍፁም ተቃራኒ የሆነ እኩይ አጀንዳ በማንገቡ መሆኑ አሁን ግልፅ ሆኗል፡፡ ፍላጎቱ ሰላም ባለመሆኑም ነው፣ አልሳካልህ ያለውን ጽንፈኝነት ለመፈብረክ ነጋ ጠባ የሚደክመው፡፡ የህዝቦች ተፈቃቅሮ እና ተከባብሮ መኖር አልዋጥልህ ቢለው ነው ጽንፈኝነትን እና ሽብርን በዶኩመንታሪ ፊልም ለማቀናበር አለቅጥ ደፋ ቀና የሚለው፡፡ … የህዝቦች በሰላም መኖር፣ ሰላም ቢነሳው ነው በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና ክርስቲያኖች መካከል ጥላቻን ለመዝራት፣ ሁከትና የእርስ በርስ ግጭትን ለመጋበዝ ያለ አንዳች ኃፍረት በዘመቻ መልክ መንቀሳቀስ የጀመረው፡፡ …
… ዛሬ አመሻሽ ላይ አንድ ወንድሜ “ኢትዮጵያን ዳያስፖራ” የተሰኘ አሜሪካ ውስጥ የሚሰራጭ የራዲዮ ጣቢያ በቅርቡ ካሰራጫቸው ዝግጅቶች የቀዳቸውን የተወሰኑ ድምፆች ልኮልኝ ሳደምጥ የተረዳሁት ይህንን እና ይህንን ሐቅ ብቻ ነው፡፡ የኢሕአዴግ መንግሥት እና አጫፋሪዎቹ ለዚህች አገር እና ለህዝቧ ምን እየደገሱለት እንደሆነ ማሰብ በጣም ይዘገንናል፡፡ ምን ያህል አቅላቸውን ቢስቱ ይህንን ለማድረግ እንደወሰኑ ለእኔ ፈጽሞ ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ምን ያህል አዕምሯቸው ማሰብ ቢሳነው ነው የዚህ ተግባራቸውን ውጤት አስከፊነት ለመገመት ያልቻሉት ለሚለው ጥያቄዬ ፈጽሞ መልስ ላገኝለት አልቻልኩም፡፡ ሃይማኖትን በመሰለ ለሰዎች ስሜት እጅግ ቅርብ በሆነ ጉዳይ ላይ እንዲህ ያለ መርዘኛ የጥላቻ እና የግጭት ቅስቀሳ ያውም በራዲዮና በድረ ገፅ ማሰራጨት እንደምን ለአገር ሰላም አሳቢ ሊያሰኝ እንደሚችል አላውቅም፡፡ ከዓመታት በፊት በአንድ የአገሪቱ አካባቢ በተፈጠረ ሃይማኖት ነክ ሁከት ላይ ‹‹እንዲህ እና እንዲያ አደረጉን›› የሚሉ የሰዎችን ስሜት በመጥፎ መልኩ የሚኮረኩሩ መልዕክቶችን ማሰራጨት እውን ለአገር ሰላም ከማሰብ የመነጨ ነውን? … የመንግሥት ሥልጣን ከስኳር እንደሚጥም ቢያንስ መገመት አያቅተኝም፡፡ ፖለቲከኞች ከጠላት ጋር የሚደረግ ጦርነትን ለሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያነት እንደሚጠቀሙባትም አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን በሥልጣን ላይ ለመቆየት ሲባል ለረዥም ጊዜ ሊገዙት የሚሹትን የራስን አገር ህዝብ በሃይማኖት ለማጋጨት ታጥቆ መነሳት፣ ፖለቲካዊ ጥበብ ሳይሆን “እኔ ከሞትሁ ሰርዶ አይብቀል” ያለችውን አህያን መሆን ይመስለኛል፡፡ አላህ ከአህያነት ይጠብቀን!!
ኢሕአዴግ ህዝበ ክርስቲያኑን ከሙስሊሙ ጋር ለማጋጨት ታጥቆ በተነሳበት በአሁኑ ወቅት ከወደ አሜሪካ እንዲህ ያለ መርዘኛ ፕሮፖጋንዳ በራዲዮና በድረ ገፅ መሰራጨቱ፣ አገራችን እና ህዝቧ ምን ያህል ከባድ አደጋ እንደተደቀነባቸው በግልፅ ያሳያል፡፡ ምንም እንኳ እንዲከሰት የሚናፍቁት የህዝቦች የእርስ በርስ ግጭት ቢከሰት (በአክራሪ እና በጽንፈኛ ዲስኩራቸው) ሙስሊሙን ተጠያቂ ለማድረግ እንደሚንደረደሩ ግልፅ ቢሆንም፣ አደጋው ግን በሙስሊሙ ላይ ብቻ የተደቀነ አለመሆኑን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ክርስቲያኑም ጭምር በውል ሊገነዘበው ይገባል፡፡ በዚህ ግንዛቤ ላይ በመመሥረትም፣ ይህን በእኛ በኢትዮጵያውያን ላይ የተደቀነ ወቅታዊ አደጋ ወይም ፈተና፣ የረዥም ዘመናት አብሮ መኖር ባስተማረን ትዕግስት፣ ብልሀትና ጥበብ በአሸናፊነት ለመወጣት የየድርሻችንን ኃላፊነት እንወጣ እላለሁ፡፡ ይህንንም ለማድረግ የኃያሉን ፈጣሪያችንን እገዛ እማፀናለሁ፡፡ …
ላለፉት ሁለት ዓመታት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም፣ በሚሊዮኖች ከሚቆጠሩ የእምነት ወንድምና እህቶቼ ጋር ለሃይማኖት ነፃነቴ መከበር በሰላማዊ መንገድ እየታገልኩኝ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ነገር ግን የሃይማኖት ነፃነቴ መከበር ከሚያስጨንቀኝ ባላነሰ፣ ምናልባትም በበለጠ የኢሕአዴግ መንግሥት ህዝበ ክርስቲያኑን ከሙስሊሙ የማጋጨት ዕኩይ ሤራ ያስጨንቀኛል፡፡ እናም በአላህ ፈቃድ እና እገዛ ይህንን ዕኩይ ሤራ እስከ መጨረሻው አምርሬ እታገላለሁ፡፡ ለእኔ ከዚህ በላይ ኢትዮጵያዊነት የለም፡፡
… ቅኑን መንገድ በተከተሉ ሁሉ ላይ ሰላም ይስፈን፡፡ የዓለማት ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ከክፋት ኃይሎች ክፋት ይጠብቅልን፡፡ አሚን፡፡
_______________________
*መልዕክቴን ከተጋራችሁት፣ በሰሌዳችሁ ላይ ለሌሎች ብታጋሩት ደስ ይለኛል፡፡ አመሰግናለሁ፡፡

Tuesday, August 20, 2013

ከእሁድ እስከ እሁድ ( የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች ከተለያዩ ምንጮች)

ነዋሪዎች በውሃ እጦት ተሰቃየን አሉ
 
በሳምንት አንድ ቀን ውሃ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች፣ በውሃ እጦት አካባቢያቸውን በመጥፎ ጠረን የሚበክሉ የኮንዶሚኒየም መኖሪያዎች፣ ለተደጋጋሚ አቤቱታ ምላሽ ሳያገኙ በርካታ ወራት እየተቆጠሩ የሚማረሩ ነዋሪዎች የአዲስ አበባ የዘመኑ ገጽታ ሆነዋል፡፡
 
በቂ ውሃ ስለሌለ በራሽን ለማከፋፈል እየሞከረ መሆኑን የሚልፀው የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በበኩሉ፤ የኤሌክትሪክ መቆራረጥና የአንዳንድ ሰራተኞች እንዝህላልነት፣ ለመንገድ ግንባታ የሚቆፈሩ ቧንቧዎች እንዲሁም በከንቱ የሚባክን ውሃ መብዛቱ የውሃ እጥረትን እንዳባባሱ ይናገራል፡፡
 
የአገሪቱ እንዲሁም የአህጉሪቱ መዲና በሆነችው ከተማ፣ ለዚያውም በሰለጠነ ዘመን በርካታ ነዋሪዎች የዝናብ ውሃን ደቅኖ ለማጠራቀም ሲሯሯጡና በጀሪካን ተሸክመው ውሃ ሲያመላልሱና የፎቅ ደረጃዎችን ለመውጣት ሲውተረተሩ ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡
 
በገርጂ፣ አየር ጤና፣ ጀሞ፣ እንቁላል ፋብሪካ፣ አዲሱ ገበያ፣ እንዲሁም በየአቅጣጫው የተገነቡ ኮንዶሚኒየሞችን ጨምሮ በርካታ የከተማዋ ሰፈሮች፣ በውሃ እጥረት የተቸገሩ ነዋሪዎች “አወይ ስልጣኔ” በማለት መላ እንደጠፋባቸው ይገልፃሉ፡፡
 
የፉሪ አካባቢ ነዋሪ ወ/ሮ አልማዝ ሞገስ፣ ቀድሞም ቢሆን በሁለት በሶስት ቀን ነበር ውሃ የምናገኘው ይላሉ፡፡ አሁን ግን ብሶበታል፣ ይሄውና በሰፈሩ ውሃ ካገኘን ከሳምንት በላይ ሆኖናል የሚሉት ወ/ሮ አልማዝ፤ ውሃ የምናገኘው ጀሪካን ተሸክመን ሰፈር አቆራርጠን ነው ብለዋል፡፡ ብዙ ጊዜ አቤቱታ አቅርበን ደከመን፤ ምንም መልስ አላገኘንም ብለዋል – ወ/ሮ አልማዝ፡፡
 
በጀሞ ቁጥር 1 መኖር ከጀመረች ሁለት አመት የሆናት ሰናይት ፈቃደ በበኩሏ፣ የውሃ ችግር የጠናብኝ ዛሬና ትላንት አይደለም፣ በጣም ቆይቷል ትላለች፡፡ ድሮ ድሮ ሌሊት ላይ ብቅ ይል የነበረው ውሃ፤ ዛሬ ሽታውም የለም የምትለው ሰናይት፣ የኮንዶሚኒየም ቤት ያለ ውሃ የስቃይ ቤት ማለት ነው ብላለች፡፡ የመጀመሪያ ፎቅ ነዋሪዎች የዝናብ ውሃ ደቅነው ለማጠራቀም ይሞክራሉ፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ፎቅ ግን አይሞከርም፡፡ ቧንቧ በየቤታችን አለ፤ ውሃ የምናመጣው ግን እንደ ጥንቱ የገጠር አኗኗር ነው የምትለው ሰናይት፤ ለውሃና ፍሳሽ አመልክተናል፡፡ ውሃውን ወደ ላይ ለመሳብ የፓምፕ ሃይል ስለሚያስፈልግ ነው ይሉናል፤ ይህንን እንደ በቂ ምላሽ ይቆጥሩታል በማለት ግራ መጋባቷን ትገልፃለች፡፡
 
ጀሞ ብቻ አይደለም፡፡ የጐሮ ነዋሪ ናርዶስ አስማረ አንድ ቀን ውሃ ከመጣ ለሁለትና ለሶስት ቀን ይጠፋል፤ ቅዳሜና እሁድ ውሃ ያገኘንበት ጊዜ የለም ትላለች፡፡ በየሳምንቱ አቤቱታ ስናቀርብ የምናገኘው ምላሽ ሁልጊዜ ተመሳሳይ ነው የምትለው ናርዶስ፤ አሁን ይስተካከላል ይሉናል፤ ግን ተስተካክሎ አያውቅም ትላለች፡፡
ውሃ የሚጠፋበትን ቀን ዘርዝሮ ከመናገር ይልቅ ውሃ የሚመጣበትን ቀን መናገር ይቀላል የሚለው የአዲሱ ገበያ ነዋሪ ልዩነህ አያሌው፤ ውሃ ይግባልን ብንል ይሻላል፤ በሳምንት አንዴ ውሃ ከመጣ ፌሽታ ነው፤ ብርቅ ይሆንብናል ሲል ይናገራል፡፡
አዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ወ/ሮ እፀገነት ተስፋ ምላሽ ሲሰጡ፤ በአዲስ አበባ የውሃ ችግር አለ በማለት ነው የሚጀምሩት፡፡ ዋናው ምክንያት የውሃ እጥረት ነው የሚሉት ወ/ሮ እፀገነት፤ ከነእጥረቱም ቢሆን ውሃውን ለህብረተሰቡ ለማድረስ ደግሞ የተለያዩ መሰናክሎች እንደሚገጥሙ ገልፀዋል፡፡ ኤሌክትሪክ ሲቋረጥ ከፍታ ቦታ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች በፓምፕ ውሃ ማድረስ አንችልም ይላሉ፡፡
 
ሌላው ችግር በራሳችን ሰራተኞች የሚፈጠር ነው የሚሉት ሃላፊዋ፣ የውሃ ቧንቧ ተበላሽቷል ተብሎ ሲነገራቸው አንዳንድ ሰራተኞች ብልሽቱን እንደመጠገን ውሃውን ዘግተውት ይመጣሉ ብለዋል፡፡ በመንገድ ስራና የተለያዩ ግንባታዎች የውሃ ቧንቧ እንደሚሰበር ሲያስረዱ፣ ለምሳሌ በሃያ ሁለት አካባቢ፣ በመንገድ ግንባታ ምክንያት ዋናው የውሃ ቧንቧ በመቋረጡ አሁን በተዘረጋ ጊዜያዊ ቧንቧ የምናቀርበው ውሃ በአስር እጥፍ ያነሰ ነው ብለዋል፡፡ በዚያ ላይ ለከተማዋ ከሚቀርበው ጠቅላላ የውሃ መጠን ውስጥ ከአንድ ሦስተኛ የሚበልጠው በከንቱ ይባክናል ብለዋል ሃላፊዋ፡፡ (ምንጭ፤ አዲስ አድማስ)
የኢህአዴግ አባላት ክርስቶፎር ስሚዝ በሚያረቁት ህግ ላይ የተቃውሞ ፊርማ ማሰባሰብ ጀመሩ
ከደጋፊዎቹ የመረጃ ለውውጥ ለመረዳት እንደተቻለው ኮንግረስ ማን ክሪስ ስሚዝ በቅርቡ በኢትዮጵያ ዙሪያ የግንቦት 7 መሪ ዶ/ር ብርሀኑ ነጋን፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ፣ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሀላፊ ሚ/ር ያማማቶ እና ሌሎችንም ታዋቂ ሰዎች በመጋበዝ በኢትዮጵያ ዙሪያ የተለያዩ ሀሳቦችን ማሰባሰባቸው ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶችን እንድታከብርና ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን እንድትገነባ፣ ኮንግረሱ የህግ ረቂቅ እንደሚያዘጋጅ ሚ/ር ስሚዝ ገልጸዋል።
 
የህጉን መረቀቅ የተቃወሙት የኢህአዴግ ደጋፊዎች  ለሚ/ር ስሚዝ ደብዳቤ መላክ ጀምረዋል። በደብዳቤው ላይ ሚ/ር ስሚዝ በኢትዮጵያ መንግስት አሻባሪ የተባሉትን ሰዎች ለውውይት መጋበዛቸውን አውግዘዋል። በኢትዮጵያ ላይ የሚረቀቀው ህግ የአሜሪካንና የኢትዮጵያን ግንኙነት የሚያበላሽ መሆኑን፣ ኢትዮጵያ በውጭ ተጽኖ አቋሟን የማትቀይር መሆኗንና ሚ/ር ስሚዝም ኢትዮጵያን ለመደገፍ የሚያስችል የህግ ረቂቅ እንዲያዘጋጁ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች እየፈረሙ በሚልኩት ደብዳቤ ላይ ተመልክቷል።
 
አስቸኳይ በሚል ርእስ ለኢህአዴግ አባላት በተላከው የኢሜል መልዕክት ላይ ህጉ የሚረቀቅ ከሆነ በኢትዮጵያ ላይ ከባድ ተጽኖ እንደሚያስከትል ተመልክቷል።
 
chris smith
ህዳሴ ካውንስል የሚባለው የኢህአዴግ አባላትንና ደጋፊዎችን የያዘው ቡድን የድጋፍ ፊርማ የማሰባሰብ ተልእኮ የተሰጠው ሲሆን፣ በአጠቃላይ እስከ 10 ሺ የሚደረሱ ፊርማዎችን አሰባስቦ የመላክ እቅድ ተይዟል።
 
የ1997 ዓም ምርጫን ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ በተመሳሳይ መንገድ የተረቀቀው ህግ ዲኤል ኤ ፓይፐር በተባለው ተቋም ድለላ እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወቃል።(ምንጭ፡- ኢሳት)
በሙስሊም ማኀበረሰብ አካላት ላይ መንግሥት እየወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ ሶስት ፓርቲዎች አወገዙ
የመብት ጥያቄ ያነሱ የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አካላት ላይ መንግሥት እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ አጥብቀው እንደሚቃወሙት ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሰሞኑን ባወጡት መግለጫ አስታወቁ።
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፣ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ እና የመላ ኦሮሞ ሕዝብ ድርጅት ነሐሴ 5 እና 6 ቀን 2005 በተናጠል ባወጡት መግለጫዎች መንግሥት አለመግባባቱን ለመፍታት እየተከተለ ያለውን የኃይል እርምጃ ተገቢ አለመሆኑን ገልፀዋል።
 
muslim ethiopiansጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ጋር ሰሞኑን ባደረጉት ቃለምልልስ ‘‘ጽንፈኞች’’ ያሏቸውን የመብት ጥያቄ ያነሱ የሙስሊም ማኀበረሰብ አካላት እያደረጉ ያሉት እንቅስቃሴ ፀረ-ሕገመንግስታዊ መሆኑን አመልክተዋል።
 
‘‘የሃይማኖት መንግስት እንመሰርታለን፣ የሸሪዓ ሥርዓት እናሰፍናለን’’ የሚል አቋም እንደሚያራምዱ የጠቀሱት ጠ/ሚኒስትሩ መንግስት ሃይማኖታዊ ተልዕኮ ያላቸው መስሏቸው ከፅንፈኞች ጋር የሚተባበሩ ተከታዮችን በጅምላ ላለመጉዳት በትግስት ሁኔታውን ሲከታተልና የማሳመን ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
 
ጽንፈኞችን ከሌሎች የእምነቱ ተከታዮች ለመለየት የተደረገው ጥረት የተሳካ እንደነበርና መንግስት ሰሞኑን የወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ከጽንፈኞች ጋር ተቀናጅተው የአገሪቷን ሠላም ለማወክ ይንቀሳቀሳሉ ያሏቸውን የተቃዋሚ ፓርቲዎችንም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አስጠንቅቀዋል። (ምንጭ፡- ሰንደቅ)
የዋጋ ግሽበት በድጋሚ በማገርሸት ላይ ነው
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚን ላለፉት በርካታ ዓመታት እየፈተነ የሚገኘው የዋጋ ግሽበት ለዓመታት ከነበረበት ባለሁለት አኃዝ ምጣኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ነጠላ አኃዝ ከሦስት ወራት በፊት ቢወርድም፣ በሐምሌ ወር መጨረሻ ደግሞ በድጋሚ በማሻቀቡ ስምንት በመቶ ደርሷል፡፡
 
መንግሥት በወሰደው ከፍተኛ የገንዘብ አቅርቦት ቁጥጥር፣ ጥንቃቄ የተሞላበት የበጀት አጠቃቀምና መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችን ከውጭ በማስገባት ማከፋፈል ዕርምጃዎች በአገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ፈተና የሆነውን የዋጋ ግሽበት ከሁለት ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ነጠላ አኃዝ ማለትም ወደ 7.6 በመቶ ማውረድ አስችሎታል፡፡
 
marketጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የዋጋ ግሽበቱ መውረዱን አስመልክቶ መንግሥታቸው የወሰዳቸው ጥብቅ ቁጥጥሮች ውጤት ማምጣታቸውን በተደጋጋሚ በመግለጽ፣ በቀጣይም በበለጠ ቁጥጥሩን በመቀጠል የዋጋ ግሽበት ምጣኔው እንዳያንሰራራ መንግሥታቸው እንደሚሠራ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
 
የዋጋ ግሽበቱ ወደ ነጠላ አኃዝ ከወረደበት ከመጋቢት ወር ቀጥሎ ባሉት ወራት ማሽቆልቆሉን የቀጠለው እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ ድረስ ብቻ ነው፡፡ በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ አጠቃላይ የአገሪቱ ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት ምጣኔ 6.3 በመቶ የደረሰ ቢሆንም፣ በቀጣዮቹ ወራት ግን ከቁጥጥር ማምለጥ የጀመረ ይመስላል፡፡
 
አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ በሰኔ ወር በፍጥነት ማሻቀቡን በመቀጠል በወሩ መጨረሻ አጠቃላይ ዓመታዊ ግሽበቱ 7.4 በመቶ ሲደርስ፣ ይህም የግሽበቱን ግስጋሴ ለመግታት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ውጤታማነት እምብዛም መሆኑን ያሳያል፡፡ በመሆኑም በሐምሌ ወር አጠቃላይ ዓመታዊ ግሽበቱ ግስጋሴውን በመቀጠል 8.0 በመቶ መድረሱን ማዕከላዊ የስታትስቲክስ ባለሥልጣን በየወሩ ይፋ የሚያደርገው የአገር አቀፍ የገበያ ዋጋና የዋጋ ግሽበት መረጃ ያስረዳል፡፡
 
ከዚህ ቀደም 45 በመቶ ደርሶ ለነበረው አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ዋነኛ ምክንያት በምግብ ነክ ምርቶች ላይ የሚታይ የዋጋ ጭማሪ ነበር፡፡ ይህንንም አስመልክቶ በቅርቡ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት መነሻ ዋነኛው በምግብ ነክ ምርቶች ላይ የሚታየው የዋጋ ንረት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
 
ይህንን የዋጋ ግሽበት ያመጣው የምግብ ነክ አጠቃላይ ፍላጐትና አቅርቦት አለመጣጣም መሆኑን በመግለጽ፣ መፍትሔውም የግብርና ዘርፍ ምርታማነትን ማሳደግ መሆኑን ጠቁመው ነበር፡፡
 
ማዕከላዊ የስታስቲክስ ባለሥልጣን መረጃዎችም የቀድሞዎቹ ዓመታት ከፍተኛ የግሽበት መንስዔ የምግብ ነክ ዋጋ መናር መሆኑን ያሳያሉ፡፡ አሁን እየታየ ላለው የዋጋ ግሽበት ዋነኛ ምክንያት በመሆን የተጠቀሰው ግን ምግብ ነክ ባልሆኑ ምርቶች ላይ የሚታይ የዋጋ ንረት ነው፡፡
 
በተለይም አልባሳትና ጫማዎች፣ የቤት ቁሳቁሶችና የማስጌጫ ዕቃዎች ላይ የታየው የዋጋ ግሽበት ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ለታየው ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት ማሻቀብ ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን የባለሥልጣኑ ትንተና ያስረዳል፡፡ (ምንጭ፡- ሪፖርተር)
የ6 አመቷን ህፃን የደፈሩት የ60 አመት አዛውንት በ14 አመት እስራት ተቀጡ
*ዐቃቤ ህግ ቅጣቱ አንሷል ሲል በውሳኔው ላይ ቅሬታ አለኝ ብሏል
የ6 አመቷን ህፃን አታለው ደፍረዋታል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ህግ ክስ የመሰረተባቸው የ60 አመቱ አዛውንት አቶ አምደላ ነአምሳ ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ፍርድ ቤት በ14 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ሲል የቅጣት ውሳኔውን አስተላለፈ። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ዐቃቤ ህግ ግን በቅጣት ውሳኔው ላይ ቅሬታ እንዳለው በመግለፅ ለፍርድ ቤቱ ደብዳቤ ፅፏል።
 
በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ግለሰቡን ጥፋተኛ ያላቸው የዐቃቤ ህግን የክስ መዝገብ መርምሮና የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን መርምሮ ነው። ዐቃቤ ህግ በክሱ እንዳመለከተው፤ ተከሳሽ ለአቅመ ሔዋን ካልደረሰች ልጅ ጋር የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ለመፈፀም አስበው በሐምሌ 8 ቀን 2004 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 7 ሰዓት ሲሆን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 14/15 ክልል ልዩ ቦታው ገብስ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ስሟን የማንገልጽላችሁን የ6 አመቷን ህፃን አታለውና አግባብተው ወደመኖሪያ ቤታቸው በማስገባት፤ አልጋ ላይ እንድትተኛ አድርገው የመድፈር ወንጀል ፈፅመውበታል ሲል ይከሳል።
 
Injusticeየጉዳዩን ግራና ቀኝ ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎትም ተከሳሹ ዐቃቤ ህግ ያቀረባቸውን የሰውና የሠነድ ማስረጃዎች በአግባቡ ማስተባበል አልቻሉም ሲል ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
 
ፍ/ቤቱ ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2005 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፤ ተከሳሹ ጥፋተኛ በሆኑበት ወንጀል ላይ ቅጣት ያስተላለፈ ሲሆን፤ የወንጀሉን ደረጃ ከባድ በማለት የህፃኗን ዕድሜ እንደምክንያት ያቀረበው ፍርድ ቤቱ ከ20 አመት እስከ 22 አመት ሊያስቀጣ እንደሚችል ይጠቅሳል። ዐቃቤ ህግ ምንም አይነት የወንጀል ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን፤ ተከሳሹ በበኩላቸው የቤተሰብ አስተዳዳሪና ምንም አይነት የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው መሆናቸውን መጥቀሳቸው የቅጣት እርከኑን ዝቅ እንዳደረገላቸው ለመረዳት ተችሏል። በዚህም የቅጣት መነሻው 22 አመት ላይ እንዲያርፍ ሆኗል።
 
የግራቀኙን አስተያየት ያደመጠው ፍርድ ቤቱም ጉዳዩን መርምሮ የ60 አመት አዛውንቱን ጥፋተኛ በተባሉበት ወንጀል በ14 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራትና ለአምስት አመታት በሚዘልቅ ከመምረጥ መመረጥ ህዝባዊ መብታቸው እንዲታገዱ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ደስተኛ ያልሆነው የክፍለ ከተማው ፍትህ ጽ/ቤት ዐቃቤ ህግ ቅሬታውን ጠቅሶ ደብዳቤ መፃፉንና ቅጣቱ መሻሻል እንደሚገባው ማመልከቱን ለማወቅ ተችሏል።(ምንጭ፡-ሰንደቅ)
አንድነት ፓርቲ የማተሚያ ማሽን ለመግዛት ጨረታ አወጣ
በሶስት ቋንቋዎች የፓርቲው ልሳኖች ይዘጋጃሉ
andinet -UDJአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የራሱን ማተሚያ ቤት ለመክፈት ባለፉት ሶስት ወራት በአገር ውስጥና በውጭ ባከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ ጥረት በቂ ገንዘብ ማግኘቱን በመግለጽ የማተሚያ ማሽን የግዢ ጨረታ አወጣ።
 
በፓርቲው ሲዘጋጅ የነበረው “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ በማተሚያ ቤት እጦት እንደተቋረጠ የገለፁት የፓርቲው አመራር አባል፣ ማተሚያ ማሽን ተገዝቶ ስራ ሲጀምር “ፍኖተ ነፃነት”ም ለአንባቢያን ትደርሳለች ብለዋል፡፡ ከጋዜጣው በተጨማሪ በትግርኛና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች የሚዘጋጁ ጋዜጦችና ሌሎች ህትመቶችንም እንደሚሰራ ፓርቲው ጠቅሶ፣ ፓርቲዎች በንግድ ስራ ውስጥ መግባት ስለማይችሉ ለግል ጋዜጦች የህትመት አገልግሎት አንሰጥም ብሏል።
 
የሀገር ውስጥ አቅራቢዎች በጋዜጣ ላይ በወጣ የጨረታ ማስታወቂያ በቀረበው ዝርዝር መረጃ መሠረት መሳተፍ እንደሚችሉ የተናጋሩት የፓርቲው ተወካይ፤ ማሽኑን ከሀገር ውስጥ መግዛት ያስፈለገበት ምክንያት ከውጭ ተገዝቶ ሲገባ ያለውን ረጅም ጊዜ ለመቀነስና ማሽኑን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመግዛት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡(ምንጭ፤ አዲስ አድማስ)
ከአንድ ሥጋ ቤት በተመሣሣይ ወቅት ሥጋ ገዝተው የተመገቡ ነዋሪዎች በህመም እየተሰቃዩ ነው
ከአንድ ሥጋ ቤት በተመሳሳይ ወቅት ሥጋ ገዝተው የተመገቡ የልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች በህመም እየተሰቃዩ ነው። ነዋሪዎቹ ከቆየ ደንበኛቸው ሥጋ ገዝተው ለልደት፣ ለሽምግልና፣ ለሰርግ የተጠቀሙበት ሁኔታ ቢኖርም ታዳሚዎቹም ሆነ ባለቤቶቹ በሙሉ ለህመም መዳረጋቸውን ገልፀውልናል።
 
የልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወጣት ፀሐይ ሙላቱ ቤተሰቧ ለነበረበት የሽምግልና ፕሮግራም ከሥጋ ቤቱ 25 ኪሎ ሥጋ የገዙ መሆናቸውን ገልፃ ተጠርተው የነበሩት ወደ 60 የሚጠጉት ታዳሚዎች በዕለቱ ከምሽትና ከሌሊት ጀምሮ ለከባድ ህመም የተጋለጡ መሆናቸውን ገልፃልናለች። በአመጋገብ በኩልም የተገዛውን የከብት ሥጋ ሳይሆን ዶሮ ብቻ የተመገቡ ሰዎች ግን ያልታመሙ መሆናቸው ወጣት ፀሐይ ገልፃለች።
 
meat sellerበተመሳሳይ መልኩ አቶ ተሾመ ሙላቱ የተባሉ በልደታ ክፍለከተማ የቀድሞው ወረዳ 5 የቤት ቁጥር 048 ነዋሪ ከሥጋ ቤቱ የተገዛውን ምግብ ተመግበው ለህመም መዳረጋቸውን ገልፀውልናል። ጌጃ ሰፈር የሚባል ነዋሪዎችም ከዚያው ተመሳሳይ ሥጋ ቤት ገዝተው ለልደት ዝግጅት የተጠቀሙ ነዋሪዎችም ለከፍተኛ ህመም የተዳረጉ መሆናቸውን ገልጸውልናል። የህመሙን ሥሜት በተመለከተ የገለፁልን ታማሚዎቹ በዋነኝነት ማንቀጥቀጥ፣ ማስመለስ፣ ተቅማጥ፣ የአቅም ማነስ፣ ቁርጠት የራስ ምታትና ለመግለፅ የሚያስቸግር የህመም ስሜት የፈጠረባቸው መሆኑን ገልፀውልናል።
 
በልደታ ተክለ ሃይማኖት ክሊኒክ በተደረገላቸው ምርመራም ውጤቱ የምግብ መበከል የሚያሳይ መሆኑን የተገለፀ መሆኑን ነዋሪዎቹ ገልፀውልናል። ነዋሪዎቹ ምግቡን ከተመገቡ ቀናት ቢቆጠሩም የህመሙ ስሜት ባለመጥፋቱ የምርመራቸውን ውጤት ይዘው ወደ ክስ የሚያመሩ መሆኑን ጨምረው አመልክተዋል። (ፎቶ ለማሳያ የቀረበ – ምንጭ፡-ሰንደቅ ጋዜጣ)
መንግስት የሼህ ኑሩ ይማምን ግድያና የሙስሊሙን ተቃውሞ ከአንድነት ፓርቲና ኢሳት ጋር ሊያያዝ ሞከረ
መንግስት ትናንት ሼህ ኑሩን ማን ገደላቸው በሚል ርእስ በኢቲቪ በለቀቀው ዘጋቢ ፊልም ላይ አንድነት ፓርቲ የሼህ ኑሩን ግድያ ደግፎ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲጠራ ማድረጉን የግንቦት7 ልሳን የሆነው ኢሳት ቴሌቪዥንም አሸባሪዎችን ” አይዞአችሁ በርቱ” እያለ ድጋፍ እንደሰጣቸው አንድ ግለሰብን በማናገር አቅርቧል
 
በዘጋቢ ፊልሙ ላይ ሶስት ተጠርጣሪ ገዳዮች ቀርበው የሚናገሩ ሲሆን፣ ፊልሙ  ከአንዱ ክፍል ተቆርጦ ከሌላው ክፍል እየተገጣጠመ የተቀናበረና ገዳይ የተባሉትም ከፉኛ የተደበደቡ በሚመስል መልኩ ለመናገር ሲቸገሩ ይታያል።
 
nuruአንድነት ፓርቲ   ”የሙስሊሞችን ጥያቄና የሼክ ኑሩን ግድያ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ማያያዝ ወንጀል ነው” በሚል ርዕስ  ባወጣው መግለጫ ዘጋቢ ፊልሙ መቅረቡን በጽኑ ተቃውሞአል።
 
ፓርቲው  ፊልሙ ” የገዥውን ፓርቲ ብፅእና ከመተረክም በላይ ጉልበተኝነትንና ፍረጃን ማእከል አድርጎ ከአኬልዳማ እና ከጃሀዳዊ ሀረካት የቀጠለ በፓርቲያችን እና በዜጎች ላይ የተቃጣ ህገ ወጥ የፕሮፓጋንዳ ስራ ነው” ብሎታል፡፡
 
የመንግስትነት ስልጣን የያዘ አካል ሀገራዊ ችግሮችን ለምን በዶክመንተሪ ፊልም ለመፍታትና ለማዳፈን እንደሚጥር እንቆቅልሽ ሆኖብናል የሚለው አንድነት ”  የሙስሊም  ጥያቄ በውይይትና በመግባባት ላይ ተመስርቶ ሊመለስ እንደሚገባና የሀይል እርምጃው መቆም እንዳለበት አሳስቧል።
 
ፊልሙ የኢህአዴግ የፍረጃ ፖለቲካ የተንፀባረቀበት፤ የተለየ ሀሳብና ጥያቄ ያቀረቡ ግለሰቦችንና ተቋማትን ማሸማቀቅ ብሎም የማጥፋት እኩይ ተግባር ማሳያ መሆኑንም ፓርቲው ገልጿል። አንድነት ፍርድ ቤት በተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ አድርጎ ውሳኔ ሳያሳልፍ በቴሌቪዥን ፍርድ መስጠቱ ገዢው ፓርቲ በህግ የማይገዛ አምባገነን ስለመሆኑ ግልጽ ማሳያ ሲሆን የፍትህ ስርዓቱ ልዕልናም በአንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ መገፈፉን ገልጿል።
 
የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት የፓርቲያችን አመራሮች በየግዜው የሚያደርጉትን ንግግሮች ሞያንና ንጹህ ህሊናን በሚያጎድፍ መልኩ እየቆራረጠ ሙሉ ትርጉሙን እንዳይዝ አድርጎ በማስተላለፍ እየፈጸመ ያለው አሳፋሪ ተግባር እንዲታረም፣  በሼህ ኑሩ ላይ የተፈጸመው ግድያ በየትኛውም አካል የተፈጸመ ቢሆንም ህገ ወጥ እና ኢሰባአዊ መሆኑን ፓርቲው ጠቅሷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ መንግስት በክርስቲያኑና በሙስሊሙ መካከል ልዩነት እንዲፈጠር እየሰራ ነው በማለት አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢሳት ገልጸዋል።
 
መንግስት በተለያዩ ቀበሌዎች ስብሰባዎችን እየጠራ ክርስቲያኑ ወገን በሙስሊሙ ጥያቄ ፍርሀት እንዲሰማው እያደረገ መሆኑን እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች ገልጸዋል።
 
መንግስት በአሁኑ ሰአት በመላ አገሪቱ የሀይማኖት ጉበኤ መክፈቱ ታውቋል። (ምንጭ፡-ኢሳት)
 
ጎልጉል  http://www.goolgule.com/

Monday, August 19, 2013

ለአቶ መለስ ሙት አመት መታሰቢያ የመንግስት ሰራተኞች በግድ እንዲገኙ ታዘዙ

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ሙት ዓመት በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል በልዩ ልዩ
ፕሮግራም ታስቦ እንደሚውል ለማወቅ የታቸለ ሲሆን፣ በዛሬው እለት ደግሞ  የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች ምሽትና ነገ  ሻማ በማብራት እንዲዘክሩት ታዘዋል።

አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች  ኢቲቪ አቶ መለስ ዜናዊ ከተናገራቸው ንግግሮች መካከል እያለ ሲያቀርብ መሰንበቱ እንዳሰለቻቸው ተናግረው፣ የፓርቲው ካድሬዎች በየመስሪያ ቤቱ የሚገኙ ሰራተኞች በግድ ተገኝተው እንዲዘክራቸው ማስፈራሪያ አዘል ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ነሃሴ 7 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስአበባ የመለስ ዜናዊ የአረንገዴ ልማት ማዕከል የመሰረት ድንጋይ  በአድዋ
ፓርክ የተጣለ ሲሆን የዚህን ፕሮጀክት ወጪ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳዳር ለመሸፈን ቃል መግባቱን መዘገባችን ይታወቃል።
ከሃያት ሆስፒታል ፊት ለፊት ማረፊያውን የሚያደርገው ማዕከሉ ከ100 ሄክታር በላይ ስፋት ሲኖረው ፥  በተለያዩ
የአረንጓዴ ዕፅዋት በመሸፈን በውስጥ ትላልቅ የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካትታል ተብሏል።

ባለፉት 15 ቀናት የአዲስአበባና የክልል ከተሞች ነዋሪዎች እና የመንግስት ሰራተኞች ዕለቱን ለማሰብ የችግኝ
ተከላ ማካሄዳቸው የሚታወስ ሲሆን መንግስትም በዚህ አጋጣሚ የመለስን ሌጋሲ ለማስቀጠል የገባውን ቃል ዳግም
ያደሰበት አጋጣሚ መሆኑን በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሲናገር ከርሟል።

አቶ መለስ ዜናዊ ታምመው በሕክምና ሲረዱ መቆየታቸው በከፍተኛ ሚስጢር ተይዞ ከቆየ በኃላ ነሃሴ 14 ቀን 2004
ዓ.ም መሞታቸውን መንግስት በይፋ ማመኑ የሚታወስ ነው፡፡

ገዢው ፓርቲ የአቶ መለስን ሞት ለፖለቲካ ድጋፍ ማስገኛ እየተጠቀመበት ነው በሚል ሲተች ቆይቷል። አቶ መለስ በኢኮኖሚው ዘርፍ መጠነኛ ለውጥ እንዳመጡ ቢነገርላቸውም፣ የኢትዮጵያን ህዝብ አንድነት በማዳከም፣ አገሪቱን ወደብ አልባ በማድረግና የሰብአዊ መብቶችን በመጣስ ይወቀሳሉ። በህይወት በነበሩበት ጊዜ በተለይም ኢፈርት የተባለ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ተቆጣጥሮ ዬያዘ የንግድ ኩባንያ እንዲቋቋም በማድረግ አንድን ብሄር ብቻ ለመጥቀም ተንቀሳቅሰዋል እየተባሉ በተቃዋሚዎቻቸው ይተቹ ነበር።

ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን የመለስን ፋውንዴሽን በበላይነት እየመሩ ይገኛሉ።

የነሱ ድፍረት የኛ ፍርሀት ነው

August 19, 2013
ሉሉ ከበደ

ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለት አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተገደሉ ነው።  በጽናት፤ በጀግንነትና በብልሀት እናም በመስዋእትነት የመብት ትግላቸውን ቀጥለዋል። በለተ – አውዳመት ኢድ አልፈጥርም የመስዋእትነት ደማቸውን፤ …ኢትዮያን የተቆጣጠራት የትግራይ ዱር አራዊት መንጋ አፍሷል። የሞቱትን ሁሉ አላህ በጀነት ነፍሳቸውን ያኑር ከማለት በቀር ምን ይባላል ?  ለሁሉም ወገኖቻችን ለቤተሰቦቻቸው፤ ለዘመዶቻቸው አላህ ጥናቱን ይስጥ እላለሁ። በከንቱ ለፈሰሰ ደማቸውም እሱ በማያልቅበት ስልጣኑ ፍርዱን ይስጥ። ሳይውል ሳያድር።…አላህ ሁ አክባር!!!

አፋር ለብቻው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። ኦሮሞ ለብቻው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ  ነው። ሶማሌ ለብቻው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። አማራው  እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። ደቡቡም ቤኔሻንጉሉም…ሁሉም! ድፍን ኢትዮጵያ….

የኢትዮጵያ ሳተላይት ሬዲዮና ቶሌቪዥን ከተመሰረተ ወዲህ፤ ይህ ህዝብ፤ አንዱ ባንዱ ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ መከራና ግፍ ሌላው ሳይሰማ ቀርቶ አይደለም፤ ከዳር እዳር ለአመጽ ያልተነሳው። አንዱ ላንዱ ለመድረስ ሳይፈግ ቀርቶ ሳይሆን፤ አንድ ሆኖ የጋራ ጠላቱን ህውሀትንና የየክልሉን ባንዳዎች አምርሮ የሚታገልበት ድፍረቱ የጠፋው ነው የሚመስለው።  ከየቋንቋው ተናጋሪ፤ ዛሬን ኖረን እንሙት ብለው በቆረጡ የጥቅም ምርኮኞች ወያኔ ያዋቀረው የስላላ መረብ፤ የማያፈናፍን በመሆኑም ሊሆን ይችላል ህዝቡ ከየአቅጣጫው መነሳት ያቃተው። የህውሀት ሰላዮች አብዛኛዎቹ የትምህርት ደረጃቸውና የስራ ልምዳቸው የማያስገኝላቸውን ጥቅም ለማግኘት ሲሉ ወገኖቻቸውን አሳልፈው የሚሰጡ፤ ይህ ስልጣን ላይ ያለው ቡድን ንቅንቅ የማይል ነው ብለው የሚያምኑ ናቸው። ህልውናቸውን ከስር አቱ ጋር ስላቆራኙት ተግተው ወገኖቻቸውን ሁሉ ያስበላሉ። ይህ ፍርሀት በያንዳንዱ ሰው ልብ ውስጥ ነግሶ ይሆን ?  ከሁሉም በላይ ግን ሁሉንም አንድ ላይ መጨፍለቅ የሚችለው የህዝብ ቁጣ ነው። ለምን ይሆን የዘገየው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጣ ?
መልካሙ ነገር ወያኔ በመላው ኢትዮጵያ ከትግራይ ክፍለሀገር ጨምሮ የጠላቶቹን ቁጥር እያበራከተ መሄዱ ነው ። ይህም በመሆኑ የሚወስደው እርምጃ ሁሉ የውስጥ ፍርሀቱንም ጭምር ይገልጻል። የሚፈራውም  አንድ ቀን፤ ከአንድ ጥግ፤ ወይ ከመሀል የሚነሳ የተንቀለቀለ ቁጣ ማእበሉ በሚያስገርም ፍጥነት በመላ ሀገሪቱ ተስፋፍቶ፤ ወያኔ ለወሬ ነጋሪ እንኳ እንዳይተርፍ ሊያደርገው ይችላል። አንባገነኖች አፈናውንና ጭቆናውን እያበዙት በሄዱ ቁጥር፤ የፍርሀታቸውም መጠን እየጨመረ መሄዱ የማይቀር ነው። የፍርሀታቸው መጠን በጨመረ ልክ፤ በህዝብ ላይ የሚፍጽሙትም ግፍ እየከፋ ይሄዳል። በሙስሊም ወንድሞቻችን ላይ የሚያካሂዱት ጭፍጨፋ ይህንኑ ያመለክታል።

ባንድ አጋጣሚ መብቱንና ነጻነቱን ለማይረቡ ደካሞች አሳልፎ የሰጠ ህዝብ፤ በውዴታ ወይም በክብር መልሶ ነጻነቱን ሊያገኝ ከቶም አይቻለውም። በቁጣ እና በሀይል ነው ከጅ ያመለጠ ነጻነት የሚገኘው። በተደራጀ ሀይልና በቆራጥ ትግል ነው ከጅ ያመለጠ ነጻነት የሚገኘው። ወያኔዎች በተቀናጀ የፖሊስና የጦር ሀይል ህዝብን በማሸበር ስራ ላይ ተሰማርተው ህዝቡን አሸባሪ ይሉታል።
 ህዝቡን እየገደሉት ተገደልን ይላሉ። ባንዲራ ቀደው እያራገቡ ህዝቡን ባንዲራ ቀደደ ይሉታል። ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ይህችን ምድር ትቶላቸው ወዴት እንዲጋዝ አስበዋል? አዎ ይህን ህዝብ አሸንፈውታል። ጥለውታል። ፈሪ ከጣለው ላይ አይነሳም እንዴ?… ፈሪ ግልግል አያውቅም እንዴ? ካንድ መንደር የተውጣጡ ወሮበሎች ይህን ህዝብ በሀይል ጸጥ አድርገው እየገዙ እንድሚዘልቁ አምነዋል? እኛስ እየተረገጥን ተገዝተን መኖር እንዳለብን አምነን ተቀብለናል?

ምን ጊዜም የአንባገነኖች ብርታትና ጥንካሬ የህዝብ ፍርሀትና መንበርከክ ነው። የኛ ችግር ደግሞ ከፍተኛ ፍርሀት በልባቸው ውስጥ መኖሩን አውቀን መድፈር አለመቻላችን ነው። እነሱ ይህን ስልጣን ተነጥቀው በጃቸው ያስገቡትን የሀገሪቱን ሀብት እንዳያጡ ይፈራሉ። እኛ ደሞ ከሞቱት በላይ ከነሱ በታች አድርጋ የምታኖረንን ኩርማን እንጀራ እንዳናጣ እንፈራለን። እየፈራንም ድንገት ባላሰብነው ሁኔታ ያቺን የምንፈራላትንም ጥቅም አሳጥተውን እንደምንወድቅ አሳይተውናል። ስንት ሺ ህዝብ ነው በማያውቀው ምክንያት ከስራ የሚባረረው? ብረት የተሸከመው መለዮ ለባሽ ሳይቀር ስንቱ ሺ ስንት ጊዜ ከሰራዊቱ ተባረረ? መፍራቱ፤ አቤት ወዴት እያለ ለነሱ መታዘዙ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለኑሮና ለህይወት ዋስትና ነው ብሎ የሚያምን ይኖር ይሆን?

ሀይሌ ገብረስላሴ እግራቸው ስር የወደቀው ፕሬዚደንት እሆናለሁ እያለ መለፍለፍ የጀመረው ሀብቱን ንብረቱን ሊዘርፉት እንደሚችሉ ጠንቅቆ በመረዳቱ ይመስላል። የሚወደውን የኢትዮጵያ ህዝብ ጠልቶ አይመስለኝም እነሱ ስር መለጠፍ የፈለገው። ጨካኝ ወንጀለኞች መሆናቸው አስፈርቶት ነው። ስልጣኑ አይደለም አንባገነኖችን ጨካኝና ጨፍጫፊ የሚያደርጋቸው። ጥቅሙ ነው። ያን ጥቅም የማጣት ፍርሀት ነው ክፉ የሚያደርጋቸው ። ጥቅሙ የሚገኘው ስልጣኑን ተከትሎ ነውና።

የሰው ልጅ በተፈጥሮው የሚገባውን ሰባዊ መብት አላውቅም፤ አልቀበልም፤ አላከብርም፤ ብሎ በህዝብ ላይ ያሻውን እየፈጸመ ለመኖር የቆረጠ የህገወጦች ቡድን ሁሉን በተቆጣጠረበት አገር ውስጥ፤ እርግጥ ፍርሀት የህብረተሰብ የለትተለት ህይወት  ሊሆን ይችላል ። እንዳንታሰር መፍራት፤ እንዳንገደል መፍራት፤ በእስር ቤት የቁምስቃይ እንዳይደርስብን መፍራት፤ ልጄን ወንድሜን ይገሉብኛል ብለን መፍራት፤ ስራዬን አጣለሁ ብለን መፍራት፤ ያለኝን ሀብት ነጥቀው ያደኽዩኛል ብለን መፍራት፤ አዎ ባሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ መሰረት ያለው ፍርሀት ነው። አንካካድም። እንዲህም ሆኖ ግን የሚደርስባቸውን ሁሉ እያወቁ፤ ለህይወታቸውም ለንብረታቸውም ቅንጣት ሳይሳሱ፤ በግላቸው ለመጠቀም ሳይሆን፤ ኢትዮጵያውያን መብት ነጻነትና ዲሞክራሲ ያስፈልገናል ብለው፤ እነእስክንድር ነጋ፤ እነ አንዷለም አራጌ፤ ወያኔ እስር ቤት የታጎሩት የነጻነት ታጋዮች በሙሉ፤ የሙስሊም ወንድሞቻችን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት  ብሎም መላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም በሙሉ፤ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እየጮሁ ይህን የነፍሰገዳዮች ቡድን ሲሞግቱ፤ አብሮ ለመነሳትና ለመከተል ወኔ ማጣታችን ነው ከሁሉም የከፋ ፍርሀት። የመጣው ይምጣ ብሎ ጀግና ተነስቶ ይህን አራዊት ቡድን ሲጋፈጥ እያዩ ቶሎ ተነስቶ ከጎኑ መቆም ያለመቻል ነው አደገኛው ፍርሀት።
የቱኒዚያው ለውጥ የመጣው አንድ ወጣት እራሱን በማቃጠሉ፤ ከዳር እስከዳር የሀገሪቱ ሰው ሁሉ ተነቃንቆ፤ በጥቂት ቀናት ነገሩን ሁሉ ቀየረው። በኢትዮጵያ ውስጥ ጀግናው የኔ ሰው ገብሬ ለፍትህ ሲል ራሱን አቃጠለ። ወያኔ በህዝቡ ላይ የጫነው የፍርሀት ድባብ በልጦ ነው መሰለኝ የተንቀሳቀሰ ሰው አልታየም::

በማናቸውም ስርአት ውስጥ ኢትዮጵያ ጭቆናን፤ አንባገነንነትን፤ ዘረኝነትን፤ የሚቃወሙ ጀግኖች ሞልተዋታል። ቀድመውን የተነሱትን  ፈጥኖ የመከተል ወኔ ነው የጎደለን። ሰማያዊ ፓርቲ አዲስ አበባ ውስጥ በቅርቡ በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከሶስት መቶ ሺህ ህዝብ ያላነሰ ወቷል። የቀረው እቤት ውስጥ ምን ያደርግ ነበር ?.. ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለተኛ አመታቸውን ይዘዋል ድምጻችን ይሰማ፤ የሀይማኖት ነጻነታችን ይከበር፤ ህገመንግስቱ ይከበር እያሉ ሲጮሁ፤ ሲገደሉ፤ ክርስቲያኑ ምን እያደረገ ነው ? እስላም መንግስት ሊሆንብህ ነው ብሎ ወያኔ የሚያወራው ውሸት  ለኢትዮጵያዊው ክርስቲያን የመዝናኛ የመሳቂያ ቀልድ ነው። ከወንድሞቹ ጋር መነሳት ያቃተው፤ ለራሱ ነፍሱ በፍርሀት ብትቀጥን ነው እንጂ። ( በነገራችን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎች ሲደብራቸው ወያኔ ዛሬ ምን  ውሸት አወራ? ቴሌቪዥን ያየ አለ?  ማለት በየቤቱ የተለመደ ሆኗል ይባላል) እርግጥ የሀገር ቤቷ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በወያኔ ተማርካለች፤ የሀይማኖት መሪዎች፤ የወያኔ ባንዳና ቅጥረኞች ሆነዋል። የሙስሊሙን ቅጥረኛ መጅሊስ ምእመኑ እንቢ እንዳለ፤ የክርስቲያኑም ምእመን ያንኑ አቁዋም ይዞ ከወንድሞቹ ጎን መታየት ነበረበት። በሙስሊም ወንድሞቹ ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ኢትዮጵያዊውን ክርስቲያን እያሳመመው እያንገበገበው ነው። ይሄ ምንም የሚያጠራጥር ነገር የለውም። ሙስሊሙ በየመስጊዱ ያደረገውን ክርስቲያኑ በየ ቤተክርስቲያኑ ለማድረግ ግን ዘግይቷል። ጊዜ ግን ምንጊዜም አለ። ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችም ተነሱ!

ዊንስተን ቸርችል ተናገሩት ተብሎ ከተጻፈ ጥቅስ እንዲህ የሚል አየሁ “….ታያላችሁ እነዚያን በተደላደለ መሰረት ላይ ተደላድለው የተቀመጡ አንባገነኖች? በወታደሮቻቸው አፈሙዝ ተከበው፤ በፖሊሶቻቸው ቆመጥ ተከበው….ግን በልባቸው ውስጥ ለመግለጽ አዳጋች የሆነ ፍርሀት አለባቸው። …መልካም አስተሳሰቦችን ይፈራሉ። ጠንካራ ቃላትን ሳይቀር ይፈራሉ። ስለ ስርአታቸው ስለሁኔታቸው ከውጭ የሚወሩ ነገሮችን ይፈራሉ። በሀገር ውስጥ የሚንሸራሻሩ ትክክለኛ ሀሳቦችን ይፈራሉ። ስለሚያስፈሯቸውም ሀሳቦችን ያግዳሉ። ያፍናሉ። ሰው ሀሳቡን እንዳይገልጽም ይከለክላሉ። እነሱ ከሚያስቡት የተለየ ኢምንት አስተሳስብ በሀገር ውስጥ ሲንቀሳቀስ ካዩ በፍርሀት  በድንጋጤ ይርዳሉ….”

የህውሀት ሰዎች የኢትዮጵያን ህዝብ ለማፈን የሚደክሙት ለምንድነው? የሽብርተኛ ህግ አውጥተው የሚቃወማቸውን ሁሉ፤ ጋዜጠኛውን ሁሉ እስር ቤት የሰበሰቡትና ድፍን ያገሪቱ ህዝብ እነሱ የሚዋሹትን እንጂ እንዳይሰማ ለማድረግ ባለመታከት የሚጥሩት ለምንድነው? መልሱ ከላይ ዊንስተን ቸርችል ከተናገሩት ውስጥ አለ። እኛ የተጎዳነው ፈሪዎች መሆናቸውን ማወቅ አቅቶን ደፍረን እነሱን ለማንበርከክ አለመተጋገዛችንና አለመነሳታችን ነው።

ከደቡብ አፍሪካው አፓርታይድ ጋር ይፋለም የነበረው የነማንዴላ ድርጅት እንደ አወሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ1949 ዓም ላይ አመታዊ ጉባኤውን ሲያካሂድ ህዝቡን በማንቀሳቀስ ተግባራዊ የሚሆን የሰላማዊ ትግል እርምጃዎችን አቅዶ ነበር። እነዚያም እቅዶች ቦይኮት፤ የስራማቆም አድማ፤ እቤት የመዋል አድማ፤ ከመንግስት ጋር ያለመተባበር፤ ዘረኛ ለሆኑ ህጎች ያለመገዛት፤ ባጠቃላይ ሀይል ያልተቀላቀለበት አመጽ፤ እንቢታ የመሳሰሉት ነበሩ።

በ1951 መጨረሻ ላይ ይህንኑ የትግል ስልት በተግባር ሊጀምሩ፤ የኤ-ኤን-ሲ መሪዎች ተሰበሰቡና አግባብነት የሌለውንና አፓርታይድ ህዝቡን ለማፈን ያወጣውን ህግ ባደባባይ ጥሰው በማሳየት፤ ለመታሰር የሚፈልጉ በጎ ፍቃደኞችን ማሰባሰብ ቀጠሉ።  በሀገራችን ወያኔ እንደሚጠቀምበት የሽብረተኛ ህግ ማለት ነው። በ1952 መጀመሪያ ላይ ወደተግባር ሲሻገሩ በበጎ ፍቃደኝነት ህግ ጥሰው ለመታሰር የወሰኑ በርካታ ሰዎች ተሰለፉና ነጮች ብቻ መዘዋወር የሚችሉበት አካባቢ ጥሰው መግባት፤ ለጥቁሮች ያልተፈቀዱ ሁቴሎችና መዝናኛዎች ጥሰው መግባት፤ ለነጮች ብቻ በተፈቀደ የማመላለሻ አውቶብሶችና ባቡሮች ላይ ሆ ብለው መግባት፤ ለጥቁሮች ከተፈቀደ ሰአት ውጭ ማምሸት ተግባር ላይ እያዋሉ ሆን ብለው በብዛት ወደ እስር ቤት ይገቡ ጀመር። ይህ የመጀመሪያው የእንቅስቃሴ ክፍል ሲሆን በሁለተና ደረጃ የተነደፈው በመላ ሀገሪቱ ባንድ ጊዜ አንድ አይነት ሰላማዊ እርምጃ መውሰድ ነበር። ያም ብሄራዊ እንቢተኝነትና ብሄራዊ የስራ ማቆም አድማዎች ነበሩ።

ጁን 26 1952 ህግን የመጣስ ተቃውሞ በያለበት ተጀመረ። ህዝቡ በነቂስ ወቶ በጎ ፍቃደኞቹን እያበረታታና እየዘመረ ድጋፉን ሰጠ። ጥቁሮች እንዳይደርሱ በህግ የተከለከሉባቸውን ቦታዎች እየጣሱ በሀይል በመግባት በጅምላ ወደ እስር ቤት መጋዝ ጀመሩ። በርካታ የኤ-ኤን-ሲ መሪዎችም ቡድኖችን እየመሩ አብረው ታሰሩ። ፖሊስ ያሰረውን ህዝብ በሙሉ ፍርድ ቤት እያመላለሰ በመክሰስ ስራ ላይ ተጠመደ። “ሁላችንንም እሰሩን” እያለ ህዝቡ፤ “ማንታስሮ ማን ይቀራል” እያለ፤ በፉክክር መንግስቱን ፈተና ላይ ይጥለው ጀመር። በመጀመሪያዋ የአመጽ እለት 250 በላይ በጎ ፍቃደኞች ህግ ጥሰው ታሰሩ። በተካታታይ በተካሄደ የአምስት ወር ዘመቻ 8500 ሰዎች በበጎ ፍቃድ ህግ የመጣስ ዘመቻ ተካፍለው እስር ቤት ገቡ። የህክምና ዶክተሮች፤ የህግ ጠበቃዎች፤ የፋብሪካ ሰራተኞች፤ የዩኒቭርስቲ መምህራንና ተማሪዎች ባጠቃላይ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ፍጹም ወደር በሌለው አንድነትና መተባበር ያንን መንግስት እስከመጨረሻ ሊታገሱት እንደማይችሉ አረጋገጡለት። ህዝቡ ይዘምር ነበር የባለስልጣናቱን ስም እየጠራ “ ክፈቱት.. ክፈቱት በሩን፤ የእስር ቤቱን…እንፈልጋለን መግባቱን..” እያለ።ይህን ህዝባዊ ሰላማዊ አመጽ ያቀደውና የመራው የማንዴላ ድርጅት ኤ-ኤን-ሲ በህዝቡ ዘንድ እጅግ ትብብርና ድጋፍ በማግኘቱ፤ ባንድ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ከ20‹000 ወደ 100‹ 000 ተተኮሰ።

ከዚያ በፊት የደቡብ አፍሪካ ህዝብ በዘረኞቹ ገዢዎች አንጻር፤ አንድ መሆኑን ያረጋገጠበት አጋጣሚ ነበር። ነሀሴ 1943 ዓም ላይ ንብረትነቱ የነጮች የሆነ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ኩባንያ የአውቶብስ አገልግሎት ዋጋ ከአራት ሳንቲም አንድ ሳንቲም ጨምሮ ከፍ አደረገ። እነማንዴላ ህዝቡ ባውቶብሶቹ እንዳይሳፈር አድማ ጠሩ ( ቦይኮት ) ዘጠኝ ቀን አውቶብቹ ሰው የሚባል አጠገባቸው አልደርስ አለ። ኩባንያው ተሽመድምዶ ቁጭ አለ። ጠባቂውና ተንከባካቢው ዘረኛው የነጮች መንግስት ህዝቡን ደብድቦ ባውቶሶቹ እንዲገለገሉ ማድረግ አልቻለም። ዘሮቹን አጽናንቶ ከባጀቱ ለኪሳራው ማካካሻ ከመስጠት በቀር። የህዝቡን መቁረጥ የተረዳው ኩባንያ መጀመሪያ በሚያስከፍለው አራት ሳንቲም ስራውን ቀጠለ። አገልግሎቱን ለመስጠት ተገደደ። ህዝብ እንዲህ ለአንድ አላማ በአንድ ድምጽ በአንድ አቋም ጸንቶ እርምጃ ከወሰደ፡ ካልተንጠባጠበ፤ ማናቸውንም የአመጸኞች ስርአት የማንበርከክ ሀይል አለው። አንድ መሆን ያቃተው ህዝብ ግን ዝንተአለም እየተረገጠ ሲገዛ ይኖራል።

ኢትዮጵያን ዳግም በልጆቿ አንድነት ተነሳለች!

ሞት ለወያኔ

lkebede10@gmail.com


Sunday, August 18, 2013

ህዝባዊ ተቃዉሞ እየተስፋፋ የመጣዉ ለምንድን ነዉ?

 ሰዎች መንግስት ፍላጎታቸዉን እንደሚያሟላላቸዉና የይኮኖሚዉ ስርዓት እንደሚፈልጉት እንደሆነ ከተሰማቸዉ ተቃዉሞ ለማሰማት ኣያስቡም ::ችግሮች ቢኖሯቸዉ እንኴ ስርዓቱን ተከትለዉ ችግሮቻቸዉን ለመፍታት ይጥራሉ፤ በሌላ በኩል ግን ህዝቡ፤ባለስልጣናት በሙስና የተዘፈቁ እንደሆነ ፤የፍትህ መጔደልና ስርዓቱ ጥቂቶችን ብቻ የሚጠቅም እንደሆነ ሲሰማዉ ተቃዉሞ የሚቀሰቀስበት ሁኔታ ይፈጠራል።
ብዙ ጊዜ ሰዎች እርምጃ ለመዉሰድና ችለዉ የኖሩትን ነገር ለመለዉጥ የሚያነሳሳቸዉ የሆነ ምክንያት ይኖራል።ለምሳሌ ሞሀመድ ቡኣዚዚ ታህሳስ  17 ቀን2010 ሁሉ ነገር ከኣቅሙ በላይ የሆነበት ፤ በቱኒዚያ ጎዳናዎች ሸቀጥ እያዞረ የሚሸጠዉ ይህ የ26 ዓመት ወጣት የተሻለ ስራ ዓለማግኘቱ በራሱ ሆድ ዓስብሶታል። በዚያ ላይ ደግሞ ምግባረ ብልሹ ባለስልጣናት ጉቦኛ መሆናቸዉ ዓበሳጭቶታል።ይህ እንዳይበቃዉ በዚህ ዕለት ጠዋት ላይ ተቆጣጣሪዎች መሀመድ እያዞረ የሚሸጠዉን ፍራፍሬ ወሰዱበት።ሊወሰድበት ሲል ለመከላከል ሞከረ በዚህ ጊዜ ዓንዴት ፖሊስ በጥፊ እንደመታችዉ የኣይን ምስክሮች ገልፀዋል።
በደረሰበት ሁኔታ ዉርደት የተሰማዉ መሀመድ ኣቅራቢያዉ ወደሚገኘዉ የመንግስት መስሪያ ቤት በመሄድ ቅሬታዉን ቢያሰማም ጀሮ የሚሰጠዉ ኣላገኘም።በዚህ ግዜ መሀመድ ከመስሪያቤቱ ፊት ለፊት ታዲያ ምንሰርቼ ልብላ ብሎ ጮኽ።ከዚያም ሰዉነቱ ላይ ተቀጣጣይ ፈሳሽ ካርከፈከፈ በኋላ ክብሪት ለኩሶ ህይወቱን ኣጠፋ።መሀመድ የወሰደዉን እርምጃ ተከትሎ በቱኒዚያም ሆነ በሌሎች ኣገሮች ህዝባዊ ኣመጽ በመቀስቀስ ለመንግስት ግልበጣ ምክንያት ሆኗል።
ሙስና እና ፍትህ መጔደል ከመቸዉም ጊዜ ይበልጥ ዛሬ በጣም ተስፋፍቷል።መረጃዎችም በሞባይል ስልኮች በፌስቡኮች በዜናማሰራጫዎች (...) በመሳሰሉት በፍጥነት ስለሚሰማ  በርካታ ሰዎች ተቃዉሞኣቸዉን በኣንድ ግዜ በማሰማት መንግስትን በኣጭር ግዜ ማስወገድ ይቻላል።እርግጥ የሰዉ ልጆች ጨቌኝ ስራቶችን የመቃወም የሞራል ግዴታ እንዳለባቸዉ ይሰማቸዋል።ለምሳሌ መሀመድ ቡኣዚዚ፤የኔሰዉ ገብሬ እና ሌሎችም ሰዎች የወሰዱት ርምጃ ድምፃቸዉን ለማሰማት የሚያስችል የተሻለ ኣማራጭ እንደሌለ ስለሚሰማቸዉ ነዉ።በቅርቡ መምህር የኔሰዉ ገብረሬ  ራሱን ለኣሰቃቄ ሞት በመስጠት ዛሬ በፍትህና በዴሞክራሲ እጦት የሜቃጠለዉን በኑሮ ዉድነት እና በድህነት የሜነደዉን የህዝብ ኑሮ ለመላዉ ኣለም ለማሳየት ራሱን በማቃጠል በቁሙ የሜቃጠለዉን ህዝብ በተምሳሌትነት ኣሳይቷል።ይህን በማድረጉ በኣገራችንና በኣለም ዙሪያ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።ህዝባዊ ተቃዉሞ ያለማቌረጥ ሰባኣዊ ክብራችን እስኪጠበቅልን፤መብቶች እስከሚከበሩልን፤እኩልነት እስኪረጋገጥልንና ፍትህ እስኪሰፍንልን ድረስ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት እዉን እንዲሆን ያለማቌረጥ ብሶትን በኣደባባይ መግለፅ ኣለብን።
ኣዘጋጅ ባይሌ ደርሰህ

Saturday, August 17, 2013

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከኤፈርት ዳይሬክተርነት ተነሱ

ገዢው ፓርቲ የሟቹን ጠቅላይ ሚ/ር ሙት ዓመት ለመዘከር ደፋ ቀና እያለ በሚገኝበት በዚህ ሰዓት የሟቹን ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍንን ከኤፈርት ዳይሬክተርነት ማንሳቱን የኢሳት ራድዮ ዘገበ። የራዲዮው ዘገባን ያድምጡት።

http://ethsat.com/2013/08/16/esat-radio-aug-16/

የአንባገነኖች የስልጣን አለቅም ግብ-ግብ መጨረሻ ፤ ዉርደት ፣ እስር እና ሞት

ከበትረ ያዕቆብ
ባደጉትና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት በቻሉት የምዕራቡ ሀገሮች አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ግለሰብ ሰላማዊ በሆነ የህዝብ ምርጫ ስልጣን ላይ ይወጣል፡፡ ግዳጁን ባጠናቀቀ ግዜ ወይም በወከለዉ ህዝብ ዘንድ አመኔታን ሲያጣ ደግሞ እንደ አወጣጡ ሁሉ በሰላም ከስልጣኑ ዉልቅ ይላል፡፡ በእነዚህ ሀገራት ከዚህም በተለየ ሁኔታ መሪዎች በሀገር ላይ ከሚጋረጡ ፈተናዎች ጋር በተያያዘ ሀላፊነታችንን መወጣት አልቻልንም ሲሉ ተፈፀሙ ለሚሏቸዉ ስህተቶች ሁሉ ሀላፊነቱን በመዉሰድ ሌላ አቅምና እዉቀት ለሚፈቅድላቸዉ ሰዎች ስልጣናቸዉን አስረክበዉ በሰላምና በፍቅር ከነሙሉ ክብራቸዉ ሹልክ ይላሉ፡፡
አሁን አሁን ይህን መሰል ዲሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር በብዙ ሀገሮች እየተስፋፋና እየተለመደ የመጣ ሲሆን ፤ ኃላ ቀር በሚባለዉ የአፍሪካ አህጉር ዉስጥ በሚገኙ አንዳንድ ሀገራት ጭምር መታየት ጀምሯል፡፡ ለምሳሌ ያህል ጋናን እና ጎረቤታችን የሆነችዉን ኬንያን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ያም ሆኖ ግን ዛሬም ቢሆን በብዙ የአፍሪካ ሀገሮች መሰል ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ፈታኝ ሆኖ እንደቀጠለ ነዉ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ኋላ ቀር ሀገራት አሁንም ገዥዎች ወደ ስልጣን የሚወጡትም ሆነ ከስልጣናቸዉ የሚወርዱት ያዉ በጠመንጃ ወይም በህዝብ አመፅ ብቻ ነዉ፡፡ እዚህ ላይ ባለፉት 50 ዓመታት ዉስጥ በሀገራችን የተካሄዱ የስልጣን ሽግግሮች አይነተኛ ማሳያ ይሆናሉ፡፡
ብዙዉን ግዜ በእንደዚህ ዓይነት በሐይል በታጀበ የስልጣን ሽግግር ወቅት ስልጣናቸዉን የሙጥኝ የሚሉ አንባገነኖች መጨረሻቸዉ ዘግናኝና አሳፋሪ ዉድቀት ነዉ፡፡ ብዙዎቹ በስልጣን ልቀቅ አለቅም ትግሉ ሕይወታቸዉን ሲያጡ የቀሩት ደግሞ ስልጣናቸዉን ሲነጠቁ በስልጣን ዘመናቸዉ በፈፀሙት ግፍ ስም ወደ ግዞት ይወረወራሉ ወይም ከተወለዱባት እናት ሀገራቸዉ ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ተዋርደዉ ይሰደዳሉ ፤ አንዳንዴም ከዚህ የከፋ ነገር ይገጥማቸዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል ከቱንዚያ ተነስቶ የአረቡን ዓለም ያዳረሰዉ አሁንም የት ላይ እንደሚቋጭ ያልታወቀዉ የፀደዩ አቢዎትን ተከትሎ ከስልጣናቸዉ በሰላም እንዲወርዱ ሲለመኑ አሻፈረኝ በማለት ከህዝብ ጋር ግብ ግብ የገጠሙትን የኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊን መጨረሻ መመልከት ይቻላል፡፡ ጋዳፊ ስልጣን በሰላም አስረክቦ ከነሙሉ ክብሩ ሹልክ ማለት እየቻለ በእብሪት ተወጥሮ አሻፈረኝ በማለቱ ከራሱ አሳፋሪና ወራዳ ሞት ባሻገር የልጆቹን ህይወት እንደ ቅጠል አርግፏል፡፡
በተመሳሳይ ስልጣን በሰላም እንዲያስረክብ ሲጠየቅ እንቢ ሲል የኖረዉ የግብፁ ሙባረክም አረፍ ብሎ ሰላማዊ አየር እየተነፈሰ ጣፋጭ ህይወት ከቤተሰቦቹ ጋር በሚያጣጥምበት የእርጅና ዘመኑ ተዋርዶ ወደ እስር ቤት የተወረወረ ሲሆን ፤ የእርሱ ጦስ ለልጁም ሊተርፍ ችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እነሎረንስ ባግቦን ፣ ቤን አሊንንና ሌላ በርካታ አንባገነኖችን መጥቀስ ይቻላል፡፡
እንግዲህ የሀገራችንንም ታሪክ ስንመለከት በአፄ ሐይለ ስላሴና ባለስልጣናቶቻቸዉ የደረሰዉ ተመሳሳይ ነበር፡፡ ንጉሱን ጨምሮ ብዙ ባለስልጣኖቻቸዉ በያሉበት እየተለቀሙ የሞት እራት ነበር የሆኑት፡፡ እንደዚያ መለኮታዊ ሐይል ያላቸዉ ይመስል ስንት ሲባሉ የነበሩት ንጉስ በክብር የመቀበር ወግ እንኳን አልደረሳቸም፡፡ በተመሳሳዩ እነርሱን ተክትለዉ ወደ ስልጣን በመጡት የደርግ ባለስልጣናት ላይም የደረሰዉ ያዉ የተለመደዉ ዉርደት ፣ እስር እና ሞት ነበር፡፡ ብዙወች በየጦር ግንባሩ የጥይት ሲሳይ ሲሆኑ ፤ የተቀሩትም ዛሬ በየ እስር ቤቱ ተወርዉረዉ በሚያሳዝን ሁኔታ ዉስጥ ይገኛሉ፡፡ ያገዛዙ ቁኝጮ የነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ ሐይለማርያምም ቢሆኑ መኮብለል ቢሳካላቸዉም እንኳን የዉርደት ማቅ ከመከናነብ ግን አላመለጡም፡፡ በተሰደዱበት አገርም ቢሆን የተዝናና ህይወት ሳይሆን የገጠማቸዉ ተቃራኒዉ ነዉ፡-ፍርሀትና ሰቀቀን የበዛበት ህይወት፡፡
የኢህአዴግ ባለስልጣናት የቁልቁለት መንገድ
ምንም እንኳን የአንባገነኖች ከስልጣን አንለቅም ግብ ግብ ዉጤቱ ከላይ እንዳየነዉ በጣም የከፋ ቢሆንም የወቅቱ የሀገራችን መሪዎችና ባለስልጣናቱ ከታሪክ መማር አቅቷቸዉ የህዝብ የሆነን ስልጣን እደግመዋለሁ የህዝብ የሆነን ስልጣን ሙጭጭ በማለት ወደ ዉድቀት አፋፍ በፍጥነት እየተንደረደሩ ይገኛል፡፡
እንደሚታወቀዉ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከስልጣን ዉረዱ አንወርድም ግብግቡን በ1997 ከተካሄደዉ ሀገር አቀፍ ምርጫ ማግስት ጀምሮ በይፋ የጀመሩት ሲሆን ፤ ከቅርብ ግዜ ወዲህ የተቀዋሚ ፓርቲዎችን አመራሮች እና አባላትን በማሳደድ እንዲሁም የነፃዉን ፕሬስ ዉጤቶች ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ በማጥፋትና ጋዜጠኞቻቸዉንም በሐሰት ዉንጀላ በግፍ በማሰር አፈናዉን ከምን ግዜዉም በላይ አጠናክረዉ ቀጥለዋል፡፡
ይህ እየሆነ ባለበት ሁኔታ የኑሮ ፈተና ፣ የፍትህ ማጣት ፣ ጭቆና እና እንግልት… የበዛበት ምስኪን ኢትዮጵያዊ ብሶቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መጦ ዛሬ ለመፈንዳት ቋፍ ላይ ይገኛል፡፡ እንግዲህ ይህ በግልፅ የሚያመለክተዉ በስልጣን ላይ የሚገኙ ባለስልጣናት በታሪካችን እንዳየናቸዉ እና በነኮሎኔል ጋዳፊ እንደደረሰዉ ሁሉ የከፋ አወዳደቅ ለመዉደቅ ቀናቸዉን እየቆጠሩ እንደሆነ ነዉ፡፡
በተለይም የህወሓት ጠንሳሽና የኢህአዴግ መስራቹ እንዲሁም ሀገሪቱን ለ21 አመታት በመዳፋ አስገብቶ የገዛዉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በህመም ከስልጣኑ ከተገለለበት ቆይቶም ከሞተበት ግዜ ጀምሮ በብሶት ተወጥሮ የኖረዉ ጭቁን ህዝብ ከምግዜዉም በላይ ለለዉጥ የበለጠ በማቆብቆብ ላይ ነዉ፡፡ እዚህ ላይ በቅርቡ በመዲናችን አዲስ አበባ እንዲሁም በጎንደር እና ደሴ ከተሞች የተካሄዱት ህዝባዊ ተቃዉሞዎች የሚያስብ ህሊና ላለዉ ሰዉ ብዙ ያስተላለፉት መልዕክት አለ፡፡
በተያያዘም አገዛዙ ለርካሽ ትርፍ ሲል የፈለሰፈዉ የጎሳ ፖለቲካ ዛሬ የጠቅላይ ሚኒስትር መለሽ ዜናዊን ሞት ተከትሎ በተነሳዉ የስልጣን ሽኩቻ ምክንያት በራሱ በኢህአዴግ ላይ የማይጠግኑት ትልቅ ስንጥቅ እየፈጠረ ሲሆን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እንደ ስልጣናቸዉ መከታ በሚቆጥሩት ጦር ዉስጥም ትልቅ መከፋፈል እያመጣ ስለመሆኑ መረጃዎች እየጠቆሙ ይገኛል፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ አለማቀፋዊ ጫናዉ በዛዉ ልክ እየበረታ ሄዷል፡፡ እንግዲህ ይህ ሁሉ ከህዝቡ ቁጣ ጋር ተደማምሮ አገዛዙን ከምን ግዜዉም በላይ ከዉድቀት አፋፍ ላይ አድርሶታል ማለት ይቻላል፡፡
ሆኖም ግን በጣም የሚያሳዝነዉ ፤ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማሪያም “ለአንዳንድ ሰዎች ቁልቁለት ቁልቁለት መሆኑ የሚታወቃቸዉ ወርደዉ ወርደዉ ወድቀዉ ሲከሰከሱ ነዉ” ሲሉ “አደጋ ያንዣበበበት የአፍሪካ ቀንድ” በሚለዉ መፅሐፋቸዉ እንደገለፁት ሁሉ አገዛዙ እንዲህ ከዉድቀት አፋፍ ላይ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ባለስልጣናቱ ከአጠገባቸዉ በሞት የተለዩትን የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚንስትር ስም እንደ ዳዊት ቃል እየደጋገሙ እና የማይጨበጥ ተስፋ እየሰበኩ ጭቆናቸዉን ለማስቀጠል ደፋ ቀና በማለት ላይ ይገኛሉ፡፡
በሰከነ አዕምሮ በማሰብ የህዝቡን የዲሞክራሲና የፍትህ ጥያቄ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በመመለስና ሌላም የህዝቡን ቁጣ ማብረጃ እርምጃዎችን በመዉሰድ ከፊታቸዉ እየመጣ ካለዉ አስፈሪ ሕዝባዊ ማዕበል እንደማምለጥ ፤ እራሳቸዉንና ቤተሰቦቻቸዉን ከሚመጣዉ መዓት እንደማዳን እነሱ ግን በጭፍን አዕምሮአቸዉ ስልጣናቸዉን ሙጭጭ እንዳሉ የማያዋጣ ግብ ግብ ከህዝብ ጋር ይዘዋል፡፡ የዚህ ግብ ግብ መጨረሻም እየየቀረበ ይገኛል፡፡
ምንም እንኳን ያለፉትን 21 አመታት አንዴ በጉልበት አንዴ በማምታታት ማለፍ ቢቻልም ከዚህ በኋላ ግን ያን መድገም የሚቻል አይመስለኝም፡፡ በፍትህ ፣ ዲሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር እጦት እንዲሁም በድህነት እና ለቁጥር በሚታክቱ ማህበራዊ ችግሮች የሚያቃትትን ህዝብ አይዞህ ኮንዶሚንየም ልገነባልህ ነዉ ፣ ባቡር እየመጣልህ ነዉ ፣ 11 ፐርሰንት እድገት… ቅብርጥሴ ማለት ብዙ እርቀት አያስጉዝም ፤ ከሚመጣዉ መዓበልም አያድንም ባይ ነኝ ፡፡
መፍትሄ
የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅር ባይ ነዉ፡፡ እንኳን ለአብራኮቹ ክፋይ ነዉና ለዉጭ ጠላት እንኳን ቢሆን ይንን ይቅር ባይነቱን አይነፍግም፡፡ ስለዚህ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ይህችንን የወገናቸዉን ደግነት በመረዳት ጊዜ ሳይሰጡ ለፈፀሙት በደል ይቅርታ መጠየቅ እና የህዝቡን የፍትህና የዲሞክራሲ ጥያቄ መመለስ ይኖርባቸዋል ብየ አምናለሁ፡፡ ይህንን ማድረግ ሽንፈት ሳይሆን ድል ነዉ ፤ ሞኝነት ሳይሆን ብልጠት ወይም የፖለቲካ ብስለት ነዉ፡፡
እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት የኢህአዴግ ባለስልጣናት ይህንን በመፈፀማቸዉ እራሳቸዉንና ቤተሰቦቻቸዉን ከሚመጣባቸዉ ችግር ከማዉጣት ባሻገር ስማቸዉንም በኢትዮጵያ ታሪክ ዉስጥ በበጎ ይፅፋሉ፡፡ በህዝቡም ዘንድ ትልቅ ከበሬታን ይጎናፀፋሉ፡፡ በተያያዙት የጭፍን ጉዞ ከቀጠሉ ግን በቅርቡ እነርሱም በታሪክ እንዳየናቸዉ ግዞት ቤታቸዉ እንግልት ሕይወታቸዉ እንደሚሆን ጥርጥር የለዉም ፤ ሲልም ከዚያ የከፋ ነገር ሊገጥማቸዉም ይችላል፡፡

Azeb Mesfin lost TPLF’s cash cow

August 17, 2013
by Najib Mohammed
In the West, we are accustomed to hearing politicians lie to serve their interest and fulfill their ego. For example, when two politicians are running for an office and one tells the truth and the other lies by saying  what the public wants to hear, the one who says what the public wants to hear wins the election. Therefore, it is expected that if one wants to win an election, one better lie, because the guy who’s telling the truth doesn’t have a chance of winning. Yes, there are extreme cases when leaders in the West lie and mislead their people in order to send their army to execute wars outside their borders for which they usually get exposed and pay dearly with their reputation and honor. However, they would never lie to declare war or to incite violence between the different religious or ethnic segment of their population as it is the case in Ethiopia.May the Almighty Allah bring justice and peace to Ethiopia
Ethiopia’s despotic leaders do not need to lie to win elections. They steal elections. In fact, the election they hold is but to lie and mislead the international public opinion. They believe that since they came to power through the barrel of the gun they must stay in power by the same gun. They lie when they want to cover-up murders or plan to murder their own people. They always plot and plan to create instability to stay in power. They tightly control every faucets of their people’s life including their religious practices. Divide and rule is the easiest and obvious method they deploy to stay in power.  Time and again we have witnessed the Ethiopia government use ethnicity to incite interethnic conflicts to dislocate Ethiopian from one region or another. Now, Ethiopians of different ethnic groups have rejected to play the ethnic card, the government is resorting to the most heinous and dangerous card of religion.
Though for the last two years the official government media was waging the propaganda war against the Muslim population to create fear and apprehension among the Christians and did not succeed, the threat and the fear mongering has become the duty of the higher office holder in the country.
Right after the crackdown on peaceful Ethiopian Muslims who were out celebrating the end of Ramadan, and before the blood of those who were massacred by the government forces at Kofele, Oromia dries, the prime minister of Ethiopia, Ato Haile Mariam, gave an interview blaming the innocent victims of the brutal unprovoked crackdown of being terrorist who are bent in destabilizing the country.  Thank God for social media. The world witnessed the innocent victims whom the Prime Minister called terrorists. Women, men, the young and the elderly even pregnant women who were out celebrating fell victims of the crackdown. In fact, he threatened to take harsher measures to kill, maim, and incarcerate more innocent people who dare to demand their constitutional rights.  Amnesty International reported the crackdown the same day urging the Ethiopian Government to respect the human right of the people.
One would think that when the leader of a country appears on national TV on a holiday, it is either to congratulate the country on the happy occasion or to inform the people of an emergency. Both situations were present for Prime Minister Hailemariam. The occasion of Eid AlFitr holiday and the massacre that took place in Kofele, Oromia and Addis Ababa and the rest of the country right after the Eid prayers. These occasions would have warranted the Prime Minister to congratulate the people on Eid and express his sincere apology for the atrocities committed by his security forces. Instead, the Prime Minister went on TV and with straight face lied to the public and shamefully blamed the innocent men and women, young and old victims of the brutal crackdown.
Once, I read an article about the prime minister of Ethiopia, Ato Hailemariam that he is a religious person who wakes up early in the morning and spends at least 30 minutes praying to God before going to his office. Is it perhaps he gets up early to get 30 minutes instruction of how to mislead his people?  I wonder how he will answer the God he is praying to when He asks him about the outright lies he uttered about Ethiopian Muslims and why as a leader he approves the killing and maiming of the innocent. As I was listening to the Prime
Minister’s speech I could not help it but to think perhaps he was getting his 30 minutes instructions from the Far Right Islamophob evangelicals of the West. It is perplexing to hear the Prime Minister lie that Ethiopian Muslims are demanding to establish an Islamic State and impose Sharia law on every Ethiopian. What an absolute fabricated lie. If he is trying to justify the killing and maiming and incarcerating of Ethiopian Muslims based on these lies, we urge him to please pay attention to what the Muslims have been demanding. Mr. Prime Minister, have you not heard that the government prosecutor who is prosecuting the falsely accused Muslim leaders has thrown out the charges against of trying to establish an Islamic state, for lack of evidence? Have you not heard the members of the arbitration committee that you unjustly incarcerated repeatedly and on record say that Ethiopian Muslims demand is nothing but for the government to respect the constitution by staying out the religious affairs of its citizens?
Mr. Prime Minister, does not your conscious bother you? Where and when did you hear Muslims demand for establishment of an Islamic State? What a shear lie! No Ethiopian Muslim in his/her right mind would ever say that. By God, if you are trying to frighten our Christian brethren and create animosity between Muslims and Christians, you and your government have failed miserably.  In fact, to your surprise Mr. Prime Minister, the thousands of peaceful Muslims fleeing the brutal attack by the military and federal police were given shelter by their Christian fellow citizens. You might not like this but according to eye witnesses, Ethiopian Christians were witnessed grieving and tending the injured Muslims and sheltering them from the inhuman forces that were pursuing them. Time and again, and no matter how hard the Ethiopian government tried to create animosity between the religious groups, they have proven to be inseparable and they will forever stand together for justice and the rule of law. In fact the more the repression, the more they become united against injustice.
There is a saying in Ethiopia: “ Libelwat yalwaten Amora yelawatal Gigra”. Ethiopian Muslims never asked to establish an Islamic State; they never once asked for Sharia to be the law of the land. Their only demand is for the government to respect the constitution and to refrain from interfering in the religious affairs of its people. It is true that despots fear the rule of law and they will not hesitate to use force to kill and maim whoever stands to speak the truth.
Ultimately, Truth is always the winner! Remember Mr. Prime Minister, you and your government will be accountable for every drop of the innocent’s blood you shade!
Ethiopian Christians deserve all appreciation for standing beside their brave Muslim brethren and seeing through the lies and mischiefs of the Ethiopian Government. As they lived peacefully side by side for over 1400 years, Ethiopian Muslims and Christians forever will live in peace!
May the Almighty Allah bring justice and peace to Ethiopia and its peaceful people! May He make her a prosperous Nation in which not a single person is ill-treated! Ameen!!!