Monday, March 24, 2014

ኢህአዴግ ባደባባይ የወደቀውን ፈተና “በጓሮ” አለፈ

March 24/2014

ግልጽነትና ተጠያቂነት ፈረዱ ወይስ ተፈረደባቸው?
short eiti eprdf


ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።
የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።
በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።
ማመልከቻው እንደገና እንዲታይና የቦርዱ የቀድሞ ውሳኔ እንዲገለብጥ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የቀድሞ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ ትብብር ሚ/ር የሆኑት ክሌር ሾርት መሆናቸውን የድርጅቱ መግለጫው ይፋ አድርጓል። እኚህ ግለሰብ የአፍሪካ አምባገነኖችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን ይህ ከጥቅማቸው ጋር የተሳሰረው ግንኙነታቸው አሁንም ኢህአዴግን እንዲደግፉ እንዳደረጋቸው ይነገራል፡፡ እንዲሁም በሌሎች ኢህአዴግ ባቋቋማቸው ዓለምአቀፋዊነት ሽፋን በተላበሱ ድርጅቶች ውስጥ የአመራር አባል በመሆን ሚስ ሾርት እንደሚያገለግሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የእንግሊዝ ፓርላማ አባል በነበሩበት ወቅትም ያላወጡትን ወጪ አውጥቻለሁ በማለት በብዙ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆናቸው በወቅቱ ዴይሊ ቴሌግራፍ ባወጣው መረጃ አጋልጦ ነበር፡፡ የተወሰነውን ገንዘብ የመለሱ ቢሆንም ጋዜጣው በወቅቱ ያወጣው መረጃ ግለሰቧ የሕዝብን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው የተጠቀሙ “ሙሰኛ” መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
clare
ክሌር ሾርት
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከሆነ ባለፈው ረቡዕ ኦስሎ፤ ኖርዌይ ላይ ውሳኔው በተላለፈበት ወቅት ሚስ ሾርት በግልጽ የኢህአዴግ ደጋፊ በመሆን ተጽዕኖ በማድረግ ወደ ውሳኔ እንዲደረስ ግፊት አድርገዋል፡፡ ግለሰቧ ባላቸው ኃላፊነት በመጠቀም (የEITI የቦርድ ኃላፊ ናቸው) እንዲህ ዓይነቱ ግልጽና ወገናዊነት የታየበት ድጋፍ በማድረግ ከድርጅቱ አሠራር ውጪ ውሳኔ እንዲሰጥ ማድረጋቸው ለወደፊት በሚቀርቡ ማመልከቻዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የአሠራር ችግር እንደሚያስከትል ካሁኑ እየተጠቆመ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ከማዕድን ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ ማህበራዊ ቀውስ የደረሰባቸው አካባቢዎች እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አካባቢዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ባልጸዳ የሽያጭ ሂደት ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ የገዙት ሻኪሶ የወርቅ ማዕድን በህዝብ ላይ እያደረሰ ችግር የሚዘገንን ነው። በየጊዜው ግልጽ ባልሆነ የማስፋፊያ ውል የሚፈናቀሉና ከፋብሪካው በሚወጣው ዝቃጭ ለከፍተኛ ብክለት የተጋለጡ ዜጎች ድምጻቸውን ሲያሰሙ መታሰራቸው፣ መገረፋቸው፣ ለይስሙላ በተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የተፈረደባቸው እንዳሉ ታዛቢዎች ያስታውሳሉ።
በጋምቤላ ኢንቨስትመንት ህዝብን እየበላ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች “ኢንቨስትመንት በከፍተኛ ደረጃ የሚደገፍና የሚበረታታ ተግባር ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ ደረጃ መጠቀም፣ ማስተዳደር፣ መምራትና ኢንቨስትመንቱን ህዝብ “የኔ” ብሎ በመቀበል እንክብካቤ እንዲያደርግ የሚያስችል ስርዓት አለማበጀቱን እንደ ዋንኛ ችግር ያነሳሉ። ኢህአዴግን ያዘጋጀው ህወሃት በራሱ ሰዎች አማካይነት ከውጪ ሰዎች ጋር እየተሻረከ ለህዝብ ጥቅም ሊውል የሚገባውን ሃብት ወደ ውስን ቋት እንደሚያግዝ የሚገልጹት እነዚሁ ክፍሎች” ይህ ዓለም የሚያውቀውን፣ ራሳቸው ህወሃቶችም የማይክዱትን እውነት ነው ብለዋል። ዜጎች የአገራቸው ሃብት ተጠቃሚ ከመሆን ይልቅ አካባቢያቸው ባደላቸው የተፈጥሮ ሃብት ሳቢያ መከራ ሲደርስባቸው፣ ሲሰቃዩ፣ ሲገረፉና፣ ሲገደሉ ማየት በተለመደባት ኢትዮጵያ ውስጥ ለኢህአዴግ የማይገባውን ካባ መደረብ ውሎ አድሮ የሚጋለጥ ክፉ ተግባር እንደሆነም አመልክተዋል።
አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው ቢከሽፋም በመጨረሻ ተሳክቶለታል። ስኬቱንና የስኬቱን መንገድ፣ በተለይም የዳይሬክተሯ ክሌር ሾርት ጉዳይና የተዘጋውን ፋይል በማንሳት ውሳኔው የተገለበጠበት አካሄድ ኦስሎ በሚገኘው ሃያ የቦርድ አባላት ባሉበት ተቋም ውስጥም ግራ ያጋባቸው እንዳሉ መረጃዎች አሉ።
ኢህአዴግ አጓድለሃል ተብሎ የሚከሰስባቸውን የዴሞክራሲ ግባቶችና የሰው ልጆች የተፈጥሮ መብቶች፣ አንዲሆም አፋኝ የተባሉትን ህጎች አጠናክሮ ተግባር ላይ ባዋለበት ሁኔታ፣ የዚሁ የአፈናው ሰለባዎች በተለያዩ ማጎሪያዎች ውስጥ ሆነው ድምጻቸውን በሚያስተጋቡበት ወቅት፣ EITI ከተቋቋመበት ዓላማና “መሰረቴ” ከሚለው የግልጽነትና ተጠያቂነት መርህ በተጻራሪ ግልጽነትና ተጠያቂነት በጎደለው መልኩ ለኢህአዴግ የደረበው ብሉኮ ጉዳይ እየተመረመረ አንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ጉዳዩን የሚከታተሉ “ግልጽነትና ተጠያቂነት በኦስሎ ተፈረደባቸው” ሲሉ ምጸት ሰጥተዋል፤ የክሌር ሾርትንም አካሄድ በEITI የህወሃት/ኢህአዴግ ተወካይ በማለት ተችተዋል። ይህንኑ ጉዳይ እመልክቶ ከሳምንት በፊት ለሪፖርተር አጭር መልስ የሰጡት የማዕድን ሚኒስትሩ EITI ውሳኔውን ያነሳል የሚል ጥርጣሬ እንዳለባቸው የሚያሳብቅባቸው መልስ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ዳያስፖራው እንደሚገባው አለመንቀሳቀሱ እንደ ሽንፈትና አቅጣጫ መሳት እንደሚቆጠር ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡ ዳያስፖራው ከጥቃቅንና ስሜታዊ ጉዳዮች በማለፍ በከፍተኛና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የማድረግ አመለካከቱን ማስፋት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ አለበለዚያ ኢህአዴግ እንደዚህ ዓይነቱን አጋጣሚ በመጠቀም የራሱን ገጽታ በዓለምአቀፍ መድረኮች እየወለወለ በማቅረብ የሥልጣን ዘመኑን እንደሚያራዝም ጠቁመዋል፡፡

Nile River Dam Threatens War Between Egypt and Ethiopia

March 23/2014

by Cam McGrath

Ethiopia is building one of the largest dams in the world, the Grand Millennium Dam (GERD), on the River Nile near the Sudan border. (InternationalRivers.org)
CAIRO - When Egypt’s then-president Mohamed Morsi said in June 2013 that “all options” including military intervention, were on the table if Ethiopia continued to develop dams on the Nile River, many dismissed it as posturing. But experts claim Cairo is deadly serious about defending its historic water allotment, and if Ethiopia proceeds with construction of what is set to become Africa’s largest hydroelectric dam, a military strike is not out of the question.
Relations between Egypt and Ethiopia have soured since Ethiopia began construction on the 4.2 billion dollar Grand Renaissance Dam in 2011.
Egypt fears the new dam, slated to begin operation in 2017, will reduce the downstream flow of the Nile, which 85 million Egyptians rely on for almost all of their water needs. Officials in the Ministry of Irrigation claim Egypt will lose 20 to 30 percent of its share of Nile water and nearly a third of the electricity generated by its Aswan High Dam.
Ethiopia insists the Grand Renaissance Dam and its 74 billion cubic meter reservoir at the headwaters of the Blue Nile will have no adverse effect on Egypt’s water share. It hopes the 6,000 megawatt hydroelectric project will lead to energy self-sufficiency and catapult the country out of grinding poverty.
“Egypt sees its Nile water share as a matter of national security,” strategic analyst Ahmed Abdel Halim tells IPS. “To Ethiopia, the new dam is a source of national pride, and essential to its economic future.”
The dispute has heated up since Ethiopia began diverting a stretch of the Nile last May, with some Egyptian parliamentarians calling for sending commandos or arming local insurgents to sabotage the dam project unless Ethiopia halts construction.
Ethiopia’s state-run television responded last month with a report on a visit to the site by army commanders, who voiced their readiness to “pay the price” to defend the partially-built hydro project.
Citing a pair of colonial-era treaties, Egypt argues that it is entitled to no less than two-thirds of the Nile’s water and has veto power over any upstream water projects such as dams or irrigation networks.
Accords drawn up by the British in 1929 and amended in 1959 divvied up the Nile’s waters between Egypt and Sudan without ever consulting the upstream states that were the source of those waters.
The 1959 agreement awarded Egypt 55.5 billion cubic meters of the Nile’s 84 billion cubic meter average annual flow, while Sudan received 18.5 billion cubic meters. Another 10 billion cubic meters is lost to evaporation in Lake Nasser, which was created by Egypt’s Aswan High Dam in the 1970s, leaving barely a drop for the nine other states that share the Nile’s waters.
While the treaty’s water allocations appear gravely unfair to upstream Nile states, analysts point out that unlike the mountainous equatorial nations, which have alternative sources of water, the desert countries of Egypt and Sudan rely almost entirely on the Nile for their water needs.
“One reason for the high level of anxiety is that nobody really knows how this dam is going to affect Egypt’s water share,” Richard Tutwiler, a specialist in water resource management at the American University in Cairo (AUC), tells IPS. “Egypt is totally dependent on the Nile. Without it, there is no Egypt.”
Egypt’s concerns appear warranted as its per capita water share is just 660 cubic meters, among the world’s lowest. The country’s population is forecast to double in the next 50 years, putting even further strain on scarce water resources.
But upstream African nations have their own growing populations to feed, and the thought of tapping the Nile for their agriculture or drinking water needs is all too tempting.
The desire for a more equitable distribution of Nile water rights resulted in the 2010 Entebbe Agreement, which replaces water quotas with a clause that permits all activities provided they do not “significantly” impact the water security of other Nile Basin states. Five upstream countries – Ethiopia, Kenya, Uganda, Tanzania and Rwanda – signed the accord. Burundi signed a year later.
Egypt rejected the new treaty outright. But after decades of wielding its political clout to quash the water projects of its impoverished upstream neighbors, Cairo now finds itself in the uncomfortable position of watching its mastery over the Nile’s waters slip through its fingers.
“Ethiopia’s move was unprecedented. Never before has an upstream state unilaterally built a dam without downstream approval,” Ayman Shabaana of the Cairo-based Institute for Africa Studies had told IPS last June. “If other upstream countries follow suit, Egypt will have a serious water emergency on its hands.”
Ethiopia has sought to assure its downstream neighbors that the Grand Renaissance Dam is a hydroelectric project, not an irrigation scheme. But the dam is part of a broader scheme that would see at least three more dams on the Nile.
Cairo has dubbed the proposal “provocative”.
Egypt has appealed to international bodies to force Ethiopia to halt construction of the dam until its downstream impact can be determined. And while officials here hope for a diplomatic solution to diffuse the crisis, security sources say Egypt’s military leadership is prepared to use force to protect its stake in the river.
Former president Hosni Mubarak floated plans for an air strike on any dam that Ethiopia built on the Nile, and in 2010 established an airbase in southeastern Sudan as a staging point for just such an operation, according to leaked emails from the global intelligence company Stratfor posted on Wikileaks.
Egypt’s position was weakened in 2012 when Sudan, its traditional ally on Nile water issues, rescinded its opposition to the Grand Renaissance Dam and instead threw its weight behind the project. Analysts attribute Khartoum’s change of heart to the country’s revised domestic priorities following the secession of South Sudan a year earlier.
According to AUC’s Tutwiler, once Sudan felt assured that the dam would have minimal impact on its water allotment, the mega-project’s other benefits became clear. The dam is expected to improve flood control, expand downstream irrigation capacity and, crucially, allow Ethiopia to export surplus electricity to power-hungry Sudan via a cross-border link.
Some studies indicate that properly managed hydroelectric dams in Ethiopia could mitigate damaging floods and increase Egypt’s overall water share. Storing water in the cooler climes of Ethiopia would ensure far less water is lost to evaporation than in the desert behind the Aswan High Dam.
Egypt, however, is particularly concerned about the loss of water share during the five to ten years it will take to fill the dam’s reservoir. Tutwiler says it is unlikely that Ethiopia will severely choke or stop the flow of water.
Houseboats line the Nile bank in Cairo. Some 85 million Egyptians depend on the Nile for water. (Cam McGrath/IPS)
© 2014 Inter Press Service

ለዜጎች ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ አፈናና እስራት ምላሽ አይሆንም! (ሰማያዊ ፓርቲ)

March 23/2014

ከሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የወጣ የአቋም መግለጫ
የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት መጋቢት 14 ቀን 2006 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛ ዓመት አራተኛ መደበኛ ስብሰባው የካቲት 30 ቀን 2006 ዓም የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ በተገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት ላይ ፖሊስና ፍርድ ቤት በመተባበር የፈጸሙትን ሕገ መንግስት የጣሰ ተግባር፣ እንዲሁም ከአሜሪካ መንግስት በደረሳቸው ግብዣ መጋቢት 12 ቀን 2006 ዓም ምሽት ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቦሌ አውሮፕላን ማረፈያ በተገኙት የፓርቲያችን ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ላይ ራሳቸውን ከህግ በላይ ያደረጉ የደህንነት ኋይሎች የፈጸሙትን አሳፋሪና ሕገ ወጥ ተግባር በመመርመር የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡Statement from Semayawi party of Ethiopia, regarding Nile issue.
1. የሴቶችን ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ የተገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት በሩጫው ከተሳተፉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች የሚለዩት የነጻነትን ቀን ሊያከብሩ በተገኙበት ቦታ ስለ ነጻነት፣ስለ ፍትህ፣ስለዴሞክራሲ፣ስለ ሰብአዊ መብት ወዘተ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው በማሰማታቸው ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 29/2 «ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሀሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው» ተብሎ የተደነገገውን ከምንም ያልቆጠረውና ሕጉን ሳይሆን ጠመንጃውን ተማምኖ፣ የሙያውን ሥነ ምግባር ሳይሆን የአለቆቹን ትዕዛዝ አክብሮ እንደሚሰራ በተግባሩ ያረጋገጠው ፖሊስ እነዚህን የሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣቶች አፍሶ ሲያስር አንዳችም ህጋዊ ምክንያት አልነበረውም፣ የፖሊስ ሕገ ወጥ ተግባር በዚህ ሳያቆም የታሰሩ የትግል አጋሮቻቸው የሚገኙበትን ቦታና ሁኔታ ለማወቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄዱ የፓርቲው አመራር አባላትንም አሰረ፡፡ ዋስትና ለማስከልከል አይደለም ለክስ የሚያበቃ ምንም ምክንያት ሳይኖረው ለፍ/ቤት ምርመራየን አልጨረስኩም የግዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ በማለት አባላቱ ለአስር ቀናት በጣቢያ እስር እንዲጉላሉ በማድረግ ሕግን ለማስከበር ሳይሆን የፖለቲከኞችን ፍላጎት ለማስፈጸም የቆመ መሆኑን በተግባር አረጋግጠ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ይህንን ሕገ መንግሥቱን በግልጽ የጣሰ የፖሊስ ተግባር በጽኑ እያወገዘ፣ፖሊስ የግለሰቦች ሥልጣን ጠባቂ ሳይሆን ሕግ አስከባሪ መሆኑን በተግባር እንዲያሳይ ይጠይቃል፡፡
2. የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 19/4 «የያዛቸው የፖሊስ መኮንን ወይም ህግ አስከባሪ በጊዜው ገደብ ፍርድ ቤት በማቅረብ የተያዙበትን ምክንያት ካላስረዳ ፍርድ ቤቱ የአካል ነጻነታቸውን እንዲያስከብርላቸው የመጠየቅ ሊጣስ የማይችል መብት አላቸው፡፡» ተብሎ የተደነገገውንእንዲያቀርቡ አዟል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምር ፍርድ ቤቱ ለህግ የበላይነት የሚሰራና በመተላለፍ ታሳሪዎቹን የዋስትና መብት ከልክሎ ለሁለት ግዜ ለፖሊስ የግዜ ቀጠሮ የፈቀደው ፍርድ ቤት፣ የእኔ ሥልጣን አይደለም መደበኛ ፍርድ ቤት አቅርቡዋቸው በማለት ካሰናበት በኋላ የምርመራ መዝገቡ ለክስ አይበቃም ተብሎ በአቃቤ ሕግ ውድቅ የተደረገበት ፖሊስ መልሶ እዛው ፍርድ ቤት ሲያቀርባቸው እያንዳንዳቸው 1300 ብርና የሰው ዋስ በጣምራ ለፍትህ መከበር የቆመ አለመሆኑን በተግባር ያረጋገጠበትን ይህን ተግባር እያወገዘ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 79/2 «በየትኛውም ደረጃ የሚገኝ የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግሥት አካል፣ከማንኛውም ባለሥልጣን ሆነ ከማንኛውም ሌላ ተጽዕኖ ነጻ ነው» እንዲሁም በአንቀጽ 79/3 ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነጻነት ያከናውናሉ፣ከሕግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም »ተብሎ የተደነገገው በተግባር እንዲገለጽ አጥብቆ ይጠይቃል፡፡
3. የፓርቲያችን ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ወደ አሜሪካ የሚያደርሳቸውን አስፈላጊ የጉዞ ሰነድ አሟልተው ሻንጣቸው አውሮፕላን ላይ ካስጫኑ በኋላ ፓስፖርታቸው በደህንንት ኋይሎች ተቀዶ ጉዞአቸው እንዲስተጓጎል ተደርጓል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ይህን ሕገ ወጥ ብቻ ሳይሆን እጅግ አሳፋሪ የሆነና የደህንነት ክፍሉን ብቻ ሳይሆን የአየር መንገዱንም ስም የሚያጎድፍ ተግባር በጽኑ እያወገዘ ድርጊቱን በፈጸሙት ማን አለብኝ ባዮች ላይ ከሕግ በላይ ሊሆኑ እንደማይችሉ የሚያሳይ ሕጋዊ ርምጃ አንዲወሰድ እንጠይቃለን፡፡ 4–መንግሥት ለዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብት ጥያቄ እስራት አፈናና ማስፈራራት ምላሽ እንደማይሆን ከታሪክ በመማር ለዜጎች የመብት ጥያቄ ትክክለኛውን ምላሽ እንዲሰጥና ትግሉ ሰላማዊ፣ ዓላማው ሕዝባዊ ግቡ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን ማድረግ ከሆነው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ የጥፋት እጁን እንዲያነሳ አጥበቀን እንጠይቃለን ፡፡
መጋቢት 14/2006 ዓም አዲስ አበባ

Sunday, March 23, 2014

ወላይታ ሶዶ ነፃነት አልባዋ የማፊያ ካድሬዎች ከተማ!!!

March 23/2014

ከወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የእስርና እንግልት ማብራሪያ

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ በደቡብ ቀጠና በወላይታ ዞንና በሲዳማ ዞን አዋሳ ከተማ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የፓርቲውን የትግል ስትራቴጅክ ዕቅዶች ላይ ማብራሪያ፣ ደንብና ፕሮግራም ለመስጠት እንዲሁም የስራ ጉብኝት ለማድረግ በ 12/07/06 ወደ ወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ተገኝተው ነበር፡፡ በ13/07/06 ደግሞ ከሶዶ ከተማ ስራ አስፈፃሚና ከወረዳ አመራር አባላት ጋር የፓርቲያችንን ደንብ፣ ፕሮግራምና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ አስመልክቶ የተሰናዳው ውይይት ላይ ለመታደም ከ32 በላይ አመራሮችም ተገኝተው ነበር፡፡

ቅዳሜ በ 13/07/06 ዓ.ም ከአባላት ጋር ባለው ዕቅድ መሰረት የፓርቲያችንን ህጋዊ ሰነዶችን ለወረዳና ለዞን አመራሮች ለመስጠት፣ ቀጣዩን ሀገራቀፍ ምርጫ አስመልክቶ መረጃ ለመለዋወጥ ምርጫችን የነበረው የፓርቲያችን አባል የሆነውና ወጣ ብሎ ፀጥታ የሰፈነበት ግቢ ነበር፡፡ ይህንን ለማድረግ ህገ መንግስታዊ መብት ነበረን፡፡ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የፖለቲካ ደንብና ፕሮግራማቸውን ለዞንና ለወረዳ አመራሮች ለማስጨበጥ ፈቃድ እንደማያስፈልግ ጠንቅቀን እናውቅም ነበር፡፡

በተለይም ሃለማሪያም ደሳለኝ በሞግዚትነት ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ወላይታ ሶዶ ነፃነት አልባ ከተማ እንደሆነች ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ ወላይታ በካድሬ ተወጥራለች፡፡ ዝርዝሩን በቀጣይ እንደምናቀርብ ቃል እየገባን ለአሁን በእኛ ላይ የደረሰውን በቅንጭቡ እንደሚከተለው ለኢትዮጵያ ህዝብና ለታሪክ እናቀርባለን፡፡

1. 32 የሚሆኑ አንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራሮች የተሰባሰቡት ከላይ በገለፅነው አላማና ህገ መንግስታዊ መብታችንን ተጠቅመን ቢሆንም ለውይይት ቅድመ ዝግጅት ስናደርግና ውይይቱን ለመጀመር ስንዘጋጅ መታወቂያ የሌላቸው ከ 8-10 የሚሆኑ ጡንቻቸው የፈረጠመ ግለሰቦች እንደ ኮማንዶ ለውይይት የተገናኝበትን የአባላችንን ጊቢ ሰብረው በመግባት የያዝናቸውን የፓርቲ ሰነዶች፣ ሳምሰንግ ጋላክሲ ስልኮችና ያገኙትን ሁሉ ዘርፈው ሂደዋል፤ አመራሮችን ደብድበዋል፡፡

2. እነዚሁ ደብዳቢዎች ታርጋ ቁጥር በሌላቸው ሞተሮች በመታጀብ ፖሊስ ይዘው በመምጣት ፕሮግራማችንን ለማደናቀፍ በሃይልና በጉልበት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደውናል፡፡

3. ፖሊስ ጣቢያውም እኛን የደበደቡንንና ንብረታችንን የቀሙንን ሲቢል ለባሽ ካድሬዎች በመልቀቅ የአንድነት ፓርቲ 20 አመራሮችን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሻለቃ ላሊሼ ኦሌ ቢሯቸው አስገብተው ችግሩን እንደሚቀርፍ አመራር ካነጋገሩንና ቃላችንን ከተቀበሉ በኋላ ሞባይሎቻችንን በመንጠቅ እንድንታሰር አድርገዋል፡፡

4. የእስሩ ሰዓት ከቀኑ 5፡00 ጀምሮ ነው፡፡ እንድ ቀፋፊና አስቀያሚ ማጎሪያ ውስጥ ካስቀመጡን በኋላ ከምሽቱ 2፡00 ላይ ህገወጥ ስብሰባ አድርጋችኋል በማለት ቃል ስጡ የሚል ምዝገባና ህገ ወጥ ስብሰባ እንዳደረግን እንድንመሰክር ለማስገደድ ቢሞክሩም እኛ መብታችንን እንደተጠቀምን እንጂ እነሱ እንደተረጎሙት ህገ ወጥ ስብሰባ እንዳላደረግን ሀቁን ስንነግራቸው እንዲሁም ሀሰትን ከመቀበል መታሰር እንደሚቻል የአንድነት አባላት ቁርጠኛ እንደሆንን ሲያውቁ ግራ ተጋብተው የበላይ አካል እስከሚያረጋግጥላቸው ጠብቀው ከእኩለ ለሊት በኋላ (ከምሽቱ 6፡30) በኋላ በእስር ላይ የቆዩ ከ20 በላይ ከፍተኛ አመራሮች እንዲወጡ ተደርጓል፡፡ ይሄ የሆነው ለመፍታት ታስቦ ሳይሆን ከወረዳ የመጡ አባላት ማደሪያ ቦታ እንዲያጡና ለአደጋ እንዲጋለጡ በማሰብ ነው፡፡

5. ስንታሰር ከተዘረፉ ሞባይሎች ውጭ በፖሊስ ጣቢያ አዛዡ ተይዞ የነበረው የታሳሪዎች ሞባይል ባልታወቀ ነገር ተነክሮ ከአገልግሎት ውጭ ተደርጓል፡፡ ሞባይላችን የተነከረውና ከጥቅም ውጭ የተደረገው በኬሚካል ይሁን በሌላ ነገር አልተረጋገጠም፡፡ የማንኛችንም ሞባይል ግን ከጥቅም ውጭ ሁኗል፡፡ ይሄ የሆነው የፖሊስ አዛዡ አቶ ላሊሼ ቢሮ የታሰረ ሞባይላችን ነው፡፡

ነገ ምን እንደሚገጥመን ማወቅ አይቻልም፡፡ ያረጋገጥነው ነገር ቢኖር ወላይታ ሶዶ ነፃነቷን የተነፈገች፣ በታርጋ አልባ ሞተሮች የምትታመስና ምንም ዋስትናና ህግ የሌለባት ከተማ መሆኗን ነው፡፡ ስለዚህ ነፃነት አልባዋ ወላይታ ነፃ መውጣት አለባት!!!
የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር አባላት ከምሽቱ 9፡00 ሠዓት



ሶዶ ከተማ

ከሰው ለሰው ድራማ የሚገኘው ገቢ ለማንም እንዳይከፈል በፍርድ ቤት እግድ ተጣለበት

March23/2014

በየሳምንቱ ረቡዕ ማታና በድጋሚ ቅዳሜ ላለፉት 127 ሳምንታት በመተላለፍ ላይ ካለው ‹‹ሰው ለሰው›› ድራማ የሚገኘው ማንኛውም ዓይነት ገቢ ለማንም እንደይከፈል፣ መጋቢት 2 ቀን 2006 ዓ.ም. በፍርድ ቤት ዕግድ ተጣለበት፡፡


ክፍያው እንዳይፈጸም በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የግልግል ዳኞች ክልከላ የተጣለባቸው፣ አቶ መስፍን ጌታቸው (በአሁኑ ጊዜ የድራማው ፕሮዲዩሰርና ዳይሬክተር) አቶ ሰለሞን ዓለሙ (ስክሪፕት ጸሐፊ ተዋናይ)፣ አቶ ነብዩ ተካልኝ (የኢትዮ ኢንተር ኤጁኬት ፕሮሞሽን ባለቤት)፣ የአቶ ዳንኤል ኃይሌና የአቶ ሰለሞን ዓለሙ ስፓርክ ፊልም ፕሮዳክሽን የሚባለው ድርጅት ናቸው፡፡

የግልግል ዳኞቹ የዕግድ ትዕዛዙን ያስተላለፉበት ምክንያት፣ የሰው ለሰው ድራማ ፕሮዲዩሰርና በድራማው ‹‹ናርዶስ›› የምትባለውን ገጸ ባህሪ ወክላ የምትተውንና በፋይናንስና አድሚኒስትሬሽን ኃላፊነት ትሠራ ከነበረችው ወ/ሮ ብሥራት ገመቹ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ክስ በመመሥረቱ መሆኑን የዕግድ ትዕዛዙ ያስረዳል፡፡

ወ/ሮ ብሥራት ገመቹ፣ አቶ ነብዩ ተካልኝ፣ አቶ መስፍን ጌታቸው፣ አቶ ሰለሞን ዓለሙና አቶ ዳንኤል ኃይሌ ታኅሣሥ 22 ቀን 2003 ዓ.ም. በሰነዶችና ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤት ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ለማዘጋጀት ተስማምተው የሽርክና ውል መፈራረማቸውን የክስ ማመልከቻው ያስረዳል፡፡

ቀድሞ ‹‹የመጨረሻው ሰሞን›› የሚል ስያሜ ሰጥተውት የነበረውን ድራማ ‹‹ሰው ለሰው›› በማለት ሰይመው ለመሥራት ሲስማሙ፣ ወ/ሮ ብሥራትና ሦስቱ ተከሳሾች የትርፍ ክፍፍላቸውን በመቶኛ እንደየተሳትፏቸው ለመከፋፈል ተስማምተው መፈራረማቸው በሰነዶቹ ላይ ተጠቅሷል፡፡

ኢትዮ ኢንተር ኤጁኬት ፕሮሞሽን በተባለው የአቶ ነብዩ ተካልኝ የንግድ ድርጅት ፈቃድ፣ ከኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጋር ውል ተፈራርመው ‹‹ሰው ለሰው›› ድራማን በመሥራት ላይ እያሉ፣ ንግድ ፈቃዳቸውን ሲያድሱ የአቶ ሰለሞን ዓለሙ ድርጅት መሆኑ በተጠቀሰው ስፓርክ ፊልም ፕሮዳክሽን በሚል ድርጅት ስም በማደስ፣ ከሳሽ ወ/ሮ ብሥራት የትርፍ ተካፋይ የማትሆንበት አሠራር መጀመሩን ክሱ ይገልጻል፡፡  22 ማዞሪያ አካባቢ በሚገኘው ቡና ባንክ ቅርንጫፍ አቶ ሰለሞን ዓለሙና አቶ መስፍን ጌታቸው በጋራ ሒሳብ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበርም የክሱ አቤቱታ ይጠቁማል፡፡

ለድራማው ቀረፃ ቤቷንና መኪናዋን በማቅረብ ተባብራ ስትሠራ የነበረችው ከሳሽ ወ/ሮ ብሥራት ድራማው ከተጀመረ ጀምሮ በፕሮዲዩሰርነት፣ በፋይናንስ አድሚኒስትሬሽን በወር አምስት ሺሕ ብር ተከፍሏትና ‹‹ናርዶስ›› የተባለችውን ገጸ ባሕሪ ወክላ ትሠራ እንደነበርም ለፍርድ ቤት ያቀረበችው ሰነድ ያብራራል፡፡

በመሆኑም በኃላፊነትም ሆነ በተዋናይነት እንዲሁም ከትርፍ ሊከፈላት የሚገባው ክፍያ ሳይፈጸምላት፣ ለጊዜው በግልጽ መግለጽ በማትፈልገው ምክንያት ከአንዱ ተከሳሽ ጋር አለመግባባት በመፈጠሩ፣ ከድራማው 54ኛ ክፍል ጀምሮ ‹‹ናርዶስ››ን ሆና ትተውንበት የነበረውን ገጸ ባህሪ መነጠቋን፣ ከ90ኛው ክፍል ጀምሮ ደግሞ ከፕሮዲዩሰርነቷ መሰረዟን በክሷ ለፍርድ ቤቱ አስረድታለች፡፡ ከድራማው 26ኛ ክፍል ጀምሮም የገቢ ክፍፍል እንዳልተፈጸመላት አክላለች፡፡

አቶ መስፍንና አቶ ሰለሞን ከተለያዩ ስፖንሰሮችና ከኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት መጠኑን ያላወቀችው ክፍያ እያሰባሰቡ ለግል ጥቅማቸው እያዋሉት መሆኑን፣ አቶ ዳንኤል የተባሉት ተከሳሽም የጥቅም ተጋሪ መሆናቸውን አስረድታ፣ 100 ሺሕ ብር በካሽ አዋጥታ ካቋቋመችው የድራማ መድረክ በዕውቀትና በዓይነት ከሰጠችው አገልግሎት በላይ ሞራል የሚነካ (ለኢትዮጵያ ሕዝብ ክብር ሲባል የማይገለጽ) ተግባር እንደተፈጸመባት በክሷ ዘርዝራ አቅርባለች፡፡

ከሳሽ ወ/ሮ ብሥራት ከቴሌቪዥን፣ ከማስታወቂያና ከስፖንሰሮች ከተሰበሰበውና የአገር ውስጥ ገቢ ተቀንሶ የሚደርሳት 16.25 በመቶ ድርሻዋ በወራት ተባዝቶ ከነወለዱ እንዲከፈላት፣ በፋይናንስና አድሚኒስትሬሽን ለሠራችበት በወር የሚከፈላትን አምስት ሺሕ ብር በ35 ወራት ተባዝቶ እንዲከፈላት፣ ‹‹ናርዶስ›› የምትባለውን ገጸ ባህሪ ወክላ ለተወነችበት 56 ክፍሎች በ500 ብር ታስቦ በድምሩ 163 ሺሕ ብር እንዲከፈላት ዳኝነት ጠይቃለች፡፡

የከሳሽን አቤቱታ ዝርዝር ማብራሪያ የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ምድብ ሁለተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት በሰጠው ብይን፣ ከሳሽና ተጠሪዎች እያንዳንዳቸው አንድ ዳኛ እንዲመርጡ፣ የግራ ቀኙን ተከራካሪ የሚሰበስብ ዳኛ በጋራ እንዲመርጡና በሽምግልና ዳኝነት እንዲታይ የተወሰነ ቢሆንም፣ በአንድ ወር ውስጥ መምረጥ ባለመቻላቸው በፍርድ ቤቱ ሬጅስትራር በኩል የግልግል ዳኛ እንዲሾም አዞ ነበር፡፡

የግልግል ዳኞች በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አቤቱታ በመመርመር ላይ ቢሆኑም፣ ከሳሽ ወ/ሮ ብሥራት የግልግል ዳኝነቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከድራማው የሚገኘው ገቢ እንዲታገድላት ለግልግል ዳኞቹ ማመልከቻ በማቅረብዋ፣ የግልግል ዳኞቹ በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 154 መሠረት ክርክሩ እልባት እስከሚያገኝ፣ ለተጠቀሱት ተከሳሾችም ሆነ ለሦስተኛ ወገን ምንም ዓይነት ክፍያ እንዳይፈጸም የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥንን ድርጅት ታዟል፡፡ 

የአንድነት የወላይታ ዞን ምክር ቤት ስብሰባን የመለስን ቲቨርት የለበሱ የመንግስት ካድሬዎች በኃይል አደናቀፉት

March 21/2014

የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋ ላይ ነው፡፡
የሟቹን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ ምስል ያለበት ቲሸርት የለበሱ ከ 10 የሚልቁ የመንግስት ካድሬዎች በወላይታ ሶዶ እየተደረገ የነበረውን አንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክርቤት ስብሰባን በሀይል ማደናቀፋቸውን ከስፍራው ለፍኖተ ነጻነት የደረሰው ዘገባ አመለከተ፡፡

ካድሬዎቹ የስብሰባ አዳራሹን በሃይል በመስበር ከተሰብሳቢዎቹ ላይ የተለያዩ ሰነዶችን የቀሙ ሲሆን ብብደባ በመፈፀም ላይ ናቸው፡፡ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ የነበሩት የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋላይ መሆኑን ለፍኖተ ነፃነት ተናግረዋል፡፡

Ethiopia: In Accepting Ethiopia, Transparency Group ‘Sacrifices Credibility’ BY CAREY L. BIRON

March22/2014

Washington — A major international initiative aimed at promoting transparency in the extractives industry is coming under harsh criticism for accepting an application from Ethiopia, despite significant ongoing legal restrictions on the country's civil society.

The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI), a standards programme based in Oslo, had declined a previous application for candidature from Ethiopia, in 2010.


The previous year, the Ethiopian government had passed a law widely seen as repressive, and the EITI board stipulated that the country's application would be deferred until that law was struck down.

Yet despite the fact that the law remains in place, on Wednesday the EITI board voted to accept Ethiopia's application to become a candidate for full membership in the organisation. Some say the group has now violated its own rules.

"We're very disappointed by this. If these people don't follow the criteria, what's the point of having criteria?" Obang Metho, executive director of the Solidarity Movement for a New Ethiopia, a Washington-based advocacy group, told IPS.


"Today it is impossible for civil society to function in Ethiopia, because of this bill. We can wait for years for changes, but as long as the current government is there I can't foresee any tangible change. This decision [by EITI] is not going to be productive."

The law in question is known as the Charities and Societies Proclamation (CSP). Ethiopia's first comprehensive legislation to regulate the registration of civil society groups, the law places onerous restrictions on groups that receive more than 10 percent of their funding from foreign sources.

It also forbids organisations from engaging in a range of activities central to ensuring public oversight over the government and its officials.

The United Nations has warned that the law has "devastating" ramifications for the ability of Ethiopians to effectively form and operate civil society organisations.

Such concerns are particularly relevant for EITI, which, since its founding in 2003, has offered a unique platform for cooperation between the extractives industry, government and civil society.

Importantly, each of these elements is to receive equal voice within the EITI system, with the immediate aim of sector-specific transparency meant to translate into broader strengthening of good governance.

Thus, if the civil society component isn't able to function effectively, the entire process would cease to function. That, anyway, was EITI's own concern in 2010, when it rejected Ethiopia's application - the first time the board had ever taken such an action.

The EITI "board concluded that Ethiopia's [CSP] would prevent civil society groups from being sufficiently independent and meaningfully participate in the process," Anthony Richter, a member of the EITI board, stated in 2010. "The board decided, in effect, not to admit Ethiopia 'until the [CSP] is no longer in place'."

The EITI board made another high-visibility decision on Wednesday, voting to accept the candidature application of the United States (as well as that of Papua New Guinea). Yet if EITI has gone back on its own rules, critics say, the standard's important overall potential will have been weakened.

"Before this decision, EITI was a prominent global initiative, considered to be one of the leading efforts to increase transparency and give citizens a chance to have a voice in important matters in their countries," Lisa Misol, a senior business and human rights researcher at Human Rights Watch (HRW), a watchdog group, told IPS.

"Now I think all governments need to ask themselves what's the value of being part of an initiative that allows in a country that doesn't allow its citizens to make any use of this transparency. Unfortunately, EITI has sacrificed its credibility and irreparably harmed its own reputation."

Neutered criteria

EITI currently lists 26 countries as compliant with its standards, and another 18 countries, including Ethiopia and the United States, as candidates. In total, 35 countries have produced formal EITI reports over the past decade.

Yet the decision to move forward with and approve Ethiopia's application during this week's EITI meeting reportedly led to deep divisions in the group's board.

While the EITI secretariat did not respond to a query from IPS, it has been quick to note that acceptance of Ethiopia's application to become a candidate country means that the Ethiopian government now has three years to come into full compliance with EITI's standards.

"Some opposed this decision, but it should be remembered that becoming a candidate does not mean that any country has met the EITI Standard," Clare Short, the EITI chair, said in a statement after the board's meeting.

"In the case of Ethiopia, the decision shows that the Board was convinced by the government's commitment to the EITI's principles.

Membership of the EITI will mean that all stakeholders, including civil society, will have a better platform to hold the government and the companies to account and ensure the better management of the burgeoning sector."

For its part, the Ethiopian government states that it has already set up a national steering committee made up of government, industry and civil society representatives, and has begun a series of trainings on the EITI standards. Its most recent application, from October, also deals directly with concerns over the CSP.

"In our view, the proclamation is not meant to restrict the operation of the civil society," an introductory letter, presumably written by Minister of Mines Sinknesh Ejigu, states, "rather to create conducive environment for their activities as well as ensure transparency and accountability, establish a legal framework for their operation."

Yet critics are pushing back strongly against the suggestion that EITI will now have more leverage to effect positive change in Ethiopia.

"The simple fact is that the EITI process won't be able to advance any improvements unless civil society is at the table and has a voice," HRW's Misol says.

"It's shocking to me that the board of an initiative that values civic participation has just endorsed Ethiopia as a candidate when there is no ability to have a functioning civil society in that country. The moment of leverage was before joining Ethiopia to join the club - not once it's in. In effect, EITI has now neutered its own civil society criteria."

Ethiopia will now be required to submit its first formal report to EITI by March 2016.

More on This
Govt Approved for Membership Contrary to Extractive Industries Rules
A prominent international natural resource transparency group has damaged its credibility by approving membership for … see more »

Saturday, March 22, 2014

“ውሃ፣ መብራት፣ ኔትዎርክ የለም ፤ ኑሮ ከበደን” ሰሚ ጆሮ ያጣ የሕዝብ እሮሮ

March22/2014

“ውሃ የለም፤ መብራት፤ ኔትዎርክ የለም፤ መብት የለም፤ ፍትህ የለም፤ ኑሮ ከበደን” እያሉ ስለኑሮዓቸው የተሰማቸውን በሀቅ የተናገሩ ልጃገረዶች በጋጠወጥ የህወሓት ካድሬዎችና ታጣቂዎች እጅ መከራና ስቃይ እየደረሰባቸው ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በእነዚህ ለጋ ወጣቶች ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በዝምታ ያልፋል ተብሎ አይታመንም።
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮን ጨምሮ በወያኔና የጥቅም ተጋሪዎቹ ሥር የሚተዳደሩ መገናኛ ብዙሃን በየዕለቱ ያለማቋረጥ ከሚዘገቡት የልማትና የዕድገት ዘገባዎች ከፍተኛውን ስፍራ የሚይዘው በአገራችን ውስጥ እየተሠሩ ስላሉ ትላልቅ የሃይድሮ ኤለክትሪክ ማመንጫ ግንባታዎች፤ በየከተማው ስለተዘረጉ የውሃ መስመሮች፤ የስልክ አገልግሎት ለማዳረስ ስለተወሰዱ እርምጃዎች፤ ስለ ረጃጅም የባቡር መስመሮች ግንባታ እና ስለ አገር አቋራጭ የመንገድ ሥራዎች የሚቀርቡ የተጋነኑ ዘገባዎች ናቸው።
እነዚህ የልማት አውታሮች ግንባታ በአብዛኛው የሚካሄዱት ከምዕራባዊያን መንግሥታት በሚሰጡ የገንዘብ እርዳታና ዕዳው ለልጅ ልጆቻችን በሚተርፍ አለም አቀፍ የገንዘብ አበዳሪ ድርጅቶች ወለድ እያስከፈሉ በሚሰጡት የረጅም ጊዜ ክፍያ ብድር እንደሆነ ግልጽ ነው።
ወያኔ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 23 አመታት በድህነት ቅነሳና የልማት ማስፋፊያ ስም ከአለም አቀፍ ኅብረተሰብ የተቀበለው የገንዘብ መጠን ሲሰላ ኢትዮጵያ አገራችን እንደ አገር ከተመሰረተችበት ዘመን ጀምሮ በብድርም ሆነ በእርዳታ ስም ይህንን ያህል መጠን ገንዘብ አግኝታ እንደማታውቅ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ ። በዚህም መሠረት ገንዘቡ በአግባብ ሥራ ላይ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አገራችን የትና የት በደርሰች ነበር እያሉ የሚቆጩ የአገሪቱ ልሂቃንና ቅን አሳቢ ዜጎች ቁጥር ቀላል አይደለም ።
የተባበሩት መንግሥታት የልማት ድርጅት ከ3 አመት ገደማ በፊት ይፋ ባደረገው አንድ መረጃ ወያኔ ሥልጣን በተቆጣጠረባቸው የመጀመሪያዎቹ 9 አመታት ብቻ ከ11.5 (አሥራ አንድ ነጥብ አምስት ) ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በህገወጥ መንገድ ከአገር አሽሽቶ በምዕራባዊያን አገሮች ባንኮች ደብቆአል ። ይህ ከደሃው ጉሮሮ ተቀምቶ በባለሥልጣናቱ የተዘረፈና በህገወጥ መንገድ ከአገር የሸሸው 11.5 ቢሊዮን ዶላር በትክክል ልማት ላይ ውሎ ቢሆን ኖሮ ወያኔዎች “ባለ ራዕዩ መሪያቸን” በሚሉት ዘረኛው መለስ ዜናዊ ሥም ለመሰየም ደፋ ቀና የሚሉትን ጅምር “የህዳሴ ግድብ” አይነቱን ሁለት ግዙፍ ግድቦችን በመገንባት የአገሪቷን ገጽታ አበላሽቶ የኖረውን ረሃብ ከምንጩ ማጥፋት ይቻል ነበር።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከአገሪቱ የሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ፤ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ “ውሃ የለም፣ መብራት የለም፣ ኔትዎርክ የለም። የሚላስ የሚቀመስ ነገር ማግኘት ተስኖናል፤ ኑሮ ከአቅማችን በላይ ሆኖአል። ትዳር መስርተንና ልጆች ወልደን እያሳደግንበት ካለው የደሃ ጎጆዎቻችን በቀበሌ ካድሬዎች ትዕዛዝ ቤቶቻችን በዶዘር ላያችን ላይ እንዲፈርስ ተደርጎ ሜዳ ላይ ተበትነናል። ከአያት ቅድመ አያቶቻችን ጊዜ ጀምሮ እንገለገልበት ከነበረው የእርሻ ማሳችንና የግጦሽ መሬታችን ተነቅለን ዓይኖቻችን እያዩ ከህንድ፣ ከቻይናና ከአረብ አገር የመጡ ከበርቴዎች መሬታችንን ተቀራምተውታል። አቤት የምንልበት አጣን። ኑሮ መሮናል!!!” የሚሉ እሮሮዎች የወያኔ አፈና የፈጠረውን የፍርሃት ዝምታን ሰብሮ ከአጥናፍ አጥናፍ እየተሰማ ነው።
ይህንን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና እየከረረ የመጣውን የሕዝብ እሮሮ ለማዳመጥ ጆሮ ያልፈጠረበት የዘረኛው ህወሓት አገዛዝ ግን “ነጋ ጠባ የሚደሰኮረው ልማት ምድር ላይ ጠብ አላለልንም፤ መሠረታዊ ችግሮቻችን ከመፍታት ይልቅ እያባባሰ ያለው ምን የሚሉት ልማት ነው?” ብሎ የጠየቀውን ሁሉ “ፀረ-ልማት፣ ፀረ-ሰላም፣ ሽብርተኞ” የሚል ስም እየለጠፈበት ማሰር ማዋከብና ማሳደድ የዘወትር ተግባሩ አድርጎታል።
በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ አለም አቀፍ የሴቶች በዓል ሲከበር ይኸው የሕዝብን ብሶት ባስተጋቡት ወጣት እህቶቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ የዚህ የወያኔ አፈና እርምጃ ማሳያ ነው። “ብሶት የፈጠረኝ ነኝ” የሚለው ህወሓት፤ ብሶት እሱን ብቻ ፈጥሮ የመከነ ይመስለዋል።
ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔ እያካሄድኩ ነው በሚላቸው ትላልቅና ትናንሽ ግንባታዎች መጠነ ሰፊ ብዝበዛና ዘረፋ እያካሄደ መሆኑን የሚያጋልጡ በቂ መረጃዎች አሉት። የወያኔ ልማትና እድገት ማሳያ ተደርጎ ከሚጠቀሱ የኮንዶሚኒዬም ቤቶች ግንባታ አንስቶ በመላው አገሪቱ ለሚሠሩ የኮንስትራክሽን ሥራዎች በሙሉ የሚያስፈልጉ የግንባታ ዕቃዎች ስምንቶ፤ አሸዋና ብረታ ብረት የመሳሰሉትን የሚያቀርቡት በባለሥልጣናቱ ንብረትነት የሚታወቁና በቤተሰቦቻቸው ወይም የቅርብ ዘመዶቻቸው ስም የሚተዳደሩ የግል ድርጅቶች ናቸው። የግንባታዎቹን ሥራ ደግሞ የሚያካሂዱት በወያኔ ንብረትነት የሚታወቁ የኢፈርት ሥራ ተቋራጭ ድርጅቶች ናቸው። በዚህ አይነት ኮንትራት ሰጪ፤ ኮንትራት ተቀባይና ዕቃ አቅራቢ በመሆን በሚበዘበዘውና በሚዘረፈው የሕዝብ ሃብት የወያኔ ሹማምንትና ግብረ አበሮቹ እስከ ልጅ ልጆቻቸው በልተው የማይጨርሱትን ሃብት አግበስብሰዋል።
ይህ አልበቃ ብሎአቸውም አይናቸው ያረፈባቸው ቁልፍ የከተማ ቦታዎች ላይ የሰፈረውን ደሃ ሕዝብ በማፈናቀልና ጎዳና ላይ በመበተን ረጃጅም ፎቆችን እየሰሩ በማከራየት ሥራ ላይ ተጠምደዋል። ከአመታት በፊት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በአነስተኛ ንግድ የተሰማሩ በርካታ ዜጎች የያዙትን ቦታ ለማስለቀቅ ሆን ተብሎ ንብረታቸው በእሳት እንዲወድም ተደርጎአል። በሕይወት ዘመናቸው ያፈሯት ሃብት በእሳት እንዲጋይባቸው የተደረጉ ዜጎች አቤት የሚሉበት ስላልነበራቸው ሥራ አጥና የጎዳና ተዳዳሪ ለመሆን ተገደዋል። ባለፈው ሁለት ሳምንት ተመሳሳይ እርምጃ ሀረር ከተማ ውስጥ በአነስተኛ ንግድ በተሰማሩት ወገኖቻችን ላይ ደርሶ እንባ ሲራጩ ተመልክተናል።
ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔ በልማት ስም በወገኖቻችን ላይ የሚፈጽመውን የማፈናቀል ዘመቻ ማስቆም የእያንዳንዳችን ግዴታ ነው ብሎ ያምናል። ሕዝባችን በጨለማ እየተሰቃዬ ከደጃችን የሚመረት የመብራት ኃይል ወደ ጎረቤት አገር እየተላከ ለማይጠረቃው የወያኔ ሃብት የማጋበስ ጥማት ማርኪያ መሆን ማስቆም የምንችለው እኛው ብቻ ነን። ወገኖቻችን በረሃብ አለንጋ እየረገፉና ነፍሰ አድን የምግብ እርዳታ ከፈረንጅ በምጽዋት እየተቸረን በምድራችን የሚመረት እህል ባህር አቋርጦ ለባለጸጋ አገሮች ገቢያ ሲውል አይተን እንዳላየን ማለፉን ማስቆም የኛ ተግባር ነው። ዕዳው ለልጅ ልጆቻችን የሚተርፍ የብድር ገንዘብ በየአመቱ አገር ውስጥ በገፍ እየገባ እናቶችና ህፃናት በንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት መሰቃየታቸውን ማስቆም የምንችለው እኛው ነን። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህፃናት በቂ የትምህርት እድልና የጤና አገልግሎት የሚያገኙበት ገንዘብ በሙስናና በሌብነት በተጨማለቁ የአገዛዙ ሹመኞች መዘረፉን ማስቆም ያለብን እኛው ነን።
“ውሃ የለም መብራት የለም ኑሮ ከአቅማችን በላይ ሆኖ መኖር አቅቶናል” የሚለውን የወገን እሮሮ ያሰሙ ልጃገረዶችን ድምጽ መስማት ግዴታችን ነው። የእነዚህ ወጣቶች አርዓያነትን በመቀበል ዛሬውኑ የትግሉን ጎራ በመቀላቀል እብሪተኛውንና ዘረኛውን የወያኔ አገዛዝ ፍጻሜ በማፋጠን ነፃነታችንን እንድንጎናጽፍ ግንቦት 7 የትግል ጥሪውን ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ግብፅ አፄ ምኒልክ በተፈራረሙት ውል እየተከራከረች ነው

March 22/2014

ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለችው የታላቁ የህዳሴ ግድብ አፄ ምኒልክ በ1902 ከእንግሊዝ ጋር የተፈራረሙትን ውል የሚጥስ ነው ሲል የግብፅ መንግስት ቃል አቀባይ ቢሮ መግለጫ ያወጣ ሲሆን አፄ ምኒልክ ውሉን ሲፈራረሙ የውሀውን ፍሰት አናቆምም እንጂ አንጠቀምበትም በሚል እንዳልተስማሙ ሰነዶች ያመለክታሉ፡፡

 የቃል አቀባይ ቢሮው ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአባይ ላይ እየገነባች ያለችው ግድብ በ1902 በእንግሊዝ እና በአፄ ምኒልክ የተፈረመውን የሚጥስ ነው፣ አፄ ምኒልክ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ተብለው ስልጣን ላይ ከወጡ በኋላ ከእንግሊዝ ጋር በተፈራረሙት ውል መሰረት ከእንግሊዝ እና ሱዳን ፈቃድ ውጪ  ኢትዮጵያ በአባይ፣ በጣና ሀይቅ እና በሶባት ላይ ምንም አይነት ግንባታ እንደማታደርግ እና ለመንባት የሚሞክሩ ወገኖችንም እንደምትከለክል ተስማምታለች፤

ስለዚህ የአሁኑ ግንባታ ስምምነቱን ይጥሳል ብሏል፡፡ በአለም አቀፍ ህግ የውሀ ባለሙያ የሆኑት አቶ እምሩ ታምራት ጉዳዩን አስመልክተው ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ በመጀመሪያ ደረጃ ግብፅ የ1902 ስምምነት አካል ስላልሆነች፤ ይህን ስምምነት በመከራከሪያ ማንሳት አትትችልም፤ ሌላው የስምምነቱ  የአማርኛ ትርጓሜ  “ኢትዮጵያ ውሃውን ሙሉ በሙሉ የሚደፍን ስራ አትሰራም ይላል እንጂ ጥቅም ላይ አታውል” ብላ አልተስማማችም፡፡

አዲስ አድማስ


ከአሜሪካ የመጡ የሙስሊም ምሁራን የታሰሩ ሙስሊሞችን ከመንግስት ጋር ያደራድራሉ

March 22/2014

 በአሜሪካ አገር ‹‹በድር ኢትዮጵያ›› የተሰኘውን የሙስሊም ማህበር የሚመሩ ምሁራንና ታዋቂ ሰዎች፤ የታሰሩ ሙስሊሞችን ከመንግስት ጋር ለማሸማገል በኢትዮጵያ መንግስት ፈቃድ ሰሞኑን አዲስ አበባ መግባታቸው ተነገረ።

በአወሊያ ትምህርት ቤት ሰበብ የተቀሰቀሰው ውዝግብ ቀስ በቀስ እየተካረረ፤ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫም የመወዛገቢያ ነጥብ ወደመሆን እንደተሸጋገረ የሚታወስ ሲሆን፤ በ2004 ዓ.ም በርካታ የተቃውሞ ሰልፎች ከተካሄዱ በኋላ ነው፤ በሐምሌ ወር ሃያ ዘጠኝ ሰዎች ታስረው ክስ የተመሰረተባቸው፡፡ ታህሳስ 2006ዓ.ም. አስሩ ታሳሪዎች የሚያስከስስ ጥፋት የለባቸውም ተብለው በፍ/ቤት ቢለቀቁም የአስራ ዘጠኝ ታሳሪዎች ክስ በፍ/ቤት እየታየ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ በሚል ስያሜ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ታሳሪዎች፤ “የአወሊያ ት/ቤት ራሱን ችሎ መንቀሳቀስ አለበት፤ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫ በተጽእኖ ስር የተከናወነ ነው” በማለት ተቃውሞ ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡ የአወሊያ ት/ቤትን ተገን በማድረግ አክራሪነትን ለማስፋፋት እንቅስቃሴ ሲደረግ ነበር የሚለው መንግስት በበኩሉ፤ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ምርጫ በአግባቡ አልተከናወነም የሚለው ተቃውሞ፤ ግጭት ለመቀስቀስ ታስቦ የተዘጋጀ መሰረተ ቢስ ውንጀላ ነው ይላል፡፡

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ ባለው የክስ ሂደት አስራ ዘጠኙ ተከሳሾች በአቃቤ ህግ ለቀረበላቸው የክስ ማስረጃ መከላከያ እንዲያቀርቡ የታዘዙ ሲሆን ከሚቀጥለው ማክሰኞ ጀምሮ ለ15 ቀናት በተከታታይ መከላከያ ያሰማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በዚህ መሃል ነው፤ በሽምግልና ታሳሪዎቹን ሊያስፈቱ ይችላሉ የተባሉ ታዋቂ ሙስሊሞች ሰሞኑን ከአሜሪካ የመጡት፡፡
‹‹በድር ኢትዮጵያ›› የተሰኘው ማህበር መሪዎችና አባላት የሆኑት እነዚሁ ሙስሊም ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች አዲስ አበባ የገቡት በመንግስት ፈቃድ እንደሆነ የገለፁልን ምንጮች፤ ታሳሪዎችን ያነጋግራሉ ብለዋል፡፡

BREAKING NEWS: Semayawi party chairman barred from boarding flight to the US.

March 21, 2014
(9:05 PM EST) Update: Semayawi Party Chaiman, Eng Yilkal Getnet was barred from boarding his flight to the United States on Friday, March 21, 2014 at Addis Ababa airport. He was scheduled to fly to the US to attend a fellowship program of the Young African Leaders Initiative of the United States State Department. Eng. Yilkal was told to see a TPLF supervisor by airport crew right before boarding time where he was told he would not be flying. His luggage was unloaded from the plane and he stayed at the airport for more than 3 hours thereafter questioned by TPLF agents. He has returned back to his home after 2:00am local time Saturday.
Semayawi Party
———————————————
(9:00PM EST) Eng. Yilkal Getnet, Chairman of the Blue Party (semayawi party) was barred from boarding a plane to the US by TPLF (Ethiopian government security) agents at Bole Airport tonight, March 21, 2014.
Eng. Yilkal was coming to the US as a fellow under “Young African Leaders Initiative” of the United States govt.
Eng. Yilkal’s luggage were unloaded from the plane and he stayed at the airport for more than 3 hours questioned by TPLF thugs.
Stay tune for more updates…
Semayawi party chairman barred from boarding flight
Eng. Yilkal Getnet, Chairman of the Blue Party (semayawi party)

IN ETHIOPIA BETTER CITIZENS LANGUISH IN PRISON

March 21, 2014
by Jonas Clinton
Political prisoners in Ethiopia
As the most educated Ethiopian immigrants migrate to North America looking for economical opportunities, it has been suggested, and most will end up being stalwart of customer service jobs such as driving taxis and ultimately shutter an Ethiopian dream of being useful to their home countries. In Ethiopia, like in North America, where the most inspiring, patriotic and educated citizens are located is not in the important institutions of the country being part of the affairs of the country, but like in North America, in the wrong places, inside the brutal and deadly Kaliti prison.
Early this month, a milestone was reached in Kaliti prison, one of Africa’s worst prisons, as one of its celebrated political prisoners, Reeymot Alemu, marked her 1000th day of being a political prisoner. The award winning journalist of the prestigious UNESCO/Guillermo Cano World Press Prize and the Hellman/Hammett Press Freedom Prize, Reeymot is fast becoming the face of Ethiopia and how wrong the country’s progress and priority has been.
The now 35 year old Alemu, was an English teacher and an occasional journalist when she was noticed by the Ethiopian government. She was one of Ethiopia’s eloquent voices in the then rare independent print media –Feteh – and wrote on government shortcomings and policies. In a country that still views constructive criticism as treason; the paper she wrote for was closed down by government officials and most of its journalists fled the country.
Alemu stayed behind and in a bold and daring move, started her own monthly publication – Change – and focused on long investigative reporting.
As she became a noted voice, the Ethiopian government closed her new publication and charged the young journalist with treason under Ethiopia’s 2009 Anti-Terrorism Proclamation. The Anti-Terror Proclamation was, according to Amnesty International, is intended to “restrict freedom of expression, peaceful assembly and the right to fair trial with serious implications”.
She was tried and convicted in secret with no substantive evidence and was sent to prison for 14 years and a monetary fine of $1500 – a hefty fine in Ethiopia. The government wanted to use her as an example to surpass other journalists, much like the respected Eskender Nega, and have them endorse government propaganda’s instead.
Since her arrest, She has been denied due medical care, been confined to darkness and been denied basic necessities of life in anticipation of her sharing information on her former journalist colleagues. She has refused as her suffering has continued.
Ethiopia has continued to arrest and imprison journalists while embracing its reputation of being an oppressor of press freedom and dissent in Ethiopia. Alemu once reflected how she believes that she “must contribute something to bring a better future (to Ethiopia).”Since there are a lot of injustices and oppressions in Ethiopia, I must reveal and oppose them in my articles,” and that her “principles” is “to stand for the truth, whether it is risky or not.”
As Ethiopia refuses to acknowledge the brutal treatment of its better citizens such as Nega and Alemu and many other political prisoners – what is fast becoming is the reality that Ethiopia is still a broken system that rewards bad while punishes good as it transitions to a better country in name only.

Ethiopia Regularly Records Phone Calls of opposition activists and journalists

March 21, 2014

Group: Ethiopia Regularly Records Phone Calls of opposition activists and journalists

(AP) A rights group says that Ethiopia’s government regularly listens to and records the phone calls of opposition activists and journalists using equipment provided by foreign technology companies.

Human Rights Watch said in a report Friday that the foreign equipment aids the Ethiopian government’s surveillance of perceived political opponents inside and outside the country.


The group’s Arvind Ganesan said Ethiopia is using its government-controlled telecom system to silence dissenters. The group says that recorded phone calls with family and friends are often played during abusive interrogations.

Human Rights Watch said most of the monitoring technology is provided by the Chinese firm ZTE. Several European companies have also provided equipment, the group said, including from the U.K., Germany and Italy.

Friday, March 21, 2014

Free Reeyot Alemu, an Ethiopian Prisoner of Conscience

March 21,2014
Reeyot Alemu is an Ethiopian school teacher and columnist whose wings have been clipped and her mouth sealed. Reeyot has been in prison, after an unfair trail, for the past 1000 days.
Reeyot, prior to her unjust incarceration, wrote a weekly column for many Amharic-language newspapers. One of the fall-outs of the Arab Spring was that authoritarian governments in the MENA region panicked. As is wont with tyrants, many governments were afraid that the wave of dissent might spread to their country and engulf their regime.
In Ethiopia, Reeyot and four other journalists who were arrested in 2011 and convicted based on a trumped up charge of terrorism. The other journalists are Woubshet Taye, Eskinder Nega, Yusuf Getachew and Solomon Kebede.  
On June 21, 2011, Reeyot Alemu was abducted from the high school where she taught English Language. The place of her arrest and the charges for which she was being detained were concealed from her family. According to the Safe World for Women, Reeyot’s dignity was assaulted by Ethiopian authorities for “refusing offers of clemency in exchange for providing information on other journalists, was punished with nearly two weeks in solitary confinement.”
What was Reeyot Alemu’s crime? Safe World for Women explains: “Four days before her arrest, Alemu had written a scathing critique of the ruling political party’s fundraising methods for a national dam project, and had apparently drawn parallels between late Libyan despot Muammar Gaddafi and Ethiopia’s then-Prime Minister, Meles Zenawi.”
Reeyot was held in solitary confinement for three months before her trial, without legal counsel. Her charges were both vague and witnesses sprung from thin air to implicate her. And as though that were not enough, in a pre-mediated media framing, a documentary ran on state television in Ethiopia that painted Reeyot as a terrorist.
Eventually Reeyot was handed a 14 year sentence after a sham trial. In August 2012, the appeal court commuted the 14 years sentence to a five years prison sentence. The court also threw out the terrorism charges against her.
Reeyot Alemu is currently has a tumour in one of her breasts, which is also bleeding. Sadly her condition is without proper medical diagnosis, thus giving great concern about her health conditions. It should be noted that women with malignant breast lumps, in absence of specialized and immediate treatment stand chances of losing a whole breast or even death. 
Reeyot deserves to be free; it is not a privilege but a human right. Her dignity has been violated, her voice has been so forcefully silenced and above all her life hangs treacherously on a thin line. Reeyot Alemu, a prisoner of conscience, should be commended not condemned. This woman of valor should be praised not imprisoned. Free Reeyot now before she dies in prison!By Nwachukwu Egbunike

ለነፃነት የምናደርገው ትግል በህገ ወጥ እስርና ማስፈራሪያ አይደናቀፍም! (በሰማያዊ ፓርቲ)

March 21, 2014
ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
“ማርች-8″ የሴቶችን ነጻነትና እኩልነት እንዲሁም ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚከበር የሴቶች ቀን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህን በዓል አስመልክቶ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ባለፈው ዕሁድ የካቲት 30/2006 ዓ.ም ሴቶች ብቻ የሚሳተፉበት የጎዳና ላይ ሩጫ ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ የሐገራችንም ሆነ የዓለም ሴቶች የነጻነት ቀናቸውን በሚያከብሩበት ዕለት እንደሌሎች ሴቶች ሁሉ የሰማያዊ ፓርቲ አአባላትም አላማውን ደግፈው በዕለቱ ቀኑን አስመልክቶ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ ተሳትፈዋል፡፡ በዚህ በሴቶች የነጻነት ቀን በስርዓቱ ላይ የሚነሱ ብሶቶችን ካሰሙት ተሳታፊዎች ውስጥ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሚገኙበት ሲሆን፣ በተለየ መልኩ በእነዚህ አባላቶቻችን ላይ ያነጣጠረ የአፈሳ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንደዚህ አይነት ህዝባዊ መድረኮችን ላይ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል በማጋለጥ መብት እና ለአገራችን ብሄራዊ ጥቅም በመቆም በገዥው ፓርቲ ተደጋጋሚ ህገ ወጥ እርምጃ ሲወሰድበት ቆይቷል፡፡ የተደረገው ህገ ወጥ ድርጊት ከዚሁ ፓርቲው ለህዝብና ለአገር መቆሙን ተከትሎ እየደረሰበት ያለው የከፋ የጭቆና አካል ነው፡፡Semayawi party press conference, Addis Ababa
ህገ ወጥ ድርጊቱን የበለጠ አስገራሚ የሚያደርገውም አባላቶቻችን የታሰሩበት ምክንያት “የጣይቱ ልጅ ነን” ፣ ህወሓት/ኢህአዴግን ምን ያህል ከታሪክ ጋር የተጣላ መሆኑን ከማሳየቱም በተጨማሪ አባላቶቻችን ለማስር እንግልት ወቅት በአባላቶቻችን ላይ የደህንነት አካላት ነን በሚሉ ግለሰቦች ማስፈራሪያና ዛቻ ተፈፅሞባቸው፡፡ አንዳንዶቹ አባላቶቻችን በሌሊት ጭምር ከእስር ክፍላቸው ወጥተው ቃል እንዲሰጡ ተከልክለዋል፡፡ ሙከራ ተደርጎባቸዋል፡፡ ከጠያቂ ቤተሰቦቻቸውና የትግል ጓደኞቻቸው ጋር እንዳይገናኙ ተከልክለዋል፡፡ የተጠረጠሩበት ክስ የማያስከስስና በነፃ የሚያስለቅቃቸው መሆኑ በየካ ክፍለ ከተማ ፍትህ ፅ/ቤት አቃቤ ህጎች ከተገለፀላቸው በኋላም በድጋሚ ፍርድ ቤት በማቅረብ እያንዳንዳቸው 1300 ብርና የመታወቂያ ዋስ በዋስትና እንዲቀርቡ ተጠይቀዋል፡፡
ፓርቲያችን ይህ እርምጃ በአባላቱ ላይ የተወሰደው ሰማያዊ ፓርቲ በመላው አገሪቱ መዋቅሩን እያደራጀና ህዝብን ከጎኑ እያሰለፈ ባለበት ወቅት መሆኑ፣ የህዝብ ድጋፍ የሌለው ገዥው ፓርቲ በሰበብ አስባቡ ሰማያዊ ፓርቲን ከወዲሁ ለማዳከም የወሰደው ነው ብሎ ያምናል፡፡ በተለይ የምርጫ ወቅት እየቀረበ መሆኑን ተከትሎ ይህን ህገ ወጥ እርምጃ መውሰዱ አሁንም ቢሆን የአገራችን የፖለቲካ ምህዳር ምን ያህል እየጠበበ እንደሄደ ያሳያል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ መቼም ቢሆን ይህንና መሰል የአገዛዙን አፈናዎች አጥብቆ የሚያወግዛቸውና የሚታገላቸው መሆኑን እየገለጸ በሴቶች የነጻነት ቀን ያለአግባቡ ታስረው ህገወጥ እርምጃ በአባላቶቻችን ላይ የወሰዱትን የፖሊስ አካላት በህግ የምንጠይቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ በተጨማሪም ይህን መሰሉ የህገ ወጦች እርምጃ ሳይገታን ትግላችንን አጠናክረን የምንቀጥል መሆናችንን እናረጋግጣለን፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!
መጋቢት 12 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ