Thursday, March 5, 2015

የአድዋ ድልን እያከበርን ለዛሬ ነፃነታች ቃል እንግባ!

March 5,2015
pg7-logoመቶ አስራ ዘጠነኛውን የአድዋ ድል በዓል እየዘከርን እንገኛለን። እንደዛሬው ሁሉ ያኔም ቀደምቶቻችን በርካታ የውስጥና የውጭ ችግሮች ነበሩባቸው። እንደዛሬው ሁሉ ያኔም በመካከላቸው የሀሳብና የጥቅም ልዩነቶች ነበሩ። ያም ሆኖ ግን ቀደምቶቻችን በአገር ነፃነት ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ መግባባት ላይ መድረስ በመቻላቸው በዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችና ድርጅት የተጠናከረውን የአውሮፓ ጦር በጥቁር የጦር አዛዦችና ተዋጊዎች መመከት ቻሉ። ከአድዋ በፊት አፍሪቃ በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ አውሮፓዊያን የተሸነፉባቸው ተናጠል አውደ ውጊያዎች ነበሩ፤ ጦርነትን ሲሸነፉ ግን አድዋ የመጀሪያው ነው። በዚህም ምክንያት ነው የአድዋ ድል የአፍሪቃውያን ከዚያም አልፎ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ ድል ተደርጎ የሚወሰደው።
ዛሬ ግን እኛ ያኔ የነበሩት አያትና ቅድመ አያቶቻችን እደረሱበት የመግባባት ደረጃ ላይ መድረስ ባለመቻላችን አገር በቀሉን ቅኝ ገዢ – ህወሓትን – ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ ላይ ማውረድ አቅቶን አገራችንና ሕዝቧን ከባዕድ በባሰ ሁኔታ እያዋረደ በመግዛት ላይ ይገኛል።
ያኔ ለሀገሩ፣ ለነፃነቱና ለክብሩ ቀናዒ የሆነው ኢትዮጵያዊ ራሱን ወታደር አድርጎ በየጎበዝ አለቃው አዝማችነት በጠላት ላይ ዘምቶ ድልን ተቀዳጅቷል። ዛሬ ግን ቁጥሩ ቀላል ያልሆነ የመከላከያ ሠራዊት አባል ለህወሓት አዛዦች ሎሌነት አድሮ የራሱን ወገን ይፈጃል። ያኔ በአገዛዙ ላይ ብሶት የነበረው እንኳን ሳይቀር ብሶቱን ችሎ ለሀገር ሉዓላውነትና ክብር ሲል ተዋድቋል። ዛሬ ግን ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ወገኖቻችን የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ከብሶቶቻቸው በላይ አሻግረው መመልከት ተስኗቸዋል።
ዛሬ 119ኛውን የአድዋ ድል በዓል አያቶቻችንን በማድነቅ ብቻ ልናሳልፈው አይገባም። የአያቶቻችንን ገድል ስናከብር ዛሬ የምንገኝበትን ሁኔታ መመዘን ይገባናል። ራሳችንን ከእነሱ ጋር በማስተያየት እንደምን ያለን ውለታ መላሽ ያልሆንን የልጅ ልጆች መሆናችንን መመዘን እና ራሳችንን መውቀስ ይገባናል። የሚሳዝነው ዛሬ ራሱን ከሚወቅሰው በላይ አያቶቹን የሚወቅስ መብዛቱ ነው። እነሱ ችግሮችን ተሻግረው የምንኮራበትን ድል አቀዳጅተውን አልፈዋል። እኛ ግን እነሱ ያቆዩልንን ድል እንኳን ማስጠበቅ አልቻልንም። ከአድዋ ድል አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ዓመታት በኋላ አገራችንን ለህወሓት የአገር ውስጥ ቅኝ አገዛዝ ማስረከባችን ሊያመንና ሊያንገበግበን ሲገባ ድሮ ሊደረጉ ሲችሉ አልተደረጉም በምንላቸው ነገሮች ላይ እየተከራከርን ግዜያችንን እናጠፋለን።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ታላቁን የአድዋን ድል ለአጎናፀፉን ቀደምቶቻችን ያለንን ክብር መግለጽ ያለብን ዛሬ አገራችን ከህወሓት የአገር ውስጥ ቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት በምንገባው ቃል ኪዳን ነው ብሎ ያምናል። አገራችንን በቅኝ ግዛትነት እያስገዛን የቀደምቶቻችንን ድል መዘከር ለእኛ ለልጆቻቸዉ የሚያሳፍር ተግባር ነው ብሎ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አገር በቀል ቅኝ ገዥ በሆነው ሕወሓት እየተመራ የኢትዮጵያን ሕዝብ የማዳከሙን ተግባር በአስቸኳይ ማቆም ይኖርበታል ብሎ ያምናል። ስለሆነም የመከላከያ ሠራዊት አባላት ልባችሁንም ክንዳችሁንም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር አድርጉ። ቀደምት አባቶቻችን አድዋ ላይ ድል የነሱት ቅኝ ገዥ ዛሬ ቀለሙን ለውጦ “ህወሓት” ተሰኝቶ ያንተ አዛዥ ሆኗል። መሣሪያህን በህወሓት አዛዦችህ ላይ የምታዞርበት ወቅት አሁን ነው። ንቃ፤ ተነስ!
አገርን ለጠላት አስረክቦ በቀደምት ጀግኖች ታሪክ መኩራት አሳፋሪ ነው። አባቶቻችን በነፃነት ያቆዩልን አገር የህወሓት መፈንጫ ሆና ማየት የሚያሸማቅቅ ነው። የጀግኖች አያቶቻችን የልጅ ልጆች መሆናችንን የምናስመሰክረው አገራችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ ስናወጣና የዜጎቿ መብቶች የተከበሩባት ፍትህና እኩልነት የሰፈኑባት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ስንመሠርት ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ ታላቅ ዓላማ ይነሳ ሲል አርበኖች ግንቦት 7 ጥሪ ያስተላልፋል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአድዋ ድልን እያከበርን ዛሬ ነፃነታችንን ለማስከር ለመታገል ቃል እንግባ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር በሰራው ዘፈን የተነሳ ከደህንነት ሃይሎች ማስፈራሪያ እየደረሰው መሆኑ ተሰማ * ስልኩ ተጠልፏል

March 5,2015
ጃኪ የተቀረጸው ዘፈኑን በሄኖክ ነጋሽ ኮምፒውተር ሲያደምጥ

ጃኪ እና ብርሃኑ ከሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር በስቱዲዮ ውስጥ                       ጃኪ የተቀረጸው ዘፈኑን በሄኖክ ነጋሽ ኮምፒውተር ሲያደምጥ

(ዘ-ሐበሻ) ብርሃኑ ተዘራ (ብሬ ላላ) ከጃኪ ጎሲ ጋር የሠራው ወቅታዊ ዘፈን በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ካተረፈ በኋላ አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ስልኩ በደህንነቶች መጠለፉን እና በስር ዓቱ ሰዎችም ከፍተኛ ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰው እንደሚገኝ ለድምጻዊው ቅርብ የሆኑ ወገኖች ለዘ-ሐበሻ አስታወቁ::

በዛሬው ዕለት ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ፃፈው በሚል “ዘፈኑን ተሰርቄ ነው; ጃኪ የፖለቲካ ዘፈን አይዘፍንም” የሚል ጽሁፍ በፌስቡክ የተሰራጨ ሲሆን ይህ ጽሁፍ በአድናቂዎቹ እንጂ በጃኪ ጎሲ አለመፃፉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: የጃኪ ጎሲ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶቹ ላይ ይህ ዜና እስከተዘገበበት ጊዜ ድረስ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር ስለዘፈነው ዘፈን የሰጠው አስተያየት የለም:: ሆኖም የድምጻዊው አድናቂዎች ዘፈኑ ካለርሱ እውቅና ውጭ የተሰራ አድርገው የለጠፉት መረጃ ብዙዎችን ከማደናገሩም በላይ በተለይ ለአራት ቀናት ጃኪ ጎሲ በዋሽንግተን ዲሲ የሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር ሄዶ ከብርሃኑ ጋር ሲቀረጽ የተመለከቱ የዓይን እማኞች “ጃኪ ለምን ይዋሻል?” የሚሉ አስተያየቶችን በየሶሻል ሚዲያው እያሰራጩ ነው:: ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ በፌስቡክ ገጹ ምንም ያለው ነገር ባለመኖሩ አስተያየት ከመስጠት መቆጠብ ይሻላል የሚሉ ወገኖች; ጃኪ በስሙ በወጣ መግለጫ የተነሳ በስሙና በቀጣይ ሥራው ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ሳያደርስበት አቋሙን እንዲያሳውቅ ጠይቀዋል::

ጃኪ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ የሚገኝ ሲሆን የደህንነት ኃይሎች ስልኩን በመጥለፍ ከማን ጋር እንደሚያወራ እንደሚከታተሉት ዘፈኑን እንዲያስተባብል ከፍተኛ ጫና እያደረጉበት መሆኑን ለድምፃዊው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል:: ጃኪ ከዚ ቀደም “ማን እንደ ሃገር” የሚል ነጠላ ዘፈን ሰርቶ የለቀቀ ሰሞን ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የድምፅአዊው የቅርብ ወዳጅ ተወዛዋዡ አብዮት መሃል ላይ ሰማያዊ የሌለበትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በኪሊፕ ሰርቶ ሲለቅ ጃኪም ይህን የሙዚቃ ክሊፕ ፌስቡኩ ላይ ሼር ሲያደርግ ደህንነቶች እንዴት ሕገመንግስቱ የማይፈቅደውን ባንዲራ በክሊፑ ላይ ትጠቀማለህ? በሚል ባደረሱበት ማስፈራሪያ ከፌስቡክ ገጹ ዘፈኑን ማስወጣቱን የሚጠቅሱት እነዚሁ የቅርብ ወገኖች አሁንም ደህንነቶች በሚያደርሱበት ወከባ ከፍተኛ ጫና ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል::
በጃኪ ስም አድናቂዎቹ የለጠፉት አደናጋሪ የፌስቡክ መልዕክት; ይህ በጃኪ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶች ላይ አልወጡም

በጃኪ ስም አድናቂዎቹ የለጠፉት አደናጋሪ የፌስቡክ መልዕክት; ይህ በጃኪ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶች ላይ አልወጡም

በዚህ ዘፈን ዙሪያ ድምፃዊው ብርሃኑ ተዘራን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም::


Wednesday, March 4, 2015

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አበል ካልተሰጠን ፍርድ ቤት አንቀርብም አሉ

March 4,2015
በከሳሽ ኣቃቤ  እና  ህግ በተከሳሽ አቶ ኣስገደ ገ/ሥላሴ መካከል ሲደረግ በነበረው ክርክር  ለምስክርነት የተጠሩት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሊቀርቡ ባለመቻካቸው  በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ  ቢታዘዝም፤  ባለስልጣናቱ  ከለመዱት ምቹ ህይወት አኳያ ማቅረብ ሳይቻል ቀረ።
የህወሀት የደህንነት ሰራተኛው ብስራት አማረ  የመሰረተባቸውን ክስ  ተከትሎ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲከራከሩ  የቆዩት የቀድሞው የህወሀት ታጋይና የአሁኑ የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ አስገደ ገብረስላሴ ላይ  ክሳቸውን እንዲከላከሉ  በፍርድ ቤት ብይን መሰጠቱ ይታወቃል።
ይህን ተከትሎ አቶ ኣስገደ ከጠሩዋቸው የመከላከያ ምስክሮች ውስጥ አራት ከፍተኛ  የህውሃት  አመራሮችና   ከፍተኛ  የመንግስት  ባለስልጣናት  ይገኙበታል። ለምስክርነት የተጠሩት እነኚህ ባለስልጣናት  እነ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አቶ ኣባይ ፀሃዬ፣ አቶ ስዩም መስፍን እና አቶ ኣርከበ ዕቁባይ ናቸው።
ባለስልጣናቱ  ለመጁመሪያ ጊዜ  ለ የካቲት 6 ቀን /2007 ዓመተ ምህረት  የመከላከያ ምስክርነታቸውን ለመስጠት እንዲቀርቡ ትእዛዝ ቢደርሰዋቸውም ፤ እዚያው መቀሌ ከተማ  ውስጥ እያሉ የዳኛውን ትእዛዝ በማጠፍ ሳይቀርቡ መቅረታቸውን አቶ አስገደ ገልጸዋል።
እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ለየካቲት  13  ቀን 2007 ዓመተ ምህረት  በፖሊስ እንዲቀርቡ ዳኛዋ  ቢያዙም፤ በድጋሚ እዚያው መቀሌ እያሉ  የሉም ተብለው ሳይቀርቡ ይቀራሉ።
ለ3ኛ  ጊዜ  ለየካቲት 24 ቀን 2007 ዓ/ም በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ  ሲታዘዝ  ፖሊስ ቅድመ ሁኔታ ማቅረቡን ያመለከቱት አቶ አስገደ፤  ከቅድመ ሁኔታዎቹም  አንዱ  ተጠርተው ሲመጡ ከፍተኛ የሃገር ባለስልጣናት ከመሆናቸው አኳያ  በሸራተን አዲሰ  ደረጃ  ባለ ሆቴል ማረፍ ስላለባቸውና  በመቀሌ  ያለው የዚያ  ተመሳሳይ ሆቴል “ፕላኔት ሆቴል” በመሆኑ፤  ምስክር ጠሪው አቶ አስገደ  በፕላኔት ሆቴል ለየአንዳንዳቸው ከነ ሁለት ኣጃቢዎቻቸው የአልጋ ዋጋ   ሊከፍሉ ይገባል የሚል እንደሆነ ገልጸዋል።
ባለስልጣናቱ ከዚህም በተጨማሪ በከፍተኛ ፕሮቶኮል  ማለትም በቪ አይ ፒ ደረጃ  የኣየር ትኬት ከነ ኣጃቢዎቻችን  ለመቁረጥ የሚያስችለን ገንዘብ፣ መቀሌ ለምንቆይበትም ቀናት የውሎ አበል  ታስቦ ካልተሰጠን አንመጣም ብለውኛል ብሎ ፖሊስ  ለፍርድ ቤቱ በጽሁፍ  ሪፖርት ማቅረቡን አቶ አስገደ ገልጸዋል። አቶ አስገደ አስተያየታቸውን ሲያጠቃልሉ፦<<እዚህ ላይ የፖሊስ ሃላፊነት ምን መሆን ነበረበት? ተይዞ ይቅረብ የተባለው ድሃ ሰው ቢሆን ንሮ ምን ያጋጥመው ነበር?በኢትዮጰያ የህግ የበላይነት ተረጋግጧል ማለት ይህ ነውን?በማለት በ አጸንኦት ጠይቀዋል።
ምንጭ ኢሳት ዜና 

በግፍ ላይ ግፍ በህወሓት..! ቐሺ ሕሉፍ ኸሕሳይ የዓረና-መድረክ ኣባል በመሆናቸው ብቻ ዘግናኝ ድብደባ ደርሰባቸው

March 4,2015
ቐሺ ሕሉፍ ኸሕሳይ ይባላሉ። በምዕራባዊ ዞን ቓፍታ ሑመራ ወረዳ በረኸት ከተማ(ቀበሌ) ኑዋሪ የሆኑት የዓረና-መድረክ ኣባል ናቸው።በፎተው እንደሚታዩት የዓረና-መድረክ ኣባል በመሆናቸው ብቻ ይህ ዘግናኝ ድብደባ ደርሶባቸው ሂወታቸው ልታልፍ ምንም ኣልቀረላቸውም ነበር።ይህ ድብደባ በ17/ 2007ዓ/ም ማታ 1 ሰዓት ኣከባቢ በ1ፖሊስ ድምብ ልብስ የለበሰ፣ 1 የፈጥኖ ደራሻ ደንብ ልብስ የለበሰ፣ 1 የመከላከያ ደንብ ልብስ የለበሱ ሰዎች ከለላነት ተደብቆ የነበረ ሰው በድንጋይ ደጋግሞ በመደብደብ ለዚህ ኣደጋ እንዲዳረጉ ኣድርገዋል።
3ቱ የታጠቁ ሰዎች ሰው እርዳታ እንዳያደርግ የተከላከሉ ሲሆን ደብዳቢውም በቁጥጥር ስር እንዳይውል ከፍተኛ ከለላ ሰጥተዋል።ቐሺ ሕሉፍ ኻሕሳይ በክረምት 2006 ዓ/ም በቀበሌው ህዝብ ፊት ቀርበው "..ይህ ሰውየ ዓረና ነው፣ በቤታቹ ቃጠሎ እንዳያደርስባቹ፣ እንዳይሰርቃቹ.." ወዘተ የመሳሰሉ የስም ማጥፋት ዘመቻና ማስፈራርያ ከሌሎች3 የዓረና ኣባላት ጋር ደርሶባቸው ነበር።ኣቶ መዓሾ ኣስመላሽ የተባለ የቀበሌ ኣመራርም ሰበካ ጉባኤ(የቤተክርስትያን ሃላፊዎች) በመሰብሰብ "...ቐሺ ሕሉፍ በዓረናነት ስለተጠረጠረ እንዳይቀድስ .." የሚል ትእዛዝ ባስተላለፈው መሰረት ከቅዳሴ ታገዱ።
ቐሺ ሕሉፍ የካድሬው እገዳ ተከትለው ወደ ቀበሌው ፖሊስ ኣቤቱታ በማሰማታቸው የቅስና ምስክር ወረቀታቸው እንድያመጡ በታዘዙት መሰረት ምስር ወረቀታቸው ለፖሊስ በማስረከብ ፍትህ እንዲያገኙ ጥረት ኣደረጉ።

ፖሊስም በተረዋ ምስክር ወረቀታቸው ለሁለት ሳምንት ይዞ ያለ ምንም መፍትሄ ኣቆየባቸው።
የምስክር ወረቀቱ ለማስመለስም ተጨማሪ ክስ ኣስፈለጋቸው። ፖሊስ በስንት ውጣ ውረድ ወረቀታቸው የመለሰላቸው ሲሆን ከዚህ በሗላም ስንት ዛቻ ደረሳቸው።
ዘግናኝ ድብደባ የተፈፀመባቸውም ከዚህ ሁሉ ውጣ ወረድና ማንገላታት በሗላ ነበር። ህግ ባለበት ሃገር የሰው ልጅ እንዲህ ተቀጥቅጦ ይጣላል እንዴ...?
እነዚህ ለለውጥ ብለው የተሰዉ 60 ሺ ሰማእታት፣ 100 ሺ ኣካል ጉዳተኞች ውጤታቸው መሆን የነበረበት ይህ ነው...? በጣም ሗላቀርና ህወሓት ታግየ ጣልኩት ካለቸው ደርግ በእኩልነት የሚያስመድባት ኣፀያፊ ተግባር ነው። በትግራይ የዓረና መድረክ ኣባል መሆን ይሄ የመሰለ መስዋእትነት ያስከፍላል።
በሉ ያገራችን ሰዎች ..! ታፍሩበት ትኮሩበት ዘንድ ይሄውላቹ የኛ ዲሞክራሲ፣ የኛ ፍትህ፣ የኛ ነፃነት።
ይህ ኣስቃቂ ተግባር ሁሉም ዜጋ ሊቃወመው ይገባል።
ነፃናታችን በእጃችን ነው..!
IT IS SO..!

የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርን ከኃላፊነቱ አነሳ

March4,2015

<<ውሳኔው ፖለቲካዊ ነው›› አቶ አዲሱ ጌታነህ

11043128_885271564848776_4028315024485403437_n
የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን ተወካይ እንዲሁም የምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃምና አዊ ዞን የምርጫ ግብረ ኃይል አባል የሆነውን አቶ አዲሱ ጌታነህን ‹‹ማኔጅመንቱን ያውካል፣ የስራ ተነሳሽነት የለውም›› በሚል ከኃላፊነቱ ማንሳቱን በደብዳቤ አሳውቋል፡፡

ይሁንና መስሪያ ቤት ጥቅምት 23/2007 ዓ.ም በብቃቱ መሰረት በኃላፊነት እንደመደበው በደብዳቤ የገለጸ ሲሆን አሁን የተወሰደው እርምጃ ከወቅቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ መሆኑን አቶ አዲሱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

‹‹ባህርዳር ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ኃይል እየተፈጠረ ነው፡፡ በተለይ የአንድነት መዋቅር ሰማያዊን ከተቀላቀለ በኋላ ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ይህንም ተከትሎ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች ጋር ያደረግናቸው ውይይቶች ብአዴንን አስደንግጦታል›› ያለው አቶ አዲሱ መስሪያ ቤቱ የወሰደበት እርምጃ ፖለቲካዊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ መዋቅር በአካባቢው ህዝብ ላይ የሚደርሰውን በደል፣ እንዲሁም ምርጫ ቦርድ ከዕጩ ምዝገባ ጋር በተያያዘ የሚፈጥራቸውን ችግሮች ለሚዲያ በማጋለጥ ላይ መሆኑ ከኃላፊነት ለመነሳቴ አንድ ምክንያት ነው ሲል ገልጾአል፡፡

የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የቦርድ አባላት የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ሲሆኑ ከእነዚህም መካከል የባህርዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ላቀ አያሌው፣ የክልሉ ም/ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ያለው አባተ፣ የክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ኃላፊ አቶ አየነው ይገኙበታል፡፡

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አላስተላልፍም›› ብሎ መለሰ

March 4 ,2015
• ‹‹ቀድሞውንም እንዳያማ ጥራው፣ እንዳይበላ ግፋው ነው›› አቶ ስለሽ ፈይሳ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) የሰማያዊ ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹እንደገና አስተካክሎ ካልላከ ለማስተላለፍ እቸገራለሁ›› በሚል መመለሱን ለፓርቲው በፃፈው ደብዳቤ አስታወቀ፡፡
ኢብኮ አላስተላልፍም ብሎ ለመመለሱ በዋነኛነት የጠቀሰው ምክንያት ‹‹ለማጀቢያነት ለተጠቀማችሁት ሙዚቃ የባለመብቶቹን ፈቃድ ስለመኖሩ ማረጋገጫ አላመጣችሁም›› የሚል ነው፡፡ ኢብኮ ሌሎች ጉድለቶችን ያልጠቀሰ ቢሆንም በጥቅሉ ‹‹የምርጫ ህጉን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ፣ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን ህጎች ወይንም ማንኛውም ህግ የሚተላለፍ መሆኑን በቂ ምክንያት ካለው መልዕክቱን አላስተላልፍም የማለት መብት አለው....›› በሲል ፓርቲው የላከውን የቅስቀሳ መልዕክት ለማስተላለፍ እንደሚቸገር ገልጾአል፡፡
በሌላ በኩል የፓርቲው የምርጫ ጉዳይ ኃላፊና ም/ሊቀመንበር አቶ ስለሽ ፈይሳ ገዥው ፓርቲ የግለሰብና የፓርቲ ስም እያጠፋ፣ የመደራጀት፣ ሀሰብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብትን በጣሰ መልኩ ቅስቀሳ እያደረገ እንደሆነ ገልጸው ሰማያዊ ፕሮግራሙ ላይ ያስቀመጣቸውን ሀሳቦች እንዲቀይር እየተጠየቀ መሆኑ ሚዲያዎቹ ለገዥው ፓርቲ ያላቸውን ወገንተኝነት በድጋሜ ያጋለጠ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
‹‹የመንግስት ሚዲያዎች ተግባር ቀድሞውንም እንዳያማ ጥራው እንዳይበላ ግፋው ነው፡፡ ቢያንስ በዚህ ጊዜ እንኳን ፍትሓዊ መሆን ነበረባቸው›› ያሉት አቶ ስለሽ የመንግስት የሚባሉት ሚዲያዎች በወንጀል ሊያስከስስ የሚችለውን የኢህአዴግ ቅስቀሳ ያለ ምንም ምርመራ እያስተላለፉ ሰማያዊ ላይ ህገ ወጥ ቅድመ ምርመራቸውን ቀጥለዋል ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
ኤፍ ኤም 96.3 ሰማያዊ ፓርቲ ለቅስቀሳ በላከው መልዕክት ላይ በማጀቢያነት የተጠቀመበት ሙዚቃ የባለ መብቱን ፈቃድ አላገኘም በሚልና መልዕክቱ ላይ የተጠቃለሉትን የፓርቲው አቋሞች እንዲያስተካክል በሚል የቅስቀሳ መልዕክቱን መመለሱ ይታወሳል፡፡

Tuesday, March 3, 2015

ግልጽ ደብዳቤ፣ በምርጫ ቦርድ ድረ ገጽ ለወጣው የአመክንዮ ክሽፈት ጽሁፍ ባለቤት

March 3, 2015
ከግርማ በቀለ ( የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት ሊቀመንበር)1.መግቢያ፡-
በምርጫ ቦርድ ኦፊሺያል ዌብ ሳይት ላይ ስለ ኢ/ር ይልቃል ‹‹የአመክንዮ ክሽፈት›› የተለጠፈ አንድ መግለጫ ይሁን ማብራሪያ ፣ ማስፈራሪያ ይሁን ማስተማሪያ መሆኑ ያለየለት/ወይም ለመለየት የሚስቸግር እንዲያው በጥቅሉ ቦርዱ ራሱን ከኢ/ር ይልቃል ጋር እያወዳደረ ወይም እልህ የገባ ወይም በፈጠራ ወንጀል ለመጥለፍ እየተዘጋጀ መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ጽሁፍ ይነበባል፡፡ የጽሁፉን ይዘት በሚመለከት አጭር አስተያየት የምንሰጥበት ሆኖ አንባቢ ሲያነብ እነዚህን ጥያቄዎች በአዕምሮው ይዞ ቢሆን የዚህን አስተያየት መነሻ ምክንያትና አመክንዮ የመረዳት መንገዱን ያቀልለታል፡፡ እነዚህም– በይዘቱ ላይ የሚነሱ ሌሎች መከራከሪያዎች ቀርተው ጽሁፉ በምርጫ ቦርድ ኦፊሺያል ዌብ ሳይት ላይ በመውጣቱ ብቻ ፡- ለቦርዱ ይህን ግለሰብን/ያውም የፓርቲ መሪን/ በስም መስደብና መወንጀል የሀገሪቱ ህግ ይፈቅድለታልን/የሚፈቅድለት ህግ አለን ወይስ ቦርዱ ከህግ በላይ/ ‹‹የባለሥልጣን ዶሮ›› ስለሆነ ጠያቂ የለኝም በሚል ያደረገው ነው? በተሻሻለው የምርጫ ህግ አንቀጽ 5 ላይ ለቦርድ ከተቀመጠው ዓላማ /ገለልተኝነት፣ ኢ-አድሎኣዊነት…./ አይጋጭምን? አንቀጽ 7 ላይ ለቦርድ ከተቀመጠው ተግባርና ኃላፊነት የወጣ አይደለምን?Girman Bekele Ethiopian politician
ጽሁፉ በመነሻው ላይ የቦርዱን ያላሰለሰ ጥረትና የሚጠበቀውን ውጤት ሲገልጽ ‹‹…ከእንከን የፀዳ ሆኖ እንዲጠናቀቅ…››ይላል፡፡ ጸሃፊው የቦርዱ ሰብሳቢ በአደባባይ/ሸራተን/ ‹‹እንከንየለሽ/ከእንከን የጸዳ/ ምርጫ በዓለማችን የለም ›› ያሉትንና ሁሉንም/ቢያንስ ከእኔ ኃሳብ የሚስማማ/ የሚያስማማ ንግግር አልሰማም ወይስ ምርጫ 2007 በዓለም ታይቶ የማይታወቅና በ‹‹ ጊነስ ቡክ››የሚመዘገብ ታሪክ ለማስመዝገብ ግብ ማስቀመጡን የቦርዱ ሰብሳቢ አልሰሙም ማለት ነው?
እዚህ ላይ አንድ ጉዳይ ጠቅሶ ማለፍ የጽሁፌን ዓላማ ግልጽ ያደርገዋል፡፡ ይህም ይህን የምጽፈው ለኢ/ር ይልቃል ጥብቅና ለመቆም (በራሳቸው አይደለም በአገራቸውና በዜጎች የሚፈጸመውን ህገወጥ ተግባር ለመመከት ያላቸውን ብቃት አስመስክረዋልና የእኔ ድጋፍ አያስፈልጋቸውም በሚል) አይደለም፤ ይልቁንም በአመክንዮ ስም የሚደረገውን ከአመክንዮ የወጣ ጽሁፍ ዝም ብሎ ማለፍ ተገቢ ሆኖ ስላላገኘሁበትና ከጽሁፉ በተቃራኒ በቦርዱ የተደረገውንና በቀጣይም ‹‹ሠይጣን ለማሳቻ ከመጽኃፍ ቅዱስ ይጠቅሳል›› እንዲሉ መሆኑን ለማሳየት/ለማጋለጥ ነው፤ ምን ያልተጋለጠ አለና በከንቱ ትደክማለህ ካልተባልኩ በቀር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሳይሆን ባልተናነሰ በጽሁፉ የተነሳው ጉዳይ በግልና እንደ ድርጅት መሪ በቀጥታ የሚመለከተኝ በመሆኑና በተነሳው ጉዳይ ሂደትና ውጤት በቀጥታና በተዘዋዋሪ የተጎዳሁ በመሆኑ ነው፡፡
የጥያቄዎችን መልስና ስለ ጽሁፉ ዓላማ ያነሳሁትን በዚሁ ልግታና በ‹‹ምርጫ ቦርድ›› ጽሁፍ ላይ ወደ ተነሱት የአመክንዮ ክሽፈት ነጥቦች እናምራ፡፡
2. የተነሱ የአመክንዮ ክሽፈት ነጥቦች፤
2.1. ክሹፍ አመክንዮ 1 ላይ–
ይህ ላይ የቀረበውን የጽሁፉን ይዘት ስናጠቃል ‹‹ህግ መቃወም አይችልም›› የሚል አንድምታ እንዳለው እንመለከታለን፡፡ የተደራጁ ዜጎቸ ቀርቶ አንድ ዜጋ እንኳ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ አንድን አዋጅና ህግ አይደለም፣ህገ መንግስቱን መቃወም፣ የሚቃወመውንም ለመቀየር/እንዲቀየር መታገል ይችላል፤ ይህ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ህገ መንግስቱም ሆነ አዋጆች/ህጎች የፈጣሪ ቃል አይደሉምና ሊተቹ አይደለም ሊቀየሩ እንደሚችሉ ስለሚታወቅ ህገ መንግስቱን የማሻሻያ ስርዓት በህገ መንግስቱ በግልጽ ሰፍሯል፡፡ የኢትዮጵያ የምርጫ ህግና የፓርቲዎች ምዝገባ አዋጆች መሻሻላቸው ወደፊትም ሊሻሻሉ የሚችሉ መሆናቸው የሚያረጋግጠው ይህንኑ ነው፤ በመሆኑም ጉድለትን መተቸት፣መቃወም፣ የማይቻልም ወንጀልም አይደለምና ባለ አመክንዮው ጸሃፊ/ቦርዱ ይህንን ከየት እንዳመጣው አልገለጸምና አመክንዮኣዊነቱን ባዶ ያስቀረዋል፡፡
ሌላው በጽሁፉ የተነሳው ጉዳይ የኢ/ር ይልቃልን ኃሳብ ‹‹…የፖለቲካ ፓርቲዎቹን ህጋዊ ሰውነት የሚገዳደር…›› በማለት የቀረበው ነው፡፡ ይህ ኢንጂነሩ ‹‹ህጋዊ ሰውነታቸውን ለተገዳደሩኣቸው›› ፓርቲዎች በመቆርቆር የተነሳ ኃሳብ ከሆነ በአንድ በኩል እውነትም ቦርዱ ለፓርቲዎች ዋስ ጠበቃ እየሆነ ነውና መጪው ጊዜ ከቦርዱ ጋር ለፓርቲዎች ‹‹ብሩህ›› መሆኑን ያሳያልና እሰዬው እንበል፤ በሌላ በኩል እንዲያውም በተቃራኒው ህጋዊ ሰውነታቸውን ኢንጂነሩ ለተገዳደሩባቸውና ቦርዱ ዋስ ጠበቃ ለሚሆንላቸው ፓርቲዎች ‹‹መብታቸውን የማያውቁ፣የራሳቸውን መብት ማስጠበቅ የማይችሉ፣ ደካሞች፣…›› የሚል መልዕክት የሚያስተላልፍና ለመብታችሁ እድንቆምላችሁና መጪው ጊዜ ከእኔ ጋር ብሩህ እንዲሆንላችሁ ከጎኔ ተሰለፉ ጥሪ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አመክንዮውን የበለጠ ባዶ የሚያስቀረው ጸሃፊው/ቦርዱ ስለፓርቲዎች ህጋዊ ሰውነት የተቆረቆረው በምርጫ አዋጁ የተቀመጠለትን ተግባር ተከትሎ ከኦሕዲኅና 9 ፓርቲዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች መልስ ባልሰጠበት መሆኑ ነው፡፡
ግልጽ ላድርገው–ከቦርዱ ዓላማ፣አሰራርና እየፈጸመ ያለውን ከታች በ2.1.3. ስር በተጠቀሰው የምርጫ ህግ አንቀጽ 12 የቦርድ አባላት ስነ ምግባር ቁጥር 1፣2፣5፣እና አንቀጽ 38 መሰረት እንመልከተው፡- ከላይ ጸሃፊው/ቦርዱ ለፓርቲዎች ህጋዊ ሰውነት ተቆርቋሪነቱን የገለጸው በምን ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ነው ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ የሚከተለው ነው፡፡
2.1.1. ቦርዱ ኦሕዲኅ አመራሩና አባላቱ በምርጫ 2007 በ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ምልክት›› እንዲወዳደሩ የፈቀደበትን ምክንያትና መነሻ የሚያብራራና ይህም በቦርዱ የጸደቀ መሆኑን የሚያሳይ ደብዳቤ (በቁጥር-ኦህዲኅ/0017/07፣በቀን ጥር 30/07 ) በቦርዱ ሳይታይ በጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ ተጽፎ ሲሰራጭ ለኦህዲኅ ያልደረሰ ህገወጥ የጓሮ በር መልስ በሰጡበት፣ ይህንንም በመቃወም ለቦርዱ በድጋሚ ለቀረበው ይህ የም/ኃላፊው ደብዳቤ እንዲሻር በኦሕዲኀ የተጻፈ ደብዳቤ (በቁጥር-ኦህዲኅ/0017/07፣በቀን የካቲት 10/07 ) የውኃ ሽታ ሆኖ በቀረበትና በዚህም ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸው የኦሕዲኅ አመራርና አባላት አቤቱታ ሳይቀርብባቸው በምርጫ የጊዜ ሰሌዳው መሰረት የዕጩ ምዝገባው በ04/06/07 ከተጠናቀቀ ሳምንት በኋላ በ11/04/07 በስልክ ትዕዛዝሙሉ በሙሉ ከዕጩነት በተሰረዙበት፤
2.1.2. በተመሳሳይ የቦርዱ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ የ9ኙ ፓርቲዎችን ህጋዊ ሰውነት በመካድ በ‹‹ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ/ትብብር›› በቅንጅት ለመስራት ያቀረቡትን ጥያቄ (በመንገድ ቁጥር በቀን 21/02/ 2007 ዓ.ም. ወጪ የሆነ ደብዳቤ) ከህግ አግባብ ውጪ አፍነው ለማስቀረት በተደጋጋሚ የሄዱበትን አሰራር በመቃወም ለቦርዱ ሰብሳቢ ላቀረቡት ደብዳቤ መልስ ባለመስጠቱ የ‹‹ትብብሩ››አባላት የጋራ እንቅስቃሴኣቸውን ለማቆም በተገደደቡት፤
2.1.3. በተቃራኒው ሌሎች 9ኙ ፓርቲዎች (አሁን በጋራ በመስራት ላይ ያሉት- የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር) ደግሞ የጋራ ተግባራትን በጋራ ለመስራት ‹‹የስነ ምግባር ህጉ አንቀጽ 3 (የተፈጻሚነት ወሰን) ቁጥር 1 ( ይህ አዋጅ- በማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ፣የግል ዕጩ ተወዳዳሪ፣እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅንጅት፣ ግንባር፣ ጥምረት፣ ወይም ንቅናቄ…ተፈጻሚ ይሆናል)፣አንቀጽ 38 ላይ (‹‹ማንኛውም ህግ ወይም አሰራር በዚህ አዋጅ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡››) በሚልበት በህጋዊ ሰውነታቸው በሚመነጨው መብታቸው ላይ ቆመው በጋራ ለመስራት (ጥምረት ይሁን ንቅናቄ ዕውቅና/ሰርቲፊኬት ቦርዱን የሚጠየቁበት ህግ በሌለበት) የተስማሙ፣ ነገር ግን ለዚህ የቦርዱን ዕውቅና ያልጠየቁ (ቦርዱ ዕውቅና/ሰርቲፊኬት የሚጠየቀው በቅንጅት፣ በግንባር ለመስራት ወይም ለመዋሃድ ብቻ ሆኖ ባለበት) ለ9ኙ ፓርቲዎች ዕውቅና/ ሰርቲፊኬት አልሰጠሁም በሚል ‹‹…ሰማያዊ አስተባብራለሁ…›› እያለ… በሚወነጅልበትና የድርጅቶችን ህልውና ከተቋቋመበት ዓላማ በተቃራኒ ራሱ እየካደ፣ ይህ ኃላፊነትና ተግባር ከማይጠበቅበት እንዲያውም የራሱን ዓላማና ፓርቲ ከሌላው የሚሻልበትን/የሚበልጥበትን ማሳየት የማያስጠይቀው ወገን /ሰማያዊ/ ላይ ጣት መጠንቆል፤ አመክንያኣዊ ነውን?
ከላይ እንዳልነው መልሶቹንና ፍርዱን ለአንባቢ፣ ለኢትዮጵያዊያን በመተው፣ይህንንም መዝግበን ወደ ቀጣዩ የጸሃፊው/ቦርዱ ‹‹የአመክንዮ ክሽፈት›› ትንታኔ እንለፍ፡፡
2.2. ክሹፍ አመክንዮ 2 ላይ –
ይህም ከላይ ከተጠቀሰው ብዙም የተለየ አይደለም፤ ህጉን ‹‹አይነኬና አይጠየቄ›› ከማድረግ ባለፈ በዓላማ ደረጃም አነሳሱ ባዶ ውንጀላ በማቅረብ የማስፈራሪያ ፣ሲያልፍም በመሰረተ ቢስ ክስ ለመጥለፍ እየተደረገ ያለውን ዝግጅት አብሪ ጥይት ነው ማለት ይቻላል፡፡ እስቲ ማሳያዎቹን ጠቅለል አድርገን እንመልከት፡፡
በዚህ ክፍል የቀረበውን የጽሁፉን ይዘት የ‹‹ከስነ ምግባር ደንቡ ጋር የሚያላትማቸዉ ስለመሆኑ ልብ ያሉት አይመስሉም ወይም የህግ ጥሰቱን የስራቸዉ አንድ አካል አድርገዉታል ማለት ነዉ፡፡›› በማለት የተገለጸው ያጠቃልለዋል ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ደግሞ ጸሃፊው/ቦርዱ ‹‹አይነኬና አይጠየቄ›› ባደረጓቸው ህጎች (የመተቸትና መጠየቅ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ተቀብለናቸው) አንጻር እንመልከት፡፡
ይህን እስኪ የምርጫ ህግ አንቀጽ 12 (የቦርድ አባላት ስነ ምግባር) ቁጥር 1.(በነጻነት፣ ገለልተኝነትና ቅን ልቡና ማገልገል)፣ ቁ.2 (በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የቱንም ወገን ያለመቃወም ወይም ያለመደገፍ)፣ቁ.5 (በማንኛውም ሁኔታ የቦርዱን ወይም የአባሉን ተኣማኒነት፣ገለልተኝነትና ነጻነት ከሚጎዳ ወይም ከሚያጎድፍ ማንኛውም ተግባር መቆጠብ)፣ አለበት ከሚለው አንጻር እንዳሰው ፡፡
2.2.1. ከዚህ አንጻር የሥነ ምግባር ደንቡ ዝግጅት የቀረቡት (በሂደት/አዘገጃጀት/ እና ይዘት/) ጥያቄዎች ሳይመለሱ የጸደቀን የስነ ምግባር ህግን፣ያውም በዝግጅቱ ወቅት ያልነበረ ፓርቲን መቃወም አይችልም የሚል ክስ ማቅረብ አመክንዮ መነሻ ከየት የመጣ ነው/ወይም አመክንዮኣዊ ነውን?
2.2.2. የምርጫ ህጉስ ቢሆን በፓርቲዎች ዕጣ አወጣጥስ የዕጩዎች በፓርቲ አመራር ያላቸውን ደረጃ፣ የፓርቲው አደረጃጀት/ብሄራዊ ወይም ክልላዊ/፣ ዕጩዎችን ያቀረቡ ፓርቲዎች በምርጫው ያላቸው ተሳትፎ/ያቀረቡት ዕጩዎች ብዛት/፣ የፓርቲዎች በአገራዊ ፖለቲካው ያላቸው እንቅስቃሴ/ተሳትፎ-የቢሮ ብዛት፣ለህዝብ ተደራሽነት/… ባለማካተቱ ጉድለት አለበት ማለት አይቻልም የሚል አመክንዮስ ከየት የመጣ ነው/ወይም አመክንዮኣዊ ነውን?
2.2.3. ለመሆኑ ቦርዱ ራሱ የሥነ ምግባር ህጉን፣ያውቀዋል፣ እየተገበረ ነውን? ለዚህ ጥቄ መነሻ ማሳያዎች -
የምርጫ ህጉ አንቀጽ 8 (የቦርዱ ሰብሳቢ ስልጣንና ተግባር) ቁጥር 4 ላይ ‹‹የፖለቲካ ድርጅቶችን የጋራ መድረክ በሰብሳቢነት ይመራል›› ይላል፡፡ የሥነ ምግባር ህጉ ደግሞ የጋራ መድረክ ሰብሳቢ ማን እንደሆነ አንድም ቦታ አይገልጽም፣ይህን በሁለት አዋጆች መካከል መናበብ በሌለበት ሁኔታ ባልተጻፈ ህግ በዘፈቀደ የሚከወነውን አፈጻጸም አይነኬ ማድረግ ነውን አመክንያዊነት?
ቦርዱስ በምርጫ ህጉ በአንቀጽ 7 ቁጥር 9 ላይ (‹‹የፖለቲካ ድርጅቶችን የጋራ መድረክ የማደራጀትና ማስተባበር) የተጣለበትን ኃላፊነት እየተወጣ ነውን?
2.2.4. የስነ ምግባር ደንቡን ከኢህአዴግ ጋር ያረቀቀው/ያዘጋጀው…መኢአድ በጋራ ምክር ቤት ተሳትፎ ማድረግ ባቆመበት/እምነት ባጣበት/ ህጉ ሲወጣ ላልነበረው ለሰማያዊ ፓርቲ መሪ አይነኬ ማድረግ ነውን አመክንያዊነት?
የሚሉትን ስንመለከት ጸሃፊው/ቦርዱ ከላይ በምርጫ ህጉ ቀ 12 በቦርዱ ላይ የተጣለበትን ሥነ ምግባር የተከተለ አሰራር ባልተከተለበት፣ነጻነቱ፣ገለልተኝነቱ… ተኣማኒነቱ ከጥያቄ ውስጥ ወድቆ ባለበት፣በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር ባላከናወነበት…በሌላው ያውም በግለሰብ ላይ ይህን ዓይነት ጽሁፍ መጻፍና በዌብሳይቱ ላይ መለጠፍ እንደምን ህጋዊና ምክንያታዊ ያደርገዋል፣በምን የሞራል መሰረት በአመክንዮ ለመከራከር ያስችለዋል? መልሱንና ፍርዱን ለአንባቢና ለባለቤቱ መራጭ ህዝብ እንተወውና ወደ ቀጣዩ እንሸጋገር፡፡
2.3. ክሹፍ አመክንዮ 3 ላይ፡-
በዚህ ክፍል ውስጥ በጽኁፉ ‹‹…. 23 ተጠቋሚ እጩዎችን አቅርበዋል፡፡ይሁንና ከእነዚህ መካከል ሁለቱ የአንድነትና የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኀብረት አመራሮች በመሆናቸዉና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በሰማያዊ ፓርቲ ጥላ ስር (በ9 ኙ ፓርቲዎች ትብብር ስም )ለመወዳደር የተመዘገቡ በመሆናቸዉ እንዲሰረዙ ሆኗል፡፡ ›› የሚለውን እናገኛለን፡፡
ይህ ደግሞ የባሰበትና ጆሮ ደፍኖ/ይዞ በህግ አምላክ እያሉ የሚያስጮህ በቅጥፈትና ክህደት የተሞላ ነው፣ እንዴት የሚለውን አብረን እንመልከት፤
2.3.1. ጽሁፉ ‹‹….(በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ስም) በመመዝገባቸው እንዲሰረዙ ሆኗል›› ያለው በ9ኙ ትብብር ስም የቀረበ ዕጩ በመላ አገሪቱ ባሉት ምርጫ ክልሎች ቢታሰስ በማይገኝበት በመሆኑ ትዝብት ላይ የሚጥል ነው፤/በዚህ ላይ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ኢትዮምህዳር የካቲት 18/07 ቅጽ2 ቁጥር 96 እትም እና Fortune Vol 15 No 773, Feb 22/15/ ይመልከቱ፤
2.3.2. ቦርዱ ‹‹…አመራሮች በመሆናቸዉና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በሰማያዊ ፓርቲ ጥላ ስር…›› ይላል በሌላ በኩል የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አባል የሆነው መኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ የፋይናንስ ኃላፊ አቶ ኑሪ ሙዲስር ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ሆነው ተመዝግበዋል፡፡ ይህ የዕጩ ምዝገባው በህግ ሳይሆን በዘፈቀደና በምርጫ ቦርድ በጎ ፈቃድ ወይም በድርብ መመዘኛ/Double Standard/ የተመራ መሆኑን በግልጽ ያሳያል፡፡
2.3.3. ይህን በሚመለከት ኦህዲኅ ከላይ በ2.1.1. ሥር የተገለጹትን ሁለት ደብዳቤዎች አቅርቦ መልስ ባላገኘበት በጓሮ በር ትዕዛዝ አመራሩና አባላቱ ከዕጩ ምዝገባ ቀን በኋላ በስልክ በተሰጠ ትዕዛዝ በተሰረዙበት፤ እውነት ውስጥ የሆነው ነው አመክኒዮኣዊነት?
እንግዲህ በዚህ መልክ የተሰራውን/ጸሃፊው/ ወይም የሰራውን /ቦርዱ/ ነው ክሹፍ አመክንዮ እና ህገወጥ እየተባለ የተፈረጀው፡፡ ፍርዱን ለአንባቢ ትተን የያዝነውን ጉዳይ እናጠቃለው፡፡
3. ማጠቃለያ፡-
3.1. ውሉ የጠፋበት/ የቦርድ መግለጫ ይሁን የቦርድ ሠራተኛ አስተያየት/ የክስ ማቀበያና ፈሪ ከተገኘም ማስፈራሪያ ጽሁፍ መሆኑ፤ ይህን አቶ ወንድሙ በአየር ሰዓት ድልደላ ላይ ሰማያዊ ላቀረበውን ጥያቄና ተቃውሞ ምላሽ ከዚህ ቀደም የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ አስታውሰው ‹‹በቀጣይ ከእንዲህ ዓይነቱ ተግባር የማይቆጠብ ከሆነ ቦርዱ እርምጃ ለመውሰድ ይገደዳል›› ካሉት ጋር ሲታይ፤
3.2. በጽሁፉ ማብቂያ ላይ ‹‹እንደ አጠቃላይ ኢ/ር ይልቃል በምርጫዉ ሂደት ላይ ጭቃ ይለጥፉ ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ መድረኮችን ረግጦ መዉጣት፣ በኢ-ተገቢ ዘለፋ መጀገን እና የሀገሪቱን የምርጫና የስነምግባር ደንቡን የሚገዳደር ተግባር በመፈጸም መጀገን የሚያስከፍለዉን ዋጋ ካለማወቅ ወይም ለማወቅ ካለመሻት መነሾ ባደረገ መልኩ እየገፉበት ነዉ፡፡›› የሚለውን ስንመለከት፤
3.3. ከላይ የቀረቡትን ጥያቄዎችና በተጨባጭ መረጃዎች የተደገፉ ማሳያዎችን እና የተጠቀሱትን የህግ አንቀጾች ከጽሁፉ ይዘት ጋር ስናገናዝብ፤
የጽሁፉ መልዕክትና ይዘት ወገናዊነት ግልጽ መሆኑ ቀርቶ ይህ ዓይነቱ በአንድ የፖለቲካ አመራር ላይ ያነጣጠረ ጽሁፍ በቦርዱ ዌብሳይት መውጣቱ በራሱ የቦርዱን ገለልተኝነት አጠያያቂ ከማድረግ አልፎ ህገወጥና የሚስጠይቅ ያደርገዋል ወይም ያስጠይቀው ‹‹ነበር›› ብሎ ማጠቃለል ይቻላል፡፡
ሆኖም ምርጫ ቦርድ የሚመካበት አለውና ድርጊቱም ‹‹እስመ አልቦ ነገር ዘይሳነው ለምርጫ ቦርድ›› እየሆነ ነውና አይደለም ኢ/ር ይልቃልን፣ ፓርቲንም ከሁለት ወንጀለኞች በህግበተሰጠው መብትና ኃላፊነት መሰረት በመዳኘት ሳይሆን በራሱ መንገድ የተሻለውን በመምረጥ የፈለገውን ማድረግ እንደሚችል አሳይቶናልና በአመክኒዮኣዊ ክርክር ከመድከም ወደ አቋሙ ቢገባ መልካም ይሆናል ፣ያሊያ ጽሁፉ ጠረን ‹‹ አያ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ›› የሚያስብል ነው፡፡
እንዲያው በማብቂያው ላይ ቢሆንም ለጽሁፌ ማዋዣ እንዲሆን ጠርጥረን ብናበቃስ–ይሄው ጽሁፍ በፋና ብሮድካስት ዌብሳይትም መለጠፉን፣እና ከዚህ በፊት በፋና ም/ሥራአስኪያጅና ኢ/ር ይልቃል ‹‹ሞጋች›› ፕሮግራም ላይ የነበረውንና ከፋና ‹፣ጠፍቶበት/በስህተት ሳይቀዳ ቀርቶ›› በኢሳት በሰማነው ክርክር ያስመዘገቡትን ‹‹ማርክ/ነጥብ›› ለመዘኑ ሰዎች ምርጫ ቦርድና ፋና ሬዲዮ እንደማይጠየቀው የኢህአዴግና አጋሮቹ ግንኙነት የ ‹‹አጋርነት›› ውል ተፈራረሙ ብሎ መጠርጠር በምርጫ ህጉም ሆነ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ያስጠይቅ ይሆን?
በመጨረሻም ማሳሰቢያ
የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት እንከን የለሽ ምርጫ ለማድረግ እንኳን እኛ እነርሱም አልደረሱምና በእኛ አገርም እየሆነ ያለውን ሁላችንም- እኛም፣ ቦርዱም፣ መንግስትም/ገዢው ፓርቲም፣ ህዝቡም ያውቀዋልና በመስተዋት ቤት ውስጥ ያለ ድንጋይ ለመወርወር ቀዳሚ መሆን ተገቢ አይደለም፤ ከነዚህ ሁሉ በላይ ህዝብ ያውቃል፣ይታዘባል፤ በጊዜውም ይፈርዳል፡፡ ማንም ምን ይበልም ለማድረግ ይፈልግም፣ያድርግም– የእኛ የማይናወጥ አቋም – ትግላችን ህገ መንግስታዊ መብታችን ላይ የተመሰረተ፣በሰላማዊና ህጋዊና ህጋዊ መንገድ ብቻ የሚጓዝ በመሆኑ ማንም ዜጋ ከህግ ባሻገር የኅሊና ፣ከሥልጣን በላይ የዜግነት ግዴታና የታሪክ ተጠያቂነት አለበት፤ ይህን የዘላቂ ሰላምና ልማት ወደ ዲሞክራሲ ሥርዓት የሚያደርስ የትብብሩን አካታችና ባለው ላይ መገንባት ምርጫው ያደረገ አካሄድ የመጥለፍ ሳይሆን የማበረታታት የሞራል ግዴታ እንዳለበት ማስተዋል ለሁላችንም- ለዜጎችም ለአገራችንም- ጠቃሚ መሆኑን በማሳሰብ አበቃለሁ፡፡
አንድ ሙስሊም ወዳጄ የነገረኝን ውስጤ የቀረ የታላቅ ኃይማኖት መሪ አስተምህሮ ለመዝጊያ ልጠቀመው ‹‹መልካምነት የተወደደ/በጣም ጥሩ/ ነው፤ መልካም ሆኖ መልካም ማድረግ ደግሞ የበለጠ የተወደደ/እጅግ በጣም ጥሩ/ ነው››፡፡ ለዚህ እንድበቃ ማስተዋሉን ተችረን በቸር አሰንብቶን በቸር ያገናኘን በሚል መልካም ምኞት መለያየት መልካም ነው፡፡ እስከዚያው መልካም ሆነን መልካም መልካሙን እያሰብንና እየሰራን እንድንቆይ ፈቃዱ ይሁን፡፡

Monday, March 2, 2015

አሁንም ደግመን እንነግራችኋለን

March2,2015
pg7-logoኢትዮጵያችን እግዚአብሔርንና ሰውን በማይፈሩ ጨካኞች እጅ ወድቃ የመከራ አገር ከሆነች ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል። በህዝባችን ላይ የተመዘዘው የመከራ ሰይፍም ወደ ሰገባው የሚመለስ አልሆነም። እንዲያውም በህዝባችን ላይ ሲዘንብ የቆየው የመከራ መንፈስ እንደገና ታድሶ ገና “ልክ እናስገባችኋለን” የሚል የጣዕረ ሞት ድምፅ ከህወሃት መንደር እየተሰማ ነው።
አባይ ፀሃይ የሚባለው ወላዋይና አደር ባይ ግለሰብ በህዝቡ ላይ ሲፈፅመው በኖረው ወንጀል ገና የረካ አይመስልም። ሌላ ግዲያ፤ ሌላ ስደት፤ ሌላ የላቀ መከራ ለኢትዮጵያዊያን ደግሶላቸዋል። አባይ ፀሃይ ለአዲስ አበባ ከተማ ልቀት እርሱ ብቻ አሳቢ፤ እርሱ ብቻ ተቆርቋሪ ሁኖ ራሱን ሹሟል።የአዲስ አበባም ሆነ በአካባቢው የሚኖረው ኗሪ ህዝብ ግን አባይ ፀሃይን የሚያውቁት በእኩይ ተግባሩ እንጂ በደግ ተግባሩ እንዳለሆነ እኛ ልናስታውሰው እንወዳለን። በዚህ ግለሰብ አማካሪነት የተጀመረው ኗሪውን ህዝብ የማፈናቀል፤ ቤተሰብን የመበተን፤ የህዝቡን አብሮነት የማፍረስ ተግባር ገና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል “ገና ልክ እናስገባችኋለን” በሚል መፈክር ሥር እንደሚቀጥል ታቅዷል። አዲስ አበባን በማስፋፋት ሰበብ ብዙ ገበሬዎች ከኖሩበት መንደር ያለምንም ካሳ ተፈናቅለው የሌላ ሎሌ እንዲሆኑ መደረጉ የሚረሳ አይደለም። ይሄን የአንድን ህዝብ ማንነት የማጥፋት ድርጊትን የተቃወሙ ብዙ ወጣቶች በሞት እና በእሥራት እንደተቀጡም አረሳነውም። ትላንት የፈሰሰው ደም ሳይደርቅ፤ የፈሰሰው እንባ ሳይታበስ፤የተበተነው ሳይሰበሰብ፤ የተሰበረው ሳይጠገን እንደገና ለሌላ ዙር ጥፋት እየተዘጋጁ እንደሆነ ነግረውናል።
አባይ ፀሃይ “ልክ እናስገባችኋለን” ሲል የተማመነው ጠመንጃ ያነገተውን ኢትዮጵያዊ ወታደር እንጂ ህዝብን እንዳልሆነ እናውቃለን። ወታደር አገሩን መጠበቅ፤ ህዝቡንም ከጥፋት መታደግ፤ አጠቃላይ የአገሪቷን ህግም ማስከበር ዋናው ተልዕኮው ነበር። የአገራችን ወታደሮች ግን ዋናውን ተልእኳቸውን ትተው ኢትዮጵያን እንደ አገር እንዳትቀጥል የሚያደርጉ ቡድኖችን እድሜያቸውን ለማራዘም እየሰሩ እንደሆነ እያየን ነው።በአገራችን ጠመንጃ የታጠቁ ኃይሎች መከላከያ ኃይል አባላት፤ የፖሊስ አባላት፤ የፌዴራል ፖሊስ አባላት እና በአገራችን ታሪክ በነፍሰ ገዳይነቱ የሚታወቀው አግዓዚ የተባለው ክፍለ ጦር አባላት እና የአገር ውስጥ ደህንነት አባላት የህወሃትን ዕድሜ ለማራዘም ከልብ የመነጨ ፍላጎት አላቸው ብለን አናምንም። እነዚህ ኃይሎች የወጡበትን ጎጆ፤ ነገ ዞሮ መግቢያ የሚሆናቸውን ማህበረሰብ ወደውና ፈቅደው ያፈርሳሉ ብለን ለማሰብ ይቸግረናል።በሌላ በኩል ደግሞ ድርጊታቸው ብዙዎችን እያስከፋ እንደሆነም እናውቃለን።
አሁንም ደግመን ደጋግመን በኢትዮጵያችን ጠመንጃ ላነገቱ ኃይሎች መልዕክት መላካችንን አናቋርጥም። ጠመንጃውን ያነገቱ ኃይሎች ካነገቱት ጠመንጃ የተለዩ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ስሜት አሏቸው፤ ፍላጎት አሏቸው፤ ማሰብ የሚችል አዕምሮም እንዳሏቸውም የሚካድ አይደለም።የሚያዝንና የሚደሰት ስሜት፤ ለመኖር ፍላጎት፤ በጎውን ከክፉ ለመለየት የሚያስችል አዕምሮ ያሏቸው ስለሆነ ፈፅሞ እስከ ሚመሽ ድረስ መልዕክታችንን ከመስደድ አናቆምም። መልዕክታችንም አጭርና ግልፅ ነው። በዚያች አገር ውስጥ ጠመንጃ የታጠቀው ኃይል ጋር ጠላትነት የለንም።በእኛ እምነት መከላከያ ኃይል፤ ፖሊስ እና የደህንነት ሠራተኞች ጠላቶቻችን አይደሉም። እኛ ጠላት የምንለው ጠመንጃ የታጠቀውን ድሃ እና ከርታታ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ይህን ኃይል በገዛ ወገኑ ላይ ሰይፉን እንዲመዝ እና የንፁሃንን ደም እንዲያፈስ የሚያደርገውን ኃይል ነው።የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አሁን ባለበት ሁኔታ ለተሻለ ውጤት የሚያበቃው አማራጭ ስለሌለው ሂሊናው እየወቀሰውም ቢሆን የገዛ ወገኑን ደም እያፈሰሰ ለመቆየት የተገደደ ይመስላል። ይህን ማለታችን የድርጊቱን መፈፀም ትክክል ነው እያልን አይደለም። በማንኛውም መለኪያ የንፁህ ሰውን ደም ማፍሰስ ትክክል አይደለም። በሰማይ በእግዚአብሄር ፊት የሚያስጠይቅ፤ በምድር በሰው ዘንድም የሚያስወቅስ ክፉ ተግባር መሆኑን ሳንናገር አናልፍም።
እስከ ዛሬ የተሻለ መረጃ ስለሌለኝ፤ የተሻለ አማራጭ ስላጣሁ፤ የተሻለን መንገድ ለመፈለግ ሁኔታው ስላልፈቀደልኝ ከሂሊናየ ውጪ ሁኜ ለመኖር ተገድጄአለሁ የሚለው ምክንያት አሁን አብቅቷል። አሁን መረጃ አለ፤ ኢትዮጵያን እንደ አገር እንድትቀጥል ለማስቻል የተሻለ አማራጭም አሁን ተዘጋጅቷል። መረጃና አማራጭ መንገድ ካለ ደግሞ ከሂሊና ጋር ታርቆ እንደ ሰው ለመኖር ሁኔታው የተመቸ ሁኗል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል፤ የፖሊስ ሠራዊት አባላት፤የአገር ውስጥ የደህንነት ኃይሎች ሆይ ስሙን !
ህወሃቶች እናንተን ተገን አድርገው የገዛ ወገኖቻችሁን “ልክ እናስገባለን” ማለታቸውን ሰምታችኋል የሚል ግምት አለን። ልክ ማስገባት ማለት-ከሥራ ማባረር፤ከትውልድ ሥፍራ ማፈናቀል፤ እስር ቤት መጨመር፤ ለስደት መዳረግ እና መግደል ማለት ነው። የአባይ ፀሃይ ልክ ማስገባት ይሄን ይመስላል።ይሄን የምትፈፅሙት ደግሞ ጠመንጃ ያነገታችሁ ኃይሎች ትሆናላችሁ። ወገኖቻችሁ በህወሃቶች እጅ እንባቸውን በመዳፋቸው ሲያፍሱ ኑረዋል።በህወሃት አገዛዝ ሥር ያለች አገራችሁ ከውዳቂ አገራት ተርታ ገብታለች፤ ከዓለም አስር ፍፁም ድሃ አገሮች መካከል አንዷ ሁናለች።የአገራችሁ ወጣቶች ሞትን ፊት ለፊታቸው እያዩ ተሰደው የዓዞና የበርሃ ዕራት ሁነው ቀርተዋል። ከዚህ የተረፉትም የዓረብ መጫወቻ ሁነዋል። ይህ ሁሉ መከራ ህወሃት በተባለው ክፉ ዘረኛና ቂመኛ ቡድን ይፈፀማል። አሁን ይሄን በቃ ለማለት ግዜው ነው። ከእንግዲህ ወዲያ ታዝዤ ነው፤ ለእንጀራ ብየ ነው፤ ልጆቼን ላሳድግ ብየ ነው፤ አማራጭ አጥቼ ነው፤ የሚሉ ምክንያቶች ሚዛን የሚያነሱ ባለመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም።
አሁን አስተማማኝ አማራጭ አለ። የኢትዮጵያ ውረደት ያንገበገበን፤ የህዝባችን ጉስቁልና ያስቆጨን ወገኖች የአያቶቻችንን ጋሻና ጦር አንስተን ለግዳጅ ተዘጋጅተናል። ከመቸውም ግዜ በተሻለ ህዝባዊ መሠረት ላይ የቆመ ድርጅት መሥርተን ንቅናቄ ጀምረናል። ትግላችን ኢትዮጵያዊያን ከተዘፈቁበት ጭለማ ወደ ብርሃን የሚያሻግር ነው። ትግላችን ህወሃት የጫነውን የዘረኝነት ቀንበር የሚሰብር ነው። ትግላችን ህወሃት የዘረጋውን የዝርፊያ መረብ የሚበጣጥስ ነው። ትግላችን ህዝቡን በሙሉ የተጫኑ ጥቂት መንደርተኞች ሥፍራቸውን እንዲይዙ ማድረግ ነው።ትግላችን ጎጠኛ አስተሳሰብን አምክኖ ብሄራዊ ስሜትንና ውህደትን የሚፈጥር ነው። ትግላችን ዜጎች በዜግነታቸው ብቻ በኢትዮጵያ ውስጥ በማንኛውም ሥፍራ ያለ ፍርሃት የሚኖሩበትን ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ትግላችን አብዛኛው ህዝብ በመረጠው መንግስት የሚተዳደርበት፤ ይህም መንግስት ህዝቡን ፈርቶና አክብሮ የሚሠራበት ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ትግላችን የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አገሩንና ህዝቡን የሚጠብቅ እንጂ የገዛ ወገኑን ደም በከንቱ የሚያፈስበት ሁኔታ እንዲያበቃ የሚያደርግ ነው።ጠመንጃውን ያንገትከው ኃይል የቀረበልህ አማራጭ መሥመር ይሄ ነው።
ደግመን እንነግርሃለን አሁን አማራጭ መንገድ አለህ። በገዛ ወገኖችህ ላይ ስይፍህን ለመምዘዝ እምቢ የማትል ከሆነና አሁንም በዚያው በጭለማ መንገድ መሄድን ከመርጥክ መጨረሻህ መልካም አይሆንም። እኛ እንድሆንን ተነስተናል። ከመንገዳችን የሚያቆመን ምዳራዊ ኃይል አይኖርም።የቃየል ልጆች ሲያጠፉን እንዲያው ዝም ብለን የምንጠፋ አይደለንም።ከእኛ ዘንድ እውነት አለ፤ ከእኛ ዘንድ የነፃነት ብርሃን አለ፤ ከእኛ ዘንድ የፍትህ ዘንግ አለ፤ከእኛ ዘንድ የእኩልነት ሚዛን አለ፤ ከእኛ ዘንድ እግዚአብሄር አለ።ይሄን ሁሉ ይዘን እናሸንፋለን እንጂ አንሸነፍም።የምናሸንፈው ለበቀል እንዳይደለ አሁንም እንነግራችኋለን። የምናሸንፈው በክፉው ላይ መልካሙን ዘር በመዝራት ነው።በጭቆና ላይ ነፃነትን፤ በአድልዎ ላይ ፍትህን፤ በህግ አልባነት ላይ የህግ የበላይነትን፤ በጎጠኛ አስተሳሰብ ላይ ብሄራዊ አስተሳሰብን ማስረፅ ስንችል ነው አሸንፈናል የምንለው። የጎሰኛነትን አጥር አፍርሰን የኢትዮጵያዊነት ስሜት ማስረፅ ስንችል ነው አሸንፈናል የምንለው። እኛ ስናሸነፍ የሚሆነው ይሄው ነው። ከእኛ ዘንድ የበቀል ስሜት የለም። ከእኛ ዘንድ ያለው ሁሉም ከህግ በታች ሁኖ ህግና ፍትህ እንዲነግሱ የሚያስችል ብርቱ ፍላጎት ነው።
ስለዚህ ጠመንጃ ያነገታችሁ ኃይሎች እኛ ከቆምንለት ቅዱስ ዓላማ ጋር እንድትተባበሩ እንጠራችኋለን።ኑና የጭለማ ኃይሎችን ምሽግ አፍርሰን የብርሃን ልጆችን አምባ አብረን እንሥራ። ኑና አብረን የወገኖቻችንን እምባ እናብስ። ኑና በግፍ ያለፍርድ የታሠሩትን እናስፈታ ።ኑና የጭቆናን ቀንበር አብረን እንስበር። ኑና አብረን አገራችንን ከፍ ከፍ እናድርጋት።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

Saturday, February 28, 2015

ሰበር ዜና: የወያኔ ሰላይ ከሆላንድ ተባረረ!

February 28,2015

ከመሃል ያለው ኢዛና (እስራኤል ገደቡ) ለ'ኢንቨስትመንት" አዲስ አበበ ያለፈው ወር በሄደ ጊዜ
ከመሃል ያለው ኢዛና (እስራኤል ገደቡ) ለ’ኢንቨስትመንት” አዲስ አበበ ያለፈው ወር በሄደ ጊዜ
ሂሩት መለሰ – ከሮተርዳም
ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል።


የሮተርዳም ከተማ ፍርድ ቤት በአለማየሁ ላይ የተመሰረተውን የስለላ ክስና ማስራጃ ለረጅም ጊዜ ሲመረምር ከቆየ በኋላ የግለሰቡ የመኖርያ ፈቃድ እና ቤት እንዲነጠቅ፣ የሆላንድን ምድርም በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ውሳኔ አስተላልፏል። ከሆላንድ የምመራ ቡድን እንደተረዳነው ከሆነ – የግለሰቡ ቤት ሲፈተሽ ወያኔ የሰጠው እውነተኛ መታወቂያ እና በርካታ የስለላ ሰነዶች ተገኝተውበታል። በእርዳታ ስም የተቋቋመለት ድርጅትም ተፈትሾ ማስረጃዎች እንደተገኙ ለማወቅ ተችሏል።
alemayehu-sentayehu
ይህ ሰው ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፎላ ይባላል። በደርግ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባል ሆኖ ለረጅም አመታት አገልግሏል። ወያኔ ስልጣን ሲቆጣጠር ለፖለቲካ ተሃድሶ አዋሳ ደቡብ ጦር ቅጥር ግቢ ተላከ። በተሃድሶ በነበረበት ጊዜ ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ የሰራዊቱ አባላትን ለወያኔ በማጋለጥ ታማኝነቱን ሲያሳይ እንደነበር የዚህ ዜና ዘጋቢ እማኝ ነው። የበርካታ ኢትዮጵያውያን ደም በእጁ ያለው አለማየሁ ከተሃድሶው ከወጣ በኋላ እስራኤል ገደቡ (የፓልቶክ ስሙ ኢዛና) ከተባለ ወታደር ጋር በመሆን የሰላም ተጓዥ ነኝ ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ሲታይ ነበር። አለማየሁ እና ኢዛና በየሃገሩ እየዞሩ ስለ አዲሱ ስርዓት መልካምነት ሲሰብኩ ከረሙ። ከዚያም አስመራ ድረስ ተልከው የሻእቢያውን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂን በወታደሩ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።

አለማየሁ እና ኢዛና ለወያኔ በሰሩት ውለታ ሆላንድ ገብተው እንዲቀሩ ተደረገ። ይህም የተደረገበት ምክንያት በአውሮፓ የሚኖሩ ኢዮጵያውያንን ተቃዋሚ በመምሰልና በረቀቀ መንገድ እንዲያበጣብጡና እንዲሰልሉ ነው። በሆላንድ ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ ለወያኔ ቡድን የስለላ ስራ መስራት ወንጀል ነው። አለማየሁ የሆላንድ ዜግነት ቢኖረው ኖሮ ቅጣቱ የከፋ ይሆን እንደነበር ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ የህግ ባለሙያዎች ተናግረዋል።

የአለማየሁ መባረር በተሰማ ግዜ በሮተርዳም ያሉ የህወሃት ደጋፊዎች የአቤቱታ ደብዳቤ በመጻፍ ፊርማ ማሰባሰብ ቢጀምሩም ሊሳካላቸው አልቻለም። የአቤቱታ ደብዳቤው ግለሰቡ እዚህ የተወለዱ ሁለት ለጆቹን እየመጣ እንዲጎበኝ ይፈቀድለት የሚል ነበር።
አለማየሁ ስንታየሁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሆላንድ ተባረረ። ኢዛና ግን አሁን የተቃዋሚ ጭንብሉን አውልቆ በግልጽ ወያኔ መሆኑን መናገር ጀምሯል። ኢዛና የሆላንድ ዜግነት ቢኖረውም በሆላንድ ሃገር ስራ ሰርቶ አያውቅም። የቀንና ማታ ስራው በፓልቶክ ላይ ነው። ባለፈው ወር ኢትዮጵያ የተጓዙ ዲያስፖራ ኢንቨስተሮችን እየመራ በቴሌቭዥን መግለጫ ሲሰጥ አይተነዋል። ይህ ትርኢት የወያኔ ኢንቨስተሮች በጨበጣ እንደሚንቀሳቀሱም ያሳየናል።

British support for Ethiopia scheme withdrawn amid abuse allegations

February 27, 2015

Department for International Development will no longer back $4.9bn project that critics claim has funded a brutal resettlement programme

(The Guardian) The UK has ended its financial support for a controversial development project alleged to have helped the Ethiopian government fund a brutal resettlement programme. Hundreds of people have been forced from their land as a result of the scheme, while there have also been reports of torture, rape and beatings.
An Anuak woman at work in Abobo, a village in Ethiopia’s Gambella region.
An Anuak woman at work in Abobo, a village in Ethiopia’s Gambella region. It has been claimed that UK money has funded abuses against Anuak people in the area. Photograph: Alamy
Until last month, Britain’s Department for International Development (DfID) was the primary funder of the promotion of basic services (PBS) programme, a $4.9bn (£3.2bn) project run by the World Bank and designed to boost education, health and water services in Ethiopia.
On Thursday, DfID said it had ended its PBS contributions because of Ethiopia’s “growing success”, adding that financial decisions of this nature were routinely made after considering a recipient country’s “commitment to partnership principles”.
It has been alleged that programme funds have been used to bankroll the Ethiopian government’s push to move 1.5 million rural families from their land to new “model” villages across the country.
Opponents of the commune development programme (CDP) say it has been characterised by violence. One Ethiopian farmer is taking legal action against the British government, claiming UK money has funded abuses against Anuak peoplein the Gambella region. The man, an Anuak known as Mr O, says he was beaten and witnessed rapes and assaults as government soldiers cleared people off their land. DfID has always insisted it does not fund Ethiopia’s commune development programme.
scathing draft report from the World Bank’s internal watchdog recently concluded that inadequate oversight, bad audit practices, and a failure to follow the bank’s own rules had allowed operational links to form between the PBS programme and the Ethiopian government’s resettlement scheme.
Although the bank’s inspection panel found that funds could have been diverted to implement villagisation, it did not look into whether the resettlement programme had involved human rights abuses, claiming such questions were outside its remit.
DfID, which has contributed nearly £745m of UK taxpayer money to the PBS programme, said the decision to withdraw financial support was prompted in part by Ethiopia’s “impressive progress” towards the millennium development goals.
“The UK will now evolve its approach by transitioning support towards economic development to help generate jobs, income and growth that will enable self-sufficiency and ultimately end poverty,” it said.
“This will go alongside additional funding for specific health, education and water programmes – where impressive results are already being delivered – resourced by ending support for the promotion of basic Services programme.”
A DfID spokesman said the move had nothing to do with Mr O’s ongoing legal action or the World Bank’s internal report, but added: “Changes to programmes are based on a number of factors including, but not limited to, country context, progress to date and commitment to partnership principles.”
The department said its overall financial commitment to Ethiopia, one of the largest recipients of UK aid, would remain unchanged, with almost £256m due to be spent between 2015 and 2016.
The Ethiopian government said DfID’s decision was not a matter of concern.
“They have been discussing it with pertinent government bodies,” said the communications minister, Redwan Hussien.
“What they said is that the aid that they’re giving will not be refused or stopped, it will be reorganised.”
The World Bank’s executive board met on Thursday to discuss the internal report on the PBS programme and the management response.
In a statement released on Friday, the bank said that although its inspection panel had concluded that the seizing of land and use of violence and intimidation were not consequences of PBS, it had determined that the programme “did not fully assess and mitigate the risks arising from the government’s implementation of CDP, particularly in the delivery of agricultural services to the Anuaks”.
The World Bank Group president, Jim Yong Kim, said that one of the institution’s core principles was to do no harm to the poor, adding: “In this case, while the inspection panel found no violations, it did point out areas where we could have done more to help the Anuak people. We draw important lessons from this case to better anticipate ways to protect the poor and be more effective in fighting poverty.”
Opponents of the villagisation process have been vocal in their criticisms of the bank’s role.Jessica Evans, senior international financial institutions researcher at Human Rights Watch, said the inspection panel’s report showed the bank had “largely ignored human rights risks evident in its projects in Ethiopia” and highlighted “the perils of unaccountable budget support” in the country.

በአዋሳ በደረሰው የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር ከ20 በላይ ነው ሲሉ የቃጠለው ሰለባ የሆኑ ሰዎች ገለጹ

February 27,2015
Awasaየካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል ዋና ከተማ በአዋሳ የካቲት 14 ቀን 2007 ዓም በደረሰው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር በመንግስት እንደተገለጸው አንድ ሳይሆን ከ20 በላይ መሆኑን ተገጂዎች ለኢሳት ገልጸዋል።
ከፍተኛ ንብረት ከወደመባቸውና እሳቱ ሲነሳ በስፍራው ከነበሩት መካከል አንዱ ለኢሳት ሲናገር፣ እርሱ የ6 ሰዎችን የተቃጠለ አስከሬን ማየቱን፣ በስፍራው የሚገኙ ጓደኞቹ ደግሞ በአጠቃላይ እስካሁን 27 አስከሬን ተፈልጎ መቀበሩን ተናገሩዋል።
አንድ ህጻነት እና አንዲት እናት ከ3 ልጆቿ ጋር ሞታ መመልከቱን፣ በማግስቱ ደግሞ ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ሞተው ማየቱን የሚናገረው ግለሰቡ፣ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች አካባቢውን ከነዋሪው በመከለል ማታ ማታ የተቃጠለ አስከሬን እየፈለጉ በመቅበር ላይ ናቸው ብሎአል። እናቶች አሁንም ድረስ ልጆቻቸውን እየጠየቁ ቢሆንም፣ በከንቲባው በኩል የሚሰጠው ምላሽ አሳዛኝ መሆኑን ግለሰቡ ገልጿል። ነዋሪዎቹ በመንግስት በኩል በቂ እርዳታ እንዳልተደረገላቸው በምሬት ተናግረዋል።
መንግስት የእሳቱን መነሻ እስካሁን ይፋ አላደረገም። ነዋሪዎች እንደሚሉት ግን መስተዳድሩ ቦታውን ለመሸጥ እሳቱን ሆን ብሎ አስነስቶታል። በጉዳዩ ዙሪያ የአዋሳን ከንቲባ ለማግኘት ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም።

Thursday, February 26, 2015

ምርጫ ለኢትዮጵያ ወታደርና ፓሊስ: – ለህወሓት ባርነት ወይስ ለኢትዮጵያ ነፃነት

February 26,2015
pg7-logoየኢትዮጵያ ሕዝብ ለውትድርና ከፍተኛ ክብር አለው። ውትድርና ከሙያና ሥራ በላይ የነፃነትና የክብር መገለጫ፤ ሀገርን ከባዕድ ወረራ መከላከያ ጋሻ ነው ብሎ ያምናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ህግና ሥርዓት አክባሪ በመሆኑ ለፓሊስም ከፍተኛ አክብሮት አለው። የፓሊስ ሥራ ወንጀልን መከላከልና ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ ማቅረብ መሆኑ በኢትዮጵያ ባህል የተከበረ ቦታና እውቅና አለው።
በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ግን ይህ እየተቀየረ ነው። የህወሓት አዛዦች እየመሩት ያለው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ሀገርን ከባዕድ ጠላት ከመከላከል ጋር ምንም ዝምድና በሌላቸው ሁለት አበይት ተግባራት ላይ ተጠምዷል። በህወሓት አዛዦች የሚመራው ሠራዊት ዋነኛ ተግባር ለሰብዓዊ መብቶቻቸው መከበር እና ለፍትህ መስፈን የሚታገሉ ዜጎችን ማጥቃት ሆኗል። የጦሩ ሁለተኛው አቢይ ተግባር ደግሞ ለአዛዦች የግል ጥቅም ማካበቻ ገቢዎችን በሚያስገኙ ሥራ ላይ መሠማራት ነው።
የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያዊያንን ማጥቂያ ሠራዊት መሆኑ ሲቪሉን ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የሠራዊቱንም አባላትን ጭምር ለህሊና ወቀሳ የዳረገ ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን ይህ በህሊና ወቀሳ ብቻ ሊታለፍ የማይችል ወንጀል ነው። ሠራዊቱ በህወሓት እየታዘዘ የሚዘምተው በገዛ ራሱ ልጆች፣ እህቶች፣ ወንድሞችና ወላጆች፤ በገዛ ራሱ ጥቅሞች እና በገዛ ራሱ ላይ መሆኑ መገንዘብ ይኖርበታል። በገዛ ራሱ ጥቅሞች ላይ የሚዘምት አንድም ህሊና የሌለው አሊያም ነፃነት የተነፈገው ሰው ብቻ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ሠራዊቱ እየተራበና እየታረዘ አለቆቹ የታላላቅ ህንፃዎች ባለቤቶች፣ ባለፋብሪካዎች፣ የባንክና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ባለአክሲኖች የሚሆኑበት ሥርዓት ከዳር ሆኖ የሚመለከት መሆኑ የሚገርም ነው። ሠራዊቱ ቤተሰቦቹን መመገብ አቅቶት እያለ የአዛዦቹ ልጆች ለሽርሽር ዓለምን ይዞራሉ። እንዴት ነው ሠራዊቱ እየደኸየና እየሞተ አዛዦቹ እየከበሩ የሚሄዱት? ይህ አዋራጅ ሁኔታ እንዲያበቃ መታገል የሠራዊቱ ግንባር ቀደም ኃላፊነት ነው። ሠራዊቱ ወይ ባርነትን አሜን ብሎ መቀበል አለበት አለበዚያም እሱም እንደነሱ ሰው መሆኑን ማሳየት መቻል አለበት። በኢትዮጵያ ውስጥ የህወሓት አገዛዝ ወድቆ የሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ ከሚጠቅማቸው የኅብረተብ ክፍሎች ግንባር ቀደሙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ናቸው። በዚህም ምክንያት የሠራዊቱ አባላት ለሥርዓቱ መውደቅ በግልጽም በስውርም መታገል የዜግነት ብቻ ሳይሆን አዕምሮ ያለው ሰው ሆነው በመፈጠራቸው የተቀበሉት ግዴታ ነው።
ፓሊስን በተመለከተም ሁኔታው ተመሳሳይ ነው። ህወሓት የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ ለመግዛት የቻለው በዋኛነት የፓሊስን ኃይል ለአፈናው ተግባር የሚጠቀም በመሆኑ ነው። የተቃውሞ ድምጾች በተሰሙ ቁጥር የኢትዮጵያ ፓሊስ በወገኖቹ ላይ የሚያወርደው ዱላ የሚዘገንን ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት መግደልና ማቁሰል፤ አረጋዊያንን፣ ሴቶችንና ሕፃናትን መግደል፣ ማቁሰል፣ መደብደብ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ፓሊሶችን በቡድንም በግልም በህግ የሚያስጠይቅ ከባድ ወንጀል ነው። በህወሃት እየተመራ ያለው የኢትዮጵያ ፓሊስ ተግባራት ተበዳዮችን ብቻ ሳይሆን ራሱ ፓሊስንም ጭምር አንገት የሚያስደፋ ተግባር ነው። ለመሆኑ አንድ ተራ የኢትዮጵያ ፓሊስ ባልደረባ ከህወሓት አገዛዝ ምን ተጠቀመ? መልሱ “ምንም” የሚል ነው። ይልቁንስ በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ፓሊስ የተናቀና የተዋረደ ሥራ ሆነ። በህወሓት አገዛዝ ፓሊስ እንደሰለጠነ አዳኝ ውሻ “ያዝ” ሲሉት የሚነክስ፣ የሚያደማ፣ የሚቦጭቅ ሆኗል። ይህ ለፓሊስ፣ ወንጀልም ውርደትም ነው። በህወሓት አገዛዝ መገርሰስ እና በምትኩ የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መስፈን ፓሊስ ከሁሉ በላይ ተጠቃሚ ነው፤ ሰብዓዊ ክብሩን ያረጋግጥለታልና።
ዛሬ በኢትዮጵያችን ውስጥ የታዘዙትን የሚፈጽሙ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ስላሉ ነው የህወሓት ሹማምንት ልባቸው ያበጠው። ለማስረጃ ያህል ሰሞኑን የህወሓቱ ሹም አባይ ፀሐዬ የአዲስ አበባ ዙሪያ ገበሬዎች በግዴታ መነሳታቸው የሚቃወሙትን ዜጎችን ሁሉ ”ልክ እናስገባቸዋለን” ብሎ በሸንጎ የዛተው የታዘዘውን የሚፈጽም የጦርና የፓሊስ ሠራዊት መኖሩን ተማምኖ ነው። እስከ መቼ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊትና ፓሊስ ሕዝብን ማስፈራሪያ መሣሪያ ይሆናል?
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የኢትዮጵያ የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ለራሳቸው እና ለወገናቸው የሚበጀው ሥርዓት የቱ እንደሆነ ያውቃሉ ብሎ ያምናል። በዚህም ምክንያት ስብዕናቸውን እያዋረደ እና እያደኸያቸው ያለውን የህወሓት አገዛዝን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመሆን ይፋለሙታል ብሎ ያምናል። ይህ ውሳኔ ግን ሠራዊቱ በጅምላ ሳይሆን እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል በግሉ የሚወስደው ውሳኔ እንደሆነ አርበኞች ግንቦት 7 ይገነዘባል።
በዚህም መሠረት ተደጋጋሚ ጥሪ እየተደረገለት፤ ጥሪውንም እየሰማ ከህወሓት ጋር ወግኖ ሕዝብን መውጋት የቀጠለ የሠራዊቱ አባል ላደረሰው ጥፋት በግል መጠየቁ የማይቀር መሆኑ ሊገነዘብ ይገባል። በእያንዳንዳንዱ የጦርና ፓሊስ ሠራዊት ባልደረባ ፊት የቀረበው ምርጫ “ለህወሓት ባርነት ታድራለህ ወይስ ራስህንና ሀገርን ነፃ ታወጣለህ” የሚል ነው።
ራስህንና ሀገርህን ነፃ ለማውጣት የመረጥክ የሠራዊቱና የፓሊስ ባልደረባ አሁኑኑ ሕዝባዊ ትግሉን ተቀላቀል። እስከዛሬ የበደልከውን ሕዝብ ለመካስ ምቹ ሁኔታ አለህ። በግልጽ የነፃነት ኃይሎችን እንድትቀላቀል፤ አሊያም አለህበት ሆነህ በውስጥ አርበኝነት እንድትደራጅና ተግባራዊ ሥራ እንድትጀምር መንገዱ ተመቻችቶልሃል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Wednesday, February 25, 2015

አዋራጅ ሰልፎችና ድግሶች እንዲያበቁ ህወሓት ይወገድ!

February 25,2015
pg7-logoድግሶችን፣ ወታደራዊ ሰልፎችንና ሀውልቶችን ማብዛት የአባገነኖች ሁሉ የጋራ ባህርይ ነው። ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝም በሕዝብ እየተጠላ፣ እያረጀና እየወላለቀ በሄደ መጠን በየተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግሶ መብላት፤ ወታደራዊ ሰልፍና የመሣሪያ ጋጋታ ማሳየት እና በየመንደሩ ሀውልት መመረቅ ሙያው አድርጎት ቆይቷል።
የህወሓት ድግሶችና ፌሽታዎች የአገራችን ሀብት ከማሟጠጣቸውም በላይ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ የአርሶ አደሮችንና የአነስተኛ ነጋዴዎችን ኪስ እያራቆቱ ናቸው። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች በእስር ቤቶች እየማቀቁ በሚገኙበት ሁኔታ፤ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ የአማራ አርሶአደሮች ተፈናቅለው እያለ፤ በጋምቤላና በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ የጅምላ ጭፍጨፋዎች እየተደረጉ፤ በአፋር፣ በሲዳማ፣ በቦረና፣ በወልቃይት እና በመላው ኢትዮጵያ ግጭቶች በበዙበት፤ ሕዝብ እያለቀሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት “የብሔር፣ ብሔረሰቦች መብት ተከበረ” እያሉ እነዚህኑ በደል እየደረሰባቸው ያሉ ዜጎችን ማስጨፈር እና ለእነዚህ ጭፈራዎች በርካታ ሚሊዮኖች ብር ማውጣት በእጅጉ ያስቆጫል። እነዚህ ጭፈራዎች ለህወሓት ሰዎች የገቢ ምንጮች መሆናቸው ጥርጥር የለውም፤ ለድሀው ኢትዮጵያዊ ግን መራቆቻዎች ናቸው። ከዚህም አልፎ በዘረኝነት እየተበደለ ያለ ሕዝብ ስለእኩልነት ዝፈን ማለት ክብረ ነክ ተግባር ነው። ዘንድሮ በአሶሳ የተደረገው አገር አቀፍ ድግስ ካለቀ ጥቂት ወራት በኋላ አገራችን በሌላ ዙር የህወሓቶች ድግስ ተወጥራለች።
ሰሞኑን በባህር ዳር በተደረገው የጦር ሠራዊት ሰልፍ እና ሰልፉን ተከትሎ በነበረው የድግሶች ግርግር ከሁሉም በላይ የተሰደበውና የተዋረደው የሠራዊቱ አባል ነው። አዛዦቹ መቶ በመቶ የህወሓት አባላት የሆኑበትን ሠራዊት “የኢትዮጵያ መከላከያ” ተብሎ መጠራቱ ራሱ የሚያሳፍረው ኢትዮጵያዊ ወኔ በልባቸው ውስጥ እየተንቀለቀለና እልህ እየተናነቃቸው ያሉ የሠራዊቱን አባላት ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንዴት የኢትዮጵያ ጠላቶች በሆኑ የህወሓት ካድሬዎች ይመራል? እንዴት የአስር አለቃ እንኳን ሊሆን የማይገባው የህወሓት ካድሬ “ጄኔራል” ተብሎ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮችን እንደ ሎሌው ያዛል? እንዴት አንድ የህወሓት ሎሌ ሹመት ተሰጥቶት እየፏለለ በልምድ፣ በትምህርትና በእውቀት የሚበልጠውን ኢትዮጵያዊ ተንቆ ይዋረዳል? ይህ ቁጭትና እልህ ሠራዊቱ የዘረኛውን ህወሓት ሰልፍ አድማቂ መሆኑ የሚያከትምበት ጊዜ ይበልጥ እንዲናፍቅ የሚደረገው ነው። አልያማ ሰልፍ ያሳመረ ሠራዊት ሁሉ አሸናፊ እንዳልሆነ የታወቀ ነው። በሰልፍ ብዛትና በመሣሪያ ትዕይንት ማሸነፍ ቢቻል ኖሮ የትም አገር አምባገነኖች ባልወደቁም፤ ህወሓት ራሱን ስልጣን ላይ ባልወጣም ነበር።
የህወሓት ምሥረታ 40ኛ ዓመት ድግስም ሌላው የታሪክና የሀብት ውድመት የሚያስከትል ክስተት ነው። የካቲት 11 ቀን 1967፣ ጥቂት ኢትዮጵያዊያን እናታቸውን ኢትዮጵያን ለመግደል ያሴሩበት እና ልጆች በእናታቸው ላይ ቢላዋ የሳሉበት ዕለት በመሆኑ በሀዘንና በሱባኤ እንጂ በድግስና በጭፈራ የሚታሰብ ዕለት አይደለም። ሲነሳ ምንም ይሁን ምን ዛሬ በደረስንበት ሁኔታ ሲገመገም፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ ህወሓትን የመሰለ መሠሪና አድርባይ ድርጅት ገጥሟት አያውቅም። እነሆ ዘንድሮም ይኸው አድርባይ ድርጅት የመሪዎቹን የሀብትና ዝና ረሀብ ለማስታገስ ሲል ያልነበረ ታሪክ እየፈጠረ በድግስ ስም ከድሀው ገንዘብ እየሰበሰበ ለሀብታም የህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ያሸጋግራል። የድግሶቹ ሁሉ አዘጋጆች፣ እቃ አቅራቢዎችና ተጠቃሚዎች ራሳቸው የህወሓት መሪዎችና አሽቃባጮቻቸው ሲሆኑ ከፋዩ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። በህወሓት ድግስ የሚባክነው የሕዝብ ሀብት ስንት ሆስፒታል ይገነባ እንደነበር ስናስብ እና ይህ ሀብት በተገቢው ቦታ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ስም ብቻ የያዙ ዩንቨርስቲዎቻችንን ትምህርት መቅሰሚያ ማድረግ እንችል እንደነበር ስናሰላ ሀዘናችን ጥልቅ ነው። ህወሓት ለልጅ ልጆቻችን የሚተርፍ ዕዳ እየቆለለ ዳንኪራ ሲረግጥና ሲያስረግጥ ማየትና መስማት ህሊና ሊሸከመው ከሚችል በላይ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት ወታደራዊ ሰልፍ እና የመሣሪያዎች ትዕይንት የሚረበሽ ድርጅት አይደለም። ይልቁንም በሰልፉ ጨኸት የታፈነው የኢትዮጵያዊ ወታደር ጩኸት ይሰማዋል። ኢትዮጵያዊ ወታደር በአዛዦቹ ላይ ጥርሱን ነክሶ፣ ቂም አርግዞ ሰልፋቸውን እንደሚሰለፍ አርበኞች ግንቦት 7 ያውቃል። አርበኞች ግንቦት 7፣ የሠራዊቱ አባላት ውስጥ ውስጡን እየተሰቃዩ የታዘዙትን መፈፀማቸው መብቃት አለበት ይላል፤ ወይ ተቀላቀሉን፣ አሊያም እውስጡ ሆናችሁ ሥርዓቱን የማዳከም ሥራዎችን ሥሩ። በእናንተ ውርደት የዘራፊዎች፣ ሙሰኖች፣ ጎጠኞችና ዘረኞች ደረት አብጦ መታየት የለበትም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ የዘንድሮው የህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል የጨረሻው በዓል እንዲሆን፤ ከርሞም ተመሳሳይ አዋራጅ በዓል እንዳናከብር፤ ሠራዊቱ በዘራፊዎች ታዞ የሚሰለፍበት ውርደት እንዲያበቃ ተባብረን ህወሓትን እንቅበር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ድል የአላማ ጽናት እንጂ የመሳሪያ ጋጋታ ዉጤት አይደለም

February 25,2015

pg7-logoጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ዉስጥ ዋና ከተማዋን ከተለያዩ የጣሊያን ከተሞችና ጣሊያንን ከፓሪስ፤ከሙኒክ፤ከጄኔቫና ከቪዬና ጋር የሚያገናዉና በአመት ከ 150 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን የሚያስተናግድ አንድ ትልቅ የባቡር መስመር አለ። ይህ የባቡር መስመር የሚጠራዉ ሮማ ተርሚኒ እየተባለ ሲሆን የባቡር መስመሩ አድራሻ ደግሞ የአምስት መቶዎቹ አደባባይ በመባል ይታወቃል። ወደዘህ ትልቅ ባቡር መስመር ሲገባ አንድ እጅግ በጣም ትልቅ ሀዉልት ወለል ብሎ ይታያል፤ ይህም ሀዉልት የአምስት መቶዎቹ አደባባይ ወይም ፒያዛ ዴ ቺንኮቼንቶ በመባል የታወቃል። የፒያሳ ዴ ቺንኮቼንቶ መታሰቢያ ሀዉልት የተሰራዉ ወራሪዉ የጣሊያን ጦር አገራችንን ለመወረር ሲመጣ ዶጋሌ ላይ በራስ አሉላ ጦር የተገደሉትን አምስት መቶ የጣሊያን ወታደሮች ለማስታወስ ነዉ። በ1877 ዓም ዘመናዊ መሳሪያ ታጥቆ ጦርና ጎራዴ በታጠቀዉ የራስ አሉላ ጦር ዉርደት የተከናነበዉ የጣሊያን ወራሪ ሠራዊት ብድሩን ለመመለስ በ1888 ዓ.ም ብዛት ያለዉ ካባድ መሳሪያ፤ መድፍና መትረየስ ታጥቆ አድዋ ድረስ ቢመጣም በዳግማዊ ሚኒሊክ የተመራዉ ጀግናዉ የኢትዮጵያ ሠራዊት እንደገና ዉርደት አከናንቦት በጥቁር ህዝብ ታሪክ ዉስጥ ትዝታዉ ምንግዜም የማይደበዝዝ ድል አስመዝግቧል። የኢትዮጵያ ሠራዊት ዶጋሌና አድዋ ላይ እስካፍንጫዉ የታጠቀዉን የጣሊያን ወራሪ ጦር ደጋግሞ ያሸነፈዉ በመሳሪያ በልጦ ወይም የተሻለ የዉትድርና ችሎታ ስለነበረዉ ሳይሆን ከወራሪዉ ጦር የበለጠ ቆራጥነትና የአለማ ጽናት ሰለነበረዉ ነዉ።
በሃያኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን የተደረጉ ሌሎች የነጻነት ትግሎችን ስንመለከት በወቅቱ የአየር ኃይል ያልነበራት ትንሿ አገር ቬትናም በባህር፤ በአየርና በየብስ ጦርነት የገጠማትን ትልቁን የአለማችን ሀይል አሜሪካንን አሸንፋ ነፃነቷን ያስከበረችዉ በመሳሪያ ጋጋታ ሳይሆን የዛፍ ላይ ቅጠልና የተቦጫጨቀ ጨርቅ በለበሱ ነገር ግን ከፍተኛ የአላማ ጽናት በነበራቸዉ ጀግኖች ልጆቿ አማካይነት ነዉ።
አለማችን ትልቅ የጦርነት አዉድማ ናት ቢባል አባባሉ እምብዛም ከእዉነት የራቀ አባባል አይደለም። በእርግጥም አለም የጦርነት መድረክ ናት። ወደድንም ጠላን ወይም ብናምንም ባናምንም ጦርነቶች ሁሉ የተካሄዱት የህዝብን ነፃነት በሚደፍሩ ኃይሎችና መብቴንና ነጻነቴን አትንኩ በሚሉ ኃይሎች መካከል ነዉ። የአለማችን ታሪክ ወለል አድርጎ እንደሚያሳየን ደግሞ ይዋል ይደር እንጂ ሁሉም ዘለቄታዊ ድሎች የተመዘገቡት የአላማ ጽናት ባላቸዉ መብቴንና ነጻነቴን አትንኩ በሚሉ ኃይሎች ነዉ እንጂ የመሳሪያ ጋጋታ በተሸከሙ ኃይሎች አይደለም። የመሳሪያ ጋጋታ የተሸከመና ብዛት ያለዉ ወታደር ያሰለፈ ነገር ግን ለምን እንደሚዋጋ የማያዉቅና የአላማ ጽናት የሌለዉ ሠራዊት ግዜያዊ የጦር የጦር ሜዳ ድል ለያገኝ ይችላል፤ ሆኖም ጦርነቱን አሸንፎና የህዝብን ነጻነት ቀምቶ መዝለቅ በፍጹም አይችልም።
የአለም ታሪክ በነጭ ወረቀት ላይ በጥቁር ቀለም ቁልጭ አድርጎ የጻፈዉ አንድ ግዙፍ ሀቅ ቢኖር እልፍ ታንክና እልፍ አዕላፋት መድፎች ቢታጠቁም አምባገነኖች ለግዜዉ እንደተቆጣ ነብር ያስፈራሉ እንጂ ህዝባዊ አለማና ጽናት ያለዉ ጦር ፊት ሲቆሙ ፀሐይ እንደገላመጠዉ በረዶ ሟሽሸዉ የሚጠፉ ደንባራ ፈረሶች ናቸዉ። ለዚህም ነዉ ህዝብ አምባገነኖችን የወረቀት ላይ ነብር እያለ የሚጠራቸዉ።
ዛሬ ዕድሜዉ 35 እና ከዚያም በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚኒልክን ቤ/መንግስት ተቆጣጥረዉ የረገጡትን፤ የገደሉትንና መብቱንና ነጻነቱን ገፍፈዉ ያዋረዱትን ሁለት የወረቀት ላይ ነብሮች ያስታዉሳል የሚል ሙሉ እምነት አለን። ደርግ በ1967 ዓም “ያለ ምንም ደም እንከኗ ይዉደም” እያለ ወደ ሥልጣን ሲመጣ በፊዉዳሉ ስርዐት ጀርባዉ የጎበጠዉን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ደስ አሸኝቶ ነበር። እየቆየ ሲሄድና የተደበቀ ትክክለኛ መልኩ አደባባይ ሲወጣ ግን ያንን “ያለ ምንም ደም” የሚለዉን መፈክሩን ረስቶ ኢትዮጵያን የደም ገንዳ ሲያደርጋት በኢትዮጵያ ህዝብ ተጠልቶ አይንህን ለአፈር ተባለ። በሩሲያ ሰራሽ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች አስካፍንጫዉ የታጠቀዉና በቁጥሩና በወታደራዊ ብቃቱ አፍሪካ ዉስጥ ትልቁን ሠራዊት የገነባዉ ደርግ “እንደ ዉኃ የሚያጥለቀልቅ ኃይል አለኝ” እያለ ቢፎክርም እሱ እራሱ ተጥለቅልቆና በያለበት ተሸንፎ አገራችን ኢትዮጵያን ለዘረኛ አምባገነኖች ያስረከበዉ ለእግሩ ጫማ ለወገቡ መታጠቂያ በሌለዉ የገበሬ ጦር ተሸንፎ ነዉ። ደርግ እንደታጠቀዉ መሳሪያ ብዛት፤ እንዳደራጀዉ ወታደራዊ ብቃትና እንደ ወታደራዊ መሪዎቹ ችሎታ ቢሆን ኖሮ ደርግን እንኳን ተዋግቶ ለማሸነፍ በዉግያ ለመግጠምም የሚያስብ ኃይል በፍጹም አይነሳም ነበር፤ ነገር ግን ድል ምን ግዜም ቢሆን የመሳሪያ ጋጋታ ዉጤት ሳይሆን የራዕይ ጥራትና የአላማ ጽናት ዉጤት በመሆኑ በወቅቱ ይህንን የተገነዘቡ ኃይሎች ህብረትና አገር ዉስጥ የተቀሰቀሰዉ ህዝባዊ ቁጣ አንድ ላይ ሆነዉ ደርግን ጠራርገዉ የታሪክ ቆሻሻ ዉስጥ ሊጨምሩት ችለዋል።
ዛሬ ደርግን አሸንፈዉ ደርግ የተቀመጠበት ወንበር ላይ የተቀመጡት ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የአገርን ኃብት ከመዝረፍ፤ የተቃወማቸዉን ከመግደልና የኢትዮጵያን አንድነት ከማፍረስ ዉጭ እንዴትና ለምን ደርግን የመሰለ ሠራዊት እንዳሸፉ የተገነዘቡ አይመስልም። ወያኔዎች ደርግ ከወደቀ ከ24 አመት በኋላ ዛሬም በየቀኑ ደርግን ቢኮንኑም ተቀምጠዉ አገር የሚገዙት ልበቢሱ ደርግ የተቀመጠበት ወንበር ላይ ነዉና የደርግ በሽታ ተጋብቶባቸዉ እነሱም እንደደርግ ልበቢሶች ሆነዋል።
ኢትዮጵያ በየዘመኑ እያደገና እየዘመነ የመጣ፤ ከተለያዩ የአገራችን ክፍሎች የተዉጣጣና ሞያን፤ ችሎታንና ወታደራዊ ሳይንስን አዳብሎ የታጠቀ ዘመናዊ የአገር መከላከያ ተቋም የነበራት አገር ነበረች። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ ይህንን ዘመናዊ የአገርና የወገን መመኪያ የሆነ ሠራዊት አፍርሰዉና በየበረሃዉ ለእናት አገሩ የተዋደቀዉን ሰራዊት ለማኝ አድርገዉት ነዉ እነሱ ወርቃማዉ ዘር ብለዉ በሚጠሩት ዘር የበላይነት ላይ የተመሰረተ የመከላከያ ተቋም የገነቡት። ወያኔ የገነባዉ የመከላከያ ተቋም ባለፉት ሃያ አራት አመታት ዉስጥ አዲስ አበባ፤ ኦጋዴን፤ ጋምቤላ፤ ደቡብ ኦሞና በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የወሰዳቸዉን ፀረ ህዝብና ፀረ አገር እርምጃዎች ስንመለከት ተቋሙ እዉነትም ለአገር ጥበቃ ሳይሆን የወያኔን የበላይነት ለማረጋገጥ የተቋቋመ ኃይል መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይችላል።
ይህ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪዎች የሚታዘዘዉ መከላከያ ሠራዊት ጋምቤላና ኦሞ ሸለቆ ዉስጥ ገበሬዉ ከቀዬዉ ተፈናቅሎ መሬቱ ባዕዳን ሲቸበቸብ አፉን ዘግቶ እንዲመለከት አድርጓል። ይሄዉ ሠራዊት በ1997 ዓም በአግአዚ ነብሰ ገዳዮች እየተመራ የህዘብ ድምጽ ይከበር ያሉ ከ200 በላይ ሠላማዊ ዜጎችን በግፍ ጨፍጭፏል፤ ከዚህ በተጨማሪ የወያኔ መከላከያ ሠራዊት አጋዴንና ጋምቤላ ዉስጥ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽሟል አሁንም እየፈጸመ ነዉ። እዚህ ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ትኩረት ሰጥቶ ሊመለከተዉ የሚገባዉ ነገር አለ፤ እሱም ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች ልማታዊ ሠራዊት ብለዉ እያሞካሹና “የመከላከያ ኃይሎች ቀን” የሚል ስያሜ ሰጥተዉ በየአመቱ ማክበር የጀመሩት በዐል የሚያወድሰዉ ይህንኑ አንድነቱንና ነፃነቱን እጠብቃለሁ ብሎ ቃል ኪዳን የገባለትን ህዝብ ያለ ርህራሄ የሚጨፈጭፈዉን የወያኔ ሠራዊት ነዉ። በተለይ ወያኔ ባለፈዉ ሳምንት ባህር ዳር ዉስጥ ያለ የለሌ የመሳሪያ ጋጋታዉን አደባባይ አዉጥቶ ለህዝብ እያሳየ ባከበረዉ የመከላከያ ቀን በዐል ለህዝብ ማስተላለፍ የፈለገዉ መልዕክት ቢኖር “ይህንን እያያችሁ ከወያኔ ጋር በእሳት አትጫወቱ “ የሚል የሞኝ መልዕክት ነዉ።
ይህ ባህር ዳር ላይ የተላለፈዉ መልዕክት ለማን እንደሆነና በተለይ ባህር ዳር የመልዕክቱ ማስተላለፊያ ቦታ ሆና የተመረጠችበት ምክንያት ለማንም ኢትዮጵያዊ ግልፅ ይመስለናል። የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች መሰባሰቢያ የሆነዉ ህወሓት የተወለደዉም ሞቶ የሚቀበረዉም ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን እሱም ደጋፊዎቹም ካወቁ ቆይቷል። ዉቧና የጀግኖች መፍለቂያ የሆነችዉ ባህር ዳር ደግሞ ይህንን የወያኔን የቀብር ጉዞ ከጀመረች አመታት አስቆጥራለች። እንገዲህ ወያኔ በየቀኑ ከባድ መሳሪያና ስፍር ቁጥር የሌለዉ ወታደር ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚያጓጉዘዉ ከዚሁ ከማይቀርለት ዉድቀቱ የሚያድኑት እየመሰለዉ ነዉ። እዚህ ላይ አንድ ወያኔ በፍጹም ያልተረዳዉ ነገር ቢኖር ህወሓትን ከኢትዮጵያ ምድር ጠራርጎ የሚያጠፋዉና ግብዐተ መሬቱን የሚፈጽመዉ ይሄዉ ወያኔ በነጋ በጠባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚያጓጉዘዉ ሠራዊት መሆኑን አለመረዳቱ ነዉ። የወያኔ አይን ያወጣ ዘረኝነት በከፍተኛ ደረጃ ከተንጸባረቀባቸዉና በየቀኑ በዘረኝነት እሳት ከሚለበለቡ የህብረተሰብ ክፍሎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የመከላከያ ሠራዊት ነዉ። ይህ ሰራዊት እንደ መሬት የሚረግጡትን የወያኔን አለቆቹን ትዕዛዝ ተቀብሎ ከታሰረበት የዘረኝነት እስር ቤት ነፃ ሊያወጡት በሚታገሉ የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ኃይሎች ላይ መሳሪያዉን ያዞራል ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ያለ አይስለንም፤ በሌላ በኩል ደግሞ የወያኔን የመሳሪያ ጋጋታ አይቶ ለእናት አገሩ አንድነትና ለኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ነጻነት ህይወቱን ከመስጠት ወደ ኋላ የሚል ኢትዮጵያዊ ቢኖር እሱ ከወያኔ ጋር በጥቅም የተጋባ ከሃዲ መሆን አለበት። የኢትዮጵያ ህዝብ ምንግዜም ቢሆን በወሬ ቱማታና በመሳሪያ ጋጋታ ትጥቁን ፈትቶ አያዉቅም። በ1930ዎቹ ፋሺስት ጣሊያኖችንና በ1970ዎቹ ወታደራዊዉን ደርግ ተዋግቶ ያሸነፈዉ እነዚህ ኃይሎች የታጠቁትን መሳሪያ እየቀማ በተዋጋቸዉ ነጻነት የጠማዉ ኃይል ነዉ። የዛሬዎቹ የወያኔ ፋሺስቶች እጣም ጣሊያንና ደርግ ከገጠማቸዉ ሽንፈት የተለየ አይሆንም።
የአገራቸዉን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ከጠላት ለመከላከል የመከላከያ ሠራዊትን የተቀላቀሉ የኢትዮጵያ ልጆች “ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት” የሚለዉን የአባቶቻቸዉ ምሳሌያዊ አባባል ምንነት በሚገባ የሚረዱ ይመስለናል። ስለሆነም ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ በዘር ለይቶ እየረገጣቸዉ፤ እያዋረዳቸዉና ከሰዉ በታች አድርጎ እየተመለከታቸዉ ይህንን ቅጥ ያጣ በደል ለማረሳሳት የመከላከያ ቀን እያለ በሚያከብረዉን የይስሙላ በዐል እንድም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባል ሊታለል አይገባም። ከአግአዚ ነብሰ ገዳዮች ዉጭ ያለዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንደማንኛዉም የወያኔ እስረኛ እንደሆነ የህብረተሰብ ክፍል ነፃ መዉጣት የሚገባዉ ክፍል ነዉ። ይህ የህዝብ ወገን የሆነዉ የመከላከያ ሠራዊት እራሱን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹንና እህቶቹን ጭምር ከወያኔ ዘረኝነት ነጻ ሚያወጣት አለበት። እስከቅርብ ግዜ ድረስ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ብዙም አማራጭ ስላልነበራቸዉ አንገታቸዉን ደፍተዉ የጠላታቸዉን የወያኔን ትዕዛዝ እየተቀበሉ ሲፈጽሙ ቆይተዋል፤ አሁን ግን አንገታቸዉን ቀና አድርገዉ የወያኔን አንገት የሚያሰደፉበት አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮላቸዋል። ዛሬ ለእናት አገራቸዉ ነጻነት በህይወታቸዉ ቆርጠዉ ብረት ያነሱ የነጻነት አርበኞች የመከላከያ ሠራዊት የወያኔ አለቆቼን ትዕዛዝ ላለመቀበልም ሆነ ወይም የታጠቀዉን መሳሪያ ወደ ጠላቱ ወደ ወያኔ ማዞር የሚችልበትን አመቺ ሁኔታ ፈጥረዉለታል።
ዉድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ሆይ ጨለማዉ ሊጠራ ሲል ይበልጥ ይጨልማልና ወያኔ ወደ ሰሜናዊዉ የአገራችን ክፍል የሚያጓጉዘዉ የመሳሪያ ጋጋታና የሠራዊት ብዛት በፍጹም ልትደናገጥ አይገባም። ወያኔን ካንተ በላይ በቅርብ የሚያዉቀዉ የለም፤ የወያኔ ኃይለኝነትና ትልቅ መስሎ መታየት አንተ በዉስጡ ስላለህበት ብቻ ነዉ። ስለዚህ ይህንን ፀረ ኢትዮጵያ ኃይል ለቅቀህ በያለህበት ላንተ፤ ለወገኖችህና ለእናት አገርህ ነፃነት መከበር ከቆረጡ ወገኖችህ ጋር በፍጥነት ተቀላቀል። ይህንን ማድረግ የማትችለዉ ደግሞ ወያኔ ከገዛ ወገኖችህ ጋር እንድትዋጋ ትዕዛዝ ሲሰጥህ የታጠከዉን መሳሪያ ወደ ወገኖችህ ሳይሆን ወደ ራሱ ወደ ወያኔ አዙር። ወያኔ ለትንሽ ግዜ የማይበገር መስሎ ሊታይ ይችል ይሆናል የማይቀረዉ የዘለቄታ ድል ግን ምን ግዜም የህዝብ ነዉ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ደግሞ ትናንት አንደነበረ ሁሉ ዛሬም የኢትዮጵያ ህዝብ አለኝታ ነዉ።
ድል የህዝብ ነዉ!

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በጨለማ ቤት መታሰራቸውን አስታወቁ

February 25,2015

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ የሚገኙት የሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀጠና/ዞን አመራሮች ለ16 ተከታታይ ቀናት በጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ለፍርድ ቤት አስታወቁ፡፡
ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ (የፓርቲው የጎንደር አደራጅ አቶ አግባው ሰጠኝ)፣ የአንድነት እና መኢአድ የዞን አመራሮች ‹‹መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ›› እያሉ እንደሚደበድቧቸውና በጨለማ ክፍል እንዳሰሯቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ አሁንም መረጃየን ሰብስቤ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ 8 ቀናት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡
ተጠርጣዎቹ በማዕከላዊ እየደረሰባቸው የሚገኘውን ሰቆቃ አስመልክተው ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የቀረበበትን አቤቱታ እንዲያስተካክል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በጎንደርና ጎጃም አካባቢዎች የዛሬ አራት ወር ገደማ በፖሊስ ታስረው ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ እንዲዛወሩ የተደረጉ ሲሆን፣ ጠበቃቸው በተደረገባቸው ክልከላ ምክንያት ተጠርጣሪዎቹን ካገኟቸው 2 ወር እንደሞላቸው ተናግረዋል፡፡ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አቶ አግባው ሰጠኝ እየተፈጸመበት ያለውን የመብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አድማውን ከጀመረ ሁለተኛ ቀኑ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፍርድ ቤቱ በሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መሰረት አመራሮቹ የካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Tuesday, February 24, 2015

የጦፈ ሙስና ከመንገድ ሥራ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና ከቤቶች ልማት

February 24,2015
በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ ነው - ሚኒስትሩ

lightrail road

* ከ30 እስከ 40% የግንባታ ወጭ ይዘረፋል!!

የኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና፣ ከቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑን አምነዋል።

 የፀረ ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው ጥናት በባቡር መስመር ግንባታ 2.3 ኪሜ የባቡር ሃዲድ መስመር በሙስና ምክንያት ከደረጃ ውጭ እንዲሆን በመደረጉ የ124 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ደርሷል። የአደጋ መከላከያ ብረቶች የተሰሩት ከወጣላቸው የጥራት ደረጃ በሶስት እጅ ያነሱ ሆነው በመገኘታቸው ጉዳዩ ለቦርድ ሰብሳቢው አርከበ እቁባይ ቢቀርብም ምላሽ ሳይሰጠው በመቅረቱ በቢሊዮየኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ፣ን የሚቆጠር ገንዘብ የት እንደገባ ማወቅ አለመቻሉን ገልጿል።
የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ምላሽ የሰጡት ሚኒስትር መኩሪያ ሃይሌ፣ ችግሩ የተፈጠረው ለምርጫው ሲባል የባቡሩ ግንባታ እንደ ትልቅ የምርጫ ማሳመኛ በመያዙ ነው ።
የግንባታ ኢንዱስትሪው ከሚያወጣው ወጪ ከ30 እስከ 60 በመቶ የሚሆነው በሙስና ይባክናል ሲሉም ሚኒስትሩ አክለዋል።
እንደዚያም ሆኖ በቅርቡ የተመረቀ የአዲስ አበባ መለስተኛ የባቡር ግንባታ፣ አገልግሎት ከመጀመሩ ከወዲሁ በርካታ የመፈራረስ ችግሮች እያጋጠሙት ነው። ለፖለቲካ ፍጆታና ለፕሮፓጋንዳ ሲባል ቶሎ ቶሎ እንዲሰራ ከማድረግ ዉጭ እነ አቶ አርከበ እቁባይ የሕዝቡን ፍላጎት ከግምት ያላስገቡ ሲሆን፣ አስፈላጊ የጥንቃቄ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በዋናነት የባቡ ሃዲዱ ከተማዋን ለሁለት የከፈለ ሲሆን ከሃዲዱ በስተቀኝ እና በስተግራ ያሉ ነዋሪዎች ለመገናኘት እጅግ በጣም ብዙ ርቀት ለመጓዝ ተገደዋል።