Friday, August 5, 2016

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ለምን ፍርድ ቤት አልቀረበም ?

Augest 5,2015
ከሙሉቀን ተስፋው
በፍርሃት ውስጥ የተዋጠው የወያኔው መንግስት በአማራው ህዝብ ላይ ያለውን ጥርጣሬ እንደቀጠለ ውሎአል በዚህም ምክንያት ኮለኔሉን ወደ ፍርድ አልማቅረቡ ብዙዎቹንም አስቆጥቶአል። ለምን አልቀረበም የሚለውን የዜና ትንታኔ ሙሉቀን ተስፋው ከቦታው ያጠናቀረው አጭር ዘገባ ትንሽ ነገር የሚያጭር ሲሆን ፣ ወያኔ የጎንደር ህዝብን ሃያልነት እና አልበገሬነት እንደዚሁም የትግል ጦር ጃንደረባ እንደሆነ ስለሚያውቅ ብቻ ፍራቻውን ከመግለጽ ተቆጥቦ ከርሞአል ፣ ስለዚህ የህዝቡ አልገዛም ባይነት እና እንቢኝ መሬቴን አልነጠቅም የሚለው የጎንደር ህዝብ ትግል መጨረሻው የሃገሪቱን የትግል የነጻነት ጎራ ሊቀይስ ያሰበ ይመስላል ፣እንደዚህም ሆኖ የሁሉንም ህዝብ አንድነት በጋራ የሚጠይቅ እና በትግሉም አንድ ሆኖ አገር እና ህዝብን የማዳን ስራ ሊሰራ ይገባአዋል ብለው ብዙሃኑ ያምናሉ ።
በዚህም መሰረት በኦሮሞ ንቅናቄ ላይ ለሚመለከተው ሁሉ በጋራ የምንቀሳቀስ ሲሆን የኦሮሞ ተወላጆች ግን በግለኝነት የኦሮሞነትን ነጸብራቅ ይዘው የሚወጡ ከሆነ አላማ እና ሴራቸው ከወያኔ የማይተናነስ አገርን የማጥፋት ስራ ስለሆነ ከዚህ ተቆጥበው ትግሉን በጋራ አንድ በመሆን ፣ለአንድቷ ሃገራችን መታገል ይገባናል ሲሉ የጎንደር ህዝብ ጥያቄ አቅርበዋል ።
ኦነጋዊ ስርአትም ሆነ ወያኔአዊ ስርአት ሳይሆን ኢትዮጵያዊነት ስርአት መገንባት ይኖርብናል።
በጎንደር የዐማራ ተጋድሎው ቀጥሏል፤ የኮሎኔሉ ፍርድ ቤት አለመቅረብ መነሻ ምክንያት ሆኗል
• ሁሉም የኮሜቴው አባላት ለነሐሴ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጧቸዋል
• ፖሊስ አስለቃሽ ጪስ እየተጠቀመ ነው

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ፍርድ ቤት ቀርበዋል በሚል በብዙ ሽዎች የሚቆጠሩ ዐማሮች በሰሜን ጎንደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ረፋዱ ላይ ተሰባሰቡ፡፡ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሌሉበት ሊመለከተው መሆኑን ያወቁት የጎንደር ሕዝብ ፍርድ ቤቱ ሳይዘጋ ኮሎኔል ከሳሽ ካለውም ይከሰስ ከሌለውም በቶሎ ወደ ቤተሰቦቹ ይመለስ የሚል ጥያቄ በፍርድ ቤቱ አቅራቢያ ጩኸት በረከተ፡፡
የአድማ ብተና ፖሊስ የፍርድ ሒደቱትን ለመከታተል በመጣው የዐማራ ሕዝብ ላይ የኃይል ርምጃ መውሰድ ሲጀምር የወጣቶቹ ቁጣ ገነፈለ፡፡ የፍርድ ቤቱ መስኮቶች በድንጋይ ረጋገፉ፡፡ ወያኔ ሌቫ፤ ወልቃይት ዐማራ… ወዘተ የሚሉ የዐማራ ተጋድሎ ድምጾች በመለዋ የጎንደር ከተማ ከጫፍ ጫፍ ተስተጋባ፡፡ ጎንደር የሚገኘውን የወያኔ ደኅንነት ቢሮ አካባቢ የተጋድሎ ሠልፍ በረከተ፡፡ ፒያሳና መስቀል አደባባይ በአንድ ሳምንት ብቻ ሁለት ጊዜ ዐማሮች ጩኸታቸውን ማሰሚያ መድረክ ሆኑ፡፡
እስከዚህ ሰዓት ድረስ በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋ ባይኖርም የአድማ ብተና ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ ከመጠን በላይ በዐማሮች ላይ እየበተነ ነው፡፡ ከተጋድሎው ተሳታፊዎች መካከል አንድ ሰው ከፍተኛ አደጋ የደረሰ ቢሆንም አሁን ላይ በሙሉ ጤንነት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ኮሎኔል ደመቀ በሌሉበት ጉዳያቸውን እንዲታይ ወስኗል፡፡ ኮሎኔል ደመቀ ከማረሚያ ቤት ሆነው በቪዲዮ ኮንፈረንስ (ፕላስማ) ለፍርድ ቤቱ ከሳሽ ከቀረበባቸው ይከላከላሉ፤ ካልቀረበም ፍርድ ቤቱ ወሳኔ ይሰጣል የሚል መልስ ቢኖርም የጎንደር ከተማ ሕዝብ አሁንም ተቃውሞውን እያሰማ ነው፡፡
በተያያዘም በማእከላዊ ፍርድ ቤት ያሉት የታፈኑ የወልቃይት ጠገዴ ዐማራ ማንነት ኮሚቴ አስተባባሪዎችም ነሐሴ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ አዲስ አበባ ማእከላዊ ታፍነው የሚገኙት የኮሜቴው አባለት አቶ አታላይ ዛፌ፣ አቶ ጌታቸው አደመ፣ መብራቱ ጌታሁን፣ አቶ አለነ ሻማ፣ አቶ አዲስ ሰረበ እና አቶ ነጋ ባንቲሁን ናቸው፡፡
አዳዲስ ነገሮችን በየሰዓቱ እናቀርባለን፡፡
የዐማራ ሕዝብ ትግል ያሸንፋል!!









No comments: