Monday, August 1, 2016

ብአዴን በአማራ ህዝብ ብሶት ላይ ተሳለቀ!!

Augest 1,2016
በአማራነታችን እዬደረሰብን ያለው ግፍ አንገሽግሾን ወደ አደባባይ ወጥተን ድምፃችንን ያሰማንበትን ሰላማዊ ሰልፍ ክልሉን አስተዳድራለሁ የሚለው ብአዴን የሰጠው መልስ ሚሊዬን አማሮችን አስቆጥቷል። የአማራ ህዝብ ሳይወክለው የአማራን ህዝብ እያስተዳደረ ያለው ብአዴን የትናንቱ ሰልፍ ምክንያት የመልካም አስተዳደር እና የልማት ጥያቄ ነው ሲል በአማራነት ጥያቄ ላይ ተሳልቋል።
የሰላማዊ ሰልፉ ዋና አላማ በወልቃይት ምድር ላይ በሕወሓት ማንአለብኝነት በአማራነታችን ላይ የተጫነብንን ትግራዊነት ማውገዝ እና አማራነታችን ማፅናት ነው። በተጨማሪም የአማራነት ማንነታቸውን ለማስከበር በሰላማዊ መንገድ እየታገሉ ያሉ የወልቃይት አማራ ማንነት ጠያቂ ኮሜቴዎቻችን ላይ ህወሓት ያካሄደችውን አፈና መቃወም ነበር የሰላማዊ ሰልፉ አላማ ። በአጠቃላይ የጎንደሩ ሰላማዊ ሰልፍ የአማራ ህልውናን የተመለከተ ሰልፍ ነው።በሕወሓት እና በተቀጥላዎቿ አማካኝነት በአማራነታችን እዬደረሰብን ያለውን ተቆጥሮ የማያልቅ ግፍ ለመቃወም እና ለማውገዝ ያደረግነውን ሰላማዊ ሰልፍ አማራን አስተዳድራለሁ የሚለው ብአዴን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ነው ብሎ መሳለቁ ምን ያህል ለአማራ ህዝብ ባዳ እንደሆነ እና የህወሃት ቅርብ ዘመድ እንደሆነ በግልፅ አይተናል ። በመግለጫው ላይ አንድም ቦታ‪#‎ወልቃይት‬ የምትል ቃል አለመግለፁ ብአዴን መቼውንም የአማራን ህዝብ ጩኸት ሊሰማ የማይችል ድርጅት እንደሆነ በድጋሜ አስመስክሯል።
ስለሆነም ሕዝባችን ድምፁ እስኪሰማ ድረስ ትግሉን አጠናክሮ ይቀጥላል። የጎንደር አማራ ድጋሜ ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት አስቧል። መላው አማራም ከጎኑ ይሰለፍ ። ሰላማዊ ሰልፉ በጎንደር ብቻ ሳይወሰን በተለያዩ የአማራ ከተሞች ላይ እንደሚካሄድ የታመነ ነው።
ብአዴን ውስጥ ያላችሁ ትክክለኛ የአማራ ልጆች ከህዝብ ጎን እንድትቆሙ አበክረን እንመክራለን!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!

No comments: