Sunday, February 21, 2016

የ24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በገፍ እየገዱ መሆናቸው ታወቀ፡፡

February 21,2016
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
በሰሜን ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍል በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለረጅም ዓመታት የዘለቀ የሽምቅ ውጊያ ጥቃት ሲደርስበት፣ እስከ ሬጅመንት ድረስ እየተደመሰሰ ሲፈርስና እንደገና በሰው ኃይልና በጦር መሳሪያ በተደጋጋሚ ሲገነባ የኖረው 24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በውጊያ በእጅጉ ተሰላችተውና በስርዓቱ ተስፋ ቆርጠው በከፍተኛ ሁኔታ በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በተለይም ደግሞ የሽምቅ ውጊያ ጥቃቶች የመጀመሪያ ገፈት ቀማሽ የሆኑ በሁመራና አካባቢው ሰፍረው የቆዩ ሬጅመንቶች ውልቃቸውን በመቅረታቸው ከአዘዞ እና ጭልጋ ሌሎች ሬጅመንቶችን አንስቶ የመተካት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ የነፃነት ድርጅቶች ክንድ እየፈረጠመ መምጣት እና ዕለት ከዕለት በሚያደርጓቸው የሽምቅ ውጊያ ጥቃቶች የሚያሳርፉት ዱላ እየበረታ መሄድ በዋነኝነት አርበኝነት በሚፋፋምበት አካባቢ የሚገኘውን 24ኛ ክፍለ ጦር አፍረክርኮታል፡፡

No comments: