Saturday, April 30, 2016

ፍሪደም ሃውስ ኢትዮጵያና ኤርትራን የጋዜጠኞች ወህኒ ቤት ብሏቸዋል

April 30,2016
ዋና ጽ/ቤቱን በአሜሪካ ያደረገው ፍሪደም ሃውስ ባወጣው ሪፖርት ሁለቱን የምስራቅ አፍሪካ አገራት ኢትዮጵያና ኤርትራን ከሰብ ሰሃራን አገራት መካከል ዋነኞቹ የጋዜጠኞች እስር ቤት በማለት ሰይሟቸዋል፡፡
Eskinder-Nega-ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ የተወሰኑ ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን ከእስር ብትፈታም ሪፖርቱ ከኤርትራ በመቀጠል ዋነኛዋ ጋዜጠኞችን አሳሪ አገር በማለት ፈርጇታል፡፡
ሪፖርቱ በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ጋዜጠኞች ባለፈው ዓመት የፖለቲካ ጫናዎች ተደርጎባቸዋል ብሏል፡፡
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የብሩንዲው ፕሬዘዳንት ህገ መንግስቱን በማሻሻል ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ እንደሚቀርቡ ማሳወቃቸውን ተከትሎ ነጻ የነበሩ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች ተዘግተዋል ወይም እንዲጠፉ ተደርገዋል በማለት ጠቅሷል፡፡
እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በምስራቅ አፍሪካ በ2016 መጀመሪያ በኡጋንዳ በተካሄደው ምርጫ ጋዜጠኞች ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ሽፋን በመስጠታቸው ከፍተኛ አድልኦ ተደርጎባቸዋል፡፡በኬንያ ገዳቢ ህጎችን በሚዲያው ላይ ከማውጣት አንስቶ ስልታዊ የሆኑ ጫናዎች በጋዜጠኞች ላይ መደረጉን አጋልጧል፡፡
በፍሪደም ሃውስ ማውጫ መሰረትም ኢትዮጵያ፣ኤርትሪያ፣ሱዳን፣ደቡብ ሱዳን፣ሶማሊያና ጂቡቲ ከሌሎች 20 የአፍሪካ አገራት ጋር ነጻ ሚዲያ የሌለባቸው ተብለው ተቀምጠዋል፡፡
እንደ ሪፖርቱ ከሆነም ያለፈው ዓመት ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት በ12 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ እጅግ ዝቅተኛ ነጥብ የተመዘገበበት በመሆን ተጠናቅቋል፡፡
በ2007 ሱዳንና ግብጽ ከፍተኛ የሆነ ማሽቆልቆል የተመዘገበባቸው አገሮች በመሆን ተመዝግበዋል፡፡
ሪፖርቱ ከአለማችን ህዝብ 41% በአንጻራዊነት ነጻ ሚዲያን የሚያገኝ ሲሆን 46% የሚሆነው ደግሞ ነጻ ሚዲያ በሌለበት ከባቢ ውስጥ ይኖራል ብሏል፡፡
ምንጭ ፍሪደም ሃውስ

Sunday, April 24, 2016

የጋምቤላ ክልል ፕሬዘዳንትና ሪክ ማቻር የተሳፈሩባት መኪና በሰልፈኞች ጥቃት ደረሰባት

April 23,2016
ስለፈ
 በጋምቤላ ክልል ጃዊ በተባለ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ በደቡብ ሱዳን ሱደተኞች ተጨፍጭፈው ከ17 የሚልቁ ኢትዮጵያዊያን መገደላቸው ቁጣን ቀስቅሷል፡፡
በዛሬው ዕለት ድርጊቱን ለማውገዝ የጋምቤላ ከተማና አካባቢዋ ህዝብ ወደ አደባባይ ወጥቷል፡፡ሰልፈኞቹ ኢትዮጵያዊያኑን በግፍ በገደሉ ስደተኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለመጠየቅ በሞከሩበት ሰዓት ፌደራል ፖሊሶች ሰልፈኞቹን ህገ ወጥ ሰልፍ በመሆኑ እንዲያቆሙ በመንገር ጥይት መተኮስ በመጀመራቸው ሰላማዊው ሰልፍ መልኩ ተቀይሯል፡፡ሰልፈኞቹ ወደ ስደተኞቹ ካምፕ በማምራት ደቡብ ሱዳናዊያን ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከሩ ቢሆንም በወታደሮች ታግተው የተወሰኑት መታሰራቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ሰልፈኞቹ በጋምቤላ የደቡብ ሱዳናዊያን ናቸው ያሏቸውን ሆቴሎች ፣መኖሪያ ቤቶችና መኪኖችን በድንጋይ መደብደባቸው የተሰማ ሲሆን የደቡብ ሱዳኑ ሪክ ማቻርና የጋምቤላ ክልል ፕሬዘዳንት  ጋትሏክ ቱት የተሳፈሩባት መኪና በሰልፈኞቹ በድንጋይ መደብደቧን ነገር ግን በሰዎቹ ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱ ተሰምቷል፡፡

Saturday, April 23, 2016

በወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ሰቆቃ፤ ሞትና ስደት ለማስቆም ሁላችንም ጠንክረን እንታገል!!!

April 23,2016
የአርበኞ ግንቦት 7 ሳምንታዊ ርዕስ አንቀጽ
አፕሪል 22 2016
ህወሃት ሥልጣን ከተቆጣጠረበት 1983 ጀምሮ በህዝባችንና በአገራችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ወንጀል ቁጥር ስፍር የለውም። እስከ አምናና ካቻምና የሆነውን እንኳ ትተን በዚህ በያዝነው አመት ብቻ በወገኖቻችንና በአገራችን ላይ ከተፈጸሙት ወንጀሎች ጥቂቶቹን ብናስታውስ የሚከተሉትን እናገኛለን ፤
በጎንደር በኩል አገራችንን ከሱዳን ጋር የሚያዋሰነውን ለምና ድንግል መሬት ቆርሶ ለርካሽ የፖለቲካ ጥቅም ማራመጃ ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት የተፈጸመውን ስውር ስምምነት የተቃወሙ በርካታ ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ ስቃይና እንግልት ተፈጽሞአል።
ለዘማናት ተዋህዶ የኖረውን የቅማንትና የአማራ ህዝብ በማንነት ጥያቄ ለመከፋፈልና ለማጋጨት በተደረገው ደባ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ህይወት እንዲቀጠፍ ተደርጎአል።
የወልቃይት ህዝብ ያነሳውን የማንነት ጥያቄ ለማዳፈን ሲባል ለዓመታት ወደ ክልሉ ተሰዶ በሠላም ሠርቶ የሚኖረውን የትግራይ ተወላጅ በማስታጠቅና በማነሳሳት በሁለቱ መሃል ጥላቻና ቂም እንዲረገዝ ተደርጎአል።
በደቡብ የአገራችን ግዛት የማንነት ጥያቄ ያነሱና ወያኔ ለሚያካሂደው የስኳር ምርት ከመሬታቸው አንፈናቀልም ባሉ የኦሞ ሸለቆ ነዋሪዎች ላይ ግዲያና እስር ተፈጽሞአል። በባሪያ ፈንግል ዘመን ይካሄድ በነበረ አዋራጅ ሁኔታ ዜጎች ራቁታቸውን እጅና አንገታቸውን በገመድ ታስረው በወታደር መኪና ሲጓጓዙ ታይቶአል።
በአርባምንጭ ፤ በቴፕና ማጂ በአገዛዙ ዘረፋና ሙስና የተማረሩና ተቃውሞ ያነሱ ዜጎች ሽብርተኛ ተብለው ተደብድበዋል፤ ተገድለዋል፤ ታስረዋል፤ ከሥራቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ተጥለዋል።
በብዙ ድካምና ጥረት ያገኙትን ገንዘብ አጠራቅመው ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው መጠለያ ቤት በአነስተኛ ቦታ ላይ የገነቡ በርካታ ዜጎች የሠሩት ቤት ለከተማ ውቤት አይመጥንም ተብሎ በላያቸው ላይ በቡልዶዘር እንዲፈርስ ተደርጎ ለበረንዳ አዳሪነት ተዳርገዋል።
በአፋርና በሱማሌ ክልሎችም እንዲሁ ከመሬት ነጠቃ ጋር በተያያዘ ወንጀል ከመሬታችን አንፈናቀልም ያሉ ዜጎች ታስረዋል ፤ ተገድለዋል ፤ ለስደት ተዳርገዋል።
ሃሳባቸውን በነጻነት ለመግለጽ የሞከሩ፤ የአገዛዙን ዘረኛ አካሄድና ዘረፋ የተቃወሙ በርካታ ዜጎች በተቀነባበረ የሽብርተኝነት ወንጀል እየተከሰሱ ዝብጥያ ወርደዋል፤ እስር ቤት ውስጥ እያሉም በጨካኞችና አረመኔዎች አሰቃቂ ድብደባና ማሰቃያ እርምጃ ተፈጽሞባቸዋል።
ለወያኔ ባለሥልጣናት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ የሆነውን የመሬት ዘረፋ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሥም ለማካሄድ የተደረገውን እንቅስቃሴ ተቃውመው አደባባይ በወጡ የኦሮሚያ አካባቢ ተወላጆች ላይ መጠነ ሰፊ የሆነ ጭፍጨፋ በአጋዚ ጦር እንዲካሄድ ተደርጎአል። በዚህም የተነሳ ከ400 በላይ ዜጎች ህይወት ተቀጥፎአል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ከትምህር ገበታቸው ታድነው እስር ቤት ተወርውረዋል፤ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ዜጎች አካባቢያቸውን ለቀው ተሰደዋል።
ህዝባችን ከፍተኛ የረሃብ አደጋ አንዣቦበት አለም አቀፍ ለጋሾች ህይወት ለማዳን በሚራወጡበት ወቅት ለባለሥልጣናቱ መኖሪያ ዘመናዊ ቪላ ለመገንባት ከመንግሥት ካዜና በብዙ መቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ወጪ እንዲሆን ተደርጎአል።
የወያኔ መሪዎች ከደሃው ህዝብ ጉሮሮ እየዘረፉ ወደ ውጪ ከሚያሸሹት በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ውስጥ አምስት ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ በአንድ የወያኔ አባል በሻንጣ ተይዞ እንግሊዝ አገር ለማስገባት ሲሞከር ተይዞአል።
በቅርቡም በቻይና አየር ማረፊያ በተመሳሳይ መንገድ የተገኘ ብዙ ሺህ የአሜሪካን ዶላር ለሥርዓቱ ቅርበት እንዳለው በተገለጸ ሰው እጅ ተገኝቶ በቁጥጥር ሥር ከዋለ ቦኋላ በባለሥልጣናቱ ጣልቃገብነት መለቀቁ ተዘግቦአል።
ይህ ሁሉ ሰቆቃና ግዲያ መንግሥት ነኝ በሚለው የህወሃት አገዛዝ በወገኖቻችንና በአገራችን ላይ መፈጸሙ አንሶ ድንበር አቋርጠው ገቡ የተባሉ ታጣቂ ሃይሎች ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ከ230 በላይ ወገኖቻችንን ገድለው ከ150 በላይ ህጻናትን ከእናቶቻቸው ጉያ ነጥቀው ተሰውሮአል። በጣም የሚያሳዝነውና አገራችን ያለቺበትን የውድቀት ደረጃ ፍንትው አድርጎ የሚያሳየው ደግሞ በሁለት ቀናት ዕድሜ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋ በወገኖቻችን ላይ ፈጽሞ ወደመጣበት የተመለሰ የውጭ ታጣቂ ሃይል ማንነት እስከዛሬ አልታወቀም መባሉ ነው ።
ሌላው አሳዛኝ ክስተት በአገራቸው ተስፋ የቆረጡና ኑሮ የምድር ስኦል ሆኖባቸው በስደት የተለያዩ አፍሪካ አገሮች ውስጥ በመንከራተት ላይ ከነበሩ ኢትዮጵያዊያን መካከል በጀልባ ወደ አውሮጳ ለማምለጥ ሲጓዙ ከ200 በላይ የሚሆኑት ሜዲትራንያን ባህር ውስጥ ሰጥመው የአሳ እራት ሆነዋል። በታንዛኒያ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙ በርካታ ወጣቶች ለረጅም ወራት በታንዛኒያ እስር ቤት ውስጥ ሲማቅቁ ቆይተው ከተለቀቁ ቦኋላ የታንዛኒያ መንግሥት አገልግሎቱን እንደጨረሰ ዕቃ ኬንያ ጠረፍ ላይ ወስዶ አራግፎአቸዋል። በእርምጃው ደስተኛ ያልሆነው የኬንያ ፖሊስም ወጣቶቹን አፍኖ ወደ መጡበት ታንዛኒያ ምድር በመመለስ አውላላ ሜዳ ላይ አራግፎአቸው ተመልሶአል። አዛኝና ተቆርቋሪ መንግሥት የሌላቸው እነዚህ ወጣቶች በማያውቁት አገር ለጅብ እራት አሳልፈው ተሰጥተዋል ። ይህ ሁሉ መከራና ስቃይ በወገኖቻችን ላይ ሲፈራረቅ ህዝባችንን ለዚህ ሰቆቃ የዳረጉት ወያኔና ግብረአበሮቹ ከህዝብ በዘረፉት ገንዘብ ፎቅ ላይ ፎቅ በመገንባት በዶላር እያከራዩ ሃብት ላይ ሃብት ያከማቻሉ። ልጆቻቸውንና የቅርብ ዘመዶቻቸውን በዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ከአገር እየሸኙ ውድና ምርጥ በተባሉ ትምህርት ቤቶች ያስተምራሉ ።
አርበኞች ግንቦት 7 በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመው ሰቆቃ ፤ ግዲያ ፤ እስርና ስደት መቆም የሚችለው የአፈናው ፤ የግዲያው እና የስደቱ ምንጭ የሆነው የወያኔ አገዛዝ ከህዝባችን ጫንቃ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ መወገድ ሲችል ብቻ ነው ብሎ ያምናል። ለአገሩና ለወገኑ የሚቆረቆር ማንኛውም ዜጋ የዚህን ዘረኛና ከፋፋይ አገዛዝ የሥልጣን ዕድሜ ለማሳጠር የተጀመረውን ሁለገብ ትግል አቅሙ በፈቀደ መንገድ ሁሉ እንዲያግዝና ትግሉን እንዲቀላቀል አርበኞች ግንቦት 7 ወገናዊ ጥሪውን ያቀርባል። ሁላችንም ጠንክረን በመታገል በአገራችንንና በወገኖቻን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ፤ ግዲያና ስደት ማስቆም እንችላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

Tuesday, April 19, 2016

በጋሚቤላ ወገኖቻችን ላይ ለደረሰው ጭፍጨፋ ተጠያቂው ወያኔ ነው!!!

April 19,2016
ባለፈው ዓርብ ሚያዚያ 7 ቀን 2008 ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ድንበር ጥሰው በመግባት በላሬና ጃካዋ ወረዳዎች በሚኖሩ የኑዌር ወገኖቻችን ላይ ጭፍጨፋ ማካሄዳቸውን በአገዛዙ ቁጥጥር ሥር ያሉ ሚዲያዎች ጭምር ዘግበዋል። 

ህወሃት ሥልጣን ከተቆጣጠረ ወዲህ በጋምቤላ ክልል ነዋሪ በሆኑ ወገኖቻችን ላይ እንዲህ አይነት የጅምላ ጭፍጨፋ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በ1996 የህወሃት ልዩ ጦር የተሳተፈበት የዘር ማጥፋት ወንጀል በአኝዋክ ተወላጆች ላይ ተካሂዶ ከ400 በላይ ሰላማዊ ዜጎች ህይወታቸው ተቀጥፎአል። በወቅቱ የፈደራል ጉዳዮች ሃላፊ የነበረው አባ ጸሃይና ሌሎች ቱባ ቱባ የመከላኪያና የደህንነት ባለሥልጣናት እጃቸው እንደነበረበት ቢታወቅም እስከዛሬ ድረስ አንዳቸውም ለፍርድ አልቀረቡም። ከ1996ቱ ጭፍጨፋ በተጨማሪም በክልሉ የሚካሄደውን የመሬት ቅሚያ የተቃወሙ፤ ከአያት ቅድሜ አያቶቻችው የወረሱትንና እትብታቸው ከተቀበረበት በሃይል አንፈናቀልም ያሉ በርካቶች ተገድለዋል ፤ ተደብድበዋል፤ ለእስርና ለስደት ተዳርገዋል። ከእስርና ከስደት ያመለጡ በርካቶችም በገዛ መሬታቸው ለአዳዲሶቹ ባለሃብቶች ጭሰኛ ሆነዋል አለያም ለጎዳና ተዳዳሪነት ተዳረገዋል። ይህ ሁሉ ግፍና መከራ አልበቃ ብሎ ከሰሞኑ ደግሞ "ማንነታቸው ያልታወቁ" የተባሉ ታጣቂዎች ከጎሬቤት ደቡብ ሱዳን ድንበር ተሻግረው ከ208 በላይ የኑዌር ተወላጅ ወገኖቻችንን ጨፍጭፈው ወደመጡበት ተመልሰዋል። ከተጨፈጨፉት ወገኖቻችን ከሃምሳ በላይ የሆኑት ህጻናት ሲሆኑ ሴቶችና አቅመ ደካማ የሆኑ ሽማግለዎች ቁጥርም ቀላል አይደለም። 

ለመሆኑ ወያኔ "ማንነታቸው ያልታወቀ" የሚላቸው እነዚህ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው 40 እና 50 ኪሎ ሜትር ወደ ውስጥ ገብተው ምንም መሣሪያ ባልታጠቁ ወገኖቻችን ላይ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋ ሲፈጽሙ የአገር ዳር ድንበር ለመጠበቅ የተቀጠረው መከላኪያ ሠራዊት አንዳችም የአጸፋ እርምጃ እንዳይወስድ ካምፕ ውስት ተዘግቶ እንዲቀመጠ የተደረገው ለምንድነው?የጥቃት ፈጻሚዎቹ ማንነትና የመጡበት ቦታ እንኳ በትክክል እንዳይታወቅና ተድበስብሶ እንድቀርስ የተፈለገው በምን ምክንያት ነው? የአገር ዳር ድንበርና የዜጎችን ደህንነት በአስተማማኝ የሚጠብቅ በሌለበት የአካባቢው ህዝብ ከጥንት ጀምሮ እራሱንና ንብረቱን የሚከላከልበት ነፍሰ ወከፍ መሣሪያ እንዲፈታ ማድረግ ለምን አስፈለገ?የሚሉ ጥያቄዎች ከጭፍጨፋው በስተጀርባ የወያኔ እጅ እንዳለበት ማሳያ ናቸው። ወያኔ የአገዛዝ ዕድሜውን ለማራዘም አንዱን ብሄር ከሌላው በማጋጨት በመካከላቸው መተማመን እንዳይኖር ፍርሃትና ጥርጣሬ እንዲነግስ ሲያደርግ የኖረ ቡድን ነው። ከዚህም የተነሳ "ድንበር ተሻግሮ ጥቃት ፈጸመ የተባለው ታጣቂ " ጋምቤላ ውስጥ የሚካሄደውን የመሬት ቅርመታ የሚቃወሙትን ለማዳከም ሆን ተብሎ የጋምቤላንና የጎሬቤት ሱዳን ዜጎችን ለማጋጨት ከሚጠነስሰው ተንኮል ውጭ ሊሆን አይችልም። በክልሉ የሰፈረው የአገሪቱ መከላኪያ ሠራዊት ምንም አይነት እርምጃ ሳይወስድ ከ208 በላይ ዜጎችን የጨፈጨፉ ታጣቂዎች ከመቶ በላይ ንጹሃን ዜጎችን አግተው በሰላም ወደ መጡበት መመለስ መቻላቸው ለዚህ ዋቢ ምስክር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 ምንም አይነት መንግሥታዊ ከለላና ጥበቃ በሌለው የኑዌርና የአኝዋክ ህዝባችን ላይ የተፈጸመውን ይህንን ዘግናኝ ጭፍጨፋ አጥብቆ ያወግዛል። የመንግሥትን ሥልጣን ለሃብት ዘረፋ ብቻ እየተጠቀመ ዜጎች ለእንዲህ አይነት ዕልቂት እንዲጋለጡ የአደረገው የወያኔ አገዛዝ በጋምቤላ ለደረሰው ለዚህ እልቂት ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ እንደሆነም ለመላው የአገራችን ህዝብና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስታወቅ ይወዳል።


ንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት 7 በዜጎቻችን ላይ ለደረሰው ለዚህ የጭፍጨፋ ወንጀል ተጠያቂ የሆኑ የወያኔ መሪዎች ህግ ፊት እንዲቀርቡ የጀመረውን ሁለገብ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል። ፍትህ እኩልነትና ነጻነት በአገራችን እንዲሰፍን የሚታገሉ የዲሞክራሲ ሃይሎች ሁሉ በህዝባችን ላይ የሚፈጸመውን ጭፍጨፋና ሰቆቃ ለማስቆም በተናጠል ከሚያካሂዱት ትግል ወደ ትብብርና የጋራ ግንባር እንዲመጡ የሚያደርገውን ጥረት እንደሚገፋበት ይገልጻል። ለዚህ ጥረት መሳካትም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ወገኖች ቀናና ያላሰለሰ ትብብር እንዲያሳዩ ወገናዊ ጥሪውን ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

Monday, April 18, 2016

Saving Ethiopians from Ethiopia

April 18,2016
By Lalisaa Hiikaa
andargachew
Ethiopians

In my previous article, “Refugees in The United States,” I appealed to Ethiopians to rally together in attempt to save Ethiopian immigrants detained here in the state of Florida.  The Oromo Community of Tampa Bay, Ethiopian community members, and Kefyalew Fekade of Miami, organized a massive campaign to save these desperate individuals from deportation.

On behalf of the Oromo Community and Ethiopian Community members, I would like to thank www.zehabesha.com  for promptly publishing the previous article “Refugees in United States.” I also thank Mr. Tamagn Beyene and Dr. Aklog Birara of Global Alliance, Mr. Shibabaw of Tampa, and the Odaa Self Help Association members for the quick and critical financial support they pledged/provided in support of this cause.

I am confident that many of our people have been made aware of the 16 individuals currently detained in the Broward Transitional Center and Krome Detention Facility in Florida. The situation has been extensively reported on ESAT radio, OMN (Oromia Media Network), and in online publications. Tragically, countless Ethiopians in similar plights have been deported in the past, facing horrific consequences. We call on the US government and international humanitarian organizations to investigate the state of these individuals, and hold the Ethiopian government accountable for violations of their human rights. The hope is that the group currently in Florida will avoid deportation and the fate of their predecessors. I continue to believe that we have a moral obligation to stand up in support of our countrymen as they face persecution, detention, and death from the Ethiopian government if deported.

Ethiopia

The Ethiopian government is controlled by incompetent, unqualified dummies who obtained their positions based on loyalty to the TPLF junta and EPDRF. Dedication to the rights of its people and enforcement of laws to protect its citizens does not exist; as everyone from doctors to students; from farmers to businessmen; have been terrorized in their own country for the last 25 years. Those in power are taking the country on extremely dangerous path in order to satisfy their personal greed and financial gain.  Educated citizens are barred from key government positions, and blind followers are recruited into the military to kill their own people. The regime is both dangerous and powerful, committing terrorist acts against Ethiopian citizens both at home and abroad.

Western Hypocrisy

It is difficult, if not impossible, to believe that the US government is not aware of the fate awaiting Ethiopian citizens seeking asylum if deported back to their country. In the most recent “election”, the current government of mannequin prime minister, Haile Mariam Desalegn, claimed victory with 100% of the votes. To any observer, it is clear that opposition is silenced, nonexistent, and there is no democratic process or governance in that country. During a recent interview, US National Security Adviser Susan Rice couldn’t help but laugh when questioned about legitimacy of the election, then illustrating how ridiculous the notion of fairness is within the Ethiopian government. However, the European Union and US Governments were “largely silent” during the elections; instead choosing to celebrate a “peaceful election.”

President Obama’s visit to Ethiopia in 2015 was largely protested by Oromo and Ethiopian Americans; fearing that without addressing human rights issues, the visit simply legitimizes the authoritarian regime and its atrocious acts. During the joint press conference in Addis Ababa on 27 July 2015, President Obama described the Ethiopian regime as a “a democratically elected” government, while Human Rights organizations have extensively reported on the arbitrary arrests of opposition leaders and journalist.  None of these issues were discussed during the president’s visit in which he toasted Champagne with offending government officials. Indeed, billions of dollars continue to be given to Ethiopia from their US, UK, and European allies for “aid,” seemingly in support of a regime that is allowed to render its terrorized citizens voiceless. By allowing the horror to continue, Western governments are simply enabling and arming the regime while ignoring laughing at the victims subjected to the atrocities of the regime.

Could it be true that democracy is not the priority of these governments as claimed? Western leaders appear to speak strongly about human rights and democratic freedom, but actions tell a different story entirely

Ethiopian Government: Terrorist??

According to the 16 Ethiopian detainees, Ethiopian government agents are terrorizing them without consequence from ICE or DHS officials. We would like to ask the Justice and State Departments to launch an investigation into this matter. While the Ethiopian regime kills, tortures, and displaces its helpless people at home, it then works tirelessly to recover those who flee from its tyranny. In contrast, there are countries that go so far as to hire attorneys and help their nationals secure freedom.

The other example of this regimes terrorist activity is the case of Mr. Andargachew Tsige, a UK citizen illegally kidnapped, abused and tortured. Mr. Tsige continues to be held nearly 2 years later without consequence to the Ethiopian government. If Mr. Tsige was a citizen of Russia or Israel, Ethiopia wouldn’t dare oppose demands for his release.

Our People

Sadly, the Ethiopian junta has been successful in its campaign to divide the people of Ethiopia into clashing segments. By instigating conflict, the regime ensures that interethnic groups do not unite, leaving them weaker than if they rallied together.

According to Reuters News Agency, Ethiopian officials said on Saturday that gunmen from South Sudan had crossed the border, killed 140 people and abducted more than 39 children. The Ethiopian government has no regard for the lives of these poor citizens.

As recently as 2015, government security forces burned down businesses owned by Amharas in the Oromo region and blamed it on Oromos; inciting hate and distrust between the groups. Discord is then encouraged using propaganda on TV, radio and other media- spreading deceptively democratic messages spewing hatred and fear.

To reward the Ethiopian regime with ethnic dispute is to augment its power to terrorize. When Oromo farmers are evicted and forced to become beggars on their own land, Amhara people sit idly by. When Amhara people face similar injustice, Oromo people also turn away. With such discord, the regime can easily crush any uprising, and feels confident that the groups will continue to allow each other to suffer violence and maltreatment. If Oromo and Amhara citizens came together, their objections would come from a much stronger opposing force.

Oromo people from around the world are gathering in Washington DC on April 19th for the Tom Lantos Human Rights Commission briefing. This campaign was organized to push human rights issues and stop the madness in this Ethiopia. This cause affects all Ethiopians; not only the Oromo who have been active thus far. The Woyane reign of terror cannot be stopped until all Ethiopians stand together and demand justice for all.

Call To Action

Today we fight for the 16 endangered individuals we have identified in Florida. There are surely more in need of assistance across the United States. I am calling on all Ethiopians to come together, to unite, to use every resource available- and locate and support our countrymen in need across the US. I would encourage courageous individuals to initiate their own campaigns to save our people not only in the US, but throughout the world. We have seen ISIS executions of Ethiopians in Libya. Shame on us! It is obvious that our government is incompetent; but at least we, the Diaspora, who have freedoms our fellow Ethiopians do not, should come together and speak for those in need. We should lobby the UN and peace-loving countries to stand with us and help resolve the issues in Ethiopia. Our mission is to save Ethiopians from Ethiopia’s thuggish regime.

For this campaign, contributions of any amount are gratefully accepted, and can be directed to: https://www.gofundme.com/ethiopiandetainees  This fund has been set up by the Oromo and Ethiopian Communities of Tampa Bay and Mr. Kefyalew in Miami.

By Lalisaa Hiikaa: focatampabay@gmail.com

Sunday, April 17, 2016

ወያኔና ትግሬ

April 17,2016

(ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም)
tplf 40
አዳም በበደለ መድኃኔ ዓለም ካሠ፤ የተጠቀሰውን አባባል የማያውቅ ክርስቲያን ያለ አይመስለኝም፤ ለእስላሞችም ቢሆን አዲስ ነገር አይሆንባቸውም፤ አዳም ትእዛዝ ጥሶ ዕጸ በለስን በላና ተረግሞ ከገነት ወጣ፤ አዳም በደለ የሚባልበት ምክንያት ይህ ነው፤ አዳም በገነት ባካሄደው አብዮት የተነሣ የሰው ልጆች ሁሉ ከገነት እንደወጡ የሚቀሩ ሆነ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር አዘነ፤ በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር ወልድ ከሰማየ ሰማያት ወረደና ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ እግዚአብሔር ይህንን በማድረጉ ሰዎች ከአዳም የወረሱት የጅምላ ኃጢአት ተሻረ፤ ከዚያ በኋላ ኃጢአት የግል እንጂ የጅምላ መሆኑ ቀረ፤ ይህ የሆነው መድኃኔ ዓለም የሰው ልጅን ከራሱ ጥፋት ለማዳን በመሰቀሉ ነው፤ ሃይማኖት ለመስበክ ሳይሆን የጅምላ አስተሳሰብ ቀና እንዳልሆነ እግዚአብሔር እንዳስተማረን ለማመልከት ነው፤ በዚህም መሠረት ፍትሐ ነገሥት ልጅ በአባቱ ወንጀል አይጠየቅም፤ አባቱም በልጁ ወንጀል አይጠየቅም ይላል፤ በአስተሳሰብና በፍትሕ ጉዳይ የሰው ልጅን የእድገት በር የከፈተው ይህ ነው፤ እያንዳንዱ ሰው የሚመዘነውና የሚፈረድለት ወይም የሚፈረድበት እሱው ራሱ በሠራው ነው፤ ይህ ቁም-ነገር ዛሬ በሠለጠኑ አገሮች ሁሉ ሕግ ሆኖ የሚሠራበት ነው፤ ወደማኅበረሰብ ደረጃ ሲወርድ ቁም-ነገሩ ሰፊውን ሕዝብ አዳርሷል ለማለት ያስቸግራል።
ከላይ እንደመግቢያ ያቀረብሁት አስተያየት ከወያኔ ጎሠኛ አስተዳደር ጋር ተያይዞ የመጣ አንድ የአስተሳሰብ ግድፈትን ቢቻል ለማረም ነው፤ ይህ መሠረታዊ የአስተሳሰብ ግድፈት በአጠቃላይ የሰው ልጅን ሁሉ የሚመለከት ቢሆንም ኋላ-ቀሮችን ይበልጥ ያጠቃል፤ በተለይ ደግሞ በአንዳንድ ልዩነቶች ላይ ጎልቶ ይታያል፤ ለምሳሌ ወንዶች ሁሉ ስለሴቶች ያላቸው የተዛባ አመለካከት ከአካላዊ ልዩነት ተነሥቶ አእምሮንና መንፈስንም ጨምሮ ሴቶችን ከወንዶች በታች ያደርጋል፤ ዛሬ ሴቶች ያልገቡበትና ያልተደነቁበት ሙያ ባይኖርም አንዳንድ ወንዶች አሁንም አሮጌ አስተሳሰብን ይዘው የቀሩ አሉ፤ እንዲሁም ስለጥቁሮች ያረጀ አስተሳሰብ ይዘው የቀሩ ነጮች አሉ፤ ክርስቲያኖችም፣ እስላሞችም እንዲሁ፤ በእውቀት ዓለም አጠቃላይ ወይም የጅምላ አስተሳሰብ የሚፈቀድበት ጊዜ አለ፤ ይህ የሚሆነው ተጨንቀው፣ ተጠብበው፣ ብዙ ፈተናዎችን አልፈው ነው ወደማጠቃለያው የሚደርሱት፤ ሁለት ነጫጭ ውሻዎችን ያየ ሰው፣ ሁለት ነጫጭ ውሾች አየሁ ቢል እንቀበለዋለን፤ ነገር ግን ውሾች ሁሉ ነጫጭ ናቸው ወደሚል ማጠቃለያ ቢደርስ የከረረ ሙግት ይነሣል።
የቀለም ልዩነት ባለበት አገር ሁሉ ቀለም ለአስተሳሰብ ግድፈት መነሻ ይሆናል፤ ነጮች ጥቁሮችን ይንቃሉ፤ የሚንቁት አንድ ደደብ፣ ወይም አስቀያሚ፣ ወይም ባለጌ … ሆኖ ያገኙትንና የሚያውቁትን አንድ ጥቁር ሰው አይደለም፤ እንዲሁ ሾላ በድፍን አይተውት የማያውቁትን ጥቁር ሰው ሁሉ ያለምንም ሚዛን በአንድ ከረጢት ውስጥ ጨምረው ነው፤ እውነትን ለሚፈልግ በአውቀት መለኪያ ከብዙ ነጮች የሚበልጡ ጥቁሮች ይኖራሉና ጥቁሮችን በጅምላ ደደብ ማለት ልክ አይደለም፤ በውበት መለኪያም ቢሆን ያው ነው፤ በሌላ በማናቸውም ነገር ቢሆን የጅምላ ሳይንሳዊ ፈተናዎቹን ያላለፈ የጅምላ አስተሳሰብ ቁም ነገርን ያበላሻል፤ እንዲህ ያለው የአስተሳሰብ ግድፈት የሚያቀራርብና የሚያሳድግ አይደለም።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደርግና ወያኔ የእውቀትን ደረጃ ሰባብረው ጉልበትን የደረጃ መለኪያ በማድረጋቸው የአስተሳሰብ ግድፈት እየተስፋፋ በመሄድ ላይ ነው፤ መነሻው ጥላቻ ነው፤ ወያኔ ጥላቻን በስልቻ ቋጥሮ አመጣና በኢትዮጵያ ላይ ዘራው፤ የማሰብ ችግር ስላለ የተዘራው ጥላቻ ፊቱን አዙሮ ወደራሱ ወደወያኔም እንደሚደርስ አልተገነዘበም ነበር።
አሁን ብዙ ሰዎች የወያኔ የአእምሮ ሕመም ተጋብቶባቸው ትግሬዎችን በሙሉ ወያኔ በማድረግ ያላቸውን ጥላቻ በመረረ ቋንቋ ይገልጻሉ፤ በቅርቡ አንድ ሰው ይህንኑ እኔ በሽታ የምለውን ስሜት በፌስቡክ ላይ ገለጠና የሚከተለውን ሀሳብ ጫረብኝ።azeb and aster
የእኔ አመለካከት እንደሚከተለው ነው፤ ትግሬን የማየው በሁለት ከፍዬ ነው፡– ወያኔ የሆኑ ትግሬዎችና ወያኔ ያልሆኑ ትግሬዎች፣ ወያኔን ደግሞ እንደገና ቢያንስ ለሁለት እከፍለዋለሁ፡– ዘርፎ የከበረ ወያኔና ደሀ ወያኔ፤ ዓይኖቹን ከፍቶ ደሀ ወያኔዎችን ማየት ያልቻለ ሰው ከአለ እኔ ለማሳየት ዝግጁ ነኝ፤ ጥቅም ያቅበዘበዘው ወያኔ ዘራፊው ነው፤ ግን ሲዘርፍ ያልዘረፈውን ወያኔ መሣሪያ አድርጎ ነው፤ ለምሳሌ በማእከላዊና በቃሊቲ ያሉ ጠባቂዎች ወያኔዎች የዘራፊዎቹ መሣሪያዎች ናቸው፤ ከተዘረፈው ሲንጠባጠብ ይለቅሙ ይሆናል እንጂ እነሱ መናጢ ደሀ ናቸው፤ የዘረፉ ወያኔዎች በመቀሌ ሕዝቡ “የሙስና ሰፈር” ብሎ የሰየመውን የሀብታሞች መንደር ሠርተዋል፤ በአዲስ አበባም “መቀሌ” ተብሎ የተሰየመውን የሰማይ-ጠቀስ ፎቆች መንደር ሠርተዋል፤ በሻንጣ የአሜሪካን ብር ወደውጭ ይልካሉ፤ ሌላም ብዙ አለ።
እነዚህ በዘረፋ ሀብታም የሆኑ ወያኔዎች ረዳት መሣሪያ አድርገው የሚጠቀሙባቸው ሌሎች ደሀ ወያኔዎች እንዳሉ ሳይታለም የተፈታ ነው፤ የተባረሩም ወያኔዎች እንዳሉ አውቃለሁ፤ የተባረሩበትንም ምክንያት አውቃለሁ፤ ወደመቀሌ የሚሄዱበት የአውቶቡስ መሳፈሪያም የሰጠኋቸው ነበሩ፤ ለሚያምኑኝ ሰዎች እነዚህን መረጃዎች የምሰጠው ለመመጻደቅ አይደለም፤ እውነቱን እንዲረዱልኝ ነው፤ እውነትን ለማየት የሚችሉ ሰዎች እንዳይሳሳቱ ለመርዳት ነው፡፡
ስለወያኔ ግፈኛነት፣ ዘራፊነትና ጭካኔ ከብዙ ዓመታት በፊት ጀምሮ ያላልሁት ያለ አይመስለኝም፤ ነገር ግን እንኳን ትግሬን በጅምላና ወያኔንም በጅምላ ለመኮነንና ለመርገም የአእምሮ ብቃትም ሆነ የኅሊና ጽዳት ያለው ሰው የለም፤ የወያኔን ፍርደ-ገምድልነት የሚጠላ በፍርደ-ገምድልነት በትግሬ ሁሉ ላይ አይፈርድም፤ ጥላቻ ኅሊናን ያቆሽሻል፤ ጥላቻ አእምሮን ያሰናክላል፤ ጥላቻ ወደኋላ እንጂ ወደፊት የማየትን ችሎታ ይጋርዳል፤ ጥላቻ በተለይ በማቆጥቆጥ ላይ ያለውን ወጣት እንደበረሀ ጸሐይ እርር ድብን አድርጎ ያጫጨዋል።
በአጠቃላይ ስለ ወያኔ ገዳይ፣ ዘራፊ፣ ቀማኛ … መሆን አንካካድም! ልዩነታችን ትግሬ ሁሉ ወያኔ ነው፤ ስለወያኔ የምንናገረው ሁሉ ለትግሬዎች ሁሉ ይሆናል የሚለው የተሳሳተ አሰተያየት ላይ ነው፤ እኔ በማእከላዊም ሆነ በቃሊቲ ጎንደሬዎች፣ ጎጃሜዎች፣ ወሎዬዎች፣ አሮሞዎች፣ ወላይታዎች … የወያኔዎች አገልጋዮች ሆነው እስረኞችን ሲያሰቃዩ አይቻለሁ፤ ትግራይም ሄጄ ከሌለው የኢትዮጵያ ክፍል የተዘረፈው ሀብት ሁሉ እንኳን ለትግሬ ሁሉና ለወያኔዎች ሁሉ እንዳልተዳረሰና ገና ከጥቂት አልጠግብ ባዮች ወያኔዎች እንዳልወጣ አይቻለሁ።Bereket-Simon-tplf
በሌላ በኩል ሲታይ ወያኔም የተነሣው “አማራ” የሚባል ጭራቅ በዘበዘን፤ ብቻውን እየወፈረ እኛን አከሳን በማለት በ”አማራ” ላይ ወፍራም ጥላቻውን እያስፋፋ በአፈ-ጮሌዎቹ በመለስ ዜናዊ፣ በረከት ስምዖንና ዓባይ ጸሐይ ስብከት ጀሌዎቹን አሳምኖ ነው፤ ወያኔዎች ገና ሰሜን ሸዋ ሲዘልቁ የሚያዩአቸው ሰዎች፣ የሚያዩአቸው ቤቶች ውሸታሞቹ ጮሌዎች እንደነገሯቸው አለመሆኑን ሲገነዘቡ ጥያቄ ያነሡ እንደነበረ ሰምተናል፤ ዛሬም ሌሎች የመለስ፣ የበረከትና የዓባይ የመንፈስ ደቀ መዝሙሮች ኢላማውን ገልብጠው በትግሬዎች ላይ በጅምላ እያነጣጠሩ ነው፤ አንድን ከአንድ መቶ፣ ዝርዝርን ከጅምላ፣ ፖሊቲካን ከዘር መለየት የሚችል አእምሮ ሳይኖር ከአለንበት ሁኔታ አንወጣም፤ ብንወጣም ከጣልነው ጋር ለመንከባለል ነው፤ ወያኔ ደርግን ጥሎ አልተነሣም፤ እዚያው ከሬሳ ጋር ሲንከባለል ተዳከመ! የተሻልን እንሁን!
ወያኔ ሁሉ ትግሬ ነው፤ ትግሬ ሁሉ ወያኔ አይደለም፤ የወያኔ ዘረፋ እንኳን ለትግራይ ሕዝብና ለወያኔዎች በሙሉ አልደረሰም፤ በየዕለቱ በጠዋት እየተነሣች ምን እንደሆነ የማላውቀውን ዕቃ አዝላ ወደትምህርት ቤት ከሚሄዱ ልጆችዋ ጋር ከቤትዋ እየወጣች ከሰዓት በኋላ ዕቃውን አዝላ የምትመለስ ወያኔ አውቃለሁ፤ ይቺ ወያኔ (ትግሬ አላልሁም፤) በወያኔ ሥርዓት ተጠቅማለች የሚለኝ ሰው ወደሀኪም ዘንድ መሄድ ያስፈልገዋል።
ሚያዝያ 2008