Wednesday, October 29, 2014

ፕሬዚዳንት ኦባማ ስለኢትዮጵያ ምርጫ ምን ያህል “ያውቃሉ”? ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

October 29,2014
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ  

ፕሬዚዳንት ኦባማ .. 2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው “ምርጫ” ምን ያህል ያውቃሉ? 
ባለፈው ሳምንት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በኢትዮጵያ ካለው የገዥው አካል የልዑካን ቡድን አባላት ጋር በዚህ በዋሽንግተን ዲሲ ላይ በመገናኘት እንዲህ የሚል ንግግር አሰምተው ነበር…”በዚህ ዓመት ጠቅላይ ሚስትር [ኃይለማርያም ደሳለኝ] እና መንግስታችሁ በኢትዮጵያ ምርጫ ለማካሄድ የዝግጅት እንቅስቃሴ በማደረግ ላይ ትገኛላችሁ፡፡ ስለዚያ ጉዳይ ጥቂት ነገሮችን አውቃለሁ…እናም ስለሲቪል ማህበረሰቡ እና ስለመልካም አስተዳደር እንደዚሁም ኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ ያስመዘገበችውን አንጸባራቂ እድገት እና ተምሳሌትነት እንዴት አድርጎ ወደ ሲቪል ማህበረሰቡም ማሸጋገር እንደሚቻል ለመነጋገር ጥሩ አጋጣሚ ይፈጥርልናል…“  
ገና ከመጀመሪያው ጀምሬ አስተያየቴ ምን ላይ አንዳተኮረ ግልጽ ላድርግ፣ ይህ የአሁኑ ትችቴ ትኩረት አድርጎ የሚያነጣጥረው ጠቃሚ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በተለየ መልኩ በፕሬዚዳንት ኦባማ ላይ ነው፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያቴ እርሳቸው በፈቃዳቸው በኢትዮጵያ የምርጫ ፖለቲካ  ውስጥ በተለይ “የማውቃው ነገሮች አሉ” በማለት እመር ብለው ዘለው ገብተውበታል፡፡ እንደዚህ ልዩ በሆነው መግለጫቸው ስለዚያ ምርጫ ጉዳይ የማውቃቸው ጥቂት ነገሮች አሉ በማለት በይፋ በማወጃቸው ስለዚያ ምርጫ ጉዳይ የሚያውቋቸው “ጥቂት ነገሮች” ምን እንደሆኑ በይፋ ለህዝብ ግልጽ ማድረግ እንዳለባቸው ለመጠየቅ እፈልጋለሁ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚያች አገር በየጊዜው ምርጫ እየተባለ የህዝብ እና የመንግስት ሀብት ያለአግባብ እየባከነ ለይስሙላ የሚካሄደውን ምርጫ በማስመልከት እኔም የማውቃቸውን “ጥቂት ነገሮች” ለእርሳቸው ግንንዛቤ እንዲረዳቸው ላካፍላቸው እፈልጋለሁ፡፡ በፕሬዚዳንቱ ያልተጠበቀ የቃላት አመራረጥ እና አጠቃቀም ግራ ተጋብቻለሁ፣ በትክክል ምን ለማለት እንደፈለጉም ለማወቅ ጉጉት ያደረብኝ ሲሆን ይህ ፈሩን የለቀቀ የሸፍጥ አነጋገር ግን ሳልተች አንደአላልፍ ተገድጃለሁ፡፡
ፕሬዚዳንቱ ስለቀጣዩ የኢትዮጵያ ምርጫ “ጥቂት ነገሮችን” አውቃለሁ ሲሉ እንደ ስለላ ተቋም በሚስጥር የማውቀው ነገር አለ ማለታቸው ነውን? ፕሬዚዳንቱ ስለምርጫው ጥቂት የማውቃቸው ነገሮች አሉ ሲሉ ከዚህ ቀደም የተደረጉ የተጭበረበሩ እና በቀን ብርሀን የምርጫ ኮሮጆዎች እየተገለበጡ በሸፍጥ የተካሄዱ የይስሙላ ምርጫዎች ነበሩ ለማለት ፈልገው ነውን? እ.ኤ.አ በ2015 ስለሚካሄደው የኢትዮጵያ ምርጫ ፕሬዚዳንት ኦባማ የሚያውቋቸውን ጥቂት ነገሮች ግልጽ እንዲያደርጉልኝ በእርግጠኝነት ለማወቅ እፈልጋለሁ፣ ምክንያቱም የንግግራቸው ዳህራ አቀራረብ ጆርጅ ኦርዌል እንዳሉት “በቅጥፈት የታጀበን አንደበት እውነት ማስመሰል“ ከሚለው ጋር መሳ ለመሳ አስመስሎታል፡፡ ፕሬዚዳንቱ የሚያውቋቸውን ጥቂት ነገሮች ለማወቅ በዛር እንደተለከፈ ሰው መንቀጥቀጥ አለብን እንዴ?
እ.ኤ.አ በ2010 በኢትዮጵያ በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ በህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ሕወሀት) የበላይነት የሚመራው ገዥው ፓርቲ በጠራራ ጸሐይ የድምጽ ኮሮጆ እየገለበጠ በመዝረፍ እና ምርጫ በማጭበርበር 99.6 በመቶ የመራጮችን ድምጽ በማግኘት ጠቅላላ የፓርላማውን መቀመጫ እንደተቆጣጠረ ያውቁ ነበርን? ይህ የምርጫ ውጤት መቶ በመቶ (100%) ለመሆን የቀረችው የአንድ ፐርሰንት አራት አስረኛ ብቻ ነበረች፡፡
እ.ኤ.አ በ2010 የፕሬዚዳንት ኦባማ ብሄራዊ የደህንነት ምክር ቤት እንዲህ የሚል መግለጫ አወጣ፣ “የኢትዮጵያ ምርጫ ዓለም አቀፍ የምርጫ መስፈርትን የማያሟላ መሆኑን ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢዎች ያረጋገጡት ስለሆነ ይኸ ጉዳይ አሳስቦናል…ከምርጫው ዕለት በፊትም እንኳ ለነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ የሚሆን የተስተካከለ የምርጫ ሜዳ በስራ ላይ አልዋለም ነበር፡፡ ከቅርብ ዓመታት ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን በማስፈራራት እና በማሸማቀቅ የፖለቲካ ምህዳሩን በማጥበብ የሲቪል ማህበረሰቡን እና  የነጻውን ፕሬስ እንቅስቃሴ ገድቧል…“ ብለው ነበር፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ ይህንን ሲሉ በአሁኑ ጊዜ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና አመራሮች በገዥው ፓርቲ አምባገነናዊ ማንአለብኝነት ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው፣ እየተሸማቀቁ፣ እየታሰሩ፣ እየተሰቃዩ እና በሸፍጥ የፍርድ ቤት ክስ እየተጉላሉ መሆናቸውን ያውቃሉ?
ፕሬዚዳንት ኦባማ ለመሆኑ እ.ኤ.አ በ2010 በተካሄደው የመጨረሻ አገር አቀፍ ምርጫ የምርጫ ዘገባ በማቅረባቸው ምክንያት ምርጥ እና የብሩህ አዕምሮ ባለቤት የሆኑት የኢትዮጵያ ጀግኖች ጋዜጠኞች ከሰብአዊነት በወረደ መልኩ በየእስር ቤቶች እየታጎሩ በመማቀቅ ላይ እንደሚገኙ ያውቃሉ? ክቡር ፕሬዚዳንቱ እ.ኤ.አ በ2010 የዓለም የፕሬስ ቀንን ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ተጣብቆ የሚገኘውን ገዥ አካል በስም እየጠሩ በተለይም በነጻ ፕሬሱ ላይ እያካሄደ ያውን ጭቆና በማውገዝ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምተው አልነበረምን?፣ “በአሁኑ ጊዜ ህዝቦች ከምንጊዜውም በላይ በኢንተርኔት አገልግሎት፣ በተንቀሳቃሽ ስልክ እና በሌሎች ተገጣጣሚ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አማካይነት አስፈላጊውን መረጃ እያገኙ ባለበት ሁኔታ እንደ ቻይና፣ ኢትዮጵያ፣ ኢራን እና ቬንዙዌላ የመሳሰሉ አገሮች የህዝቦቻቸውን ሀሳብን በነጻ የመግለጽ ነጻነትን በመገደብ እና እነዚህን ዘመኑ ያፈራቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዳይጠቀሙ በማድረግ ላይ ናቸው“ አላሉም ነበር እንዴ?
በኢትዮጵያ ባለው ገዥ አካል ቀያጅ የሆነው የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ መውጣት ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ማህበራት ቁጥር እ.ኤ.አ በ2010 የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ብቻ ከነበረበት 4,600 ወደ 1,400 አሽቆልቁሎ መውረዱን ሊያስታውሱ ይችላሉን? እነዚህ የተረፉት ጥቂት ድርጅቶች ህልውናቸውን ለማቆየት ሲሉ የሰራተኞቻቸውን ቁጥር ከ90 በመቶ ወይም ከዚያ በላይ በሆነ መጠን የቀነሱ መሆናቸውን አያውቁምን? እ.ኤ.አ በ2009 “ስህተት እንዳትሰሩ፣ የሲቪል ማህበረሰቡ–የሲቪል ቡድኖች መንግስቶቻቸው በተሻለ የማስተዳደር ብቃት እና መስፈርት ላይ እንዲሆኑ ያግዛሉ“ በማለት የሲቪል ማህበረሰቡን ሁኔታ በማስመልከት ያደረጉትን ንግግር ሊያስታውሱ ይችላሉን? በኢትዮጵያ ውስጥ እ.ኤ.አ በ2009 ወይም በ2010 ከነበረው ቁጥራቸው እጅግ በጣም ባነሰ ሁኔታ ጥቂት ብቻ የሆኑ ድርጅቶች በ2014 በሀገሪቱ ውስጥ ሁሉም በሚባል መልኩ የገዥው አካል ደጋፊ እና ታዛዥ በሆኑ ጥቃቅን የጎጆ ኢንዱስትሪ መሰል ድርጅቶች ባለቤትነት፣ ተግባሪነት እና አመራር ሰጭነት የሚንቀሳቀሱ ብቻ ናቸው ያሉት ብለው የተናገሩትን ሊያስታውሱ ይችላሉን?
ፕሬዚዳንት ኦባማ ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ እድሚያቸው በ20ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ የሆኑ ወጣት ወንዶች እና ሴቶች በፌስ ቡክ እና በሌሎች የማህበራዊ ድረ ገጾች አማካይነት ሀሳባቸውን በመግለጻቸው ብቻ አሸባሪ የሚል ታፔላ ተለጥፎባቸው በቀጥጥር ስር ውለው ወደ ዘብጥያ ተወርውረው በእስር ቤት በመማቀቅ ላይ እንደሚገኙ ያውቃሉን? በኢትዮጵያ ያለው የነጻው ፕሬስ በጭቆና ውስጥ ያለ መሆኑን፣ መታፈኑን እና  እየተዘጋ መሆኑን አያውቁምን? ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ብቻ ስድስት ታዋቂ ነጻ ህትመቶች ማለትም አፍሮ ታይምስ፣ አዲስ ጉዳይ፣ እንቁ፣ ፋክት፣ ጃኖ እና ሎሚ የተባሉ መጽሔቶች እንዲዘጉ ተደርገዋል፣ በደርዘን የሚቆጠሩ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞችም ወደ እስር ቤት እንዲወረወሩ እና ከሀገር እንዲሰደዱ ተደርገዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 የዓለም የፕሬስ ቀንን በማስመልከት “የጋዜጠኞችን፣ የጦማሪያንን እና የሰላማዊ አመጸኞችን በነጻ የመጻፍ እና የመናገር አቅም እንዳይገደብ ለመጠበቅ እና ምንም ዓይነት የበቀል እርምጃ እንዳይወሰድ እንዲሁም የጉዞ እቀባን ለማስቆም እና ሌሎች ቀጥተኛ ያልሆኑ የሳንሱር ስራዎችን አለማድረግ እና ዜጎች ዓለም አቀፋዊ የሆኑ መብቶቻቸውን ያለምንም ገደብ መጠቀም እንዲችሉ ማድረግ“ ብለው የተናገሩትን ሊያስታውሱት አይችሉምን? የተከበሩ ፕሬዚዳንት ኦባማ በኢትዮጵያ  ከዜጎች ፈቃድ እና ፍላጎት ውጭ በኃይል ተፈናጥጦ በማተራመስ ላይ ላለው ገዥ አካል መሪዎች “ወጣት የኢትዮጵያ ጦማሪያንን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑትን ጋዜጠኞች በስም እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ ከእስር ይፈቱ“ በማለት እስከ አሁን ድረስ ያቀረቡት ጥሪ የሌለ መሆኑን ያውቃሉን?
ፕሬዚዳንት ኦባማ ለመሆኑ የፕሬስ ነጻነት፣ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በከፍተኛ ጭቆና ውስጥ እየተሰቃዩ ባሉበት እና የፖለቲካ ምህዳሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እየጠበበ በመጣበት ሁኔታ የሚደረግ የይስሙላ እና የሸፍጥ ምርጫ ከስም የዘለለ ፋይዳ ሊኖረው እንደማይችል ሊገነዘቡት ይችሉ ይሆን? እ.ኤ.አ በ2009 በጋና አክራ ላይ ለአፍሪካ ህዝቦች ያደረጉትን እንዲህ የሚለውን ንግግራቸውን “…ይህ ምርጫ ከማካሄድ በላይ ነው፣ እንደዚሁም ደግሞ በምርጫዎች መካከል ምን እንደሚደረግ የማወቅም ጉዳይ ነው፡፡ የጭቆና መገለጫዎች ብዙ ናቸው፣ በዚህም መሰረት ብዙ መንግስታት ምርጫ በማካሄድ ላይ ያሉትም እንኳ ህዝቦቻቸው በረሀብ አደጋ ችግር እየተሰቃዩ በህዝቦቻቸው ይወገዛሉ፡፡ የሀገር መሪዎች የሀገሮችን ሀብት ለግል ጥቅማቸው እያዋሉ እና ኢኮኖሚውን እየመዘበሩ ባሉበት ሁኔታ አንድ ሀገር ሀብት ማፍራት አትችልም…የትርፉን 20 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆነውን የአገር ሀብት የሚመዘብር መንግስት ባለበት ሀገር ማንም ቢሆን ከውጭ ሀገር ሄዶ መዋዕለ ንዋዩን ሊያፈስ አይችልም፣ የህግ የበላይነት ቀርቶ ጭካኔ እና የባርነት አገዛዝ በተንሰራፋበት ማህበረሰብ ውስጥ ለመኖር የሚፈልግ ማንም ሰው የለም፡፡ ያ ዴሞክራሲ አይደለም፣ ይልቁንም አንዳንድ ጊዜ ለይስሙላ ምርጫ እየተዘጋጀ ቢቀርብም ያ የለየለት አምባገነናዊነት ነው፡፡ እናም እንደዚያ ዓይነቱን የግፍ አገዛዝ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ለማስወገድ ጊዜው አሁን ነው፡፡“ በማለት የተናገሩትን አስመሳይ ንግግር ፕሬዚዳንት ኦባማ ሊያስታውሱት ይችሉ ይሆን?
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ እስከ አንገታቸው ድረስ በሙስና በተዘፈቁ አስመሳይ አምባገነን መሪዎች እና የእነርሱ ጋሻጃግሬዎች ኢኮኖሚውን በብቸኝነት አንቀው ይዘው እየመዘበሩ እራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን በማበልጸግ ላይ እንዳለሉ እንዲሁም አልፎ አልፎ የይስሙላ ምርጫ እያሉ በአገሪቱ ውስጥ ዴሞክራሲ እንዳለ በማስመሰል በዓለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚሰጠውን እርዳታ እና ብድር በማጋበስ ለግል ጥቅማቸው በውጭ አገር በሚገኙ ባንኮች የሂሳብ አካውንት እየከፈቱ በማጨቅ ያሉ ዘራፊዎች እና ማፊያ ጭልፊቶቸ መሆናቸውን ፕሬዚዳንት ኦባማ ሊያውቁ ይችላሉን? እ.ኤ.አ በ2008 እጩ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ታውቃላችሁ፣ ለማቆንጀት ሲባል የዓሳማን ከንፈር ቀለም መቀባት ትችላላችሁ፣ ሆኖም ግን ዓሳማው አሁንም ቢሆን ያው ዓሳማ ነው፣ ዓሳማነቱን አይቀይርም፡፡ አንድን የጠነባ ዓሳ በወረቀት ጠቅልሎ ለውጥ ማለት ይቻላል፡፡ ከስምንት ዓመት በኋላም ቢሆን ያው መጠንባቱን አይተውም፡፡“ እንደዚሁም ሁሉ ቆንጆ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማስመሰል ምርጫ የሚባል የጠነባን ቀለም በምርጫ ካርድ በመጠቅለል የዘራፊዎችን ከንፈር መቀባት ይቻላል፣ ሆኖም ግን የሚደረገው የይስሙላ ሽርጉድ ምርጫ ውጤት ከ23 ዓመታት የሸፍጥ ምርጫም በኋላ ያው በዘራፊዎች ከንፈር ላይ ሆኖ መጠንባቱን የማይለቅ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኦባማ በውል ተገንዝበውት ይሆን? ወሮበላነትን ምርጫ በሚባል የጠነባ ነገር በምርጫ ካርድ ወረቀት መጠቅለል ይቻላል፣ ሆኖም ግን ከ23 ዓመታት በኋላም ቢሆን ያው መጠንባቱን እንደማይተው ፕሬዚዳንት ኦባማ አልተረዱም ይሆን?
ስለምንናገረው ነገር ማወቅ፡ .. 2015 በኢትዮጵያ ምርጫ ሊኖር ይችላልን?
“ፖለቲካ እና የእንግሊዝኛ ቋንቋ“ በሚል ርዕስ ባዘጋጁት በባለ 1946 ገጽ ድርሰታቸው ጆርጅ ኦርዌል እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “ሀሳብ ቋንቋን የሚያሻግት ከሆነ ቋንቋ እራሱም ሀሳብን ያሻግታል፡፡“ መጥፎ አጠቃቃም በህዝቦች መካከል በዘልማድ ይተላለፋል፣ የተሻለ እውቀት ባላቸው ሰዎችም ቢሆን እንኳ፡፡ ኦርዌል እንዲህ የሚል የመከራከሪያ ጭብጥ አቅርበው ነበር፣ “የፖለቲካ የቃላት አጠቃቀም ውሸትን እውነት ለማስመሰል ተብሎ የሚዘጋጅ ነው፣ እናም  የተከበረን ነገር እውነት በማስመሰል ይገድላል፣ ባዶ ነፋስን ጠንካራ እና ጠጣር በማስመሰል፡፡“
እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ፕሬዚዳንት ኦባማ የሚያወሩት ሁሉም ነገር ባዶ ነፋስ/ውሸት ነው፣ ሸፍጥ የተሞላበት ምርጫ ለማካሄድ የሚነገር ቋንቋ እውነት ሊመስል ይችላል እናም ወሮበላነት የተከበረ ዴሞክራሲ ይሆናል፡፡ በአሁኑ የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ “ምርጫ” የሚለው ቃል መሰረተቢስ እና እርባናቢስ ነው፡፡ “እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ምርጫ ይካሄዳል” ማለት ወይም ደግሞ “እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው ምርጫ ጥቂት የማውቀው ነገር አለ” የሚለው አባባል የፕሮፌሰር ኖአም ቾምስኪን አባባል እንዳለ የሚደግም እና ትርጉመቢስ እና እርባናየለሽ የሆነ ሆኖም ግን በሰዋስዋዊ አግባቡ ትክክል የሆነ ዓረፍተ ነገር ማለት ሲሆን “ቀለም የሌላቸው አረንጓዴ ሀሳቦች በብስጭት ይተኛሉ” እንደማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ “ምርጫ” ማለት በሶስት ቀለበት የሰርከስ ላይ ተውኔት የሚተወን ምርጫ የሚባል የህዝቡን ድምጽ በተቀነባበረ ሌብነት እና ዝርፊያ የሚነጠቅበት ከመሆን የዘለለ ፋይዳ የለውም፡፡ እንደዚህ ዓይነቱነን የተጭበረበረ የዘረፋ እና የውንብድና ሂደት ምርጫ ነው ማለት ውሸት ማለት እውነት ነው እንደማለት ነው፡፡
ፕሬዚዳንት ኦባማ እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው ምርጫ ጥቂት የማውቀው ነገር አለ ብለው ከማወጃቸው በፊት ጥቂት ኢትዮጵያወያን/ት እና የተወሰኑ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሀን ስለዚሁ ጉዳይ ሲነጋገሩበት ነበር፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ መልኩ እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ የሚካሄደው ምርጫ የምርጫ ዘዋሪ ቀበኛው ልዩው መሀንዲስ ያለፈው መለስ ዜናዊ በሌለበት በዚህ ወቅት እውነት ነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ የሚካሄድ ስለመሆኑ ወይም አለመሆኑን አስመልከቶ ትንሽም ቢሆን ተስፋ ስለመኖሩ እና አለመኖሩ ሙያዊ ትንታኔ እንድሰጥ ጥያቄ ቀርቦልኝ ነበር፡፡ ተስፋ በቆረጠ መልኩ “የምን ምርጫ?” ነበር ያልኩት፡፡ ወያኔ ምርጫውን አሁንም በድጋሜ ይሰርቃል፡፡ ጥቂቶቹ የዘረፋውን እርግጠኛ እውነትነት ባረጋገጠ መልኩ የምጸት ሳቅ ነበር የሳቁት፡፡ ጥቂቶቹ ደግሞ የምርጫ ቅስቀሳ ተብየው በዘራፊው የገዥ አካል በይፋ ሲጀመር የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት በተቀናጀ እና በተደራጀ መልኩ ዘርፈ ብዙ የሆነ የሰላማዊ አመጽ እና እንቢተኝነት ዘመቻ ሊያካሂዱ እና የምርጫውን እርባናየለሽነት ለአገር ውስጥ እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት ነግረውኛል፡፡ እንዲህ የሚል ጥያቄ ተጠየቅሁ፣ “የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና የፖለቲካ ፓርቲዎች እራሳቸውን ከምርጫው ሊያገልሉ ይችላሉን?“ በሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣ በአንድ ወይም በሌላ መልኩ የተጠየቅሁት ጥያቄ ደግሞ “የወያኔው የፖሊት ቢሮ አባላት ኃይለማርያም ደሳለኝን (የይስሙላ ጠቅላይ ሚኒስትር) አሽቀንጥሮ በመጣል በሌላ አሮጌ እና ነባር በሆነ የጫካ ዘብ ይተኩ ይሆን“ የሚል ነበር፡፡ (የወያኔ አለቆች በ2015 በሚደረገው አገር አቀፍ ምርጫ ኃይለማርያም ዳሳለኝን በማስወገድ በቀጥታ ወደ ቅርጫት ይጥሉታል የሚል ግምት አለኝ!)
.. 2015 ስለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ኃይለማርያም ደሳለኝ ምን ይህል ያውቃሉ? 
እ.ኤ.አ ጁን 11/2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አፍሪካ ዘገባ/Africa Report ለተባለ የዜና ወኪል በሰጡት ቃለመጠይቅ ነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄዳል የሚል የሀሰት መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ለማንኛውም የሰጡት ቃለመጠይቅ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
.. 2015 በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተወካዮች ምክር ቤት ብዙ መቀመጫዎችን ያገኛሉ ብለው ያስባሉን 
ምርጫዎች እስካሉ ድረስ ትኩረት ማድረግ የምንፈልገው በሂደቱ ላይ ነው፡፡ የምርጫ ሂደቱን በህዝቦቻችን ፊት ዴሞክራሲያዊ፣ ነጻ፣ ፍትሀዊ እና ታማዕኒነት ያለው ማድረግ አለብን፡፡ ከዚያ በተረፈ ውጤቱ የህዝቡ ነው፡፡ እነዚህ ብዙ መቀመጫዎች ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም ደግሞ ለኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህዴግ) ይሰጣሉ ብየ ለመገመት አልችልም፡፡
የምርጫ ሂደቱ ዴሞክራሲያዊ ይሆናል ብለው ያምናሉ?
ተቋማዊ ሂደታችን፣ ህጎቻችን እና ደንቦቻችን ሙሉ በሙሉ እንከን የላቸውም፡፡ ህጉ በእራሱ አይደለም እንቅፋት የሚሆነው፣ ሆኖም ግን እነዚህን ህጎች ከመተግበሩ ላይ ነው፡፡ ስለሆነም ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመሩበት የምርጫ መመሪያ ህገ ደንብ/Cod of Conduct አዘጋጅተን በስራ ላይ አውለናል፡፡ በማያወላውል መልኩ ለዚህ ህገደንብ ተገዥ መሆን ምርጫውን የበለጠ ዴሞክራሲያዊ፣ ነጻ፣ ፍትሀዊ እና ለህዝብ ታዕማኒነት እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡
2010 አገር አቀፍ ምርጫ ጋር ተመሳሳይ ውጤት የሚኖረው ከሆነ እና አንድ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩ ብቻ አሸንፎ ወደ ፓርላማ የሚገባከሆነ ይኸ ሁኔታ በመንግስት ላይ የሚኖረውን ታዕማኒነት ከጥርጣሬ ላይ ሊጥለው ይችላል ብለው ያስባሉን?
ይህንን አላስብም ምክንያቱም ውሳኔው በህዝቡ የሚወሰድ ከሆነ ሁላችንም በዚያ ውሳኔ ላይ መስማማት አለብን፡፡ የምርጫው ውጤት አንዳንድ ጊዜ ለአንዳንዶቻችን ቢመቸንም ባይመቸንም ምንም ይሁን ምን ውጤቱን መቀበል አለብን፡፡
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ኃይለማርያም ደሳለኝ የእርሳቸውን (ይቅርታ የህወሀትን ማለቴ ነው) የ2015ን ምርጫ እና እንዴት አድርገው የ2010ን የምርጫ ውጤት እንዳለ በመድገም በዝረራ በማሸነፍ ድልን ሊቀዳጁ እንደሚችሉ እና በእንዴት ዓይነት ማጭበርበር ዝርፊያውን ለማስኬድ እንዳቀዱ ባለሶስት ምላስ አጠቃላይ የምርጫ ስትራቴጂ ነድፈዋል፡፡ ይኸውም፣
1ኛ) እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ የሚካሄደው አገር አቀፍ የምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊ፣ ነጻ፣ ፍትሀዊ እና በህዝብ ዘንድ ታዕማኒነት ያለው እንዲመስል የመንግስት የመገናኛ ብዙሀንን እና ሀብትን በመጠቀም የኢትዮጵያን ህዝብ ማታለል፤
2)  ፍጹም እና እከንየለሽ የሆኑ ተቋማዊ ሂደቶቻችንን፣ ህጎቻችንን እና ደንቦቻችንን ወደ ተግባር በማሸጋገር፤
3ኛ) ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፈረሙትን እና የተቀበሉትን የምርጫ ህገ ደንብ እንዲቀበሉት እና እንዲተገብሩት ማስገደድ የሚሉት ናቸው፡፡
የወያኔ ባለሶስት ጣት የምርጫ ስትራቴጂ በእርግጠኝነት እንከን ለሌለው የተጭበረበረ ምርጫ እንከንየለሽ የምርጫ ጨዋታ ዕቅድ ነው፡፡ አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ እንከንየለሽ የሸፍጥ የምርጫ ጨዋታ ህግ መጽሐፍ እ.ኤ.አ በ2010 ጽፎ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት የእርሱ ፓርቲ እንከንየለሹን ምርጫ 99.6 በመቶ የፓርላማ መቀመጫዎችን በማግኘት አሸናፊነቱን አረጋግጧል፡፡ ከዚህ የበለጠ እንከንየለሽ የምርጫ ውጤት ማግኘት ሰብአዊነት ነውን? (አሁን በህይወት የሌለው ሳዳም ሁሴን ብቻ ነው እ.ኤ.አ በ2002 በተካሄደው አገር አቀፍ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ከ11,445,638 ድምጽ ሰጭዎች መቶ በመቶ ድምጽ በማግኘት እከንየለሽ የድምጽ ውጤት በማግኘት በመፎከር ላይ የነበረው፡፡) የሸክስፒርን አባባል በመዋስ፣ የመለስ ሙት መንፈስ እ.ኤ.አ በ2015 በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ላይ ለማጥላት “በጨላማው የሲኦል ቦታ ላይ እንደ እሬሳ ሳጥን“ ትንጠለጠላለች፡፡
ስለህዝቦች አገዛዝ/አስተዳደር ሳይሆን ህዝቦችን ለመግዛት ያፈጠጠ ምርጫ 
የበከተ አስተሳሰብን በመያዝ እና  እና የሞራል ስብዕና በሌላው መልኩ እ.ኤ.አ በ2014 የኃይለማርያም አለቆች ከእርሳቸው በስተጀርባ ሆነው እንከንየለሽ ተቋማዊ ሂደት፣ ህጎችን እና ደንቦችን በመጠቀም ተግባራዊ አድርገው ምርጫ ማሸነፍ እንዳለባቸው ብቻ አይደለም እምነታቸው ሆኖም ግን ኢትዮጵያን ለዘላለም ለመግዛት ባላቸው መብት የኢትዮጵያ ህዝቦች እንከንየለሽ ገዥዎች መሆናቸውን ለማረጋገጥ ጭምር እንጅ፡፡ በእነርሱ እና በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስተሳሰብ በቀጣይ ኢትዮጵያን የሚገዛት ማን ነው የሚለው ከጥያቄ ውሰጥ የሚገባ ጉዳይ አይደለም፡፡ ይኸ ጉዳይ ለውይይት የሚቀርብ አይደለም፣ የሚያከራክርም አይደለም፣ እናም ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ በእርግጥ መለስ እ.ኤ.አ በ2010 በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ የተጎናጸፈውን የምርጫ ድል አስመልክቶ ባደረገው ንግግር እንዲህ የሚል ግለጽ መልዕክት አስተላለፎ ነበር፣
“…በዚህ ምርጫ የህዝቡን የምርጫ ድምጽ ድጋፍ ላላገኛችሁት እና ስኬታማ ላልሆናችሁት ፓርቲዎች በዚህ ፓርላማ ወንበር ይኑራችሁም አይኑራችሁም የህዝቡን ፍላጎት፣ የአገሪቱን ህገመንግስት እና ሌሎችን የአገሪቱን ህጎች እስካከበራችሁ ድረስ ከእናንተ ጋር በመቀራረብ እናንተን በታላላቅ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በማሳተፍ እየተመካከርን አብረን እንሰራለን” ነበር ያለው፡፡ የውሸት እና የሸፍጥ ፈጣጣ ንግግር!
በቀላል አነጋገር ማንም ቢሆን እ.ኤ.አ በ2015 የሚካሄደውን እንከንየለሽ የምርጫ ውጤት አልቀበልም የሚል ልቡ ያበጠበት ወጠጤ ካለ በኃይለኛው ጡንቻ የመደምሰስ አደጋ ይገጥመዋል፡፡ አራት ነጥብ! ሆኖም ግን ምንም የማይሉ ሆኖም ግን የተባሉትን ብቻ የሚቀበሉ ዓላማቢስ እና ስሜት አልባ በመሆን አንገታቸውን ደፍተው ጫማ የሚልሱ ወንዶች እና ሴቶች ከሆኑ ያለምንም ችግር የመሸለም ዕድልን እየተጎናጸፉ በታላላቅ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በማማከር እና እንዲያውም በማሳተፍ ይህችን በእድገት ጎዳና ላይ እንደ እሮኬት ጥይት በመምዘግዘግ ላይ ያለች ሀገር የበለጠ እንድትተኮስ ያደርጓታል፡፡ እንዲያውም ባለሁለት አሀዙ የኢኮኖሚ ዕድገት እጅግ በጣም ከመጦዙ የተነሳ ወደ ባለሶስት አሀዝ ሳይገባ ይቀራል ጎበዝ! ከዚህ በላይ በአገር እና በህዝብ ላይ ከመቀለድ የከፋ እና የከረፋ ከቶውኑ ምን ነገር ሊኖር ይችላል! እ.ኤ.አ በ2015 የሚካሄደውን እንከንየለሽ አገር አቀፍ ምርጫ ውጤት አልቀበልም የምትሉ ዕደለቢሶቹ ሁሉም የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች (ውይ! ለምስክርነት ካላችሁ ማለቴ ነው)፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመራሮች ካላችሁ በምርጫው ወቅት አንድም እንደ አህያ ዱላውን ተቀበሉ አለያም ደግሞ በእስር ቤት ውሰጥ በመግባት እየማቀቃችሁ የአህያውን ኑሮ መኖር ነው የሚጠብቃችለሁ፡፡
ሌሎቹስ ስለኢትዮጵያመ ምርጫ ምን ያህል ያውቃሉ? 
እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2009 “የ2010 የኢትዮጵያ ምርጫ እብድነት” በሚል ርዕስ የሚከተለውን ጥያቄ በማንሳት ትችት ጽፌ ነበር፣ “የፖሊስ መንግስት በተንሰራፋበት ሀገር ፍትሀዊ እና ነጻ ምርጫን ማካሄድ ይቻላልን?“ (ይህ ጥያቄ የፕሬዚዳንት ኦባማን የከንፈር ቀለሙን እና የዓሳማውን ጉድኝት የሚያመሳስል ቀላል የተመሳስሎ አቀራረብ ነው፡፡)
ያ ትችት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እ.ኤ.አ በ2001 ከኢትዮጵያ ከስልጣናቸው መንበራቸው እስከለለቀቁበት ድረስ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት የነበሩት ባቀረቡት የምርጫ ዘመቻ ዘገባ ላይ መሰረት ያደረገ ነበር፡፡ ዶ/ር ነጋሶ በምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኘውን ደምቢዶሎን ወክለው ለተወካዮች ምክር ቤት ለመወዳደር ለምርጫ ቅስቀሳ በተንቀሳቀሱበት ወቅት በገዥው ፓርቲ የበታች አካላት ልክ የድሮዎቹ የኮሙኒስት ፍልስፍናን ሲያራምዱ የነበሩ አገሮች ሲያደርጉት እደነበረው ሁሉ ህዝቡን አስጨንቀው በመያዝ የአዛዥ እና የቁጥጥር ስርዓት/Command and Control በመዘርጋት ሲያደርጉት የነበረውን የአፈና አሰራር ነው፡፡ እርሳቸውም ተዘዋውረው በተመለከቱት መሰረት በደምቢዶሎ የገዥው ፓርቲ የታችኛው እርከን ድርጅቶች የደህንነት፣ የፖሊስ እና ሌሎች በታችኛው የስልጣን መዋቅር ላይ ያሉት የሲቪል ማህበረሰብ መሰል ድርጅቶችን ሁሉ ሳይቀር በቁጥጥር ስር በማዋል አንድ ወጥ የሆነ የቁጥጥር መዋቀር በዞኖች፣ በከተሞች፣ በወረዳዎች፣ በመንደሮች፣ በጎጦች እና በቤቶች ሳይቀር ተጠርንፈው የተያዙ መሆናቸውን ግልጽ አድርገው ነበር፡፡
ዶ/ር ነጋሶ የመረጃ ሰጭዎች፣ የወኪሎች እና የሚስጥር ፖሊስ መሰል አደረጃጀቶች ሆነው እነዚህም የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን ለማሸማቀቅ፣ ለማስፈራራት፣ የስለላ መረጃ ለመሰብሰብ እና ተቃዋሚዎችን በማዳካም ሰርስሮ ለመግባት የተዋቀሩ አደረጃጀቶች እንደነበሩ እጀ እረጅም በመሆን ህሉን አድራጊ ፈጣሪ እንደነበሩ ግልጽ አድርገው ነበር፡፡ በደምቢዶሎ በፖለቲካ ፓርቲው እና በህዝብ ደህንነቶች መካከል ምንም ዓይነት የስራ ክፍፍል ልዩነት የለም በማለት ሲሞግቱ ነበር፡፡ ሁለቱም በአንድ የፖለቲካ ጥላ ስር የተዋቀሩ እና የአካባበኒውን የፖለቲካ እና የማህበራዊ ሁነት በጅምላ የተቆጣጠሩ እና የበላይነትን የያዙ ነበሩ ብለዋል፡፡ የመንግስት ሰራተኞች፣ አርሶ አደሮች፣ የአካባቢው ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የአነስተኛ ብድር እና ቁጠባ ድርጅቶች እና ሌሎችም በግዳጅ በሚስጥራዊው የፓርቲ መዋቅር ስር እንዲሆኑ ይገደዳሉ፡፡ የቁጥጥር ስርዓቱ መጥበቅ ሁሉን ነገር የሚያሽመደምድ ነበር በማለት ዶ/ር ነጋሶ እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “እያንዳንዱ ቤተሰብ በየዕለቱ ወደ ቤቱ የሚመጡትን እንግዶች እና ጎብኝዎች የመጡበትን ምክንያት፣ ምን ያህል ጊዜ እንደሚቆዩ፣ በቆይታቸው ጊዜ ምን እንደተናገሩ እና እዳደረጉ እንዲሁም በምን ስራ ላይ እንደቆዩ ዘገባ ማቅረብ ይጠበቅበታ”:: እንግዲህ ያ ነበር የመለስ የደህንነት ዋስትና በመሆን በ2010 እንከንየለሽ ምርጫ በማካሄድ 99.6 በመቶ ድምጽ በማግኘት የቅጥፈት የድል ከበሮ ሲደልቅ የነበረው፡፡ አሁን ከኃይለማርያም በስተጀርባ ያሉት ስምየሾች፣ አረመኔዎች እና ራዕይየለሾች በተመሳሳይ መልኩ እንደገና በ2015 ለሚደረገው ምርጫም ተመሳሳዩን የሸፍጥ ስራ ለመስራት እና ለማግኘት ደፋ ቀና ይላሉ፡፡
እ.ኤ.አ በ2010 በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ የምርጫ ውጤት ላይ ትችት በማቅረብ ፕሮፌሰር ቶቢያስ ሐግማን የተመለከቱትን እንደሚከተለው አስፍረዋል፡፡ “የኢትዮጵያ መንግስት እ.ኤ.አ በ2005 በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ውርደትን ባከናነበ መልኩ ሽንፈትን ከተጎነጨ ወዲህ አ.ኤ.አ በ2010 በተደረገው አገር አቀፍ ምርጫ መንግስት የመጨረሻ የፖለቲካ ስተራቴጂ ነድፎ የገባበት ነው፡፡ ይህ የአካሄድ እስትራቴጂ ዱላ እና ካሮትን ሁለቱንም አካትቶ የያዘ ነበር፡፡ ዱላው የሚያካትተው ማስፈራራትን፣ ማሸማቀቅን እና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን እና የእነርሱ ደጋፊ ይሆናሉ ብለው የሚያምኑባቸውን በቁጥጥር ስር እያዋሉ ወደ እስር ቤት መወረወወር ሲሆን ካሮቱ የሚያካትታቸው ደግሞ ገዥው ፓርቲ አዲስ የፓርቲ አባላትን በገፍ መመልመል እና አዲስ የትንታኔ ዘገባ እንደሚጠቁመው ጠንካራ የተቃዋሚ አባላት በሚገኙባቸው ወረዳዎች በቀጥታ ከፌዴራል ወደ ወረዳዎቹ ገንዘብ እንዲላክ በማድረግ በጣም ጠንካራ የሆኑትን በገንዘብ መደለል እና በገንዘብ የምርጫ ድምጽ በመግዛት ዓላማቸውን ማሳካት ነበር… በምርጫ 2010 የተገኘው 99.6 በመቶ የምርጫ ድምጽ ውጤት ሲታይ ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ ለህዝብ አስተዳደር ሳይሆን ህዝቡን ለመግዛት የሚያመላክት ጠንካራ ምልክት ነው… ከ20 ዓመታት በላይ በስልጣን ላይ ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝቦቸች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) በፖለቲካ ውክልናው እና በውሳኔ ሰጭነቱ ህጋዊነትን ያልተላበሰ አድራጊ ፈጣሪ ጠቅላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲ ማለት ምን ማለት እንደሆነም በእራሱ አረዳድ እና ዓላማ ጠቅልሎ የያዘ ህጋዊነትን ያልተላበሰ ድርጅት ነው፡፡”
የፕሮፌሰር ሄግማን ምልከታዎች በተጨማሪም የወያኔ አመራሮች (እና የእነርሱ ጋሻ ጃግሬዎች) በእብሪተኝነት እና ሊለወጥ በማይችል ቀኖናዊ አመለካከት ወጥመድ ውስጥ የተያዙ በመሆናቸው ምክንያት እድሜልካቸውን ለመግዛት ሀሳብ አላቸው፡፡ ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ምርጫ ማካሄድ ምንም ዓይነት እርባና የሌለው እና ከንቱ ነገር መሆኑን ፕሮፌሰሩ አጽንኦ በመስጠት አስቀምጠውታል፡፡ የምልከታቸውን ተጨባጭነት ይበልጥ ለማረጋገጥ እንዲህ ይላሉ፣ “ይህ ሁኔታ ኢህአዴግ እራሱን በሚያይበት መነጽር ላይ በግልጽ ሲንጸባረቅ ይታያል – በስም እራሱን አውራ ፓርቲ/Vanguard party እና የመንግስትነት ስልጣንን ጨብጨ የመምራት መብት የእኔ መብት ሆኖ ልማት ማለት ምን ማለት እደሆነ እና ዴሞክራሲ እንዴት መደራጀት እና መዋቀር እንዳለበት የምወስነው እኔ ነኝ፡፡ ስለሆነም ማንም ይሁን ማን ከኢህአዴግ አመለካከት ውጭ የሆነ ሁሉ ጸረ ልማት ወይም ደግሞ ጸረ ሰላም ነው፣ እናም ማንም ማን ይሁን የእርሱን ፖሊሲ የሚቃወም ሁሉ ጸረ መንግስት ነው“ በማለት የድርጅቱን (የጠቅላዩን እና ዘላለማዊ ገዥውን) ከንቱነት በማያሻማ መልኩ አስቀምጠውታል፡፡
.. 2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ምን ያህል አውቃለሁ?
በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ እኔ የማውቀው ይልቁንም የበለጠ የተወሳሰበ ነገር ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ በርካታ ጥያቄዎችን እጠይቃለሁ፣ እነዚህም ለእኔ የሚታወቁ ታዋቂዎች፣ ታዋቂ የማይታወቁዎች፣ እና የማይታወቁ የማይታዎቁዎች ናቸው፡፡ ይቅርታ አድርጉልኝ አንዳንድ ጊዜ እንቆቅልሽ ማውራት ይቀናቸው እንደነበሩት እንደ ቀድሞው የዩኤስ አሜሪካ የመከላከያ ሚኒስትር ዶን ሩምፌልድ ዓይነት አቀራረብ ተከትየ ከሆነ፡፡ ዶን እንዲህ ብለው ነበር፣ “የምናውቃቸው የሚታወቁ ነገሮች አሉ፣ እንደዚሁም የምናውቃቸው የማይታወቁ ነገሮች አሉ፣ ይህም ማለት የማናውቃቸው ጥቂት ነገሮች አሉ፡፡ ሆኖም ግን የማናውቃቸው የማይታወቁ ነገሮች አሉ፣የማይታወቁ እና እኛም የማናውቃቸው፡፡“
ሙሉ በሙሉ ግልጽ ላድርገው፡፡ በእርግጠኝነት ጥቂት ነገር አውቃለሁ፡፡ የወያኔ ገዥ አካል እ.ኤ.አ በ2015 የሚካሄደውን አገር አቀፍ ምርጫ እንደ ቁማር ጨዋታ ሻጥር ይሰራበታል፡፡ እንደዚሁም ደግሞ የምርጫው ዕለት የድምጽ ቆጠራ ገና ሳይጠናቀቅ እና የቆጠራ ጣቢያዎች ገና ሳይዘጉ የወያኔ ገዥ አካል በዝረራ አሸንፎ ድልን እንደተቀዳጀ በማስመሰል በህዝብ ግብር በሚተዳደረው መገናኛ ብዙሀን ማናፋቱን ይቀጥላል፡፡ ይኸ እንግዲህ ታዋቂው የማውቀው ነገር ነው፣ ምንም ዓይነት ሊያስረዳኝ የሚችል ሌላ ጭንቅላት አያስፈልገኝም፡፡
ሆኖም ግን የሚታወቁ የማላውቃቸው ነገሮች አሉ፡፡ ይህም ማለት እ.ኤ.አ በ2015 በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ የወያኔ ገዥ አካል ቢያንስ በ99.6 በመቶ ያሸንፋል፣ ሆኖም ግን ይህ እንደ እስስት ተለዋወጭ የሆነው ገዥ አካል በ99.7፣ በ99.9፣ በ100 ወይም ደግሞ በ110 በመቶ ለማሸነፍ ዕቅድ ይዞ ይሆናል (ይህም እንግዲህ ከ2010 ጀምሮ የሞቱ ድምጽ ሰጭዎችን ቆጥረው ማለት ነው)፡፡ ሆኖም ግን በ2015 የሚደረገው ምርጫ የመራጮች ድምጽ ውጤት ከ99.6 በመቶ ያነሰ የድል ውጤት ተመዝግቦ ከሆነ መለስ ከመቃብር ውስጥ ሆኖ ለዚህ የሸፍጥ ምርጫ ስኬታማነት ተንቀሳቅሶ ሊሆን ስለሚችል የማይታወቅ የማላውቀው ነገር መሆኑ ነው፡፡
ለእኔ እ.ኤ.አ በ2010 በተደረገው አገር አቀፍ ምርጫ የወያኔ ገዥ አካል 99.6 በመቶ የመራጮች ድምጽ ውጤት አመጣሁ ብሎ የድል ከበሮ ሲደልቅ ፕሬዚዳንት ኦባማ በውስጠ ታዋቂነት ይህንን ተቀብለው ቡራኬ በመስጠት ማጽደቅ መቻላቸው የሚታወቀው የማውቀው ነገር ነው፡፡ ፕሬዚዳንቱ ለዚህ ጉዳይ ጆሮዳባ ልበስ፣ አላየሁም አልሰማሁም ነው ያሉት፡፡ (ሆኖም ግን እ.ኤ.አ በ2013 በዚምባብዌ በተደረገው አገር አቀፍ ምርጫ ሮበርት ሙጋቤ የፕሬዚዳንትነት ወንበሩን በ61 በመቶ ድምጽ በማግኘት አሸንፊያለሁ ብለው ድንፋታ ሲያሰሙ ፕሬዚዳንት ኦባማ ለወያኔው ገዥ አካል እንዳደረጉት ሁሉ በዝምታ አላለፉም፡፡) እንዲያውም እንደህ ነበር ያሉት፣ “ዚምባብዌያውያን/ት አዲስ ህገመንግስት አላቸው፡፡ ኢኮኖሚው በማገገም ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ወደፊት በእድገት የመገስገስ ዕድሉ ይኖራል፣ ሆኖም ግን ይህ ተፈጻሚነት ሊኖረው የሚችለው ነጻ፣ ፍትሀዊ እና ሰላማዊ ምርጫ ሲካሄድ ብቻ ሲሆን በዚህም መሰረት ዚምባብዌያውያን/ት የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን እራሳቸው ምንም ዓይነት የማስፈራራት ፍርሀት እና የብቀላ እርምጃ ሳይወሰድባቸው ሲወስኑ ነው፡፡ 61 በመቶ የመራጮች ድምጽ በማግኘት አሸናፊ የሆነ ምርጫ ነጻ እና ፍትሀዊ አይደለም፣ ስለሆነ ህዝባዊ ውግዘት ሊደርስበት ይገባል“ ነበር ያሉት፡፡ ሆኖም ግን 99.6 በመቶ የመራጮችን ድምጽ በማግኘት አሸናፊ የሆነ ምርጫ እንደ ክቡር ፕሬዚዳንቱ መንታ ምላስ ሁኔታ ነጻ እና ፍትሀዊ ነው፣ እናም ታላቅ የሆነ የግል ሙገሳ ያስፈልገዋል!
ፕሬዚዳንት ኦባማ እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ስለምርጫው ጥቂት የማውቀው ነገር አለ ሲሉ የማይታወቀው እኔም የማላውቀው ነገር ማለት ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ምናልባት ፕሬዚዳንቱ የሚያውቁት ሆኖም ግን ማንም ኢትዮጵያዊ የማያውቀው ነገር ሊኖር ይችላል፡፡
እ.ኤ.አ በ2015 በኢትዮጵያ በሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ የተለያዩ የህወሀት ተስፈንጣሪ ቡድኖች የጠቅላይ ሚኒስትርነቱ ቦታ ለእኔ ይገባል፣ ለእኔ ይገባል በሚል የንግስና ጦርነት ለማካሄድ ዝግጅት ሊያደርጉ የሚችሉበት የማይታወቅ እኔም የማላውቀው ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም አንጻር የተለያዩ የህወሀት ተስፈንጣሪ ቡድኖች አሮጌ ብር በማጣበቂያ ታሽጎ አንድ እንደሚሆነው ሁሉ እነርሱም ለጥቅም ሲሉ ብቻ አንድ ሊሁኑ የሚችሉበት የማይታወቅ እኔም የማላውቀው ነገር ሊኖር ይችላል፡፡ ሆኖም ግን የሚታወቅ እና እኔም የማውቀው ነገር አለ፣ ይኸውም የምርጫ ዘራፊዎች የሚከባበሩበት እና የማይከባበሩበት ያልተጻፈ ህግ አለ፣ እርሱም፣ “በምርጫ ወቅት አንድ ዘራፊ በሌላው ዘራፊ የምርጫ ጓደኛው ላይ ጦርነት አይከፍትም፣ ምክንያቱም በምርጫ ጦርነት የሚያሸንፉ የምርጫ ዘራፊዎች የሉምና፡፡“ ስለወያኔ ውስጣዊ ባህሪያት እና አሰራር በርካታ የማይታወቁ እና የማናውቃቸው ነገሮች አሉ፡፡ አጋጣሚ ሆኖ ስለወያኔ የማይታወቁ የማናውቃቸውን የሚያውቁ ንግግር አያደርጉም፣ እናም ንግግር የሚያደርጉት ስለወያኔ የማይታወቁትን የማናውቃቸውን አያውቁም፡፡ ኦ! በጣም አደናጋሪ ነገር ነው!
የነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ትክክለኛ ትርጉም እና ተሞክሮ፤
ምርጫዎች እና ምርጫዎች አሉ፡፡ በሸፍጥ የተሞሉ እና የተጭበረበሩ ምርጫዎች እራሳቸው ማለት ናቸው፡፡ አንድ ምርጫ ነጻ እና ፍትሀዊ ነው ወይም አይደለም “የተቋማዊ የአሰራር ሂደቱ፣ ህጎቻችን እና ደንቦቻችን እንከንየለሾች ናቸው“ ብሎ በመወሰን የማወጅ ያህል አይደለም፣ ችግሩ እንከንየለሽ የተቋማዊ የአሰራር ሂደት፣ ህጎች እና ደንቦች ያለመኖር አይደለም፣ ይልቁንም እነዚህ እንከንየለሽ ተቋማዊ የአሰራር ሂደቶች፣ ህጎች እና ደንቦች  ተፈጻሚነት የማይኖራቸው እንከን በእንከን በተሞሉ ሰዎች ስር በመሆናቸው ብቻ ነው፡፡ ችግሩ ያለው እነዚህን እንከንየለሽ ህጎች በሚጽፉት ሰዎች እጅ እና በትክክል ቅን ልቦና ኖሯቸው ወደተግባር አምጥተው በቅንነት መተግበር በማይችሉ እንከን በእንከከኖች ነው፡፡ ከሁሉም በላይ እንከን በእንከን የተሞሉ ሰዎች እንዴት እንከንየለሽ የአሰራር ሂደቶችን፣ ህግችን እና ደንቦችን ያወጣሉ? እነርሱ እራሳቸውን እንከንየለሾች ነን ብለው የሚያምኑ በቀላሉ ነገሮችን የመረዳት ወይም ደግሞ የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ናቸው፣ እናም ያ ዓይነት አመለካከት ያላቸው አጠቃላይ የጅምላ እንከን በእንከን ቁልሎች ናቸው፡፡  ከኃይለማርያም ደሳለኝ በስተጀርባ ያሉት ኃይሎች እንከን በእንከን የሆነችውን ኢትዮጵያ ለመግዛት ከላይ ተቀብተው የመጡ እና በክልል፣ በሙስና እና የጅምላ ሰብአዊ መብትን እየጣሱ በእነርሱ የእንከንየለሽ መስፈርት ለማድረስ እየዳከሩ ያሉ ለመሆናቸው በእርግጠኝነት እምነቱ አለኝ፡፡
በእርግጥ በኢትዮጵያ እንከንየለሽ ደንቦችን፣ ህጎችን እና ሂደቶችን በማውጣት ብቻ እንከንየለሽ ምርጫ ይካሄዳል ብሎ የሚጠብቅ ሰው የለም፡፡ ነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ጥቂት እንከኖች ያሉበት፣ ቁስሎች እና ህጸጾች መኖራቸው ተፈጥሯቂ ነው፡፡ እንደዚህ ያሉት ምርጫዎች የመከሰታቸው ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸው መስፍርቶች እና መርሆዎች ያሉ ሲሆን መፍትሄዎችም ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መክፈት እና ማስፋት፣ የተቃዋሚ አባላትን ማስፈራራት እና ማሸማቀቅ ማስወገድ፣ በሲቪል ማህበረሰቡ ላይ ያለውን የቁጥጥር ደረጃ ማላላት እና የነጻውን ፕሬስ መብት በማረጋገጥ ለዜጎች መረጃ እንዲሰጥ እና ዘገባ እንዲያቀርብ መፍቀድ ናቸው፡፡
ፍትሀዊ እና ነጻ ምርጫዎች ህዝቡ በዕለቱ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሄድ የምርጫ ካርዱን ጥሎ በመምጣቱ ብቻ የሚከሰቱ አይደሉም፡፡ ይልቁንም ከምርጫው ዕለት በፊት የመከወኑ ነገሮች ናቸው፡፡ ፕሬዚዳንት አቦማ ጋና ላይ እንደተናገሩት፣ “ይህ በአጠቃላይ ምርጫ ከማካሄድ በላይ ነው፡፡ እንደዚሁም ደግሞ በምርጫዎች መካከል ምን ተከናወነ የሚለውም መታየት አለበት“ ነበር ያሉት፡፡ ከሁሉም በላይ በመጀመሪያ ነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ተግባራዊ ሊሆን የሚችለው የህግ የበላይነት ባለበት እና መሰረታዊ የሆኑ የሰብአዊ መብቶች በተከበሩበት ሁኔታ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህግመንግስት “የሀገሪቱ የህጎች ሁሉ የበላይ” ለድምጽ ሰጭዎች እና ለዕጩዎች (በአጠቃላይም ለዜጎች) ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብትን ያጎናጽፋል፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ፖለቲካዊ የሆኑ መልዕክቶች እና መረጃዎችን ከምርጫው በፊት እና ከድህረ ምርጫ በኋላ ወደ ህዝብ  ለማሰራጨት እና መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችለውን የፕሬስ ነጻነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ በህገመንግስቱ የማይገዙት ለምንድን ነው?
ህገመንግስቱ ለሁሉም ድምጽ ሰጭዎች፣ ፓርቲዎች እና እጩ ተወዳዳሪዎች፣ ነጻ፣ ከማንም ጋር ያልወገነ የምርጫ ሂደቱን የሚያስፈጽም የምርጫ ቦርድ እንዲኖር ዋስትና ይሰጣል፡፡ በዜጎች የፖለቲካ ፓርቲዎችን እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ለመመስረት በሚያደርጉት ጥረት የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብት ላይ በዘፈቀደ የሚደረግ ጣልቃገብነት መኖር የለበትም፡፡ እንደዚሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊ ሰልፍ እና የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ለማድረግ ሲፈልጉ ያለምንም ችግር በነጻ መንቀሳቀስ እንዲችሉ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡  ዜጎች የፖለቲካ አመለካከታቸውን በነጻ የማራመድ እና ከማንኛውም ተጽእኖ ነጻ ሆነው መግለጽ እንዲችሉ መብታቸው ሊጠበቅ ይገባል፡፡ ዜጎች መረጃ የመፈለግ፣ የመቀበል እና የማካፈል መብታቸው ሊረጋገጥ ይገባል፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ የዘመቻ ቅስቀሳ ለማድረግ እና ከሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዥው ፓርቲ ጋር ጭምር እኩል በሆነ መልኩ የመንቀሳቀስ መብታቸው ሊጠበቅ ይገባል፡፡
የፖለቲካ አመለከካከታቸውን ለማራመድ እና በህዝብ ዘንድ ለማስረጽ እንዲችሉ ማንኛውም እጩ ተመራጭ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ለሚዲያ በተለይም ለብዙሀን መገናኛ እኩል እድል ሊያገኙ ይገባል፡፡ ከምርጫ እና ከፖለቲካ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ መልኩ የሚነሱ ውዝግቦችን በሰላማዊ መልኩ ለመዳኘት እንዲቻል ነጻ እና ከማንም ያልወገኑ ተቋማት ያስፈልጋሉ፡፡ የህገመንግስቱን ትዕዛዛት ለምን አይከተሉም?
የተቃዋሚ ፓርቲ እጩዎች እና ፓርቲዎች ለህዝብ ቀርበው ሀሳቦቻቸውን እና ፕሮግራሞቻቸውን ሊያስረዱ የሚቸችሉበት መንገድ ሊቀየስ ይገባል፡፡ ገዥው ፓርቲ ፖሊስን፣ ወታደሩን፣ የፍትህ አካላቱን፣ የመንግስት ሰራተኛውን፣ የምርጫ አስፈጻሚ ባለስልጣኖችን ከህግ አግባብ ውጭ ወገንተኝነት እንዲያሳዩ እና እራሱ እንዳይጠቀምባቸው ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ማድረግ እና መረጋገጥ አለበት፡፡ የመንግስት ገንዘብ እና የማስፈጸሚያ ቁሳቁሶች በምንም ዓይነት መንገድ ለፓርቲ ስራ ገዥውን ፓርቲ ጨምሮ መዋል የለባቸውም፡፡ ጥብቅ በሆነ መልኩ መከልከል አለባቸው፡፡ የምርጫ ሂደቱ ምንም ዓይነት ችግር የሌለበት የመራጮች ምዝገባ፣ ሊደረስባቸው የሚገባ የምርጫ ቦታዎች፣ የምርጫ አስፈጻሚ ኃላፊዎችን ክብር ያረጋገጠ አያያዝ ማድረግን፣ ለሁሉም ክፍት የሆነ እና ግልጽነትን የተላበሰ የመራጮች ድምጽ ቆጠራ እና የማረጋገጥ ስራ ሂደት፣ ምርጫዎችን በሰለጠነ እና ከማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ነጻ በሆኑ ኃላፊዎች ታዛቢነት እንዲኖር ማድረግ እና የምርጫ ማጭበርበር ያለመኖሩ መረጋገጥ አለበት፡፡
እ.ኤ.አ በ2010 በኢትዮጵያ ለተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ የአውሮፓ የምርጫ ታዛቢ ቡድን የመጨረሻ ዘገባ፣
የምርጫው ሂደት በተለይም የሂደቱን ግልጽነት እና ለሁሉም ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እኩል ምህዳር ባለመስጠቱ ዓለም አቀፍ የምርጫ መስፈርትን አያሟላም፡፡ የበለጠ ፍትሀዊ እና ወካይነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲኖረው ተደረጉት ጥረቶች አናሳ ሆነው ተገኝተዋል…በመሆኑም ሙሉ፣ አድሎአዊ ያልሆነ እና መሰረታዊ የሆኑ መብቶችን ለመጠቀም ባለመቻሉ የምርጫው ሂደት በችግር ተተብትቧል… የገዥው ፓርቲ በመላ አገሪቱ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች ከመገኘቱ አንጻር ሲገመገም በተለይም የገጠሩ አካባቢ 80 በመቶ የሚሆነውን ህዝብ የሚሸፍነው የህብረተሰብ አካል የተቃዋሚ ፓርቲዎች ተወካዮች እና ተወዳዳሪዎች አልነበሩም፡፡ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በተለይም የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ባካተተ መልኩ የመሰብሰብ ነጻነቶች፣ ሀሳን በነጻ የመግለጽ፣ በነጻ የመንቀሳቀስ መብቶች ወጥ በሆነ መልክ አልተከበሩም…በመንግስት ቁጥጥር ስር ያለው የብዙሀን መገናኛ ለሁሉም እኩል በሆነ መልኩ ሽፋን አልሰጠም፣ በተለይም ለገዥው ፓርቲ ከ50 በመቶ በላይ የህትመት እና የብሮድካስት ሽፋን ሰጥቷል…በብዙዎቹ የአገሪቱ ዝቅተኛ የመንግስት አስተዳደራዊ መዋቅሮች ዘንድ በገዥው ፓርቲ እና በመንግስት መዋቅር መካከል የጠራ ልዩነት አልነበረም፡፡ የአውሮፓ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በቀጥታ የመንግስት ሀብቶች ለገዥው አካል የምርጫ ዘመቻ ቅስቀሳ አገልግሎት መዋላቸውን አረጋግጧል፡፡ በስልጣን ላይ ያለው ገዥው ፓርቲ በግልጽ ጠቀሜታ ያለው መሆኑ በግልጽ የሚታይ ቢሆንም የምርጫ ቡድኑ የ2010ሩ አገር አቀፍ ምርጫ በብዙ መልኩ የምርጫ ምህዳሩ ፍትሀዊ አልነበረም፣ በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ገዥው ፓርቲ ያደላ ነበር…
አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎችን ቡድን የምርጫ ዘገባ “ለምንም የማይውል ወደ ቆሻሻ ቅርጫት መጣል ያለበት“ በማለት በአደባባይ አጣጥሎታል፡፡ እንዲህ ብሎ ነበር፣ “የምርጫ ዘገባው ስለእኛ ምርጫ አይደለም፡፡ ይኸ ጉዳይ በገዥው ፓርቲያችን መጠናከር ደስተኞች ያልሆኑት የምዕራቡ ዓለም ኒዮሊበራሎች አመለካከት ነው፡፡ ማንም ወረቀት እና ብዕር የያዘ ሰው የፈለገውን ነገር መሞነጫጨር ይችላል፡፡“ በእርግጥ መለስ በፖለቲካ መድረክ ላይ እንደዚህ ያለ አስቀያሚ ቋንቋ ማስተላለፍ መቻሉ አፈታሪክ ነበር፡፡ መለስ በአፍሪካ አህጉር ማንንም የፖለቲካ ሰው መሳደብ፣ የጭቃ ጅራፉን ማጮህ፣ መበጥበጥ፣ መዘለፍ፣ ጥላሸት ሲቀባ የቆየ ሰው ነበር፡፡ መለስ የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድን የምርጫ ዘገባን “በውሸት ቁልል የታጨቀ“ ብሎታል፡፡
ፕሬዚዳንት ኦባማ ስለ2015 ምርጫ ማወቅ እና ማድረግ ያለባቸው ነገሮች፣
ፕሬዚዳንት ኦባማ እያወቁ ያላወቁ በመምሰል የሚያደርጉትን ትተው የምርጫ 2010 ስህተት በ2015ም እንዳይደገም ለመከላከል ማወቅ እና ማድረግ የሚኖርባቸው ጥቂት ነገሮች እንደሚከተለው ቀርበዋል፣
ቅድመ ምርጫ ከባቢ፡ የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን በ2010 እንደተመለከተው “ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻዎቻቸውን ነጻ እና ለሁሉም እኩል በሆነ የምርጫ ምህዳር ሜዳ ላይ የመወዳደር መብት እንዳለቸው ህጉ ይፈቅዳል”፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ የወያኔ ገዥ አካል የፖሊስ መንግስት ሆኖ የቀጠለ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከምርጫው በፊት በሚኖሩት ወራት ሰላማዊ ሰልፎች ለማካሄድ እና በአገሪቱ በሙሉ የፖለቲካ ከባቢ አየሩ ከማስፈራራት እና ከማሸማቀቅ ነጻ በመሆን እኩል የምርጫ ጨዋታ ምህዳር እንዲኖር ያላቸውን የፕሬዚዳንትነት ስልጣን ተጠቅመው እውን እንዲሆን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡
የመንግስት ሀብትን መጠቀም፡ ለአንድ ለፖለቲካ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ስራ በሚል የህዝብን ወይም የመንግስት ሀበት መጠቀም በህግ የተከለከለ ነው፣ ሆኖም ግን በ2010 በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የአውሮፓ የምርጫ የታዛቢዎች ቡድን እንደዚህ ያሉ ሀብቶች በስፋት በስራ ላይ ውለው እንደነበር ምስክርነቱን ሰጥተቷል (ተሽከርካሪዎች፣ በስራ ላይ ያሉ የመንግስት ሰራተኞች ለገዥው ፓርቲ ለምርጫ ቅስቀሳ መሰማራት፣ በየአካባቢው ያሉ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ለምርጫ ቅስቀሳ ማዋል፣ ወዘተ) ፕሬዚዳት ኦባማ የህወሀት ገዥ አካል የመንግስት ሀብቶችን እና ተቋማትን ለእራሱ የፖለቲካ ስራ የሚጠቀምበት መሆኑን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ እንደዚህ ያሉ የተሳሳቱ አሰራሮች ሊወገዱ እንደሚገባ ፕሬዚዳንቱ ጥረታቸውን ሊያደርጉ ይገባል፡፡
የሜዲያ ከባቢ፡ የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ተዛቢ ቡድን በ2010 በደረሰበት ድምዳሜ መሰረት በመንግስት በሞኖፖል የተያዘው የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት በአገሪቱ ያለውን ብቸኛ የኢንተርኔት አገልግሎት ተቆጣጥሮታል፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ ይደረጋል፣ እንደዚሁም አንዳንድ በዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን የሚንቀሳቀሱ ድረ ገጾች ይሰለላሉ፡፡ የወያኔ አገዛዝ በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉንም ነጻ ጋዜጦችን እና መጽሔቶችን የዘጋ መሆኑን፣ እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎትን መዝጋቱን መቀጠሉን እና የሳቴላይት እና የሬዲዮ ስርጭቶችን በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ወጭ እያደረገ እያፈነ መሆኑን ፕሬዚዳንት ኦባማ ሊያውቁት ይገባል፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ ያላቸውን ስልጣን በመጠቀም ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ምርጫው ዕለት ድረስ በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉት ሚዲያዎች እኩል በሆነ መልክ እንዲያገልግሉ ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኞች እንዲፈቱ እና ሜዲያው በነጻ እንዲያገለግል እና ሁሉን ዓይነት መረጃ ማቅረብ እንዲችል እንዲያደርጉ፡፡
ሲቪል ማህበረሰብ፡ የአውሮፓ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በ2010 ምርጫ ዘገባው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በበጎ አድራጎት እና ማህበራት ቀያጅ አዋጅ ምክንያት የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በምርጫ ሂደቱ ስራ በእጅጉ ስራቸው ተደናቅ ፎነበር፡፡ ይህ ህግ ከ10 በመቶ በላይ የሚሆነውን ገንዘብ ከውጭ ምንጭ የሚያገኙ ከሆነ የአገር ውስጥ ድርጅቶች እንዲባሉ ተደረገ፡፡ በሀገር ውስጥ ያሉ ደርጅቶች ብቻ ናቸው በሰብአዊ መብት እና በዴሞክራሲ ላይ መስራት የሚፈቀድላቸው፡፡       
ከአንድ ሳምንት ገደማ አካባቢ በኒዮርክ ከተማ በክሊንተን ግሎባል ኢኒሼቴቭ ባራክ ኦባማ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምተው ነበር፣ “የሲቪል ማህበረሰቡ መሪዎች ብቻ ናቸው በብዙ መልኩ ዘለቄታዊነት ያለው ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉት፡፡ ምክያቱም አባባሉ ሲነገር በነበረበት ጊዜ በጣም ጠቃሚው ርዕስ “ፕሬዚዳንት” ወይም “ጠቅላይ ሚኒስትር” አይደለም፣ በጣም ጠቃሚው ርዕስ “ዜግነት”… ዜጎች ሲቪል ማህበረሰብ ለምን በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ያስታውሰናል፡፡ ህዝቦች ሀሳባቸውን በነጻ መግለጽ ሲችሉ እና መሪዎቻቸው ተጠያቂ እንዲሆኑ ሲደረጉ መንግስት መልስ ሰጭ እና ውጤታማ ይሆናል፡፡“ ፕሬዚዳንት ኦባማ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ማህበራት ተብሎ የታወጀውን ቀያጅ አዋጅ እንዲወገድ ወይም ደግሞ ጠቃሚነት ያለው ማሻሻያ እንዲደረግበት ጥረት እንዲያደርጉ በአጽንኦ እጠይቀዎታሉ፡፡ የሲቪል ማህበረሰቡ ለዴሞክራሲያዊ ሂደቱ ዋናው እምብርት በመሆኑ ላይ ሙሉ እምነት ስላላቸው ፕሬዚዳንት ኦባማ ያላቸውን ኃላፊነት ተጠቅመው የ2015 አገር አቀፍ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት የሲቪል ማህበረሰቡ ስራውን እንዲጀምሩ እና ነጻ ሆኖ እንዲሰራ እንዲደረግ እንዲያደርጉልን፡፡
የፕሬዚዳንት ኦባማ ኃይል ምንድን ነው? የእርዳታ ገንዘብ፡፡ በጥረት የተገኘ የአሜሪካ የዶላር  ግብር ከፋይ ህዝብ፣ አፍሪካውያንን/ትን በመርዳት ሰበብ የአሜሪካንን ዶላር ለአፍሪካ አምባገነኖች መስጠት ሆኖም ግን የአፍሪካ አምባገነኖችን የሂሳብ አካውንት ማቆም፣ የእርዳታ ገንዘብ ይናገራል፣ እናም በወያኔ ደንቆሮ አለቆች አንደበት በከፍተኛ ደረጃ ይሰማል፡፡ ዳምቢሳ ሞዮ በመጽሐፏ ላይ የሞተ እርዳታ/Dead Aid ብላ ባሰፈረችው መሰረት የወያኔ ገዥ አካል 97 በመቶ የሚሆነውን በጀት የሚያገኘው ከውጭ እርዳታ ነው፡፡ በቀላል አነጋገር የወያኔ ገዥ አካል ከአሜሪካ ጠንካራ ሰራተኛ ግብር ከፋዮች የሚሰበሰብ እርዳታ እስካላገኘ ድረስ ለአንዲት ቀን እንኳ መቆየት እንደማይችል እና ህልውና እንደሌለው ግልጽ ሊሆን ይገባል፡፡ ፕሬዚዳት ኦባማ ዓመታዊውን የደህንነት እርዳታ ለለማኞቹ የወያኔ ተመጽዋቾች ለመስጠት እጅዎን ሲዘረጉ እ.ኤ.አ በ2009 በጋና አክራ ለአፍሪካውያን/ት ምን የሚል ንግግር አድርገው እንደነበር ያስታውሱ፡፡ 
ልማት በመልካም አስተዳደር ላይ የሚወሰን ነው፡፡ የእራሳቸውን ህዝቦች ፍላጎት የሚያከብሩ፣ በስምምነት የሚገዙ እና በጭቆና የማይገዙ መንግስታት በጣም ሀብታሞች ናቸው፣ የተረጋጉ ናቸው እናም ከሌሎች የዚህ ዓይነት ባህሪያት ከሌላቸው መንግስታት የበለጠ ስኬታማ ናቸው፡፡ መንግስታት የህዝቡን ሀብት እየመዘበሩ የእራሳቸውን ኪስ የሚያዳብሩ ከሆነ ማንም አገር ቢሆን ሀብት ሊፈጥር አይችልም፡፡ የህግ የበላይነት ቦታውን ለጨካኝነት እና ባርነት የሚለቅ ከሆነ በዚህ ዓይነት ማህበረሰብ ውስጥ መኖር የሚፈልግ የለም፡፡ ያ ዴሞክራሲ አይደለም፣ ይልቁንም ያ አምባገነናዊነት ነው፡፡ እናም በአሁኑ ጊዜ የዚያ ዓይነት መንግስት መወገጃው ጊዜው አሁን ነው…
2015 የኢትዮጵያ ምርጫ ከነፋስ ጋር አብሮ ይሄዳል፣
እ.ኤ.አ በአስራ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አራት ኦር ዌል እንዲህ ብለው ጽፈው ነበር፣ “የወደፊቱን ስዕል የምትፈልግ ከሆነ በሰው ፊት ላይ ለዘላለም ማህተም የተደረገ የቦት ጫማ በህሊናህ ውስጥ አስብ፡፡“ የ2015ን የኢትዮጵያን ምርጫ ስዕል ለማየት ከፈለግህ በጠራራ ጸሐይ በቀን ብርሀን የተሰረቀን የምርጫ ውጤት እና በምርጫ ቦት የምርጫ ሌቦችን እና ዘራፊዎችን የሚያባርሩትን ፊቶች፣ ግን ለብዙ ጊዜ አይቆይም፣ ግን በጣም ለረዥም ጊዜ አይቆይም፡፡
በ2015 በኢትዮጵያ ስለሚደረገው ምርጫ የፕሬዚዳንት ኦባማ ንግግር “ባዶ ነፋስ” ነው፣ (“የውሸት ቁልሎች” ከመለስ ዜናዊ ዘለፋ በመጥቀስ) ውሸትን እውነት የሚያስመስል ፖለቲካዊ ቋንቋ፡፡ ታሪክ ብዙ ነገሮች “ከነፋስ ጋር እንደሚሄዱ” ያሳያል፡፡ “እርሱ የእራሱን ቤት የሚያስቸግር ነፋስን ይወርሳል፡ እናም ቂል የብልህ አሽከር ይሆናል የሚለውን ሁላችንም ልናውቀው ይገባል”፡፡ አሁን በህይወት የሌለው መለስ እና የእርሱ ደቀመዝሙሮች በአሁኑ ጊዜ አስቸጋሪ በሆነ መልኩ የኢትዮጵያን ቤት በማስቸገር ላይ ይገኛሉ፣ እናም ነፋስን ይዘግናሉ! አውሎ ነፋስም በቅስፈት ይዞዋቸው ይሄዳል።
በ2015 በኢትዮጵያ ምርጫ አለ፡፡ ምርጫው ሰዎችን እንዴት በብር መግዛት እንደሚቻል ነው፣ እናም ስለሰዎች አስተዳደር አይደለም፡፡ በኢትዮጵያ በ2015 ምርጫ አይኖርም፣ ሆኖም ግን ሸፍጥ ለመስራት የሚቆይ ምርጫ አለ፡፡ 
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ጥቅምት 15 ቀን 2007 . 

በደቡብ ትግራይ፣ ሃገረሰላም ከተማ ህዝባዊ ኣመፅ ተቀሰቀሰ

October29,2014
አምዶም ገብረስላሴ – ከትግራይ

በትግራይ ደቡብ ምስራቅ ዞን ሃገረሰላም ከተማ በሙስና ምክንያት መሰራት የነበረበት ባለ ሁለት መስመር መንገድ ኣንድና በጣም ጠባብ ኣድርገው የደጉዓ ተንቤን ኣስተዳዳሪዎች ሊያሰሩት ሲሉ ሰኞ 17 / 02 / 2007 ዓ/ ም ህዝባዊ ኣመፁ ሊቀሰቀስ ችለዋል።

የኣመፁ መነሻ ከመቐለ ተነስቶ ሃገረሰላም፣ ዓብይ ዓዲ፣ ዓድዋ የሚደርሰው የፌደራል መንግስት በመደበው በጀት የሚሰራው የኣስፋልት መንገድ ሃገረሰላም ከተማ ሲደርስ የድሮ መንገዱ ጠባብና ኣንድ መስመር የነበረ ሲሆን እንደሌሎች የኣገራችን ከተሞች የሚፈቀደው ስታንዳርድ ባለ ሁለት መስመር የከተማ መንገድ መሆን ሲገባው ባለ ኣንድ ኣድረገው ለመስራት በመሞከራቸው ነው።

ስራው ህብረተሰቡ “…እድሉ ሁለተኛ ግዜ ኣይገኝምና የፈረሱ ቤቶች ፈርሰው ለወደፊቱ የከተማዋ እድገት በሚፈቅድ መሰረት እንዲሆን ፈቅደናል…” የሚል ውሳኔ ኮንትራት ለያዘው የመከላከያ ኮንስትራክሽን የከተማዋ ህዝብ “..እንኳን ደህና መጣቹ..” የሚል ግብዣ ባዘጋጁበት ወቅት ነበር።

ችግሩ የተፈጠረው ኣንድ የከተማዋ “..ሃብታም ነኝ..” ባይ ሰው በመንገዱ ሁለት ኣቅጣጫዎች ፕላስ ዋን ፎቆች ኣሉበት። ይህ ሰውዬ ከወረዳዋ ኣስተዳደር በመመሳጠር “..ለከተማዋ የሚፈርሱ ቤቶች ይውላል..” ተብሎ የተመደበው ብር ተመላሽ በማድረግ መንገዱ በቂ እንደሆነ ኣድረገው “..የተጠና..” ብለው ለመከላከያ ኮንስትራክሽን በመስጠት በጀቱ ተመላሽ እንዲሆን ኣድረገዋል።

ህዝቡ “..ህገ ወጥ ውሳኔው..” ስለደረሰው ወደ ወረዳ፣ ዞን፣ ክልል፣ ፌደራል መንግስት ኣቤቱታ ቢያቀርብም ሰሚ ጀሮ ኣላገኘም።
“.. ሃብታም ነኝ..” ባይ ሰውዬም 2 ሌሎች ሰዎች ኣስከትሎ እስከ ፌደራል መንግስት የወረዳው ውሳኔ እንዲፀና ተከራከረ።

ብር ይዞ በየ ደረጃው ያሉ ኣቤቱታ ሰሚ ኣካላት ኣፋቸው የለጎማቸው ሰውየ ብር ብቻ ሳይሆን የህወሓት ኣገልጋይና ህብረተሰቡ ሁሌ የሚያነሳው የልማት ጥያቄ በማኮላሸት የሚታወቅ ነው።
ተመሳሳይ የሰውየው ተግባር በ1996 በመላ ተንቤን የተነሳው የመሰረተ ልማት ጥያቄ እንዳይሳካ ኣፍራሽ ተራ የተጫወተ ነው።

የመንገድ ስራውና የሙስናው ግልፅ መሆን ኣስገራሚ የሚያደርገው የድሃ የሚባሉ ቤቶች መሃንዲሱ በቀየሰው መሰረት ከፈረሱ ኣንድ ዓመት ማሳለፋቸው ነው። መንገዱ የወረዳው ባለስልጣናት እንደወሰኑ ተግባራዊ ቢደረግ ዚግዛግ ይሰራል።

ህዝቡ ወደ ኣመፅ የተሸጋገረው መንገዱ መሰራት ሲጀምር ነው። ህዝቡ በኣንዴ በመሰባሰብ ስራው እንዲቆም ኣድርገዋል።

ፖሊስ ኣመፁ እንዲ በትን በወረዳው ኣስተዳዳሪዎች ቢታዘዝም የህዝቡ ቁጣ በመስጋት የወሰደው እርምጃ የለም።
ህዝባዊ ኣመፁ እስከ ኣሁን መፍትሄ ኣልተበጀለትም። የመከላከያ ኮንስትራክሽንም ስራው ኣቁሟል።

ኣዎ…! ህዝቡ ኣይኑ ያፈጠጠ ሙስና ሊሸከም ፍቃደኛ ሊሆን ኣልቻለም። መንግስትም ለስልጣኑ ሲል( ለህብ ብሎ መስራት ካቆመ ብዙ ስላደረገ ነው) ኣወንታዊ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል እንላለን።

Tuesday, October 28, 2014

A blessing in disguise for Temesgen Desalegn

October 28, 2014
by Belay Manaye
“He wrote blaming and defaming the government as it kills, arrests, and suppresses…”
That was read in a courtroom where Temesgen’s verdict was heard yesterday. It was very disgraceful to hear this. After two years lengthy of the court case, Temesgen Desalegn was found ‘guilty’ of inciting violence and defamation. That was really funny. Criticizing the government becomes defaming it in Ethiopia. Unlucky!An Ethiopian editor is facing as many as 10 years in prison
The government filed over 100 lawsuits against Temsegen so far. And though it was unsurprising, the government, through its Kangaroo court, has sentenced Temesgen Desalegn, one of the most courageous journalists in Ethiopia, to three years in jail yesterday.
Temsegen is now in jail for he wrote ‘blaming and defaming the government as it kills, arrests, and suppresses’. Isn’t it a fact that the government has been doing all these on Ethiopian people? Didn’t the government kill innocents during post election period of 2005? Didn’t the government kill innocent University students last year? Didn’t the government jail journalists? It did these all. What is blaming then? Why don’t we blame the government for killings and jailing journalists and dissents?
Temsegen was just exercising his constitutional right to freedom of expression. I believe his only crime is exercising his right courageously. And I take my hat off for his job. I am not going to cry for him. He is not going to be disturbed by their arrest because he knows them very well. Yes, he knows that the government ‘arrests, kills and suppresses.’ What happened to him now is what he has been writing about.
Eskinder Nega, another hero in Kaliti prison cell, was expecting Temesgen’s sentence. During my visit last Saturday, he was telling me that EPRDF would definitely put Temesgen in prison for about 2-3 years. Eskinder was right! Temesgen has already joined him in prison, escalating the number of jailed journalists to 18, second jailer of journalists next to Eritrea in Africa.
Of course, Temesgen’s sentence is a blessing in disguise for him. He has gone several times to court. It is tiresome! Three years is too short for Temesgen as he knew they would do this on him anytime they like. He bravely discharged his responsibility. Yes, he has accomplished his job. What remains is ours! We must not let Eskinder, Reeyot, Wubshet, Temsegen, and others down. We have to keep writing, speaking out and struggle for our right.
Temsegen is jailed while exercising his right to freedom of expression courageously. The homework is on us. We shall not be jailed while we are doing nothing. I said Temesgen’s sentence is a blessing in disguise for him because he has done his part, even beyond his part, and hence need to have time to look back his journey and articulate his future move. Temesgen is really a free man; a free man behind the bar.
Yes, the government sentenced the free man. And we remain silent. Jailing is becoming a profitable business for the government because we still are silent. It is a load for us out here. For Temsegen, it is a blessing in disguise.
Stay strong Teme!

Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).

October 28,2014
FOR IMMEDIATE RELEASE
MEMORANDUM
TO: The United Nations Security Council Sanctions Committee
FROM: Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy.
DATE: October 27, 2014
SUBJECT: Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).
Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy expresses its high regards to The United Nations Security Counciland would like to use this opportunity and bring to the attention its reservations regarding some references made about it in SEMG report of October 13, 2014.
1. The SEMG report states that “Ginbot 7 is a banned opposition group”. We would like to call the attention of the International Community to the infamous “Anti-Terrorism Proclamation” promulgated by the TPLF/EPRDF regime of Ethiopia with the aim of stifling political dissent. The dictatorial regime has used this proclamation as an instrument to label and criminalize Ginbot 7, as well as other political opposition organizations, human rights advocacy groups, civil society, journalists and bloggers inside and outside of Ethiopia.
2. Let alone the claim in the report that Ginbot 7 was established in 2005, which is categorically false, even the so-called Anti-Terrorism Proclamation was not promulgated until 2009.
Ginbot 7 was formed in 2008 after few members among its leadership spent almost two years in prison in the aftermath of the ill-fated election of May 15, 2005. As well known by the International community, the regime overturned the election results that clearly showed the opposition party Coalition for Unity and Democracy (CUD) has won the majority throughout the country. This is a fact corroborated by international election observes such as the European Union’s Election Monitoring Group that was present in Ethiopia to observe the election in 2005. Those who formed Ginbot7, then leaders of the CUD, were among the leaders thrown in prison on trumped up charges.
Ginbot 7 was formed as a political movement in order to advance justice, freedom, and liberal democracy in Ethiopia. Ginbot 7 believes that no meaningful and genuinely competitive elections can take place in the country due to the prevailing and ever worsening egregious human rights violations, the closing of political space, the harassment and persecution of members of the legal and peaceful political opposition. Furthermore, an entrenched minority ethnocratic dictatorship in Ethiopia has determined to perpetuate its hold on power by all and any means necessary.
3. SEMG’s claim in the report that Ginbot 7 was established by “Amhara elites” is grossly erroneous given the ethno-religious mix of its leadership and membership. The report’s characterization of Ginbot 7 as an organization established by “Amhara elites” is not only factually inaccurate, but a clear indication of the bias of the report. It seems like SEMG has bought lock, stock and barrel the dictatorial regime’s fabricated story of Ethiopian politics as an entirely ethnic based phenomena.
The SEMG could have easily established the facts by taking a cursory look at Ginbot 7′s website rather than unquestioningly accepting the regime’s characterization with regard to Ginbot 7′s multi ethnic membership and leadership, its organizational principle and its well established position on ethnic based politics in Ethiopia. No effort seems to have been made by the SEMG to balance its report by counterchecking its claims from Ginbot 7 or other sources instead of recycling the minority regime’s long standing targeting and demonization of the Amharas, the second largest ethnic group in Ethiopia.
4. The SEMG, despite its familiarity with political conditions in the Horn of Africa, fails to realize what is very obvious to all regarding the TPLF/EPRDF regime’s agitation, use of threat, torture and at times bribery when presenting helpless prisoners under its custody to echo unfounded guilt they are coerced to rehearse for interviews and media presentations. Hence, presenting forced confessions and unreliable information from such prisoners as evidence is beyond comprehension.
5. The SEMG’s claim to have retrieved information from an alleged Ginbot 7 fighter captured in Gonder is no different from what is explained above.
6. SEMG’s reference in its report to weapons’ serial numbers to suggest the source of certain weapons as being from Eritrea, clearly neglects the fact that numerous prisoners of war, weapons and ammunitions have exchanged hands between Ethiopian and Eritrean forces during their numerous wars.
7. Needless to say that the SEMG has been manipulated to construe that Ginbot 7 needs to extend its recruitment to the southern tip of Africa, while what Ginbot 7 objectively faces is the capacity to accommodate the tens of thousands forcing their ways into its fold from amongst the millions who support it. These are Ethiopians from very diverse backgrounds seeking a genuinely liberal democratic and just order, freedom and equality which have been denied to them by the brutal dictatorial regime of the TPLF/EPRDF.
8. It is unfortunate to note that the SEMG has been misguided to misrepresent Ginbot 7’s prevailing organizational reality that clearly demarcates boundary between its own political bodies from that of other organizations that may have opted to attain their objectives by any other means they deem appropriate.
9. Ginbot 7 found the claim in the report regarding persons SEMG suggests were received by Andargachew Tsege upon their arrival in Asmara and who have “joined a group of 30 to 60 Ginbot 7 fighters at Harena Military Camp” comical, simply because the arithmetic percentile between 30 and 60 is 100% and hence too large a difference for any wrong guessing.
10. The SEMG clearly states in its report that it was unable to verify the claims of the alleged Ginbot 7 fighters, which begs the question, then, as to why the SEMG had to dwell in its defamatory claims and tarnish the image of Ginbot 7.
11. The same can be said about SEMG’s statement in its report regarding its inability to assess the extent of this unsubstantiated support as compared with Asmara’s support of Ginbot 7 in the past.
12. The SEMG seems to be deliberately overlooking or otherwise incognizant of TPLF/EPRDF regime’s well recorded expertise in passport, travel document, and other forms of forgeries going back to its days as a guerrilla force. Had this not been the case, understanding the nature of documents presented to it by the regime’s security officials, should not have been beyond the comprehension of the SEMG.
The allegations by SEMG may be well calculated and deliberate distortions aimed at upholding the sanctions imposed on Eritrea. However, we fail to comprehend why Ginbot 7, or the Ethiopian people for whose rights our organization is struggling for, is interjected in these maneuvers.
Ginbot 7, however, would like to use this opportunity to assure all concerned, including the United Nation’s Security Council, that it is ready to give freely and candidly tangible explanations related to its mission and the achievements in the process of registering its just struggle.
Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy would like to respectfully conclude its MEMORANDUM by strongly affirming that it stands ready and willing to cooperate with the International Community, in good faith, and contribute everything within its capacity for sustainable regional peace and stability in the Horn of Africa.
We look forward to your timely reply.

ሚሊዮኖች ድምጽ -ሃብታሙ አያሌው ቶርቸር እየተደረገ ነው !

October 28,2014
ክስ ሳይመሰረትበት ለአራት ወራት በማእከላዊ እስር ቤት የሚገኘው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ ከፍተኛ ኢሰብአዊ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ ታወቀ።
“ወደ ፖለቲካው የማትመለስ ከሆነ ትወጣለህ። አለበለዚያ እዚሁ ነው የምትሞተው” በማለት አማራጭ ቢያቀርቡለትም፣ ሃብታሙ መሞትን እመርጣለሁ የሚል መልስ የሰጣቸው ሲሆን፣ እየደረሰበት ባለው ስቃይ በጣም እየታመመ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። “እስኪ ትግሉን እናስቀጥላለን የሚሉ ሰዎች ያድኑህ ? “ ሲሉ አሳሪዎቹ በስቃዩ የሚደሰቱ ሲሆን፣ ከባለቤቱ በስትቀር ጠበቃዉም ሁሉ ሳይቀር እንዳያየው ተደርጓል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ ፣ በታፈነና አየር በማያስወጣ ክፍል ዉስጥ እንዲታሰር በመደረጉ በተደጋጋሚ ለተቅማጥና ተያያዥ በሽታ መጋለጡን፣ እንዲሁም የመተንፈስ ችግር እንዳለበት ለማወቅ ችለናል። “የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድን ነው ? አንድነት ዉስጥ ያሉ ጠንካራ አባላት እነማን ናቸው ? “ በሚል ጥያቄ የቀረበለት ዳንኤል ሺበሺ፣ ክብሩን በሚነካ መልኩ እንደሚሰደብም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ሃብታሙ አያሌው ፣ በእርሱ ላይ እይደረሰ ያለው ግፍ በማንም ዜጋ ላይ መድረስ እንደሌለበት በመግልጽ “የግፈኛው አገዛዝ እንዲያበቃ የኢትዮጵያ ሕዝብ መነሳት አለበት” ሲልም ለህዝቡ የትግል ጥሪ አስተላልፏል።
የአንድነት ራዲዮ የዘገበዉን እንደሚከተለው ያድምጡ !

Monday, October 27, 2014

የ “ካዛንችሱ መንግስት በአዲሰ አበባ ማዘጋጃ ቤት” – ከግርማ ሰይፉ ማሩ

October 27.2014
ዛሬ ጥቅምት 17/ 2007 እግር ጥሎኝ አዲሰ አበባ ማዘጋጃ ቤት ጎራ ብዬ ነበር፡፡ የታዘብኩት ነገር ያስታወኝ ኤርሚያስ ለገስ “የመለስ ትሩፋቶች” በሚል ባወጣው መፅሃፍ ውስጥ “የካዛንችስ መንግሰት” ብሎ ያስነበበንን በገሃድ ከካዛንችስ ቦታ ቀይሮ አዲስ አበባ መስተዳደር ግቢ ውስጥ መኖሩን ነው፡፡ የካዛንችሱ መንግሰት ምን እንደሚሰራ እዚህ መዘርዘር አይጠበቅብኝም፤ በጥቅሉ ግን የአዲስ አበባ ህዝብ “መርጦ” ወይም ቀጥሮ ያስቀመጣቸው ሰዎች ሳይሆን ውሳኔ የሚስጡት ሌሎች በስውር በደህንነት ስም በኢህአዴግ የተቀመጡ ሰውር እጆች መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
እነዚህ ሰውር እጆች ለእኛ ለተቃዋሚዎች አዲስ አይደሉም ለምሳሌ፤
· በሆቴሎች አዳራሽ ለማከራየት አንችልም ምንም ጠቃሚ ገንዘብ ቢሆን ሆቴሎች ፈቃደኞች አይደለም፤
· ማተሚያ ቤቶች የተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም እነርሱን ይደግፋሉ የሚባሉ የግል ጋዜጦችና መፅሄቶች አያትሙም
· መብራት ኃይል ለአንድነት የማተሚያ ማሽን ሊያንቀሳቅስ የሚችል የኤሌትሪክ ሀይል (ሰሪ ፌዝ የሚባል ሀይል) ለፓርቲ ለማስገባት ፈቃደኛ አይደለም፤
· ቤት አከራዮች ቤታቸውን ለማከራየት ይፈራሉ፤
· በቅስቀሳ ጊዜ መኪና እና የድምፅ መሳሪያዎች ማግኘት ፈተና ነው፤
· ለቅስቀሳ የወጡ ሰዎች እንደ በግ በየጣቢያው ሲታሰሩ የሚያስሩት ሰዎች በግልፅ ዩኒፎርም የለበሱት ፖሊሶች ሳይሆኑ በሬዲዮ የሚያዙ ማን እንደሆኑ የማይታወቁ ናቸው፤ ወዘተ ይህ ሁሉ የሚሆነው በህግ አግባብ ሳይሆን በሰውር መንግስት ውስጥ ያሉ ሰውር እጆች የሚሰሩት ነው፡፡
ለዛሬ ፅሁፌ መነሻ የሆነኝ ግን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ኦፌሰር የሆኑት አቶ ማርቆስ ብዙነህ የሰጡን ምላሽ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ በቀጣይ ፓርቲው በሚያደርገው እንቅስቃሴዎች የፓርቲ አባላትን በስነ ምግባር የታነፁ እና ሰላማዊ ትግል በሰለጠነ መንገድ የሚደረግና በግብግብ ሳይሆን በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ እንዲሆን ለማድረግ ለሚያካሂደው ስልጠና ለማካሄድ አዳራሽ ለመከራየት ባቀረብነው ጥያቄ በጎ ምላሽ እንደሌለ ከውስጥ ሰምተን ምክንያቱን በግንባር ለማወቅ ሄጄ የሰማሁት ምላሽ በአንድ መንግሰታዊ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ ደሞዝ ከሚበላ ሲቪል ሰራተኛ የሚጠበቅ ሆኖ አላገኘሁትም፡፡ የሰጡን ምላሽ “አራት ሰዎች መጥተው ፍቃዱ እንዳይስጥ ጠይቀው አለቃይ እንዳትሰጥ ስለአለኝ ነው የሚል ነው፡፡” በቃ ይህ ነው ምክንያቱ፡፡ አንድነት ፓርቲ ይህን ፈቃዳ ላለማግኘት አንድም ያጎደለው መስፈርት የለም፡፡ አቶ ማርቆስ አለቃቸው ይህን መልስ ሲሰጣቸው ለምን? እንዴት ብዬ? ከመመሪያ አንጻር ልክ አይደለም ብለው አይጠይቁም፡፡ አለቃቸውንም አይሞግቱም፡፡ እርሳቸውም የሚያውቁት አለቃቸውም ቢሆን እራሳቸው እንደማይወስኑ፡፡ የሚወስነው ይህ ስውር እጅ ያለው ካዛንችስ የነበረው አሁን በመስተዳድር ቅፅር ግቢ የሚገኘው መንግሰት እንደሆነ፡፡
አንድ መስሪያ ቤት ሰራውን የሚሰራው በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን በደንብ እና መመሪያ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ኦፊሰሮች ተግባራቸውን ሲያከናውኑ ደግሞ እነዚህ የህግ ማዕቀፎች መሰረት አድረገው ነው ብለን እንጠብቃለን፡፡ በዚህች ምስኪን ሀገር ግን ይህ ምፀት ነው፡፡ በህግ ማዕቀፍ የሚሰራ ኦፊስር ማግኘት ዘበት እየሆነ መጥቶዋል፡፡ አለቃው በቃል አድርግ ያለውን የሚያደርግ የማርቆስ ዓይነት ኦፊሰር ሞልቶ ተርፎዋል፡፡ በጣም የሚገርመኝ የዚህ ዓይነት ኦፊሰሮች ለልጆቻቸው ሰራ ሄጃላሁ የሚሉ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ባይሉ
ዋቸው ደግ ነው፡፡ ይህን ሊያደርጉ መሄዳቸውን ሲያውቁ ያፍሩባቸዋል ብዬ ስለማስብ ነው፡፡ ለምን ለልጆቻችን ማፈሪያ እንደምንሆን አይገባኝም፡፡
መልካም አስተዳደር አስፍናለሁ የሚል መንግሰት መልካም አሰተዳደር የሚሰፍነው በአዳራሽ ኮፍያና ቲ ሸርት ለብሶ በሚደረግ ዲስኩር እንዳልሆነ የገባው አይመስለም፡፡ መልካም አስተዳደር የሚሰፍነው በህግ ማዕቀፍ አገልግሎት የሚሰጥ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛ አገልግሎት ሲሰጥ እንጂ በስውር በቃል በሚሰጥ ትዕዛዝ እንዳለሆነ መረዳት ይኖርብናል፡፡ ማርቆስ በሚሰጠው መልስ እየተበሳጨ፣ እያዘነ ሲከፋውም እየተሳደበ የሚሄድ ተገልጋይ መዘዝ እንደሚያመጠ ግን የገባቸው አይመስለኝም፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ደግሞ በስውር መንግሰት በዚህ መንገድ እንዲሆን ስለሚፈልግ ነው፡፡
ዛሬ በግልፅ የተረዳሁት በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ብሎም በሀገር አቀፍ ደረጃ መልካም አስተዳደር የማሰፈን ችግር ምንጭ በደህንነት ስም በስውር ያለው መንግሰት የሚሰጠው ትዕዛዝ ሲሆን፣ ሲቀጥልም አድርግ ያሉትን ለማድረግ በተጠንቀቅ ዝግጁ የሆነው የማርቆስ ዓይነት ደሞዝ እየበሉ ያሉ ሲቪል ሰራተኞች ናቸው፡፡ አለቃዬ እንዲህ አድርግ ብሎኝ ነው በሚል መመሪያን መሰረት ያላደረግ ትዕዛዝ የሚሰፈፅሙ የማርቆስ ዓይነት ኦፊሰሮች የዚህች ሀገር መከራ እንዲረዝም፣ ህዝቡ የመልካም አስተዳደር ትሩፋት እንዳያገኝ ተባባሪ እንደሆኑ አበክረን መንገር ይኖርብናል፡፡ ይህንን አሜን ብሎ የተቀበለ ህዝብ መከራውና ግፉ ተስማምቶኛል እንዳለ ይቆጠራል፡፡ የዚህ ዓይነት ህዝብ ደግሞ ምንም ዓይነት አንባገነን መንግስት ቢመጣ የሚገባው ነው ማለት ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ኢህአዴግ አይመጥነንም ያለ ህዝብ በቃ!!!! ሊለው ይገባል፡፡ ኢህአዴግ በቃ ሊባል ይገባል!!!!
ቸር ይግጠምን

Sentencing of Ethiopian journalist Temesghen Desalegn

October 27, 2014

Ethiopian court sentences journalist to three years in prison

CPJ Nairobi, October 27, 2014The Committee to Protect Journalists condemns today’s sentencing of Ethiopian journalist Temesghen Desalegn to three years’ imprisonment on charges of defamation and incitement that date back to 2012. A court in Addis Ababa, the capital, convicted Temesgen on October 13 in connection with opinion pieces published in the now-defunct Feteh news magazine, according to news reports. He was arrested the same day. Authorities have routinely targeted Temesghen for his writing. Temesghen’s lawyer said he plans to appeal the ruling, according to local journalists.charges against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn
“With each journalist sentenced to prison, Ethiopia takes another step further from freedom of the press and democratic society,” said CPJ East Africa Representative Tom Rhodes. “We urge Ethiopian authorities to overturn Temesghen’s conviction on appeal and release him and all other journalists jailed for doing their jobs.”
A state crackdown on independent publications and bloggers has taken place in Ethiopia this year, prompting several Ethiopian journalists to flee into exile, according to CPJ research. With at least 17 journalists in jail, Ethiopia is the second worst jailer of journalists in Africa, second only to its neighbor Eritrea, CPJ research shows.

Meles’ Legacy Is Tripping The TPLF

October 27, 2014
by Kaleab Tessema
Let it be known that I never personally met or spoke with Meles, nor did I have the ability to read his mind. What I will say, just like everyone else, I can perceive the character of the man through his actions—the actions of a divider of people, murderer of the innocent, and thief of a nation’s potential.PM Meles Zenawi of Ethiopia
Thus, after the death of Meles an undisclosed illness, some people were speculating that the Tigray People Liberation Front (TPLF) would take the opportunity to abandon their fascist form of government and intractable “divide and rule” policies. Not only to end this cruel policy, the TPLF became worse than their late capricious prime minister. The TPLF hid Meles’ death from the people for about a month while his political party the Tigray People Liberation Front (TPLF) schemed and plotted to continue his legacy of oppression. Right now, they are brutally beating and harassing the people who disagree with their policies. While Andargachew Tsige was interrogated briefly by the regime’s security apparatus on Woyanne owned TV, we heard people being tortured in the background. The victims were screaming in excruciating pain. It is unprecedented that a government dare to show a shocking and a disturbed voice to the public.
Funny enough, the Woyanne groups are uneducated who do not care about people; they just perpetuate their own interests to buy more time to run the country for another twenty two years by preaching and adulating their late prime minister’s policies. Of course, Hailemariam Desalegne outcries about Meles’ greatness and a visionary leader, that brought a sustainable democracy which embraces all ethnicities in the country. it is quite clear that Meles was the one who picked Hailemariam as his deputy prime minister and if Hailemariam idolizes his late boss, no one would be surprised. In addition to that, Meles knew that Hailemariam is too much to divulge his repugnancy towards Amhara ethnic group which made him very loyal and closer friend to Meles.
I have been scrupulously watching the regime and its supporters on how they disseminate invidious discrimination of propaganda about Amhara by calling ‘NEFTEGNA’ to create an ethnic cleansing with other ethnics in order to stay in power which is dangerously wrong. There is no doubt that Meles and his party had a deep hatred towards Amhara. Even after Meles died, the so-called ruling political coalition, EPRDF junta government, each and everyone has anti-Amhara sentiment. I still do remember when Shabia and Woyanne were in the bush, their core principle of the slogan was first to break the back bone of Amhara. Of course, no one deny that Amaras have been suffered since the TPLF gripped the power.
Sadly enough, the TPLF brutal killing of innocent Amharas peasants in the southern part of the country was not enough; the TPLF tried to inject some sort of sterilizer into Amhara women that would make them unable to conceive. Further, a few years ago a report given to Woyanne parliament about the disappearance of 2.4 million Amharas in the census conducted was an evidence. The TPLF tried any means necessary to reduce the number of Amhara population. These diabolic actions on Amharas, it is not new, it is already in the record.
It is fact that Today’s TPLF and its surrogates control vast areas of wealth in Ethiopia. Of course, whether like it or not, many Tigryans are beneficiary more than any one of the Ethiopian ethnic group under the TPLF rule. For no reason, Amharas have been made the main target of vilification, and demonization by TPLF for the last twenty-two years. I know some of the TPLF’s sympathizers will not agree with the facts that I reveal about the TPLF ethnic junta is doing to the innocent Amharas in the south. At this point of time, the Woyanne propaganda on Amhara they created racial antipathy between other ethnic groups is not a lasting, it is a transient.

What are the Meles’ Legacies?

Since Meles’ passing, the TPLF have had a hard time to replace their late prime minister. The TPLF tried to look for a person whose ethnic origin is Tigryan or Eritrean who has a tendency to prevaricate about Ethiopian history, but they might think they would excoriate for the replacing their own ethnicity, and then the TPLF, after assiduously thinking, artfully and systematically appointed Hailemariam Desalegne as prime minister of Ethiopia whose ethnicity is from Welayita to divert the attention of the people. Funny enough, Hailemariam is a vulnerable prime minister who is not a decision maker where under surveillance of the TPLF. Every one knows in Ethiopia that Hailemariam is a puppet prime minister who takes an order from the TPLF cabal.
Having said that, Meles was a ferocious and a perfidious person who mortified the nation and its people in the eyes of the world in the twenty first century. Let us not forget that, Meles was the one who made Ethiopia landlocked and ninety million people left without port. He also publicly said that “Ethiopian’s history is only 100 years old, and its flag is a piece of rag.” At one time, I was surprised by his flippant remarks about Tewoderos and Menilik that he was comparing himself claiming that Ethiopians for the first time got a peace under his rule. Surprisingly enough, a despicable and a traitor person comparing himself to those great men and a true sons of Ethiopia who protected Ethiopians from foreign invaders is a bluffing and a gimmick. Anyway, that was his usual prating.
Going back to my point, the regime is worshiping of the late dictator to persuade his policy whose actions were anti-Ethiopian that put the country on a dangerous path of the division along ethnic and language line based federalism. At the matter of fact, Meles was a one-man rule who had an absolute power and spun the Woyane for the last twenty one years. Now the regime tries to preach personal cult of a tyrant leader by bemusing the true dictatorial legacy of Meles.
Meles was a capable of dissimulation to stay in power by creating an idea where most people agree with it, like ‘Renaissance Dam’, to divert the issues and muzzling the political dissents. When Meles wants to detain the people who disagree with his policies, he blackmails by creating false documents that involves with terror activities, and when he gets a big criticism from the people, he immediately changes his mind to release those who falsely put in prison. Then after brutally tortured and demeaned, the prisoners were required to sign a letter of apology to Meles Zenawi with preconditions.
Now, the Meles’ legacy is the word of God for Woyanne, which is not working well as worked well for him. Since Meles died, mass killings and incarceration have doubled in the country. As the result, these criminal acts made Ethiopians more united inside and outside against the TPLF than before. For example, recently in Washington D.C., the brave and courageous young people occupied the Woyanne Embassy and brought down the provocative TPLF flag, then hoisted the true colors of the Ethiopian flag. Thus, the dubious policies being made by Meles that put the present brutal regime into a deeper political quagmire. Arresting and torturing the people will not bring any solution for TPLF; rather, it aggravates civil strife and instability in the country.
Finally, I call on opposition forces to stand up and be a voice for defenseless people who have been physically and verbally assaulted by the brutal regime in Ethiopia. It is about time to put aside their differences and to work together at this critical time, otherwise, the TPLF continues to repress the people and dismember the country. I do not have a moral authority to tell the opposition what to do, but I would like to share my humble opinion to the opposition forces that unity is paramount in order to remove the Tigryan ruling oligarchy.

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት

October27,2014
የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ቀን በዋለው ችሎት 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ ፍትህን ሲያሳትም የነበረውና ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ማስተዋል ህትመትና ማስታወቂያ በ10 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበታል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅም 3/2007 ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አሁን የተፈረደበት በትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በአንደኛው ክስ ነው ተብሏል፡፡ የጥፋነኝነት ክሱ በተነበበት ወቅት ግን ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል ብሎ ጽፏል፡፡›› በሚል ጥፋተኝ ነው ተብሏል፡፡
አቃቢ ህግ የቅጣት ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ሆነ ጠበቃው የቅጣት ማቅለያ አላቀረቡም፡፡ በሌላ በኩል የጋዜጠኛው ጠበቃ አምሃ መኮንን ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስታውቀዋል፡፡
(ነገረ ኢትዮጵያ)

ህወሃትና የጦር አበጋዞቹ እሴቶች

October 27,2014
ህወሃት የትግሬ ተወካይ ብቻ ሳልሆን ለትግራይ ህዝብ የሚያመልከውን አምላክም ጭምር የምመርጥለት እኔ ነኝ በሚል እብሪት ውስጥ ይገኛል። በዚህ እብሪቱም እየተመራ የምታመልኩትን ልመርጥላችሁ ብሎ አጠቃላይ ሙስሊሙንም ክርስትያኑንም እያመሰው እንደሆነ እያየን ነው። እኔን የማይቀበል እጣ ፈንታው ከመታመስ በላይ የሆነ ወዮታ ነው የሚል ያልተፃፈ አዋጅም አለው። ህወሃት በትግራይ ትከሻ ላይ ተፈናጦ፤ ትግራይን ምርጫ አሳጥቶ እኔን እምኑ መንገዳችሁም ህይወታችሁም እኔ ብቻ ነኝ ብሎ ራሱን የትግራይ ጣዖት አድርጎ ሹሟል። ይሄን ጣዖት አንቀበልም፤ እኛ የራሳችን ሂሊና ያለን እንደ ሰው ማሰብ የምንችል ነን ያሉ ብዙ የኢትዮጵያ ልጆች ባልታወጀው አዋጅ መሠረት አብዮታዊ ፀሎት እየተፀለየላቸው አፈር ለብሰው ቀርተዋል።የህወሃት የእብሪቱ መጀመሪያ “እኔ ያልኩት ካልሆነ ሁሉም ገደል ይግባ” ማለቱ ነው። የትግራይ ተወካይ እኔ ብቻ ነኝ ሌላው ሁሉ የትግራይ ህዝብ ጠላት ነው የሚል እምነቱ የድርጅቱን ሥር የሰደደ መሠሪነትና እብሪት የሚያሳይ ነው።
ብዙ ኢትዮጵያዊያን ህወሃት የቆመው ለትግራይ ህዝብ ነው የሚል ዕምነት አሳድረዋል። ይሄን አስተሳሰብ መቀበል የሚጠቅመው ለህወሃት ብቻ ነው።ህወሃት ለትግራይ ህዝብ ክብርም ፍቅርም ያለው ቡድን አይደለም። ለትግራይ ህዝብ በጎ ምኞት እና ክብር ያለው ቢሆን ኑሮ የትግራይ ህዝብ የወደደውን እንዲመርጥ፤ ያልወደደውን እንዲተው ያልተሸራረፈ ነፃነት እንዲኖረው ያደርግ ነበር። እኛ እንደምናየው ግን የትግራይ ህዝብ የወደደውን ለመምረጥ፤የጠላውን ለመተው እንዲችል ነፃነትያለው ህዝብ አይደለም። የትግራይ ህዝብ ነፃነቱን በነፃነት ሥም ያጣ ህዝብ ሁኗል። ህወሃቶች የትግራይን ህዝብ ነፃነት ሸራርፈው ሸራርፈው ህዝቡን በሙሉ መያዣ አድርገውና ከወገኑ ለይተውት እየገዙት ይገኛሉ። የትግራይም ህዝብ ሳይወድ በግዱ ህወሃቶችን ተሸክሞ መከራው በዝቶ እየተገዛ ይገኛል።
ህወሃት መራሽ በሆነው መከላከያ ድህረ-ገፅ ላይ “ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ማስረፅ” እሴታችን ነው የሚል መፈክር በጉልህ ተፅፏል። ህወሃቶች መከላከያ ኃይሉ የቆመው የህዝቡን ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲዊያ አስተሳሰብ ለመንከባከብ ነው እያሉን ነው። የህዝቡ ዲሞክራሲያዊ መብት ሳይሸራረፍ ተከብሮ ቢሆን ኑሮ ጋዜጠኛ ሚሊዮን ሹርቤ ተሰዶ ሂዶ በባዕድ አገር ባልሞተ ነበር። ህዝቡ በኑሮ ውድነት ባልተሰቃየ ነበር፤ አገሪቷ ሠላም ርቋት እዚህም እዚያም የዜጎች ደም በከንቱ ባልፈሰሰ ነበር፤ የአገሪቷ ብሄራዊ አንድነት ላልቶ ዜጎች ይሄ ክልል አገራችሁ አይደለም እየተባሉ ከኖሩበት መንደር ውጡ ባልተባሉ ነበር፤ ዜጎቿ አገር ውስጥ ከመኖር ይልቅ በባህር ውስጥ አዞ መበላትን ምርጫቸው ባላደረጉ ነበር። አገሪቷ እንዲህ ምስቅልቅሏ ወጥቶ ባለበት ሁኔታ ህወሃቶች ያልተሸራረፈ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን መንከባከብ የሚችል ሠራዊት ገንብተናል እያሉ እያላዘኑ ይገኛሉ። ይሄንንም ለማጠናከር ስንል የጦር አበጋዞችን መሾም አስፈልጎናል ብለው የአንደኛ ደረጃ ፊደል ቆጥረው ያልዘለቁ ሽፍቶችን ሹመት በሹት እያደረጓቸው ነው።
“ዘላለማዊ ክብር” በሰይጣን መንፈስ ሲመራ ለነበረው ለመለስ ዜናዊ ይገባል ብሎ የሚያመነው “ክርስትያኑ” ደሳለኝ ኃ/ማሪያም በመለስ ዜናዊ መንፈስ እየተመራ ስልጣኑን ከያዘ ግዜ ጀምሮ 4 ሌተናል ጄኔራሎች፤ 9 ሜጄር ጄኔራሎች፤ 28 ብርጋዴር ጄኔራሎችን ሹሟል። ብዙ ሰዎች ግን ደሳለኝ ኃ/ማሪያም በዚህ ሹመት ውስጥ የመወሰን ድምፅ የለውም ይላሉ። እንዲያውም ደሳለኝ የነብሩን ጭራ ይዞ እንዳይለቀው ጭንቅ ሆኖበት የሚኖር ብኩን ግለሰብ ነው ሲሉም ያክላሉ። ያም ሆነ ይህ ደሳለኝ ኃ/ማሪያም የመለስ ዜናዊን ራዕይ ሊያስፈፅም በትር ስልጣኑን ጨብጧልና በእርሱ ዘመን ለሚሆነው ሁሉ ኃላፊነት ይወስዳል።
ወደ ጦር አበጋዞቹ እንመለስ ከእነዚህ የጦር አበጋዞች መካከል አብዛኞቹ የህወሃት አባሎች መሆናቸው የታወቀ ነው። በዚህ ጥቅምት ወር ብቻ 3 ሌተናል ጄኔራሎች እና 3 ሜጄር ጄኔራሎች ተሹመዋል። እነዚህ የጦር አበጋዞች በየትኛው መደበኛ ጦር አውድማ ላይ ውለው ለዚህ ማዕረግ የሚያበቃቸውን ምግባር እንደፈፀሙ የሚያውቅ የለም። ሽፍቶች እና ጎሬላ ተዋጊዎች መሆናቸው ግን የሚካድ አይደለም። የሽፍትነትና የጎሬላ ውጊያ ልምድ ግን ለዚህ ማዕረግ የሚያበቃቸው ሊሆን እንደማይችል የታወቀ ነው።
ሌተናል ጄኔራል ሁነው ከተሾሙት መካከል
1ኛ. አብርሃም ወ/ማሪያም
2ኛ. አደም መሃመድ
3ኛ. ብርሃኑ ጁላ
ሲሆኑ ወደ ሜጀር ጄኔራልነት ያደጉት ደግሞ
1ኛ. ክንፈ ዳኘ
2ኛ. ተክለብርሃን ወ/አርጋይ
3ኛ. ዘውዱ እሸቴ ይባላሉ።
የእነዚህ የጦር አበጋዞች ሹመት ባላቸው የትምህርት ደረጃ፤ ለህዝባቸው ባላቸው ክብር፤ ለአገራቸው ባላቸው ፍቅር ሳይሆን ለጣዖቱ ህወሃት ያላቸው ታማኝነት ሚዛን ደፍቶ በመገኘቱ ነው።
ከስድስቱ የጦር አበጋዞች መካከል የአራቱ ሹመት ቤተሰባዊ ዝምድናን መሠረት ያደረገ ስለመሆኑ የሚከተለውን ትሥሥር እንድትመለከቱ እንጋብዛላእን።
1ኛ. በሌተናል ጄኔራልነት ማዕረግ የተሾመው አብርሃም ወ/ማሪያም የመለስ ዜናዊ የሥጋ ዘመድ ነው። የመለስ ዜናዊ ቅደመ አያት በጎን ከሌላ ሴት የወለዷቸው ሴት ልጅ ልጅ ነው።
2ኛ. ሜጄር ጄኔራል ክንፈ ዳኜ ደግሞ አባቱ አቶ ዳኜ ገ/ስላሴና የመለስ አባት የአቶ ዜናዊ እናቶች እህትማማቾች ናቸው።
3ኛ. ሜጄር ጄኔራል ዘውዱ እሸቴ ደግሞ የመለስ ዜናዊን የቅርብ ዘመድ አግብቶ በጋብቻ ተሳስሯል። ሚስቱ ደግሞ በ18 ዓመት ታንሰዋለች።
4ኛ. ሜጀር ጄኔራል ተክለብርሃን ወ/አረጋይ የመለስ ዜናዊ የአክስት ልጅ ነው።
ይህ መከላከያ ኃይል ተብሎ የአንድን ጎጠኛ ድርጅት ህልውና ለመጠበቅ የቆመውን ቡድን የሚመሩት የጦር አበጋዞች በትምህርት ደረጃቸው ከሚያዟቸው ተራ ወታደሮች የማይሻሉ፤ ከራሳቸው ወዲያ ህዝብና አገር የሚባል ነገር የማያውቁ፤ በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ የአገሪቷን ሃብት ለመዝረፍ የሚሸቀዳደሙ እና ራሳቸውን እንደ ኢንቨሰተር የሚቆጥሩ፤ የውትድርናን ሙያ ከነፍስ ግዲያና ከጭካኔ ለይተው የማያዩ እና ርህራሄ የሌላቸው ስለመሆናቸው የህወሃት ድርሳናት ይመሰክራሉ።
ህወሃት ርህራሄን የማያውቁ ጭካኞችን የጀግንነት ማዕረግ እየሰጠ በአገሪቷ ላይ እያሰማራ ይገኛል። የህወሃቶች ስነ-ምግባርም ሆነ ስነ-ልቦና ለጀግንነት የሚያበቃቸው አይደለም። በህወሃት መንደር ጀግናና ጀግንነት አይታወቁም። ጀግና እውነትን አይፈራም። ህወሃት እውነትን ስለሚፈራ ገና ድክ ድክ የሚሉ ነፃ ሚዲያዎችን ያለ ምንም ማወላወል ሊደመስሱ የሚሸቀዳደሙትን ይሾማል። ጀግና ነፃ ሚዲያን የሚፈራበት ምንም ምክንያት አይኖረውም። ጀግና ነፍሰ ገዳይ አይደለም። ህወሃት ህፃን ነብዩን የመሰሉ እንቦቀቅላዎችን ግንባር ግንባራቸውን ብለው ለመግደል የማይራሩ ጨካኞችን ይሾማል። ጀግና ሌብነትን ከልቡ ይፀየፋል። ህወሃት ግን ሌብነትን የሚፀየፉትን ሳይሆን የድሃ ንብረት ሰርቆ ሃብት ማካበትን እንደ ብልጠት የሚቆጥሩ ደካሞችን ጄኔራል እያለ ያሰማራል።
በዚህ በጥቅምት ወር የተሾሙት 6 የጦር አበጋዞች ለሹመት ሲታጩ የትምህርት ዝግጅታቸውና ብቃታቸው፤ ለአገራቸው ያደረጉት የላቀ አስተዋፅዖ፤በውጊያ አውድማ ያሳዩት ጀግንነት ታይቶ ነው የሚል ወሬ ከህወሃት መንደር ተሰምቷል። ህወሃቶች እና ደጋፊዎቻቸው ይሄን ለማመን አይቸገሩም። የእነዚህ ቡድኖች ዋና መለያ የገዛ ውሸታቸውን እውነት ነው ብለው አምነው ጥሩ እንቅልፍ መተኛት የሚችሉ መሆናቸው ነው። የገዛ ውሸቱን እውነት ነው ብሎ የሚያምን ግለሰብ ብርቱ የሆነ የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ የወደቀ መሆንኑ የስነ-አዕምሮ ተማራማሪዎች ይናገራሉ። ህወሃቶችም ብርቱ በሆነ የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ ለማየት የዕለት ተዕለት ውሸቶቻቸውን እና የሚፈፀሙትን ፀያፍ ድርጊቶች ማየት በቂ ይሆናል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል በጥቂት በዘረ ሃረጋቸውና በቤተሰብ ክር በተሳሰሩ ወንበዴዎች እጅ ወድቋል። በእነዚህ ዘራፊዎች የሚመራ የሠራዊት ኃይል የህዝቡን ዲሞክራሲያዊ መብት ማስከበር አይቻለውም። የጦር አበጋዞቹ የአገሪቷን አንጡራ ሃብት እየዘረፉ ከገነቧቸው ህንፃዎች በየወሩ የሚሰበስቡትን ገንዘብ የሚጠይቅ ለህዝብ ወገንተኛ የሆነ መንግስት እንዲመሰረት ምንም ፍላጎት አይኖራቸውም። ለእነዚህ ጦር አበጋዞች ነፃነት፤ ፍትህ፤ እኩልነት እና እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚባሉ ነገሮች ያሸብሯቸዋል። እነዚህንም ጥያቄዎች ያነሳ አሸባሪ ተብሎ የዚህን ምድር ሥቃይ እንዲያይ ይደረጋል።ይሄ ቡድን ሥልጣን ላይ እስከቆየ ድረስ ነፃነት ፤የህግ የበላይነት፤ እኩልነት የሚባሉ እሴቶች በኢትዮጵያ ይሰፍናሉ ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው።
በመጨረሻም ተራው ወታደር እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነፃነቱን ተገፎ ለምንና ለማን እንደሚገልና እንደሚሞት ሳያውቅ በገዛ ወገኖቹ ላይ እየተኮሰና የንፁህ ደም እያፈሰሰ እንደሚኖር እያየን ነው። ተራው ወታደር ጋምቤላ ሂዶ ያገኘውን ሁሉ የሚገድለው ለምንድ ነው? ኦጋዴን ሂዶ የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚፈፅመው ለምንድ ነው? ጉራፋርዳ ወርዶ የመዥንግሮችን ደም የሚያፈሰው በምን ምክንያት ነው? ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲን አስፍነናል ከተባለ ይሄ ሁሉ ውጊያ ምንጩ ምንድ ነው? ሠራዊቱ ለእነዚህና ለመሰል ጥያቄዎች በቂ መልስ መፈለግ ይኖርበታል።ምንም ትርጉም በሌለው ውጊያ ውስጥ እየሄደ የንፁህ ደም ማፍሰሱን ለማቆምና ነገ በወንጀል ከመጠየቅ ራስንም ለማዳን ሠራዊቱ ራሱን ከዘረኞቹና ከዘራፊዎቹ የጦር አበጋዞች መለየት ይኖርበታል።ከእርሱ በሞራልም ሆነ በትምህርት ደርጃቸው ከማይሻሉ ጄኔራል ተብየዎች ራሱን ለይቶ ለነፃነት፤ ለፍትህ እና ለእኩልነት ከሚታገሉ ኃይሎች ጎን እንዲሰለፍ ጥሪያችንን አሁንም እናስተላልፋለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Sunday, October 26, 2014

የእንግሊዙ ጠ/ሚ የአቶ አንዳርጋቸው የሞት ፍርድ እንዳይፈጸም ጠየቁ

October 26,2014
“ክቡር ጠ/ሚ አባታችንን ከሞት ያድኑልን”  የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጆች
Andargachew Tsige.jpg2የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን በእስር ላይ በሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ከአምስት አመታት በፊት የተጣለው የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንዳይሆንና በቆንስላ ሰራተኞች መጎብኘት እንዲችሉ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በግላቸው በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ከትናንት በስቲያ ዘገበ የአቶ አንዳርጋቸው ልጆች አባታቸውን ከሞት እንዲታደጉላቸውና ከእስር ተፈትተው ዳግም የሚገናኙበትን መንገድ በማመቻቸት በኩል ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው የሚጠይቅ ልብ የሚነካ ደብዳቤ እንደላኩላቸው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን፣ የልጆቹን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ለጠቅላይ ሚንስትር ሃይለማርያም ደብዳቤ መላካቸውን አስታውቀዋል፡፡
የእንግሊዝ የስራ ሃላፊዎች በእስር ላይ የሚገኙትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በቋሚነት መጎብኘት እንዲችሉ ግፊት ቢያደርጉም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት በጎ ምላሽ እንዳልሰጡ ለልጆቹና ለእናታቸው በሰጡት ምላሽ የገለጹት ዴቪድ ካሜሩን፣ ከዚህ በፊት የተደረገው ጥረት ውጤታማ አለመሆኑን በማጤን በግላቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደብዳቤ መላካቸውን አመልክተዋል፡፡የእንግሊዝ መንግስት የቆንስላ አባላት አንዳርጋቸው ጽጌን በቋሚነት መጠየቅና ማማከር የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችና መንግስታቸው ሲቃወመው የቆየው የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንደማይሆን ማረጋገጫ እንዲሰጥ በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን የገለጹት ዴቪድ ካሜሩን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለ ማርያም ለደብዳቤያቸው በጎ ምላሽ እንደሚሰጧቸው ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል፡፡
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጅ የሆነችው የ7 አመቷ ምናበ እና መንታ ወንድሟ ይላቅ፣ ለጠቅላይ ሚንስትር ዴቪድ ካሜሩን በላኩት ደብዳቤ፣ “አባታችን ልጆቹን የሚወድና የሚንከባከብ መልካም አባት ነው፡፡ አባታችንን ከእስር ለማስፈታት ምንድን ነው የሚያደርጉልን?” በማለት መጠየቃቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ የመጀመሪያ ል©cW የ15 አመቷ ህላዊት በበኩሏ፣ “አባታችን በጣም ናፍቆናል፡፡ እባክዎት በቅርብ ጊዜ መልሰው ወደ ቤታችን ያምጡልን” በማለት ስሜቷን እንደገለፀች ዘገባው ጠቁሟል፡፡

Hailemariam Desalegn responds to UK PM David Cameron on the Andargachew Tsege case

October 26,2014
Late Friday, Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn gave a brief response to UK prime minister David cameron who pleaded for the life of imprisoned rebel leader Andargachew Tsege.

Mr. Cameron has reportedly “written personally” to Desalegn requesting that Mr Tsege be saved from death penalty. In response to local media questions, Mr Desalegn said he can not “interfere with the legal proceedings” facing Tsege in Ethiopia.
Mr Desalegn also revealed that the prosecution has received “new and updated evidence” that Mr Tsege and his Ginbot7 organization is actively engaged in terrorist activities against the Ethiopian government. He is reportedly referring to a recent article by US based website “Ethiomedia” which interviewed Ginbot7 Chairman Berhanu Nega this week. Mr Berhanu told Ethiomedia that Ginbot7 is training its militia in Eritrea in order to fight the Ethiopian government.
Andargachew-Tsige1
Desalegn said Tsege has been given a defense lawyer, though his chances of winning are “very low.” But Mr Desalegn advised London to “review its policy” of giving asylum and rewarding citizenship to individuals and groups engaged in violent anti-goverment activities in Africa. He mentioned the ONLF rebel group example, whose leadership resides in the city suburbs of London. In 2007, ONLF rebels in southeast Ethiopia admitted murdering over 70 Ethiopian and chinese mine workers. Over the years, the ONLF rebels have also been accused of assassinating many somali-Ethiopians and bombings that killed civilians, including children. The Ogaden-Somali community in London provides most of the funding for ONLF rebels.
Mr Desalegn said Mr Tsege might still become eligible for reduced prison sentence (presidential pardon) in 2015 if the court decides to convict him.