Wednesday, August 12, 2015

አለቃዎ ሳይሆን ቅን ህሊናዎ የሚያዝዎትን በመፈፀም መልካም ዜጋ ይሁኑ!

August 12, 2015
def-thumbመልካም ዜጋ ማለት ምን ማለት ነው?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ በርካታ መጻሕፍት መፃፍ ይቻላል፤ መሠረተ ሀሳቡን ግን በጥቂት ዓረፍተ ነገሮች ማቅረብ ይቻላል።
መልካም ዜጋ ኢፍትሃዊ ተግባር ሲፈፀም “እኔ ምናገባኝ?” አይልም። መልካም ዜጋ “ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ”፤ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶም አይብቀል”፤ “እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም” እና በርካታ መሰል ምሳሌዎችን አይሰማም። መልካም ዜጋ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ቢሆን ከነፃና ቅን ህሊናው ጋር ታርቆ ይኖራል።
የህወሓት አገዛዝ፣ መልካም ዜጋ ማለት የመንግሥት ሥልጣን የያዘን ማንኛውም አካል ማክበርና በታማኝነት ማገልገል ተደርጎ እንዲተረጎምለት ይሻል። ፍትህ የሚያዛባ መንግሥትን መቃወም የመልካም ዜጋ አቢይ ተግባር መሆኑ የዘመናችን ወጣት እንዳይገነዘብ ያደርጋል። በተለይ ባለሙያዎች የሚያገለግሉትን አገዛዝ ባህርይ እግምት ውስጥ ሳያስገቡ የተቀጠሩበትን ሥርዓት በታማኝነት ማገልገል የዜግነት ግዴታቸው አድርገው እንዲወስዱት ይወተውታል።
ኦስካር ግሮኒንግ ( Oskar Groening)የዘጠና አራት ዓመት ሽማግሌ ጀርመናዊ ነው። በጀርመን የሂትለር አገዛዝ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንፁሃን የተፈጁበት አሽዊትስ ካምፕ ውስጥ የሂሳብና ጽህፈት ሠራተኛ ነበር። ኦስካር ግሮኒንግ አንድም ሰው አልገደለም፤ አንድም ሰው አልገረፈም። እሱ ሂሳብ ነው የሠራው። ሆኖም በደል ሲፈፀም አይቶ “ምናገባኝ” ብሎ አልፏልና ከብዙ ዓመታት በኋላ ተከሶ በቅርቡ የ4 ዓመታት እስር ተፈርዶበት በሁለት እግሮቹ መቆም በማይችልበት በ 94 ዓመቱ በእርጅናውና በመጦሪያው ዘመን ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ፊት ተዋርዶ እስር ቤት ወርዷል።
በአንፃሩ ኦስካር ሽንድለር (Oskar Schindler) በጀርመን ናዚ ወቅት ሂትለር ይመራው የነበረው የናዚ ፓርቲ አባልና ሰላይ ነበር። ሆኖም ግን የሥርዓቱን ኢሰብዓዊነት ሲረዳ እዚያው የናዚ ፓርቲ ውስጥ ሆኖ አለቆቹ ያዘዙትን ሳይሆን ቅን ህሊናው ያዘዘውን በምስጢር መሥራት ጀመረ፤ በዚህም የ 1200 ሰዎችን ሕይወት ታደገ። ከጦርነቱ በኋላ ኦስካር ተከብሮ የኖረ በርካታ የክብር ስሞችና ሽልማቶች የተሰጠው በመልካም አርዓያነቱ የሚጠቀስ ሰው ሆነ።
በአገራችንም በአምስት ዓመታቱ የፋሽስት ወረራ ወቅት ስመ ጥር የውስጥ አርበኞች ነበሩ። ከነፃነት በኋላ ባንዶች እንኳን በውስጥ አርበኝነት ለመጠራት ያደርጉት የነበረውን እሽቅድድም ልብ በሉ።
በህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴግ፣ ደህዴግ እንዲሁም አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ ያላችሁ ወገኞች ኦስካር ግሮኒንግን ወይንስ ኦስካር ሽንድለርን መምሰል ትፈልጋላችሁ? በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ነገ የምትዋረዱበትን ሥራ መሥራት ነው የሚበጃችሁ ወይስ ዛሬ ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ እየኖራችሁ ነገ ደግሞ ልጆቻችሁና የልጅ ልጆቻችሁ የሚኮሩበትን ተግባር መፈፀም ትፈልጋላችሁ? በአገዛዙ የስለላ ድርጅቶች ውስጥ ያላችሁ ወገኖች ስማችሁን በመልካም ማስጠራት አትሹምን?
ልቦና ያላችሁ ወገኖቻችን ሆይ! መልካም ዜግነት ሎሌነት አይደለም። መልካም ዜግነት ለቅን ህሊና ታማኝ መሆን ነው። መልካም ዜግነት ሲመች በገሀድ፤ ሳይመች በምስጢር ኢፍትሃዊነትን መዋጋት ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በማናቸውም መንገድ በአገዛዙ የፓለቲካ፣ የጦርና የፓሊስ ተቋማት፤ በስለላም ይሁን በሌላ የሲቪል ሙያ የተሰማራችሁ ወገኖቻችን የታዘዛችሁትን ሳይሆን ቅን ህሊናችሁ የሚጠይቃችሁን በመሥራት ኢፍትሃዊ፣ ፋሽስታዊና ዘረኛ የሆነውን የህወሓት አገዛዝን እንድታዳክሙ ጥሪ ያቀርብላችኋል። በአገዛዙ ውስጥ ሆናችሁ እያለም የምትሠሩት ለሀገርና ለትውልድ የሚጠቅም በርካታ ሥራ አለ። የአገዛዙን ምስጢራዊ ሰነዶች ለአርበኞች ግንቦት 7 እንዲደርስ ማድረግ፤ አሊያም በማኅበራዊ ሚዲያዎች (ለምሳሌ ፌስ ቡክና ቱተር) ማሰራጨት ትልቅ ዋጋ ያለ ሥራ ነው። የህወሓት ፀረ-አገር እና ፀረ-ሕዝብ ፕሮጀክቶችን ማሰናከል ሌላ ትልቅ ሥራ ነው። በነፃነት ታጋዮች ላይ የሚደረጉ ዱለታዎችን ማክሸፍ ሕይወት አድን ሥራ ነው። ድርጅቶቹ ውስጥ ሆኖ ድርጅቶቹን ማዳከም የመልካም ዜግነት ግዴታ መወጣት ነው።
በሥርዓቱ ውስጥ ሆነው ኢፍትሃዊነትን ለማጋለጥ እና ሥርዓቱን ለማዳከም ለሚጥሩ ወገኞች አርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ ክብር አለው፤ ደህንነታቸው እንዲጠበቅም የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል። ፀረ ኢትዮጵያ እና ፀረ ሰው የሆነውን የህወሓትን ሥርዓት ለመጣል እና በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲ፣ እኩልነትና የሀገር አንድነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከሥርዓቱ ውስጥም ውጭም የሚደረገውን ትግል እናፋፍም።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Sunday, August 9, 2015

በባህር ዳር ቀበሌ 11 ወጣቶችና በፖሊሶች መካከል ግጭት ተፈጠረ * አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል አለመተማመኑ ስር ሰዷል

August 9,2015
Photo File
Photo File
አርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ እንደዘገበው የባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 አባይ ማዶ ወጣቶች አንድ አካባቢ ላይ ተሰባስበው በመጫወት ላይ እያሉ ፖሊሶች ድንገት መጥተው “ለምን አንድ ላይ ተሰብስባችሁ ቆማችሁ?” በማለት አምባጓሮ በመፍጠራቸው ነበር ግጭቱ የተነሳው፡፡

ፖሊሶቹ ወጣቶችን ከቆሙበት በኃይል አባረው ወደየቤታቸው ለማስገባት ሲሞክሩ ወጣቶቹ በፖሊስ ላይ የአጸፋ እርምጃ በመውሰዳቸው አንድ ፖሊስ ለከፋ ጉዳት እንደተዳረገ ታውቋል፡፡ የህወሓት አገዛዝ ለስልጣኑ የሚያሰጋውን የህብረተሰብ ክፍል እየመረጠ ትጥቅ ማስፈታቱን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አምባገነናዊ ስርአት የግብአተ መሬት ጊዜውን በጥቂቱም ቢሆን ያራዝምልኛል ብሎ ከነደፋቸው እቅዶች መካከል አንዱ የሆነውን ህዝቡን ትጥቅ የማስፈታት ተግባር በታች አርማጭሆ ገበሬዎች ላይ በተለየ ሁኔታ በግፍ የሚያስታጥቀው የህብረተሰብ ክፍል ያለው ዘረኛው የህወሓት ቡድን በአማርኛ ተናጋሪው ገበሬ ላይ አሁን እየፈፀመ የሚገኘው የትጥቅ ገፈፋ ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ሲያደርገው የቆየው መሆኑ ይታወቃል፡፡
አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል ውስጥ ተፈጥሮ የቆየው አለመተማመን ስር ሰዶ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ታወቀ፡፡

ለሰላም ማስከበር ተልኮ ወደ ደቡብ ሱዳን ሊሄዱ የተመለመሉት የአየር ሀይል አባላት የደቡብ ሱዳን ጉዞ ተሰርዞ ወደ ሱማሊያ እንደሚሄዱ ስለተነገራቸውና በግምገማ በመወጠራቸው ምክንያት በርካታ አብራሪዎች፣ ቴክኒሻኖች እና ሌሎች የተለያዩ ክፍሎች ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በመሆኑም በአየር ሀይል ውስጥ አለመተማመኑ ገደቡን አልፎ አብራሪዎች ለልምምድ በሚያበሩት አውሮፕላን ውስጥ የህወሓት አባላት ከጎን እንዲቀመጡ እየተደረገነው፡፡ በተጨማሪም አብራሪዎች ነዳጅ በሚሞሉበት ጊዜ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ከዘ- ሐበሻ የተወሰደ

Woyane and the Million dollar hacking scheme

August 8, 2015
by Yilma Bekele
You can take your family and friends on a Caribbean cruise. May be buy a one way ticket to Las Vegas and hope to turn it into four million. Who needs a return ticket when you are going back to wherever you came from by private plane? There is one little thing wrong with this scenario. The million Dollar is not your money. You are entrusted by the people to spend it wisely. Can we start again?
One Million US is about twenty Million Ethiopian Bir. I am sure that kind of money can build a library or two. You can purchase a sturdy pump to use both for irrigation or bring water to the village. Imagine how many teachers can be trained with that kind of dough? The list is endless for a poor country like Ethiopia. At the moment the proud nations exists on handout from foreigners. The budget is balanced by heavy subsidy from European Union and generosity of few rich countries. Our country is on Welfare.
The rogue and amateur Ethiopian government hackers attempts
So think hard before you spend that hard earned money collected from the poor citizen. How would you spend one million US if you are the Ethiopian government? Remember that you are aware of the sad state of education, the lack of potable water, the dismal state of the health care, the shortage of food among other problems – how would you allocate that twenty Million Bir?
Yes it is a little confusing on one hand to say the economy is growing double digits and on the other hand stretch your hand out since you cannot pay your bills without the kindness of others. So the Diaspora all over the world that sends money to family, the Diaspora that build condominiums on illegally obtained land and the foreign sponsors are the lifeblood of Woyane. Of course they pooh pooh the Diaspora contribution and hide the foreign alms.
How to spend the million plus US dollars is not a theoretical question. The dictatorship under the late dead PM Banda Meles Zenawi was faced with such issue. Well to tell you the truth by the mere fact that they control the purse they are forced to make a choice on how to spend the money the collected through taxing the citizen, selling Coffee and cereal and other revenues at their disposal. A normal government will submit the budgeting and the Parliament discusses the proposal invite opinions from the citizens and approves or disapproves based on the needs of the constituents that elected them and the welfare of the country as a whole.
It does not work like that in ‘democratic’ Ethiopia. The parliament is a bunch of illiterate and weak individuals recruited and appointed by the TPLF Party. The voting part is for foreign consumption as evidenced by the testimony given by President Obama. The TPLF Party based on the Tigrai core group but purporting to be representing all of Tigrai controls the Parliament (Legislative), Executive (Co-Prime Minister, Foreign Minister, Defense Minister, Federal Affairs Minister, State Security, National bank, etc) and the Judiciary. No one ethnic group has controlled Ethiopia like this before!
So it looks like Meles Zenawi and Debretsion Gebremichael decided to spend our money by hiring a British (Gamma Group) and an Italian (Hacking Team) security companies to hack into the computers, mobile phones and Skype accounts of Ethiopians. How did we find that out. Surprise, surprise the Italian company company ‘hacking Team’ itself was hacked! More than 300GB of documents was made public and our Ethiopia was in the midst of this. We might be poor, we might be technologically backward but TPLF was willing to spend a million dollars to purchase this offensive technology to spy and get the upper hand. The hacking was announced via Hacking Team’s own compromised Twitter account, what a sweet revenge!
So what did Meles and Debretsion use this ‘offensive technology’? They were caught red handed by researchers at the Citizen Lab—a digital watchdog group at the University of Toronto’s Munk School of Global Affairs.
The first hacking attempt against ESAT was targeting the Amsterdam ESAT studio. An individual using the name Yalfalkenu Meches sent an article but when they tried to open the attachment they noticed it was prepared in a different format. Citizens Lab was able to show using Skype logs from the targeted computer. Here is a brief illustration:
Ethiopian government hacking attempts
The alert ESAT manage (may the Gods bless him/her) did not open the file and confronted the individual. Here again is the exchange from Skype.
Ethiopian government hacking attempts
The Woyane bastard did not give up but tried a new trick.
Ethiopian government hacking attempts
That was formated to look like a word document but it was not. According to Citizens Lab ‘A user who opened the file saw a blank Word document, which quickly closed itself. The document exploited a bug in Microsoft Windows (CVE-2012-015844) to run a program that downloaded and executed a file’
If you don’t succeed the second time try again seems to be the way the Ethiopian Information Network Security Agency (INSA) Debretsion’s outfit operates. Thus their third attempt was aimed at ESAT’s studio In Virginia USA.
Ethiopian government hacking attempts
ESAT and Citizens Lab were already aware of Woyanes workings and this time they confronted Debretsion’s lackey and here is the conversation.
Ethiopian government hacking attempts
Ethiopian government hacking attempts
Citizens Lab of course made their investigation official. When asked by reporters an Ethiopian Embassy spokesperson Tesfaye Welde claimed ‘Ethiopia did not use and has no reason to use any spyware or other products provided by Hacking team or any other vendor inside or outside Ethiopia.’ Today thanks to smart hackers that hacked this enemy of Ethiopia Company we have the original thank you email from dictator Meles and a copy of the million dollars he paid so he could buy more time and abuse our people and nation. That is one million dollars that could have gone to schools, libraries and clinics.
The second time they were caught when they tried to hack ESAT’s Managing Director Ato Neamin Zelek’s computer using word document by hijacking an email address they have obtained previously.
Ethiopian government hacking attemptsAto Neamin promptly forwarded the suspicious email to Citizens Lab. Lo and behold it was no other than Debretsion of of INSA knocking again. It seems like the morons have used the the same command as before and the servers are shown to be registered to Ethio Telecom. The hacking Team’s Operations Manager was heard to have said ‘(Citizens Lab) found the source of the attack because these geniuses used the same email address they had used in the previous attack to send the doc with the exploit.’ so much for Woyane smartness,
Today the TPLF minority regime is being forced to answer to charges of illegal spying on foreign soil. In the US it is considered a Federal crime and the court has allowed the case to continue. There will be many others that will come out pretty soon. Citizens Lab is looking at more computers and doing a deep investigation suitable for the courts.
We Ethiopians have long ago understood the cheap, criminal and shameful character of Woyane. We are not surprised by anything coming out of Arat Kilo. To the outsider it is surprising how a small poor country would find itself using twenty first century technology to monitor its own people. They are always surprised how brazen and reckless Woyane’s are. Again to an Ethiopian there is no surprise here. Woyane kills in broad daylight and demands the victim’s family pay for the bullet. Woyane is so used to such outrageous conduct inside the country it is only natural they would try the same abroad too.
They have hacked the computers of a vast majority of those they suspect are working to dismantle their criminal enterprise. They are are so paranoid they think all of us are the enemy and they will spend millions so they could uncover ‘plots’ find ‘compromising’ information for blackmail or coerce individuals to work for their criminal enterprise. It is a temporary solution for a deep seated problem.
My dear Ethiopian family and friends as you can see what has been said by many about the destructive and criminal nature of the people in power has not been a figment of someone’s imagination. I wrote this so you can see clearly what the independent experts have found about the regime and its practice.
It has been said plenty of times that “woyane cannot be reformed.” It has been carrying out this criminal activity since its inception. It is too late to talk of reform. Removal by any means without prejudice is the only option left to the peace loving people of Ethiopia. The gallant effort that is being waged by our patriots is the only medicine to get rid of this virus.
The current smart way of fighting TPLF led by Patriotic Ginbot7 is the last chance we have as a country before they turn our homeland into another Iraq, Libya, Syria or Yemen. That is what is awaiting our country if we do not come together to get rid of the common enemy. Every Ethiopian is a hidden patriot ready to strike at Woyane when the time arrives. Be a patriot and love your mother.
I have included links that would make a good reading before you go to bed.

Saturday, August 8, 2015

ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል

August 8,2015
አሜሪካ ሃሳቡ ቀርቦላታል ተብሏል
four front map

ኢህአዴግ በአራት አቅጣጫዎች የጦር ጥቃት ለመሰንዘር ማሰቡ ተሰማ፡፡ ይኸው ሃሳብ ለአሜሪካ ቀርቦላታል፡፡
በቅርቡ የተጠናከረ እንቅስቃሴ የጀመረው የአርበኞች ግንቦት ፯ ኃይል በተደጋጋሚ በሚያወጣው መረጃ በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ማድረሱን በይፋ ቢገልጽም ኢህአዴግ ጥቃቱን በቀጥታ ለማስተባበል እስካሁን አልወደደም። ይሁን እንጂ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ “ህዝብ አስፈቅደን” ሲሉ ኤርትራን እንደሚወጉ ይፋ አድርገዋል። አብዛኞች እንደሚስማሙበት ዛቻው ግጭት ስለመኖሩ የሚያረጋግጥ ነው። በሌላው አንጻር ደግሞ ይህንን የሃይለማርያም ንግግር የኤርትራው ሹም በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የተለመደ የህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያና ዛቻ በማለት አጣጥለውታል፡፡
የግጭቱን ደረጃና በኢህአዴግ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ኢሳት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን መውቀሰና ማስፈራራት የጀመረው ኢህአዴግ፣ ቀጣናው ሊተራመስ እንደሚችል ስጋቱን ገልጾ ኤርትራን ለመደብደብ የሚያስችለውን ፈቃድ ስለማግኘቱ ጎልጉል መረጃ ደርሶታል። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) አራተኛዋ ሹም ዊንዲ ሼርማን ግንቦት ፯ን በስም በመጥቀስ በተቃወሙ ማግስት የባለሥልጣኗን የድጋፍ ቃል አስመልክቶ ቴድሮስ አድሃኖም በኢህአዴግ በኩል ያለውን ውለታ ሲናገሩ “ለምንከፍለው ዋጋ መጠን ተመጣጣኝ ክፍያ ነው” ሲሉ ውስጡ በርካታ የፖለቲካ “ጥሬ ሃብት” የሞላበት አስተያየት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ሰጥተው ነበር።
የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ፕሬዚዳንት ኦባማ አዲስ አበባ በነበሩበት ወቅት የህወሃት ሰዎች ይህንኑ ጉዳይ በዋናነት አንስተው ነበር። ኢህአዴግ በሶማሊያ እያበረከተ ላለው ተግባር መሰናክል ተደርጎ የቀረበው የኤርትራ ተቃዋሚዎችን የመርዳት ጉዳይ እልባት እንዲበጅለት አሜሪካ ድጋፍ እንድትሰጥ የጠየቀው ኢህአዴግ፣ አሜሪካ ያሉ የከፍተኛ ተቃዋሚ አመራሮች ገደብ እንዲጣልባቸው ተማጽኗል። አሜሪካ ኢህአዴግ “አሸባሪ” ብሎ የሚፈርጃቸውን በሙሉ በሽብርተኛነት በመፈረጅ የመን የተጫወተችውን አይነት ሚና እንድትደግም ተጠይቃለች። ጥያቄው የቅዠትም ሆነ የምር፣ የግንቦት ፯ አመራሮች ነቅለው አስመራ መግባታቸው ጥያቄውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል የሚሉ አሉ
አሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄዎች ስለመቀበሏ ያልጠቀሱት የመረጃው ባለቤቶች፣ ኤርትራ ውስጥ መተራመስ ሳይፈጠርና ክልሉና ቀጣናው ሳይናጋ ጥንቃቄ የተሞላበት ርምጃ ቢወሰድ አሜሪካ ተቃውሞ እንደማይኖራት ማረጋገጫ መስጠቷን አመልክተዋል። ይህ አቋም ኦባማ አዲስ አበባ ከመሄዳቸው በፊት በተለያዩ ደረጃዎች ተመክሮበት ከስምምነት የተደረሰበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር አቶ ስብሃት ነጋ “ከኤርትራ ጋር የሚካሄድ ውጊያ ጥንቃቄ ይጠይቃል” ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።
በዚሁ መነሻ ኢህአዴግ በጎንደር፣ በሱዳን ድንበር፣ በአፋርና በትግራይ የተለያዩ ግንባሮች ድንገተኛ ማጥቃት ለመሰንዘር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። ወቅቱ የዝናብ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ ለዚሁ ጥቃት ሠራዊቱ የሚወጋው “ተቃዋሚ የሆኑ የራሱን ወገኖች ሳይሆን ሻእቢያን ነው” በሚል የማነቃቂያ ስራ እየተሰራ እንደሆነ የመረጃው ሰዎች ተናግረዋል። በድጋሚ የመሥራቱ ጉዳይ ገና ባይታወቅም ይህ አካሄድ በባድመ እንደተደረገው የወኔ ማነቃቂያ እና የውጊያ ሞራል ማነሳሻ ለማድረግ ታስቦ በጥናት የተደረገ ለመሆኑ የመረጃው አቀባዮች ያስረዳሉ፡፡ አያይዘውም “ጦርነቱ ኢህአዴግ ካሰበው ውጪ ባንድ በኩል ከተሰበረ በጦሩ ውስጥ የሚገኙ የሌሎች ኅብረተሰብ ክፍል አባላት የሆኑ ወታደሮች ሊከዱና የተቃዋሚ ኃይሎችን ሊቀላቀሉ ይችላሉ” የሚል ስጋት ስለመኖሩ ሪፖርት መቅረቡን ይጠቅሳሉ።
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያለው ሚዛን ያልጠበቀ የኃላፊነት ደረጃና የህወሃት አባላት ያላቸው የተጋነነ የበላይነት በመሃል አገር ከሚፈጸመው ረገጣ ጋር ተዳምሮ የተከማቸው ቅሬታ ሊፈነዳ ይችላል የሚል ጥርጣሬ እንዳለም እነዚሁ ክፍሎች ያስረዳሉ።
ኢህአዴግ የትጥቅ ትግል አውጀው ኤርትራ ከመሸጉና መሣሪያ አንግበው ትግል እያደረጉ መሆናቸውን ይፋ ካደረጉ ግንባሮች ሁሉ በድርጅታዊ አቅሙ ከፍተኛ የሚባለውን (ደሚት/ትህዴን) የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን እስካሁን በሽብርተኛነት አለመፈረጁ ይታወቃል።
ከ ጎልጉል ድህረገጽ የተወሰደ

Friday, August 7, 2015

የፕሬዚዳንት ኦባማ የአፍሪካ ኅብረት ንግግርና እንደምታው

August 7, 2015
def-thumbየዩ ኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ሐምሌ 21 ቀን 2007 ዓም አዲስ አበባ ውስጥ በአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ያደረጉት ንግግር በርካታ ቁምነገሮችን የያዘ በመሆኑ አንጽዖት ሊሰጠው እንደሚገባ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
ፕሬዚዳንቱ በዚህ ንግግራቸው የአፍሪቃን በተለይም ደግሞ የአገራችንን ችግሮች ነቅሰው አሳይተዋል። ሰብዓዊ መብቶች ሰው በመሆናችን ያገኘናቸው በመሆኑ በቆዳችን ቀለም፣ በተወለድንበት አካባቢ፣ በምንናገረው ቋንቋ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያቶች ሊሸራረፉ የማይገቡ መሆኑን በመግለጽ “ሁላችንም እኩል ተወልደናል” በማለት ዘረኞችን አፍ የሚያዘጋ ኃይለቃል ተናግረዋል። “ሁላችንም ከአንድ ግንድ የበቀልን ነን፤ ሁላችንም አንድ ቤተሰብ ነን፤ ሁላችንም አንድ ጎሳ ነን” ካሉ በኋላ በዓለም ያለው አብዛኛው ችግር ይህንን መረዳት አለመቻላችን፤ ራሳችንን በእያንዳንዳችን ውስጥ ማየት አለመቻላችን ነው ብለዋል።
ይሁን እንጂ በብዙ የአፍሪቃ አገሮች፣ ዜጎች ነፃነታቸው የተገፈፈ መሆኑን፤ ምርጫ መኖሩ ብቻ ዲሞክራሲ ሰፈነ ማለት አለመሆኑ አብራርተዋል። ጋዜጠኞች፣ የተቃውሞ ፓለቲካ መሪዎችና ግንባር ቀደም ተሳታፊዎች፣ የሲቪክ እንቅስቃሴዎች መሪዎችን በእስር ቤት እያጎሩ ወይም በነፃነት እንዳይቀሳቀሱ እያደረጉ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አደረግን የሚሉ አገሮች መኖራቸው ለመግለጽ ኢትዮጵያን በዋቢነት ጠርተዋል።
ፕሬዚዳንት ኦባማ የሰላምና የደህንነት ጉዳይ ምን ያህል አሳሳቢ መሆኑን በሰፊው ከገለጹ በኋላ ለሰላም ሲባል ነፃነትን መንፈግ ሁለቱንም ሊያሳጣ የሚችል መሆኑም አስገንዝበዋል።
እድገትን በማፋጠን ዜጎችን ከድህነት ለማውጣት አዲስ አስተሳብ ያሻል፤ ለአዲስ አስተሳሰብ ደግሞ በነፃነት ማሰብ፤ ድምፃቸው የሚሰማ ዜጎች መኖር እና የሰብዓዊ መብቶች መከበር ቁልፍ ጉዳዮች መሆናቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል። የአፍሪቃ መሪዎች ሥልጣን ላለመልቀቅ የሚሄዱትን ርቀት በማንሳት ተሳልቀውበታል፤ ሙስናም የልማትና የመልካም አስተዳደር ፀር መሆኑን አስምረውበታል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ፕሬዚዳንት ኦባማ ይኸ ቀራቸው በማይባል ሁኔታ በአህጉራችን በአፍሪቃ በተለይ በኢትዮጵያ የሰፈነው ክፉ አገዛዝ መተቸታቸው፤ ይህንን እዚያው የአፍሪቃ መዲና በሆነችሁ አዲስ አበባ ተገኝተው መናገራቸው በበጎ ይመለከተዋል። እሳቸው ያነሷቸውን ቁም ነገሮችን አድምጠው ማስተካከያዎችን የሚያደርጉ ገዢዎች ኑረውን ቢሆን ኖሮ የኛ ትግል ባላስፈለገ ነበር። ችግሩ መስማት እንጂ ማዳመጥና መተግበር የማያውቁ ገዢዎች የሰፈኑብን መሆኑን ነው።
ስለሆነም፣ አርበኞች ግንቦት 7: ፕሬዚዳንት ኦባማ በአፍሪቃ ኅብረት ንግግራቸው ሀቁን አብጠርጥረው በመናገራቸው የተሰማውን አድናቆት ይገልፃል፤ በዚሁ አጋጣሚ ደግሞ በንግግራቸው ያነሷቸው ቁምነገሮችን መደመጣቸውና በተግባር መተረጎማቸውን እንዲከታተሉ አበክሮ ይጠይቃል።
የፕሬዚዳንት ኦባማ ንግግር በሀቅ ላይ የተመረኮዘ በመሆኑ የህወሓት ሽማምንት የተከፉ ቢሆንም የኢትዮጵያን ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እውነታ የመቀየር ኃላፊነት የእኛው የኢትዮጵያዊያን ኃላፊነት መሆኑን በመረዳት፤ ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲና ለአገር አንድነት ግድ ያለን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ተባብረን አገራችን ከዘረኛውና ፋሽስታዊ ህወሓት አገዛዝ ነፃ የማውጣት ተጋድሎዓችን አጠናክረን እንድንቀጥል አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Tuesday, August 4, 2015

በሙስሊም እንቅስቃሴ መሪዎች ላይ የተሰጠውን ፍርደገምድል ፍርድን እናወግዛለን!

August 4, 2015
def-thumbየህወሓት አገዛዝ የሚዘውረው የይስሙላ ፍርድ ቤት ዛሬ ሀምሌ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. በሙስሊም ወገኖቻችን መሪዎች ላይ ፍርደገምድል ውሳኔ ሰጥቷል። በዚህ ውሳኔ መሠረትም የእምነት መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው በሰላማዊ በሆነ መንገድ የጠየቁ ወገኖቻችን መሪዎች እስከ 22 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።
ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄዎቻቸው ሰላማዊ በሆነ መንገድ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ሥርዓቱ ያደረገውን ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን ተቋቁመው “ድምፃችን ይሰማ!” የሚል አቤቱታ ከማቅረብ የዘለለ አንዳችም የኃይል እርምጃ ወስደው አያውቁም። ሆኖም “በደል ደርሶብኛልና ልሰማ” ብሎ አቤቱታ ያቀረበ ሕዝብ መሪዎችን እስከ ሃያ ሁለት ዓመታት በእስር መቅጣት የአገዛዙ እብሪትና ማናለብኝነት አጉልቶ የሚያሳይ ተግባር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህን ፍርደገምድል ውሳኔ አጥብቆ ያወግዛል።ይህ ፍርደገምድል ውሳኔ የተሰጠው ፕሬዚዳንት ኦባማ በአገራችን መዲና ተገኝተው “ለሰላም ሲባል ነፃነትን ማፈን ሁለቱንም ያሳጣል” ባሉ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሆኑ አገዛዙ የሚሰማ ጆሮ የሌለው መሆኑ የሚያረጋግጥ ሆኗል።
የሙስሊም መሪዎች በእስር ላይ በነበሩት ጊዜ በምርመራ ስም ተደብድበዋል፤ ክብራቸው ተደፍሯል፤ የተለያዩ ዘግናኝ ሰቆቃዎች ተፈጽሞባቸዋል፤ የሀሰት ዶክመንታሪ ፊልሞች እንዲሰራጩ ተደርገው ስማቸውን ለማጥፋት ሙከራ ተደርጓል።
በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የደረሰው በደል ሃይማኖት ሳይለይ በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰ በደል ነው፤ መፍትሄ የምናገኘውም በጋራ በምናደርገው ትግል ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና የአገር አንድነት የሚጠብቅ የመንግሥት ሥርዓት ስናቆም ነው። ከዚህ በመለስ የሚገኝ መፍትሄ የለም። የእምነት መብቶች የሚከበሩት ሰብዓዊ መብቶች ሁሉ ሲከበሩ እንደሆኑ “በድምፃችን ይሰማ” ሥር የተሰባሰቡ ወገኖቻችን ይረዳሉ ብለን እናምናለን።
አርበኞች ግንቦት 7 ሙስሊም ወገኖቻችን ለዓመታት ያለመታከት ያካሄዱትን ትግል ያደንቃል። ከእንግዲህ ደግሞ እጅ ለእጅ ተያይዘን፤ ተደጋግፈን በመታገል ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ለሁላችንም የምትመች አገር እንድንገነባ ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

Ethiopia hands lengthy prison terms to Muslim activists

August 4, 2015
(Reuters) – Aug 3 An Ethiopian court sentenced 17 Muslim activists on Monday to prison sentences ranging from seven to 22 years on charges they plotted to create an Islamic state in the majority Christian country.Ethiopian Muslims Arbitration Committee
A journalist for a Muslim newspaper was also sentenced for conspiring with the activists, the court in Addis Ababa said.
The defendants, who all denied the charges, were arrested in 2012 on charges of plotting to stage attacks to create an Islamic state in Ethiopia, which has a sizable Muslim minority.
The sentencing comes as Ethiopia faces increasing scrutiny from human rights groups that have regularly accused it of arresting activists, journalists and bloggers to stamp out dissent. The government dismisses the allegations.
The activists were arrested during protests between 2011 and 2013 by Muslims – a rare event in this tightly-controlled country – who accused the government of interference in their affairs. Officials have denied this.
The protesters accused the government of trying to impose a little-known Islamic sect called Al Ahbash on the country’s Muslim population as a moderate bulwark against the hardline Islam it believes is being spread by extremist preachers.
Ethiopian Muslim leaders say their community follows traditional Sufi-inspired Islam and not any radical movement.
The court sentenced four of the activists to 22 years in jail, five to 18 years, another five to 15 years and four defendants to seven years behind bars. One in the last group was the journalist working for the Muslim newspaper.

Saturday, August 1, 2015

የናትናኤል ፈለቀ ማስታወሻ – ጥቂት ስለ ማዕከላዊ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

August 1, 2015
ናትናኤል ፈለቀ (ከቂሊንጦ እስር ቤት) – ምንጭ ዞን9 ፌስቡክ ገጽ
An economist by training and a human right activist by interest.
ናትናኤል ፈለቀ
ይህንን ጽሁፍ ስጽፍ ዓላማዬ ማዕከላዊ ያሉ ሥራቸውን አክብረው የኢትዮጵያውያንን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ የሚሰሩ ጥቂት ፖሊሶችን (ምናልባትም በአንድ እጅ ጣቶች ተቆጥረው የሚያልቁ መርማሪዎችን) ለማበረታታት አይደለም፡፡ ይህን ዓላማ በሌላ ጽሁፍ እመለስበት ይሆናል፡፡ ለነገሩ ሥራቸውን አክብረው የሚሰሩ ባለሙያ ፖሊሶች የኔ ማበረታታትን የሚፈልጉ አይደሉም፡፡ ያሉበት ደረጃ ላይ ለመድረስ በኃላፊነት ማሰብ የቻሉ ስለሆኑ፡፡
ስለዚህ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በተቋሙ ውስጥ ኢትዮጵያ የምትተዳደርባቸውን ሕጎች ለማክበር (የተላለፉትን ለይቶ ለማስቀመጥና በስህተት የተጠረጠሩትን ነጻ ለማውጣት) ሳይሆን የአገዛዙን ዕድሜ ለማርዘም የሚሰሩትን አብዛኞቹን ሙያቸውን የማያከብሩ ፖሊሶች ‹‹ምርመራ›› ሴራቸውን እንዴት እንደሚፈትሉ ለማሳየት፣ ቢያንስ ሌላ ስልት እስኪፈጥሩ ድረስ በሀገሪቷ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ኢትዮጵያውያን አንዴ በተቋሙ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሊገጥማቸው የሚችለውን የተንኮል መረብ ለማስረዳት እና ቀድሞ ለማዘጋጀት ያሰበ ነው፡፡
እውነት ለመናገር እነዚህ የስርዓቱ ጠባቂ ሎሌዎች የህዝብን ደህንነት ለአደጋ የሚያጋልጥ ወንጀልን እና ወንጀለኞችን ለይተው አውቀው ፍትህ እንዲያገኙ አድርገው ጭራሹንም አያውቁም ማለት አልችልም፡፡ ስለዚህ አሁን የማብራራው ጉዳይ ለወንጀለኞችም መዘጋጃ ሊሆን እንደሚችል አምናለሁ፡፡ ነገር ግን ወንጀለኞች ከፍትህ እንዲያመልጡ ጠብታ ውሃ ማቀበል አልፈልግም፡፡ አንድ ነጻ ሰው ባልሰራው ወንጀል ከሚቀጣ መቶ ወንጀለኞች ቢያመልጡ ይሻላል የሚለው የህግ መርህ የበለጠ አቋሜን ያስረዳል፡፡
ሁለት ማሳሰቢያዎች አሉኝ፤ አንደኛ፡-እኔ ተይዤ ማዕከላዊ እስክገባ ድረስ ልታሰር እንደምችል አስቀድሜ ባውቅም ሊጠብቀኝ የሚችለውን የ‹‹ምርመራ›› ሂደት (የሴራ መረብ የበለጠ ይገልጸዋል) አጽንዖት ሰጥቼ አላሰብኩበትም፡፡ የምርመራው ሂደትን ተንተርሼ የማነሳቸውን ሀሳቦች የተረዳሁት በምርመራ ውስጥ ካለፍኩ በኋላ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ይህንን ጽሁፍ የሚያነቡ ሰዎች እኔ በፍርሃት ያላደረኳቸውን ነገሮች እንዲያደርጉ (በምርመራ ሂደት) የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ሁለተኛ ይህንን ጽሁፍ በሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል እና ሀሳቡን ሕገ-መንግስታዊ ድንጋጌዎች በሚፈቅዱት መሰረት በነጻነት የሚገልጽ ሁሉ ጊዜ ሳይሰጥ ቢያነበው እመክራለሁ፡፡
ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ሀሳብ የአቃቤ ህግ ምስክር ከተሰማ በኋላ በብይን የተለቀቁ ሙስሊም ወንድሞች መጻፋቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ያ ጽሁፍ የተሻለ የተደራጀ ነው ብየ ስለማስብ እንዲነበብ እጋብዛለሁ፡፡ በተጨማሪም ስርዓቱን የሚደግፉ ሰዎች ይህንን ጽሁፍ በማንበብ ወንጀለኞች ከሚጠቀሙበት ለተሻለ አላማ ያውሉታል ብዬ ስለማስብ ሁለቱም ባያነቡት ይሻላቸዋል፡፡
ወደ ዋናው ሀሳብ ልግባ፤ ከተያዝኩ በኋላ በነበሩ የመጀመሪዎቹ ቀናት ውስጥ የነበሩት‹‹ምርመራዎች›› እውነቱን እና የማውቀውን ብቻ በመናገር እራሴን ነጻ ማውጣት እንደምችል መተማመኛ መስጠትን ያለሙ ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ሚያዝያ 18/2006 (በተያዝኩኝ በማግስቱ ቅዳሜ) የነበረውን ምርመራ ም/ሳጅን መኮንን በተረጋጋ ሁኔታ የምርመራው ሂደት በመከባበር እንደሚቀጥል፣ ልክ እኔ የዕለት ስራየን ለማከናወን ሙያ እንደሚጠይቀው ያክል የፖሊስ ምርመራም ተመሳሳይ እንደሆነ፣ በቁጥጥር ስር የዋልኩት ተጠርጥሬ ብቻ እንደሆነ እና በምርመራው ሂደት ወንጀል አለመፈጸሜ ከተረጋገጠ በነጻ ወደቤቴ እንደምሄድ ነበር ያስረዳኝ፡፡ ይንቁናል የሚል ስሜት አስቀድሞ ስለሚያድርባቸው ተቋሙን እና እራሳቸውንም ከፍ የሚያደርግ ነገር በነዚህ የመጀመሪያ ‹‹የምርመራ››ቀናት ይናገራሉ፡፡
‹‹ይህ የወረዳ ጣቢያ አይደለም፡፡ የክልልም አይደለም፡፡ ይህ የፌደራል ወንጀል ምርመራነው፡፡ ሚኒስትር ደረጃ የደረሱ የመንግስት ባለስልጣናት ሳይቀር እዚህ ተመርምረዋል›› ነበር ያለኝ ም/ሳጅን መኮንን በአጽንኦት፡፡ ከዚህ ገለጻ በኋላ ነበር ስለህይወት ታሪኬ በመጠየቅ ቃል የመስጠት ሂደቱን የጀመርኩት፡፡
ማስታወሻ- 1. ቃል ያለመስጠት መብት
ቃሌን ያለመስጠት መብት ስላለኝ ቃሌን አልሰጥም ለማለት መጀመሪያ መብቱ እንዳለ ማወቅ ይጠይቃል፡፡ በወቅቱ ይህ መብት እንዳለኝ ማወቄን እጠራጠራለሁ፡፡ አውቅ ከነበረም ግን በፍጹም ትዝ አላለኝም፡፡ ቃል አለመስጠት አንድ ለምርመራ ሂደቱ ተባባሪ አለመሆንን ማሳያ ነው፡፡ ለተቋሙ የጭቆና መሳሪያ ስለመሆኑ በቂ ማስረጃ እንዳለ አምነን ተጨማሪ ማረጋገጫ ዕድል (benefit of the doubt) መስጠት የማንፈልግ ከሆነ ይህ ትክክለኛው አማራጭ ይመስለኛል፡፡ ከግምት መግባት ያለበት ቃል በመስጠቱ ሂደት ውስጥ ፖሊስ በእርግጠኝነት ስህተት መስራቱ አይቀርም፡፡ ይህም የማይቀረው ክስ ሲመጣ ተቋሙን ማጋለጥ እንደ ስልት የሚወሰድ ከሆነ እንደማስረጃ ሊቀርብ ይችላል፡፡ ለምሳሌ በኛ ጉዳይ የቀረበብን ክስ የሽብር ቡድን በኅቡዕ አደራጅተዋል በሚል ሲሆን ሁላችንም ቃል ስንሰጥ የተጠየቅነው እና ስናብራራ የነበረው ግን በይፋ ስንጽፍበት እና ዘመቻዎቻችንን ስናካሂድበት ስለነበረው ዞን 9 ነው፡፡
አቃቤ ህግ በክሱ እያለ ያለው የከሰስኳችሁ በመጻፋችሁ እና መብትን የሚጠይቁ ዘመቻዎችን በማድረጋችሁ (በአጠቃላይ ከዞን-9 ጋር በተያያዘ) ሳይሆን ሌላ የህቡዕ ቡድን መስርታችሁ ለሽብር ዓላማ ስትንቀሳቀሱ ስለነበር ነው፡፡ የሰጠነው ቃል እና ክሱን ለመደገፍ የቀረቡት ማስረጃዎች ግን ስለ ዞን-9 አውርተው አይጠግቡም፡፡ በመጀመሪያዎቹ ቀናት የሚነግረውን ‹‹ተቋሙ ገለልተኛ ነው፣ ሰዎችን ወንጀለኛ ለማድረግ ሳይሆን እውነትን ፈልፍሎ አግኝቶ ነጻ ሰውን ወደቤቱ ይሸኛል›› የሚለውን ዕምነት በቀላሉ ማስረጽ ከቻሉ የሚቀጥሉት ጥርጣሬ ወደመዝራት ይመስለኛል፡፡ በቀላሉ ያሉትን የማያምኑ ከሆነ ግን የተጠርጣሪውን በራስ መተማመን ለመሸርሸር ህገ-ወጥ ተግባራቸውን ይቀጥላሉ፡፡
‹‹ምርመራ›› በጀመርኩ በአራተኛው ቀን የተከሰተው ይሄው ነው፡፡ ሚያዝያ 21/2006 ዓ.ም ምሽት ድረስ ‹‹በምርመራው›› ሂደት ውስጥ ስሳተፍ የነበረው በሙሉ የራስ መተማመን ነበር፡፡ ለምሳሌ ም/ሳጅን መኮንን፣ ም/ሳጅን እቴነሽ፣ እና ሳጅን ፈይሳ በነበሩበት ታስሬ ‹‹እየተመረመርኩ›› ያለሁት ሀሳቤን በነጻነት ለመግለጽ ባለመፍራት ነው፡፡ ያኔ ‹‹ፖሊስ ለህዝብ የሚሰራ ተቋም ነው የምትሉትንም አላምንም፡፡ በአሁኑ ሰዓት ፖሊስ እንደ ተቋም እየሰራ ያለው አገዛዙን ስልጣን ላይ ለማቆየት ነው›› ብያቸዋለሁ፡፡
ከላይ በጠቀስኩት ቀን ማታ ግን ሌላ ሊከሰት እንደሚችል የማውቀው፣ ግን ከምር ያልተዘጋጀሁበት ነገር ተከሰተ፡፡ ምሽት 1፡00 አካባቢ የተጀመረው ‹‹ምርመራ›› ቶሎ ኃይለ ቃል ወደመሰንዘር እና ዛቻ ተለወጠ፡፡ በወቅቱ ም/ሳጅን መኮንን፣ የመጀመሪያ ቀን ፍርድ ቤት የወሰደን እና በየመተላለፊያው ሳገኘው ጭምር ቤተሰብ እንዲያገኘን መብት አለን፣ ፍርድ ቤት አዝዞልን ሳለ ለምንድነው የማታገናኙን እያልኩ ስጠይቀው የቆየሁት ሳጅን ምንላርግልህ እና ማዕረጉን የማላስታውሰው ፀጋየ (በቅጽል ስሙ ጥጋቡ) የሚባል መርማሪ ነበሩ፡፡ የ‹‹ምርመራ››ውም ዋነኛ አጀንዳ የዞን 9 ድብቅ ግብ እና የውስጥ የስራ ክፍፍል (መዋቅር)በተመለከተ ነበር፡፡ በሁለቱ ጉዳይ ላይ እውነተኛው የማውቀው መልስ ‹‹መዋቅር የለውም›› የሚለው ነበር፡፡ ዞን 9 ድብቅ ግብም መዋቅርም ኖሮት አያውቅም፡፡ ሳጅን ምንላርግልህ መልሴ አላጠገበውም፡፡ ‹‹እኔ እንደሱ እንዳልመስልህ (የእኔን ጉዳይ በዋነኛነት ወደያዘው ም/ሳጅን መኮንን እየጠቆመ) አለቅህም! ሽባ ነው ማደርግህ! ልብስህን አስወልቄ ሳልለጠልጥህ እውነቱን ብትነግረኝ ይሻልሃል!›› የሚሉ ዛቻዎች ደረደረ፡፡ እኔ ግን መዋቅሩን በተመለከተ ስራ ለማቅናት ሲባል ምክረ ሀሳብ ቀርቦ እንደተወያየንበት፣ ነገር ግን ሀሳቡ ውድቅ እንደተደረገ ከማስረዳት በቀር የምጨምረው የማውቀው እውነት አልነበረም፡፡ ም/ሳጅን መኮንን እና ፀጋየ (ጥጋቡ) በየተራ ክፍሉን ለቀው ከወጡ በኋላ ሳጅን ምንላርግልህ ከወንበሩ በመነሳት ምቾት በሚነሳ ሁኔታ ከተቀመጥኩበት ፊት ተጠግቶኝ ቆሞ ጥያቄዎችን ይደረድር ጀመር፡፡
ጥያቄ፡- ‹‹ለምንድነው እነ ርዕዮትን ብቻ የምትጠይቁት?››
መልስ፡- ‹‹ኢትዮጵያውያን ስለሆኑ እና የታሰሩት በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ነው ብለን ስለምናምን፡፡››
ጥያቄ፡- ‹‹(በቁጣ) ባንክ የዘረፈውስ ኢትዮጵያዊ አይደለም? ለምንድነው ሌላውን ወንጀለኛ የማትጠይቁት?››
በእውነት እዚህ ጋ ሳቄ መጥቶ ነበር፡፡ በርግጥ የታሰረን ሁሉ ከተቻለ መጠየቅ ለህሊና የሚያስደስት ስራ ነው፡፡ እግዜርም ይወደዋል፡፡ ግን ርዕዮትን ስጠይቅ እንዲሰማት የምፈልገው፣ ትግሏ ዋጋ እንዳላጣ እና እንዳልተረሳች ነው፡፡ ይህም ትንሽም ቢሆን ብርታት ይጨምርላታል ከሚል ተስፋም ጭምር ነው፡፡ ተመሳሳይ ነገር የባንክ ዘራፊ እንዲሰማው በፍጹም አልፈልግም፡፡ ጥያቄው ቀጠለ፣
‹‹ዝዋይ ለምን ሄዳችሁ?››
‹‹እነ ውብሸትን ለመጠየቅ››
‹‹አትዋሽ! በቀለ ገርባን ለመጠየቅ ነበር?››
‹‹አዎ በቀለንም ለመጠየቅ ነበር፡፡››
‹‹በቀለ ምን እንደሚል ታውቃለህ? ለምን እንደታሰረ ታውቃለህ? ኦሮምኛ ትችላለህ?››
‹‹አልችልም››
‹‹በቀለ እኮ የሚለው ኦሮምኛ የማይችሉ ሰዎች በሙሉ ይታረዱ ነው፡፡››
ስለ በቀለ ገርባ የማውቀው ጥቂት ነገር ከሚለኝ ጋር ፍጹም የሚጣጣም ስላልነበር የፊቴን መለዋወጥ መቆጣጠር አልቻልኩም፡፡ ፊት ለፊቴ ተደንቅሮ የጥያቄ ዝናብ ሲያወርድ የነበረው ሳጅን ምንላርግልህ አሁን ማድረግ የሚፈልገውን ለማድረግ በቂ ምክንያት አገኘ፡፡ የመጀመሪያዋን ጥፊ ሰነዘራት፡፡ መብቴን እየነካ እንደሆነ ስነግረው ‹‹ይህንን ነው አይደል ፈረንጆቹ ወስደው የሚያሰለጥኗችሁ?›› በማለት ስራውን ቀጠለ፡፡ ድብደባው እዚያ ቤት ከሚፈጽሙት ሰቆቃዎች (torture) አንጻር ትንሽ ቢሆንም አሸነፈኝ፡፡ አሁን የሚጸጽቱኝንም ቃላት ተናገረኝ፡፡ ከውጭ የነበሩት ሁለቱ መርማሪዎች ድብደባ ሲፈጸምብኝ በነበረበት ወቅት በመሐል መጥተው ገላጋይ ሆነው ነበር፡፡ ምንላርግልህ ግን ለያዥ ለገናዥ አስቸገረ፡፡
ማስታወሻ፡-2. መርማሪዎች አንድ አላማ ነው ያላቸው
ሁለትና ከዚያ በላይ ሆነው ሲመረምሩ የትኛውንም ማመን አያስፈልግም፡፡ በኋላ ላይ ከሌሎች ተጠርጣሪዎች ጋር ሳወራ የተረዳሁት ይህ የተለመደ አሰራር መሆኑን ነው፡፡
ሌላ ተጠርጣሪ ሲመረመር ሳጅን ምንላርግልህ ገላጋይ ሌላኛው ደግሞ እምቡር እምቡር ይላል፡፡ ከዚያም ፀጋየ (ጥጋቡ) እኔ ላይ ሲያደርግ እንደነበረው ገላጋይ የሚሆነው መርማሪ ‹‹እኔ ችግር ውስጥ እንድትገባ አልፈልግም፤ ለምን እውነቱን አትነግረንምና ራስህን አትጠብቅም? ደግሞ ዘጠኝ ሆናችሁ ለሰራችሁት ስራ አንተ ብቻህን ለምን ትጎዳለህ? ሌሎቹ እኮ እየተናገሩ ነው፤ አይደለም ዘጠኝ ሰው የሚያውቀው ነገር ይቅርና ለሌላ አንድ ሰው የነገርከው ነገር እኮ ሚስጥር መሆኑ ያበቃል›› የሚሉ ማግባቢያዎች በመደርደር ምስኪን ምስኪን ሊጫወት ይሞክራል፡፡
የዛን ምሽት ምርመራ ሲጠናቀቅ የሁለት ሰዓት ማሰቢያ ጊዜ ተሰጥቶኝ የዞን 9 ግብ ምን እንደሆነ እና የመዋቅራችንን እያንዳንዱን የስራ ዘርፍ እንዳስታውስ የቤት ስራ ተሰጥቶኝ ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ተመልሼ እንደምጠራ ተነግሮኝ ነበር ወደ ማረፊያ ቤት ውስጥ የተመለስኩት፡፡
በተለምዶ ሳይቤሪያ የሚባለው ማረፊያ ቤት ባለአንድ ፎቅ ህንጻ ሲሆን የታችኛው ወለል በኮሪደር ተከፍሎ በግራና በቀኝ አምስት አምስት ክፍሎች አሉት፡፡ ኮሪደሩ መሀል ላይ አንድ የግድግዳ ሰዓት ተሰቅሏል፡፡ የመጀመሪያ ሰሞን ልብ ስላልኩት ሰዓት የማውቀው ምርመራ ክፍል ካሉት ሰዓቶች በመነሳት በግምት ነበር፡፡ ከሳጅን ምንላርግልህ በተሰጠኝ የቤት ስራ መሰረት ከምሽቱ አምስት ሰዓት ሲል ተመልሼ ወደ ምርመራ እጠራለሁ፡፡ ከምርመራ ከተመለስኩ ጀምሮ በአዕምሮዬ ሲመላለስ የነበረው ነገር ተጨማሪ መልስ ልሰጣቸው እንደማልችል እና በዚህ ምክንያት ተመልሼ ከሄድኩ በኋላ የሚደርስብኝ ሰቆቃ ማብቂያ ምን እንደሚሆን ማሰብ ነበር፡፡ ቀኑን ሙሉ በምርመራ በማሳለፌ ድካም የነበረብኝ ቢሆንም እንቅልፍ ሊወስደኝ ግን አልቻለም፡፡ ራሴን አረጋግቼ በተሰጠኝ ሁለት ሰዓት እረፍት መውሰድ ብፈልግም ምንም ዓይነት ድምጽ በሰማሁ ቁጥር አምስት ሰዓት የሆነ እየመሰለኝ እባንን ነበር፡፡ እነምንላርግልህ ግን አልፈለጉኝም፡፡ አይነጋ የለም ሌሊቱም ነጋ፡፡ ጠርተው ቢደበድቡኝ ይሻል ይሆን እንደነበር እንጃ!
ማስታወሻ፡- 3. እራስን አረጋግቶ በቂ እረፍት መውሰድ
መርማሪዎቹ መቼም ቢሆን ምርመራ ጨርሰናል ደህና እደሩ ብለው አይሸኙም፡፡ ሁል ጊዜ‹‹በኋላ እንገናኛለን፤ አስብበት›› ብለው ነው የሚጨርሱት፡፡ አንዳንድ ጊዜ በቀጠሮ መሰረት ምርመራው ይቀጥላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የውሃ ሽታ ይሆናሉ፡፡ በቀጠሮ መሰረት ብጠራም ባልጠራም ያለችውን ጊዜ በቂ እረፍት ለማድረግ መጠቀሚያ ማድረግ የሚያዋጣው አማራጭ ነው፡፡ ከድብደባው በባሰ የሚጎዳው የማያቋርጥ ጭንቀት እና የእረፍት እጦት ነው፡፡ ከአሁን አሁን ወደምርመራ ተጠራሁ ብሎ መጨነቅ ጥሪውን የማዘግየትም የማስቀረትም አቅም የለውም፡፡ ‹በኋላ እንገናኝ› የምትለዋ ቀጠሮ እረፍት መንሻ ዘዴ ናት፡፡
በመቀጠል የምርመራው ዓላማ የነበረው ከጓደኞቼ ያገኟቸውን መረጃዎች በመጠቀም ብዙ እንደሚያውቁ ጥያቄ የሚጠይቁትም ከኔ ይምጣ ብለው እንጂ ሁሉ ነገር ላይ መረጃ እነዳላቸው ለማሳመን መጣር ነበር፡፡ በወቅቱ የእኔ ምላሽ የነበረው ሁሉንም የሚያውቁ ከሆነ ለኔ ጥሩ እንደሆነ እና ምንም ጥፋት እንደሌለብኝ ከዛ በላይ ማስረጃ እንደሌለ የሚያስረዳ ነበር፡፡
ማስታወሻ፡-4. አብረው የሚሰሩ ጓደኛሞች ወጥ መልስ ለመስጠት አስቀድመው ስምምነት ላይ መድረስ
ስለ አንድ ጉዳይ ሁለት ጓደኛሞች የተለያየ መልስ ከሰጡ ሰቆቃው ሁለቱም ላይ የጠና ነው፡፡ አንደኛው ወደ ሌላኛው መልስ የሚጠጋ ነገር እስካልተናገረ ድረስ ሁለቱም ይሰቃያሉ፡፡ በኛ ምርመራ ወቅት አስቀድመን ምንም የምንደብቀው ወይንም የምንዋሸው ነገር እንዳይኖር ስንነጋገር ስለከረምን በተነጋገርነው መሰረት የአንዳችን ቃል ከሌላችን የጎላ ልዩነት አልነበረውም፡፡
በጓደኞች መሀከል ክፍተት ለመፍጠር ሙከራ ያደርጋሉ፡፡ ለምሳሌ ለበፍቄ ‹‹ናትናኤል እኮ እውነቱን ነግሮናል፡፡ በፍቃዱ ነው አብዮት እና አመጽ እንድንጠራ የሚገፋፋን ብሏል፡፡ አንተ ለምንድነው እንዲህ የምትደብቅላቸው እነሱ እውነቱን እየተናገሩ›› ብለውታል፡፡ ቀዳዳ ካገኙ ቅያሜ በመፍጠር ከጓደኛሞች መሀል አንዱን መስካሪ ለማድረግ ይጥራሉ፡፡ ማስፈራሪያዎች በታጨቁበት ምርመራ መሀል እራሴን ነጻ ማውጣት ቀላሉ አማራጭ እንደሆነ ደጋግመው ይነግሩኝ ነበር፡፡ ፀጋዬ (ጥጋቡ)፣ ም/ሳጅን መኮንን እና ኢንስፔክተር አሰፋ እየመረመሩኝ በነበሩበት ወቅት ፀጋዬ ተራ ስድቦችን እና ዛቻዎችን ከሰነዘረ በኋላ በዛው አፉ እኔን ማቆየት እንደማይፈልጉ እና የሚፈልጉትን ካልኩላቸው ወዲያውኑ ወደቤቴ እንደሚሸኙኝ አባቴንም መንከባከብ እንደሚሻለኝ ሲነግረኝ ነበር፡፡ የአባቴ ጤንነት እንዳሳሰበኝ ስለገባቸው ባገኙት አጋጣሚ ለምርመራው ግብአትነት ይጠቀሙበት ነበር፡፡
አብዛኛው የምርመራ ጊዜ በተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና ተደጋጋሚ መልሶች የሚያልፍ ነው፡፡ ይህም ምርመራዎችን እጅግ አድካሚ እና አሰልቺ ያደርጋቸዋል፡፡ ዝርዝር ጉዳዮችን በተደጋጋሚ በመጠየቅ ከምሰጠው መልስ ላይ ልዩነት ለማግኘት ይህንንም ተጠቅሞ ሌላ አዲስ ነገር ለማውጣጣት ይጥሩ ነበር፡፡ የተሳካላቸው ግን አይመስለኝም፡፡ በተቻለኝ አቅም ቀዳዳ ሳገኝ የማምንበትን አቋም ከመናገር ወደኋላ አላልኩም፡፡ የማውቀውን ለማካፈልም እንደዚያው፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 39ን የሚቃወም መርማሪ አግኝቼ ለምን ልክ ነው ብዬ እንደማምን አስረዳኋቸው፡፡ በተለያየ ጊዜ የወሰድኳቸው የበይነ መረብ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችንም በተመለከተ ያብራራሁለትም መርማሪ ነበር፡፡
ማስታወሻ፡-5. በተገኘው አጋጣሚ አቋምን ማስረዳት
መርማሪዎቹ በተደጋጋሚ ስለተነገራቸው ብቻ የሚያምኑት ብዙ ነገር አለ፡፡ ኢህአዴግ ትግል ላይ በነበረበት ወቅት ጭራቅ ተደርጎ ይሳል እንደነበረው አሁንም የነጻነት ትግል እያደረጉ ያሉትን ሰዎች እንደ ሰው በላዎች የሚቆጥሯቸው መርማሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ በነዚህ መርማሪዎች ይህን ከተማ (አ.አ) ተወልዶ ያደገ ሰው ፖለቲካ ውስጥ ቦታ የለውም፡፡ ተደጋግሞ ሲነሱልኝ ከነበሩት ጥያቄዎች መሀል ይህ መንግስት ምን በድሎሃል (በግል) እንዴት እንደዚህ አይነት አቋም ልትይዝ ቻልክ? የሚለው እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ መልሴ ግን አጭር ነበር፡፡ ነጻነቴን ዋጋ እሰጠዋለሁ!!
ከምክትል ሳጅን መኮንን ጋር በነበረን ጊዜ የተረዳሁት ስለ አቋሞቼ በጥልቀት ማወቅ ቢፈልግም እንደ ጦር እንደሚፈራቸው ነው፡፡ ገና ማስረዳት ስጀምር ቶሎ ብሎ ‹ወደ ጉዳያችን እንመለስ፣ ዳግም ወደ አንተ ልትስበኝ ነው?› ይለኝ ነበር፡፡ ሌሎችም መርማሪዎች ተመሳሳይ ፍላጎት አይቸባቸዋለሁ፡፡ አንድ የማይረሳኝ ምሳሌ ከኢሜሌ ላይ የተገኘውን የዜና መጽሔት በተመስጦ ሲያነብ የነበር አንድ መርማሪ አለቃቸው ድንገት ቢሮውን ከፍቶ ሲገባ ወረቀቱን በድንጋጤ ወርውሮታል፡፡ ከዚህ መገንዘብ የቻልኩት እነዚህን በአንድ በኩል መረጃ የተደፈኑ ሰዎች ሌላኛውን ጎን ማሳየት በሌላ አማራጭ የማያገኙት መረጃ ምንጭ መሆን ስለሆነ በምርመራ ወቅት እንደ አንድ ዓላማ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው፡፡
አልፎ አልፎ ከሌላ ቦታ የሚመጡ (ከደህንነት መስሪያ ቤት) መርማሪዎች ለመመለስ አደጋች የሆኑ ውስብስብ ጥያቄዎችን ከመጠየቃቸው ውጭ የሚጠየቁት ጥያቄዎች እዚህ ግባ የሚባሉ አይደሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ መርማሪዎች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች ለራሳቸውም ግልጽ አይደሉም፡፡ ጥያቄዎችን የሚያበጁት ከጀርባ ሆነው ምርመራውን የሚመሩት አለቆቻቸው ናቸው፡፡ አልፎ አልፎ ለመመለስ አደጋች የሚመስሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ፡፡ ለምሳሌ ሚያዝያ 27 ቀን (የአርበኞች ድል ቀን) ኢንስፔክተር አሰፋ እና አንድ የደህንነት ባልደረባ ሆነው ባካሄዱብኝ ምርመራ ወቅት አንድ አስቸጋሪ ጥያቄ ተነስቶ ነበር፡-
የደህንነት ባልደረባው፡- ‹‹ዞን 9 ምን ማለት ነው?››
መልስ ፡- ‹‹ዞን 9 ማለት ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን የተነጠቀ ታሳሪ ነው ለማለት የተጠቀምንበት ስም ነው፡፡››
‹‹እኔም የዞን 9 አባል (ነዋሪ) ነኝ ማለት ነው?››
‹‹አዎ!››
‹‹ጥሩ! ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን የተነጠቀ ከሆነ መቼ እና እንዴት ነው ዞን9 ነጻ የሚወጣው?››
ይህ ጥያቄ ትንሽ ለመመለስ አስቸጋሪ ነበር፡፡ በርግጥ እንደማነኛውም ግለሰብ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን መቼ ያገኛል ለሚለው ጥያቄ የራሴ አስተያየት ቢኖረኝም በዚህ ምርመራ ወቅት ሀሳቤን በነጻነት ብናገር የሚያመዝነው አደጋው ነበር፡፡ ስለዚህ ማለት የቻልኩት ዞን 9 የሚለውን ተምሳሌታዊ ስያሜ አምነንበት ብንጠቀምም የዞን 9 ነዋሪዎችን ነጻ ማውጣት ግን እንደ ግብ ያስቀመጥነው እና እንዲሳካም ኃላፊነት ወስደን የሰራንበት ጉዳይ እንዳልነበር ነው፡፡
አጠቃላይ የእስር ቤቱ የአያያዝ ሁኔታና የምርመራው አሰልቺነት በየዕለቱ መርማሪዎቹ ከሚነግሩኝ የራሳቸው እውነት ጋር ተደማምሮ ሊያሸንፈኝ ዳር ዳር ብሎ ነበር፡፡ ነገር ግን በተባራሪ የምንሰማቸው ጓደኞቻችን እና መታሰራችን የሚቆረቁራቸው ሰዎች የሚያደርጉት ሰላማዊ ሰልፍ እና የበይነ መረብ ዘመቻ ተጨማሪ የጥንካሬ ምንጭ ሆነውኛል፡፡ የማታዎቹ ምርመራዎች ለዚህ ምቹ ናቸው፡፡ ካስተዋልኩት የተረዳሁት የማታውን (የሌሊቱን) የምርመራ ጊዜ መርማሪዎቹ ለሚከፈላቸው ተጨማሪ ገንዘብ እና ስላመሹ መ/ቤቱ ለሚያቀርብላቸው ቆሎ እና ውሃ ካልሆነ በስተቀር አይፈልጉትም፡፡
በማታው ምርመራ ወቅት ቶሎ የመሰላቸት እና የኃይል እርምጃ ወደ መውሰድ ይሄዳሉ፡፡ ብዙ ማውራት አይፈልጉም፡፡ ስለዚህ አለቆቻቸው የሰጧቸው ጥያቄዎች ሲያልቁባቸው የተለያዩ ስፖርታዊ ቅጣቶች በማዘዝ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው አማካኝነት ጨዋታ (game) ይይዛሉ፡፡ ወይንም ሌላ ክፍል ምርመራ ላይ ካለ ጓደኛቸው ጋር በኢንተር ኮም ወግ ይይዛሉ፡፡ በተመርማሪዎች ላይ ያላግጣሉ፡፡ በማታዎቹ ምርመራዎች ወቅት ለሚነሱ ጥያቄዎች ረዘም ያሉ መልሶችን መምረጥ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ መልሶችንም በህገ-መንግስቱ ስለተፈቀዱ መብቶች፣ ስለ ተቋማት ነጻነት አስፈላጊነት፣ እና መሰል ፖለቲካዊ ጉዳዮች ወደ ማብራራት ማጠጋጋት፣ ከተቻለ የመርማሪዎቹን ቀልብ ለመሳብ እና ከሚወስዷቸው አላስፈላጊ የኃይል እርምጃዎች መከላከል ይቻላል፡፡
ማስታወሻ፡-6. አቤቱታ ማሰማት
የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ፍርድ ቤት በሚወሰዱበት ጊዜ ያለውን አጋጣሚ በሚገባ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በተለምዶ ፍርድቤት በፖሊስ የአያያዝ በደል ተፈጽሞብኛል ብሎ የሚያመለክት ሰው ከፍርድ ቤቱ መልስ ተመልሶ ማዕከላዊ እንደሚገባ ስለሚያውቅ የባሰአደጋ ለመቀነስ በሚል አቤቱታ ከማቅረብ ሊቆጠብ ይችላል፡፡ ነገር ግን አቤቱታውን አቀረበም አላቀረበም ሰብዓዊ መብቱን ከመረገጥ አይድንም፡፡ ልዩነቱ የሚሆነው የፍርድ ቤቱ መዝገብ ላይ የመብት ጥሰቱ ተመዝግቧል ወይስ አልተመዘገበም የሚለው ነው፡፡
እዚህ ላይ የምመክራቸውን ነገሮች ያለማድረግ ቁጭት በእኔ ብቻ ሳይሆን ብዙ ታሳሪዎች ላይ ያስተዋልኩት ነው፡፡ ያላደረግሁትን አድርጉ ብሎ የመጠየቅ ይሉኝታም ጽሁፉን ልጻፍ ወይስ ይቅርብኝ ብዬ እንዳንገራግር አድርጎኝ ነበር፡፡ ውስጤ ከሚብላላ ግን ጽፌው አንብቦ ቢያንስ አንድ ሰው የተለየ መንገድ ተከትሎ ጉዳት ቢቀንስ የተሻለ ነው የሚለው ሀሳብ የተሻለ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ሌሎቹም ጓደኞቼ ተመሳሳይ መንገድ አልፈዋል፡፡ የነሱንም የምርመራ ሂደት ይጽፉታል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እስከዛው ድረስ መታገስ ያልቻለ የሀገር ውስጥ ነዋሪ ግን ወደ ቂሊንጦ ጎራ ብሎ ከራሳቸው አፍ ጠይቆ መረዳት ይችላል፡፡ እኔ ቀረኝ የምለው ነገር ካለኝ በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ፡፡
ማስታወሻ፡-7. የማዕከላዊ ቤቶችን (ክፍሎች) ይተዋወቁ
ማዕከላዊ
በግቢው ውስጥ ሶስት የእስረኛ ማቆያ ቦታዎች አሉ፡፡ በተለምዶ ጣውላ ቤት፣ ሳይቤሪያ እና ሸራተን በመባል ይታወቃሉ፡፡ጣውላ ቤት አምስት ክፍሎችን በተርታ የያዘ ሲሆን የምርመራ ቢሮዎች ያሉበት ህንጻ ጀርባ ምድር ላይ ያሉ ክፍሎች ናቸው፡፡ እኛ ማዕከላዊታስረን በነበርንበት ወቅት ሶስቱ ክፍሎች ለሴት ተጠርጣሪዎች ማቆያ ሲሆኑ ቆርቆሮ መከለያ ተደርጎለት፣ ደግሞ የተቀሩት ሁለቱ ምስክርለመሆን የተስማሙ ወንድ ተመርማሪዎች ማቆያ ነው፡፡ ማሂ እና ኤዶም ከሶስቱ ክፍሎች በአንደኛው ከሌላ ሴት ታሳሪዎች ጋር እንዳይገናኙሁለቱ ብቻ ተለይተው ነበር፡፡ ጣውላ ቤት ፊት ለፊት የክፍሎቹ ወለል ጣውላ መሆኑ ነው ጣውላ ቤት የሚል ስያሜ ያሰጠው፡፡ ይህንንማቆያ ቤት አልፎ አልፎ ሂልተን በማለት የሚጠሩት ሰዎች ገጥመውኛል፡፡
ሳይቤሪያ የሚባለው የእስረኛ ማቆያ በቅዝቃዜው ምክንያት ነው ስሙን ያገኘው፡፡ ይህ ባለአንድ ፎቅ ህንጻ ምድር ላይየሚገኘው ማቆያ ቦታ በረጅም ኮሪደር የተከፈለ ሲሆን በግራና በቀኝ ከ2 ቁጥር እስከ 10 ቁጥር የተለጠፈባቸው አምስት አምስት ክፍሎች አሉት፡፡ 8 ቁጥር ከተለጠፈበት ውጭ ሌሎቹ ወጥ ክፍሎች ሲሆኑ 8 ቁጥር የተለጠፈበትን በር ተከፍቶ ሲገባ ግን ሌሎች ራሳቸውን የቻሉ አራት ክፍሎች አሉት፡፡ የበለጠ ቅጣት እንዲቀጣ የሚፈልጉት ተመርማሪ እነዚህ ሁለት ሜትር በሁለት ሜትር የሆነ ጨለማ ክፍል ውስጥ ያስሯቸዋል፡፡ ሳይቤሪያ የምርመራ ግለቱ እስኪሰክን ድረስ ተመርማሪዎች የሚቆዩበት ቦታ ሲሆን ሁሉም ክፍሎች ከኤሌክትሪክ መብራት ውጭ ምንም አይነት ብርሃን አይደርሳቸውም፡፡ የክፍሎቹ ግድግዳዎች ወለሉና ጣራው ከኮንክሪት የተሰራ ነው፡፡ ቀኑን ሙሉ ከውጭ ተዘግቶ የሚውለው ክፍል በቀን ለሶስት ጊዜ ያክል ይከፈታል፡፡
ሳይቤሪያ ውስጥ ያሉ ክፍሎች ጠዋትና ማታ በተራ በተራ እየተከፈቱ ተመርማሪዎች በጋራ ወደሚጠቀሙት ባለስድስት ክፍል ሽንት ቤት እና መታጠቢያ ቤት እንዲሄዱና ተጠቅመው እንዲመለሱ ለደቂቃዎች ፈቃድ ያገኛሉ፡፡ ለሌሎች ጥቂት ደቂቃዎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን ለማግኘት ይፈቀድልን ነበር፡፡ ፀሐይ የምናገኘው በጣውላ ቤት እና በህክምና ክሊኒኩ መሐከል ባለ ክፍት ቦታ ላይ ነበር፡፡ጣውላ ቤት ያሉት ክፍሎች በር ክፍት ስለሚሆን ከማሂ እና ኤዶም ጋር በዓይን እና በምልክት ብቻ እናወራ ነበር፡፡ የሳይቤሪያ ክፍሎች በየተራ በሳምንት አንድ ቀን የሚጸዱ ሲሆን ባለችን መታጠቢያ ጊዜም የምናገኘው በነዚህ ቀናት ብቻ በሳምንት አንዴ ነው፡፡
ሸራተን ለ12 ሰዓት ፀሐይ የሚገኝበት፣ ቲቪ የሚታይበት እና የሽንት ቤት እና የመታጠብ ፍላጎት ያለው ሰው የፈለገውን ማድረግ የሚችልበት ቦታ ነው፡፡ የምርመራው ሂደት ሲጠናቀቅ ቀለል ባለ ጉዳይ የሚመረመር ሰው ወይንም ደህና ባለስልጣን ዘመድ ያለው ሰው ሸራተን ሆኖ የማዕከላዊ ቆይታውን ያጠናቅቃል፡፡
በመጨረሻም አንድ እብሪተኛ መርማሪ በተናገረኝ ንግግር ማስታወሻየን ላጠናቅቅ፡፡ እንዲህ ነበር ያለኝ፣ ‹‹መንግስት ብዙ ዓይኖች እና ጆሮዎች አሉት፡፡ እናንተ ደግሞ ስታወሩ የነበረው በእኛው ስልክ፣ ከሀገር ስትወጡ የነበረው በእኛው በሀገራችን አየር መንገድ እና በቦሌ በኩል ነበር፡፡ እያንዳንዱ እንቅስቃሴያችሁን መረጃ አለን፡፡ አንተ አሁን እየደበቅህን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለአንተ አይጠቅምም፡፡ እኛ ምርጫ እንሰጥሃለን፡፡ ሕይወትህን ወደብርሃን መውሰድ የምትፈልግ ከሆነ ወደዚያው እንመራሃለን፡፡ አይ አልፈልግም የምትል ከሆነ ደግሞ መውጣት ወደማትችለው ድቅድቅ ጨለማ እንከትሃለን፡፡ ምርጫው የአንተ ነው፡፡››

Friday, July 31, 2015

ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ለምን ያስጨንቃቸዋል?

July 31, 2015
ሽብሬ ደሳለኝ
Andargachew Tsige is Ethiopianባለፉት 24 ዓመታት ወያኔዎች በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) ለውጥ ለማምጣት የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካ ድርጅቶች እና ፖለቲከኞች ከማዳከም አልፈው በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት ተጽኖ መፍጠር እንዳይችሉ አድርገዋቸዋል።

አብዛኛዎቹ ፖለቲከኞች የወያኔ አፈና ሲበረታ ከማምረር ይልቅ ፖለቲካውን እርግፍ አድርገው ይተውታል ወይንም ደግሞ ስደት ይወጡና ቀደም ሲል የተሰደደውን የኢትዮጵያ ስደተኛ ተቀላቅለው እንደ አብዛኛው ስደተኛ ቤተሰቦቻቸውን እና እራሳቸውን በኢኮኖሚ የማሻሻል ተግባር ላይ አተኩረው ይቀራሉ። ይህ እየተለመደ የመጣ አካሄድ ወያኔዎቹን ተመችቷቸው ኖረዋል፣ እነ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የጨዋታውን ህግ እስከቀየሩት ድረስ።

በርግጥም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ ወደ ፖለቲካው ሜዳ ያመጡት አዲስ የጫወታ ህግ ሰርቷል!
ወያኔ አዲሱን የጨዋታ ህግ ከጅምሩ አልወደደውም፣ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ኋይት ሃውስ ፊት ለፊት ሻማ ከማብራት ያለፉ እንዳይሆኑ ምኞቱ ነበር። ይህ አልሆነም።

አቶ አንዳርጋቸው እና ጓዶቹ ኢትዮጵያውያን የአሜሪካን ወይንም የእንግሊዝን መንግስት በመለመን ነጻነታቸውን እንደማይቀናጁ ይልቁንም ብረት አንስተው ወያኔን በሚገባው ቋንቋ የማነጋገር አስፈላጊነትን አስተማሩ፣ ወተወቱ፣ የመውጪያ መግቢያ ቀዳዳዎችንም አመላከቱ… ኤርትራ!

ወያኔ በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን ሲያዳፍን፣ ለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን እንደሚያማትር አልጠፋውም፣ ወያኔዎች የለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን በስራ ላይ ለማዋል ተባባሪ/ፈቃደኛ የጎረቤት ሃገሮች እንደሚያስፈልጉት ቀደም ብሎ መተንበዩ አልቀረም (ወያኔ ከደርግ መንግስት ጋር ባደረገው የሃይል ትግል ወቅት ሱዳን እና ሶማሊያ ዋንኞቹ መጠለያው ነበሩ)። ከሃገር ጥቅም ይልቅ ለመንበረ ስልጣኑ ቅድሚያ የሚሰጠው ወያኔ ለኢትዮጵያ አጎራባች ሃገሮች ሁሉ የሚጠይቁትን እየሰጠ (ለምሳሌ ሱዳን ከሃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ ይገባኛል የምትለውን የኢትዮጵያ መሬት ከወያኔ ተቀብላለች) በምላሹም ተቃዋሚዎቹን እንዳያስጠልሉ፣ አልፎ ተርፎም ተቃዋሚዎቹን እያደኑ እንዲያስተላልፉለት አግባባቸው። ይሁንና ይህ አካሄድ በጎረቤት ኤርትራ ሊሰራለት አልቻለም።

አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ አውርተው አልቀሩም፣ ከኤርትራ መንግስት ጋር የተሳካ ግንኙነት ፈጠሩ፣ ጦርም ማደራጀት ቻሉ፣ ቀደም ሲል ጀምሮ በኤርትራ መሬት ይንቀሳቀሱ በነበሩት ሃይሎች መካከልም መልካም እና መተማመን የሰፈነበት ግንኙነት እንዲኖር አስቻሉ።

ወያኔ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረገው የለውጥ እንቅስቃሴ እየበረታ መሄዱን በመገንዘብ እንቅስቃሴውን በእንጭጩ ለማስቀረት መንቀሳቀሱ አልቀረም፣ ይህንን ወያኔን እንቅልፍ የነሳ እንቅስቃሴ ወደ ተግባራዊነት እየቀየሩ ባሉት የግንቦት 7 አመራሮች ላይ አነጣጥሮ በተገዙና የተቃዋሚ ካባ በደረቡ ግለሰቦች አማካኝነት አመራሮቹን ከህዝብ ለመነጠል ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርግም ውጤቱ አመርቂ አልሆነም። ወያኔ ከዚህ በኋላ ነበር አማተር ሰላዮቹን ወደ ኤርትራ በመላክ አርበኛውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመግደል ሙከራ ያደረገው ይህም አልተሳካም እንደውም ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ደረሰበት (ብዙዎች አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጠንቅቀው የማያውቁት ሳይቀሩ የአንዳርጋቸውን ማንነት ለመገንዘብ ቻሉ)።

ወያኔ በመጨረሻ ያደረገው ሙከራ ተሳክቶለት አቶ አንዳርጋቸውን ከየመን አፍኖ ወደ አዲስ አበባ መውሰድ ቻለ።
ለጊዜው ወያኔዎች ከፍተኛ የድል አድራጊነት ሰሜት ተሰምቷቸው ጮቤ ረገጡ ይሁንና ብዙም ሳይቆይ ደስታቸው እንደጉም በኖ እስካሁን በሚያቃዣቸው ስጋት ውስጥ እንዲዘፈቁ ሆነ። ጀግናቸው (አንዳርጋቸው ጽጌ) በወያኔ እጅ መውደቁን የሰሙ ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከጫፍ ተነቃነቁ፣ አንዳርጋቸው የጀመረውን የትግል ጉዞ ከግብ ለማድረስም ቁርጠኝነትቸውን አሳዩ፣ የአንዳርጋቸው ቤተሰቦች ሴት ከወንድ ሳይባል በአንዳርጋቸው ጽጌ እግር ተተክተው አንዳርጋቸው ያቀጣጠለውን ችቦ ተረከቡ።
የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራሮችና የአንዳርጋቸው የትግል ጓዶች ዙሩን አከረሩት፣ በተደጋጋሚ ከወያኔ ጋር ባካሄዳቸው የሽምቅ ውጊያዎች ልምድ ካካበተውና የሰሜኑን የኢትዮጵያ ግዛቶች መግቢያ መውጫ ጠንቅቆ ከሚያውቀው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጋር ውህደትን ፈጠሩ፣ በውጤቱም አርበኞች ግንቦት 7 ተወለደ።

በለስ ቀንቷቸው አቶ አንዳርጋቸውን በእጃቸው ያስገቡት ወያኔዎች ከሚቆጣጠሩት ግዛት ውጪ እየተካሄ ያለው እንቅስቃሴ በአንዳርጋቸው መያዝ ምክንያት መባባሱን ተረድተዋል። የእንቅስቃሴውን ፍጥነት ለመግታት በቁጥጥራቸው ስር ያለውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመጠቀም በማሰብ እየቆረጡ እና እየቀጠሉ የሚለቋቸው የአዳርጋቸው ጽጌ ቪዲዮዎች ምንም ውጤት አላመጡም፣ ይልቁንም በኢትዮጵያውያኑ ዘንድ ከፍተኛ ቁጭትን እየጫሩ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ ቃላቸውን እንዲያድሱ አድርጓቸዋል።

ለዚህም ይመስላል አንዳርጋቸው ጽጌን የስፖርት ቱታ በማልበስ ሰው በሌለበት ጎዳና ላይ ፎቶ አንስተው “ተመልከቱ እባካችሁ አንዳርጋቸው ሰላም ነው” በማለት ኢትዮጵያውያኑን ለማረጋጋት የሞከሩት።
አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት መፈጸም ከጀመረና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ገብቶ በአንዳርጋቸው እግር መተካቱ ከተሰማ በኋላ ደግሞ ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጉዳይ ፍም እሳት ሆኖባቸው የሚያደርጉትን አሳጥቷቸዋል፣ ለዚህም ምልክቱ ቴድሮስ አድሃኖም በቪኦኤ ላይ የተናገረው ነው “አንዳርጋቸው ላፕ ቶፕ ተሰጥቶት መጽሃፍ ጽፎ ጨርሷል፣ አንዳርጋቸው የሃገሪቱን ልማት ማየት ፈልጎ እያዟዟርን አሳይተነዋል ወዘተ…”

እውነታው ግን አንዳርጋቸው ጽጌን የት እንዳሰሩት አይናገሩም፣ አንዳርጋቸውን ቤተሰብም ሆነ ማንኛውም ሰው አይጎበኘውም። በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ወያኔዎች በአንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሚያውቁትን የማሰቃያ መንገዶች ሁሉ በመጠቀም አንዳርጋቸው እነርሱ የሚፈልጉትን አይነት መልእት እንዲያስተላልፍ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። ይሁንና ጀግናው አንዳርጋቸው ጽጌ እስካሁን የሚፈልጉትን አልሰጣቸውም (ይህንንም ለማረጋገጥ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ስቃይ እየፈጸሙ ቀርጸው የሚያሰራጯቸውን ቪዲዮዎችን መመልከት ይበቃል)።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በአካል ተገኝቶ ትግሉን መምራት ባይችልም መንፈሱ ግን ትግሉን በማቀጣጠል ላይ ይገኛል። እንግዲህ ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌን ለመቆጣጠር ነው ቁጭ ብድግ በመስራት ላይ ያሉት፣ ይሳካላቸው ይሆን? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል።

ሁሉም በያለበት የነፃነት ትግሉን ይቀላቀል!!!

July 31, 2015
def-thumbእኛ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የሰውነት መብታችን ተገፎ የዜግነት ነፃነታችን ተረግጦና ተዋርደን የምንገኝበት ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው፡፡ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ እስርና የጅምላ ስደት እንደ ዘመነ ወያኔ የታየበት ዘመን የለም፡፡ ህፃናት በረሀብ ከሚማሩበት ክፍል ውስጥ የሚወድቁበት ፤ ወንድ ልጅ በደህንነት ሀይሎች ታፍኖ የሚደፈርበት፤ ሴት ልጅ በገመድ የታሰረ የባልዋነወ ብልት መንገድ ለመንገድ እንድትጎትት የተደረገበት ዘመን ቢኖር ያሳለፍነው የወያኔ ዘመናት ብቻ ነው፡፡ ባጠቃላይ የሰው ልጅ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ መከራና ሰቆቃ እንድንሸከም የተገደድንበት ዘመን ላይ እንገኛለን፡
በአንፃሩም ስለ ለፃነት ስለ ፍትህና እኩልነት ሲሉ የተሰዉ ዋጋም የከፈሉ፤ አሁንም እየከፈሉ የሚገኙ ጥቂት አይደ ሉ ም፡፡ ከነዚህም አንዱ አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ይህ ለነፃነት ለፍትህና ለ ዲሞክራሲ የሚደረገው ተጋድሎ ውሎ አድሮ ዛሬ ከዋናውና ወሳኝ ከሆነው ምእራፍ ላይ መድረሱ ደግሞ የሁላችንንም ተስ ፋ ያለመለመና የተደፋው አንገታችን ቀና ያደረገ መሆኑና በተቃራኒው የወያኔን ካንፕ ያሸበረ መሆኑ በገሀድ እየታየ የሚገኝ እውነት ነው፡፡
እንግዲህ ይህን ወራዳ ስርአት አስወግዶ በምትኩ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመተካት የሚደረገው ትግል ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የተደረገው ርብርብ ቀላል ባይሆንም ቀሪውን አጠናቆ ከዳር ለመድረስ ከመቼውም ጊዜ በላይ የእያንዳዱን ኢትዮጵያዊ የተግባር ተሳትፎ የሚጠይቅ፤ ሁሉም ከያለበት ስለ ነፃነት የሚደረገውን የአርነኝነት ትግል በመቀላቀል የድርሻ ውን ሀላፊነት መወጣት ከሚጠይቅበት ወሳኝ ምእራፍ ላይ መድረሳችንን መረዳት ግድ ይላል፡፡
እኛ ኢትዮጵያውያን ያለ ማንም እርዳታና ድጋፍ ዋጋ ከፍሎ ለፃነትን የማሰከበር እንግዳ ሳንሆን በታሪክ የምንታወቅበት መለያችን መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ እንኳን ዛሬ አለም አለም በጠበበችበት ዘመን ቀርቶ ትናንት በጨለማው ዘመን እንኳ እነ ዶ/ር መላኩ በያን ከአኛ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት ፈር ቀዳጅ ሆነው የተገኙበትን ታሪክ ማስታወስ ይገባል፡፡
እናም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኟውም ስፍራ የሚገኝ ሁሉ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል እውቀት ያለው በእውቀቱ፤ ጉልበት  ያለው በጉልበቱ፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ለመደገፍ ዛሬ ነገ ሳይል አሁኑኑ ከአርበኝነቱ ትግል መቀላቀል ይጠበቅበታል፡፡ ኢትዮጵያዊነታችንን ብቻ ሳይሆን ሰው መሆናችን የሚረጋገጠው ነፃነታችንን አስጠብቀን በነፃነት መኖር ስንችል ብቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡
ስለዚህ ዛሬ አርበኞች ግንቦት ሰባት የለኮሰው የነፃነት ቀንዲል ከነጻነት አደባባይ ለመትከል የጀመረውን ጉዞ በሰው ሀይል፤ በገንዘብና በቁሳቁስ በማገዝ ሁላችንም የድርሻችንን እንድንወጣ ጥሪ ስናደርግ ለእኛ ኢትዮጵያውያን ከእኛ ኢትዮጵ ያውያን ውጭ ማንም እንደሌለ በማስገንዘብ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

Wednesday, July 29, 2015

ከአምስት በላይ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች እና የሸዋሮቢት ነዋሪዎች በእስር ላይ መሆናቸው ተገለጸ

July 29,2015
በሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ሸዋሮቢት ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች እና ወጣት የለውጥ አራማጅ የፓርቲው አቀንቃኞች በመንግስት ሃይል ታፍነው ወደ እስር ቤት ከተወረወሩ ከወር በላይ መሆናቸውን ከክልል ሶስት ሰሜን ሸዋ ዞን የሸዋሮቢት ከተማ አስተደር ነዋሪዎች የሆኑ እና የፓርቲው አባሎች እና አመራሮች ለማለዳ ታይምስ የአባሎቻቸውን መታሰር ጠቁመዋል ።
እነዚህ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች በየትኛው ቦታ እና እንዴት እንደታሰሩ ለመጠየቅ ቢሄዱም የመንግስት ሃይሎች ምንም አይነት መረጃም ሊሰጧቸው እና ያሉበትንም ሁኔታዎች ሊያሳውቋቸው ባለመቻላቸው በከፍተኛ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ የሚገኘውን የሰማያዊ ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት ለማግኘት እና ስለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መግለጫ እንዲያወጡ ለመጠየቅ በደጋግሚ ቢጥሩም ምንም ምላሽ ሊሰጧቸው አለመቻሉ እራሱ አሳሳቢ ከመሆኑም በልይ በክልሉ ለሚገኙት አባሎች እራስ ምታት መሆኑን ገልጸዋል ።
የፓርቲው አመራር ምላሽ መስጠት ሲገባቸው እንደ ወያኔ መንግስት ለአባሎቻቸው ዝምታን መፍጠሩ ለለውጥ የተዘጋጁ ሳይሆኑ ለጥቅሞቻቸው የተነሱ ሃይሎች መስለው ነው የታዩን ብለው የተናገሩት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት እና የቀወት ወረዳ የሰማያዊ ፓርቲ የወጣት መልማዮች ዋና ሃላፊ በዛሬው እለት ይህንን መግለጭ ወደ ግል መገናኛ ብዙሃን ልናመጣው የቻልነው ሰሚ አካል ብናገኝ ጥሩ ነው በሚል ምክንያት ነው ሲሉም አክለው ገልጸዋል ። ከአንድ ወር በፊት የታሰረውን ወጣት ቴዎድሮስ ሃብቴ እስካሁን ያለበትንም ሁኔ ካለማወቃችን የተነሳም ለፍርድ እንኳን አቅርበው ጥፋተኝነቱንም ህነ የተከሰሰበትን ሁኔታ ለመረዳት አልቻልንም የሌሎችንም ወጣት የዘርፍ ክፍሎቹንም ለመከታተል አልቻልንም ሲሎ ገልጸዋል ።

Monday, July 27, 2015

ፕ/ት ኦባማ «ኤርትራ ያለ ተቃዋሚ ድርጅትን በአሸባሪነት ለመፈረጅ» የሚያስችል በቂ መረጃ የለንም አሉ፤

July 27,2015
ኢሳት ዜና ፦ የአሜሪካው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት ” በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ ፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ምክትል ሃላፊ ዌዲ ሸርማን አርበኞች ግንቦት7ትን በአሸባሪነት እንዲፈረጅ ያቀረቡትን ጥያቄ፣ ለፕ/ት ኦባማም ማቅረባቸውን የሚያመለክት ነው። ፕ/ት ኦባማ በመልሳቸው «ፖሊሲያችን መንግስትን በሃይል ከስልጣን ማውረድን አይደግፍም፣ ይህ ፖሊሲያችን በዲሞክራሲያዊ ሁኔታ የተመረጠውን የኢትዮጵያን መንግስትንም ያካትታል» ካሉ በኋላ፣ «በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩብኝ ነው በማለት የሚፈርጃቸው ድርጅቶች እንዳሉ እናውቃለን፣ ይሁን እንጅ በመንግስት ላይ ተቃውሞ ቢያሰሙም የሽብር ዝንባሌ እንደሌላቸው የእኛ የመረጃና የደህንነት መረጃዎች ያሳዩናአል» በማለት በኢህአዴግ መንግስት በኩል የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ተናግረዋል። «ይህንን በመገምገም በኩል ግልጽ የሆነ መስፈርት አለን ያሉት ኦባማ፣ ለወደፊቱ እነዚህ ድርጅቶች የሽብር ጥቃት ይፈጽማሉ አይፈጽሙም የሚለውን ለወደፊቱ የምናየው ይሆናል ብለዋል።
.
«አንድ ድርጅት የፖለቲካ ተቃውሞውን ቢገልጽ ፣ ከአስተሳሰቡ ጋር ባንስማማም እንኳ ከለላ እንሰጠዋለን፣ ይሄ በአሜሪካ በሌላም ቦታ የሚሰራበት እውነታ ነው፤ ይህን ማድረግ ለዲሞክራሲ እድገት አስፈላጊ ነገር ነው» ያሉት ኦባማ ፣ ድርጅቶቹ ወደ ሃይል ሲያዘነብሉና በህገመንግስት የተቋቋመን መንግስት ለመገልበጥ ሲሞክሩ፣ ድርጊቱ ያሳስበናል።» በማለት መልሰዋል። የውጭ አገር ጋዜጠኞች ፣ በእስር ላይ ስለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እንዲሁም ስለኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ ጉዳይ ለፕ/ት ኦባማና ለአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ፕ/ት ኦባማ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥበቃ እና በዲሞክራሲ ዙሪያ ከአቶ ሃይለማርያም ጋር ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን፣ አሜሪካ በቅርብ ሁና እገዛ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልጸዋል። የኢህአዴግ መንግስት ከፕ/ቱ ጉብኝት በዋናነት የሚጠብቀው ለስልጣኑ ስጋት የሚፈጥሩ ድርጅቶች በሽብረተኝነት እንዲፈረጁለት ቢሆንም፣ ይህንን ሳያገኝ ቀርቷል። ይሁን እንጅ ባራክ ኦባማ የኢህአዴግን መንግስት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችን ሳያስቆጣ አይቀርም። ኦባማ በአንድ በኩል በኢትዮጵያ እየጠበበ ስለመጣው የፖለቲካ ምህዳር ሲናገሩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ የሚል ካባ ማልበሳቸው፣ የአሜሪካ የውጭ ፖሊሲን ተቃርኖ የሚያሳይ ነው።
.
በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል ለፕሬዝደንት ኦባማ በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታውቀዋል። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት መንግስት ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገውን የእራት ግብዣ ያልተቀበሉት፣ «አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ፣ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም» ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም «የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ» ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸውም ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ «ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው» ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ኢ/ር ይልቃል

July 27,2015
ኢ/ር ይልቃል መንግስት ለፕሬዝደንት ኦባማ ያዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታወቁ
• ‹‹ኦባማ ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ ውሃ የሚቸልስ ነው››
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ ለነገረ ኢትየጵያ ገልጸዋል፡፡ የራት ግብዣው ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥሪ የተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል ‹‹ አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም›› ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም ‹‹የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው›› ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል በነገው ዕለት የአሜሪካ ኤምባሲና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የወያኔ ታጣቂዎች በታህታይ አድያቦ ወረዳ እርስ በራሳቸው ተዋጉ

July 27,2015
በታህታይ አድያቦ ወረዳ አካባቢ የሚገኙ የገዢው የኢህአዴግ ስርዓት ወታደሮች እርሰ በራሳቸው እየተገዳደሉ እንደሚገኙ ተገለፀ። በትግራይ ሰሜናዊ ምእራብ ዞንEthiopian dictatorial regime troopsታህታይ አድያቦ ወረዳ ተሰማርተው የሚገኙ የኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት በመካከላቸው አንድነትና ፍቅር እንደሌላቸው የገለፀው መረጃው በተለይ ደግሞ በአባላትና በአዛዦች መሃል በተከሰተው ያለመስማማት ምክንያት ወታደር ታዘዘ ደበበ የተባለ ግለሰብ መቶ አለቃ አስራት ባዩና አምሳ አለቃ ካሳ አለሙ የተባሉን በጥይት ገድሎ ለራሱም ህይወቱን እንዳጠፋ የተገኘው መረጃ አስረድቷል።
በተመሳሳይ- በአዲ ሃገራይ አካባቢ የሚገኙ የኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት አንድ ወታደር 3ት ኮነሬሎችን ከነ አጃቢዎቻቸው ገድሎ ራሱን ህይወቱን እንዳጠፋ ባላፈው የዜና ዘገባችን መግለፃችን ይታወሳል።
ምንጭ – ትህዴን

የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት ነው

July27,2015

(ወለላዬ ከስዊድን)


አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል።
“ወደ ሰፈር፣ ወደ ሰፈር እየወረድኩ ነው ንጉሥ ሆይ!”
“ምነው ደህናም እማይደለህ?”
“ጣቴን ድንጋይ ቀርጥፎኝ ነው ንጉሥ ሆይ!”፤ ትንሽዋን ጣቱን በጨርቅ ነገር ጠቅሎ አንከርፏል።
“ና እስቲ! ቀረብ በልና የተጎዳኸውን አሳየኝ”፤ ሰውየው ንጉሡ ጋ ቀርቦ የቋጠራትን ጨርቅ ፈቶ ጣቱን ሲያሳይ ንጉሡ ትንሽ ጭረት ቢጤ ብቻ ያያሉ።
“ሌላ ቦታም ተጎተሃል እንዴ?”
“የለም! ይሄው ብቻ ነው።”
“እና! ይቺን ቁስል ናት! ብለህ ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ?”
“ይችኑስ ቢሆን በማን ልላካት ጌታዬ?” ብሎ ንጉሡን እንዳሳቃቸው ይነገራል። እኔም ለሌላ ሰው የሚላከክ ቢሆን የአቶ መለስን ሙት መንፈስ እዚህ ጋ ባልሸነጎርኩ ነበር። ሆኖም የሳቸው ቁስል ምንም እንኳን አነስተኛ ባይሆንም በማንም ልላክከው ስለማልችል ማንሳት ሊኖርብኝ ነው። አንድ ጊዜ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሁራንን ሰብስበው ንግግር አደረጉ። ምሁራኑ በአንክሮ ሰሟችው። የአነጋገራቸውን አካሄድ ተንኮልና ክፋት እንዳዘለ ቢያውቁም ብዙዎቹ ሊናገሩ አልፈለጉም። በኋላ ግን አንድ እጅ ከመሃል ተቀሰረች። አቶ መለስ ምሁሩ እንዲናገሩ ዕድል ሰጡ። ሰውዬው ከማንም ይበልጥ የአቶ መለስ ንግግር አንገብግቦአቸዋል። ማንገብገብ ብቻ አይደለም በእንዲህ አይነቱ መሪ አገሪቷና ህዝቡ ወደፊት የሚደርስበት ውርጅብኝ የበዛ እንደሚሆን በደልና ስቃዩም አስከፊ ደረጃ እንደሚደርስ ተሰምቷቸዋል።
ምሁሩ ዕድሉን ተጠቀሙበት፤ ማለት የሚገባቸውን አጠቃለው እስኪጨርሱ አንዳችም ፍርሃትና መደናገር ሳይታይባቸው “… አሁን ለሁሉ ነገር ጊዜው አልፏል። እርስዎ እያሉ ገበሬው ውስጥ ገብቶ አደራጅቶ ፋይዳ የሚያመጣ ፓርቲ ይኖራል ተብሎ አይገመትም። ስለዚህ ኳሷ በርስዎ ቁጥጥር ስር እስከዋለች ድረስ ከምንም ነገር በላይ ቅንነትዎን ብቻ እንፈልጋለን። ቅንነትዎ አይለየን ቅን ሆነው ይምሩን ይሄን ብቻ ነው የምንጠይቅዎ …” ነበር ያሉት።
ምሁሩ አቶ መለስ እስከወዲያኛው ቀና እንደማይሆኑና በቀናነት ሊመሩ እንደማይችሉ አላጡትም። ነገር ግን ቀና ማድረግ ባይቻል እንኳን ቀና እንዳልሆኑ ለማሳወቅ ፈልገዋል። ሆኖም አቶ መለስ ቀና ባይሆኑ አይገርምም ከሚሰሩት ተንኮል አንጻር ቀናነት ኪሳራ እንጂ ትርፍ ሊያስገኝላቸው አይችልም። ተፈጥሮአቸውም ቢሆን በቀናነት ተቃኝቶ በሥነ ምግባር ጎልብቶ የቀናነትን ጎዳና የተከተለ ስላልሆነ ቀና ልሁን ቢሉ እንኳን አይችሉም። ይህ ብቻ አይደለም ከአመራራቸው ግብና ዓላማም ጋር ቀናነት አብሮ አይሄድም።
ገና ከትምህርት ቤት ጀምሮ የመሰሪነት ባህሪ እንደነበራቸው የሚመሰክሩ ብዙዎች ናቸው። ስንት ታጋይ ጓደኞቻቸውን ወደ እማይመለሱበት እየላኩ ለሥልጣን የበቁም ናቸው። ከሥልጣን በኋላም ሞት እጃቸውን እስከሰበሰበው ድረስ አለ እረፍት ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያን ያዋረዱ፤ ህዝብ የናቁ፣ የከፋፈሉ፣ ያሰሩ፣ የገደሉ፣ ባንዲራን ያቃለሉ፣ ያገር ክብር የደፈሩን ሰው በምንም አይነት ቅንነት ልንመኝላቸው አንችልም።
እንግዲህ ስለአቶ መለስ ቀና አለመሆን ከተፈጥሮቸውና ከዓላማቸው አንጻር ነው ብለናል። ነገር ግን አቶ መለስን የሚያወግዝ፣ ለዲሞክራሲ ለሠላምና ለእኩልነት መከበር የቆመ፣ የተጣመመን ፍትህ አቃናለሁ የሚል፣ በሰው ልጅ እኩልነት የሚያምንና ይህንንም ለማስከበር የተነሳ ለአገሩ ብልጽግናና ነጻ መውጣት የሚያስብ ቅንነት ከጎደለው ከዓላማና ግቡ ጋር የተቃረነ መሆኑ አያጠራጥርም። አቶ መለስ የጣሏትን ቅንነት አንስቶ በጉያው ካልያዘ ልዩነታቸው ብዙም የተራራቀ አይሆንም። ለሳቸው ቅንነት ይጎዳቸዋል እሱ ደግሞ አለቅንነት ምንም አይነት የነጻነት ጉዞ ሊጓዝ አይችልም።
እንደውም ቀና ልቦና የሌለው ታጋይ ጊዜውና ሁኔታው ሲገጥመው አንዳንዴ ብልጭ እያለች የምታሳጣውን መጥፎ ባህሪ ሰው ጥላቻና ክፋት እፊት ለፊት አውጥቶ እማይጠቀምበት ምንም ምክንያት የለውም። ያንን እስከሚጠብቅና ድብቅ ፍላጎቱን እስኪያሟላ ድረስ ተፈጥሮው እያወከው ለትግል ጓዶቹ የማይመች የትግል እንቅፋት ሆኖ መቆየቱ አይቀሬ ነው።
ጎኑ ያለውን የትግል ጓዱን ያልወደደ ለዲሞክራሲ ቆሜያለሁ፣ ለነጻነት እፋለማለሁ፣ ለነፍትህ እዋደቃለሁ፣ … ቢለኝ አላምነውም፤ ባህሪው የገባበትን ዓላማ እንዳያሳካ አንቆ ስለያዘው የሱን ታጋይነት እጠራጠራለሁ። እውነቴን ነው ይህ ሰው ጫፍ ድረስ አይዘልቅም ይሰናከላል። ተሰናክሎም ያሰናክላል።
እናም የኢትዮጵያ ህዝብ ከገባበት የእጅ አዙር የባርነት አገዛዝ፣ ከነፃነት እጦት፣ ከእስር፣ ከንግልት፣ ከስደትና ከረሃብ ለማላቀቅ የተነሳህ፤ ፍትህ እንዲከበር፣ ዲሞክራሲና ሰላም፣ እድገትና ብልጽግና እንዲገኝ የምትፈልግ ሁሉ የትግልህ መጀመሪያ የቀና ልቦና ባለቤትነት መሆንን በማመን በቀናነት ከትግሉና ከታጋዩ ጋር ተቀላቀል። ቀና ልቦና ያለው መንገዱ ሁሉ ክፍት ይሆንለታል፣ በቀላሉ አይሰናከልም፣ ልቡ አያውከውም፣ አቀራረቡ ግልጽ ነው። አይፈራም፣ አይዋሽም፣ አያታልልም፣ አይጠራጠርም፣ ለቂም አያደባም፣ ለዝና አይናውዝም፣ ለሥልጣን አይዳክርም …
ይህ ካልሆነ ግን፤ እታገልልሃለሁ በምትለው ህዝብ ፊት ለመቆም ጉልበትህ አይጠናም። ህዝብ የምታደርገውን የትግል እንቅስቃሴ ቢያይም የአስተሳሰብህን ሸካራነት፣ የልቦናህን ክፋት ለመረዳት ብዙ ስለማይፈጅበት ክብርና ፍቅር ሊሰጥህ ይቸገራል፣ አይከተልህም። አይዞህ ልጃችን በማለት አያበረታታህም። እንደውም ልታታልለው እንደተነሳህ፣ ልታሞኘው እንዳደባህ ስለሚቆጥርህ ልቡን ከፍቶ አያሳይህም፤ ስለዚህ ቀና ሁን።
የፖለቲካን ትርጉም ከክፋት ጋር አትቀላቅል። ሌላም የምመክርህ አለኝ፣ የትግል ጓዶችህን አክብር፣ ጓደኛህ ስህተት ካለበት በድብቅ ከማማት ይልቅ ስህተቱን ፊት ለፊት ነግረህ እንዲመለስ አድርግ። ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ አሲረህ አሳድመህ አጥቂ አትሁን፤ ቂመኛ ሀሚተኛ አትሁን፤ መልካምነትን አሳንሰህ ስህተትን አታጉላ፤ የኔ ሃሳብ ይበልጣል፣ የምናገረውና የምሠራው ሁሉ የኔ ልክ ነው አትበል። ለቡዙሃን ድምጽና ሃሳብ ተገዛ፤ ሌላውን ደካማ አድርገህ አትይ፤ ለመወንጀል አትፍጠን፤ ልብህን ለንጹህ ወንድምነት ክፍት አድርግ። መቻቻልን፣ በጋራ መሥራትን አዳብር፤ የትግል ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን ለሥልጣንና ለሀብት አትጓጓ፤ ድርሻና ኃላፊነትን ከፍ አድረገህ በመመልከት ሌሎችን አትጫን፤ መልካም ሥነምግባር በማሳየት ሌሎችም አንተን እንዲከተሉ አድርግ። አትወላውል! ለተነሳህበት ዓላማ እስከመጨረሻው ተጓዝ። ወዳጄ ሆይ! ምክር ቢበዛ ባህያ አይጫንምና ይበቃኛል። ለማንኛውም የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት መሆኑን አትዘንጋ።

የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት ባደረጉት ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ብዛት ያላቸውን የኢህአዴግ ሰራዊት ደመሰሱ

July27,2015
arbegnoch g7 በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ማይ-ሰገን በተባለው አካባቢ የሚገኙትን የኢህአዴግ የሰራዊት አባላት በግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በደረሰባቸው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ምክንያት ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውን ተገለፀ።
ባለፈው ቀናት በሑመራ አካባቢ ማይ ሰገን በተባለው ቦታ ላይ የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በኢህአዴግ ሰራዊት ላይ ባደረሱት ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ብዛት ያላቸው ታጣቂዎች ከጥቅም ውጭ ማድረጋቸውን የገለጸው መረጃው በውጊያው ከተገደሉት ታጣቂ አመራሮችም።….
ኮማንደር ወልደሚካኤል ገብረእዝጊአብሄር የሃይል አዛዥ የነበረ፤ ካሕሳይ ነጋሽ በባዕኸር የሚልሻ አዛዥ የነበረ፤ ለግዜው ስሙ ያልታወቀው የሻምበል ማእርግ ያለው በ24 ክፍለጦር የሓይል አዛዥ የሆነውና ሌሎች የሚገኙባቸው እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
እነዚህ የስርዓቱ ታጣቂዎች- በአካባቢው ሰላማዊ ህዝብ የተለያዩ ግፍ ሲፈፅሙ የቆዩ በመሆናቸው የተነሳ የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በላያቸው ላይ እርምጃ መውሰዱን የተገኘው መረጃው አስረድቷል።