Saturday, July 30, 2016

ሰበር ዜና . . . በጎንደር የአማራ ልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ ህዝባዊነት እያሳዩ ነዉ ተባለ

July 30,2016

ethiopian-army
በጎንደር ተሰማርቶ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ ባጠቃላይ ነገ የሚካሄደዉን የጎንደርን ሰልፍ ተነተርሶ የተሰጣቸዉን ሰላማዊ ሰልፍ የማክሸፍ ሴራ ያለማቀበላቸዉን የሚጠቁሙ መረጃዎች ደርሰዉናል።
·         ከየትኛዉም መንደሮች ወደ መሰብሰቢያ ቦታዉ የሚወስዱ መንገዶች በጸጥታ ሐይሎች እንዲዘጉ።
·         ሰልፉን ያስተባብራሉ ይመራሉ ይቀሰቅሳሉ የሚባሉ ግለሰቦች ከድርጊታቸዉ እንዲታቀቡ ማድረግ…… ትእዛዝ (( )) ይህ ሁኔታ የጸጥታ ሐይሎችን በመጠቀም ማስገደድንም ይጭምራል
·         የስረአቱን ቀንደኛ ደጋፊ ብአዴኖችን በመጠቀም ጥቆማዎችን አይነተኛ መሳሪያ አድርጎ ማባበያ (መደለያ) እና ማዘናጊያ እቅዶችን ማስፈጸም!!
·         ይህ ካልሆነ በጸጥታ ሐይሎች ተጠቅሞ እርምጃዎችን በተጠና ሁኔታ መዉሰድ>>>> የሚሉ ሲሆኑ እነዚህና የመሳሰሉት ሂደቶች ዉጤታማ ስይሆኑ ቢቀሩና ሰልፉ ቢካሄድ የመከላከያ ሰራዊቱ ዝግጁ እንዲሁን ትእዝዝ ቢተላለፍም ባጠቃላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላትና የጸጥታ ሐይሎች ብሎም የአካባቢ ሚሊሻ . . . . . ” አንዳችም ሰዉ ላይ ጉዳት አናደርስም ” አፈና አናካሄድም! ህዝቡ መብቱን በሰላማዊ መንገድ እየገለጸ ከመካከላችን አንዳች ስህተት ቢሰራ ዝም ብለን አንመለከትም! በማለት አቋማቸዉን የገለጹ ሲሆን በተለይም የአካባቢ ሚሊሻዎች በተለየ ሁኔታ ከህዝቡ ጎን መቆማቸዉን በድፍረት ተናግረዋል።
እነዚህ ሁኔታዎች ሁሉ ገደል በገደል የሆኑበት የትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን ሰሜን ጎንደር አይከል አካባቢ ያሰፈረዉን የአጋዚ ጦር ወደ ጎንደር እያስገባ ከመሆኑ በተጨማሪ በባሕር ዳር ስምሪት ላይ የነበረ የልዩ ሐይል ወደ ጎንደር እንዲንቀሳቀስ የተደረገ ሲሆን
….  በጎንደር የልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት ምድቦች ማንም ይምጣ ማን ይህን ህዝብ ይንኩና እንተያያለን በማለት እርስ በእርሳቸዉ ተፋጠዉ ይገኛሉ።
ዜና -በልኡል አለም

የረሃብ አድማ ላይ ያሉት ብርሃኑ ተ/ያሬድ እና ዮናታን ተስፋዬ ፍርድ ቤት ቀረቡ

July 30,2016


በቂሊንጦ የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ለ9 ቀን የረሃብ አድማ ያደረጉት እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ እና ዮናታን ተስፋዬ ትላንት ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር። እነ ብርሃኑ (ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ እየሩስ ተስፋው፣ ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ) የቅጣት ማቅለያ እንዲያመጡ ነበር የተቀጠሩት።

የተሰጣቸው ቀጠሮ አጭር ስለነበረ እና የእስር ቤቱ አስተደዳደር በሚያደርስባቸው በደል ከቤተሰብ ጋር ባለመገናኘታቸው ማቅለያው ሊደርስላቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል። በተጨማሪም አራተኛ ተከሳሽ ደሴ ካህሳይ ቤተሰቦቹ ሩቅ ሃገር በመሆናቸው ከነሱ ጋር ተነጋግሮ ማቅለያ ለማስገባት ጊዜ ስለሚፈልግ ረጅም ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ዳኛዋ የተሰጣችሁ ጊዜ በቂ ነው በማለት ከሃምሌ 29 በፊት በቢሮ ማቅለያዎቻቸውን እንዲያስገቡ እና ሃምሌ 29,2008 ፍርድ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥታለች። አቃቢ ህግ የቅጣት አስተያየቱን (ማክበጃ) አስገብቷል።

ብርሃኑ በረሃብ አድማው ምክንያት በመድከሙ ይሰጠው የነበረው ጉልኮስ ጠዋት ወደ ፍርድ ቤት ሲመጣ ነው የተነቀለለት። በዚህም ምክንያት ችሎት ውስጥ መቆም ባለመቻሉ ቁጭ ብሎ ነው የተከታተለው። ዮናታንም በተመሳሳይ ምክንያት ችሎት ውስጥ መቆም አልቻለም ነበር። ዮናታን ተቀጥሮ የነበረው የአቃቤ ህግን የደረጃ ምስክሮች ለመስማት የነበረ ቢሆንም የደረጃ ምስክሮቹ የሚሰጡትን ምስክርነት ዮናታን የሚክደው ስላልሆነ ምስክርነታቸው መሰማቱ ውድቅ ተደርጎ ለሃምሌ 28, 2008 ይከላከል ወይም አይከላከል የሚል ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ተሰጥቷል።

Friday, July 29, 2016

The poverty-bad governance conundrum simmering conflicts in Ethiopia

July 29.2016
by Getahun S. Gesso*
Ethiopia is praised for a booming economic growth over the last decade in consonance with the Africa rising mantra. Indeed, the Ethiopian economy registered consistently over 10% growth for over a decade. The structure of the economy is also changing from a predominantly agrarian economy. The service and industrial sectors are expanding fast. Other sectors such as education and health have also shown tremendous improvement albeit with their own shortcomings. Infrastructural developments in the water, power, road and rail sectors are becoming worthy examples for the rest of the developing world.
map
Further, Ethiopia has strong diplomatic ties with the east and west. Its positive contribution to peace and security in Africa and particularly in the eastern Africa Region is well recognized.
However, the level of poverty and bad governance in the country is still frightening despite reports of a small dent the economic growth has caused to the level of the large percentage of people living below the poverty line. These vices are feeding into each other making the country remain impoverished.
The recent events unfolding in Ethiopia are proving this point more than ever. Ethiopia is in the news this time around for the wrong reason: drought, hunger and violent conflicts.
In terms of drought, the number of people needing food aid and humanitarian assistance is increasing exponentially from time to time with close to 20 million citizens badly in need of help. Of these, over 6 million are children according to VOA report of 2 May 2016.
The drought is reported to be the worst of its kind in the last half century. To one’s consternation, the Government does not seem to know the extent of the drought; every month or two, we hear that the number of affected people and amount of request for humanitarian support has been revised upwards. Ethiopia seems not to have taken good lesson from the past similar droughts. It is business as usual for the Government in Addis, which leads Africa’s second most populous nation of close to 100 million.
Whitney McFerron and Frank Jomo of Bloomberg news wrote on 22 March 2016 that the Ethiopian Government “has appealed for $1.4 billion from international donors” in the form of humanitarian assistance. This is over 12% of the country’s annual budget for 2016. Taken by surprise, the Government exhausted its domestic food reserve immediately and started importing wheat and maize in a frantic manner. What is surprising is that this is happening immediately after Ethiopia declared itself food secure about three years ago. Even the dust from that declaration has not settled well.
Unfortunately, the drought and hunger occurred at a time immediately after the discourse on bad governance started heating. The extent of bad governance in the country has reached an uncontrollable level as often admitted by the Government. This becomes further complicated by the depth and breadth of abject poverty. This vicious connection between poverty, bad governance and lack of will to listen to the people led to several violent conflicts all over the country.
Bad governance is fueling questions of identity to be raised overtly or covertly. There is a wide protest in Oromia Region (including by elementary school pupils), the largest and most populous Region, with the pretext of an Addis Ababa Integrated Master Plan for developing the surrounding towns. It resulted in wanton deaths and destructions. The Plan, however, got withdrawn later. The Kimant people in Amhara Region are demanding for autonomy, which led to deadly confrontations with the security apparatus. There is a simmering grievance, since many years back, on issues of identity in the Southern Nations, Nationalities and People’s Region where more than about 45 minority ethnic groups are lumped together as one Region. The main ethnic groups in the Region like the Gurage and Sidama have been murmuring about this for decades. It is difficult o think this will not go the Kimants way. A clear evidence to this is the ongoing protest taking place in the north of the country particularly in and around Gondar resulting in several deaths including about a dozen police officers.
The situation in the country is worrying. In April, it is reported that over 200 Nuers were killed by militia groups (cattle-rustlers) from South Sudan in Gambella Region. To make things worse, these militia groups kidnapped over 100 children and took away over 2,000 heads of cattle. This is baffling to the Nuers and others in Ethiopia. It is also reported that subsequent to the Nuer attack, tribal clashes resulted in dozens of highlanders killed in Gambella. These are being taken, and rightly so, as weaknesses of the Government to provide basic security to citizens.
It appears, nonetheless, that the Government’s willingness to listen to public complaints is still at its lowest. While all of these discontents are raging, it attempted to introduce new penalty system for traffic offenders (taxi drivers) in Addis Ababa last February resulting in another frightening confrontation. When the protests got worse, the Government subdued and suspended implementation of the new regulations. Though this giving-in could be taken as a positive development, given the stubborn nature of the Government, it shows a lack of coordination and weakness to properly understand the situation in the country. This is bolstered by what happened in the aftermath of the Oromia protests: the Federal Government and the Regional Government were giving different explanations and solutions to the problem. There was manifest deficiency in coordination. These are just anecdotes of the troubles simmering in the country.
As an aspect of bad governance, corruption is making unscrupulous bureaucrats and businessmen millionaires from nothing. Flawed policies, including loose ethnic federal arrangement, are adding salt to the injury. These policies, though professed to be pro-poor, are advancing the interests of few cronies and party affiliates. As Jacey Fortin writes in The Africa Report of 9 March 2015 about “Addis Millionaires Club”, the number of dollar millionaires in Ethiopia is on the rise quickly while the the number of people getting poorer is also on the rise. This contradiction and disparity, caused by cronyism, nepotism and rent-seeking politicians and businesses is strangling the country impeding and frustrating free and fair competition.
The number of grand corruptions being exposed is shocking the public conscience, with a good case in point being that of the former minister in charge of national revenue and customs and his aides and staff in 2013. That fear is compounded by the fact that corruptions are only exposed when there is political fallout.
The state of bad governance in the country is exacerbated by the unfettered ethnic political formations that are operating under a Front, the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF). This loose ethnic political formation is making difficult for the center to pull together. The different parties forming the Front are kings unto their respective Regions and are pulling the country apart. This is making control of corruption and bad governance extremely difficult and is creating more conflict than it resolves. This is being taken advantage of by irredentist movements, terrorists and others who wish to either overthrow the Government or create havoc in the country. Bad governance is mainly responsible for the several conflicts manifested in recent months allover the country.
As noted above, all of these are exacerbated by the prevailing poverty and food insecurity problem. The dissatisfaction and disgruntlement is rising and people need to vent their anger. However, the Government is not positive to comments ad criticism. Those who wish to oppose have to choose to trade expressing their opinion with loss of their freedom and liberty guaranteed in the constitution. Although the country is party to several international human rights conventions and covenants, they are manifestly disregarded by the regime. This adds salt to injury as it exacerbates bad governance.
Human rights defenders have reported time and again that citizens are being persecuted for having a different opinion an stand to that of the Government. Obviously, not everyone can be expected to defend the Government line. This divisive thinking that “if you are not with us, you are against us” is a recipe for disaster. Criticisms and opposing voices need to be nurtured. The Constitution is very clear about fundamental human rights and freedoms including freedom of expression. Respecting it is not an option. It’s mandatory.
Thus, there is need for the country to embrace democracy to effectively fight poverty and bad governance. It’s usually professed by the regime that democracy is an existential issue for Ethiopia, but it is not practiced. The country has become practically a one-party state. In the last national election in May 2015, the ruling party won 100% of votes raising several questions: why do we have all these protests and conflicts in the country ranging from opposition to development projects to implementation of government policies to identity issues etc in a space for a few months? After a quarter-century in power, it is clear that the policies are not serving the country well. It’s time to walk the talk and introduce improvements, even if that means amending the Constitution. There is need to fundamentally rethink the process of democratization in Ethiopia.
If the Government does not become responsive to such critical issues, the little development witnessed over the last few years seems to be at risk. The situation is bleak. There is need for democratization, good governance, taming the ethnic agenda and dismantling corruption. With elementary school pupils taking part in protests and being killed in public by security forces, the writing is on the wall: “prevention is better than cure”.
+++++++


*Getahun S. Gesso is an international lawyer with specializations in international development laws and peace and security matters in Africa. 

Thursday, July 28, 2016

የፊታችን እሁድ ጎንደር ከተማ ላይ ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ሁሉም አማራ እንዲዘጋጅ ጥሪ ተደረገ: -

July 28,2016
በወልቃይት የአማራ ማንነት ላይ ያነጣጠረውን የህወሓት ጥቃት ለመቃዎም እሁድ ሃምሌ 24 2008 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ይካሄዳል ። በጎንደር እና አካባቢዋ ያለ ማንኛውም የአማራ ተወላጅ እና የአማራ ህዝብ ወዳጅ ይህን ሰላማዊ ሰለፍ እንዲቀላቀል ጥሪ ተላልፏል ። ህፃን፣አዛውንት ፣ ወጣት ፣ ሴት ፣ወንድ… ሳይል ሁሉም አማራ በአንድ ላይ ስለ አማራነቱ  ድምፁን ለማሰማት ወደ አደባባይ እንዲወጣ የሰልፉ አዘጋጆች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የሰልፉ አስተባባሪዎች አያይዘውም ይህን ሰልፍ የሚመራው እና የሚያስተባብረው ሰፊው የአማራ ህዝብ እንደሆነ ገልፀዋል።

ሰልፉ ፍፁም ጨዋነትን እና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ መሆን እንዳለበት የሰልፉ አስተባባሪዎች ለአማራ ህዝብ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ህግ አስከባሪዎች  ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ጥበቃ እንዲያደርጉም ጥሪ ተላልፎላቸዋል ።

ከባህርዳር  ጀምሮ ፣ እስቴ፣ ደብረታቦር፣ጋይንት፣ንፋስ መውጫ ሃሙሲት፣ወረታ፣አዲስ ዘመን፣ እንፍራንዝ፣አርባያ በለሳ ፣ ማክሰኝት ፣ ጠዳ ፣ቆላድባ፣ ጯሂት፣ጎርጎራ፣ደልጊ፣ሻውራ፣ እሰይደብር፣ጎይ፣ አፀደ ማ ሪያም ፣ ጋዝጌ፣ ቁንዝላ፣ሽንፋ፣ደለጎ፣መተማ፣ሽኸዲ፣ነጋዴ ባህር፣ጨው ድባ፣ጫን ድባ፣ ሰራባ፣ጭልጋ፣ ቡሆና፣አይምባ ፣ሁመራ ፣ አብደራፊ፣ሳንጃ ፣ዳንሻ ፣ሰሮቃ፣ሙሴ ባንብ፣ትክልድንጋይ ፣ ሸንበቂት፣አምባ ጊዬርጊስ፣ገደብጌ፣ዳባት፣ደባርቅ ፣ድብ ባህር ፣  ዘሪማ ፣አዲ አርቃይ ፣ ስሜን ጃናሞራ …እና በእነዚህ አካባቢ ያሉ ሌሎች የገጠር ቀበሌ ኗሪዎች ወደ ጎንደር በመዝለቅ የሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ጥሪ ተላልፎላቸዋል ። ከጎንደር ራቅ ብሎ ያለ ማንኛውም አማራም ቢሆን አቅሙ ከፈቀደለት ሰላማዊ ሰልፉን እንዲቀላቀል አማራዊ ጥሪ ተላልፎለታል።

#የአማራ_ተጋድሎ

#AmharaResistance

#ቤተ_አማራ

Tuesday, July 26, 2016

ሕወሃት በወልቃይት ተወላጆች ላይ ያደረሰው ግፍና ጭፍጨፋ በዓይን ምስክር እንዲህ ነበር የተገለጸው

July 26,2016
13754669_10155016003415744_8078283661722118718_nወልቃይት በጉልበት ወደ ትግራይ ክልል ሢከለል ለምን ይሆናል ያሉና የተቃወሙ ወጣቶች ላይ የደረሠውን ግፍ አንድ ወታደር እንደሚከተለው ተናግሮ ነበር።በመጀመሪያ ወጣቶቹ ከወልቃይት ተጭነው ወደ ትግራይ ተወሠዱ። ከዚያም እጅና እግራቸው ታጥፎ ተሠበረ። በዚህ ሁኔታ ለሀምሣ ቀናት እራቁታቸውን አንድ ቤት ውሥጥ ተዘግቶባቸው በቀን አንድ ዳቦ ከብዙ ዱላ ጋር እየተሠጣቸው እንዲቆዩ ተደረገ።ሀምሣ ቀን ሙሉ ከዚያ ቤት አልወጡም።

በሀምሣኛው ቀን አንድ የጭነት መኪና መጣና ወጣቶቹ ተዘግተውበት የነበረው ቤት ተከፈተ።በወቅቱ በአካባቢው የነበረውን ሽታ በቃላት ለመግለጽ አዳጋች ነው። ወጣቶቹ በጣም ከመክሣታቸው የተነሣ ወታደሮቹ በአንድ እጃቸው ጸጉራቸውን አንጠልጥለው ወደ መኪናው ይወረውሯቸው ነበር። አንደኛውን ወጣት ጸጉሩን ይዞ ሢወረውረው ጸጉሩ ተነቅሎ ወደቀ። ያንን ሥመለከት ሠው ሆኘ መፈጠሬን ጠላሁት። ወጣቶቹን ጭኖ የሄደው መኪና ማታ አካባቢ ባዶውን ተመለሠ።

ወጣቶቹን እንደገደሏቸው ባውቅም ከዚያ ሁሉ ሥቃይ መሞት እንደሚሻላቸው በመረዳቴ ደሥ አለኝ። ቢሆንም ግን ይህ ድርጊት በአእምሮየ እየተመላለሠ ሥለረበሸኝ ከሥራየ ልለቅ ችያለሁ።በወቅቱ ይህ ሁሉ የሚፈጸመው በትግራይ ክልል ፕሬዘዳንት በገብሩ አሥራት ቀጥተኛ ትእዛዝ ነበር።

Monday, July 25, 2016

The Ethiopian People will shrink the TPLF power space in much faster speed than the regime anticipated (OFC-ISG)

July 24,2016
WoyaneIt is very promising to see that the people of Ethiopia finally coming to common sense of terms as to how to deal with a dictatorial regime which seems only listen to the people by losing rather than soothing. For the last 25 years, TPLF/EPRDF had been enjoying the disconnection of the people of Ethiopia by TPLF’s rhetoric of deception, false promissory note to the poor, and flip flopping to stay in power term after term in every election season.
It is a factual conclusion that TPLF/EPRDF comes to power after a long civil war,  which the Ethiopian people get frustrated with  fighting Eritrean rebel force (EPLF) in Eritrea, hopping that anyone who comes to power after the Military ruler will provide the Ethiopian people at least basic freedoms, rights and economic justice. For the last 25 years, the TPLF regime had been robbing tremendous resources from the Ethiopian people to impose its economic power, under the pretext of reconstruction which at times many Ethiopians did not dear to oppose, not because of the fact that the party (TPLF) has come to power by choice, rather by the fact that TPLF contributed a lion share in toppling Mengistu.
Many of the spectators who supported the regime in every means necessary to hold its feet to the ground had been also closely watching if the model of ethnic Federalism really works or fails. If it succeeds, to export the model to other countries for implementation, and if it fails to immediately control and minimize the negative outcome. The country had been literarily became a virtual lab of Ethnic federalism.  Unfortunately, its success and practicality is not proven mainly because of the following major reasons:
  1. The temptation of the TPLF to control regional states economic resources by limitless interference into affairs of regional governments make the Ethnic Federalism in Ethiopia untested. Because most strategic decision for regional governments are made at the center by Federal government and not by regional governments, which clearly show no power sharing.
  2. Absence of historical democratic political culture that motivates citizens to react aggressively to change undisciplined government in unisons.
  3. Complications emerged in regional politics which makes outside political actors to look for dictators that can be used as a shield of fear politics, rather than standing firm in support of democracy, which of course the outcome is witnessed to be unintended consequence.
  4. The failure of the opposition political parties, until recently, before the emergence of MEDRK, to choose meaningful leadership space to unify the Ethiopian people to act in unison and create alternative political force to challenge government, most political groups tag themselves with ethnic politics, the very survival political platform (model) introduced by the TPLF regime itself to prolong its survival and defuse public cohesion among citizens.
Signs of despair:
The TPLF regime is swallowed in cloud of fear, and biting every innocent citizen, in an attempt to foil public anger and frustration. It is trying to use every means possible to detract public attention from mounting pressure and anger to confront the regime, by sending its old political prostitutes in and out to test the move. Although so many things can be said about the regime that keeps the basic rights of 90 Million people hostage, the opposition camp and the people of Ethiopia need to look back onto its past and fix weaknesses, rather than wasting time on blaming the brutality of the regime, which could have been demolished long time ago had Ethiopians acted in unisons and common sense politics of inclusion.  The regime lost sense of government as a responsible institution and acting like a child that cries without reasonable cause, poising itself like a gang losing a battle. Most wise leaders know best times moving out than moving in.
The regime is fueling violence in neighboring countries, and becoming a major make of State terror headquarter, to show its importance over other counties, which are playing meaningful peace keeping missions across Africa. This can be clearly evidenced by the current systemic and calculated ambush happened to the Kenyan battalion in Somalia, to systematically evict Kenyan solders from Somalia, and to manifest Ethiopian Army as the absolute alternative to the international donors to siphon international dollars for troops funding, and to divert attention of the international community from the current human rights abuses at home. The regime is the making and fuelling crisis, to keep itself in lucrative crisis business, and instigating unnecessary clashes to keep itself in business, rather than accomplishing its job as a responsible state institution, mandated working towards lasting peace. This same tactic is applied in South Sudan, where the rebel groups and the Government of south Sudan had been negotiating in the capital Addis Ababa, for over a month, which incurred close to a Million dollar hotel bill, which could have been a two years budget for the country.
Urgent Actions Needed and Opportunities:
It is evident that the TPLF government is involved in outrageous abuse of human right, and the act of atrocity is evidenced by international community, and media out lets. As a principle of pre-screening deployment for any solder/s, for any peace keeping mission, the United Nation (UN) body has the primary responsibility to ensure that any solder or solders that deployed for the peace keeping mission is free of such historical record of abuses. As evidenced by the current atrocity, and blatant unreserved human right abuse and violation of basic freedoms in its own county, and on its own citizens, no Nation should admit any such solders, which lacks proper basic training to respect human right to get deployed for such level of honorable mission, which needs the highest standard of discipline. Therefore, the United Nations, must take a though investigation into this matter, and send investigative team to Ethiopia, to explore genocide currently unfolding in the country. The unholy silence of International Community and its inaction to make meaningful reasonable remedial intervention to resolve a crisis of such large scale, while well informed, is below standard and manifestation of unprofessionalism, which draws reasonable suspicions on all Ethiopians, as to the impartiality, and integrity of the UN body that meant to act as a watch dog of basic freedoms.The worst failure of responsibility is to desperately attempt to use irresponsibles.   
“Oromo Protests” in line with National Quest for freedom and basic rights of All Ethiopians:
Our Nation is witnessing a greatest move in defending basic freedoms and sizeable opportunities, recently and at the same time opportunity to work on the rest of the assignments overlooked to get things done together. There is no movement in our Nation’s history that symbolizes people’s quest for basic freedoms, and rights than the Oromo Protests, just simply because it is initiated by the very victim- The Oromo people itself, and other Nations and Nationalities in Ethiopia. This is the great opportunity for both stake holders- the Oromo people, who is demanding and in defense of their basic rights and freedoms on the one hand, and other citizens of Ethiopia, who need to maintain and build a much better union on the other hand. Active participation of all citizens in the process is not only the remedial action to change the current status quo, but also an opportunity to create a strong Ethiopia, and better future to change our political culture and create a better perfect union. No citizens spared of death, abuse and humiliation by the current Ethiopian regime and it must end by concerted effort of all Ethiopians. A change is good change if all finds themselves in the process and build reasonable confidence in the future. Therefore Ethiopians should and must act in unisons to put an end to injustice by common and concerted actions, and show utmost level of determination to put this call into actions.
Conclusion:
Our political leadership should not be gauged by how deep we dig the grave of history, rather how strong we build the future of our country. All the ethnic and non-ethnic political parties in the country should be and must be willing to work together by eliciting innovative leadership models, by coming together and engage in politics of compromise and act in unisons to demolish the long lasted era of robbery in our nation’s history, and should foil systemic distancing of regional parties from the central power, by miss characterizing their political agendas and limiting their demands to regional levels.
Opposition political groups have to form unifying political campaign coordination committee to pull the public opinion together, and act in the domain of public interest, to woo their electorates, manifest capable leadership, and show their alternative position, and rebuild public confidence. This action will be an excellent lesson for the ruling body not to use any preemptive actions on political parties regardless of their strength or weakness of the. Those political groups who are shying away from engaging themselves in centric politics, because of their past historical political stance should and need to turn the page, because the ruling party is trying to use the euphoria of these groups as an opportunity to miss characterize their intention and political obsolescence, and wants to show itself as the best alternative, by playing a game of fear politics. If we do all we do together, the Ethiopian people will shrink the power space of the TPLF/EPRDF in much faster speed than the regime anticipated. Let us be leaders who defeat the past and win the future.
Winners are those who judged by the people!
OFC-ISG, June 10, 2016

Saturday, July 23, 2016

Ethiopia: The Dangers of TPLF’s Twin Competing Mentality and Gondar Uprising

July 23,2016

TPLF leaders Debretsion Gebremichael and Abay Woldu
TPLF leaders Debretsion Gebremichael and Abay Woldu
It is public knowledge that TPLF started its armed struggle in February 1975 with the sole intention of liberating and separating Tigray from Ethiopia. After EPLF pressured TPLF to abandon its objective of fighting for the separation of Tigray from Ethiopia and TPLF’s own understanding that only a radical change in Ethiopia can bring peace to Tigray, it put its original objective of the cessation of Tigray from Ethiopia to the back burner and started working for regime change in Ethiopia. However, in reality TPLF did not abandon the long preached dream of having an independent Tigray. In fact, for TPLF working for regime change in Ethiopia was considered as a good opportunity to prepare Tigray for an independent state. There are so many evidences that point to the latter argument. To mention some of them:
  1. During the late 1980’s whenever TPLF controlled cities in Wollo, Gojam, Gondar and later in Showa, it continued to loot public facilities such as buses, generators, tractors and even school desks and chairs and transported them to Tigray. When TPLF controlled Addis Ababa in 1991 every Tigrian who was returning from Addis Ababa to Mekelle was asked to take a car and drop it in Mekelle. As a result, big stores that were used by charity organizations to store grain around Mekelle before 1991 were filled with looted cars, buses, generators and even hospital equipment’s and ambulances.
  2. A big arm depot was prepared and all Armaments from all over Ethiopia was collected, transported and stored in a place called Endayesus, Mekelle.
  3. Coffee was stolen from Southern Ethiopia and exported through Massawa. In fact, when the border war between Eritrea and Ethiopia started in 1998, EPLF was able to capture a looted coffee storage area around Zalambassa.
  4. The strongest evidence that supports the claim that TPLF did not abandon its dream for an independent Tigrai was its interest for Tigray to have access to Sudan and the red sea. While incorporating Wolkaite into Tigray was done easily, having access to the red sea was set as a long term agenda. The surprising part of TPLF’s claim to Wolakite as part of Tigrai was the Tigrina name of the villages in Wollkaite. The truth is before 1991 Wolkaite had little or no contact with Tigrai. The connection was with Eritrea and the tigrina names came because many Eritreans use to travel and live in these areas. There was road connection between Wolkaite and Eritrea but not between wolkaite and Tigrai. Although telling the truth is not in TPLF’s culture, Mengesha Seyoum who was the administrator of Tigrai during the Haileslassie regime unambiguously told TPLF that Wolkaite has never been part of Tigrai. Yet the Twin Mentality TPLF considers such truth as an obstacle to its hidden agenda.
  5. To facilitate the cessation of Tigrai from Ethiopia at a later date, TPLF insisted on including article 39 in the so called Ethiopian constitution.
Given the above evidences and incidents, the people of Gondar and for that matter the people of Ethiopia have strong reason not to trust TPLF. For them TPLF is an ethnocentric looting army with no regard to the people of Ethiopia. Superficially it preaches every state (killil) has a right to administer itself and take care of its affairs. Yet the people who are running or controlling these states are either local TPLF agents or Tigreans. Moreover, almost all federal ministries including the security, defense and foreign are controlled by trusted TPLF agents of Tigrean origin. After the expulsion of Eritreans from Ethiopia in 1998 all economic sectors are controlled by TPLF affiliated Tigreans. Hence at the center of the current turmoil in Ethiopia, whether it is in Oromia or Amhara, is TPLF’s Twin Competing Mentality. To be a government in Ethiopia and use Ethiopian resources to prepare Tigray for cessation. That includes the war with Eritrea.
After 25 years of repression, killing and humiliation of Ethiopians by TPLF goons the dangers of TPLF’s twin mentality is unraveling in Oromo, Amhara and other places in Ethiopia. There no question that the recent public uprising in Ethiopia will facilitate the down fall of the ethnocentric regime in Ethiopia. Hence it time for all Ethiopians to think beyond the horizon. What kind of Ethiopia do they want to see after the down fall of TPLF?
Victory to the masses.
Source: MADOTE

Wednesday, July 20, 2016

ከሸዋ ክፍለ ሐገር ሕዝብ ለጀግናው የጎንደር-በጌምድር ክፍለ ሐገር ሕዝብ የተላከ መልዕክት

July 20,2016
ይድረስ ለጀግናው የጎንደር-በጌምድር ክፍለ ሐገር ሕዝብ፤
ጠላትም ወዳጅም እንዲያውቅልን የምንፈልገው በጎንደር ክፍለ ሐገር ውስጥ የአማራ ህዝብ እየከፈለ ያለውን መስዋዕትነት ማለትም “አማራነቴን አልነጠቅም” ተጋድሎ ለሁላችንም ለአማራነት ማረጋገጫ በመከፈል ላይ ያለ መስዋትነት እንደሆነ እንገነዘባለን። እኛ የሸዋ አማራዎች ከሽማግሌ እስከ ወጣት አካላችን ሸዋ ቢሆን ላንዲት ደቂቃ እንኳን ጎንደርን ብሎም መላውን የአማራን ግዛት የማናስብበት ጊዜ የለም።
Amhara
የጎንደር ጀግኖች ሆይ ከጎናችሁ ነን። እስከመጨረሻው የአማራ የነጻነት ቀን አብረን ለመዋደቅ ዝግጁ ነን። ዝግጅትም ጨርሰን እንገኛለን። እናንተን ለማገዝ ጎንደር መሄድ ሊያስፈልገንም ወይም ላያስፈልገንም ይችላል። በወያኔ ላይ የምናደርገው እንቅስቃሴና የመልስ ምት መጠኑም ሆነ ስፋቱ በጎንደር ውስጥ በሚኖሩት ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ እንዲሁም የጎንደር ህዝብ በሚያደርግልን ጥሪ ይወሰናል። ስለሆነም እኛ የሸዋ አማራዎች በተወካዮቻችን አማካይነት ለሁለት ቀናት ባንዲት ታሪካዊ ቦታ ተሰባስበን ከልብ ቆርጠን የትግል መላ መተን ከጎንደር አማራዎች ጎን መሆናችንን እናረጋግጣለን ።
ትግሉን የጎንደር አማሮች ጀመሩት እንጂ እኛም ጫፍ ላይ ነበርን። ወያኔ የስልጣን ማማ ላይ ከተቆናጠጠበት ከሃያ አምስት ዓመት አንስቶ የሸዋ ህዝብም ላይ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ በደልና ግፍ በወያኔ ተፈጽሞብናልና። ጠላትም ሆነ ወነ ወጃጅ ሊያውቀው የሚገባው ታላቅ ቁም ነገር ጎንደርን ለመታደግ የሸዋ አርበኞች ጎንደር ድረስ መሄድ ላያስፈልጋቸው ይችላል። እጃችን መዳፍ ውስጥ ያሉ ወያኔዎችን አመድ የሚያረጉ ከባድ የእርምጃ ስልቶች አሉን። በወያኔዎች ላይ የምንወስዳቸው እርምጃዎች አብዛኛዎቹ በተለያዩ ቦታዎችና በሁሉም ቦታዎች በተመሳሳይ ሰዓትና ደቂቃ የሚደረጉ ሳይታሰቡ እንደ እሳተ ገሞራ የሚፈነዱ ናቸው። ሁላችንም በስብሰባችን ፍጻሜ በወያኔ ላይ የማያዳግም አይቀጡ ቅጣት ለመውሰድ ተማምለናል።
አጥንታችንና ደማችን የሆነው የጎንደር ሕዝብ በወያኔ ላይ በወሰደው እርምጃ በጣም የኮራን ስንሆን በሸዋ “የነ አይምሬ” መነሳሳት ከምንግዜውም በላይ ያስደስታል። ከጎጃምና ወሎ ክፍላተ ሐገሮች ጀግኖችም ጋር እየተመካከርን ነው።እያነጠለ ከሚጨርሰን አብረን ተነስተን እንደ አባቶቻችን በአንድ ላይ በመሆን ቅኝ ገዢውንና ወራሪውን ወያኔን እናወድመዋለን!
ሐምሌ ፲፪ ቀን ፪ሺ፰ ዓ.ም
ሸዋ፣ ኢትዮጵያ

Tuesday, July 19, 2016

በጎንደር በረከት ስምኦን ለወያኔ ኣለቆቹ ውድቀታችንን አታፋጥኑ ሲል ካሳ ተክለብርሃን ሕወሓትን አያንቆለጳጰሰ ነው።

July 19,2016
 Minilik Salsawi ጎንደር፡ ዛሬ አንደተጠበቀው የብአዴን ኣና የትግሬ ፌድራሎች ስብሰባችዉን ጨርሰዋል፡፡ መግለጫም ከስብሰባዉ በሁላ የክልሉ መንግስት አዉጥቷል፡፡ መግለጫው ከወያኔ የተለምዶ ጸባይ አንጻር ስታይ በኔ ግምት መጥፎ ነው የሚባል አይደለም፡፡ ኮ\ል ደመቀ ለግዜው በጎንደር አስርቤት ዘመድ አየጠይቀው ኣንዲቆይ የተስማሙ ሲሆን ፍርድ ቤት ቀርቦ ጉዳዩ ያለምንም ጣልቃ ኣንዲታይ ተስማምተዋል፡፡
አራቱ ወያኔ ያገታችው የኮሚቴ አባሎች ኣንድሁ ወደ ጎንደር ማረሚያ ቤት አንዲመጡ ተስማምተዋል፡፡ብአዴን የትግራይ ክልል አባይ ወልዱ የፈጸመዉን ድርጊት ያለማጎብደድ በምሬት ተናግረዋል፡ ሆኖም ግን ለህዝቡ ሰዎችን ለመያዝ የመጣው ሃይል ለአንድነት ሲባል የፈድራል ኣንደሆነ ተደርጎ ኣንድነገር ተስማምተዋል፡፡ ሁለቱ ከትግራይ መጥተው ክፉኛ የቆሰሉት ትግሬዎች ወደ መቀሌ በሄልኮፕተር ሂደዋል፡፡
ጎንደር ከተማ ንብረታችው የተጎዳባችው ትግሬዎች የከንትባ ተቀባን ቢሮ በብዛት በመግባት ንብረታችንን ያወደሙ ሰዎች ተይዘው ካላየን አንወጣም ብለው ኣስከኣሁን ድረስ መስሪያ ቤቱን ከበው ይገኛሉ፡፡ ንብረታችው ተገምግሞ አንደሚከፈላችው ከንቲባው ቃል ቢገቡም አሻፈረን ብለዋል፡፡ ይህ ጉዳይ ሌላ ችግር ኣንዳፈጥር ተስግቷል፡፡ ስልክ በወያኔ ስለሚጠለፍ አብዛኛዉ ህዝብ ልዩ ጥንቃቄ ኣያደረገ ነው፡፡ ብ አዴን ኣስከአሁን ድረስ የዉስጥ መፍረክረክ ባይታይም ካሳ ተክለብርሃን የተባለው አዉሬ የወያኔ ዋነኛ ሰላይ አንደሆነ ይጠረጠራል፡፡
ሌላው ጉዳይ ትጥቅ ለማስፈታት ወያኔ ኣቅድ ይዟል ሁኔታዉ ከተረጋጋ በሁላ ፡፡ ትጥቅ በጎንደር ባህል ከኑሮ አስፈላጊ ነገሮች አንዱ ኣና ዋነኛው ሲሆን ወያኔ በስልጣን ሰክሮ ባህል መሆኑን ረስቶ ለማስፈታት ቢንደፋደፍ ውጤቱ ወደ ባሰ ቀዉስ መግባት ነው፡፡በረከት ስሞእን አሁንም ሳይፈራ ለወያኔ ኣልቆች የሁላችንን ውድቀት አታፋጥኑ ስል ተማጸኗል ብለዋል።

“ወልቃይትና ጠግዴ በኢትዮጵያ ታሪክ በትግራይ ስር ሆነው አያውቁም” ታሪክ

July 19,2016
"የአማራ ተወላጆች ወልቃይት ጠገዴ ሄደው መኖር ይችላሉ" ቴድሮስ
welkait tsegede

የወልቃይት ጉዳይ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ደም እያፋሰሰ ባለበት በሁኑ ወቅት ቴድሮስ አድሃኖም ወልቃይትን የትግራይ ግዛት አድርገው በመቁጠር “የአማራ ብሔር ተወላጆች ወልቃይት መጥተው መኖር ከፈለጉ የትግራይ ሕዝብ በደስታ ይቀበላቸዋል” በማልተ የትግራይ ሕዝብ ወክለው ስለ ወልቃይት የትግራይ ክልልነት በድፍረት በፌስቡክ ላይ ይህንን ብለዋል – ሙሉው ቃል ከዚህ በታች ይገኛል:-
በጎንደር የተከሰተውን የማንነት ጥያቄ ሰበብ በማድረግ አንዳንድ ግለሰቦች ብጥብጥ ለማስነሣት ቢሞክሩም መንግሥታችን በሰከነ ዘዴ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ሥር አውሎታል:: የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከአማራ ተወላጆች ጋር በመወያየትና በማሳመን የወልቃይትን መሬት የትግራይም ሆኑ የአማራ ተወላጆች በጋራ እንዲኖሩበት በማግባባት ላይ ይገኛል፡፡ ወልቃይት የአማራ ነው በማለት የሚነዛው ፕሮፓጋንዳም የሐሰት መሆኑና ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የታለመ በመሆኑ ሊወገዝ ይገባዋል:: የትግራይ ሕዝብና የአማራ ሕዝብ ለረዥም ጊዜያት በመቻቻልና በመከባበር አብረው የኖሩ በመሆናቸው በጥቂት ግለሰቦች ፍላጎት የሚጣሉ አይደሉም:: የትኛውም ብሔር በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል በመሄድ የመኖር መብት ያለው በመሆኑ የአማራ ብሔር ተወላጆች ወልቃይት ጠገዴ ሄደው ቢኖሩ አንድም የትግራይ ተወላጅ ቅሬታ እንደማይሰማው ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ:: በዚህ አጋጣሚ የትግራይ ሕዝብ አማራ ወንድሞቹን በፍቅር በማየት የተለመደ እንግዳ ተቀባይነቱን በተግባር ማሳየት እንዳለበት ለማሳሰብ እወዳለሁ::ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ለመሆኑ ወልቃይት የማን ነው? Horn Affairs ላይ Ze Addis በሚል መጠሪያ የተጻፈው ከታሪክ ማስረጃ አንጻር ይህንን ይተነትናል

ወልቃይት ላለፉት ሺህ ዓመታት በትግራይ ስር ተዳድራ አታውቅም – የታሪክ ማስረጃዎች

የኢትዮጵያ መንግስት (ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ) አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ከወሰዳቸው ዓብይ ኩነታት አንዱ፤ የሀገሪቱን የፖለቲካን የአስተዳደር ካርታን መቀየሩ እንደሆነ ይታወቃል:: የኢትዮጵያ ክፍላተ ሀገራት ካርታ እ.ኤ.አ. በ1994 ቢቀየርም፤ አዲሱ ካርታ ብዙ የማንነት ጥያቄዎችን አስነስቷል:: ይህ የዳግም መካለል ጥያቄ ከሚነሳባቸው ቦታዎች ውስጥ ወልቃይት አንዱ ነው።
እንዲህ አይነት የማንነትና የመካለል ጥያቄ ሲቀርብ ዋና መፍትሄ የሚሆኑት የታሪክ ሰነዶች ናቸው:: የታሪክ ሰነዶች ስለ ወልቃይት ግን ምን ይላሉ? ላለፉት ብዙ መቶ ዓመታት የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች ምን እንደሚሉ እንመርምር::
1/ ወልቃይት ጠገዴና አላማጣ ኮረም በአጼ ዮሓንስ ዘመን በትግራይ ሥር አልነበሩም የታሪክ ሰነድ ማስረጃ
አጼ ዮሓንስ ከ 1871 ዓ.ም እስከ 1889ዓ.ም (እ.ኤ.ኣ) ኢትዮጵያን የመሩ ንጉስ ናቸው:: ንጉሰ በንግሥና ዘመናቸው የራሳቸው ጠንካራና ደካማ ጎን ቢኖራቸውም፣ ከጠላት ደርቡሽ ጋር በመፋለም ለሀገራቸው ክቡር ሕይወታቸውን የሰጡ ንጉሰ ናቸው:: ጥቂት የማይባሉ የሕወሀት ሰዎች፣ ከወልቃይትና ጠገዴ ጋር በተያያዘም የሚጠቅሱት እሳቸውን ነው:: ወልቃይት እናጠገዴ ፣ ጥንት በአጼ ዮሓንስ ዘመነ መንስግት በትግራይ ስር ነበረች”በማለት እንደ ዋና መከራከርያ ሲያቀርቡት ይደመጣል:: እውነታውን የዘገቡት የታሪክ ሰነዶች ናቸውና የታሪክ ሰነዶችን እንመርምር::
በአጼ ዮሓንስ ዘመን የነበረው የትግራይ ግዛትና፣ አጠቃላዩ የኢትዮጵያ ግዛት ምን እንደሚመስል በዝርዝር በሀገር ውስጥና በውጭ ሊቃውንት ተጽፏል:: ስለ ወልቃይትም አስተዳደር በማን ስር እንደነበረ በዝርዝር ጽፈውታል:: ለዚህም የእውቁን የፈረንሳዊ የጂኦግራፊ ፕሮፌሰር ኤሊስ ሬክለስ መጽሓፍን በዋቢነት መጥቀስ ይቻላል::
በዩንቨርሲቲ ኦፍ ብረስልስ የኮምፓራቲቭ ጂኦግራፊ (University of Brussels, Professor of Comparative Geography) ፕሮፌሰርና የዴፓርትመንቱ ሀላፊ የነበረው ይሄው ፕሮፌሰር ፤ በ1880 ጀምሮ በርካታ መጽሓፎችን በዓለም ጂኦግራፊ ላይ ጽፏል:: እነዚህም መጽሓፍቱ ከለንደንና ፓሪስ ጆኦግራፊካል ሶሳይቲ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ አድርገውታል::
ከነዚህ መጻሕፍት አንዱ በ 1880 የተጻፈው The Earth and its Inhabitants የሚለው ሲሆን፤ ዘጠኝ ተከታታይ ክፍሎች አሉት። የዚሁ መጽሓፍ ክፍል አራት በገጽ 443 ላይ የሰሜን እና ምስራቅ አፍሪካን የወቅቱን ጂኦግራፊ በዝርዝር ይተነትናል:: በአጼ ዮሓንስ ዘመን የነበረውንም የኢትዮጵያን ክፍላተ ሀገራት በዝርዝር ቁልጭ አድርጎ እንዲህ ጽፎታል::
“The Amhara government provinces are: Dembia, Chelga, Yantangera, Dagossa, Kuarra, Begemidir, Guna, Saint, Wadla, Delanta, Woggera, Simen, Tselemt, Armachiho,Tsegede, Kolla Wogerra፣ Waldiba and Wolkait”
Table - Tigray territories from the book - The Earth and its Inhabitants
Table – Tigray territories from the book – The Earth and its Inhabitants
ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ይህ ጽሁፍ የተጻፈው በ1880ዎቹ አጼ ዮሃንስ የሀገሪቱ ንጉስ በነበሩበት ዘመንና የተጻፈውም በግዜው ከነበሩ ከተለያዩ የጂኦግራፊካል ሶሳይቲዎች የወርቅ ሜዳይ ተሸላሚ በሆነ ባለሙያ ፕሮፌሰር ነው:: ይህ በ1880ዎቹ የተጻፈው መጽሓፍ እንደሚያስረዳው በአጼ ዮሓንስ ዘመን ወልቃይት: ጠለምት : ዋልድባ : አላማጣ : በሙሉ በትግራይ ስር አልነበሩም:: እነዚህን ቦታዎች በስም ጠቅሶ እንደሚነግረን በትግራይ ስር ሳይሆን በጎንደር ስር ነበሩ::
“በአጼ ዮሓንስ ዘመን ወልቃይትና ጠግዴ በትግራይ ስር ስለነበሩ ነው አሁን ወደ ትግራይ የጠቀለልናቸው ” የሚለው መሰረት የሌለው መሆኑን ይሄ መረጃ ያሳየናል:: ከአጼ ዮሓንስ በፊትስ እነዚህ ቦታዎች ይተዳደሩ የነበሩት በማን ነው? የሚለውን እንመልከት። ወደ አጼ ቴዎድሮስ ዘመን እንጓዝ፡፡
2/ በኣጼ ቴዎድሮስም ዘመን ወልቃይት ጠገዴ በትግራይ ስር አልነበሩም – የታሪክ ማስረጃ ሰነዶች
በኣጼ ቴዎድሮስ (1818 – 1868 እ.ኤ.አ) የነበሩ ስመ ገናና ኢትዮጵያዊ ንጉስ ነበሩ:: በየቦታው የነበሩ መሳፍንትን አሸንፈው፣ ማዕላዊ መንግስት ከመሰረቱ በኋላ፣ ቀጣይ ራዕያቸው የምዕራብያውያንን ቴክኖሎጂ እዚሁ ኢትዮጵያ እንዲመረት ማድረግ ነበር:: ለዚህም ከበርካታ አውሮፓ ሀገራት ጋር ግንኙነት መስርተው ነበር:: የአውሮፓውያን ጥበበኞችን ኢትዮጵያ ለማስቀረት እና ጥብቅ ግንኑነት ለመመስረት፣ አጼ ቴዎድሮስ ልጃቸውን ለአንድ ስዊስ ኢንጂነር እስከመዳር ደርሰው ነበር:: በዚህም ምክንያት በርካታ አውሮፓውያን ጠቢባን በአጼ ቴዎድሮስ ዘመን ኢትዮጵያ መጥተዋል:: እነዚህም ባለሙያዎች ኢትዮጵያ መጥተው ስለ ሀገሪቱ በዝርዝር ጽፈዋአል:: የእንግሊዝ መንግስትና የኢትዮጵያ ግንኑነት መሻከር ሲጀምር፣ እንግሊዞች ስለኢትዮጵያ ይበልጥ የማወቅ ፍላጎታቸው ጨመረ::
የእንግሊዝ መንግስት የintelligence ሰዎችም የእንግሊዝ መንግስት ፓርላማና የጸጥታው ኃይል ኢትዮጵያን በሚገባ ያውቃት ዘንድ ትዕዛዝ ወጣ:: የእንግሊዙ Topographical and Statistical Department of The War Office ኤ . ሲ ኩክ (A. C. Cook) በተባለ እንግሊዛዊ ኮሎነል አማኻኝነት ስለ ኢትዮጵያ ከ15ኛው ክፍለ ዘመን ጀመሮ በተለያዩ እውሮፓውያን ተጻፉ መጻሕፍት ባንድ ላይ እንዲጠርዘ ተደረገ:: የሚደንቀው ይሄ መጽሓፍ በ 1867 ዓ.ም እ.ኤ.ኣ የታተመው በግስቲቷ ጥያቄ ለእንግሊዝ ሀውስ ኦፍ ኮመን ሎወር ሀውስ ግብአት (House of Common lower House) ይውል ዘንድ መሆኑ ነው:: በዚሁ መጽሓፍ ውስጥ፤ የወቅቱ የኢትዮጵያ ዝርዝር ጉዳይ ተጽፏል:: ይሄውም መጽሓፍ ስለ ወልቃይትና ጠገዴም በኣጼ ቴዎድሮስም ይሁን ከሳቸው በፊት በማን ስር ይተዳደሩ እንደነበር በዝርዝር ያትታል::
“The Provinces of Amhara are : Simen, Waldibba, Wolkait,Wogera,Chilga, Kuara, Belesa, Fogerra, Damot, Gojjam, Begemidir, Beshilo ….. Waldiba situated to the NW of Semein between the Tekeze and the Angereb, extends as far as the junction of the two rivers. Welkait is to the west Of Waldiba it is intersected through its whole length by the two river tekuar and guang. It is more wooded than waldiba..” (Routes in Abyssinia (printed in 1867 G.C) page 188)
ይሄው ታሪካዊ መጽሓፍ በወቅቱ የነበረውንም የትግራይ ክፍለሀገር ድንበር እና ግዛት እነማን እንደነበሩ በማያሻማ ቋንቋ እንዲህ ይነግረናል፡፡
“The territory of Tigre whose capital is Adwa, is bounded on the West by Shire, on the Southwest by Temben and Adet on the South by Geralta on the South –East by Haramat, on the East by Agame, and on the North by the rivers of Mereb and Belessa”
የትግራይ ግዛትስ? ብሎ ለሚጠይቅ ወገን ፤ ይሄው መጽሓፍ በወቅቱ የነበርቸው ትግራይ ምን እንደምትመስል እንዲህ ሲል አስፍሮታል በዚሁ መጽሓፍ ላይ ገጽ 187 – 188 የትግራይን ግዛት እንዲህ ሲል ይገልጸዋል
“The territory of Tigray whose capital is Adwa is bounded on the west by Shire, on the south west by Temben and Adet, on the south by Geralta, on the South East by Haramat, on the East by Agamae, and on the North by the Rivers Mereb and Belessa”
Map - northern Ethiopia areas
Map – northern Ethiopia areas
እዚህ ላይ በ 18ተኛው ክፍለ ዘመን የትግራይን ወሰኖች በማያሻማ ሁኔታ በግልጽ አስቀምጦታል:: የትግራይ ወሰን በምዕራብ – ሽሬ ፤ በምዕራብ ደቡብ – ተምቤን እና አዴት ፤ በደቡብ – ገር አልታ ፤ በምስራቅ – አጋሜ ፤በሰሜን – መረብና በለሳ ናቸው:: የታሪክ ሰነዶች በአጼ ቴዎድሮስም ዘመን እንደሚነግረን ፤ ወልቃይትና ጠገዴ በትግራይ ስር አልነበሩም::
ከዛስ በፊት ወልቃይትና ጠገዴ በትግራይ ስር ነበሩን? አሁንም የታሪክ ሰነድ እንመርምር::
3/ በዘመነ መሳፍንት ዘመንም ወልቃይትጠገዴ በትግራይ ስር አልነበሩም – የታሪክ ማስረጃ ሰነዶች
እንደሚታወቀው ከአጼ ኢዮአስ ሞት ጀምሮ ፤ አጼ ቴዎድሮስ እስኪነሱ የነበረው ዘመን ዘመነ መሳፍንት ይባላል:: በዚህ ዘመን ኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት አልነበራትም:: መሳፍንቶች የገነኑበትና በሀገሪቱ ማዕከላዊ አስተዳደር የጠፋበት ዘመን ነበር:: በዚህ ማዕከላዊ የመንግስት ሕግ በሌለበት ወቅት እንኳን ወልቃይት፥ጠገዴ፥ ዋልድባ ፥ አላማጣ፥ ኮረም እና የመሳሰሉ ቦታዎች በትግራይ ስር አልነበሩም:: አሁንም ማስረጃ እነሆ!
ጀምስ ብሩስ የተባለው ስኮትላንዳዊ ፥ በዘመነ መሳፍንት ኢትዮጵያ መጥቶ ኢትዮጵያ በዘመነ መሳፍንት ምን ትመስል እንደበረ፥ ቁልጭ አድርጎ አስቀምጦታል:: እያንዳንዱ መስፍን ግዛቱ የት ድረስ እንደነበረ፥ የትኛው መስፍን ማንን ይገዛ እንደነበረ በሰፊው ተንትኖታል:: በዚህም መሰረት ስለ ትግራይ ግዛትና እንዲህ ሲል ምስክርነቱን ይሰጣል :: Travel to discover source of the Nile Volume 3 page 582 ላይ
“Tigre is bounded by the territory of the Bahirenegash that is by the river Mereb on the East and Taccazze upon the west. It is about one hundred and twenty miles broad from E. to W. and two hundred from N. to S. “
ጀምስ ብሩስ በዚሁ መጽሓፉ Chapter 10 ላይ Geographical division of Abyssinia into province በሚለው አንቀጹ ላይ በይበልጥ ቁልጭ አድርጎ እንዲህ ያስቀምጠዋል
The first division is called Tigre, between Red Sea and the river Tekeze. Between that River (Tekeze) and the Nile Westwards where it bounds the Oromo, it is called Amhara.
ካለ በኋላ ወረድ ብሎ ይበልጥ ጉዳዩን ሲያስረዳ “Tekezze is the natural boundary between Tigre and Amhara”
ከላይ ለአብነት ያስቀመጥኳቸው ሊቃውንት በግዜ፣ በቦታና በዜግነት አይገናኙም:: ለምሳሌ በአጼ ዮሓንስ ዘመን የነበረው አሊስ ሬክለስ ፈረንሳዊ (French) ነው:: በአጼ ቴዎድሮስ ዘመን የነበረውን የኢትዮጵያ ግዛት የጻፈው ደግሞ እንግሊዛዊ ነው (British):: ጀምስ ብሩስ ደግሞ ስኮትሽ (Scottish)ነው:: ግን ሁሉም በተለያየ ግዜ መጥተው ያዩትና የተገነዘቡትን ጽፈዋል:: የሚናገሩት አንድ ና ተመሳሳይ ነው:: እውነት ምን ግዜም አንድ ናትና!
4/ ወልቃይት በ1630ዎቹስ በማን ስር ነበረች?
በ16ኛው መቶ አጋማሽ ላይ ያሉ ያታሪክ መዛግብትም የሚናገሩት ተመሳሳይ ነገር ነው:: በተለያዩ ወገኖች ተደጋግሞ የሚጠቀሰው የ ማኑኤል በሬዳም መጽሓፍ የሚተነትነው ያንኑ ነው:: ይሄ መጽሓፍ የተጻፈው በ1634 ሲሆን ጸሓፊውም ኢማኑኤል በሬዳ ይባላል:: በወቅቱ የነበረውን የትግራይ ግዛት በዝርዝር አስቀምጧል:: እሱም እንደሌሎቹ ጸሓፍት የትግራይ ድንበር ተከዜ እንጂ ተከዜን ተሻግረው ያሉት ወልቃይትና ጠገዴ ናቸው አይልም::
«Tractatus tres historico-geographici (1634): A seventeenth century historical and geographical account of Tigray, Ethiopia (Aethiopistische Forschungen) 1634» መጽሀፍ የመጀመሪያ ምዕራፍ ስለ ትግራይ ግዛት እንዲህ ይላል::
“Among all the kingdoms that the Emperor of Ethiopia possesses today one of the greatest if not the greatest and the most important is the kingdom Tigre. From north to south, that is from the limits of the Hamasen to Enderta, it covers an areas of from ninety to one hundred leagues (3.2 miles); and from the east, which is besides Dancali, located at the entrance to the Red sea to the southern end of the Red Sea, to the west bounded by the Tekezze River beside the Semen, it covers an area of similar size, so that the Kingdom has a nearly circular shape.”
አሁንም ወደኋላ እየራቅን እንሂድና ወልቃይት ጠገዴ በነ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን በማን ስር ነበርች? የሚለውን እንመልከት
5/ በኣጼ ዘርዓ ያዕቆብ ( 14ኛው ክፍለ ዘመን) ዘመንም ወልቃይትጠገዴ በትግራይ ስር አልነበሩም – የታሪክ ማስረጃ ሰነዶች
አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በኢትዮጵያ ታሪክ ከተነሱ ሃያልና ሊቅ ነገስታት ውስጥ አንዱ ነበሩ:: በቀድሞ ስሙ ፈጠጋር በአሁን ስሙ ኦሮሚያ አዋሽ ወንዝ አካባቢ የተወለዱት አጼ ዘርዓ ያዕቆብ፥ የሀድያ ሲዳሞ ንጉስ ልጅ የሆነችውን እሌኒን አግብተው፥ በ37 ዓመታቸው ከነገሱ ጀምሮ በርካታ ዓበይት ስራዎችን አከናውነው አልፈዋል:: እኒሁ ንጉስ ከፍተኛ የጥበብ ፍቅር የነበራቸውና ከመሆናቸው ባሻገር፥ ራሳቸው ብዙ መጻሕፍትን ጽፈዋል:: በሳቸው ዘመንም ብዙ መጻሕፍት እንዲጻፉ ድጋፍ በመስጠታቸው አያሌ መጻሕፍት በሳቸው ዘመን ተጽፈዋል:: ከነዚህ መጻሓፍት አንዱ በአክሱም ንቡረ ዕድ የተጻፈው ዜና አክሱም መጽሃፍ አንዱ ነው:: ዜና አክሱም ከሃይማኖያትዊ ሐተታው ባለፈ ስለ 14ኛዋ ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ በዝርዝር ጽፎታል:: ይህ መጽሓፍ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ወሰንና ታሪክ ብቻ ሳይሆን የክፍላተ ሀገራቱንም ድንበር ጥንቅቅ አድርጎ ዘግቦታል:: የትግራይንም ክልል በካርታና በጽሁፍ ከዚህ እንደሚከተለው ይገልጸዋል::
Chart - List of Tigrai areas on Zena Axum book
Chart – List of Tigrai areas on Zena Axum book
ይህም መጽሓፍ በተመሳሳይ መልኩ የሚነግረን፣ ወልቃይትና ጠገዴ በፍጹም ፣ የትግራይ አካል አንዳልነበሩ ነው::
ዮሓንስ መኮንን Ethiopia: the land, its people , History and Culture በሚለው መጽሓፉ Page 351 በአጼ ዘርዓ ያ ዕቆብ ዘመነ መንግስት የነበረውንና በመጽሓፍ አክሱም የተተነተውን የትግራይን ካርታ እንዲህ ያቀርበዋል
“The Book of Axum.. Shows a traditional schematic map of Tigray with its city Axum at its center surrounded by the thirteen principal provinces: Tembein, Shire, Seraye, Hamasen, Bur, Sama, Agame, Amba Senait, Geralta, enderta, Sahart and Abergele”
በተመሳሳይ ሁኔታም The World through Maps: A History of Cartography (ገጽ 352 ይመልከቱ)፡፡ በJohn R. Short የተጻፈው የዓለም ጂኦግራፊን የሚተርከው መጽሓፍ በ15ኛው ክፍለዘመን የነበሩ የትግራይ ግዛቶች ከላይ የተጠቀሱት መሆናቸውን መጽሓፈ አክሱምን በመጥቀስ ያስረዳል:: ይህም መጽሓፍ በተመሳሳይ መልኩ የሚነግረን፣ ወልቃይትና ጠገዴ በፍጹም የትግራይ አካል አንዳልነበሩ ነው::
6/ ቋንቋን መሰረት ወዳደረገ ክለላን አንመልከት
የኢትዮጵያውያን ወጣቶችና አርበኞች ቁጣ ያሳሰበው ጣልያን፣ ኢትዮጵያን በቋንቋና በዘር በትኖ ለመግዛት ያቀደውን መርዝ ይፋ አወጣ:: የዚህ እቅድ ፊታውራሪ ከሆኑት አንዱ ፋሺስቱ Baron Roman Prochàzka አቢሲንያ ዘ ፓውደር ባረል (Abyssinia: the Powder barrel) በሚል መጽሓፉ ላይ እንዳስቀመጠው፣ ኢትዮጵያውያንን ለመግዛት በዘር መከፋፈልና በመሀከላቸውም ጥላቻን በመዝራት እርስ በርስ ለማናከስ፣ ሀገራቸውን በዘር መከለል የሚለውን እቅድ መተግበር ጀመረ:: በዚሁም መሰረት፣ ዘርንና ቋንቋን መሰረት ባደረገ ሽንሸና ኢትዮጵያን አምስት ቦታ ከፈላት::
እነዚሁም ክልሎች አማራ: ኤርትራ(ትግሬ); ሐረር: ኦሮሞ-ሲዳማ: ሸዋና ሶማሌ ናቸው:: ጣልያን ይሄንን የግዛት ሽንሸና ሲያካሂድ መሰረት ያደርገው ዘርና ቋንቋን ነበር:: የሚከተለውም ሰማንያ በሃያ የሚለውን መርህ ነበር:: ከሰማንያ በመቶ በላይ ሕዝቡ የሚናገረውን ቋንቋ መሰረት በማድረግ ወደየ ክልሉ ይደለደላል:: ሸዋን ግን ለብቻው ለይቶ መቆጣጠር ይገባል ብሎ በማመኑ ሸዋን ና ሀረርን ለብቻ ለይቶታል:: ወደ ነጥባችን ስንመጣ በዚህ የቋንቋ ሽንሸና መሰረት ወልቃትና ጠገዴና ጠለምት ወደ ትግራይና ኤርትራ አልተካተቱም:: በጎንደር ስር ነበሩ::
እዚህ የጣልያን ቋንቋንና ዘርን መሰረት ያደረገ ካርታ ላይ በግልጽ እንደሚታየው ፣ የትግራይ ድንበት ተከዜ እንጂ – ከተከዜ ተሻግሮ አይደለም:: ላልፉት 25 ዓመታት ተቃዎሞ ሲካሄድባቸው የከረሙት ወልቃይት – ጠገዴ – አላማጣ ኮረም በፍጹም በትግራይ ስር እንዳልነበሩ በግልጽ ያሳየናል::
Map - Tigray during Fascist Italy
Map – Tigray during Fascist Italy
7/ አንዳንድ ሚድያዎች ደጋግመው የሚያነሱት ነጥብ አለ:: ይሄውም ወልቃይት ጸገዴና ሌሎች ወደ ትግራይ የተካለሉ ቦታዎች ጥንት የትግራይ እንደነበሩና አጼ ኃይለ ሥላሴ የምስራቃዊ ትግራይ ገዥ ከነበሩት ከደጃዝማች ኃይለሥላሴ ጉግሳ አርዓያ ጋር በመጣላታቸው – ወልቃይትና ጠገዴን ወደ ጎንደር ወሰዱት የሚል ነው:: ሌላው የማያስማማው ነጥብ ደግሞ – የቀዳማይ ወያኔን አመጽ ምክንያት በማድረግ ትግራይን ለመቅጣት – ወልቃይትንና ጠገዴን ወደ ጎንደር ከለሉት የሚል ነው::
እስካሁን ከላይ የገለጽኳቸው ሰነዶች ለዚህ ነጥብ በቂ ማስረጃ ቢሆኑም : ካርታን መሰረት ያደረገ መረጃ ለሚጠይቅ ሰው – እነሆ:: ይህ ካርታ በጣልያኖች በ1928 ዓ.ም የተሰራ ነው:: ኢትዮጵያን በደምብ ካጠኑ በኋላ ለያንዳንዱ ክፍለሀግር ካርታ ሰርተዋል:: ያኔ ገና ኃይለሥላሴ ጉግሳ አልከዳም:: ያኔ የቀዳማይ እንቅስቃሴ አልነበረም:: የቀዳማይ እንቅስቃሴ በ1943 ነበር፡፡ ይህ ካርታ ግን ከዛ ብዙ ዓመታት በፊት የተሰራ ነው:: አንባቢው አይቶ ይፍረድ:: ወልቃይት ጠገዴን ነጥለን ስንመለት ካርታው ይሄንን ይመስላል::
Map - north west Ethiopia in 1928
Map – north west Ethiopia in 1928
8/ በዘመነ መንግስቱ ኃይለማርያም ወልቃይትና ጠገዴ
በካምብሪጅ ዩንቨርሲቲ በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ይበልጡንም በኢትዮጵያ ታሪክና ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ምርምር ካደሩት ሰዎች ውስጥ በዋነኝነት የሚጠቀሱት ፕሮፌሰር ክሪስቶፈር ክላፓም: እንደ ኤሮፓ አቆጣጠር 1990 ( ህወሀት አዲስ አበባብ ከመያዙ አንድ አመት በፊት) ድንቅ የሆነ መጽሓፍ አሳትመው ነበር:: በዚሁ መጽሓፋቸው ላይም ስለ ወልቃይትና ጠግዴ እንዲህ ሲሉ ይተርኩታል
“the area concerned (welkait -Tsegede) separated from Tigray by impressive natural barrier of Setit Tekezze river has never been governed as part of Tigray at any period in the past, but has come under Gonder and Semein.” (Christopher Clapham: Transformation and continuity in revolutionary Ethiopia (Cambridge: Cambridge university press 1988 pp 259)
ስናጠቃልለው
1. 1420ዎቹ እንደተጻፈ የሚታመነው መጽሓፈ አክሱም በግልጽ እንደሚያሰረዳን የትግራይ ግዛቶችና ወሰኖች 13 ነበሩ:: እነርሱም Tembein, Shire, Seraye, Hamasen, Bur, Sama, Agame, Amba Senait, Geralta, enderta, Sahart and Abergele ናቸው::
ማስረጃ : መጽሓፈ አክሱም , Ethiopia: the Land, Its People, History and Culture By Yohannes Mekonnen. The World through Maps: A History of Cartography (ገጽ 352 ይመልከቱ) By John R. Short
2. 1634 ዓ.ም የተጻፈው የ እማኑኤል በሬዳ መጽሓፍ Tractatus tres historico-geographici (1634): A seventeenth century historical and geographical account of Tigray, Ethiopia (Aethiopistische Forschungen) 1634» እንደሚያስረዳው የትግራይ ወሰን ተከዜ እንጂ ተከዜን ተሻግረው ያሉት ወልቃይትና ጠገዴ አይደሉም
3. በዘመነ መሳፍንት ኢትዮጵያን ጎብኝቶ የነበረው የጀምስ ብሩስ መጽሓፍም በግልጽ የሚናገረው የትግራይ ወሰን ተከዜ እንጂተከዜን ተሻግረው ያሉት ወልቃይትና ጠገዴ አይደሉም፡፡ Travel to discover source of the Nile Volume 3 page 582
4. በአጼ ዮሓንስ ዘመንም የታሪክ ማስረጃዎች የሚያስረግጡት ያንኑ ነው:: የትግራይ ደንበር ተከዜ ነው:; ወልቃይትና ጠገዴ በጎንደር ስር እንደነበሩ በግልጽ ፈረንሳዊው ፕሮፌሰረ ሬክለስ ጽፎታል
5. በአጼ ቴዎድሮስ ዘመንም ወልቃይትም ይህን ጠግዴ በትግራይ ስር አልነበሩም::
6. በጣልያን ግዜም የትግራይ ወሰን በደቡብ እንዳምሆኒ, በደቡብ ምስራቅ አበርገሌ ;በም ዕራብ ሽሬና አዲያቦ ነበሩ እንጂ ወልቃይት ጠግዴ ዋጃ ኮረም እና መሰል ቦታዎች በትግራይ ስር አልነበሩም
7. ወልቃይትንና ጠገዴን ወደ ትግራይ የከለሉት አጼ ኃይለሥላሴ ናቸው:; ይህም በ1943 ዓ.ም የተካሄደውን የቀዳማይ ወያኔን አብዮት ለመበቀልና ሕዝቡንም ለመቅጣት ነው የሚለው: መሰረት እንደሌለው እነሆ ይህ ማስረጃ:: ጣልያን ይሄን ካርታ የሰራው በ1928 ዓ.ም ነበር:: ያኔም በአጼው ግዜም የትግራይ ወሰን ያው ነበር
8. የህዝብ ቁጥርና በሚነገሩት ቋንቋ ነው ወልቃይትንና ጠግዴን ወደ ትግራይ የከለልነው ለሚለውም – የዘርና የቋንቋ ክልልን ለመጀመርያ ግዜ ኢትዮጵያ ላይ የመሰረተው ጣልያን ነው:: ጣልያን ይህን ካርታ ሲሰራ የራሱን የዘርና የቋንቋ ጥናት አድርጎ ነበር:: በዚህም መሰረት ወልቃይትና ጠግዴን ወደ ትግራይ ሳይሆን ያካለላቸው ወደ ጎንደር ነበር:: ይሄ ከሆነ አንድ ትውልድ እንኳን አላለፈው:: ታድያ ያኔ አብላጫ የነበረው ቋንቋና ሕዝብ አሁን ወዴት ገባ?
9. በዚህ ዘመን ያሉ እውቅ የኢይዮጵያ ነክ ፕሮፌሰሮችም ምስክርነታቸው ያው ነው:: የካምብሪጅ ዩኒቨርስቲው ክሪስቶፈር ክላፕማን እንዳጠቃለሉት
“the area concerned ( welkait -Tsegede) separated from Tigray by impressive natural barrier of Setit Tekezze river has never been governed as part of Tigray at any period in the past, but has come under Gonder and Semein.
10. የአጼ ዮሓንስ የልጅ ልጅ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩምም እንዳረጋገጡት ” የትግራይ ወሰን ተከዜ እንጂ ተከዜን ተሻግረው ያሉት ወልቃይትና ጠግዴ አይደሉም”
አሁንም ቢሆን የወልቃይት የማንነት ጠያቂዎች የ ሃምሳ ሺህ ሰው ፊርማ አሰባስበው ነው ፌዴሬሽን ምክር ቤት ድረስ የሄዱት:: እንግዲህ ይሄ ሁሉ ጫና: ወከባና ግድያ ባለበት በዚህ ወቅት ሃምሳ ሺህ ሰው ፊርማ ማሰባሰብ ከቻሉ ነጻነት አግኝተው ሁሉም ቦታ ቢንቀስቀሱ የምን ያህል ሰው ፊርማ ማሰባሰብ እንደሚችሉ መገመቱ ቀላል ነው:: ያለው እውነታ ይሄው ነው::
ማጠቃለያ
አሁንም ከላይ የጠቀስኳቸውን የፕሮፌሰር ክላፕማንን ቋንቋ ልጠቀምና “ወልቃይትና ጠግዴ በኢትዮጵያ ታሪክ በትግራይ ስር ሆነው አያውቁም”:: ለመጀመርያ ግዜ በትግራይ ስር : እንዲካተቱ የተደረገው በ1994 ነው::
እኔን የሚያሳሰበኝ ግን ሌላ ነው:: በአንድ ሀገር ውስጥ ሆነን ስለ ድንበር እያወራን ነው:: ከዚህ የማንነት ጥያቄም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን የሰባዊ መብቶች ጉባኤ አሳውቋል:: ወዴት እየሄድን ይሆን?
(ይቀጥላል)
———–
ዋቤ መጻሕፍትና ሊንኮች
2. The Earth and its Inhabitants, Africa: South and east Africa, by Elisée Reclus 1890
5. Tractatus tres historico-geographici (1634): A seventeenth century historical and geographical account of Tigray, Ethiopia (Aethiopistische Forschungen) 1634
7. Christopher Clapham: Transformation and continuity in revolutionary Ethiopia (Cambridge: Cambridge university press 1988 pp 259
8. The World through Maps: A History of Cartography : John R Short
9. https://archive.org/details/liberaxumae00pari (the Book of Axum part one)

የአማራ ተጋድሎ የዛሬ (ሀምሌ 12 ቀን 2008 ዓ.ም.) ውሎ

July19,2016

1. በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ ክስ ተመስርቷል፤ ሐምሌ 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይቀርባል። የቀረበው ክስ ‹‹ሰው በመግደል የተጠረጠሩ›› የሚል ሲሆን ከሐምሌ 5 ቀን በፊት ባለ ጉዳይ ይሁን ወይም ሐምሌ 5 ቀን ራሱን ለመከላከል ባደረገው ጥረት የታወቀ ነገር የለም። ሐምሌ 22 ቀን ከሳሽ ማን እንደሆነም ይለያል ተብሏል።
2. ኮሎኔል ደመቀን በየቀኑ የሚጠይቀው የዐማራ ሕዝብ ብዛት እስከ 1000 (አንድ ሺህ) ይደርሳል፤ በወያኔ አዋጅ አሸባሪን የጠየቀ አይደለም በቅርብ ርቀት አብሮ ሻይ የጠጣ አሸባሪ ነው፤ ምን እንደሚሉ አይታወቅም፡፡ በነገራችን ላይ ኮሎኔል ደመቀን ከጎጃም፣ ከሸዋም፣ ከወሎም እየመጡ የሚጠይቁት (ጀግናውን የሚያዩት) ሰዎች ብዛት አላቸው።
3. ዐማሮችን በመወከል 22 ሽማግሌዎች ድርድራቸውን ቀጥለዋል፡፡ እስካሁን አሸናፊ ናቸው፡፡ ሐምሌ 5 ቀን ራሱን ለማዳን ባደረገው ተኩስ በሞቱት የወያኔ ፖሊሶች ኮሎኔል እንደማይጠየቅ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ኮሎኔል ደመቀ በምንም መልኩ ወደ ፌደራል (የትግራይ መንግሥት) ተላልፎ አይሰጥም፡፡ የታሰሩ የወልቃይት ጠገዴ የዐማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጥረት ላይ ናቸው።
4. የትግሬ ቤቶችንና ዜጎችን ለመጠበቅ ጎንደር ገብተው የነበሩ የመከላከያ ሠራዊትና የፌደራል ፖሊስ አባላት ከከተማው እንዲወጡ ተደርጓል፤ በቅርብ እርቀት ላይ ሰፍረዋል። ጸጥታውን የዐማራ ልዩ ኃይልና ሲቪል ፖሊስ ተረክቧል። የጎንደር ዐማሮች እናንተ ጠብቃችሁ አታድኗቸውም፤ እኛ ጋር ካልተጣሉ ችግር የለብንም የሚል መልስ በተመረጡ ሽማግሌዎች ተላልፏል።
5. ነገ በጎንደር የአጼ ፋሲል ስታዲዮም የፋሲል ከነማና ኢትዮጵያ መድን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፤ የከተማው ሕዝብ እኛ ከተጫዋቾች ሳይሆን ችግራችን ከወያኔ ቅጣ ያጣ አገዛዝ ጋር ነው በማለታቸው ጨዋታው በተያዘለት መርሀ ግብር መሠረት ይሔዳል። የፋሲል ከነማ ነገ ካሸነፈ የኢትዮጵያን ፕሪሜር ሊግ ይቀላቀላል።
6. ዐማሮችን የሚያወግዙ ሰልፎች በየከተሞቹ እንዲደረጉ ወያኔ ያመጣው ሐሳብ ለሁለት ተከፍሏል። እንዲያወግዙ ታስበው የተዘጋጁት ሰልፎች በዐማራና በአዲስ አበባ ወደ ተቃውሞ ይዞራሉ የሚል ስጋት በመምጣቱ ሰልፉ መቅረት አለበት ወደሚል ተደርሷል። እብሪተኛው ሕወሓት ግን ከሰልፈኞች እኩል ብዛት ያለው የመከላከያና የፌደራል ፖሊስ ጋር መውጣት አለባቸው የሚል ግትር አቋም ይዟል። ወያኔ በዚህ አቋሙ ገፍቶ ከቀጠለ የሚፈጠረውን መገመት አይከብድም።
7. የዐማራ ብሔር በሆኑ የመከላከያና የፌደራል ፖሊስ አባላት ላይ ከፍተኛ ክትትል መኖሩም ታውቋል። የመከላከያና የፌደራል ፖሊስ አባል የሆኑ ዐማሮች በምንም መልኩ ወገኖቻቸው ላይ አይተኩሱም። ወያኔም ይህን ስለሚያውቅ አቋሙን እያለሰለሰ እንደሆነ ተገምቷል።
ሌሎች መረጃዎች ሲኖሩ በየሰአቱ እናደርሳለን።
የአማራ ሕዝብ ትግል ያሸንፋል!!

Sunday, July 17, 2016

የዴሞከራሲና የሰብዓዊ መብት ጥያቄን በጠብ-መንጃ አፈሙዝ ማቆም አይቻልም (ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)

July17,2106
በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ በከፋ የፖለቲካ፣ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ምስቅልቅል ውስጥ ትገኛለች፡፡ ለሁሉም የሕዝብ ጥያቄ ምላሹ የኃይል እርምጃ የሆነው አገዛዙ መግደል፣ ማፈናቀል፣ ማሰደድ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭቶችን መቀስቀስ ዋና ተግባሩ አድርጐታል፡፡ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የሚነሱ የሕዝብ ጥያቄዎችን ተገቢውን ምላሽ መስጠት ሲገባው የኃይል እርምጃ መውሰዱ አገዛዙ ወደለየለት አምባገነንነት ማምራቱን ያሳያል፡፡Semayawi party on Gondar Protest
በጐንደር ከተማ ከማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የተነሳው ተቃውሞ እንዲሁም በአዲስ አበባ ን/ስ/ላፍቶ ሀና ማሪያም ቀርሳ ኮንቶማ አከባቢ የተፈጠረው ግጭት አገዛዙ የፈጠረው ጭቆናና አፈና ውጤት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
በጐንደር ከተማ እና በአዲስ አበባ ን/ስ/ላፍቶ ሀና ማሪያም ቀርሳ ኮንቶማ ነዎሪዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ ኃላፊነት የጐደለውና በማናለብኘነት የተወሰደ ነው፡፡ በተጨማሪም የሕዝቡን ጥያቄ “የሌላ ኃይል ፍላጐት አስፈፃሚዎች ያነሳሱት ነው” በማለት መግለፁ ለሕዝብ ያለውን ንቀት የሚያሳይ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
በመሆኑም አገዛዙ በንፁሃን ዜጐች ላይ የወሰደውን ኃላፊነት የጐደለው እርምጃ እያወገዝን የኢትዮጵያ ሕዝብ ልዩነቱን ወደ ጐን በመተው ለዚህ ምስቅልቅል ምክንያት የሆነውን አፋኝ ስርዓት ለማስወገድ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቆርጦ እንዲነሳና ከሰማያዊ ፓርቲ ጐን እንዲሰለፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሀምሌ 8 ቀን 2ዐዐ8 ዓ.ም