Thursday, August 27, 2015

መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት !


August 27, 2015
def-thumbየግል ኑሮን ለማደላደል ሲባል የወያኔ አባል መሆን “ወይን ለመኖር” የሚል ስያሜ ከተሰጠው ዓመታት ተቆጥሯል። “ወይን ለመኖር” ዜጎች ነፃነታቸውን ለጥቅም አሳልፈው የሚሸጡበት፤ የሰው ልጅ ክብር የሚዋረድበት ገበያ ነው። በወይን ለመኖር “የገበያ ህግ” መሠረት እያንዳንዱ ዜጋ ሊያገኘው መብቱ የሆነውን አገልግሎት እንዲያገኝ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴግ፣ የደህዴግ፣ የአብዴፓ፣ የቤጉህዴፓ፣ የጋህአዴን፣ የሀብሊ ወይም የኢሶዴፓ አባል መሆን፤ አልያም መደገፍ ግዴታ ነው። እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች የህወሓት ተቀጽላ ወያኔዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ ያልሆነ እንኳስ የመንግሥት አገልግሎት ሊያገኝ ጥሮ ግሮ ያፈራውንም ይነጠቃል።
በዚህም ምክንያት፣ በገጠር ያለው አርሶ አደር ቁራጭ የእርሻ መሬት፣ የግብርና ባለሙያዎች የምክር እገዛ፣ የማዳበሪያና ዘር ግዢ፣ ብድር ወይም እርዳታ ለማግኘት በአካባቢው ባለ የወያኔ ድርጅት አባልነት መመዝገብ፤ አንድ ለአምስት መደራጀት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ የሚያራዝሙ ነገሮችን መሥራት ይጠበቅበታል። በከተሞች ውስጥም ሥራ ለመቀጠር፣ ለደረጃ እድገት፣ የመኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም) ለመግዛት ሲባል መወየን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ሆኗል:: በንግዱም ዘርፍ የንግድ ፈቃድ፣ የሥራ ቦታ እና የባንክ ብድር ለማግኝት፣ የመንግሥት ጨረታዎችን ለማሸነፍ፣ ከጉምሩክ እቃ ለማስለቀቅ፣ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት መወየን ግዴታ ነው።
“ወይን ለመኖር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ያዋረደ፤ ለትውልድ የሚተርፍ የማኅበራዊ ስነልቦና ኪሳራ ያደረሰ እና ደካማውን ወያኔን ጠንካራ በማስመሰል በሕዝብ የትግል መንፈስ ውስጥ ፍርሃትን የረጨ መሆኑ ግንዛቤ እየዳበረ በመጣ መጠን እየቀነሰ የመጣ ክስተት ነው። በአሁኑ ሰዓት ከቀድሞው እጅግ በተሻለ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ራሳችንን ከህወሓት ባርነት እያላቀቅን ምሬታችንን በግልጽ መናገር የጀመርንበት ወቅት ነው፤ ከዚያም አልፎ የህቡዕ ተግባራዊ የትግል እንቅስቃዎችን ማድረግ ደረጃ ላይ ደርሰናል።
አገር ውስጥ እየተዋረደ የመጣው “ወይን ለመኖር” በአገዛዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካይነት በውጭ አገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን (ዲያስፓራ) መካከል ነፃነታቸውን በጥቅም የሚለውጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ፍለጋ ተሠማርቷል። አገዛዙ ተስፋ ያደረገው ያህል ባይሆንም ጥረቱ የተወሰነ ውጤት እያስገኘለት ነው። በጥቅማ ጥቅም እየደለለ ካመጣቸው ውስጥ በስርዓቱ ብልሹነት ያዘኑና የተሰማቸውን በግልጽ የተናገሩ መኖራቸው የሚያስደስትና የሚያበረታታ ቢሆንም ከመንደር ካድሬዎች ባነሰ ተለማማጮችና አጎብዳጆች በማየታችን ተሸማቀናል። ኢትዮጵያ ውስጥ ካለነው አብዛኛው ሕዝብ አንፃር ሲታይ በተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙት ዲያስፓራዎች መካከልም ነፃነታቸውን በጥቅም ለመለወጥ የሚፈቅዱ መገኘታቸው አሳዛኝ ነው። እነዚህ ክብራቸውን በጥቅም የለወጡ ዲያስፓራዎች ዓለም ባንክንና የዓለም የገንዘብ ድርጅትን (IMF) ተክተው ህወሓት ስላስገኘው ፈጣን እድገት በአገዛዙ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ሲነግሩን መስማት ያሳፍራል። የህወሓት አገዛዝ “ፍትህን፣ መልካም አስተዳርንና ዲሞክራሲን አስፍኗል፤ ይህንንም መጥተን በዓይኖቻችን ተመልክተናል” እያሉ የግፉን ገፈት እየቀመስን ላለነው ሲነግሩን መስማት ያማል።
እነዚህ ወገኖቻችን ህወሓትን በማሞካሸት የሚያገኙት መሬት ብዙ ድሆች የተፈናቀለቡት፤ ለእነሱ በብላሽ የተሰጠው ብድር በረሃብ ለሚጠቃ ወገን የተላከ እርዳታ መሆኑ ማሳሰብ ይገባል። ከህወሓትና አጫፋሪዎቹ ጋር ተስማምተው ባገኙት ገንዘብ የሚቆርሱት እያንዳንዱ እንጀራ የብዙ ወገኖቻችን ደምና እንባ የፈሰሰበት መሆኑ ማስገንዘብ ያሻል። ከህወሓት ጋር በማበር በወገኖቻችን ድህነትና ችጋር እየከበሩ ያሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት ከዚህ እኩይ ሥራቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቅ ይገባል። እኚህ ወገኖች የራሳቸው ክብር ማጉዳፋቸውን ብቻ ሳይሆን የልጅ ልጆቻቸውም የሚያፍሩባቸው መሆኑን ማስታወስ ይገባል። ከዚህም አልፎ የዛሬ ተግባራቸው ነገ በህግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑን ሊያውቁ ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የአገዛዙን እድሜ በማራዘም ላይ የተሰማሩ፤ በድሆች ድህነት ለመክበር በመሯሯጥ ላይ ያሉ፤ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ለአገዛዙ ጥብቅና የቆሙ የዲያስፓራ አባላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳስባል።
አርበኞች ግንቦት 7 “ከህወሓት ውድቀት በኋላ ያለው ጊዜ ለእናንተም ከዛሬው የተሻለ ይሆናል። ዛሬ ከህወሓት ጋር ያላችሁን ሽርክና አቋርጡ። ለነፃነት የሚደረገውን ትግል እርዱ፤ መርዳት ባትችሉ እንቅፋት አትሁኑ፤ አለበለዚያ ግን ከተጠያቂነት የማታመልጡ መሆኑን እወቁ” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!! !

Wednesday, August 26, 2015

በዜጎች ላይ የሚፈፀመዉ ሰቆቃ አሁንም እየቀጠለ ነው!!

August 26,2015
amharic hateta
በሺዎች የሚቆጠሩ በርካታ ሰዎች በየክልሉ በተቋቋሙ እስር ቤቶች ዉስጥ ክስ ሳይመሰረትባቸዉ እንደሚታሰሩና፤ ግርፋት ሰቆቃና ድብደባ እንደሚደርስባቸዉ አልፎ ተርፎም እንደሚገደሉ ከኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወረ አይደለም።
በኢትዮጵያ የህግ አስፈፃሚ አካላት የሆኑት ፖሊሰ፤ ፍርድ ቤቶችና ወህኒ ቤቶች ኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ሙሉ በሙሉ ከመዉደቃቸዉ ሌላ የአገሪቱ የተወካዮች ምክር ቤት እንኳ ሊያዝዛቸዉ እንደማይችል በተለያየ ወቅት ተመስክሯል።
የፖሊስ ጣቢያዎች፤ የአስተዳደር ጽ/ቤቶች፤ወታደራዊ ካምፖች፡ ህጋዊ እስር ቤቶች፡ ሚስጢራዊ ስዉር እስር ቤቶች፡ በሀገረ ማርያም፤ ሁርሶ፤ ዴዴሳ፤ አጋርፋ፤ ዝዋይ፤ ጦላይ፤ቃሊቲ፤ማእከላዊ፤ በየክልል ወህኒ ቤቶችና በተለይ በአዲስ አበባ ዘመናዊ ቪላዎች በመከራየት በእስር ቤትነት ከመጠቀሙም በላይ በእስረኞች ላይ ሰቆቃ፤ ግርፋትና ድብደባ መፈፀሚያ በማድረግ እንደሚገለገልባቸዉ ይታወቃል።
የአለም አቀፍ የሰብኣዊ መብት ድንጋጌም ሆነ ህወሀት/ኢህአዴግ ያፀደቀዉ የአገሪቱ ህገ መንግሰት በማንም ሰዉ ላይ ሰቆቃ፡ ግርፋትና ድብደባ እንዲሁም ጭካኔ የተመላበት ኢ-ሰብኣዊ ድርጊትም ሆነ ስብዕናን የሚያዋርድ  ተግባር ሊፈፅምበት እንደማይገባ ይጠቅሳል። ይሁን እንጂ ይህ በእስራት ወቅትና ከእስራት ዉጭ በመንግስት የፀጥታ ሃይሎች፤ የደህንነት፤ የፖሊስ፤ የድርጅቱ ካድሬዎችና ወታደሮች አማካይነት በመላዉ የአገሪቱ ክልሎች በዜጎች ላይ የሚፈፀም የየቀኑ ተግባር ነዉ። ይህን በመፈፀም ማእከላዊ የምርመራ ድርጅት በመባል የሚታወቀዉ እስር ቤትና የደህንነት ተቋም የናዚ ጀርመን ይጠቀምባቸዉ ከነበሩት የማጎሪያ ካምፖች ያልተናነሰ እንደሆነ ይነገራል።
ዜጎች በኤሌክትሪክ ገመድና በሌሎችም ነገሮች በመጠቀም እጆቻቸዉ በሰንሰለትና በካቴና ታስረዉ ግድግዳ ላይ በተመቱ ምስማርና ችካሎች እንዳይንቀሳቀሱ ተወጥረዉ፤  የዉስጥ እግራቸዉንና መላ አካላቸዉን በጠቅላላ አዕምሯቸዉን እስኪስቱ ድረስ መደብደባቸውና የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት የፀጥታ ሃይሎች ሱዳን፤ የመን፤ ኬንያ፤ ሶማሊያና ጅቡቲ ድረስ ድንበር ዘልቀዉ በመግባት የሚፈልጓቸዉን ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች አፍነዉ መዉሰዳቸዉና ሊያመጧቸዉ ያልተሳካላቸዉን እንደሚገድሉ የኢትዮጵያ ህዝብ በሚገባ ያዉቀዋል።
የመንግስት የፀጥታ አስከባሪዎች ሌሎች ታጣቂዎች በቀን በአደባባይ የመንግስትን የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የሚቃወሙ ናቸዉ በሚሏቸዉ ላይ ግድያ እስከመፈፀም ያልተገደበ መብት አላቸዉ፤ በእያንዳንዱ የገበሬ ማህበር ቤት እየዞሩ ኢህአዴግን መምረጥ እንዳለባቸዉና ይህን ማድረግ ካልቻሉ ግን ምንም አይነት የመንግስት አቅርቦት እንደማያገኙ፤ ቤተሰቡ የመስራትም ሆነ የመማር እድል እንደማይኖረዉ በግልፅ የተነገረበት ሁኔታ እንደነበርና ኢህአዴግን ያልደገፉ ድሃ ገበሬዎች ማዳበሪያና ሌሎች የእርሻ ግብኣት ድጋፎች እንዳይደረግላቸዉ መከልከላቸዉን የሰብኣዊ መብት ተሟጋቾች አጋልጠዋል።
ኢህአዴግ የፖለቲካ አላማዉን ለማስፈፀም ላለፉት 24 አመታት በመንግስት ስልጣን ላይ ተቀምጦ በደህንነትና በወታደራዊ ተቋሞቹ አማካይነት የአገሪቱን ፖለቲካ በግሉ ለመቆጣጠር፤ በጎሳና በዘር ላይ የተመሰረተ ፕሮግራም በማካሄድ፡ በፖለቲካና በሲቪክ ማህበራት ድርጅቶችና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ይፈፅማቸዉ የነበሩትና ዛሬም የሚፈፅማቸዉ የሽብር ተግባሮች ለመሆናቸዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠንቅቆ ያዉቃል።
እናም የህወሃት/ኢህአዴግ መንግሰት “በሽብርተኝነት” “የአገርን ሰላም በማደፍረስ” “ህገ መንግስታዊዉን ስርአት በመናድ ” “በዘር ማጥፋት” “በአገር መክዳት”   ወዘተ… የሚሉትን የወንጀል ክሶች የሚጠቀምበት ለምን አላማ እንደሆነ ግልፅ በመሆኑ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሳይበረከክ በኢህ አዴግ ስርዓትና ተቋማቱ ላይ የጀመረውን ተቃውሞውን በማጠናከር ማስቀጠል ይግባል።

Tuesday, August 25, 2015

Ethiopia needs $230-million worth food aid

August 25, 2015
(Reuters) – The number of Ethiopians who will need food aid by the end of this year has surged by more than 1.5 million from earlier estimates due to failed rains, United Nations agencies said on Monday.Ethiopians needing food aid
Ethiopia needs an extra $230 million from donors to secure aid for a total of 4.5 million people now projected to require assistance this year, the Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (UNOCHA), the World Food Programme (WFP) and the U.N. children’s agency UNICEF said in a statement.
The country of 96 million people is one of Africa’s fastest-growing economies, but failed rains have devastating consequences for food supplies.
“The belg rains were much worse than the National Meteorology Agency predicted at the beginning of the year. Food insecurity increased and malnutrition rose as a result,” said David Del Conte, UNOCHA’s acting head of office in Ethiopia, referring to the short, seasonal rainy season that stretched from February to April.
Areas normally producing surplus food in the Horn of Africa country’s central Oromia region were also affected by shortages, the statement said, adding lack of water had decreased livestock production and caused livestock deaths in other pastoralist areas.
Meteorologists have warned that the El Nino weather phenomenon, marked by a warming of sea-surface temperatures in the Pacific Ocean, is now well established and continues to strengthen. Models indicate that sea-surface temperature anomalies in the central Pacific Ocean are set to climb to the highest in 19 years.
The El Nino can lead to scorching weather across Asia and east Africa but heavy rains and floods in South America.
The United Nations cautioned that the anomaly could further affect Ethiopia’s “kiremt” rains that stretch from June to September.
“A failed belg followed by a poor kiremt season means that challenges could continue into next year,” said John Aylieff, WFP’s Ethiopia representative.

Saturday, August 22, 2015

በሶማሊያ ሀገር ህይወታቸው እያለፈ ያሉ የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው እየጨመረ ነው

August22,2015

ethiopia millitary in somaliaእየተላኩና ህይወታቸው እያለፈ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ከቀን ወደ ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ እንደሆነ ከተለያዩ ያገራችን አካባቢዎች የደረሰን መረጃ አስታወቀ።በሶማሊያ ሃገር እየሞቱ ያሉትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የሟቾቹ ቤተሰብ በየግዜው በቴለፎን መርዶ እየደረሳቸው እንደሆነ የገለፀው መረጃው በተለይም የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ለምንድነው ስልጣን ላይ ያለው ስርዓት የሞቱት ልጆቻችን የማይነግረን በመሰረቱ ልጆቻችን ወደ ሶማልያ አገር ሂደው እንዲያልቁ የሚደረገውስ ለምን ዓላማ ነው? የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቀው ግልፅ በሆነ መንገድ መነገር አለበት በማለት ጥያቂያቸውን እያቀረቡ መሆናቸው ተገለጸ።
ይሁን እንጂ የኢህአዴግ ባለስልጣን አልሸባብን ለማጥፋት በሚል ምክንያት ከሃያላን መንግስታት የሚያገኙትን ዶላር ለመሰብሰብ ካልሆነ ከአገሩ ውጭ እየሄደ ህይወቱን እያጣ ላለው ወጣትና ቤተሰቦቹ ግን ምንም ዓይነት ደንታ እንደሌላቸው የሟቾች ቤተሰብና አንዳንዱ የአገራችን ምሁራኖች አስተያየታቸው እየሰጡ መሆናቸው አስታውቋል።
በተመሳሳይ አንድ በትግራይ ማእከላዊ ዞን፤ ተምቤን ዓብይ ዓዲ ውስጥ የሚኖሩ ወላጅ ልጃቸው በሶማልያ ሃገር ሄዶ መሞቱ ለምን አላማ ሲባል ነው ብለው መጠየቃቸው ባለፈው የዜና እወጃችን መገለፁ ይታወቃል።

ሆዳም ቢሰበሰብ መግላሊት ኣይከፍትም

August 22, 2015
ከብርሃኑ ተስፋዬ
የሰይጣኑን ሙት ኣመት ለማክበር በሚዘጋጁበት ወቅት ወያኔዎች ሆዳም ዲያስፖራዎችን ወደ ኣዲስ ኣበባ ጋብዘው ቡራ ከረዩ የሚሉበት ሁኔታ ስለገረመኝ ነው ይህን ጽሁፍ ለንባብ የማቀርብላችሁ። በመሆኑን መልካም ንባብ።Ethiopian Diaspora
መነሻ
በመጀመሪያ የሰው ልጅ ከትውልድ ቀየው ወደ ተለያዩ ቦታ ወይም የኣለም ክፍሎች የሚሰደደው ኣንድም በሃገሩ ባለው የፖሊቲካ፣ የሶሽያልና የኢኮኖሚ ሁኔታ ኣለመመቻቸት ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም። እውነቱና ሀቁም ይህ ሆኖ ሳለ የተሰደደበት ችግር በሚቀረፍበት ጊዜ ኣንድም በኣካል ኣሊያም በሃሳብ፣ ማቴሪያል፣ ወይም በገንዘብ ለሃገሩ ኣስተዋጾ ያደርጋል። ይህንን ኣይነት ሁኔታ ሊፈጠር የሚችለው ግን በተሰደደበት ወቅት የነበረው የመንግስት ስርኣት ሲቀየር የሚከተላቸው ፖሊሲዎች ዲያይስፖራውን እንደ ኣንድ ኣገር ገንቢ ኣካል ቆጥሮ በእኩልነት ማሳተፍ የቻለ እንደሆነ ነው።
በኣንድ ጥናት እንደሚያሳየው በአሜሪካ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ፣ ጋናና ዚምባዌ ዲያስፖራ አባላት(2010) በ2009 ብቻ የኣመታዊ ምርታቸውን 6.5 ፣ 7.5ና 34.4 በመቶ ወደየሃገሩ ተልኩዋል። ይህም ባንድ በኩል ከዲያስፖራው ወደ ሃገር ከሚገባው የክህሎት፣ የፖሊቲካ፣ የባህልና ሶሺያል ካፒታል በተጨማሪ የተገኘ ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም።
ይህን በመነሻ ያነሳሁት ለመንደርደሪያ ይሆን እንጅ ዋናው ሃሳቤ ይህን ሃሳብ ይዤ ለመሙዋገት ኣይደለም። ሆኖም የዲያስፖራውን ሃይል ባግባቡ መጠቀም የሚፈልጉ መንግስታት ካሉ ያለውን እምቅ ሃይል ለማመላከት ብቻ ነው።
መረማመጃ
ኣሁን በኣለም ላይ ተበትኖ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ኣንድም የጉጅሌው ሰለባ የነበረ ወይም በነበረው የፖሊቲካ ኣመለካከቱ ሳይደነብር በሃገሩ መኖር ያልቻለ ስብስብ ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም። ይህን ስል ግን በቅርብ ጊዜ በስወር ለስለላ የተሰማሩ የጉጅሌው ኣባላት የሉም ለማለት ኣይደለም። እነዚህ ግን ኣምላክ ምስጋና ይግባዉና የጉጅሌው መሪ ተብየ በሞተ ማግስት በየድንኩዋኑ ሙሾ ሲወርዱ ስላገኘናቸው እርቃናቸውን ለማስቀረትና መስመራቸው ወዴት እንደሆነ መለየት ተችሉዋል። ከነሱ በተጨማሪ በጉጅሌው ተሳደድን ተገረፍን መብታችን ተገፈፈ ብለው ይጮሁ የነበሩ ሆኖም ትንሽ ትንፋሽ ሲያገኙ ማንነታቸው ገሃድ የወጡ የሆዳም ስብስቦች ኣደባባይ ወጥተዋል። በመሆኑም ነው ባሁኑ ጊዜ ባለም ላይ ከተበተነው ኢትዮጵያዊ ውስጥ ሆዳሞች ብቻ ተለይተው ወደ ሃገር ለበኣል የታደሙት።
ማንም ሰው ወደ ሃገሩ በመሄድ ቤተዘመዱንም ሆነ የተወለደበትን ቀየ ጉዋደኞቹንም ሆነ ሃገሩን መጎብኘት የለበትም የሚል እምነት የለኝም። ሆኖም ግን በውጭ ሃገር ኢትዮጵያዊነት ሲዋረድ ካዋራጆቹ ጋር ኣብሮ የሚጨፍረውን ወያኔን፣ (ሳውድ ኣረቢያ፥ ሊቢያ፥ የመን፥ሌሎች ኣረብ ሃገሮች) መልካም ገጽታ ኣለኝ ብሎ እንዲያናፍስበት የፖሊቲካ መጠቀሚያ ለመሆን ባህር ኣቓርጦ በጎርሻ በሚኖር እናት፣ ኣባት፣ ወንድምና እህት ላይ መሳለቅ ህሊናቢስ መሆን ነው።
ሌላው ኣስገራሚው ደግሞ ትላንት ጎረቤቱና የመንደሩ ገበሬ የተፈናቀለበትንና በረንዳ የተወረወርበትን ቦታ ለዚህ እኩይ ስራ እጅ መንሻነት ውሰድ ሲባል እሽ ብሎ ተቀብሎ የራሱን ፍላጎት ብቻ መመልከቱ ከሆዳምነት የመጨረሻው ሆዳምነቱን የሚያመላክት ነው።
ባሁኑ ወቅት ተሰባስበው የታደሙትን የዲያስፖራ ኣባላት በተናጠል ብንመለከት በውስጣቸው የተሰባሰቡት ኣንድም በወያኔ ድርጎ የራዲዮ ጣቢያ፣ የውይይት መድረክ ኣልያም ወያኔ ከህዝብ በዘረፈው ሀብት መዋእለ ንዋይ ተሰጥቶዋቸው ገበሬውን በማፈናቀል ቦታ የተረከቡ ናቸው። ኣንዳንዶቹም በሚኖሩበት ሃገር መንግስት ድጎማ የሚኖሩና የወር ገቢያቸወ እንኩዋን ድርጅት ለመመስረት ከወር ወር የሚያኖራቸው ኣለመሆኑን እያወቅን በሶስት ወር ሁለት ጊዜ ወደ ሃገር እንዲጉዋዙ የተደረጉ ናቸው።ይሁን እንጅ ይህ ሁኔታ ኣሁን ለምን ኣስፈለገ የሚለው መሰረታዊ ጥያቄን ማንሳት ያስፈልጋል።
ወያኔዎች ኣንድ ኣለመግባባት በመሃከላቸው በሚኖርበት ጊዜም ሆነ በሃገሪቱ ያለው ትግል ትንሽ ጉልበት ያወጣ ከመሰላቸው ጊዜ መግዣ የሚሉት ዘዴ ኣላቸው። ይህንን በ1997ቱም ምርጫ፣ ህዋህት በሚሰነጠቅበት ወቅት፣ ኣርዮስ መሪያቸው በማቀዝቀዣ በነበረበትም ሆነ ኦባማ ለጉብኝት ከመምጣቱ በፊት ያከናወኑዋቸውን ሸረኛ ስራዎች ማስታወስ ግድ ይላል። እነዚህን ነፍሱን ኣይማረዉና ለገሰ ዜናዊ ወጣት በነበረበት ጊዜ ይተኛበት በነበረው መኝታ ቤት ግድግዳ ላይ የዚያን ጊዜ ያስቀመጠውን “procratination is a theft of time” የሚል ኣባባል መቃብር ከመውረዱ በፊት ለወያኔዎቹ ጥሎ መሄዱን ያረጋግጥልኛል።በወቅቱ ይህ ኣባባል ያመለክት የነበረው የፊዳሉን ኣስተዳደር የመሬት ላራሹ መፈክርን ተግባራዊ ኣለማድረግን የሚያመላክት የነበረ ቢሆንም ከዚያ ትምህርት ቤት የተማረውን የከፋፍለው ግዛ ከ17 ኣመት በሁዋላ ተገባራዊ እንዳረገው ሁሉ ይህንንም መቃብር ይዞት ኣለመውረዱ ርዥራዦቹ እየተጠወሙበት ይገኛል።
ወያኔ ባሁኑ ጊዜ ይህ ዘዴ ኣሁን ያፈለገው በተላያዩ የውስጥና የውጭ ችግሮች መሆኑን በሚከተለው ለማሳየት እሞክራለሁ።
1. በሃገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ እየታገሉ ያሉትን ተቃዋሚዎች ለማስመመሰያነት እየተጠቀመበት ያለው ድራማ በምርጫ 2007 እርቃኑን እንዲወጣ ካደረጉት በሁዋላ ወያኔ ከህዝቡ ልብ ብቻ ሳይሆን ኣንዳንድ የራሱ ኣባላት ምን እየተደረገ ነው የሚል ጭምጭምታ መጀመራቸው ብሎም ኣንዳንድ የተቃዋሚ ድርጅት ኣባላት የወደፊቱ የትግል ኣቅጣጫ ምን መምሰል ኣለበት የሚለው ጥያቄ እያጫረባቸው መሆኑን በገሃድ እየተመለከተው በመሆኑ፣
2. በጎረቤት ሃገር ያሉ በሁለገብ ትግል የሚያምኑ ታጋዮች በመሃከላቸው ያለውን መለስተኛ ኣለመግባባት ወደ ጎን ትተው ኣይናቸውን በቀጥታ ወደ ኢላማቸው ለማነጣጠር በጋራ ለመስራት ኣንድ እርምጃ ወደፊት መጉዋዛቸው፣
3. ወያኔ ከኣለም የረድኤት ድርጅቶችና ኣበዳሪዎች ከሚያገኘው የውጭ ምንዛሪ ቀጥሎ ያለው የገቢ ምንጭ ዲያስፖራው ኣንድም ለቤተሰቡ ኣልያም በኢንቨስትመንት መልክ ወደ ሃገር የሚያስገባው ሲሆን ከዚህ ባሻገር ለዚህ ግንባታ ለዚህ ማስፋፊያ በሚል የልመና ኣቁማዳ ይዞ ሊሰበስበው ያቀደው የውጭ ምንዛሪ በትንታግ ታጋዮች በተለያዩ ኣካባቢዎች ሊሳካለት ባለመቻሉ፣
4. በሃገራችን በያመቱ 7.5 ሚሊዮን ገበሬዎች በበጎ ኣዳራጎት (safety net) ድጋፍ ይኖራሉ፣ ሆኖም ሃገሪቱ በምትከተለው ደካማና ያልተጠና የግብርና ፖሊሲ የተነሳ ራሱዋን በምግብ እህል ልትችል የቻለችው በሃይለ ማርያም ደሳለኝ ኣንደበት ብቻ በመሆኑ ባሁኑ ወቅት 4.5 ሚሊዮን ለረሃብ ኣደጋ የተጋለጡ መሆናቸው በኣለም መገናኛ መነገሩ፣
5. በተለያዩ ሜዲያዎች በሃገሪቱ የሚካሄደው የሰብአዊ መብት ረገጣና የህዝቦች ሰቆቃ የየእለት የመወያያ ርእስ በመሆኑና በሌሎችም ምክንያቶች የህዝባችንን የትኩረት ኣቅጣጫ ማስቀየስ በማስፈለጉ የተዘጋጀ ድራማ ነው።
ለዚህ ድራማና ዘፈን ደግሞ ኣጃቢ በማስፈለጉ በዲያስፖራው የተነገሩ መሰረታዊ ባይሆኑም ወቅታዊ ችግሮች በቅመምነት እንዲስተናገዱ ማድረግ ደግሞ ወያኔ የተካነበት መሆኑን ደደቢት ላይ ተነስታ ሳሞራን የጠየቀችው ኣርቲስትን ማጣቀስ ብቻ በቂ ይመስለኛል። በመሆኑም ወያኔ በውስጡ ያሉትን ኣለመግባባቶች ሽፋን መስጠት በመፈለጉና መቶ በመቶ ኣብላጫ ድምጽ ኣግኝቼ ኣሸነፍሁ የሚለውን የ2007 ምርጫ ተከትሎ ሊያዋቅር የሚፈልገውን የክልልና የዞን ምክር ቤት እስኪያዋቅር ድረስ ከምንሰማቸው ነጠላ ዜማዎች ኣንዱ ኣካል እንጅ ዲያስፖራው በጉቦ የተሰጠውን መሬትም ሆነ ንብረት ሸጦ ወደመጣበት እንደሚመለስ ወያኔም ያውቀዋል ዲያስፖራውም የለመደው ነው። ከዚህ ጋር ግን ኣብሮ መታሰብ ያለበት ይህች ዘለል ዘለል እቃ ለማንሳት ነው እንዲሉ የተለየ ቡድን ግን (ትክክለኛ ወያኔዎች) በልጅ ኣመካኝቶ ይበላሉ ኣንጉቶ እንደሚባለዉ ኣባላቶቻቸውን ለመጥቀም የተዘጋጀ መሆኑን ላፍታም መዘንጋት የለብንም።
ማሳረጊያ
ከላይ የጠቀስኩዋቸው መሰረት በማድረግ ሃሳቤን ለማጠቃለል ይረዳኝ ዘንድ ትናንት የሰማሁትን ባለ ፭ ሚሊዮን ባውንድ ኣጉዋጉዋዥ ኣብዛኛዎቻችን ስንሰማ ግር ያለን እንኖራለን ሆኖም በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ብዙ ሚሊዮኖች ቡልጋሪያ ሃንጋሪና ኡክሬይን ድረስ ተጭነው ሄደው የጦር መሳሪያ መገዛቱን ደግሞ እንረሳለን። በመሆኑም ኣሁን የተሰባሰበው የዲያስፖራ ጋጋታ ኣቅጣጫ ማስቀየሻ በመሆኑ እንደኔ ኣመለካከት ምን ቢሰበሰብ መግላሊት ኣይከፍትም ነውና ኣይናችንን ከኩዋሱ ላይ ማድረግ ብቻ ነው የሚጠበቅብን። በመሆኑም ያለን ባለን ሁሉ ትግሉ ኣንድ እርምጃ እንዲሄድ የየራሳችንን ኣስተዋጾ ማድረጉ ወሳኝነት ኣለው።
ኢትዮጵያ በልጆችዋ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች
chillalo@gmail.com

Monday, August 17, 2015

አምባገነንነትና የነፃነት ጥያቄ!

August 17,2015
ANBAGENEN amahric
የኢህአዴግ ስርዓት በአለፉት 24 ዐመታት ያዋቀራቸው ወታደራዊና የፀጥታ ኃይሎችን ተጠቅሞ የሰፊውን ህዝብ ነፃነት መግፈፍ፤ ውስጥ ለውስጥ የማይስማሙትን ማሰርና መግድል ካለምንም የርዕዮተ-ዓለም መሰረት የሚካሄዱ ከውጭ ኃይል ጋር በጥቅም በመተሳሰር በህዝባችን ላይ ዘመናዊ ባርነት እንዲፈጸም ሆን ብሎ እየተንቀሳቀሰ ነው።
የወያኔ ኢህአዴግ የመንግስት መከላከያ ሃይል፤ የፀጥታውና የፖሊሱ አወቃቀር ካለውጭ ዕርዳታና ምክር እንዲሁም ስልጠና በራሱ ኃይል የተደራጀ የሚል ሰው ካለ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምን እንደሚካሄድ አያውቅም ማለት ነው። ስለዚህም ለነፃነት የሚደረገው ትግል ብዙ የማይታሰቡ ጥያቄዎችን ይዞ መምጣቱ ብቻ ሳይሆን በአንድ አገዛዝ መገርሰስ ወይም መወገድ ብቻ አንድ ህዝብ ነፃነቱን ሊቀዳጅ እንደማይችል ከብዙ አገሮች ታሪክ የምንማረው ሀቅ ነው።
በተለይም ያለፈውን የሰላሳና አርባ ዐመታት የህዝቦችን የነፃነትና የዴሞክራሲ ትግል ስንመለከትና ስናጠና በአብዛኛው የሶስተኛው ዓለም አገሮች የህዝብ ነፃነት ተግባራዊ ሊሆን ያልቻለው የአብዛኛው ህዝብ ጥያቄ ሳይንሳዊና ፍልስፍናዊ በሆነ መንገድ መፈታት ስላልተቻለ ብቻ ነው።
አንደሚታወቀው  በዓለም አቀፍ ደረጃ ካፒታሊዝም ከተስፋፋና የበላይነትን ከተቀዳጀ ወዲህ ጭቆናዊ አገዛዝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊስፋፋና አብዛኛዎቹ የሶስተኛው ዓለም አገሮች በወታደራዊ ሃይል ስር በመዋላቸው ምክንያት በዓለም አቀፍ የጭቆናና የአፈና ሰንሰለት ውስጥ ገብተው ለስቃይ እንዲፈረዱ ግድ ሆኗል።
የጥሬ-ሀብት ጥናቶች እንደሚያረጋግጡት አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ይህንን የተትረፈረፈ ጥሬ ሀብታቸውን እያወጡ በስርዓት ለመጠቀም፤ ህዝቦቻቸውን ከድህነት በማላቀቅ ስነ-ስርዓት ያለው ኑሮ ለመገንባትና ህዝቦቻቸውን ለማስከበር ያልቻሉት ከላይ በተዘረዘረው የወታደራዊና የስለላ የጭቆና ሰንሰለት ውስጥ ስለተካተቱና በአሜሪካንና በተቀረው የምዕራቡ ካፒታሊዝም የብዝበዛ አስተሳሰብ ውስጥ ተቀነባብረው ሀብታቸውን በስርዓት እንዳይጠቀሙ ስለተደረጉ ነው።
በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች የተዋቀረው የመንግስት አሰራር በመሰረቱ የህዝቦች አለኝታና የሀብት ፈጣሪ መሳሪያ ወይንም መንገዱን የሚቀይስ ሳይሆን ድህነት እንዲስፋፋና ሁሉም ዜጋ በስርዓቱ ስር ሆኖ እንዲገዛና አስከፊ የኑሮ ሁኔታ እንዲያሳልፍ ነው የሚደረገው።
በሳይንስና ምንም አይነት ፍልስፍና ባልተከተለ መንገድ የተዋቀሩ የመንግስታት አሰራሮች፤ ስነ-ምግባርና ሞራል የጎደላቸው ማህበራዊ ህብረተሰባዊ፤ ባህላዊና ታሪካዊ ኃላፊነት በሚያሸክም መንገድ ስላልተቀመጡ ሁሉም ነገር በተራ ታዛዥነት እንዲፈፀም ምክንያት ሁኗል።
ወደ አገራችንም ስንመጣ የስርዓቱ የአሰራርና የአወቃቀር ስርዓት ከተቀሩት የአፍሪካ አገሮች እምብዛም የሚለይ ሳይሆን የባሰ መሆኑን የሚያከራክረን አይደለም። አንድ ህዝብ ዕውነተኛ ነፃነቱን ሊቀዳጅ የሚችለው ይህ ዐይነቱ እንደሰንሰለት የተያያዘ የጭቆና አገዛዝ ለዕውነተኛ ነፃነት እጦት ዋናው ምክንያት እንደሆነና የድህነትንም አፍላቂና የተስተካከለ ዕድገት እንዳይኖር የሚያግድ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ ሲገባ ብቻ ለነፃነት የሚደረገው ትግል የተቃና ይሆናል።
በሌላ አነጋገር ለዕውነተኛ ነፃነት እታገላለሁ የሚል ሁሉ አገራችን ውስጥ ላለው ፀረ ህዝብ ስርዓትና የአብዛኛዎችን የአፍሪካ አገዛዞች አወቃቀር በሚገባ መገንዘብና ከዚህ በመነሳትም እስካሁን በተካሄደው የትግል መንገድ ዕውነተኛውን የህዝብ ነፃነት ማምጣት እንደማይቻል መረዳት ይኖርበታል።

ዴምህት

Sunday, August 16, 2015

ኢትዮጵያዊነትና ብሄራዊ ስሜት

August 16, 2015
ሻለቃ አብርሃም ታከለ
በረጅሙ ዘመን ታሪካችን ኢትዮጵያዊነትንና ብሄራዊ ስሜታችንን የሚፈታተኑ ሁኔታዎች መከሰታቸዉ ተስተዉሏል። ይህ አባዜ ዛሬም ድረስ አልተወንም።
ባዕዳን ወራሪዎች ካደረሱብን መከራና በደል ይልቅ ይበልጥ አድቅቆን የነበረዉ በአገዛዝ ስም ወገኖቻችን የሚጭኑብን ኢ-ሰብአዊ የሆነ የግፍ ቀንበር መሆኑን አንስተዉም። ከእኛ በፊት የነበሩት ኢትዮጵያዉያን እንዲያ ሆነዉ አልፈዋል። በደም በአጥንታቸዉ ዋጅተዉ ባቆሙት ነፃነት ላገር እንደእንግዳ ለወገን እንደባዳ ተቆጥረዉ በነፃነትና በባርነት መካከል ባለዉ ድንበር መሃል ሲታሹ ለእፎይታ ሳይበቁ ተሰናብተዋል።”እምሽክ ድቅቅ አርጎ እኔን ከበላኝ ነጭ ጅብ ጥቁር ጅብ ምን አስመረጠኝ ” እስከማለት መድረሳቸዉም በዚህ የተነሳ ነዉ።
ይህንን እያንጎራጎሩ ኖረዉ ይኸዉ ወደ መቃብር ወርደዋል። ይህ ለመሆኑ እርግጥ ነዉ። ተረትም አይደለም የተፈፀመ እዉነት። “እናት ኢትዮጵያ ሞኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ” የተባለዉም በአብዛኛዉ ሕዝብ ስቃይና ሞት ጥቂቱ ተንደላቃቂና ፈላጭ ቆራጭ ስለሆነ ነዉ። ይህን ያሉትም እኒያዉ ለአገር አንድነትና ሉአላዊነት ዉድና ተተኪ የማይገኝለትን ሕይወታቸዉን ቤዛ ያደረጉና አካላቸዉን ያጎደሉ ሃቀኛ ዜጎች ናቸዉ። ይህ ግፍ በሕዝቡ ላይ ተፈጽሟል። ይህ ሁሉ አበሳና መከራ በሕዝቡ ላይ ደርሷል። ይሁን እንጂ ይህች አገራችን ታላቅ ከመባል የተዛነፈበት እስከቅርብ ግዜ ድረስ የለም። ሕዝቡም ቢሆን አገሩን አሳልፎ የሰጠ የሚል አሳፋሪ ስም በታሪክ አልተፃፈበትም።ረሃብ ድርቅ ድህነት ቢፈታተነዉም የነፃነት ሸማዉን ሳያስገፍፍ የአገሪቱን ሉአላዊነት አስከብሮ ኢትዮጵያዊነትን አዉርሶ ወር ተራዉን ጨርሶ አልፏል። መቸም ቢሆን የሕዝብ ዋና ኩራት በዜግነት መተማመን ነዉ። ይህን መተማመን ያጠነከረ ሕዝብ ለማናቸዉም ምድራዊ ሃይል ተንበርካኪ አይሆንም። በኢትዮጵያዊነት የማመን ጥኑ ማተብ ነዉ።የኢትዮጵያ ሕዝብ ቋንቋ ባሕልና የተለያየ እምነት ሳይከፋፍለዉ በአንድነትና በመተሳሰብ እንዲዘልቅ ያስቻለዉ። የትግራይ ነፃ አዉጪ የነፍሰገዳዮች ቡድን አገዛዝ ይህን የተከበረ የጀግንነት ኩራት ሊነጥቀን እየዳዳ ነዉ።
በዚያ ነዲድ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ላይ በረዶ ሊሞጅርበት ሌት ተቀን እየደከመ ነዉ። ከሁሉ በፊት ኢትዮጵያዊነትን ማሰብና ማስቀደም የቀድሞ ሥርአት ናፋቂ ሽብርተኛ ትምክህተኛ እያሰኘ ነዉ። ኢትዮጵያዊነት ነፍጠኛነት ከሚል የተሳሳተ የዘረኝነት ድምዳሜ ላይ እያደረሰ ነዉ። ኢትዮጵያዊነት ሁሉም ብሄረሰቦች የሚጠለሉበት አንድ ጃንጥላቸዉ ሆኖ እንዲዘልቅ የምንመኘዉን ያህል በዜግነት የመተማመን ስሜት እንደጠላ ቂጣ እለት ከእለት እየተሸራረፈ በጊዜ ሂደት ዉስጥ ተሟጦ እንዳያልቅና ጭራሹን እንዳይጠፋ የተቆርቋሪዎች ስጋት ከሆነ ሰንብቷል።
በመናወዝ ላይ የሚገኘዉ ይህ ትዉልድ ስለኢትዮጵያዊነትና ስለብሄራዊ ስሜት ጭብጥ እንስጥህ ቢሉት “አቦ ተወን….አትደብረን! ቢል አይፈረድበትም። ይህን በማለቱ ሊወቀስም ሊነወርም አይገባም። ለእርሱ ኢትዮጵያዊነት ጦርነት ስደትና ሞት ሆኖ ነዉ የሚታየዉ። ለእርሱ ኢትዮጵያዊነት ቀይ ሽብር ነጭ ሽብር ሆኖ ነዉ የሚቆጠረዉ። ለእርሱ ኢትዮጵያዊነት የእትብት አፈር ክልል አብሮ ማደግ፣ጎሰኝነትና ይህን ሃሳብ የማይቀበለዉን ወገን ማሰደድ ማፈናቀል ማሰርና መግደል ሆኖ ነዉ የሚታሰበዉ።
በዘመናችን አገርና ትዉልድ እሳትና ጭድ ሲሆኑ ተመልክተናል። ተካፋይም ሆነናል። የሃይማኖት አባቶች የመልካም ሥነ ምግባርን ትምህርት በመስጠት ፋንታ ከአምባገኖች ጋር ወግነዉና በዘር ተደራጅተዉ በመንፈሳዊ ሳይሆን በአለማዊ ሕይወት ዉስጥ ሲዳክሩ እያየን ነዉ።
አድርባይነትንና ጎሠኝነትን ተፀይፎ እዉነትን መቀበል አለመቻል ኢትዮጵያዊነትን ብቻ ሳይሆን እኔነትን ፈልጎ ለማግኘት አለመፍቀድ ይሆናል። በቅድሚያ ኢትዮጵያዊነት የዜግነት ስሜት። ከዚያ እኔነት።
የስነ ልቡና ጠቢባን ራስን ለማወቅ በጠቀሱት ቁም ነገር “አንተነትህ አንተ እስከምታዉቀዉ ድረስ ነዉ” ይላሉ እኛም እንደዚያዉ ነን። የምናዉቀዉ ይህንኑ ነዉ። የምናሳድገዉም፤ ለትዉልድ የምናስተላልፈዉም ይህንኑ ነዉ። ኢትዮጵያዊነትን።
ይህ ሳይሆን ሲቀር ዘዋሪ እንደሌለዉ ካሚዎን ነዉ የምንሆነዉ። ሁላችንም ጠፍተን አገርም ዜጋም። እና ሁላችንም ተፈላላጊ ሆነን። አገርን ወይንም ኢትዮጵያዊነትን ያየህና ወዲህ በለኝ! እንደሚባለዉ ዓይነት። መሆኑ ነዉ።

Saturday, August 15, 2015

የማለዳ ወግ…ለአሚራና ቤተሰቦቿ የጎደለው ፍትህ … !

Augest 14,2015
Amira
Amira
==================================
* ህጻን የደፋረን የ4 ወር እስር መቅጣት ምን ይሉታል ?
* ፍርዱ ቅጣት ነው?  ወይስ ማበረታታት ?
* ህግ አውጭና አስፈጻሚ አካላት ወዴት ናችሁ?
* ወላጆቿ " ወላጅ ይፍረደን፣ህዝብና ሀገር ይፍረደን!"ይላሉ
የኢፊድሬ ህገ መንግሰት ሴቶች  ልክ  እንደ  ወንዶች  በሕገ-መንግሥቱ  እኩል  መብትና  ጥበቃ  እንዲሰጣቸው ይደነግጋል ትግበራውን መከታተልና ማስፈጸም ያለባቸው ህግ እውጭና አስፈጻሚ አካላት የሴቶችን መደፈር ለመከላከል የከበደ ኃላፊነት እንዳለባቸው ይህው የፈረደበት ህገ መንግስት ያስረዳል  ! ዳሩ ግና አልፎ አልፎ የሚሰማ የሚታየው የነገር ጭብጥ ውጤት ህግ አውጭና የሚያወጡት ህግ ደንብና መመሪያ ከወንጀል ፈጻሚው ባልተናነሰ በህግ አስከባሪና አስፈጻሚዎች ህጉ ይጣሳል ። ህግ ተጥሶ የዜጎች ሰብአዊ መብት መዳጡ  በአደባባይ እየተሰማና እየታየ ህግ አውጭ አካላት የሚወስዱት እርምት እርምጃ አያስደስትም ። የሴት ጠለፋ በተለይም በህጻናትና ታዳጊዎች ላይ የሚፈጸም አስገድዶ  መድፈር ዝርዝሩ ሰፋ ያለ ይሆናል ። ዳሩ ግን የህግ እውቀት ኖሮኝ ያንን ለመተንተን ባይዳዳኝም በህግ አስከባሪዎች ፍትህ እየጎደለ በዜጎች ላይ የሚፈጸመው በደል ዘልቆ ቢያመኝ እንደ ዜጋ በጎደለው ፍትህ ተቃውሞና በቅሬታየ ዙሪያ የዜጋ ድምጼን ማሰማት ግድ ብሎኛል ...
ዛሬ ዛሬ የምንሰማው ሰው በሰው ላይ ቀርቶ በእንስሳ ላይ መፈጸም የሌለበትን ርክሰት የተጠናወተው ወንጀል ጀሯችን ሆኗል ። በተለይ በአቅመ ደካማ ህጻናት ታዳጊዎችና በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ወንጀል እያደር መክፋቱ  ጸሀይ የሞቀው እውነት ሆኗል። በዚህ ረገድ እየተኬደ ያለውን የከፋ ወንጀል ሳስበው " ወደ የት እየሄድን ይሆን?  " እያልኩ ያስፈራኛል  ! የአጉራ ዘለል አስገድዶ የመድፈር ወንጀለኞች መስፋፋት ፣ እያደር ውሎ አዳራችንና አብሮነታችን እንዳያጎድፈውም በአስፈሪ የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን  !  ሴሰኛ ወንጀለኛ ሽምጥ ጋልቦ  እዚህ ሲደርስ ወንጀሉን በጥብቅ ተከታትሎ የማያዳግም ቅጣት አርአያነት ያለው ውሳኔ ቢሰጥ ዛሬ እዚህ ባልተደረሰ ነበር ፣ ይህ አይፈጸምምና ፣ ይህ አልተደረገምና ዛሬ ውርደትን መከናነብ ግድ ብሎናል ።  የተከናነብነው ውርደት ምክንያት የሆነን ወንጀልም ሊሰሙት ከሚችሉት በላይ ሰቅጣጭና የከበደ እየሆነ ለመምጣቱ ብዙ ማሳያዎችን ማቅረብ አይገድም  !
ይህን ሁሉ የምለው በአንዲት የ4 ዓመት ከ6 ወር ብላቴና ተዳጊ ላይ የተፈጸመው ወንጀልና ተመጣጣኝ ያልሆነውን የፍርድ ውሳኔ ወደምቃዎምበት የማለዳ ወጌ የመረጃ ግብአት ለመዝለቅ ነው   ! እንደኔ የፍትህ መዛባት ዘልቆ ያመማችሁ ተከተሉኝና ፍርዱን ስጡ ... !
በያዝነው ሳምንት ማህበራዊ መገናኛ ድህረ ገጾችን ቀልብ የሳበው ጉዳይ መካከል የ4 ዓመት ከ6 ወሯ ታዳጊ  መደፈርን ተከትሎ የተላለፈው ዜና የብዙዎቻችን ቀልብ ስቧል ። ለዚህ መሰሉ ዜና አዲስ ባይንሆንም ብላቴናዋ  መደፈሯ ሳይሰማ ባሳለፍነው ሳምንት ሀሙስ  በመጨረሻ ው የፍርድ ውሳኔ ጋር ሰማን ፣ በውሳኔውም ደፋሪው የ4 ወር እስራት ቅጣት ፍርድ መሰጠቱን በአንድ ላይ ሲነገረን ማመን ከተቸገሩት መካከል አንዱ ነበርኩ።  የጉዳዩን ጭብጥ ለማጣራት ባደረግኩት ሙከራ ያገኘሁት መረጃ ይዠ የዜጋ ተቃውሞ ድምጼን በማለዳ ወጌ ላሰዳ ስውተረተር በድሬ ትዩብ ስሟን በመጥቀስ በጉዳዩ ዙሪያ የቀረበ አንድ ዘገባ ለወጌ መረጃ ግብአትነት ተጠቅሜበታለሁ ። ትክክለኛ ስሟ ስለመሆኑ ግን ማረጋገጫ አላገኘሁም ። ስሟ ቢታወቅም መግለጹ አስፈላጊ ባለመሆኑ የድሬ ትዮብን ስም ተቀብየ እዘልቃለሁ ።  ከዚሁ በተጨማሪ ሌላም ሌላ መረጃዎችን ለማሰባሰብና ለማጣራት ሞክሬ በእርግጥም ወንጀሉ ለመሰራቱና ፍርደ ገምድል ብይን የመሰጠቱ ሁነኛነት አረጋግጫለሁ  !
የተሰራጩ መረጃዎች እንደሚስረዱት ታዳጊዋን የ4 ዓመት ከ6 ወር ተዳጊዋን አሚራ ትባላለች ።  ኑሮዋም አዲስ አበባ አቃቂ ክፍለ ከተማ እንደሆነ ተጠቁሟል። ደፈረ የተባለው አስነዋሪ ወንጀል ፈጻሚ የ25 ዓመት ጎረምሳ ነው። በችርቻሮ ንግድ የሚተዳደሩት የአሚራ ቤተሰቦቿ ቤት ጎን ተከራቶ ነበር አሉ ።
ከውሳኔው አስቀድሞ ተከሳሽ አሚራን ስለመድፈሩ ክስ ቀርቦበት ፣ ጉዳዩ በፖሊስ ቀርቦና ተጣርቶ ተከሳሽ ተይዞ በፊዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአቃቂ ቃሊቲ ፍርድ ቤት ችሎት የቀረበ ሲሆን በ30 ሽህ ብር ዋስትና ተለቀቀ።  ክሱን በዋስ ወጥቶ እንዲከላከል በፊዴራድ  ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአቃቂ ቃሊቲ ፍርድ ቤት ወሰነ ። ያ ከሆነ በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ተከሳሽ  ለብይን ቀረበ ። ፍርድ ቤቱ በፖሊስ የቀረበለትም ምርመራ ተመልክቶ በሰጠው ውሳኔ " ተከሳሽ ድንግልናዋን ባይገስም በእጆቹ የማህጸኗ ግድግዳ የመሰንጠቅና የመላላጥ  ጉዳትና ማድረሱና በማህጸኗ የመቅላት ምልክት በመታየቱ  !" በሚል ማስረጃ  ፍርድ ቤተ ተከሳሽን " ሞከርክ " በሚል ወንጀለኛ ሲል የ4 ወር እስራትን አስተላልፎበታል ። ይህው ፍርድ ቤት ገና የትምህርት ገበታ ያልቀመጠችን ታዳጊ ብላቴና አመራን  የደፈረበትን የጨካኝ ድርጊት ከደፈረ ሞከረ ቀይሮ በቀረበ ማስረጃ በፍትሀ ብሔር ህግ 6264 ሀ መሰረት ውሳኔ መሰጠቱ ተነግሮናል ። አስገራሚ ፣ አስደንጋጭና አሳዛኝ የፍርድ ውሳኔ !
ክሱን አቀለለ ወደተባለው ምክንያት ስንሄድ ደግሞ ይበልጡኑ እንታመማለን ... ወንጀለኛው  " የሳንባ ነቀርሳ በሽተኛና በቀጣዩ አመት ተመራቂ !" መሆኑን በቅጣት ማቅለያነት አቅርቦ በፍርድ ቤቶ ተቀባይነት ማግኘቱ አገኘ ብለውናል  ። ለእኔ  የክስ ማቅለያ የቀረበው ሀሳብ የተማረ የተመራመረው " የዩኒቨርሲቲ ተማሪ " ነኝ ባይ ወንጀለኛ ነው ፣  ምንም የማታውቅን እምቦቃቅላ ታዳጊ ገላን በአሻው መንገድ አድርጎ ገፎታል ፣ ገፈፋውም የተፈጸመው በአንድ አዋቂ መሆኑ ብቻ ወንጀሉን ሊያከብድ እንጅ ሊያቀል ባልተገባ ነበር ባይ ነኝ ። ይህ ያቀረበው የክስ ማቅለያ ይልቁንም በሰነድ ተረጋግጦ ክሱን ማጠንከር ሲገባው ክሱን ማቅለያ ሆኖ መቅረቡና ከምን ወደ ምን እንደቀለለ ያልተገለጸው ማቅለያ ተቀባይነት ማግኘቱ በራሱ  በምንም ሚዛን ፍትሃዊነት የለውም  ! ይህን ለመናገር ሰብእናና የራስን ፍርድ መስጠት እንጅ ግዴታ ህግ ማጥናት አያስፈልገውም ...
የህዝብን መብት ለማስጠበቅ የተሰየሙትን የፍትህ አካላት የሙያ ብቃት ጥያቄ  ውስጥ የጣለው ይህ መሰሉ አሳዛኙ የፍትህ ውሳኔ ማህበረሰቡ በፍትህ እንዳይተማመን ከማድ ረግ ባሻገር በህግ ጥላ ስር መጠበቁን በጥርጣሬና እንዲ ያይ እንደሚያደርገው ጥርጥር የለኝም ። ከዚህም አልፎ ተርፎ በአሚራ ደፋሪ ላይ የተላለፈው ውሳኔ ሀገሬው  ፍትህ አጥቶ የሚንገዋለል እንዲሆን አድርጎታል ወደሚል መደምደሚያ አድርሶኛል ... የአስገድዶ መድፈር ወንጀለኞ ች ጉዳይ መስፋፋትና ገደብ ማጣት በተደጋጋሚ በመንግ ስት ላይ የሰላ ወቀሳ ይቀርባል ። በተለይም የህግ ጥበቃ ውንና ቅጣቱን ከማጠንከሩ በተጓዳኝ ተማኝነት እንጅ የሙያ ብቃት ሚዛን ሆኖ ቅጥር ስለማይፈጸም ተደጋጋሚ ችግሮች ተስተውለዋል ። የፍትህ አካላት ብዛት እንጅ ጥራት የጎደላቸው መሆኑ ከዚሁ ጋር ይጠቀሳል ።  የተባለውን ወቀሳ እውነታነት እንዳለው ለመረዳት የአሚራን አይነት በደል ተሰርቶ የተሰጠውን ውሳኔ መመልከት ብቻ  ማየት ከበቂ በላይ ይመስለኛል  ።
በአሚራ ውሳኔ አሰጣጥ  እንዳየነው ከምንም በላይ የፍትህ ስርአቱ በወንጀለኛውም ሆነ በጠበቆች የቀረበውን የተውተፈተፈ መከላከያና ቅጣት ማቅለያ መቀበላቸው ለፍትህ አካላት የደረሱበትን ደረጃ ያሳይ ከሆነ መልካም ነው ። የአሚራን ጉዳይ በግርድፉ ላየ ለተመለከተው   ጥፋታቸውን በአዞ እንባ ለመሸፋፈን ከተጉ ወንጀለኞች ጎን ለገንዘብ ብለው ጥፋቱን ለማቅለል ሚሞግቱት ጠበቆች ሰብዕና ያማል ፣  የዳኞቹ ውሳኔ አሰጣጥና ውሳኔ ማቅለያ አቀባበል ደግሞ  ይገርማል ፣ ይደንቃል ... !  ይህ መሰል ከእውነታው ጋር የሚጋጭ የተፋለሰ ፍርድ  በአደባባይ ሲሰጥ ህጉን ማስከበር ያለባቸው አቃቤ ህግ ተወካዮች የታሉ  ? ፍትህ ወዴት ነህ  ?  ያስብላል ...
በሰብዕና ላይ ወንጀል ሲሰራ በቸልተኝነት መመልከት ሊቆም ይገባል ።  የሴቶችን መብት ለማስከበር ተብሎ የወጡት ሕጎች  ተፈጻሚ  ይሆኑ ዘንድ  የኢትዮጵያ  ሰብአዊ  መብት  ኮሚሽን  አካል  የሆነ  የሴቶችና ሕጻናት  ጉዳዮች  ብሔራዊ  ኮሚሽንን  በ2005  ዓም መቋቋሙን ከሰማን አመታት ተቆጥረዋል ።  ኮሚሽኑ በሴቶችና  በሕጻናት ለሚፈጸሙ የሰብአዊ  መብት  ጥሰት  ተገን እንደሚሆን ቢጠቀስም ለአሚና የጎደለ ፍትህ ድምጹን ሲያሰማ አለመታየቱ ግር ያለው እኔን ብቻ ከሆነ መልካም ነው ፣ ግን አይመስለኝም ። " መብቷ ይከበር ፣ ፍትህ ጎድሎባታል፣  ፍትህ ታግኝ " የምንላት  ታዳጊዋ አሚራ ያለ ፈቃዷ አይደለም ገላዋ የጸጉር መጠምጠሚያ "ሂጃቧ " ሊነካ አይገባም ፣ ከተነካ ህግ ተጥሷል ! አሚና ድንግልናዋ አልተገሰሰም ፣ ማህጸኗ ግን ተነካክቷል ብሎ ወንጀለኛን ከአስገድዶ መድፈር ወንጀል ማራቅ ፣ ማሸሸት ፍትህን ማረጋገጥ ሳይሆን ፍትህን ማርከስ አድርጌ ነው የምቆጥረው ።  ወንጀለኛው " አስገድዶ የደፈረ " ለመባል አሚራ በጭካኔ ተደፍራ እንደተገደለችው እንደ ሀና ኦላንጎ መሆን አልነበረባትም  ! አሚራም ሀና እንደሆነችው ባትሆንም በአሚራም ማህጸን ዙሪያ ክብረ ነክ የመድፈር ሙከራ አድርጓል ። የቀረበው ማስረጃ የሚየስረዳው አርቆ አሳቢው የተማረ ጎልማሳ ምንም በማታውቀው የ4 ዓመት ከ6 ወር ታዳጊ ህጻን ላይ ወንጀል አስገድዶ መድፈር ለመሆኑ ሌላ ከበቂ በላይ ማስረጃ  አለ ብየ አላምንም!
የሴቶችና ሕጻናት  ጉዳዮች  ብሔራዊ  ኮሚሽንን  ሴቶች  ሥርዓተ-ፆታን  መሠረት  ያደረገ  ጥቃት ደርሶባቸው እንዲህ ሲመለከት አብሮ ከተጎጅ ወገኖች ጎን  መቆም ፣ የሕግ  ጥበቃ  ማቆም ፣ የህግ ጠበቃ የማቆም አቅም ከሌለው  የህግ ጥሰቱን በአደባባይ ተቀውሞ ስታዳጊዋ ብላቴና ስለአሚራ ፍትህ ማግኘት ድምጹን ሊያሰማ ይገባል !
በፍርድ ገምድሉ ውሳኔ ያዘኑ ቤተሰቦች  ወላጆቿ ፍትህ ጎድሎባቸው " ወላጅ ይፍረደን፣ህዝብና ሀገር ይፍረደን!" ማለታቸው ስሰማ የእነሱም ጩኸትና አቤቱታ የእኔም ለአሚራና ቤተሰቦቿ ፍትህ ርትዕ ይከበርላቸው የሚል ጥያቄ እንዳነሳ አድርጎኛል  ! ከምንም በላይ የሴት ልጅ በረከት የታደልኩ አባት እንደመሆኔ የሴት ልጅን ወሰን የሌለው ፍቅር አውቀዋለሁና ከአሚራ ቤተሰቦች ጋር ልቤ በሀዘን ተሰብሯል ፣ በጎለው ፍትህ አምርሬም አዝኛለሁ ... !
ፍትህ ለህጻን አሚራና ቤተሰቦቿ ስል እጠይቃለሁ  !
ነቢዩ ሲራክ
ነሀሴ 5 ቀን 2007 ዓም

Friday, August 14, 2015

የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች በከፍተኛ ስብሰባ ተጠምደዋል::

August14,2015

sirag fergesa and samora
የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በከፍተኛ ስብሰባ ላይ መጠመዳቸውን ከቦታው ያገኘነው መረጃ አስታወቀ:: በአዲስ አበባ ከተማ ከሃምሌ 25 ቀን 2007 ዓ/ም ጀምሮ በከፍተኛ የመከላከያ ሰራዊት አዛዦች ሳሞራ የኑስና ሲራጅ ፈርጌሳ ስብሰባ መካሄዱና በስብሰባው እንደመወያያ ርእስ ሁኖ የቀረበውም አዲስ ሰራዊት ቢጨመርም አብዛኛው የሚፈርስና የሚበታተን በመሆኑ አሁንም የሰራዊቱ ይዘት አነስተኛ ነው። እናንተ ምን እያደረጋችሁ ነው? ለምንድነው የማትቆጣጠሩት የሚል እንደነበር መረጃው አስረድቷል።
የክፍለ-ጦሮች አመራሮች የቀረበላቸውን ጥያቄ መመለስ እንዳልቻሉ የገለጸው መረጃው ስብሰባው ወደ ታች በመስመራዊ መኮነን ደረጃ ወርዶ በተለይ ከሻንበል በላይ በተደረገው ስብሰባ ላይ የሰራዊቱ መፍረስ ምክንያት በከፍተኛ የሰራዊቱ አዛዦች ውስጥ ብልሹ አሰራር፤ ወገናዊነትና አድልዎ በመኖሩ ነው ብለው መናገራቸው ተገልጿል።
መረጃው በማከልም- የበላይ የሰራዊቱ አዛዦች ከተራ ወታደሮችና የበታች የሰራዊቱ አዛዦች የነጠቁትን ገንዘብ የግል ኑሮአቸውን እያመቻቹበት ነው ተብሎ በስብሰባው በተነገረበት ግዜና የተሰጠውን ሃሳብ ተከትሎ የድጋፍ ድምፅ በተሰማበት ወቅት የመድረኩ መሪዎቹ ድንጋጤና ፍርሃት እንደተሰማቸውና በከባድ ስጋት ላይ በመውደቃቸው ምክንያት አመራሮቹ ስብሰባውን ለማካሄድ መቸገራቸውን መረጃው አክሎ አስረድቷል።

Thursday, August 13, 2015

የኤልያስ ገብሩ ቆይታ ከጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጋር (ዝዋይ እስር ቤት)

August 13, 2015
በኤልያስ ገብሩ
  • ታገሉ! ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (ከዝዋይ እስር ቤት)
  • ተመስገን ደሳለኝ ስለሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ፍርድም ሀሳቡን ሰንዝሯል
Temesgen Desalegn Fteh newspaper editor
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ቦሌ አካባቢ ብርዱ ጠንከር ያለ ነበር፡፡ ከቦሌ ብራስ ወደሚሊኒየም አዳራሽ በሚወስደው ቀጭን መንገድ ላይ ወንዱም ሴቱም በፍጥነት ይራመዳል፡፡ ከታክሲ በሁለቱም አቅጣጫዎች የወረዱ ሰዎች ወደመደበኛ ሥራቸው ለመግባት ብሎም የግል ጉዳያቸውን ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ነበር – ከትናንት በስትያ ሰኞ (ነሐሴ 04 ቀን 2007 ዓ.ም) ጥዋት 1፡45 ሰዓት፡፡
እኔ እና ወዳጄ አቤል ዓለማየሁ ወደከአዲስ አበባ 160 ኪሎ ሜትር ርቀት ወደሚገኘው ዝዋይ እስር ቤት አምርተን ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን እና ተመስገን ደሳለኝን ለመጠየቅ በዚህ ቀን ቀጠሮ ይዘን ነበር፡፡ አቤል ከቀጠሯችን 20 ደቂቃ ዘግይቶ፣ ቦሌ ጫፍ ደረሰና ወደቃሊቲ መናሃሪያ ሁለት ታክሲዎችን በመጠቀም ደረስን፡፡ ወደዝዋይ የሚጭኑ ሚኒባስ ታክሲዎች እና ‹‹አባዱላ/ዶልፊን›› የሚል መጠሪያ የተቸራቸው የህዝብ ማመላለሻ መኪኖች ቢኖሩም በተለምዶ ‹‹ቅጥቅጥ›› የሚባለውን መካከለኛ አውቶቡስ ምርጫችን አደረግን – የትራፊክ አደጋን በመስጋት፡፡
የተሳፈርንበት አውቶቡስ፣ ከቃሊቲ ትንሽ ወጣ ካለ በኋላ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ በእስር ላይ የሚገኙትን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ “ልማቱን አሳዩኝ” ሲለን ከከተማ ወጣ እያደረግን የምነሳየው… [እውነት ግን፣ በከባድ እስር ላይ መሆናቸው የሚገመተው አቶ አንዳርጋቸው ‹ልማቱን አሳዩኝ› ይሏቸዋልን?!]›› ሲሉ ለቪኦኤዋ ጋዜጠኛ ትዝታ በላቸው የገለጹትን፣ የአዲስ አበባ አዳማ አዲሱ የፍጥነት መንገድ (Express way)ን ተቀላቀለ፡፡ በዚህ መንገድ ሁለታችንም ሄደን አናውቅም ነበር፡፡ ሆኖም እስከዛሬ ካየኋቸው የመኪና መንገዶች በደረጃው ከፍ ያለ ይመስላል፡፡ [በሀገራችን አምረው የተሰሩ የመኪና መንገዶች በጥቂት ዓመታት ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የመቦርቦር፣ የመፈረካከስ፣ ውሃ የማቆር ችግሮች ገጥሟቸው እንዲሁም ከመንገዱ ዳር እና ዳር የሚገኙ የብረት አጥሮች ተሰርቀው፣ ተገጭተው፣ ተጨረማምተው፣ ተነቃቅለው … አደጋ ሲያደርሱና የተለመደ የሬንጅ የመለጠፍ ሥራ ሲሰራላቸው በገሃድ የምናየው ሀቅ መሆኑን ማስታወስ ግን የግድ ይላል] ይሄኛው መንገድ ከጠቀስኳቸውና ካልጠቀስኳቸው ችግሮች ምን ያህለ ነጻ ነው? ለሚለው ትክክለኛ መስክርነት መስጠት ያለበት ለእውነት የቆመ የዘርፉ ባለሙያ ቢሆንም በኢህአዴግ ‹ልማት› ላይ የጥራት መተማመኛ ማግኘት እጅግ ከባድ መሆኑን ግን አምናለሁ፡፡ አስፋልቱ ለፍጥነት አመቺ መሆኑን ግን በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡
በሶስት ሰዓታት ጉዞ ዝዋይ በመድረስ ምሳ ከበላን በኋላ ወደእስር ቤቱ የፈረስ ጋሪ መጠቀም ግዴታችን ነበር፡፡ አቧራማው አስቸጋሪ መንገድ፣ ከፊሉ ደቃቅ አሸዋ መልበስ ጀምሯል፡፡ የእስር ቤቱ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ፣ በፊት ውብሸትን ለመየጠቅ ስመጣ ከማውቀው ተፋጥኗል፡፡ አንዱ የሥርዓቱ “የልማት ውጤት” እስረኛ ማብዛት አይደለ ታዲያ?!
ከቀኑ 7፡30 ሰዓት ላይ የምንጠይቀውን እስረኛ በማስመዝገብ ተፈትሸን ገባን፡፡ ሁለት እስረኛ በአንዴ መጠየቅ ስለማንችል እኔ ተመስገን ጋር፣ አቤል ደግሞ ውብሸትን ለመጠየቅ ተስማምተን ነበር፡፡ አቤል ውብሸትን ከጠየቀ በኋላ እንደምንም ብሎ ተመስገንን ለመጠየቅ ጥረት እንደሚያደርግ ግን ቀድሞ ነገረኝ፡፡
ተመስገን እና ውብሸት የታሰሩበት ዞን ስለሚለያይ እኔ እና አቤል ሌላ የውስጥ ፍተሻ ካደረግን በኋላ መለያየታችን ግድ ነበር፡፡ የእስር ቤቱ ፖሊሶች የሚኖሩበትን ጉስቁልና ያጠቃቸው፣ መኖሪያ ቤቶችን አልፌ መጠየቂያው ጋር ደርሼ የታሳሪው ስም ያለባትንና በፖሊሶች የምትጻፈዋን ቁራጭ ወረቀት እስረኛን ለሚጠራው ፖሊስ ሰጠሁትና በአጣና እንጨት ርብራብ በተሰራው መጠየቂያው አግዳሚ ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ከቅርብ ርቀት የፖሊሶች ማማ ይታያል፡፡ መሳሪያ የታጠቁ ፖሊሶች ማማው ላይና ከማማው ሥር በዛ ብለው ተቀምጠው ያወጋሉ፡፡ አብዛኞቹ ፖሊሶች ከላይ የለበሷት እና “Federal prison” የሚል የታተመባት አረንጓዴ ዩኒፎርምም በፀሃይ ብዛት ነጣ ወደማለት ደርሳለች፡፡ አንዱ ፖሊስ መጣና ከእኔ በትንሽ ሜትር ራቅ ብሎ ተቀመጠ፡፡ ‹‹አዳማጭ ነው›› አልኩ በልቤ፡፡ ወደፊት ለፊቴ ወደሚታየኝ የእስር ቤት ግቢ አማተርኩ፡፡ ለእይታ የሚጋብዝ አንዳች ነገር አጣሁ፡፡ የተበታተኑ ዛፎች፣ ቅርጽ አልባ ሳሮች፣ አስታዋሽ ያጡ አረሞች፣ ግድግዳ እና ጣራቸው በቆርቆሮ የተሰሩ የእስረኛ መኖሪያዎች፣ …ብቻ ጭርታ እና ድብታ የወረረው የግዞት መንደር ይመስላል፡፡
ከአንደኛው የእስረኛ ቆርቆሮ ቤት ጣሪያ ላይ ሁለት ተለቅ ተለቅ ያሉ ሙቀት ማቀዝቀዣዎች ይሽከረከራሉ፡፡ ወደፖሊሱ ዞሬ ‹‹ለሙቀት ነው?›› አልኩት ወደ ጣራው በመጠቀም፡፡ ‹‹አዎ፣ ወባ አደገኛ ነው›› አለኝ፡፡ ‹‹እስረኞች ሲታመሙ እንዴት ይሆናሉ?›› ስል ጥያቄ ሰነዘርኩ፡፡ ‹‹ያው እዚሁ ይታከማሉ›› አለኝ ድምጹን ቀሰስ አድርጎ፡፡ የእኔም ሆነ የእሱ ልብ፣ በማረሚያ ቤቱ (በእነሱ አጠራር) በቂ ህክምና እንደማይሰጥ ግን ያውቃል ብዬ አሰብኩ፡፡ ቀጭኑ ፖሊስ፣ ‹‹ለወባ ህመም ምግብ ወሳኝ ነው›› አለኝ አስከትሎ፡፡ ‹‹በቂ ምግብ የለም ማለት ነው?›› ስል ድጋሚ ጠየኩት፡፡ ‹‹በፊት በፊት አቀራረቡ ዝም ብሎ ነበር፤ ሙያ ባሌላቸው ሴቶች ነበር የሚሰራው፡፡ አሁን ግን ለውጥ አለ›› አለኝ፡፡ ‹‹ምን አይነት ለውጥ? ጥቂትም ቢሆን ታስሬ፣ ለእስረኞች የሚቀርበውን በጣም ደረጃውን ያልጠበቀ ምግብ አይቻለሁ›› አልኩት፡፡ ‹‹በፊት ጥቁር ጤፍ ነበር የሚቀርበው፤ አሁን የነጭ ጤፍ እንጀራ ነው የሚበሉት፤ እስረኞች ችግር የለባቸውም፤ ባለሙያ ሴቶችም ናቸው የተቀጠሩት …›› ‹‹(ውስጤ አላመነምና) ለእስረኛ የነጭ ጤፍ እንጀራ እያቀረባችሁ ነው?!›› …‹‹አዎ›› ብሎ ሊያብራራልኝ እያለ ከታች ከርቀት ‹‹አረንጓዴ ኮፊያ፣ ቲ-ሸርትና ስካርፍ ያደረገ ሰው አየሁ፡፡ ትኩረቴን ከፖሊሱ አዙሬ ቁልቁል ተመለከትኩ – ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ነበር፡፡ ተሜም፣ ረጋ ብሎ በራስ በመተማመን መንፈስ ወደመጠየቂያው ሥፍራ ቀረብ ብሎ ጠያቂውን ለማወቅ ጥረት አደረገ፡፡ ሳየው አንዳች የሀዘን ስሜት ውስጤ ገባ፡፡ ቆሜ ጠበኩት፡፡ ፈገግ እያለ መጣና ተጨባብጠን አራት አምስቴ ያህል ተቃቀፍን፡፡ ‹‹በዚህ በጸሐይ ለምን መጣህ?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ከአቤል ጋር መምጣታችንን፣ እሱ ውብሸትን ሊጠይቀው መሄዱን ነገር ግን ከቂሊንጦ በኋላ እስከአሁን ዝዋይ ድረስ መጥቼ ባለመጠየቄ የጸጸት ስሜት ውስጤ እንዳለ ገለጽኩለት፡፡ ‹‹መንገዱ ረዥም ነው፣ ባትመጡም እረዳለሁ›› ካለ በኋላ፤ ‹‹ምን አዲስ ነገር አለ?›› በማለት ፊት ለፊት በእንጨት አጥር ተከልለን በመቀመጥ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡
‹‹አሁን ምን እየሰራችሁ ነው?››፣ ‹‹ክስህስ እንዴት ሆነ?››፣ ‹‹አዲስ ጋዜጣ ለማቋቋም ለምን ጥረት አታደርጉም?›› ከተመስገን በተከታታይ የተነሱ ጥያቄዎች ነበሩ፡፡ አጠር አጠር አድርጌ መለስኩለት፡፡ የጋዜጣ /የመጽሔት ህትመትን ድጋሚ መጀመር የግድ አስፈላጊ መሆኑን ግን ተመስገን አጽንኦት የሰጠበት ጉዳይ ነበር፡፡ …ስለተወሰኑ ጋዜጠኞችና የዞን 9 ጦማሪያን ከእስር መፈታት፣ ስለኦባማ የአዲስ አበባ ጎብኝት፣ በቂሊንጦ ዞን አንድ ከእነአብበከር አህመድ፣ ጦማሪ አቤል ዋበላና ዘላለም ክብርት ጋር ስለነበረው ቆይታ፣ እሱ ወደዝዋይ ከወረደ በኋላ እኔም በዚያ ዞን ገብቼ በነበረበት ጊዜ እነአቡበከር፣ አቤልና ዘላለም እሱን በተመለከተ ስለነገሩኝ ነገሮች ሳቅ እያልን አወጋን፡፡
ሰፊ ውይይት ያደረግነው በሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ በቅርቡ ከ7 እስከ 22 ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራት ፍርድን በተመለከተ ነበር፡፡ ‹‹እኛ ከሙያ ጋር በተያያዘ ነው የታሰርነው፡፡ ታስረንም እንወጣለን፡፡ ከባዱ የሙስሊሞቹ እስር ነው፡፡ ኢህአዴግ እውነተኛ ሰላም ከፈለገ እነአቡበከርን በነጻ መፍታት አለበት፡፡ እኔ የእነሱ መከላከያ ምስክር ሆኜ ምስክርነቴን ሰጥቻለሁ፡፡ በወቅቱ ዘንግቼው ያልተናገርኩት አንድ ነገር ነበር፤ አሁን ሳስበው ትንሽ ይቆጨኛል – በተናገርኩ ብዬ፡፡ ያኔ (በምስክርነት ጊዜ)፣ ‹የኮሚቴዎቹ እንቅስቃሴ ሰላማዊ ነበር ወይስ አልነበረም?› የሚለው ጥያቄ በራሱ መነሳት አልነበረበትም፡፡ እንቅስቃሴያቸው፣ ሰላማዊ ባይሆን ኖሮ እንዴት ሶስት ዓመት ሙሉ በክስ ሂደት ይቀጥላል?! ሰላማዊ ስለሆኑ እኮ ነው፣ ባለፉት ሶስት ዓመታት ምንም ያልተፈጠረው፡፡ እስኪ በእነሱ አንድ የተሰበረ መስታወት አለ?! ቅንጣት የወደመ ንብረት አለ?! የማንንስ ሕይወት አጠፉ?! በእነሱ የተፈጠረ አንድም ነገር የለም፡፡ ጥያቄያቸው ኃይማኖታዊ እንጂ ፖለቲካዊ አይደለም፡፡ ፖለቲካዊ ቢሆን ኖሮ ትግሉ አቅጣጫውን ይቀይር ነበር፡፡ ‹የመጅሊስ አመራሮችን ካለመንግሥት ጣልቃ ገብነት እንምረጥ!› ነው አንዱ ሰላማዊ ጥያቄያቸው፡፡ ያው ምስክር ስትሆን ከዚህም ከዚያ ጥያቄ ሲነሳ ስለምትዘናጋ መመስከር ያሰብከውን ነው ቅድሚያ የምትሰጠው እንጂ አሁን የምልህን ያኔ ብገልጸው በጣም ደስ ይለኝ ነበር …›› በማለት በኢትዮጵያ ውስጥ ከታሪክ አኳያ፣ በሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖት ተከታዮች መካከል ስለነበረው ግንኙነት በዝርዝር የራሱን ምልከታ እና ሀሳብ ደጋግሞ አወጋኝ፡፡ ኃይማኖታዊ መቻቻል ነበር ወይስ አልነበረም? የሁለቱም እምነት ተከታዮች ጉርብትና ነበራቸው ወይስ አልነበረባቸውም በሚሉት አንኳር ጉዳዮችም የራሱን አቋም አንጸባረቀልኝ፡፡
ኡስታዝ አቡበከር አሕመድን አስመልክቶም አንድ ጥሩ ምሳሌም አንስቶልኝ ነበር ተመስገን፡፡
‹‹አሁን ባለሁበት ዞን፣ በአንድ የወንጀል ክስ ግብረ-አበር ተብለው አምስት ዓመት የተፈረደባቸው አንድ ቄስ አሉ፡፡ እኚህ ቄስ ለጠበቃ የሚከፍሉት አጥተው የጠበቃ ክፍያ የፈጸመላቸው አቡበከር እንደሆነ ነግረውኛል››
እኔም ፣ በህዳር ወር ቂሊንጦ ዞን አንድ በነበርኩበት ጊዜ ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ነገር፣ ስለአቡበከር ሰምቼ ነበር፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፡- አንዱ እነአቡበከር ይገኙ በነበረበት ዞን 1 8ኛ ቤት ውስጥ የቀጠሮ እስረኛ ነበር፡፡ ዋስትና ይጠየቅና በዚህ ክፍል ውስጥ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ አንድ የናጠጡ ሀብታም (ልጃቸው 22 አካባቢ እጅግ ዘመናዊ ሆቴል አለው) ጋር ጠጋ ብሎ ለዋስትና የሚሆን ብር ተጨንቆ በአክብሮት ይጠይቃቸዋል፡፡ እሳቸውም ‹‹እኔም እንደአንተው እስረኛ እኮ ነኝ!›› በማለት ይመልሱለታል፤፡፡ ልጁም ያዝናል፡፡ ይህ ጉዳይ አቡበከር ጆሮ ይገባና ለልጁ የሚስፈልገውን የዋስትና ብር ከፍሎ ልጁን ከእስር እንዲወጣ አድርጎታል፡፡ እንግዲህ፣ ከሁለቱ እውነተኛ ምሳሌዎች በመነሳት፣ አቡበከር ለወገኖቹ ሃይማኖትን መሰረት ሳያደርግ፣ በሰብዓዊነት ደግ መሆኑን እንማራለን፡፡
ከተመስገን ጋር በነበረን ሰፋ ባለ የጨዋታ ጊዜ፣ ከጎኔ የነበረው ፖሊስ በተመስጦ ቢያዳምጥም፣ አንዴም አላቋረጠንም ነበር፡፡ …ስለ 100% ቱ የዘንድሮ ምርጫ ፍጻሜ፣ በሰሞኑ በአፋር ክልል ስለደረሰው የድርቅ አደጋ፣ በአይ ኤስ አሸባሪ ቡድን ስለተቀሉና ስለተገደሉት ኢትዮጵያኖች፣ ድርጊቱን በማውገዝ በመስቀል አደባባይ በተጠራው ሰልፍ ላይ ስለተፈጠረው ረብሻ፣ ጉዳትና እስር ተመስገን የራሱን አተያይ በስሜት ተውጦ የግሉን ሀሳብ አብራራልኝ፡፡ በተጨማሪም፣ አይ ኤስ ያንን ድርጊት፣ ያንን ጊዜ መርጦ አደረገ ያለበትን የራሱን የተለየ (ከማንም ያላደመጥኩትን፣ ተጽፎም ያላነበብኩትን) ሀሳብ አጋራኝ፡፡ የተለየ ሃሳብ በመሆኑም ‹‹አሃ!›› ብያለሁ፡፡
ከተመስገን በጣም የገረመኝ፣ የማስታወስ ችሎታው ነበር፡፡ በጥቅምት ወር፣ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ‹‹ጥፋተኛ›› በተባለበት ማግስት ጥዋት አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ልጠይወቅ ሄጄ በማያመች ሁኔታ ውስጥ ሆነን አብዮትን አስመልክቶ የተለዋወጥናቸውን ሃሳቦችን፣ እንዲሁም ከአቤል ጋር ቂሊንጦ ስንጠይቀው ያነሳናቸውን ሀሳቦች ድጋሚ በማስታወስ በዚህ ቀን ለተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች የውይይት ማጠናከሪያ ሀሳብ ሲያደርጋቸው አስተውያለሁ፡፡
ለተመስገን አሁን ስለሚገኝበት ዞን ሁኔታ ጥያቄ አቀረብኩለት፡፡ ቀደም ሲል ከእነውብሸት ጋር አብሮ እንደነበረ ጠቅሶ፣ ‹‹የኢትዮጵያ ገመና›› በሚል ርዕስ በእስር ቤት ውስጥ ስላወቀው ነገር ሁለት ተከታታይ ጽሑፎችን ካወጣ በኋላ ወደዚህ ዞን መዘዋወሩን ይገልጻል፡፡ አሁን ባለበት ክፍል 80 የሚሆኑ እስረኞች አብረውት አሉ፡፡ ብዙዎቹ ከደቡብ ክልል የመጡ ናቸው፡፡ ከእሱ ጋር አንድም የፖለቲካ እስረኛም ሆነ ጋዜጠኛ አብሮት የለም፡፡ [አቶ በቀለ ገርባ ከወራቶች በፊት የ3 ዓመት ከ7 ወር የእስር ጊዜያቸውን አጠናቅቀው ከዝዋይ እስር ቤት በተፈቱ ማግስት ተመስገን ከባድ ወደሆነው ወደዚህ ዞን መሸጋገሩን ነግረውኝ ነበር] አሁን ባለበት ዞንም ከእሱ ጋር እስረኞች እንዳያወሩ እና እንዲያገልሉት በዘዴ ተደርጓል፡፡ ከእሱ ጋር በቅርበት ሆነው የሚያወሩ ካሉ፣ እንደትልቅ ተስፋ በሚጠብቁት አመክሯቸው ላይ እንደመፍረድ ይቆጠራል እንደተመስገን አባባል፡፡ ‹‹በዚህ ጉዳይ ማናቸውም ላይ አልፈርድም፤ ከእኔ ጋር አውርተው የአመክሮ ጊዜያቸውን እንዲያጡ አልሻም፡፡ ግን እንዲህ ያደረጉት ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ቢሆኑ ኖሮ ይሰማኝ ነበር፡፡›› ሲል ያለበትን ከባድ ሁኔታ ያስረዳል፡፡
‹‹ማንበብ፣ ማጸፍስ ትችላለህ?›› ሌላኛው ጥያቄዬ ነበር፡፡ ‹‹መጽሐፍ አይገባም ተልክሏል፤ ያነበብኳቸው ጥቂት ልብወለድ መጽሐፍቶች አሉ፡፡ መጻፍ ትንሽ ጀምሬ በእስረኞች በኩል ተጠቁሞ የጻፍኩት ተወሰደ፡፡ ሁለት ሶስቴ ለመጻፍ ሞክሬ ነበር፡፡ ግን ተመሳሳይ እርምጃ በመወሰዱ ተውኩት፡፡›› ይላል ተመስገን፡፡ ‹‹ቀኑን እንዴት ነው የምታልፈው?›› የሚለው የመጨረሻ ጥያቄዬ ነበር፡፡ ‹‹ሁለት የማውቃቸው የአዲስ አበባ ልጆች አሉ፤ ጫናውን ችለው ያናግሩኛል፡፡ ከእነሱ ጋር ቼዝ እጫወታለሁ፡፡ የእግር ኳስ ፕሮግራም የሚተላለፍባቸው ቻናሎች ቢኖሩም መገለሉን አስበውና ደስ ስለማይለኝ ወደክፍሌ እገባለሁ›› የሚለው የተመስገን መልስ ነበር፡፡
ተመስገን አቤልን ከርቀት አይቶት ‹‹ያ አቤል ነው አይደለ?›› አለኝ፡፡ ዞሬ አየሁት፣ አቤል ውብሸትን ጠይቆት ከርቀት ወደመውጪያው በር እየሄደ ነበር፡፡ ‹‹ግን እንዴት አስገቧችሁ?፤ ይመልሱ ነበር እኮ›› አለኝ፡፡ አቤልም ተመስገንን ተመስገንም አቤልን ማግኘት ፈልገው ነበር፡፡ ብዙም ሳይቆይ አቤል አንዱን ፖሊስ እንደምንም አናግሮ ተመስገንን ሊጠይቅ መጣ፡፡ ተቃቅፈው ተሳሳሙ፡፡ የሶስትዮሽ ጨዋታችንን ለግማሽ ሰዓት ያህል አደራነው፡፡ ተመስገን ከታሰረ በኋላ የግራ ጆሮው እንደማይሰማለት እና ወገቡም ሕክምና በማጣቱ አሁንም ድረስ እንደሚያመው አልሸሸገንም – ‹‹እዚህ ያለው መድኃኒት ፓናዶል ብቻ ነው›› በማለት፡፡ አያይዞም ‹‹ሰው መጥቶ ሲጠይቅህ ደስ ይላል፤ ጥሩ እንቅልፍ ትተኛለህ፤ግን የመንገዱን ርቀት ሳስበው ሰው ባይመጣ እላለሁ›› አለን በድጋሚ፡፡
የእስረኛ መጠየቂያ ጊዜ መጠናቀቁን ፖሊሶች ነገሩንና ተቃቅፎ መለያት ግድ ሆነ፡፡ ‹‹አይዞህ የምትባል አይደለህምና ሰላም ሁን›› አልኩት፡፡ ‹‹ምን መልዕክት አለህ?›› ስል የመጨረሻ ጥያቄዬን ሰነዘርኩለት፡፡ ተመስገንም ‹‹ታገሉ!›› ሲል መለሰና በመጣበት መንገድ ቻው ብሎን እርምጃውን ቀጠለ፡፡ ሲሄድ አራት እና አምስት ጊዜ ያህል ዞረን አየነው፡፡ ስለገኘነው ደስ ቢለንም በሳሮች መካከል ባለው መንገድ ወደታሰረበት ክፍል ሲያመራ ማየት ዳግመኛ የመረበሽ እና የማዘን ስሜት በውስጤ ፈጥሮብኝ ነበር፡፡ ስሜቱ በጣም የሚገባው በቦታው ላይ ሲገኙ ነው!
ተመስገን፣ ያመነበትን ሀሳብ በድፍረት ስለጻፈ ነበር በኢ-ፍትሃዊነት ሶስት ዓመት እስር የተፈረደበት፡፡ ሰው መታሰሩ ሳያንስ፤ ከቤተሰቡ፣ ከወዳጁ፣ ከዘመዱ፣ ከጓዳኞቹ እርቆ እንዲታሰር ማድረግ ሌላ ቅጣት ነው! ሰው መታሰሩ ሳያንስ፣ ህክምና መከልከሉ፣ በሌሎች እስረኞች እንዲገለል መደረጉ፣ መጽሐፍ ማንበብ እና የግል ማስታወሻዎቹን እንዳይጽፍ መከልከሉ ይሄም ሌላ ቅጣት ነው! ሰው ግን በስንቱ ይቀጣል?! እንዲህም ሆኖ፣ ትናንት የምናውቀው ጋዜጠኛ ተመስገን፣ አሁንም ድረስ ያ ያመነበትን የመናገር ድፍረቱ፣ መንፈሳዊ ብርታትና ጥንካሬው አብሮት አለ!!! አካል ቢታሰር ህሊና መቼም አይታሰር!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

Wednesday, August 12, 2015

አለቃዎ ሳይሆን ቅን ህሊናዎ የሚያዝዎትን በመፈፀም መልካም ዜጋ ይሁኑ!

August 12, 2015
def-thumbመልካም ዜጋ ማለት ምን ማለት ነው?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ በርካታ መጻሕፍት መፃፍ ይቻላል፤ መሠረተ ሀሳቡን ግን በጥቂት ዓረፍተ ነገሮች ማቅረብ ይቻላል።
መልካም ዜጋ ኢፍትሃዊ ተግባር ሲፈፀም “እኔ ምናገባኝ?” አይልም። መልካም ዜጋ “ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ”፤ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶም አይብቀል”፤ “እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም” እና በርካታ መሰል ምሳሌዎችን አይሰማም። መልካም ዜጋ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ቢሆን ከነፃና ቅን ህሊናው ጋር ታርቆ ይኖራል።
የህወሓት አገዛዝ፣ መልካም ዜጋ ማለት የመንግሥት ሥልጣን የያዘን ማንኛውም አካል ማክበርና በታማኝነት ማገልገል ተደርጎ እንዲተረጎምለት ይሻል። ፍትህ የሚያዛባ መንግሥትን መቃወም የመልካም ዜጋ አቢይ ተግባር መሆኑ የዘመናችን ወጣት እንዳይገነዘብ ያደርጋል። በተለይ ባለሙያዎች የሚያገለግሉትን አገዛዝ ባህርይ እግምት ውስጥ ሳያስገቡ የተቀጠሩበትን ሥርዓት በታማኝነት ማገልገል የዜግነት ግዴታቸው አድርገው እንዲወስዱት ይወተውታል።
ኦስካር ግሮኒንግ ( Oskar Groening)የዘጠና አራት ዓመት ሽማግሌ ጀርመናዊ ነው። በጀርመን የሂትለር አገዛዝ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንፁሃን የተፈጁበት አሽዊትስ ካምፕ ውስጥ የሂሳብና ጽህፈት ሠራተኛ ነበር። ኦስካር ግሮኒንግ አንድም ሰው አልገደለም፤ አንድም ሰው አልገረፈም። እሱ ሂሳብ ነው የሠራው። ሆኖም በደል ሲፈፀም አይቶ “ምናገባኝ” ብሎ አልፏልና ከብዙ ዓመታት በኋላ ተከሶ በቅርቡ የ4 ዓመታት እስር ተፈርዶበት በሁለት እግሮቹ መቆም በማይችልበት በ 94 ዓመቱ በእርጅናውና በመጦሪያው ዘመን ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ፊት ተዋርዶ እስር ቤት ወርዷል።
በአንፃሩ ኦስካር ሽንድለር (Oskar Schindler) በጀርመን ናዚ ወቅት ሂትለር ይመራው የነበረው የናዚ ፓርቲ አባልና ሰላይ ነበር። ሆኖም ግን የሥርዓቱን ኢሰብዓዊነት ሲረዳ እዚያው የናዚ ፓርቲ ውስጥ ሆኖ አለቆቹ ያዘዙትን ሳይሆን ቅን ህሊናው ያዘዘውን በምስጢር መሥራት ጀመረ፤ በዚህም የ 1200 ሰዎችን ሕይወት ታደገ። ከጦርነቱ በኋላ ኦስካር ተከብሮ የኖረ በርካታ የክብር ስሞችና ሽልማቶች የተሰጠው በመልካም አርዓያነቱ የሚጠቀስ ሰው ሆነ።
በአገራችንም በአምስት ዓመታቱ የፋሽስት ወረራ ወቅት ስመ ጥር የውስጥ አርበኞች ነበሩ። ከነፃነት በኋላ ባንዶች እንኳን በውስጥ አርበኝነት ለመጠራት ያደርጉት የነበረውን እሽቅድድም ልብ በሉ።
በህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴግ፣ ደህዴግ እንዲሁም አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ ያላችሁ ወገኞች ኦስካር ግሮኒንግን ወይንስ ኦስካር ሽንድለርን መምሰል ትፈልጋላችሁ? በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ነገ የምትዋረዱበትን ሥራ መሥራት ነው የሚበጃችሁ ወይስ ዛሬ ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ እየኖራችሁ ነገ ደግሞ ልጆቻችሁና የልጅ ልጆቻችሁ የሚኮሩበትን ተግባር መፈፀም ትፈልጋላችሁ? በአገዛዙ የስለላ ድርጅቶች ውስጥ ያላችሁ ወገኖች ስማችሁን በመልካም ማስጠራት አትሹምን?
ልቦና ያላችሁ ወገኖቻችን ሆይ! መልካም ዜግነት ሎሌነት አይደለም። መልካም ዜግነት ለቅን ህሊና ታማኝ መሆን ነው። መልካም ዜግነት ሲመች በገሀድ፤ ሳይመች በምስጢር ኢፍትሃዊነትን መዋጋት ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በማናቸውም መንገድ በአገዛዙ የፓለቲካ፣ የጦርና የፓሊስ ተቋማት፤ በስለላም ይሁን በሌላ የሲቪል ሙያ የተሰማራችሁ ወገኖቻችን የታዘዛችሁትን ሳይሆን ቅን ህሊናችሁ የሚጠይቃችሁን በመሥራት ኢፍትሃዊ፣ ፋሽስታዊና ዘረኛ የሆነውን የህወሓት አገዛዝን እንድታዳክሙ ጥሪ ያቀርብላችኋል። በአገዛዙ ውስጥ ሆናችሁ እያለም የምትሠሩት ለሀገርና ለትውልድ የሚጠቅም በርካታ ሥራ አለ። የአገዛዙን ምስጢራዊ ሰነዶች ለአርበኞች ግንቦት 7 እንዲደርስ ማድረግ፤ አሊያም በማኅበራዊ ሚዲያዎች (ለምሳሌ ፌስ ቡክና ቱተር) ማሰራጨት ትልቅ ዋጋ ያለ ሥራ ነው። የህወሓት ፀረ-አገር እና ፀረ-ሕዝብ ፕሮጀክቶችን ማሰናከል ሌላ ትልቅ ሥራ ነው። በነፃነት ታጋዮች ላይ የሚደረጉ ዱለታዎችን ማክሸፍ ሕይወት አድን ሥራ ነው። ድርጅቶቹ ውስጥ ሆኖ ድርጅቶቹን ማዳከም የመልካም ዜግነት ግዴታ መወጣት ነው።
በሥርዓቱ ውስጥ ሆነው ኢፍትሃዊነትን ለማጋለጥ እና ሥርዓቱን ለማዳከም ለሚጥሩ ወገኞች አርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ ክብር አለው፤ ደህንነታቸው እንዲጠበቅም የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል። ፀረ ኢትዮጵያ እና ፀረ ሰው የሆነውን የህወሓትን ሥርዓት ለመጣል እና በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲ፣ እኩልነትና የሀገር አንድነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከሥርዓቱ ውስጥም ውጭም የሚደረገውን ትግል እናፋፍም።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Sunday, August 9, 2015

በባህር ዳር ቀበሌ 11 ወጣቶችና በፖሊሶች መካከል ግጭት ተፈጠረ * አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል አለመተማመኑ ስር ሰዷል

August 9,2015
Photo File
Photo File
አርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ እንደዘገበው የባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 አባይ ማዶ ወጣቶች አንድ አካባቢ ላይ ተሰባስበው በመጫወት ላይ እያሉ ፖሊሶች ድንገት መጥተው “ለምን አንድ ላይ ተሰብስባችሁ ቆማችሁ?” በማለት አምባጓሮ በመፍጠራቸው ነበር ግጭቱ የተነሳው፡፡

ፖሊሶቹ ወጣቶችን ከቆሙበት በኃይል አባረው ወደየቤታቸው ለማስገባት ሲሞክሩ ወጣቶቹ በፖሊስ ላይ የአጸፋ እርምጃ በመውሰዳቸው አንድ ፖሊስ ለከፋ ጉዳት እንደተዳረገ ታውቋል፡፡ የህወሓት አገዛዝ ለስልጣኑ የሚያሰጋውን የህብረተሰብ ክፍል እየመረጠ ትጥቅ ማስፈታቱን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አምባገነናዊ ስርአት የግብአተ መሬት ጊዜውን በጥቂቱም ቢሆን ያራዝምልኛል ብሎ ከነደፋቸው እቅዶች መካከል አንዱ የሆነውን ህዝቡን ትጥቅ የማስፈታት ተግባር በታች አርማጭሆ ገበሬዎች ላይ በተለየ ሁኔታ በግፍ የሚያስታጥቀው የህብረተሰብ ክፍል ያለው ዘረኛው የህወሓት ቡድን በአማርኛ ተናጋሪው ገበሬ ላይ አሁን እየፈፀመ የሚገኘው የትጥቅ ገፈፋ ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ሲያደርገው የቆየው መሆኑ ይታወቃል፡፡
አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል ውስጥ ተፈጥሮ የቆየው አለመተማመን ስር ሰዶ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ታወቀ፡፡

ለሰላም ማስከበር ተልኮ ወደ ደቡብ ሱዳን ሊሄዱ የተመለመሉት የአየር ሀይል አባላት የደቡብ ሱዳን ጉዞ ተሰርዞ ወደ ሱማሊያ እንደሚሄዱ ስለተነገራቸውና በግምገማ በመወጠራቸው ምክንያት በርካታ አብራሪዎች፣ ቴክኒሻኖች እና ሌሎች የተለያዩ ክፍሎች ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በመሆኑም በአየር ሀይል ውስጥ አለመተማመኑ ገደቡን አልፎ አብራሪዎች ለልምምድ በሚያበሩት አውሮፕላን ውስጥ የህወሓት አባላት ከጎን እንዲቀመጡ እየተደረገነው፡፡ በተጨማሪም አብራሪዎች ነዳጅ በሚሞሉበት ጊዜ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ከዘ- ሐበሻ የተወሰደ

Woyane and the Million dollar hacking scheme

August 8, 2015
by Yilma Bekele
You can take your family and friends on a Caribbean cruise. May be buy a one way ticket to Las Vegas and hope to turn it into four million. Who needs a return ticket when you are going back to wherever you came from by private plane? There is one little thing wrong with this scenario. The million Dollar is not your money. You are entrusted by the people to spend it wisely. Can we start again?
One Million US is about twenty Million Ethiopian Bir. I am sure that kind of money can build a library or two. You can purchase a sturdy pump to use both for irrigation or bring water to the village. Imagine how many teachers can be trained with that kind of dough? The list is endless for a poor country like Ethiopia. At the moment the proud nations exists on handout from foreigners. The budget is balanced by heavy subsidy from European Union and generosity of few rich countries. Our country is on Welfare.
The rogue and amateur Ethiopian government hackers attempts
So think hard before you spend that hard earned money collected from the poor citizen. How would you spend one million US if you are the Ethiopian government? Remember that you are aware of the sad state of education, the lack of potable water, the dismal state of the health care, the shortage of food among other problems – how would you allocate that twenty Million Bir?
Yes it is a little confusing on one hand to say the economy is growing double digits and on the other hand stretch your hand out since you cannot pay your bills without the kindness of others. So the Diaspora all over the world that sends money to family, the Diaspora that build condominiums on illegally obtained land and the foreign sponsors are the lifeblood of Woyane. Of course they pooh pooh the Diaspora contribution and hide the foreign alms.
How to spend the million plus US dollars is not a theoretical question. The dictatorship under the late dead PM Banda Meles Zenawi was faced with such issue. Well to tell you the truth by the mere fact that they control the purse they are forced to make a choice on how to spend the money the collected through taxing the citizen, selling Coffee and cereal and other revenues at their disposal. A normal government will submit the budgeting and the Parliament discusses the proposal invite opinions from the citizens and approves or disapproves based on the needs of the constituents that elected them and the welfare of the country as a whole.
It does not work like that in ‘democratic’ Ethiopia. The parliament is a bunch of illiterate and weak individuals recruited and appointed by the TPLF Party. The voting part is for foreign consumption as evidenced by the testimony given by President Obama. The TPLF Party based on the Tigrai core group but purporting to be representing all of Tigrai controls the Parliament (Legislative), Executive (Co-Prime Minister, Foreign Minister, Defense Minister, Federal Affairs Minister, State Security, National bank, etc) and the Judiciary. No one ethnic group has controlled Ethiopia like this before!
So it looks like Meles Zenawi and Debretsion Gebremichael decided to spend our money by hiring a British (Gamma Group) and an Italian (Hacking Team) security companies to hack into the computers, mobile phones and Skype accounts of Ethiopians. How did we find that out. Surprise, surprise the Italian company company ‘hacking Team’ itself was hacked! More than 300GB of documents was made public and our Ethiopia was in the midst of this. We might be poor, we might be technologically backward but TPLF was willing to spend a million dollars to purchase this offensive technology to spy and get the upper hand. The hacking was announced via Hacking Team’s own compromised Twitter account, what a sweet revenge!
So what did Meles and Debretsion use this ‘offensive technology’? They were caught red handed by researchers at the Citizen Lab—a digital watchdog group at the University of Toronto’s Munk School of Global Affairs.
The first hacking attempt against ESAT was targeting the Amsterdam ESAT studio. An individual using the name Yalfalkenu Meches sent an article but when they tried to open the attachment they noticed it was prepared in a different format. Citizens Lab was able to show using Skype logs from the targeted computer. Here is a brief illustration:
Ethiopian government hacking attempts
The alert ESAT manage (may the Gods bless him/her) did not open the file and confronted the individual. Here again is the exchange from Skype.
Ethiopian government hacking attempts
The Woyane bastard did not give up but tried a new trick.
Ethiopian government hacking attempts
That was formated to look like a word document but it was not. According to Citizens Lab ‘A user who opened the file saw a blank Word document, which quickly closed itself. The document exploited a bug in Microsoft Windows (CVE-2012-015844) to run a program that downloaded and executed a file’
If you don’t succeed the second time try again seems to be the way the Ethiopian Information Network Security Agency (INSA) Debretsion’s outfit operates. Thus their third attempt was aimed at ESAT’s studio In Virginia USA.
Ethiopian government hacking attempts
ESAT and Citizens Lab were already aware of Woyanes workings and this time they confronted Debretsion’s lackey and here is the conversation.
Ethiopian government hacking attempts
Ethiopian government hacking attempts
Citizens Lab of course made their investigation official. When asked by reporters an Ethiopian Embassy spokesperson Tesfaye Welde claimed ‘Ethiopia did not use and has no reason to use any spyware or other products provided by Hacking team or any other vendor inside or outside Ethiopia.’ Today thanks to smart hackers that hacked this enemy of Ethiopia Company we have the original thank you email from dictator Meles and a copy of the million dollars he paid so he could buy more time and abuse our people and nation. That is one million dollars that could have gone to schools, libraries and clinics.
The second time they were caught when they tried to hack ESAT’s Managing Director Ato Neamin Zelek’s computer using word document by hijacking an email address they have obtained previously.
Ethiopian government hacking attemptsAto Neamin promptly forwarded the suspicious email to Citizens Lab. Lo and behold it was no other than Debretsion of of INSA knocking again. It seems like the morons have used the the same command as before and the servers are shown to be registered to Ethio Telecom. The hacking Team’s Operations Manager was heard to have said ‘(Citizens Lab) found the source of the attack because these geniuses used the same email address they had used in the previous attack to send the doc with the exploit.’ so much for Woyane smartness,
Today the TPLF minority regime is being forced to answer to charges of illegal spying on foreign soil. In the US it is considered a Federal crime and the court has allowed the case to continue. There will be many others that will come out pretty soon. Citizens Lab is looking at more computers and doing a deep investigation suitable for the courts.
We Ethiopians have long ago understood the cheap, criminal and shameful character of Woyane. We are not surprised by anything coming out of Arat Kilo. To the outsider it is surprising how a small poor country would find itself using twenty first century technology to monitor its own people. They are always surprised how brazen and reckless Woyane’s are. Again to an Ethiopian there is no surprise here. Woyane kills in broad daylight and demands the victim’s family pay for the bullet. Woyane is so used to such outrageous conduct inside the country it is only natural they would try the same abroad too.
They have hacked the computers of a vast majority of those they suspect are working to dismantle their criminal enterprise. They are are so paranoid they think all of us are the enemy and they will spend millions so they could uncover ‘plots’ find ‘compromising’ information for blackmail or coerce individuals to work for their criminal enterprise. It is a temporary solution for a deep seated problem.
My dear Ethiopian family and friends as you can see what has been said by many about the destructive and criminal nature of the people in power has not been a figment of someone’s imagination. I wrote this so you can see clearly what the independent experts have found about the regime and its practice.
It has been said plenty of times that “woyane cannot be reformed.” It has been carrying out this criminal activity since its inception. It is too late to talk of reform. Removal by any means without prejudice is the only option left to the peace loving people of Ethiopia. The gallant effort that is being waged by our patriots is the only medicine to get rid of this virus.
The current smart way of fighting TPLF led by Patriotic Ginbot7 is the last chance we have as a country before they turn our homeland into another Iraq, Libya, Syria or Yemen. That is what is awaiting our country if we do not come together to get rid of the common enemy. Every Ethiopian is a hidden patriot ready to strike at Woyane when the time arrives. Be a patriot and love your mother.
I have included links that would make a good reading before you go to bed.

Saturday, August 8, 2015

ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል

August 8,2015
አሜሪካ ሃሳቡ ቀርቦላታል ተብሏል
four front map

ኢህአዴግ በአራት አቅጣጫዎች የጦር ጥቃት ለመሰንዘር ማሰቡ ተሰማ፡፡ ይኸው ሃሳብ ለአሜሪካ ቀርቦላታል፡፡
በቅርቡ የተጠናከረ እንቅስቃሴ የጀመረው የአርበኞች ግንቦት ፯ ኃይል በተደጋጋሚ በሚያወጣው መረጃ በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ማድረሱን በይፋ ቢገልጽም ኢህአዴግ ጥቃቱን በቀጥታ ለማስተባበል እስካሁን አልወደደም። ይሁን እንጂ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ “ህዝብ አስፈቅደን” ሲሉ ኤርትራን እንደሚወጉ ይፋ አድርገዋል። አብዛኞች እንደሚስማሙበት ዛቻው ግጭት ስለመኖሩ የሚያረጋግጥ ነው። በሌላው አንጻር ደግሞ ይህንን የሃይለማርያም ንግግር የኤርትራው ሹም በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የተለመደ የህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያና ዛቻ በማለት አጣጥለውታል፡፡
የግጭቱን ደረጃና በኢህአዴግ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ኢሳት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን መውቀሰና ማስፈራራት የጀመረው ኢህአዴግ፣ ቀጣናው ሊተራመስ እንደሚችል ስጋቱን ገልጾ ኤርትራን ለመደብደብ የሚያስችለውን ፈቃድ ስለማግኘቱ ጎልጉል መረጃ ደርሶታል። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) አራተኛዋ ሹም ዊንዲ ሼርማን ግንቦት ፯ን በስም በመጥቀስ በተቃወሙ ማግስት የባለሥልጣኗን የድጋፍ ቃል አስመልክቶ ቴድሮስ አድሃኖም በኢህአዴግ በኩል ያለውን ውለታ ሲናገሩ “ለምንከፍለው ዋጋ መጠን ተመጣጣኝ ክፍያ ነው” ሲሉ ውስጡ በርካታ የፖለቲካ “ጥሬ ሃብት” የሞላበት አስተያየት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ሰጥተው ነበር።
የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ፕሬዚዳንት ኦባማ አዲስ አበባ በነበሩበት ወቅት የህወሃት ሰዎች ይህንኑ ጉዳይ በዋናነት አንስተው ነበር። ኢህአዴግ በሶማሊያ እያበረከተ ላለው ተግባር መሰናክል ተደርጎ የቀረበው የኤርትራ ተቃዋሚዎችን የመርዳት ጉዳይ እልባት እንዲበጅለት አሜሪካ ድጋፍ እንድትሰጥ የጠየቀው ኢህአዴግ፣ አሜሪካ ያሉ የከፍተኛ ተቃዋሚ አመራሮች ገደብ እንዲጣልባቸው ተማጽኗል። አሜሪካ ኢህአዴግ “አሸባሪ” ብሎ የሚፈርጃቸውን በሙሉ በሽብርተኛነት በመፈረጅ የመን የተጫወተችውን አይነት ሚና እንድትደግም ተጠይቃለች። ጥያቄው የቅዠትም ሆነ የምር፣ የግንቦት ፯ አመራሮች ነቅለው አስመራ መግባታቸው ጥያቄውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል የሚሉ አሉ
አሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄዎች ስለመቀበሏ ያልጠቀሱት የመረጃው ባለቤቶች፣ ኤርትራ ውስጥ መተራመስ ሳይፈጠርና ክልሉና ቀጣናው ሳይናጋ ጥንቃቄ የተሞላበት ርምጃ ቢወሰድ አሜሪካ ተቃውሞ እንደማይኖራት ማረጋገጫ መስጠቷን አመልክተዋል። ይህ አቋም ኦባማ አዲስ አበባ ከመሄዳቸው በፊት በተለያዩ ደረጃዎች ተመክሮበት ከስምምነት የተደረሰበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር አቶ ስብሃት ነጋ “ከኤርትራ ጋር የሚካሄድ ውጊያ ጥንቃቄ ይጠይቃል” ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።
በዚሁ መነሻ ኢህአዴግ በጎንደር፣ በሱዳን ድንበር፣ በአፋርና በትግራይ የተለያዩ ግንባሮች ድንገተኛ ማጥቃት ለመሰንዘር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። ወቅቱ የዝናብ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ ለዚሁ ጥቃት ሠራዊቱ የሚወጋው “ተቃዋሚ የሆኑ የራሱን ወገኖች ሳይሆን ሻእቢያን ነው” በሚል የማነቃቂያ ስራ እየተሰራ እንደሆነ የመረጃው ሰዎች ተናግረዋል። በድጋሚ የመሥራቱ ጉዳይ ገና ባይታወቅም ይህ አካሄድ በባድመ እንደተደረገው የወኔ ማነቃቂያ እና የውጊያ ሞራል ማነሳሻ ለማድረግ ታስቦ በጥናት የተደረገ ለመሆኑ የመረጃው አቀባዮች ያስረዳሉ፡፡ አያይዘውም “ጦርነቱ ኢህአዴግ ካሰበው ውጪ ባንድ በኩል ከተሰበረ በጦሩ ውስጥ የሚገኙ የሌሎች ኅብረተሰብ ክፍል አባላት የሆኑ ወታደሮች ሊከዱና የተቃዋሚ ኃይሎችን ሊቀላቀሉ ይችላሉ” የሚል ስጋት ስለመኖሩ ሪፖርት መቅረቡን ይጠቅሳሉ።
በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያለው ሚዛን ያልጠበቀ የኃላፊነት ደረጃና የህወሃት አባላት ያላቸው የተጋነነ የበላይነት በመሃል አገር ከሚፈጸመው ረገጣ ጋር ተዳምሮ የተከማቸው ቅሬታ ሊፈነዳ ይችላል የሚል ጥርጣሬ እንዳለም እነዚሁ ክፍሎች ያስረዳሉ።
ኢህአዴግ የትጥቅ ትግል አውጀው ኤርትራ ከመሸጉና መሣሪያ አንግበው ትግል እያደረጉ መሆናቸውን ይፋ ካደረጉ ግንባሮች ሁሉ በድርጅታዊ አቅሙ ከፍተኛ የሚባለውን (ደሚት/ትህዴን) የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን እስካሁን በሽብርተኛነት አለመፈረጁ ይታወቃል።
ከ ጎልጉል ድህረገጽ የተወሰደ