Wednesday, April 30, 2014

በ10 ብር ከገበሬው ተነጥቆ በ19 ሺህ ብር እንደሚሸጥ አንድነት አጋለጠ (በኦሮሞ ተማሪዎች ዙሪያ የአንድነትን መግለጫ ይዘናል)

April 30/2014

ኢሕአዴግ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች በንጹሃን ኢትዮጵያዉያን ላይ ፣ በተለይም ሰሞኑን በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እያደረሰ ያለዉ ሕግ ወጥና ኢሰብአዊ ጥቃት አወገዘ። ዜጎችን የሚያምኑበትን የመናገር ሙሉ መብት እንዳላቸው ያስቀመጠው የአንድነት መግለጫ፣ ተቃዉሞ የሚያስሙ ወገኖች ሊደመጡ እንጂ ሊደበደቡና ሊታሰሩ እንደማይገባም ይገልጻል።

አንድነት፣ በቅርቡ የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መርህ፣ አዲስ አበባን ጨመሮ በበርካታ የአገሪቷ ክፍሎች እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል። ኢሕአዴግ መሬትን እንደ መጨቆኛና መበዝበዣ መሳሪያ አድርጎ እየተጠቀመበት እንዳለ የሚገልጸው የአንድነት መግለጭ፣ ከድሃው ገበሬ አሥር ብቻ በመስጠት የነጠቀዉን መሬት በ 17 ሺህ ብር በጨረታ እንደሚሽጥ እና ልማት ሳይሆን ገበሬዉን በማፈናቀልና በማደህየት የሚደረግ ዘረፋ እያደረገ እንዳለ ለማሳየት ሞክሯል።
ከጥቂት አመታት በፊት በመቀሌ ፣ በተለይም ከኤርትራ የመጡ ስደተኞች ከሚኖርባቸው ቤቶች፣ የሚኖሩበት አካባቢ ለልማት ያስፈልጋል ተብሎ በሃይል እንዲፈናቀሉ መደረጉ፣ በጋምቤላ ደግሞ ከመሬት ጋር በተገናኘ በሺሆች የሚቆጠር በአገዛዙ በግፍ መገደላቸዉ ይታወቃል። በቤኔሻንጉል ጉሙዝ፣ በአምቦ አካባቢ ፣ በወለጋ እንዲሁም ሌሎች በርካታ ቦታዎች ፣ ዜጎች «ይሄ አገራችሁ አይደለም» በሚል፣ ከአንድ ብሄረሰብ በመሆናቸው ብቻ የተፈናቀሉበት ሁኔታ እንዳለ በስፋት ተዘግቧል።
የአንድነት ፓርቲ በመገለጫዉ፣ የታሰሩ የኦሮሞ ተማሪዎች በአስቸኳይ ተፈተዉ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ጥይቋል።
በአንዳንድ የኦሮሞ ተማሪዎች አካባቢ «ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ናት፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ናት» የሚሉ፣ በአንዳንድ ዉጭ ባሉ አክራሪዎች የሚሰማ መፈክር በስፋት ሲስተጋማ እንደነበረ፣ ከዚህም የተነሳ ብዙዎች የኦሮሞ ተማሪዎች በሚያነሱት ጥያቄ ላይ ቅሬታ እንዳደረባቸው በመግልጽ እየጻፉ ነው።
በኦሮሚያን እና በአዲስ መካከል ግዛቱ የትና እንዴት መሆን እንዳለበት፣ የአንድነት ፓርቲ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል። እንደዚያም ቢሆን ግን ፣ ፓርቲዉ አሁን ያለው በቋንቋ ላይ የተመሰረተዉ ፌዴራል አወቃቀር፣ ያለ ሕዝብ ፍቃድ በጉልበት በሕዝቡ ላይ የተጫነ በመሆኑ፣ እንደገና ቋንቋን ጨምሮ፣ የሕዝቡን አሰፋፈር፣ ጂዮግራፊን፣ ኢኮኖሚን ፣ የሕዥቡን ፍላጎት እንደኢሁም ሌሎች ነጥቦች ባካተተ መልኩ እንደገና መዋቀር አለበት እንደሚያምን በፖለቲካ ፕሮግራሙ በግልጽ አስቀምጧል። ለፓርቲዉ ቅርበት ያላቸው እንደሚናገሩት፣ አሁን በኦሮሚያና በአዲስ መካከል የተፈጠረው ዉዝግብ አሁን ያለው ፌደራል አወቃቀር ያመጣው ጣጣ እንደሆነ በማስረዳት፣ የፌደራል አወቃቀሩ እንደገና ፣ ሁሉን አቀፍና ዴምክራሲያዊ በሆነ መንገድ ከተዋቀረ፣ ብዙ ችግሮች እልባት እንደሚያገኙ ይናገራሉ።

ሰማያዊ ፓርቲ የአርበኞችን ቀን ሊያከብር ነው – በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቅጣት ተጣለባቸው

April 30/2014

ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዝያ 27/2006 ዓ.ም የአርበኞችን ቀን በጽ/ቤቱ ታዋቂ የታሪክ ተመራማሪዎችንና ሌሎች ምሁራንን ጋብዞ እንደሚያወያይ ምክትል የህዝብ ግንኙነቱ አቶ እምላዕሉ ፍስሃ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ምክትል የህዝብ ግንኙነቱ እንዳስታወቁት ስነ ስርዓቱ ሰኞ ሚያዝያ 27 ከጠዋቱ 3 ሰዓት የሚጀምር ሲሆን ማንኛውምኢትዮጵያዊ በፕሮግራሙ መሳተፍ ይችላል ብለዋል፡፡ ‹‹የስነ ጽሁፍ ተሰጥዖ ያላቸውና በበዓሉ ስራቸውን ማቅረብ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንንም እንዲሳተፉ እንፈልጋለን ያሉት ኃላፊው›› ፕሮግራሙን ወጣቶች ስለ አባቶቻቸው ታሪክ እንዲያውቁ ከማድረግም ባሻገር ስራቸውን በማስታወስ ታካቸውን ለመዘከር እንደሚፈልጉ አክለው ገልጸዋል፡፡

 የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ህግን ለማስከበር በመጣራቸው ተጨማሪ ቅጣት ተጣለባቸው 

ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በቅስቀሳ ላይ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በ1000 (አንድ ሺህ ብር) ዋስ እንዲወጡ መወሰኑን ተከትሎ ‹‹እኛ ነጻ ነን፡፡ ገንዘብ አስይዘን እንወጣም፡፡ ስራችን ህግ ማስከበር እስከሆነ ድረስ እየታሰርንም ቢሆን ህግ
እናስከብራለን፡፡ በመሆኑም ነጻ እስካልተለቀቅን ድረስ እሰሩን፡፡›› በማለታቸው ተጨማሪ ክሶችና ቅጣቶች እየተጣለባቸው ነው፡፡ በትናትናው ዕለት ሜሮን አለማየሁና ትግስት ወንዲፍራው ‹‹ግቢ በመረበሸ›› ተጨማሪ ክስ መከሰሳቸው ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅት በቤላፖሊስ ጣቢያ የሚገኙ 14 ያህል የሰማያዊ ፓር አመራሮችና አባላትም ተመሳሳይ ክስየተመሰረተባቸው ሲሆን ባለፈው ከፍላችሁ ውጡ ከተባሉት 1000 (አንድ ሺህ ብር) በተጨማ 600 (ስድስት መቶ ብር) ጨምረው ከፍለው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡

እነዚህ አመራሮችና አባላት መጀመሪያ የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ ቢሆንም እስረኛውን በማሳመጽና በመረበሽ
ከመከሰሳቸውም በተጨማሪ ወደ ቤላ ፖሊስ ጣቢያ ተዛውረዋል፡፡ በወቅቱ ድብደባና ማዋከብ እንደደረሰባቸው የሚናገሩት
ታሳሪዎቹ ‹‹ህግን ለማስከበር የምናደርገውን ጥረት እንደ ህገ ወጥነት ተቆጥሮ ተጨማሪ ክስና በደል ቢፈጸምብንም እኛ ህግ
ማስከበራችንን እንቅጥላለን›› ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ በጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትና ዛሬ ስምንት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት
እያንዳንዳቸው 5500 ብር አስይዘው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ ይህንን ውሳኔ በመቃወም ‹‹ነጻ ካልተለቀቅን
አንወጣም!›› ያሉ ሲሆን ከዳኛው የተሰጣቸው መልስ እንዳሳዘናቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ዳኛውና አቃቤ ህጉ
ተመካክለው ነው የገቡት፡፡ በእያንዳንዳችን 5500 ብር እንድንከፍል ሲፈርዱ፤ ‹እኛ ተማሪዎችና የመንግስት ሰራተኞች ነን
ከየትም አምጥተን መክፈል አንችልም!› አልናቸው፡፡ እነሱ ልክ አንድ ሰው እቃ ሲገዛ እንደሚከራከረው ‹በቃ! 2000 ብር
ይሁንላችሁ› አሉን፡፡›› ያሉት ታሳሪዎቹ በህግ ሳይሆን በዘፈቀደ እየተሰራ መሆኑ አሳዝኗቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ‹‹ህገ ወጥ
ቢሆንም በሌላ አካባቢ የታሰሩት የእኛ ጓደኞች 1000 ብር ነው እንዲከፍሉ የተወሰነባቸው፡፡ የእኛውን ለምንድን ነው 5500
ያደረጋችሁት?›› ብለው ሲጠይቁ ዳኛው ‹‹ቅጣቱ ከጣቢያ ጣቢያ ይለያያል፡፡›› የሚል አስገራሚ መልስ እንደሰጧቸው
ገልጸውልናል፡፡

የግሉ ፕሬስ ፈተናዎች የፕሬስ ነፃነትን እየተፈታተኑ ናቸው!

April 30/2014

የፊታችን ቅዳሜ እ.ኤ.አ. ሜይ 3 ቀን 2014 የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን ይዘከራል፡፡ ‹‹የሚዲያ ነፃነት ለተሻለ መፃኢ ጊዜ-የድኅረ 2015 የልማት አጀንዳን ለመቅረፅ›› በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም የሚዘከረው ይህ ቀን፣ የፕሬስ ነፃነት በአሁኑ ጊዜ በዓለም ዙሪያ ምን ዓይነት ገጽታ እንዳለው ያሳየናል፡፡ እኛም እግረ መንገዳችንን አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ አገሮች የሚታዩ የግሉ ፕሬስ ፈተናዎችን እንቃኝበታለን፡፡

 የፕሬስ ነፃነት ቀን በሚታሰብበት ዋዜማ ላይ ሆነን ሰሞኑን በአገራችን ውስጥ በርካታ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችና ጦማሪያን (Bloggers) በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ፍርድ ቤት ቀርበውም የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡ በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ ለጊዜው በዝርዝር የምናነሳው ጉዳይ ባይኖርም፣ የፕሬስ ነፃነትን ከሚጋፉ ወይም ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን ከሚገዳደሩ ጉዳዮች መካከል አንደኛው የጋዜጠኞች እስራት እንደሆነ ግን የምናልፈው ጉዳይ አይሆንም፡፡ በአንድ ጊዜ በርካታ ጋዜጠኞች ታሰሩ ሲባል ድባቡ ደስ አይልምና፡፡ እስቲ በአገራችን የፕሬስ ነፃነትን የሚጋፉ ዋነኛ የግሉ ፕሬስ ችግሮችን እንቃኝ፡፡

የሙያ ክህሎት ችግር  

እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ የፕሬስ ጉዞ አንድ ክፍለ ዘመን ያህል አስቆጥሯል፡፡ ይሁንና ባለመታደል በአገራችን አሁን ያለው የግል ፕሬስ ሥራ ላይ ከዋለ ገና የ22 ዓመታት ዕድሜ ነው ያስቆጠረው፡፡ እነዚህ ሁለት አሥርት ዓመታት የሚያሳዩን የፕሬስ ሙያ ገና በጨቅላ ዕድሜ ላይ መሆኑን ነው፡፡ ይህ ለጋነትና የልምድ አናሳነት በግሉ ፕሬስ የዕለት ተዕለት ሥራ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ችግር እየጋረጠ ነው፡፡ የግሉ ፕሬስ ከሚፈታተኑት ዋነኛ ችግሮች መካከል ተጠቃሽ የሚባለው የሙያ ክህሎት (Professionalism) የሚባለው ነው፡፡ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አስተምረው የሚያወጡት የሰው ኃይል የገበያውን ፍላጎት የሚመጥን አይደለም፡፡ በዚህም ምክንያት ክህሎት ያላቸውን ባለሙያዎች ማግኘት አዳጋች ሆኗል፡፡

የፕሬስ ተቋማት አቅም ውስንነትና ደካማነት ተባብረው ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን ማፍራት አልተቻለም፡፡ በቂ የሆነ የሙያ ክህሎት ሥልጠና ባለመኖሩ ምክንያት በሚያሳዝን ሁኔታ የሙያ ሥነ ምግባር የለም የማይባልበት ደረጃ ላይ ነው ያለነው፡፡ የሙያ ሥነ ምግባር ባለመኖሩ ምክንያት የግሉ ፕሬስ ከምርመራ ዘገባ ይልቅ በአመዛኙ የግል አስተያየትና ሐተታ ውስጥ ተሰማርቷል፡፡ በተለይ ቁጥራቸው በማይናቅ የፕሬስ ውጤቶች ውስጥ ጋዜጠኝነትና የፖለቲካ አቀንቃኝነት ተደበላልቀው ይታያሉ፡፡ በዚህም ምክንያት በዜና ዘገባና በግል አስተያየት መካከል ያለው ድንበር ባለመታወቁ የሙያውን ሥነ ምግባር ማስጠበቅ አልተቻለም፡፡ ሌላው ቀርቶ በጋዜጠኝነት ስም የሚንቀሳቀሱ ማኅበራት ስያሜውን ከመያዛቸው ውጪ እዚህ ግባ የሚባል ሚና የላቸውም፡፡ ፈተናው ግን እየከበደ ነው፡፡

አንድ ሐኪም የተሰማራበት የሙያ ሥነ ምግባር ከሚጠይቀው ውጪ የእምነት ወይም የፖለቲካ ሰባኪ መሆን እንደሌለበት ሁሉ፣ ጋዜጠኛም የሲቪል ማኅበረሰቡን ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሥራ ተክቶ መሥራት የለበትም፡፡ መሐንዲስ መንገድ፣ ድልድይ ወይም ግድብ ሲገነባ ከሙያ ሥነ ምግባር ወጥቶ አላስፈላጊ ድርጊት ቢፈጽም የሚያደርሰው አደጋ ከፍተኛ እንደመሆኑ መጠን፣ ጋዜጠኛው የሙያ ሥነ ምግባሩን ባለመከተሉና ሙያውን በብቃት ባለመወጣቱ ምክንያት የከፋ አደጋ ይፈጥራል፡፡ ይህም በተለያዩ አገሮች ውስጥ በተፈጸሙ ዘርን ማዕከል ያደረጉ ግጭቶችና ውድመቶች ታይቷል፡፡ ስለዚህ የሙያ ክህሎት ችግር የዘመናችን የግሉ ፕሬስ ፈተና ሆኗል፡፡

የኅብረተሰቡ ግንዛቤ ማነስ

በኅብረተሰባችን ዘንድ ያለው የፕሬስ ሙያ ግንዛቤ አነስተኛ ከመሆኑ አንፃር፣ መረጃን ሙያዊ ሥነ ምግባር ተላብሰው ከሚያቀርቡ ጋዜጦች ይልቅ ለፕሮፓጋንዳና ቅስቀሳ ዓይነት ውጤቶች ትኩረት ሲሰጥ ይታያል፡፡ ጋዜጠኝነት ራሱን የቻለ ሙያ፣ በሥነ ምግባር ደንብ የሚመራና በዚህም ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ አንቱታ የተቸረው ሙያ ነው፡፡ በኅብረተሰባችን ዘንድ ግንዛቤው አነስተኛ በመሆኑ፣ ለሙያ ሥነ ምግባር ጥሰት የራሱን አዎንታዊ ሚና ይጫወታል፡፡ ጋዜጠኛው ሙስናን በተጨባጭ እንዳያጋልጥ፣ የመልካም አስተዳደር ተግዳሮቶችን እንዳይጠቁም፣ ለዲሞክራሲና ለሰብዓዊ መብት መከበር እንቅፋት የሚሆኑ ኃይሎችን ተቋቁሞ ዘገባዎችን እንዳይሠራ፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበር የራሱን አስተዋጽኦ እንዳያደርግ እንቅፋት እየተፈጠረ ነው፡፡ በተቃራኒው ጋዜጠኞች ከሙያ ሥነ ምግባራቸው እያፈነገጡ የፖለቲከኞችን ሚና ሲተኩና የሙያው ሥነ ምግባር አቅጣጫውን ሲስት በኅብረተሰቡ ዘንድ በቀና መታየቱ የግሉን ፕሬስ ሚና ፈተና ውስጥ ከቶታል፡፡ በተለይ ምሁራን ይህንን የተደበላለቀ አካሄድ ከማቃናት ይልቅ ዝም ብለው ማየታቸው ችግሩን አባብሶታል፡፡ 

የፖለቲካ ፓርቲዎች ያልተገባ አካሄድ

ጋዜጠኝነት በገለልተኝነት መርህ የሚከናወን የተከበረ ሙያ መሆኑ የታወቀ ቢሆንም፣ በአገራችን ገዥውን ፓርቲ ጨምሮ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተላላኪ ሲያደርጉት ይታያሉ፡፡ ጋዜጠኝነት ለማኅበረሰቡ መረጃ የመስጠት ሚናው እየተንኳሰሰ የፖለቲካ ጽንፎች ውስጥ እንዲሸጎጥ ይፈለጋል፡፡ ገዥው ፓርቲ በቁጥጥሩ ሥር ያሉ የመንግሥት ሚዲያዎችን በራሱ አምሳያ ቀርፆ እንደፈለገው ሲጠቀምባቸው፣ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የግሉ ፕሬስ የእነሱ አፈ ቀላጤ እንዲሆን ይፈልጋሉ፡፡ ሁለቱም ኃይሎች ጋዜጠኞችን እንደፈለጉ በማሽከርከር የፖለቲካ አቋማቸው ማስፈጸሚያ እንዲሆን በሚያደርጉት ጥረት ሙያውን በአሳዛኝ ሁኔታ እየፈተኑት ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት የግሉ ፕሬስ ነፃነትና ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ በመደረጉ ፈተናው ከብዷል፡፡

የመንግሥት ግዴለሽነት

የቀድሞው የፕሬስ ነፃነት አዋጅ 34/85 ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት ሁለት አሥርት በሥራ ላይ ያለው የግሉ ፕሬስ የመንግሥት ድጋፍ ሊያገኝ ቀርቶ በቀና ዓይን እየታየ አይደለም፡፡ መንግሥትና የግሉ ፕሬስ የሚተያዩት በበጎ ዓይን ባለመሆኑ ምክንያት ግንኙነቱ የሻከረ ነው፡፡ በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት በርካታ የፕሬስ ውጤቶች ከገበያ ወጥተዋል፡፡ ብዙ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞች ተሰደዋል፡፡ በእስር ላይ ያሉም አሉ፡፡ የመንግሥትና የግሉ ፕሬስ ግንኙነት ተበላሽቶ ለዓመታት ቢዘልቅም መንግሥት ግዴለሽነት ነው የሚታይበት፡፡ በግሉ ፕሬስና በመንግሥት መካከል መተማመን የለም፡፡ ይህ ያለመተማመን መንፈስ ሁለቱን ወገኖች እንደ ጠላት እንዲተያዩ አድርጓቸዋል፡፡ ውጤቱንም እያየነው ነው፡፡ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያሉ ሚዲያዎች ከፍተኛ በጀት ተመድቦላቸው ፍትሐዊ ባልሆነ መንገድ የግሉን ፕሬስ ገበያ ውስጥ ይወዳደራሉ፡፡ የግሉ ፕሬስ እንደ ሌሎች ኢንቨስትመንቶች ከቀረጥ ነፃና ማበረታቻ አለማግኘቱ ብቻ ሳይሆን፣ በማተሚያ ቤት የተጋነነ የሕትመት ዋጋ ሲጎሳቆል፣ በሕትመት መጓተት ሲንገላታ፣ ከዚያም አልፎ ተርፎ የሕትመት አገልግሎት ሲከለከል ጠያቂ የለም፡፡ ተጠያቂም የለም፡፡ የግንኙነቱ መበላሸት የግሉን ፕሬስ ፈተና አክፍቶታል፡፡ የነገውን ብሩህ ቀን ለማሰብም ከብዷል፡፡

የግሉ ፕሬስ ባለ ክህሎቶችን እያጣ ነው

የግሉ ፕሬስ ፈተናዎችና ውክቢያዎች ሲባባሱ ወደ ግሉ ፕሬስ መምጣት የሚገባቸው ባለ ክህሎት ወጣቶች እየሸሹ ናቸው፡፡ ሙያውንና የሥነ ምግባር ደንቡን በሚገባ ተረድተው የሚሠሩ ትጉህ ጋዜጠኞች እየተሸማቀቁ ወደ ሌላ የሥራ መስኮች እየተመሙ ናቸው፡፡ ጠንካራ የግል ሚዲያ ለመፍጠር መሠረት ሊሆኑ የሚችሉ እነዚህ ባለ ክህሎቶች በሸሹ ቁጥር የግሉ ፕሬስ የፖለቲካ አቀንቃኞችና ፕሮፓጋንዲስቶች ሰለባ ይሆናል፡፡ ከሁሉም የሚያሳስበው ግን ወጣቱ ትውልድ በዚህ ደስ የማይል ድባብ ምክንያት ሙያውን እየፈለገው ለመሸሽ ተገዷል፡፡ ይህ በራሱ አስከፊ ፈተና ነው፡፡

የግሉ ፕሬስ ኢንቨስትመንት መሳብ አልቻለም

አሁን ባለው ደስ የማይል ድባብና የጥላቻ ስሜት የተከበበው የግሉ ፕሬስ በመስኩ ሊሰማሩ የሚችሉ ኢንቨስተሮች ጭምር እየሸሹት ነው፡፡ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እየታገዘ በሙያ ሥነ ምግባር ተገርቶ ሥራውን የሚያከናውን የግል ፕሬስ በመዋዕለ ንዋይ መደገፍ ሲገባው ከአነስተኛና ጥቃቅን ሥራዎች ባልተሻለ ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ጊዜ የሚዲያ ኢንዱስትሪ ተፈጠረ ብለን መኩራራት ሲገባን ከሱቅ በደረቴ ጋር የሚወዳደር ይመስላል፡፡ የግሉ ፕሬስ በአመርቂ ኢንቨስትመንት እየታገዘ የራሱ ማተሚያ ቤት፣ የቢሮ ሕንፃና የበርካታ ቴክኖሎጂ ውጤቶች ባለቤት መሆን ሲገባው፣ ህልውናው ሳይቀር አስተማማኝ ያልሆነበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ ይህ ራሱ ትልቁ ራስ ምታትና ፈተና ነው፡፡

ምን ይደረግ?

በአገሪቱ ውስጥ ጠንካራ፣ አስተማማኝ፣ በሙያ ሥነ ምግባር የዳበረና የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ በሙሉ አቅሙ መግለጽ የሚችል የግል ፕሬስ መኖር አለበት፡፡ መንግሥት የግሉ ሚዲያ ዲሞክራሲያዊት አገር እንድትመሠረት ሚና እንዳለው ይቀበል፡፡ ዕውቅና ይስጥ፡፡ የግሉን ፕሬስ በሚመለከት አሁን ያለው የመንግሥት ፖሊሲ መለወጥ አለበት፡፡ በመንግሥትና በግሉ ሚዲያ መካከል ጥሩ ስሜት ስለሌለ በግልጽ የሚታየው አድልኦ በአስቸኳይ ይገታ፡፡ በአሁኑ ወቅት ያለው የግሉ ፕሬስ ውጤቶች ዋጋ የሕዝቡን የመግዛት አቅም የሚፈታተን በመሆኑ ከውጭ በሚገባ የወረቀት ምርት  ላይ የተጣለው ታክስ ይነሳ፡፡ ለግሉ ፕሬስ ከቀረጥ ነፃና የታክስ ማበረታቻ ይደረግ፡፡ በግሉ ፕሬስ ላይ የሚደረገው ተፅዕኖና ውክቢያ ይቁም፡፡ ለሕግ የበላይነት ቅድሚያ ይሰጥ፡፡ በሕገ መንግሥቱ የሠፈሩ መብቶች ይከበሩ፡፡ በተለይ የፕሬስ ነፃነትን የሚመለከተው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሁለንተናዊ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎች አንቀጽ 19 (Article 19) ሙሉ በሙሉ የተቀዳው የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 ድንጋጌ ይከበር፡፡ ሕግ ሲከበር የፕሬስ ነፃነት ይከበራል፡፡

በሌላ በኩል ፖለቲከኞችና የፖለቲካ አቀንቃኞች የግሉን ፕሬስ በመቀላቀል ጽንፍ ውስጥ አይክተቱት፡፡ ጋዜጠኝነት ራሱን የቻለ ሙያ ነው፡፡ የራሱ የሥነ ምግባር ደንብና ደረጃ አለው፡፡ ጋዜጠኝነት በገለልተኝነት መርህ ላይ ተመሥርቶ ለማንም ሳያዳላ ማንንም ሳይፈራ የሚከናወን ሙያ በመሆኑ የፖለቲካ መሣሪያ አይሁን፡፡ የፕሬስ ነፃነት ቀንን ስንዘክር በፕሬስ ነፃነት ላይ የተጋረጡ ፈተናዎችን እያሰብን ነው፡፡ ስለሆነም ለፕሬስ ነፃነት የሚታገሉ ወገኖች ሁሉ ይህንን ነፃነት የወረሩ ፈተናዎችን ሊረዱ የግድ ይላል፡፡ የግሉ ፕሬስ ፈተናዎች ከራሱ ጀምሮ ውጭ ድረስ የተንሰራፉ በመሆናቸው ሁላችንንም ሊያሳስበን ይገባል፡፡ ነፃ ፕሬስ፣ ነፃ ሐሳብ፣ ነፃ መንፈስ ስንል የግሉ ፕሬስ የነፃነት አየር ይተንፍስ ማለታችን ነው፡፡ ይህ ነፃነት ደግሞ በኃላፊነት ስሜት ተግባራዊ ይሆን ዘንድ የሚመለከታቸው ሁሉ አፅንኦት ሊሰጡት ይገባል፡፡ የግሉ ፕሬስ ፈተናዎች የፕሬስ ነፃነትን እየተፈታተኑ ናቸው!        

የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

April 30/2014

-በዋስ ይለቀቁ የተባሉ አባላት በነፃ ካልሆነ አንወጣም አሉ

-በሊቀመንበሩ መሪነት ሰላማዊ ሠልፍ አደረጉ

ከአዲስ አበባ አስተዳደር ሰላማዊ ሠልፍ ማድረግ እንደሚችሉ ማረጋገጫ ካገኙ በኋላ ቅስቀሳ ሲጀምሩ፣ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ውለው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ

አመራሮችና (ከሊቀመንበሩ በስተቀር) ቁጥጥራቸው 28 የሚደርሱ አባላት ሚያዝያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡

ሚያዝያ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ውለው የታሰሩት የፓርቲው የፖለቲካ አደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ጌታነህ ባልቻን ጨምሮ 14 አባላት በየካ ክፍለ ከተማ ቤላ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን፣ የብሔራዊ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢውን አቶ የሸዋስ አሰፋን ጨምሮ ስድስት አባላት ደግሞ ቀጨኔ መድኃኔዓለም አካባቢ ላዛሪስት ትምህርት ቤት አጠገብ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን የፓርቲው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንደሻው እምሻው አስታውቀዋል፡፡ ሚያዝያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ስለሺ ፈይሳ፣ የሕዝብ ግንኙነቱ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድና ስምንት አባላት የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ የፓርቲው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

አቶ ስለሺን ጨምሮ የተወሰኑት አባላት አዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀበና ችሎት ሚያዝያ 20 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀርበው በአንድ ሺሕ ብርና መታወቂያ ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ ያዘዘ ቢሆንም፣ የፓርቲው አባላት ግን ከእስር ቤት እንደማይወጡ ተናግረዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ ፖሊስ ያሰረበትን ምክንያት ፍርድ ቤት ሲጠይቀው ለሰላማዊ ሠልፍ እያሉ ሕዝቡን ሲቀሰቅሱና ሲበጠብጡ በመገኘታቸው መሆኑን ገልጾ ቢያስረዳም፣ ፓርቲያቸው ሰላማዊ ሠልፉን አድርጐ ያለምንም ችግር በሰላም በማጠናቀቁ እነሱም በነፃ እንዲሰናበቱ መጠየቃቸው ነው፡፡

ላዛሪስት ትምህርት ቤት አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያና ቤላ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ የፓርቲው አባላት ሚያዝያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው ፖሊስ የሰባት ቀን ተጨማሪ የምርመራ ቀን ጠይቆ ስለተፈቀደለት፣ ሚያዝያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. እንደሚቀርቡ ተጠቁሟል፡፡

የፓርቲውን አመራሮቹና አባላቱን ለእስር የዳረገው የሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ እንደራሴ አካባቢ ከሚገኘው ቢሮ በተወሰኑ ደጋፊዎች ሊቀመንበሩ ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በሚመሩት አባላት ጉዞውን ወደ ባልደራስ አድርጓል፡፡ ‹‹አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ ይኼ ባንዲራ ያንተ አይደለም ወይ? ራበን፣ ጠማን፣ በጨለማ ተዋጥን፣ ኔትወርክ የለም፣ መንገድ የለም…›› የሚሉ መፈክሮችን አንግበውና በድምፅ ማጉያ በማስተጋባት ዓደዋ ድልድይ አደባባይ የደረሰው ሠልፈኛ ለተወሰነ ደቂቃ እንደፈለገው መሄድ አልቻለም፡፡ ከዓደዋ አደባባይ ወደ እንግሊዝ ኤምባሲ በሚያስወጣው መንገድ ሠልፈኛው ሊሄድ ሲሞክር፣ መንገዱ በፖሊሶች የጐንዮሽ ሠልፍ ታጥሮ ‹‹መሄድ ያለባችሁ ወደ መገናኛ በሚወስደው መንገድ ነው፤›› በመባላቸው መግባባት ሳይቻል ቀርቷል፡፡

የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል በጉልበታቸው በርከክ ብለው እጃቸውን ወደ ላይ ሲዘረጉ አንዱ የፓርቲው አባል ሰላማዊ ሠልፉ ከየት ተነስቶ የት እንደሚያበቃ የሚፈቅደውን ወረቀት ለአንድ የፖሊስ ኃላፊ ሲያሳዩአቸው ‹‹መንገዱን ክፈቱት ይሂዱ›› የሚል ትዘዝ በመስጠታቸው በጥሩንባ፣ በፊሽካ፣ በድምፅ ማጉያና በጩኸት የታጀበው ሠልፍ በርከት ባሉ ፖሊሶች እየተመራ ወደ እንግሊዝ ኤምባሲ መውጫ አመራ፡፡ ‹‹We need Electricity, We need Water, We need Transportation, No Network, Free Reeyot, Eskindr, Wubshet, Muslim Brothers, Freedom, Freedom›› የሚሉ መፈክሮችን በእንግሊዝ ኤምባሲ መግቢያ በር ፊት ለፊት በጩኸትና የተለያዩ ድምፆችን ካሰሙ በኋላ፣ ጉዞአቸውን ሰላማዊ ሠልፉ የሚጠናቀቅበት በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ድንበሯ የእናቶችና ሕፃናት ሆስፒታል ጀርባ አድርጓል፡፡

መንግሥት ፖሊሲውን እንዲያሻሽል ወይም ሥልጣኑን እንዲያስረክብ፣ ዜጐች የመናገር፣ የመጻፍና ሐሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበር እንዲያደርግ፣ የሚሉ መፈክሮችንና ሌሎችንም በማንሳት ሰላማዊ ሠልፉ ተጠናቋል፡፡ ታስረዋል ስለተባሉት የፓርቲው አመራሮችና አባላትን በሚመለከት ፖሊስ ማብራሪያ እንዲሰጥ ሪፖርተር ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም ሊሳካ አልቻለም፡፡    

የታሰሩት ጋዜጠኞችና ጦማርያን ጉዳይ እያነጋገረ ነው

April 30/2014

-ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በነፃ እንዲለቀቁ እየጠየቁ ነው

-መንግሥት አደገኛ ወንጀል ፈጽመዋል እያለ ነው

የመብት ተሟጋቾች ነን ከሚሉ የውጭ ድርጅቶች ጋር በገንዘብና በሐሳብ በመስማማት፣ ሕዝብን ለአመፅ ለማነሳሳትና ለማተራመስ በኢንተርኔትና በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ

ቀስቃሽ መጣጥፎችን ለማሰራጨት ሲዘጋጁ ተደርሶባቸዋል በሚል፣ በወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ ጋዜጠኞችና ጦማርያን (Bloggers) ጉዳይ እያነጋገረ ነው፡፡

ሚያዝያ 25 እና 26 ቀን 2006 ዓ.ም. በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ በ48 ሰዓታት ውስጥ በዕለተ እሑድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል (ማዕከላዊ) መርማሪ ፖሊስ፣  ተጠርጣሪዎቹ ከውጭ ድርጅቶች ጋር በገንዘብና በሐሳብ ተስማምተው ሕዝቡን ለአመፅ ለማነሳሳት ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል ከሚል የወንጀል የጥርጣሬ ውጪ ያለው ነገር ስለሌለ፣ ‹‹ወንጀሉ ምድነው?›› የሚል ጥያቄ ከማንሳት ጀምሮ የተለያዩ መላ ምቶችን በማንሳት የተለያዩ አካላት እየተነጋገሩበት ነው፡፡

ሲፒጄ (ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ድርጅት)፣ ‹‹ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ላይ የከፋ ከሚባሉ ዕርምጃዎች አንዱ ነው፤›› በማለት በጋዜጠኞቹና በጦማርያኑ ላይ በኢትዮጵያ መንግሥት የተወሰደውን ዕርምጃ አውግዟል፡፡ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁም ጠይቋል፡፡

አምኒስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ፣ ‹‹ይኼ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ጋዜጠኞችና ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን የማሰር የረዥም ጊዜ ልምድ ነው፤›› በማለት ጋዜጠኞቹንና ጦማርያኑን ማሰር ተገቢ አለመሆኑን አስታውቆ በአስቸኳይ እንዲፈቱም ጠይቋል፡፡

ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች የኢትዮጵያን መንግሥት በማውገዝ የጋዜጠኞቹንና ጦማርያኑን መታሰር የሚያነሱትን ወቀሳና ጥያቄ ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ለውጭ ሚዲያ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹ተጠርጣሪዎቹ በአደገኛ ወንጀል የተጠረጠሩ ናቸው፡፡ ፖሊስ በተጠረጠሩበት ጉዳይ ዙሪያ ምርምራ እያደረገ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ሒዩማን ራይትስ ዎች ሚያዝያ 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ የተባሉት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ጋር ባደረገው የስልክ ውይይት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የታሰሩትን ጋዜጠኞችና ጦማርያን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል፡፡

የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ጆን ኬሪ ተጠርጣሪዎቹን እንዲፈቱ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ግፊት እንዲያደርጉ በስልክ ያስተላለፈውን መልዕክት አስመልክቶ አቶ ጌታቸው በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹መንግሥት የጋዜጠኞችን የመናገር መብት አላፈነም፣ አንዳንዶች ሙያውን ተገን በማድረግ የወንጀል ድርጊት ውስጥ ሲሳተፉ ይገኛሉ፣ ይኼን ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት አይፈቅድም፤›› ካሉ በኋላ፣ ‹‹የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ትዕዛዝን አንቀበልም፤›› ብለዋል፡፡

በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋሉት ጋዜጠኞችና ጦማርያን ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሲቀርቡ በሦስት የምርመራ መዝገብ ተከፋፍለው ሲሆን፣ ቀደም ሲል በአዲስ ነገር ጋዜጣ፣ በፎርቹን ጋዜጣና በአዲስ ስታንዳርድ ጋዜጣ ላይ ይሠራ የነበረው ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ነው የተባለው ጦማሪ ዘለዓለም ክብረትና የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ከፍተኛ አዘጋጅ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ አንድ ላይ ናቸው፡፡

በሁለተኛው የምርምራ መዝገብ የተካተቱት የአዲስ ዘመን ጋዜጠኛ የነበረችው ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀና ጦማሪ አጥናፉ ብርሃኔ ሲሆኑ፣ የአየር መንገድ ሠራተኛ ነው የተባለው ጦማሪ አቤል ዋበላ፣ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉና ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁን በሦስተኛው የምርምራ መዝገብ ተካተው ለሚያዝያ 29 እና 30 ቀን 2006 ዓ.ም. መቀጠራቸው ታውቋል፡፡

በምሥረታ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋማ) የጋዜጠኞቹንና ጦማርያኑን መታሰር በማስመልከት ባወጣው መግለጫ፣ መንግሥት የተጠረጠሩበትን ጉዳይ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ እንደሚገባው ጠቁሞ፣ መታሰራቸው ግን እንዳሳሰበው ገልጿል፡፡ ባስቸኳይ እንዲፈቱም ጠይቋል፡፡

በአገር ውስጥ ያሉ የግል የኤሌክትሮኒክስና የሕትመት መገናኛ ብዙኃን፣ ከመንግሥትና ከቅርብ ወዳጆቻቸው እንዳገኙት አድርገው በተጠርጣሪዎቹ ጋዜጠኞችና ጦማርያን ላይ እያስተላለፉት ያለው መረጃ፣ መርማሪ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዳ ፍርድ ቤቱ በምርመራ መዝገቡ ላይ ካሰፈረው የተለየ በመሆኑ፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በቀጣይ የሚቀርበውን የምርምራ ውጤት ከመጠባበቅ ባለፈ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

ከዞን ዘጠኖች አንዱ ከጆን ኬሪ ጋር – ፎቶ ይዘናል

April 29/2014
አቦጊዳ

የአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የታሰሩ ብሎገሮች ጉዳያቸው በአስቸኳይ ታይቶ እንዲፈቱ በቀጥታ የኢትዮዮጵያን መንግስት መጠየቃቸው ቃለ አቀባይዋ ሚሲስ ፕሳኪ ገለጹ።
የኢትዮጵያ መንግስት በሕገ መንግስቱ የተደነገጉትን መብቶች ማክበር እንዳለበት፣ አሜሪካ ጠንካራ አቋም እንደሆኑ የገለጹት ሚሲስ ፕሳኪ፣ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስተሩ ጆን ኬሪ በአፍሪካ ጉብኘት ባደረጉበት ጊዜ ሁሉ የሰባአዊ መብት ጉዳይ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንደሚያነሱ ለመጠቆም ሞክረዋል።
ከታሰሩ ብሎገሮች መካካል አንዱ ናትናኤል ፈለቀ፣ ከአሜሪካዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ ጋር የተነሳዉን ፎቶ ይመልከቱ።
zone9_kerry1
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ፣ በኢትዮጵያ ጉድያ ላይ ከተናገሩት ጥቂቱን ከዚህ በታች ማንበብ ይችላሉ።
======================
State Department Daily Briefing regarding Secretary Kerry’s visit to Ethiopia.
MS. PSAKI: Sure, I can. We are aware that six independent bloggers and three independent journalists were detained by Ethiopian police April 25th through 26th. We urge the Government of Ethiopia to expeditiously review the cases of these detainees and promptly release them. We have raised these concerns on the ground directly with the Government of Ethiopia.
And we, of course, reiterate our longstanding concern about the abridgment of the freedom of press and the freedom of expression in Ethiopia, and urge the Government of Ethiopia to fully adhere to its constitutional guarantees. And certainly while the Secretary is there as part of his trip to Africa, he often raises, at every opportunity, issues surrounding human rights, whether it’s media freedoms or equal treatment, freedom of speech, and I expect that will be the case this time as well.

Tuesday, April 29, 2014

አንዷለም አራጌ እና የቃሊቲው ህይወት

April 29/2014

አንዷለም-አራጌ-እና-የቃሊቲው-ህይወት/አንዷለም-አራጌ-እና-የቃሊቲው-ህይወት/
fe236-andualem-aragie5b15d
(EMF) – አንዷለም አራጌ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል የነበረ ወጣት ነው። በኋላ ላይ የኢህ አዴግ ሰዎች ባቀናበሩት ድራማ አሸባሪ ተብሎ ለእስር ተዳረገ። ቃሊቲ በእስር ላይ ሆኖ ብቻውን በጨለማ ቤት ውስጥ ከመታሰር ጀምሮ ብዙ እንግልት እና መከራን እየተቀበለ ይገኛል። ይህ ሁሉ የሆነው አንዷለም በተቃዋሚው ጎራ በመቆሙ ብቻ ሳይሆን፤ ጎበዝ መሪ በመሆኑም ጭምር ነው። አሁን በ እስር ላይ ሆኖም እንኳን፤ ስሜቱን ለመጉዳት ሲባል እሱን ለመጠየቅ የሚሄዱ ጠያቂዎች ይዋከባሉ፤ እንዲጠይቁትም አይፈቀድላቸውም።
ከትላንት በስትያ አንዷለምን ለመጠየቅ ወደ እስር ቤት ያመሩት፤ ብቸኛው የፓርላማ ውስጥ ተቃዋሚ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ ትዝብታቸውን ገልጸዋል። የአቶ ግርማ ትዝብት “አንዱዓለምን ለመጠየቅ ቃሊቲ ጎራ ብዬ ነበር፡፡” በማለት ይጀምሩና በአንዷለም ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት በዝርዝር ገልጸውታል። እንዲህ በማለት ይቀጥላሉ አቶ ግርማ….
አንዱዓለም እንደተለመደው በጠንካራ ሞራልና ለሰው ልጅ ክብር በሚሰጠው መንፈሱ ላይ ምንም ለውጥ አይታይም፡፡ የሚበድሉትን ቢሆን ለምን? ብሎ ይጠይቃል እንጂ የበቀለኝነት ሰሜት የለበትም፡፡ ነገር ግን በፍፁም ተሰፋ እያሰቆረጠው ምን አልባት ወደ ርሃብ አድማ ሊገፋኝ ይችላል ብሎ የሰጋው ከብዙ ሺ ከሚቆጠሩ እሰረኞች በተለየ ሁኔታ የሚሰተናገድበት አያያዝ ምቾት አልሰጠውም፡፡ መብቱን እያስደፈረ እንደሆነ ይሰማዋል፡፡
እሱን ለመጠየቅ ከባለቤቱ እና ከእኔ በስተቀር ይህን ሁሉ ኪሎ ሜትር አቋርጠው የመጡ ሰዎችን እየመለሱ ችግር እየፈጠሩበት እንደሆነ ነግሮኛል፡፡ ማንም ጠያቂ እርሱ እንዲጠይቅ አይፈቀድለትም፡፡ ይህ ደግሞ ፌዝ የሚሆነው ለእርሱ ደህንነት ብለን ነው የሚሉት መልስ ነው፡፡ በተለይ ትላንት ምሽት ድንገት በተደረገ ብረበራ ከማረሚያ ቤቱ ላይብረሪ ተውሶ ሲያነባቸው ከነበሩተ መፅኃፎች ላይ የያዛቸውን ማስታወሻዎች በሙሉ ወስደውበታል፡፡ በማረሚያ ቤቱ ደንብ ላይ ይህ ክልከላ ስለመኖሩ ጠይቄው የማረሚያ ቤቱን ደንብና መመሪያ እንዲሰጡኝ ከጠየቅሁ ስድሰት ወር ያለፈ ቢሆንም እስከ አሁን እንዳልሰጡት ነግሮኛል፡፡
ማረሚያ ቤቱ ከህገ መንግሰት በተቃራኒ የሆነ መመሪያ የማውጣት መብትም የለውም፡፡ በነገራችን ላይ የአንዱዓለም ጠያቂዎች እንዳይጎበኙት የተጣለበትን ክልከላ አምሳደር ጥሩነህ ዜናም እንደሚያውቁት ነገር ግን ይህ መመሪያ ስለሆነ እንደሆነ ገልፀውልኝ፣ መመሪያው ከህገመንግሰት ጋር የሚጋጭ ነገር ካለው እንደሚያዩት መደበኛ ባልሆነ ውይይት ገልፀውልኝ ነበር፡፡ አንድ እስረኛ በተለየ ሁኔታ በዘመድ አዝማድ ጓደኛ እንዳይጠየቅ ገደብ ለምን እንደሚደረግበት ሊገባኝ ባይችልም፡፡ ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ከመደበኛው በተለይ የሚደረጉ ተግባራትን ተዉ የሚል ያለ አይመስልም፡፡
አንዱዓለም ቃሊቲ ከገባ ጀምሮ በልዩ ቅጣት ክፍል የሚገኝ ሲሆን በዚህ ክፍልም ልዩ ጥበቃ ይደረግበታል፡፡ አንዱዓለም የሚላኩለት መፅሃፎች በጊዜው እንደማይገቡለትና ከተላከለት ስምንት መፅሃፍ ውስጥ 2 አይገባም ከተባለ በኋላ ወደ ቤተሰቦቹም አለመመለሱንም ገልጾልኛል፡፡ ለክፉም ለደጉ አንዱዓለም ለመጉዳት የሚንቀሳቀሱ የመንግሰት ኃላፊዎችም ሆኖ ልወደድ ባይ የማረሚያ ቤት ሹሞች ከዚህ ተግባራቸው ቢቆጠቡ ጥቅሙ የጋራ ነው፡፡ አንዱዓለም ሰርቆ ወይም ሀገር ከድቶ አይደለም በእስር ላይ የሚገኘው፡፡ ለሀገሩ ነፃነት የድርሻዬን እውጣለሁ ብሎ በሰላማዊ መንገድ ሲንቀሳቀስ ይህ ዜጋ ለወንበራችን ጠር ነው ብለው በፈሩ እና በሀሰት በወነጀሉት አካላት ምክንያት ነው፡፡ ሌቦችን ወንጀለኞች እንደፈለጉ በሚሆኑበት እስር ቤት ጀግኖችን ማሰቃየት ማንገላታ አሁንም ፍርሃታቸው እንዳለቀቃቸው ከማሳየት ውጭ አንዱዓለምን መንፈስ እንደማይጎዳው እርግጠኛ ነኝ፡፡ የአሳሪዎቹን በቀለኝነት ግን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡

TPLF/EPRDF charges nine bloggers and journalists with inciting violence

April 29, 2014
(Reuters) – Ethiopia has charged six bloggers and three journalists with attempting to incite violence, their supporters said on Monday, prompting accusations from rights groups that the government is cracking down on its critics.Ethiopia has charged six bloggers and three journalists with attempting to incite violence
All nine defendants, including freelance journalists Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, appeared in court on Sunday after they were rounded up by police on April 25 and April 26, their colleagues told Reuters.
On Monday, Human Rights Watch (HRW) called on U.S. Secretary of State John Kerry, who visits Ethiopia on Tuesday, to press the government to “unconditionally release” all the defendants, but Addis Ababa dismissed the criticism of the case.
“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, HRW’s deputy Africa director.
“The timing of the arrests – just days before the U.S. secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech,” she said in a statement.
In 2012, Addis Ababa sentenced a prominent blogger and five other exiled journalists to between eight years to life on charges of conspiring with rebels to topple the government.
In the new case, a colleague of Tesfalem said security officials in plain clothes searched his house and confiscated several materials before taking him to a detention center.
An Ethiopian government official defended the case against the nine, saying it had nothing to do with muzzling the media.
“CRIMINAL ACTIVITIES”
“These are not journalists. Their arrest has nothing to do with journalism but with serious criminal activities,” Getachew Reda, an adviser to Prime Minister Hailemariam Desalegn, said.
“We don’t crack down on journalism or freedom of speech. But if someone tries to use his or her profession to engage in criminal activities, then there is a distinction there,” Getachew told Reuters.
Critics say Ethiopia – sandwiched between volatile Somalia and Sudan – regularly uses security concerns as an excuse to stifle dissent and clamp down on media freedoms.
They also point to an anti-terrorism law, passed in 2009, which stipulates that anyone caught publishing information that could incite readers to commit acts of terrorism can be jailed for between 10 and 20 years.
Addis Ababa says the law aims to prevent “terrorist attacks” as it is fighting separatist rebel movements and armed groups.
A court in Addis Ababa adjourned the hearing for the group of bloggers and journalists until May 7 and 8.
Kerry will meet Prime Minister Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa to discuss peace efforts in the region and to strengthen ties with Ethiopia, State Department spokeswoman Jen Psaki said in a statement.
The State Department says the aim of Kerry’s African tour – which will also take in Democratic Republic of Congo and Angola – is to promote democracy and human rights.
(Editing by James Macharia and Gareth Jones)

ጆን ኬሪ በአዲስ አበባ – ኢህአዴግ አሁንም በሶማሊያ ያስፈራራ ይሆን?

April 29/2014

ኢህአዴግ የዞን9 ጦማሪዎችን “አገር በማተራመስ” ወንጀል ከሰሰ
kerry 1


የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ የኢትዮጵያ ጉዞ በርካታ ጉዳዮች የሚከናወኑበት እንደሆነ ተጠቆመ። የዘወትር የጎልጉል ምንጭ አንዳሉት የኬሪ አዲስ አበባ ጉዞ አስቀድመው የተሰሩ ስራዎች ውጤት ነው። ጥቁሩ ሰው “ውሻ ምንም ሳይመለከት አይጮህም” ሲሉ አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች ራሳቸውን ብቃት ያላቸው አማራጮች መሆናቸውን እንዲያሳዩ ጠይቀዋል። ኢህአዴግ አሜሪካንንና የምዕራቡን ዓለም እንደለመደው “ከሶማሊያ ጦሬን አወጣለሁ” በማለት መደራደሪያ ከማቅረብ ውጪ ሌላ አቅም እንደሌለው ተገለጸ። ኢህአዴግ የዞን9 ጦማሪዎችና ጋዜጠኞች “አገር በማተራመስ” ወንጀል ክስ መሰረተባቸው።
የድረገጽና የማህበራዊ ገጽ የኢህአዴግ ደጋፊዎችና የስርዓቱ ተጠቃሚ አባላት ባይዋጥላቸውም አሜሪካና ኢህአዴግ የነበራቸው ግንኙነት እየሻከረ መሔዱን ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ ሲገልጽ እንደነበር ይታወሳል። ጎልጉል የዋሽንግቶን ዲፕሎማት ምንጩን በመጥቀስ እንደዘገበው አሜሪካ ኢህአዴግን “የምስራቅ አፍሪካ ስጋት” አድርጋም ፈርጃለች። የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚከታተለውና በስቴት ዲፓርትመንት ውስጥ የተቋቋመው የቀውስ መከላከልና ዕርቅ ቢሮ ሃላፊ ከጥር ወር ወዲህ ባሉት ጥቂት ወራት ውስጥ አራት ጊዜ አዲስ አበባ ተጉዘዋል።
ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ፍትሃዊነት የጎደለው አገዛዝ ኢትዮጵያን ወደ ቀውስ እንዳመራትና ይኸው ቀውስ እልባት ካልተበጀለት የምስራቅ አፍሪካን የሚያዳርስ እንደሚሆን በአሜሪካ በኩል አቋም መያዙ ኢህአዴግን እንዳስበረገገው ተንታኞች እየገለጹ ነው። የምስራቅ አፍሪካ “የሰላም አባት ነኝ የሚለው ኢህአዴግ በውስጣዊ የፖለቲካ ቀውስ ስለሚገኝ የመወላለቅ ችግር ሳይገጠመው በፊት አሜሪካ አስቀድማ ስራዋን መስራት መጀመሯ ከራሷ ጥቅም አንጻር ነው” ሲሉ ዲፕሎማቱ እንደቀድሞው ሁሉ ሳይሸሽጉ ተናግረዋል። የኬሪ ጉዞም የዚሁ አካል እንደሆነ አስታውዋል። “ኢህአዴግ” አሉ ዲፕሎማቱ “የቀለም አብዮት እያለ እንደሚደነፋው ሳይሆን በመጪው ምርጫ በሩን ከፍቶ ለመወዳደር ከተስማማ ብቻ የለመደው ርጥባን ይሰጠዋል የሚል ግምት አለኝ” ብለዋል።
በ97 ምርጫ ወቅት እንዳደረገው በሶማሊያ ያለውን አለመረጋጋት እንደ ማስፈራሪያ በመጠቀም ጦሩን የማስወጣት ርምጃ ቢወስድስ? በሚል ለተጠየቁት “ኢህአዴግ የመጫወቻ ካርዶቹ ያለቁበት ይመስለኛል” በማለት የግሌ ያሉትን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ኢህአዴግ በምርጫ 97 ተደራደር ሲባል ጦሩን ሰብስቦ ለመውጣት በዝግጅት ላይ እንደሆነ መግለጹን የተለያዩ የውጪ አገር ሚዲያዎች መዘገባቸው አይዘነጋም።
obang-o-metho-hearingየአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ /ጥቁሩ ሰው/ “ውሻ ከጮኸ የሆነ ነገር አለ ማለት ነው” ሲሉ ለጎልጉል አስተያየት ሰጥተዋል። ኦባንግ አገር ቤት የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይህንን ጩኸት ሰምተው ህዝብን በማስቀደም ራሳቸውን አማራጭ አድርገው እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል። አማራጭ የለም የሚለውን ፍርሃቻ በመስበር ወቅቱን ለህዝብና ለአገር ጥቅም ለማዋል እንዲተጉ አሳስበዋል። የሚመሩት ድርጅት በቅርቡ በዚህ ዙሪያ የሚለው ነገር ስላለ ዝርዝር ጉዳይ ውስጥ ከመግባት ተቆጥበዋል።
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤትን በመጥቀስ የጀርመን ድምጽ እንደዘገበው ኬሪ፤ ሃይለማርያም ደሳለኝን፣ ቴድሮስ አድሃኖምንና የሚመለከታቸውን ባለስልጣናት በሰብአዊ መብት አያያዝና በዲሞክራሲ ትግበራ ዙሪያ እንደሚያነጋግሩ ማረጋገጫ መሰጠቱን ጠቁሟል። በዚሁ ዜና ላይ ቃላቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ ኬሪ ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች ጋር ይነጋገራሉ የሚል ስጋት እንዳለባቸው የሚያሳብቅ መልስ ሰጥተዋል። ኬሪ የዞን9 ድረገጽና ማህበራዊ ድር ጦማሪዎች እስርን አስመልክቶ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ ጆን ኬሪ ስለ ዞን9 አባላት እስር ሊያነሱ እንደሚችሉ ተጠይቀው “እንደምናከብረው መሪ ጥያቄውን ካቀረቡ አስፈላጊውን መልስ እንሰጣለን” ካሉ በኋላ “የዞን9 ጦማሪዎች በጋዜጠኛነታቸው አልታሰሩም” በማለት ከገጀራና ከስርቆት ወንጀል ጋር በማዛመድ ለማቃለል ሞክረዋል።
getachew
ጌታቸው ረዳ
አገዛዙ ዝም ማለቱን አስመልክቶ “የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረገ ሴል ቢኖር መግለጫ እናወጣለን” ሲሉ የመለሱት አቶ ጌታቸው፣ ጆን ኬሪ የእስረኞቹን ጉዳይ እንዲያነሱ ያሳሰበውን ሂውማን ራይትስ ዎችን “ልማዱ ነው” ሲሉ ዘልፈዋል።
የዞን9 አባላትን ታፍኖ መወሰድና በአገር ማተራመስ ወንጀል መከሰሳቸውን የሰሙ “ኢህአዴግ ማንንም ለአገር ተቆርቋሪ ሆኖ የመወንጀል ሞራላዊ ብቃት የለውም” በማለት ነው አስተያየታቸውን የሚጀምሩት። ኢህአዴግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ አሁን አስከደረሰበት ደረጃ ድረስ ዜጎችን በአገር ክህደት የመፈረጅ ብቃት ከቶውንም እንደሌለው ራሱም ጭምር የሚያወቀው እውነት እንደሆነ የደረሱን አስተያየቶች ያመላክታሉ።
ያለፈው እሁድ አራዳ ምድብ አንደኛ ችሎት የቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞችና ስድስት ጦማሪዎች በሶስት የተለያዩ መዝገቦች መከሰሳቸው የጀርመን ሬዲዮ ይፋ አድርጓል። ከታሰሩ በኋላ ከቤተሰብና ከተመልካች ተሰውረው ምርመራ ሲደረግባቸው የነበሩት የዞን9 ጦማሪዎች አስመልከቶ ወ/ሮ ሚሚ ስብሃቱ የራሳቸው በሆነው የዛሚ ኤፍ ኤም 90.7 ሬዲዮ ክስ ከመመስረቱ በፊት ስለተከሰሱበት ጉዳይ የፖሊስ ምንጭ ጠቅሰው መናገራቸውን ቪኦኤ ተናግሯል።
ወ/ሮ ሚሚን ጠቅሶ የዞን9 ጦማሪዎች አርቲክል 19 ከሚባለው ተቋም ጋር ግንኙነት ያላቸውና የተለያዩ አገራት ሄደው የሰለጠኑ መሆናቸውን፣ በአገሪቱ ትርምስ ለመፍጠር በሻዕቢያና በግብጽ በገንዘብ እንደሚረዱ ቪኦኤ በዘገበ ማግስት ነው ፖሊስ በተመሳሳይ የክስ መዝገብ የተጨማሪ ቀጠሮ ቀን የጠየቀባቸው። የዞን 9 ጦማሪዎች ኢህአዴግ ላይ ጠንካራ ትችት በመሰንዘር የሚታወቁ ናቸው።
“አርብ ሚያዝያ 17 ቀን 2006 አመሻሹ ላይ 11፡20 ገደማ ስድስት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን አባላት ናትናኤል ፈለቀ፣ በፍቃዱ ሀይሉ፣ አጥናፍ ብረሀነ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ዘላለም ክብረት እና አቤል ዋበላ በበነጋው ደግሞ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስም በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ከያሉበት ተይዘዋል፡፡ታሳሪዎቹን ለመያዝ የመጡት አካላት የማሰሪያና የመፈተሻ የፍርድ ቤት ፈቃድ የያዙ መሆናቸውን መስማታቸውን በዚሁ አጭር መግለጫ ላይ ተጠቅሷል።
zone9“ዞን 9” የጦማርያን ስብስብ አባላት ሚያዚያ 15፣2006 ባወጣነው መግለጫ ላለፉት ሰባት ወራት የዞኑ አባላት ከፍተኛ የሆነ ክትትል ሲደረግባቸው እንደነበር በጠቅላላው የተጠቆመ ሲሆን ክትትሉ የተወሰኑ የቡድኑን አባላትና የቅርብ ወዳጆችን ጭምር ያካተተ ነበር፡፡ አሁን በመንግስት የተወሰደው እርምጃ የዞኑን ተመልሶ ወደ ስራ መግባት ተከትሎ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል ሆኖም የዞን 9 አባላትና ወዳጆች በምንም አይነት ህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው እንዳልነበር ለማረጋገጥ እንወዳለ” በማለት በራሳቸው የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ዜና አሰራጭተው ነበር።
በተመሳሳይ ዜና ቻይናን “ቃል የገባሽውን ብር አምጪ” ብሎ የሙጥኝ የያዘው ኢህአዴግ “ቀለም ይፈራል” ሲሉም በቅርብ የሚከታተሉ እየተቹት ነው። “ሆድ በባሰው ቁጥር የቀለም አብዮት ” በማለት ቅስቀሳ የሚያዘወትረው ኢህአዴግ አሁን ያስፈራው የትኛው ቀለም እንደሆነ በይፋ ባይገልጽም የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑትን ኢንጂነር ይልቃል “ተስፋ የተጣለባቸው ወጣት መሪዎች” በሚል ተመርጠው ከሌሎች አቻዎቻቸው ጋር አሜሪካ ለስልጠናና ለልምድ ልውውጥ መጋበዛቸው፣ ወደ ስፍራው እንዳያመሩ መደረጉ፣ እንዲሁም አሁን በድፍረት የሚንቀሳቀሱና የሚያስተባብሩ መሆናቸው አንዱ የስጋት ምንጭ ሊሆን አንደሚችል ግምት አለ።
“የቀለም አብዮት ሰለባዎች” በሚል ርዕስ ኢህአዴግ ዩክሬንን አስታኮ ያሰራጨው ቪዲዮ አሜሪካንን በሽብር ስራ የማሰልጠን ክህሎት ያላት፣ ሽብርተኞች አገርን አንዲያተራምሱ በመደገፍ የሚታወቁ ተቋማት ባለቤት የሆነች አገር ብሎ መፈረጁ አይዘነጋም። ኢህአዴግ ተንታኝ አድርጎ ያቀረባቸው ጎረምሶች አሜሪካንና የምዕራብ አገሮችን ሲዘልፉ የሚያሳየው ፊልም መጨረሻው “ከፊል የዩክሬን ህዝብ ራስን በራስ በመወሰን መብቱ ተጠቅሞ የቀድሞ አካሉን ሩሲያን ተቀላቀለ” በሚል መሆኑና ጉዳዩ ከአሁኑ የኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር ተዛምዶ መቋጨቱ የኢህአዴግን በተለይም የህወሃትን ስጋት እንደሚያጎላው የሚያሳይ እንደሆነ አስተያየት እየተሰጠበት ነው። በሕገመንግሥቱ አገር እንድትበታተን በአንቀጽ 39 በግልጽ አስቀምጦ እስካሁን ኢትዮጵያን በ“ነጻ አውጪ ግምባር” ስም የሚመራውና “የነጻ አውጪ ግምባሩን” መሪ ወደ ተባበሩት መንግሥታት በመላክ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠል ዓለምን የለመነው ህወሃት/ኢህአዴግ፤ “የቀለም አብዮት ሰለባዎች” በማለት ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጭ ከሶቪየት ህብረት የተገነጠለችውና የዩክሬን አካል የነበረችው ክሬሚያ ወደ እናት አገሯ ሩሲያ መመለሷን አብሮ ማሰራጨቱ ዘጋቢ ፊልሙን ዋጋቢስ የሚያደርገው መሆኑን አለማስተዋሉ በራሱ ሌላ ዘጋቢ ፊልም የሚያሰራ ነው፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ናት – የኦሮሞ ተማሪዎች

April 28/2014

በአራት ዪኒቨርሲቲዎች የሚገኙ የኦሮሞ ተማሪዎች የአዲስ አበባ አዲሱን ማስተር ፓልን በመቃወም ተቃዉሞውውቸዉን አሰሙ።
በዉጭ አገር የሚገኘውና በቅርቡ የተቋቋመው የኦሮሞ ሜዲያ ንቴዎርክ ማስተር ፓልኑን በመቃወም ከፍተኛ ቅስቀሳ እያደረገ የነበረና የሚገኝ ሲሆን፣ በዶር መራራ ጉዳናን የሚመራዉ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን ጨመሮ በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች ፕላኑን አዉግዘዋል።
የኦሮሞ ተማሪዎች ም በአምቦ፣ በወለጋ፣ በጂማና በሃረማያ ሰላማዊ በሆነመንገድ ተቃዉሟቸውን ለማሰማት የሞከሩ ሲሆን፣ በአጸፋው የፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ ደብደባ በተማሪዎች ላይ እንዳደረሰ ለማወቅ ችለናል።
በወላጋ ፖሊስ ጥይት የተኮሰ ሲኦሆን በርካቶች እንደቆሰሉ የተቀረኡትን በአካባቢዉ ወዳለ ጫካ እንደትበታተኑ ለማወቅ ተችሏል። በጂማ 11 በአምቦ ደግሞ 15 ተማሪዎች ታስረዋል።
ተማሪዎቹ «ቡራዩ አይሸጥም፣ ሱሉልታ አይሸጠም፣ ለገጣፎ አይሸጥም፣ ኦሮሚያ ለኦሮሞዎች ብቻ ! ፊንፊኔ የኦሮሚያ ናት..» የመሳሰሉ መፈክሮችን ሲያሰሙም ነበር።
በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አዲስ አበባ የኦሮሚያ አካል እንደሆነች በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን፣ ኦሮሚያ ከአዲስ አበባ ማግኘት ያለባትን ጥቅም ማግኘት እንደሚኖርባትም ይደነግጋል። የኢትዮዮጵያ ግዛት ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን ብሄረ ብሄረሰቦች እንደሆነ የሚደነግገው ሕገ መንግስቱ፣ ብሄር ብሄረሰቦች ራሳቸው በራስ የማስተዳደር መብት ያዉም እስከመገንጠል እንደሚፈቅድም ይታወቃል።
አገሪቷ በቋንቋ ላይ የተመሰረተ ፌዴራል አወቃቀር እንዲኖራት የተደረገ ሲሆን፣ ይሄም አወቃቀር ያል ሕዝብ ፍቃደ በኦነግ፣ በሕወሃት እና በሻቢያ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እንደሆነ ይታወቃል።
የኦሮሚያ ሕግ መንግስት የኦሮሚያ ባለቤት ኦሮሞ ብቻ እንደሆነ በአንቀጽ ስምንት ባስቀመጠዉ መሰረት፣ ኦሮሞ ያልሆኑ ኢትዮጵያዊያን በኦሮሚያ ዉስጥ እንደ እንግዳ እንደሚታዩም የሚገልጹ በርካታ ክስተቶች አሉ።
በኦሮሞ ተማሪዎች ሲባሉ የነበሩት «ኦሮሚያ የኦሮሞውች ናት። አዲስ አበባ የኦሮሚያ ናት» የሚሉት መፈክሮች፣ አገዛዙ ራሱ በሰነድና በወረቀት የሚቀበለውና የሚስማማበት እንደመሆኑ፣ ተማሪዎች ሰላማዊ በህነ መንገድ በኦሮሚያ ሕግ መንግስት ዬትቀመጠዉን በመድገማቸው መደብደባቸው ፣ አሳፋሪ እና አዛዝኝ እንደሆነም ብዙዎች እየተናገሩ ነው።
ዜጎች በኢሕአደግ ባለስልጣናት ከቅያቸው የሚፈናቀሉት በሁሉም ክልሎች እንደሆነ የገለጹት ያነጋገርናቸው አንድ የፖለቲክ ተንታኝ ፣ በልማት ስም በኦሮሞዎችም ሆነ በማንም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርስን ግፍ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ መቃወም እንዳለበት ይናግራሉ። አዲስ አበባን በተመለከተ « አዲስ አበባ ማደጓ አይቀርም። እድገቷ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ይፈጸም መባል ነው እንጂ ያለበት፣ የኦሮሚያ ሬፑብሊክ ወደፊት ለመፍጠር ከሚኖር ፍላጎት የተነሳ የኦሮሚያ ክልል ለምን አነሰች የሚል ጠባብ መከራከሪያ የትም አያደርስም።» ሲሉ ተማሪዎቹም ሆነ በዉጭ ያሉ የኦሮሞ ብሄረተኞች ያለዉን ተጨባጭ እዉነታ እንዲገነዘቡም ይመክራሉ።
oromo1
oromo2
oromo3

Monday, April 28, 2014

Ethiopia should immediately release bloggers (HRW)

April 28, 2014
Ethiopia should immediately release bloggers (HRW)
Ethiopia should immediately release bloggers (HRW)
Human Rights Watch
(Nairobi) – The Ethiopian authorities should immediately release six bloggers and three journalists arrested on April 25 and 26, 2014, unless credible charges are promptly brought.
United States Secretary of State John Kerry, who is scheduled to visit Ethiopia beginning April 29, should urge Ethiopian officials to unconditionally release all activists and journalists who have been arbitrarily detained or convicted in unfair trials. The arrests also came days before Ethiopia is scheduled to have its human rights record assessed at the United Nations Human Rights Council’s universal periodic review in Geneva on May 6.
“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “The timing of the arrests – just days before the US secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech.”
On the afternoon of April 25, police in uniform and civilian clothes conducted what appeared to be a coordinated operation of near-simultaneous arrests. Six members of a group known as the “Zone9” bloggers – Befekadu Hailu, Atnaf Berahane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, and Abel Wabela – were arrested at their offices and in the streets. Tesfalem Weldeyes, a freelance journalist, was also arrested during the operation. Edom Kassaye, a second freelance journalist, was arrested on either April 25 or 26; the circumstances of her arrest are unclear but all eight individuals were apparently taken to Maekelawi Police Station, the federal detention center in Addis Ababa, the capital.
The police searched the bloggers and journalists’ offices and homes, reportedly with search warrants, and confiscated private laptops and literature. On April 26, another journalist, Asmamaw Hailegeorgis of Addis Guday newspaper, was also arrested and is reportedly detained in Maekelawi.
The detainees are currently being held incommunicado. On the morning of April 26, relatives were denied access to the detainees by Maekelawi guards, and only allowed to deposit food.
Human Rights Watch released a report in October 2013 documenting serious human rights abuses, including torture and other ill-treatment,unlawful interrogation tactics, and poor detention conditions in Maekelawi against political detainees, including journalists. Detainees at Maekelawi are seldom granted access to legal counsel or their relatives during the initial investigation phase.
The Zone9 bloggers have faced increasing harassment by the authorities over the last six months. Sources told Human Rights Watch that one of the bloggers and one of the journalists have been regularly approached, including at home, by alleged intelligence agents and asked about the work of the group and their alleged links to political opposition parties and human rights groups. The blogger was asked a week before their arrest of the names and personal information of all the Zone9 members. The arrests on April 25, 2014, came two days after Zone9 posted a statement on social media saying they planned to increase their activism after a period of laying low because of ongoing intimidation.
A Human Rights Watch report in March described the technologies used by the Ethiopian government to conduct surveillance of perceived political opponents, activists, and journalists inside the country and among the diaspora. It highlights how the government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.
Kerry is scheduled to meet with Prime Minister Hailemariam Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa “to discuss efforts to advance peace and democracy in the region.” Kerry should strongly urge the Ethiopian government to end arbitrary arrests, release all activists and journalists unjustly detained or convicted, and promptly amend draconian laws on freedom of association and terrorism that have frequently been used to justify arbitrary arrests and political prosecutions. The Obama administration has said very little about the need for human rights reforms in Ethiopia.
“Secretary Kerry should be clear that the Ethiopian government’s crackdown on media and civil society harms ties with the US,” Lefkow said.  “Continued repression in Ethiopia cannot mean business as usual for Ethiopia-US relations.”

ኢትዮጵያ የታሰሩ ጋዜጠኞችና ጸሃፊዎችን እንድትፈታ ሂውማን ራይትስ ወች ጠየቀ

April 28/2014


ሚያዚያ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ተጨባጭ ማስረጃ እስካላመጣ ድረስ ከ3 ቀናት በፊት ያሰራቸውን 3 ጋዜጠኞች እና 6 ጸሃፊዎችን በአስቸኳይ እንዲፈታ የሰብአዊ መብት ድርጅቱ አሳስቧል፡፡

ኢትዮጵያን የሚጎበኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ተጠሪ ጆን ኬሪ ፍትሃዊ ባልሆነ ዳኝነት በእስር የሚሰቃዩ ጋዜጠኞች እንዲሁም ያለበቂ ማስረጃ የሚታሰሩት ጋዜጠኞች እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እንዲፈቱ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ሂውማን ራይትስ ወች ጠይቋል።

የሂውማን ራይትስ ወች የአፍሪካ ዳይሬክተር ሌስሌ ሌፍኮ “የ9ኙ ሰዎች መታሰር መንግስትን የሚተቹ ሁሉ አፋቸውን እንዲዘጉ እንደሚደረጉ ማሳያ ነው” ብለዋል።

ዞን 9 እየተባለ የሚጠራ የፌስ ቡክ አካውንት በመክፈት ጽሁፎችን ሲጽፉ ከነበሩት ወጣቶች መካከል በፈቃዱ ሃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ዘላለም ክብረት እና አቤል ዋቤላ ከስራ ቦታቸውና ከመንገድ ላይ ታፍሰው መታሰራቸውን፣ ጋዜጠኛ ተስፋ አለም እና ኤዶም ካሳየም እንዲሁ ፖሊስ ወደ ማእከላዊ እስር ቤት ተወስደው መታሰራቸውን ድርጅቱ ገልጿል። የአዲስ ጉዳይ መጽሄት ዋና አዘጋጅ አስማማው ሃይለ ጊዮርጊስም እንዲሁ ወጣቶቹ በታሰሩ ማግስት መታሰራቸውን በመግለጫው ጠቅሷል።

በእስር ላይ የሚገኙት ወጣቶች ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ተደርጎ የታሰሩ በመሆኑ ለጥየቃ የሄዱ ቤተሰቦች ሳያገኙዋቸው ቀርቷል።
ዞን 9 እየተባሉ የሚጠሩ ወጣቶች ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ የሆነ ማስፈራሪያ ሲደርስባቸው ነበር።

ሂውማን ራይትስ ወች የኦባማ አስተዳደር በኢትዮጵያ ስለሚታየው የሰብአዊ መብት ጥሰት ምንም አለማለቱን ወቅሷል።
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ባወጣው መግለጫ ደግሞ መድረኩ እስካሁን በሰበሰበዉ መረጃ መሰረት ወጣቶቹን ለእስር የሚያበቃ ምን ም አይነት ማስረጃ ለማግኘት አለመቻሉን ገልጿል።

ለእስር ከመዳረጋቸው በፊት ከመንግስት ሲርስባቸዉ በነበረዉ ህገወጥ ድርጊቶች ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስራቸዉን ካቋረጡ በኋላ በቅርቡ ወደ ስራ መመለሳቸዉን ይፋ አድርገው እንደነበር ከድረገጻቸው ላይ ለመረዳት መቻሉን ኢጋመ ጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መንግስት ታሳሪዎቹን ለማሰር ያበቃዉ ተጨባጭ ማስረጃ ካለ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ ያ ካልሆነ ግን እስረኞቹን በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ ጥያቄ አቅርቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለገዢው ፓርቲ ቅርበት አለው የሚባለው ዛሚ ኤፍኤም 90.7 ከዞን 9 ጋር በተያያዘ የታሰሩ ጸሃፊዎችና ጋዜጠኞች ላይ የተጀመረው እስር በሌሎችም ላይ እንደሚቀጥል የሚያረጋግጥ ዘገባ አቅርቧል፡፡

ሬዲዮው ከፖሊስ ታማኝ ምንጮቼ አገኘሁት ባለው መረጃ መሠረት ከዞን 9 ጋር በተያያዘ የታሰሩ ብሎገሮችና ጋዜጠኞች በህቡዕ ተደራጅተው መንግስትን በአመጽ ለመጣል ማሴራቸውን፣ እንዲሁም ማናቸውንም ዓይነት ሰላማዊ ሰልፎች እንዲካሄዱና በሰልፎቹ ላይ መንግስትን ለመቃወም ስልጠናዎችን በውጪና በአገር ውስጥ መውሰዳቸውን አትቷል፡፡
እንደዘገባው ከሆነ ጤናን የሚመለከት ሰልፍም ቢሆን እንዴት ወደተቃውሞ መቀየር እንደሚቻል ተጠርጣሪዎቹ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግራል፡፡

ሬዲዮው ከታሰሩት በተጨማሪ በሕጋዊ መንገድ በመመስረት ሒደት ላይ የሚገኘው ኢትዮጽያ የጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) በተመሳሳይ መንገድ በውጪ አገር ከሚንቀሳቀሱ ተቁዋማት ጋር ግንኙነት እንዳለው ከፖሊስ መረጃ አግኝቻለሁ ከማለቱም በተጨማሪም በማህበሩ ላይ ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡ ይህ ሁኔታ በቀጣይ ማህበሩ ላይ ትኩረት መደረጉን እንደሚያሳይ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ጠቁመዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሚያዝያ 17 እና 18 ቀን በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩ ሦስት ጋዜጠኞችና ስድስት ጦማርያን በትላንትናው ዕለት እሑድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. በሶስት መዝገብ ፖሊስ ፍርድ ቤት አቅርቦአቸው የጊዜ ቀጠሮ እንደጠየቀባቸው ሪፖርተራችን ስቱዲዮ ከመግባታችን በፊት የላከችው ዘገባ ያስረዳል፡፡

ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል መርማሪ ፖሊስ ያቀረባቸው በፍቃዱ ኃይሉ፣ ማህሌት ፋንታሁን አቤል ዋበላ በአንድ መዝገብ፤ ዘለዓለም ክብረት፣ ተስፋዓለም ወልደየስና አስማማው ኃይለጊዮርጊስ በሌላ መዝገብ እንዲሁም አጥናፉ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀና ኤዶም ካሳዬ አንድ ላይ፣ ዘጠኙም ተጠርጣሪዎች ሦስት ሦስት ሆነው ቀርበዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነን ከሚሉ የውጭ ኃይሎች ጋር በሙሉ ሐሳብና በገንዘብ በመስማማት፣ ሕዝብን የሚያተራምስና አገርና መንግሥትን የሚያፈርስ ዘገባ በኢንተርኔትና በማኅበራዊ ድረ ገጾች ያልሆነ መረጃ ማስተላለፋቸውን ፖሊስ ለፍ/ቤቱ ገልጾአል፡፡ ፖሊስ ምርመራውን ባለመጠናቀቁም የ15 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቢጠይቅም የተፈቀደለት የ10 እና 11 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ነው፡፡ እስካሁን መንግስት በተጠርጣሪዎቹ ጉዳይ በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለገዢው ፓርቲ ቅርበት አለው የሚባለው ዛሚ ኤፍኤም 90.7 ከዞን 9 ጋር በተያያዘ የታሰሩ ጸሃፊዎችና ጋዜጠኞች ላይ የተጀመረው እስር በሌሎችም ላይ እንደሚቀጥል የሚያረጋግጥ ዘገባ አቅርቧል፡፡

ሬዲዮው ከፖሊስ ታማኝ ምንጮቼ አገኘሁት ባለችው መረጃ መሠረት ከዞን 9 ጋር በተያያዘ የታሰሩ ብሎገሮችና ጋዜጠኞች በህቡዕ ተደራጅተው መንግስትን በአመጽ ለመጣል ማሴራቸውን፣ እንዲሁም ማናቸውንም ዓይነት ሰላማዊ ሰልፎች እንዲካሄዱና በሰልፎቹ ላይ መንግስትን ለመቃወም ስልጠናዎችን በውጪና በአገር ውስጥ መውሰዳቸውን አትታለች፡፡

እንደዘገባው ከሆነ ጤናን የሚመለከት ሰልፍም ቢሆን እንዴት ወደተቃውሞ መቀየር እንደሚቻል ተጠርጣሪዎቹ ስልጠና መውሰዳቸውን ተናግራለች፡፡

ሬዲዮው ከታሰሩት በተጨማሪ በሕጋዊ መንገድ በመመስረት ሒደት ላይ የሚገኘው ኢትዮጽያ የጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) በተመሳሳይ መንገድ በውጪ አገር ከሚንቀሳቀሱ ተቁዋማት ጋር ግንኙነት እንዳለው ከፖሊስ መረጃ አግኝቻለሁ ከማለቷም በተጨማሪም በማህበሩ ላይ ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጻለች፡፡ ይህ ሁኔታ በቀጣይ ማህበሩ ላይ ትኩረት መደረጉን እንደሚያሳይ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ጠቁመዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሚያዝያ 17 እና 18 ቀን በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩ ሦስት ጋዜጠኞችና ስድስት ጦማርያን በትላንትናው ዕለት እሑድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. በሶስት መዝገብ ፖሊስ ፍርድ ቤት አቅርቦአቸው የጊዜ ቀጠሮ እንደጠየቀባቸው ሪፖርተራችን ስቱዲዮ ከመግባታችን በፊት የላከችው ዘገባ ያስረዳል፡፡

ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል መርማሪ ፖሊስ ያቀረባቸው በፍቃዱ ኃይሉ፣ ማህሌት ፋንታሁን አቤል ዋበላ በአንድ መዝገብ፤ ዘለዓለም ክብረት፣ ተስፋዓለም ወልደየስና አስማማው ኃይለጊዮርጊስ በሌላ መዝገብ እንዲሁም አጥናፉ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀና ኤዶም ካሳዬ አንድ ላይ፣ ዘጠኙም ተጠርጣሪዎች ሦስት ሦስት ሆነው ቀርበዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነን ከሚሉ የውጭ ኃይሎች ጋር በሙሉ ሐሳብና በገንዘብ በመስማማት፣ ሕዝብን የሚያተራምስና አገርና መንግሥትን የሚያፈርስ ዘገባ በኢንተርኔትና በማኅበራዊ ድረ ገጾች ያልሆነ መረጃ ማስተላለፋቸውን ፖሊስ ለፍ/ቤቱ ገልጾአል፡፡ ፖሊስ ምርመራውን ባለመጠናቀቁም የ15 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቢጠይቅም የተፈቀደለት የ10 እና 11 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ነው፡፡ እስካሁን መንግስት በተጠርጣሪዎቹ ጉዳይ በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም፡፡

በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ፍርድ ቤት ቀረቡ

 April 28/2014

(አዲስ ጉዳይ) ፖሊስ ለምርመራ 10 ቀናት ጠይቋል ባለፈው ሳምንት ሚያዝያ 17 እና 18 ቀን 2006 ዓ.ም በፖሊስ ቁጥጥር ስር
የዋሉት 3 ጋዜጠኞች እና 6 ብሎገሮች ዕሁድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን
ፖሊስ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቆባቸዋል።

 በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በማዕከላዊ እስር ቤት የቆዩት ተጠርጣሪዎች ሰኞ ለፍርድ እንደሚቀርቡ የተጠበቀ ቢሆንም ባልተለመደ ሁኔታ ዕሁድ እንዲቀርቡ የተደረገ ሲሆን የክሱም ሃሳብ በአጭሩ “ሀገሪቱን በሶሻል ሚዲያ ለማተራመስ ራሱን የመብት ተሟጋች ነኝ ብሎ ከሚጠራ የውጭ ኃይል ጋር በሃሳብም በገንዘብም ተረዳድተውና ተስማምተው የብጥብጥ ቅስቀሳ ለማነሳሳት አቅደው ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል” የሚል ነው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ተመሳሳይ ክስ የቀረበባቸው ቢሆንም በ3 የተለያዩመዝገቦች ተከፋፍለው ነው ፍርድ ቤት ቀረቡት፡፡ የአዲስጉዳይ ጋዜጠኛ አስማማውኃይለጊዮርጊስ፣ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር የሆነው ዘላለም ክብረት እና የቀድሞው አዲስ ነገር ጋዜጠኛና በአሁኑ ወቅት በአዲስ ስታንዳርድ መጽሔት ላይ የሚሰራው ተስፋለም ወልደየስ በመዝገብ ቁጥር 118722 የተጠቃለሉ ሲሆን፤ አጥናፉ ብርሃነ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና ኤዶም ካሣ በመዝገብ ቁጥር 118721 እንዲሁም በፍቃዱ ኃይሉ፣ ማህሌት ፋንታሁን እና አቤል ዋበላ በመዝገብ ቁጥር 118720 የተካተቱ ተጠርጣሪዎች ናቸው።


በመዝገብ ቁጥር 118721 እና መዝገብ ቁጥር 118722 የተካተቱት ተጠርጣሪዎች ለሚያዝያ 29 ቀን 2006 ተቀጥረዋል።ጉዳያቸው በመዝገብ ቁጥር 118720 የተካተተው ተጠርጣሪዎች ደግሞ ለሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓመተምህረት ተቀጥረዋል።

ጥቂት ስለ ማዕከላዊ!

April 28, 2014
አክመል ነጋሽ
ማዕከላዊን በከፊል አውቀዋለሁ፡፡ ከትናንት በስቲያ ሰባት የሚሆኑ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮችና አክቲቪስቶች መታሰራቸውን ተከትሎ ወደ ማእከላዊ መወሰዳቸውን ሰምተናል፡፡ በቀጣዮቹ ቀናት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ጨለምተኛ ልመስል እችል ይሆናል፤ እውነታው ግን ይኸው ነው፡፡
መጀመሪያ ክሱ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው አጓጊ ጥያቄ ነው፡፡ ይህን ለማወቅ ወሳኝ ፍንጭ የሚሰጠው የቤት ፍተሻው ነው፡፡ የታሰሩትን ሰዎች ቤት የሚፈትሹት ፖሊሶችና መርማሪዎች ቤቱን የሚፈትሹት ለጥቂት ሰዓታት (ቢበዛ ለሁለት ሰዓታት) ከሆነና በጣም ብርበራ ያልበዛበት ከሆነ አለቆች በጸረ ሽበር ሕግ ለመክሰስ እንዳላሰቡና አስፈራርተው ብቻ በዋስ ለመልቀቅ እንዳሰቡ ፍንጭ ይሰጣል፡፡ በተቃራኒው ፍተሻው በትንሹ ከስድስት ሰዓታት በላይ የሚረዝምና በቤቱ የተገኘውን ወረቀት፣ መጽሐፍ፣ ሲዲ፣ ኮምፒውተርና ሞባይሎች ምንም ሳይስቀሩ ሰብስቦ የሚያስኬድ ከሆነ ጉዳዩ በጸረ ሽብር ሕግ ከመክሰስ ጋር የተያያዘ እንደሆነ መጠርጠር ያሻል፡፡
ይሄ የቤት ፍተሻ የቤቱን ኮርኒስ መቅደድና ወለሉን እስከመቆፈር ይደርሳል፡፡ በዚህ ጉዳይ ውስጥ ዋናው ግንዘቤ መወሰድ ያለበት ነገር ሰዎቹ የሚያስሩት ማስረጃ በመያዝ ሳይሆን፤ ማስረጃ ሊሆን የሚችል ማንኛውም ነገር በፍተሻው አግኝቶ እሱን ቀባብቶና አሳምሮ መክሰስ መቻላቸው ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ መርማሪዎች፣ አቃቢ-ሕጎችና ተሰያሚ ዳኞች ተገናኝተው እንዲያወሩ ስለሚደረግ ነገሩን ፍርድ ቤት አድርሶ የሚፈለገውን ውሳኔ ለማስወሰን መንገዱ ጨርቅ ነው፡፡
በማእከላዊ ከተወሰዱ በኋላ ቢያንስ ለሦስት ቀን ያህል ከቤተሰብም ሆነ ከማንም ጋር መገናኘት የማይተሰብ ነው፡፡ ይህ ታሳሪዎቹንም ሆነ ቤተሰቦቻቸውን የበለጠ ለማደናገጥና የሥነ-ልቦና ጫና ውስጥ ለመክተት ወሳኝ ነው፡፡ ታሳሪዎቹ በቀጥታ የሚወሰዱት ‹‹ጣውላ ክፍል›› ወደሚባሉ የእስር ክፍሎች ነው፡፡ በዚህ ክፍል የሚታሰሩ ሰዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ለ15 ደቂቃ ያህል የሚቆይ ጸሀይ መሞቂያና መጸዳጃ ቤት መሄጃ ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡ እነዚህ ከፍሎች በግምት አራት በአራት ስፋት ያላቸውና ወለላቸው ከጣውላ ጣሪያና ግድግዳቸው ከኮንክሪት የተሠራ ሲሆን፤ ቦታው ሻል ካለው የእስር ኮሪደር ‹‹ሸራተን›› እጅግ ያነሰ ነጻነት ያለውና፤ በጣም ከባሰው ጨለማ ክፍል ‹‹ሳይቤሪያ›› የተሻለ ቦታ ነው፡፡ ምርመራው ለእስር በገቡበት ምሽት ይጀመራል፡፡ የኢ-ሜይልና ሌሎችም አካውንቶች ፓስወርዶች በግድ እንዲሰጡ ይደረግና የኮምፒውተር ሀ ሁ በማያውቁ ‹‹መርማሪዎች›› አካውንታቸው ይበረበራል፡፡
ከዚሁ ጎንለጎን ቀለል ያለ ምርመራና ጥያቄና መልስ ይካሄዳል፡፡ በቀጣዮቹ አምስት እና አስር ቀናት ‹‹ጠቃሚ ውጤት በምርመራ አላገኘንም›› ብለው ካሰቡ ወደ ሌላኛው የእስር ክፍል ወደ ‹‹ሳይቤሪያ›› ያዘዋውሯቸዋል፤ በዚህ ወቅት የምርመራ ስልቱና አጠቃላይ ሁኔታውም ይለወጣል፡፡ ታስረው መቆየት ‹‹አለባቸው›› ወይም ‹‹የለባቸውም›› የሚለውን የሚወስኑት በዚህ ጊዜ ነው፡፡ ውሳኔው ይፈቱ ከሆነ ወደ ‹‹ሸራተን›› የእስር ክፍል ያዘዋውሯቸዋል፡፡ ይህ ከቤተሰብ ጋር መገናኘት የሚያስችል የእስር ቦታ ሲሆን፣ በጊቢው ካሉት የእስር ክፍሎች ሁሉ የተሻለ አንጻራዊ ‹‹ነጻነት›› ያለው ነው፡፡
በጥቅሉ ሳይቤሪያ ከአንድ ሜትር ስኩዌር ብዙም የማይበልጥ፣ ጨለማ፣ በጣም ቀዝቃዛና አምስት ቀናት ቢቆዩቡት መላው አካልን ወደ አመድነት (ነጭነት) የሚለውጥ ዘግናኝ ቦታ ነው፡፡ በዚህ እስር ክፍል ውስጥ ሰዎች የሚታሰሩት ያላደረጉትን ነገር አድርገናል ብለው እንዲያምኑ ወይም የያዙትን ‹‹ሚስጥር›› ‹‹እንዲያወጡ›› ነው፡፡ በዚህ ክፍል የሚታሰሩ እስረኞች አንዳንዴ ያልተቋረጠና እስከ 14 ሰዓት የሚደርስ ምርመራ በፈረቃ በሚቀያየሩ መርማሪዎች ይደረግባቸዋል፡፡ በምርመራው እንደ እስረኛው ሁኔታ የሚላላና የሚጠነክር ድብደባና ቶርች መጠቀም የተለመደ ‹‹አሠራር›› ነው፡፡ ቶርች የተደረጉ ሰዎች ቁስላቸው እስከሚያገግም ከቤተሰብም ሆነ ጠበቃ ጋር ማገናኘት የማይታሰብ ነው፡፡ በእነዚህ ሁሉ ወቅቶች ቤተሰብ ምግብ ለማድረስ፣ ጠበቆች ደንበኞቻቸውን ለማግኘት የሚደርጉት ጥረት ውጤት አልባ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ይቺ ነች፡፡

Sunday, April 27, 2014

ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) የተሰጠ መግለጫ

April 26/2014

የጋዜጠኞቹና የአክቲቪስቶቹ እስር አሳሳቢ ነው፡፡

ትላንት ሚያዝያ 17 2006 አመሻሽ ላይ ዞን 9 በተሰኘ ድረ ገጽ (ብሎግ) ላይ በሳል ፖለቲካዊና ማህበራዊ  ትችቶችን በማቅረብ ከሚታወቁት ፀኀፍት መሀከል 7 ቱ (ማህሌት ፋንታሁን በፍቃዱ ሀይሉ ናትናኤል  ፈለቀ ዘላለም ክብረት አጥናፍ ብርሀነ አቤል ዋበላ ኤዶም ካሳዬ ) እና የአዲስ ነገር ባልደረባ የነበረው  ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ይታወቃል፡፡

ግለሰቦቹ በተለያየ ቦታ በየስራ ገበታቸዉ ላይ እያሉ ሁሉም በተመሳሳይ ሰ ዓት በፀጥታ ሀይሎች ተይዘዉ በማዕከላዊ ምርመራ ማዕከል ታስረዉ የሚገኙ ሲሆን፤ የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስሩ  በደንብ የታሰበበት ነበር፡፡  የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ታሳሪዎቹ ታሰሩ ከተባለበት ሰዓትና ደቂቃ ጀምሮ የሚገኙበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለማጣራት አየሰራ ሲሆን ፤ እስካሁን በሰበሰበዉ መረጃ መሰረት ልጆቹን ለእስር የሚያበቃ ምን  አይነት ማስረጃ እንደተገኘባቸው ለማወቅ አልቻለም፡፡

ሆኖም ግን ለእስር ከመዳረጋቸው በፊት ከመንግስት ሲርስባቸዉ በነበረዉ ህገወጥ ድርጊቶች ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስራቸዉን ካቋረጡ በኋላ በቅርቡ ወደ ስራ መመለሳቸዉን ይፋ አድርገው እንደነበር  ከድረገጻቸው ላይ ለመረዳት ችለናል፡፡ ይህ ጉዳይ እስሩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎብናል፡፡
ስለሆነም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መንግስት ታሳሪዎቹን ለማሰር ያበቃዉ ተጨባጭ ማስረጃ ካለ  ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ ያ ካልሆነ ግን እስረኞቹን በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ  እናሳስባለን፡፡

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ

አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

Six bloggers, journalist detained in Ethiopia on Friday

April 26, 2014
One journalist and six bloggers in Addis Ababa, Ethiopia are detained last night (Friday April 25, 2014), their family members and colleagues reported.
Tesfalem Weldeyes, freelancer for the weekly English newspaper, Addis Fortune, and Addis Standard magazine was escorted from his house around known as ‘Gotera condominium’ by the police, according to his neighbor with whom he left his house key.
“Late this evening I got a massive knock at my door. I opened and the guy by the door screamed at me “Tesfalem is calling for you outside”. I thought maybe he got into accident and run out to his place. He was surrounded by about seven people dressed civil and two policemen. They are carrying some clothes in a plastic bag and papers in another. ‘You have a spare key to his house. If anything is taken from his place you will be accountable,’ one of them screamed at me,” his neighbor wrote on her facebook wall late last night.
This morning photographs of six bloggers, known as writers of Zone Nine who criticize the government, published on social media by their friends indicating that they all are also arrested last night.
zonenine
Campaign for the release of the detainees has also started on social media by their friends. They indicated that bloggers and activists arrested last night are: Befekadu Hailu Expert at St. Mary’s University College, Natnail Feleke, HR management officer at Construction and Business Bank; Mahlet Fantahun, Data Officer, Atnaf Berhane IT Services professional, Zelalem Kibret, Lecturer at Ambo University and Abel Wabella, a Tooling Engineer at Ethiopian Airlines.
According to relatives the detainees are now held in Maakelawi, a prison in Addis Ababa known mostly for interrogating detainees. Neither the police nor the government officials have made any statement on the issue to the media so far about the arrest of the journalists, bloggers and activists. Meanwhile the detainees are expected to appear to court by Monday.
“Tesfalem like anybody else have opinions…but he has never let them influence his articles and he always reached out to all parties in order to include a wide range of views; I remember how hard he fought to get into the ruling party’s latest congress. I am absolutely uninterested to hear what trumped up charges the government has to justify his arrest, he should be freed immediately!,” said former Associated Press correspondent in Ethiopia commenting on his facebook wall.
Another relative named Adam Brookes also wrote describing Tesfalem as “an independent journalist, a modest, much-loved individual who survived the 2010 Kampala bombings, and who reports with professionalism and insight on EPRDF rule in Ethiopia.”
In a related development one of the emerging opposition party known as blue Party has called for a public rally in Addis Ababa for tomorrow (Sunday).
“…the most significant human rights problems are: freedom of expression, freedom of association, illegal detention; displacement of certain ethnic groups, politically motivated trials; harassment; intimidation of opposition members and journalists, and continued restrictions on print media are just a handful of the violations.”
“Blue Party does not believe that the Ethiopian regime is willing to facilitate a political atmosphere that will provide freedom for the people. Therefore we believe we have to fight for it,” the party said in its statement a few minutes ago.
newbusinessethiopia

Saturday, April 26, 2014

ሰበር ዜና • የአዲስ ጉዳይ ጋዜጠኛ በፖሊስ ታሰረ

April 26/2014

• ምክንያቱ እስካሁን ግልጽ አልተደረገም
የአዲስጉዳይ መጽሄት ከፍተኛ አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ እስካሁን ለመጽሔቱ ባልደረቦች ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ዛሬ ሚያዝያ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ማለዳ በፖሊስ ታስሯል።
በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ በከፍተኛ አዘጋጅነት የሚሰራው ጋዜጠኛ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው ዛሬ ማለዳ ከቤቱ ሲወጣ በመኪና ሲጠብቁት በነበሩት ፖሊሶች ሲሆን በአሁኑ ወቅት በማዕከላዊ ፖሊስ ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
አዲስ ጉዳይ ስለባልደረባው የእስር ምክንያትና ሁኔታ ለማጣራት ባደረገው ሙከራ የተገነዘበው ነገር ቢኖር ጋዜጠኛ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ ፖሊስ ክበብ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ወጥቶ በሰላም ወደስራው በመሄድ ላይ ሳለ በመኪና ቆመው ሲጠብቁት በነበሩትና ከማዕከላዊ ምርመራ እንደመጡ በተናገሩ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር መዋሉን ብቻ ነው።
ቤተሰቦቹ እንደተናገሩት የፖሊሶቹ ቁጥር 9 የሚደርስ ሲሆን ከመካከላቸው አንዱ ብቻ ነው ዩኒፎርም ያደረገው። በብርበራው ወቅት ፖሊሶቹ ወደጋዜጠኛው ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት ማንም ሰው እንዳይገባም ሆነ እንዳይወጣ ከልክለዋል ብለዋል።
የአዲስ ጉዳይ ባልደረቦች ከቤተሰቡ እንደተገነዘቡት ከሆነ ጋዜጠኛ አስማማውን ፖሊሶቹ ማለዳ ላይ ይዘውት ከሄዱ በኋላ ረፋድ ላይ መልሰው ወደቤቱ ይዘውት መጥተዋል። ከዚያም መኖሪያ ቤቱን ከማለዳው 4 ሰዓት እስከ10 ሰዓት ድረስ ሲበረብሩ የቆዩ ሲሆን አራት ፌስታል የተለያዩ ጋዜጦችና መጽሄቶችና ጋዜጠኛው የሚጠቀምበትን ላፕቶፕ ይዘው ሄደዋል።
በብርበራው ወቅት ቤተሰቦቹ ለጋዜጠኛው ምግብ ለመስጠት የጠየቁ ቢሆኑም ፖሊስ ግን ፍቃደኛ አለመሆኑን ተናግረዋል። ጋዜጠኛ አስማማው ብርበራው በተካሄደበት ወቅት በፖሊሶች በካቴና ታስሮ ቤት ውስጥ ነበር ብለዋል ቤተሰቦቹ።
በመጨረሻም ፖሊሶቹ ለምርመራ ወደማዕከላዊ ይዘውት እንደሄዱ ለቤተሰቦቹ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኛው በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ አዲስ ጉዳይ የደረሰው መረጃ የለም።
አዲስ ጉዳይ ጋዜጠኛውን ፖሊስ አነጋግሮ ይለቅቀዋል የሚል ተስፋ ይዞ እስካሁን ሰዓት ድረስ ቢጠብቅም የጋዜጠኛው ከእስር መለቀቅ አጠራጣሪ በመሆኑ ይህንን ሰበር ዜና ይፋ አድርጓል።
ጋዜጠኛ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ በሮዝ መጽሄት (በአሁኑ አዲስ ጉዳይ) ከቅጽ 1 ቁጥር 1 ህዳር 1999 ዓ.ም የመጀመሪያ እትም ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከ7 ዓመታት በላይ በጋዜጠኝነት ሙያው በመጽሄቱ ከፍተኛ አዘጋጅነት እያገለገለ የሚገኝና ጋዜጠኝነትን የሚሰራ የአዲስ ጉዳይ ጋዜጠኛ ነው።
አዲስ ጉዳይ በእስር ላይ የሚገኘውን የመጽሄቱን ከፍተኛ አዘጋጅ የእስር ምክንያት ከሚመለከታቸው አካላት በማጣራት ተከታትሎ መረጃውን ለህዝብ የሚያቀርብ መሆኑን ለማሳወቅ ይወድዳል።

የዘረኞች ነውር በድሬዳዋ

April 26/2014

ድሬዳዋ የኢትዮጵያዊያን ከተማ ነበረች። ኢትዮጵያዊያን የጎሳቸውን አጥር አፍርሰው በኢትዮጵያዊነታቸው ብቻ ለረዥም ዘመን አብረው በድሬዳዋ ኑረዋል። በዚህ ሁኔታ የሚኖረው ህዝብ አብሮ ስቆ ፤አብሮ ተደስቶ፤ ያለው ለሌለው አካፍሎና ተቻችሎ መኖርን የሚያውቅ ነበር። ዛሬ ግን ያች ቀድሞ የምናውቃት ድሬዳዋ ተረት ሁናለች። ሁሉ ስቆና ተደስቶ የሚኖርባት ከተማ ሳትሆን በየወቅቱ በእሳት እንድትጋይ ሁና ብዙዎች እንባቸውን በመዳፋቸው የሚያፍሱባት ከተማ ሁናለች። ብዙዎች የንግድ ሥፍራቸው ተቀነባብሮ በተነሳ እሳት በመጋየቱ ባዶ እጃቸውን ቀርተዋል። ልጆቻቸውም ድሃ አደግ እንዲሆኑ ሁኗል። ይባስ ብሎ ንብረቶቻቸውን ከእሳት ቃጠሎ ለመከላከል እሳቱን ለማጥፋት የተነሱ ዜጎች በአሸባሪነት ተከሰው ህወሃቶች “ ፍርድ ቤት” ብለው ወደ ሚጠሩት ሥፍራ እንዲቀርቡ ሁኗል።
ገ/መድህን ገ/መስቀል፤ ቢኒያም ጌታቸው፤ መቻል አብራር፤ ምትኩ ውብየ፤ ኢዮብ ገብሬ፤ ሃቢብ ሸምሱ፤ ለዒላ ዓሊ ፍትህን በማያውቀው በህወሃት ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ከእነዚህ ውስጥ ከገ/መድህን ገ/መስቀል በቀር ሌሎቹ የዋስ መብት ተነፍጓቸው ወሂኒ እንዲቆዩ ተደርጓል። ገ/መድህን ገ/መስቀል በምን ሁኔታ ከሌሎቹ ተለይቶ “ነፃ ሰው” ሊባል እንደቻለ የሚያውቅ የለም። ብዙ ሰዎች ግን በትግራይ ተወላጅነቱ አፍቃሬ ህወሃት ” ተደርጎ እንዲታይ ለማድረግ ነው ይላሉ። ህወሃት በልዩ አፈና የራሱ ዋሻ ያደረገውን የትግራይ ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ለማቆራረጥ እንዲህ አይነት ያፈጠጠና ያገጠጠ የዘር መድልዎ ሲያደርግ የመጀመሪያው አይደለም። ድህረ ምርጫ 97 ከአዲስ አበባ ከተማ ተግዘው ወደተለያየ ማጎሪያ ከተላኩት በርካታ ሺዎች ውስጥ የትግራይ ተወላጆችን መርጦ “እናንተ ነፃ ናችሁና ወደ ቤታችሁ ሂዱ” ብሎ እንዳሰናበተ የማያውቅ የለም። የዘረኞቹ ቁንጮ መለስ ዜናዊ በህይወት በነበረበት ወቅት ሲደረግ የነበረውና ከህልፈቱም ቦኋላ ቀጥሎ ያለው የህወሃት የዘረኝነት መገለጫ አንዱ መንገድ ይሄው ነው። በትግራይ ወጣቶች የህወት መስዋዕትነት ለስልጣን በቅተው እራሳቸውን ያነገሱ የህወሃት መሪዎች ትግሬን ነፃ ማውጣት ማለት ከሌላው ወገኑ ጋር ውሎ አድሮ ደም የሚያቃባ አድልአዊነት እንዲህ በአደባባይ መፈጸም ነው ብለው ያምናሉ። እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለቺው እንስሳ ለህወሃቶች እንዲህ አይነት ዘረኝነት ወደፊት ሊፈጥር የሚችለው አደጋ አይታያቸውም ወይም ስለርሱ ማሰብ አይፈልጉም። ።ከአማራና ከአፋር የሚዋሰኑትን ለም ቦታዎችንና በበከርሰ ምድር ማዕድን የከበሩ ሥፍራዎችን ቀምተው ወደ ክልላቸው ሲጠቀልሉና ነዋሪውን በማፈናቀል የቀድሞ ታጋዮቻቸውን ሲያሰፍሩባቸው አልሰቀጠጣቸውም። ወያኔ የራሱ ዋሻ አድርጎ በሚቆጥረው የትግራይ ክልል ውስጥ እያደረሰ ያለው ስቃይና መከራ የክልሉን ግንብ ጥሶ በመላው አለም በመሰማት ላይ ባለበት በአሁኑ ወቅት በተለያየ የአገሪቱ ክፍል ተበትኖ የሚኖረውን ጥቂት የትግራይ ተወላጅ ተጠቃሚ በማድረግ የትግሬ ነጻ አውጪ ለመምሰል የሚደረገው ጥረት በትግራይ ህዝብ ዘንድ ሳይቀር እየተወገዘ ነው። ዘረኞቹን የህወሃት መሪዎች እረፍት የነሳውና እንዲቅበዘበዙ እያደረገ ያለውም የዚህ ዘረኛ አላማቸው የራሴ ነው በሚሉት የቀድሞ ምሽጋቸው ሳይቀር እየታወቀ መምጣቱ ነው።
ዛሬ ከትግራይ ጀምሮ በመላው አገሪቱ ማለት ይቻላል የወያኔን ዘረኝነትና ዘረፋ የሚቃወሙ ሁሉ ሥልጣንን በተቆጣጠሩ በእነዚህ ዘረኞች እጅ የመከራ ፅዋቸውን እየተጎነጩ ነው። የአሬና አመራርና አባላት ብቻ ሳይሆን በቤተሰቦቻቸው ጭምር ላይ ትግራይ ውስጥ እየተፈጸመ ያለው ግፍ የሚያረጋግጠው ይህንኑ ሃቅ ነው። የታገልነውና የደም መስዋዕትነት የከፈልነው እናንት ጥቂት ዘረኞችንና ቤተሰቦቻችሁን በራሳችን ላይ ለማንገስ አልነበረም እያሉ ያሉ እንደነ አቶ አሰግድ ገብረስላሴ ያሉት ልጆቻቸው ጭምር በጎዳና እየተደበደቡ እስር ቤት ሲወርወሩ ነፍሳቸውንና ስጋቸውን ለህወሃት መሪዎች ያስረከቡት ጥቂት የትግራይ ተወላጆች ግን ከዘረፋ በተገኘ ሃብት ቢጠሩዋቸው የማይሰሙ ዲታ ሆነዋል። በልማትና እድገት ሥም በጋምቤላ ድሆችን ከኖሩበት መሬት አፈናቀለው እና ሜዳ ላይ በትነው መሬት ከተቀራመቱት ባዕዳን በቁጥር የሚበልጡት የዘረኞቹ ጋሻ ጃግሬ የሆኑ ትግሬዎች ናቸው። በአዲስ አበባ በዜጎች ደምና አጥንት ላይ የተገነቡ የትላልቆቹ ህንፃ ባለቤቶች የፋሽስቱ የህወሃት አባላት ናቸው። የአገሪቷን የንግድ ማዕከል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተቆጣጥረው በዚያች አገር የሚዘባነኑት እነዚሁ በትግራይ ሥም የሚነግዱ ቡድኖች መሆናቸውን ህዝቡ የሚያውቀው እውነት ነው።ለትግራይ ነፃ አውጪዎች ሲባል የመከራውን ፅዋ በመጎንጨት ላይ ያለው ህዝብ ቁጣ የዶፍ ዝናብ ሊጥል የተዘጋጀ ሰማይን ይመስላል።ያ ቁጣ የፈነዳ ግዜ የሚያቆመው ምዳራዊ ኃይል እንደሌለ በሚቾት የደነዘዘው የህወሃት አመራር የተገነዘበው አይመስልም።
ስለዚህ ዘረኛና ወንጀለኛ ቡድን እጅግ የሚያሳዝነው ሌላው ነገር 23 አመት ሙሉ የአገሪቱን በትረ ሥልጣን እንዳሻው እያሽከረከረም ቢሆን ከመንደርተኝነት ስሜት ሊላቀቅ አለመቻሉ ነው። ዛሬም እንደትናንቱ ትግራይን መደበቂያ ዋሻ ፤ ዞሮ ዞሮ መግቢያ ለማድረግ የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም። ቅድሜ ወያኔ የአገሪቱ ህዝብና መንግሥት ንብረት የነበሩ ንግድ ድርጅቶችን በመውረስ የደለበና ዛሬ በአገሪቱ ብቸኛ የሥራ ተቋራጭ፤ ዕቃ አቅራቢና አገልግሎት ስጪ የሆነው ኢፌርት በስም የትግራይ ህዝብ በተግባር ግን የህወሃት ባለሥልጣኖች የገቢ ምንጭ መሆኑን ያልተረዳ የለም።መመኪያ ዋሻየ ከሚለው የትግራይ ህዝብ መነጠሉን እየተረዳ የመጣው ይሄ ፋሽስታዊ አስተሳሰብ ያለው ነውረኛ ቡድን ሰሞኑን ሌላ አሳፋሪ ድርጊት እየፈፀመ ነው። ”ከትግራይ ህዝብ ጋር መታረቅ” የሚል ዜማ ይዞ ብቅ ብሏል። ህወሃት የነፃ አውጪ ስሙን እንኳን ሳይቀይር የ80 ሚሊዮን ህዝብ ገዢ እኔ ነኝ ብሎ ድርቅ ማለቱን እናውቃለን። ስማችሁን ቀይሩና አገሪቷን ግዙ ቢባሉም በጀ አላሉም። ይሄን ስም ይዘው በትግራይ ህዝብ ላይ ተንጠላጥለው አገሪቷን ሲዘርፉ ኖሩ። በዚህም ዘረፋ ትናንት ወደ ሥልጣን ሲመጡ ሲሙኒ እክሳቸው ውስጥ ያልነበራቸው ዛሬ በዓለማችን ከሚታወቁ ሃብታሞች ተርታ ለመግባት ችለዋል። መሪያቸው የነበረው መለስ ዜናዊ 3 ቢሊየን ዶላር ባለቤት በመሆን ከዓለም ሃብታም መሪዎች ተርታ ስሙ የሚነሳ ሁኗል። ሌሎችም እንደየአቅማቸው በሚሊየን የሚቆጠር ንብረት ዘርፈው ኢንቨስተሮች እኛ ነን ብለዋል። በትግራይ ነጣ አውጪነት ሥም ተደራጅተው የብዙ ንፁሃን ዜጎችን ደም አፍሰው፤ ብዙዎችን ለስደት ዳርገው፤ የብዙ ዜጎችን ቤተሰብ በትነው ሲያበቁ የትግራይን ህዝብ ይቅርታ እንጠይቅ ተባብለው ትግራይ ወርደዋል። ይሄን የሰማ ሌላው ህዝብ ሊሰማው የሚችለውን ቁጣ የትግራይ ህዝብ ያጣዋል ብለን አናስብም።ሌላው በተበደለ፤ ሌላው በተገፋ፤ ሌላው ጦሙን ባደረ፤ ሌላው ለስደት በተዳረገ የትግራይ ህዝብ ይቅርታ የሚጠየቅበት ምክንያት ምን እንደሆነ ግልፅ አይደለም። ለማንኛውም የትግራይ ህዝብ የህወሃት ዋሻና መደበቂያ አልሆንም ብሎ እንቅስቃሴ ጀምሮአል። ይሄ እጅግ የሚደገፍና ግዜው የሚጠይቀው የሞራል ግዴታም ነው። በትግራይ ሥም ተደራጅተው “ለትግሬ ብለን” እያሉ የንፁሃንን ደም ሲያፈሱ እና ቤተሰብ እየበተኑ ሜዳ ላይ ሲጥሉ እያዩ ዝም ማለት የግፉ ተባባሪ ያደርጋል እንጂ ከደሙ የሚያነፃ አይሆንም። ለዚህም ነው የትግራይ ህዝብ ወያኔ በስሙ መነገዱን እንዲያቆም ጠመንጃ ይዞ እስከመፋለም የተነሳው። የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት /ደሚት/ የትግል አላማ ይህንን ወያኔ የፈጠረውን ጥላቻ የመስበር ተልዕኮ ያለው ነው። የትግራይ መሬትና የትግራይ ህዝብ ከእንግዲህ የወንጀለኛው ህወሃት መደበቂያ ዋሻ አይሆንም።
ህወሃት ከህዝብና ከአገር ለመታረቅ ከፈለገ በትግራይ ሥም ላለፉት 23 አመታት ለፈጸመው ወንጀል ይቅርታ ፍለጋ ትግራይ መንደሮች ድረስ መዝለቅ አይጠበቅበትም። ከትግራይ ውጪ ተጀምሮ ትግራይን ባጥለቀለቀው ኢፍትሃዊነት፤ ግፍና መከራ ጸጸት ከተሰማው ሥልጣን ለመልቀቅ መዘጋጀትና ለኢትዮጵያዊያን ለማስረከብ በመወሰን እዚያው ምንሊክ ቤተመንግሥት ሆኖ አዋጅ ማስነገር ይችላል። ለዚህ ዝግጁነት ተግባራዊ እርምጃ ለምሳሌ የታሰሩትን የፖለቲካ እስረኞች፤ ጋዜጠኞች፤ የሃይማኖት መሪዎችን መልቀቅ፤ የሥልጣን ማስጠበቂያ አድርጎ በዘረኝነት መስፈርት የገነባውን የአፈና ተቋማት ማፍረስ፤ ህዝብ ሃሳቡን በነጻነት የሚገልጽበትንና መሪዎቹን በነጻነት የሚመርጥበትን ዕድል በመፍቀድ ማረጋገጥ ይችላል።
ይህ እስካልሆነ ድረስ ከአደዋ ወይም ከሸሬ የወያኔን ዕድሜ የሚያራዝም ይቅርታ ጨርሶ የሚታሰብ አይደለም። በ23 አመት የሥልጣን ዘመን የተገኘው ዘረፋ አልበቃ ብሎ ሥልጣን ላይ ለመንጠልጠል መንከላወስ ውጤቱ ሁሉንም ማጣት ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!