Tuesday, January 29, 2013

ሕወሐት ለሁለት ተሰነጠቀ፤ ወረቀት ለአባለት ተበተነ
ከኢየሩሳሌም አርአያ
ዛሬ በመቀሌ ለአባላ ትና አልፎም ለህዝቡ በተበተነ የትግርኛ ፅሁፍ እነ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ፀጋዬ በርሔ ከነባለቤታቸው እንዲሁም ሌሎች ከድርጅቱ እንዲባረሩTigray People Liberation Front Split በተበተነው መግለጫ ተጠቁሞዋል። በመግለጫው፥ ከጀርባ አሉ የተባሉትና « የዚህ መኅንዲስ» ተብለው የተፈረጁት ስብሃት ነጋ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተባሉት መካከል በዋነኛነት ተፈርጀዋል። እነ ቴውድሮስ ሃጎስ፣አዜብ መስፍንና በረከት እጃቸው እንዳለበት የተነገረለት ይኸው መግለጫ ተከታዩን ይመስላል፤
«ተቆርቋሪ ለሆናችሁ የትግራይ ተወላጆ በሙሉ፤
«ድርጅትህ ሕወሐት እስከ ዛሬ ታግላ እዚህ ደረጃ አድርሰሃለች። በተለይም የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪ የነበረው ባለ ራዕይው መሪህ በቅርብ ጊዜ አጥተኽል።
ዛሬ እነዚህን ደካማ ጐኖች ተጠቅመው ለጠላት አሳልፈው ሊሰጡህ የሚፈልጉ ያውም ደግሞ የእኔ የምትላቸው ጅቦች ተነስተውብህ ይገኛሉ። ይህንን ግልፅ ለማቅድረግ አሁን በቅርብ ጊዜ በመቀሌ የድርጅቱ ማ/ኰሚቴ ስብሰባ አካሄደን ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ ነው እንግዲህ ተከታዩ ነገር የተነሳው። ይኽውም፥ እነ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ፀጋዬ ከሚስቱ ጋርና ሌሎችም ያሉበት ይህን አሉ፤
«ድርጅታችን ጨርሶ ተዳክሞዋል። እኛ የኢትዮጲያ ሕዝብ ትግል መስራች ሆነን ሳለ ወደኋላ ተገፍትረን በአንፃሩ ሌሎች ከእኛ ኋላ የተፈጠሩና ራሳችን ያሳደግናቸው ሲጠናከሩ ድርጅታችን ግን እየተዳከመ በመሄድ ላይ ነው። ባዛው መጠን ሕዝባችን እየተጎዳ ነው። ስለዚህ አሁን ካጋጠመን አደጋ መውጣት ካለብን ከድርጅቱ -የተወገዱትን ግን በመጥፎ ጎዳና ያልተሰማሩትን መልሰን ወደ ፓርቲው ማስገባት አለብን። ይህ ካልሆነ ግን የሕዝብ ትግል አውላላ ሜዳ ላይ ጅብ በልቶት ሊቀር ነው።» በማለት ከጠላቶቻችን ጋር እንታረቅ እያሉን ነው።
“ሕዝባችን አስተውል። በዚህ አይነት ዳግመኛ በድርጅታችን ተኃድሶ እንደሚያስፈልገን ነው የተገነዘብነው። በሚቀጥለው የካቲት ወር በሚካሄደው ጉባኤያችን ይህንን ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶና አጥርቶ (ውሳኔ አሳልፎ) እንደሚወጣና እነዚህንና መሰሎቻቸው ከሚያራምዱት አቋም ጋር ጠራርጐ እንደሚያስወግድልን ተስፋ እናደርጋለን። በዚህም እያንዳንዱ እንደከዚህ ቀደሙ የተለመደ አስተዋፅኦ (ሚና) እንደሚያበረክት አንጠራጠርም።
በተጨማሪ ከጀርባ ሆኖ የዚህ አፍራሽ ዋና ቀያሽ መሃንዲስ ስብሃት ነጋ መሆኑን ደርሰንበታል።”

Monday, January 28, 2013

ኢትዮጵያ በወታደራዊ እንቅስቃሴዎች እየታመሰች ነዉ::
ኢትዮጵያ ዉስጥ ዳር አገርም ሆነ መሀል አገር በየቦታዉ የሚታየዉ ወታደራዊ እንቀስቃሴ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱን አዲስ አበባና በየክልሉ የሚገኙ ወታደራዊ ምንጮቻችን ገለጹ። በተለይ የመለስ ዜናዊ ሞት ለህዝብ ይፋ ከሆነበት ግዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ ከደርግ ዘመን ወዲህ ታይቶ በማይታወቅ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እየታመሰች መሆኗን በየክልሉ የሚገኙ ዘጋቢዎቻችን የመከላከያ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ የላኩልን ዜና ያስረዳል።
ከሁለት ሳምንት በፊት ከ35 በላይ ታንኮችን የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ምስራቅ የአገሪቱ ክፍል የተጓዙ ሲሆን፣ ከአራት ቀን በፊት ደግሞ ከ30 ያላነሱ ታንኮች በከባድ ተሽከርካሪዎች ተጭነዉ ወደ ሰሜናዊዉ የአገራችን ክፍል ተጉዘዋል። ጠብ አጫሪዉ የወያኔ አገዛዝ የጦር መሳሪያዎችን ለምን በዚህ አይነት ፍጥነትና ብዛት እንደሚያንቀሳቅስ በትክክል ለማወቅ ባይቻልም በብዙ ምዕራባዉያንና የአገር ዉስጥ ወታደራዊ ጠበብቶች ግምት አገሪቱ ውስጥ በየክልሉ በሁሉም መስክ የሚታየው ህዝባዊ አመጽና አለመረጋጋት ወያኔን ክፉኛ ስላስደነገጠዉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዉን በወታደራዊ ሀይል ለመቆጣጠር የታለመ ሊሆን ይችላል ተብሎ ይታናል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ስርዐቱን በትጥቅ ትግል የሚፋለሙ ሀይሎች በተለይ በቅርቡ የተቋቋመዉ እራሱን “የግንቦት ሰባት ሀይል” ብሎ የሚጠራዉ የተለያዩ ሀይሎች ስብስብ ወያኔን ክፉኛ እንዳስደነገጠዉ ብዙ ለአገዛዙ ቅርበት ያለቸዉ ምንጮች በመናገር ላይ ናቸዉ።

Friday, January 18, 2013

ሰበር ዜና መንግስት በምስክር እጦት ጭንቅ ውስጥ ገብቷል፡፡ የብዙዎች ምላሽ ‹‹በሐሰት አንመሰክርም›› የሚል ሆኗል፡፡     
በእስር ላይ የሚገኙ መሪዎቻችን እና ሌሎች ወንድሞቻችንን በአሸባሪነት ከስሶ ሲያንገላታ የቆየው መንግስት በምስክር እጦት ችግር ውስጥ መግባቱ ታወቀ፡፡ መንግስት ኮሚቴዎቻችን ላይ በመሰረተው ክስ በሐሰት ሊያስመሰክራቸው ያዘጋጃቸው 197 (አንድ መቶ ዘጠና ሰባት) ሰዎች መኖራቸውን ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም የተገለጸውን ቁጥር ያህል ምስክሮች ማግኘት አልቻለም፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው ለምስክርነት የታሰቡት ብዙዎቹ ግለሰቦች ምስክር ለመሆን ፈጽሞ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ነው፡፡ መሪዎቻችን ባልዋሉበት እና በማያውቁት ወንጀል የከሰሳቸው መንግስት በየአካባቢው ‹‹ድጋፍ ይሰጡኛል፤ እተማመንባቸዋለሁ›› የሚላቸውን ግለሰቦች ለምስክርነት ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያደርግላቸውም በሐሰት አንመሰክርም የሚል ቆራጥ አቋም ማሳየታቸው ተሰምቷል፡፡
ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳቸውን የመብት ጥያቄዎች ለመንግስት እንዲያደርሱለት በአስር ጣቱ አምኖባቸው የመረጣቸው ኮሚቴዎቻችን እና ሌሎች ዳኢዎች መንግስት እውቅና ሰጥቷቸውና ስለ ሰላማዊነታቸውም በመንግስት ብዙሀን መገናኛዎች መስክሮላቸው፤ ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ድርድር ሲያደርጉ እንደቆዩ ይታወሳል፡፡ ሆኖም መንግስት የቀረቡትን የመብት ጥያቄዎች ለመመለስ አለመፈለጉና እነሱም ጥያቄዎቹ እንዲመለሱ ተደጋጋሚ ጥያቄ በማቅረባቸው ‹‹አሸባሪ›› የሚል ታፔላ ተለጥፎባቸው ከሐምሌ 2004 ጀምሮ በእስር እና ስቃይ ላይ የሚገኙት መሪዎቻችን ንጹህ መሆናቸውን የተረዱ ብዙዎች በሀሰት እነሱ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በቀጥታ መግለጽ ችለዋል፡፡
መንግስት ይህን የመስካሪዎች እምቢታ ተከትሎ አዳዲስ ምስክሮችን ለመመልመል ቀን ከሌት እየሰራ እንደሚገኝ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ የመንግስት ደህንነቶች ቁጣና ንዴት በተሞላበት መልኩ ሰዎችን ምስክር እንዲሆኑ በአካልም ጨምር እየሄዱ በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ደህንነቶቹ በአዲስ አበባ አንድ አንድ መስጊዶች በመገኘት ግለሰቦችን በግድ በመያዝ ምስክር እንዲሆኑ እየጠየቁ ሲሆን፤ ፈቃደኛ አልሆንም ያሉ ሰዎችንም ‹‹የማትመሰክር ከሆነ አንተን ነው የምንከስህ›› በማለት በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ፡፡ የሀሰት ምስክርነትን (ሸሀደተ ዙር) አስከፊ ወንጀልነት የተረዱ በርካታ ሙስሊሞች አሁንም በእምቢታቸው የዘለቁ ሲሆን፤ አሁንም ግን ጥቂት የማይባሉ ‹‹ተገደን ነው የምንመሰክረው›› የሚል ምላሽ እየሰጡ ያሉ ግለሰቦች በመኖራቸው ከዚህ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡና ከአስከፊው የሀሰት ምስክርነት መዘዝ እራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲጠብቁ አደራ እንላለን፡፡
አቡበከር ሲዲቅ (ረ.ዓ) የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ማለታቸውን ዘግበዋል፡- ‹‹የከባዶች ከባድ የሆነውን ሀጢአት አልነግራችሁንም›› እኛም ‹‹አዎ! የአላህ መልዕክተኛ እንዴታ!›› አልን፡፡ እሳቸውም ‹‹በአላህ ማጋራት (ሽርክ) እና ወላጅን ያለመታተዝ ናቸው›› አሉና ተደላድለው ከተቀመጡበት ድንገት ተነስተው እንዲህ አሉ ‹‹አዋጅ! ውሸት መናገር እና በሐሰት መመስከ›› እያሉ የሚያቆሙት አልመስልህ እስኪለኝ ድረስ ደጋገሙት ፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል

Thursday, January 17, 2013

‹‹አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም››
ሁለት ወቅታዊ ጉዳዮች
1. ከመለስ ሞት በኋላ መረጋጋት የተሳነው ኢህአዴግ ከበርካታ ችግሮች ጋር ፊት ለፊት ተፋጧል፡፡ ከችግሮቹ በከፊልም የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ …በረከት ስምኦን የነበራው ተደማጭነት እየተሸረሸረ ነው፣ የበረከት ባለቤት የበረከትን መፅሃፍ ለመሸጥ (ገዥ ፍለጋ) በየተቋማቱ እየተንከራተቱ ነው፤ አዲሱ ለገሰ የተደማጭነት መስመሩን ‹‹ኢህአዴግን ለማጠናከር›› በሚል ምክንያት ይበልጥ እያደረጀ ነው፤ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከቀን ወደ ቀን በህወሓት ውስጥ ተሰሚነቱ እየጨመረ ነው፣ በእርግጥም ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የአስጊ ህመም ችግር የሌለባቸው ተብለው የሚመደቡት ደብረፅዮን፣ አባይ ፀሀዬና ቴውድሮስ አድሃኖም ናቸው፣ አቦይ ስብሃት ነጋ ‹‹መፈንቅለ ፓርቲ›› በህወሓት ውስጥ ለማድረግ ቀን ከለሌት እያሴሩ ነው፣ ከሁለት ወርበኋላ የሚደረገው የኢህአዴግ ጠቀላላ ጉባኤ አዲስ ነገር ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል፤ ኦህዴድ በሹም ሽር ሊናጥ ነው፣ አለማየሁ አቱምሳ በሩቅ ምስራቅ ለሚከታተለው ህክምና እስከአሁን ያለውንም ሆነ በቀጣይ የሚያስፈልገውን ወጪውን እየሸፈነ ያለው ሼክ መሀመድ አላሙዲ ነው፤ ለምን? አለማየሁ የመንግስት ባለስልጣን ነው፣ በተጨማሪም ሆን ተብሎ በተሰጠው መርዝ ነው ታማሚ የሆነው የሚባለውን ወሬ ይዘን፣ ከዚህ ጀርባ ማን ነው ያለው? የሚል ጥያቄ መቀርቡ አይቀርም (የሰማሁት መረጃ ጆሮ ያቃጥላል) ግን ለምን? ኩማ ደመቅሳ መልካም አስተዳደር ባለማስፈንና ሙስናን መቆጣጠር ባለመቻል እየተወቀሰ ሲሆን፣ በተቃራኒው አባዱላ ገመዳ በኦህዴድ ውስጥ መረጋጋትን በማስፈንና ስራውን በብቃት በመወጣት በሚል ተመስግኗል፣ (የማኪያቬሊ ከፋፍለ ግዛ ማለት ይህ ይሆን?) በሚያዚያ ወር የሚደረገውን ምርጫ ተከትሎ የቱኒዝያንና የግብፅን መሰል ህዝባዊ አመፅ ይቀሰቀሳል በሚል አገዛዙ ፍርሃት አድሮበታል፣ 33ት ፓርቲዎች ነገ በምርጫው ላይ የሚኖራቸውን አቁም በሰማያዊ ፓርቲ ፅፈት ቤት ከጠዋቱ አራት ሰአት ላይ የፋ ያደርጋሉ (በእርግጥ የደረሱበት ውሳኔን ብግሌ ትክክል ነው ብዬ አምናለሁ፣ ከዚህ ውጪም ገዥው ፓርቲን ለድርድር የሚያስገድድ ዕድል የላቸውም)፣ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ኦስትሪያዊውን አገር ጎብኚ ማን ገደለው? ለምን ተገደለ? የደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት ድራማስ በማን የተቀነባበረ ነው? ኃላፊነቱንስ ማን ነው የሚወስደው? የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ¬¬‹‹ለሽብር ድርጊት ሊውል ሲል ደረስኩበት›› በማለት ከተቀበረበት እንዳወጣው የነገረንን የጦር መሳሪያ ማነው የቀበረው? ይህ መሳሪያስ በእነማን የክስ መዝገብ ላይ ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ ነው የታቀደው? በቀጣይስ የቦንብ ፍንዳታ በየትኛው ከተማ፣ መቼ፣ ስንት ሰዓት ላይና በምን ሁኔታ ይደርስ ይሆን? …ይህኛው መንገድስ የት ድረስ ያስኬዳል? ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄትን ማፈኑስ ለምን አስፈለገ?
2. በሽብርተኝነት የተከሰሱትን የህዝብ ሙስሊም መሪዎችን በይቅርታ ለመፍታት መንግስት የማጭበርበሪያ ስልቱን እየተጠቀመ ነው፡፡ በዕለት ሀሙስ ጥር 2 ቀን 2005 ዓ.ም በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳቅ ይመሩ ከነበሩት ሽማግሌዎች ውስጥ የተዘጋጀ ሶስት ሰዎች ያሉት አንድ ቡድን በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝቶ ነበር፡፡ ከቡድኑ አባላት ፓስተር ዳንኤል እና ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያስ ለታሳሪዎቹ እንዲህ የሚል የማጭበርበሪያ መደራደሪያ አቅርቦ ነበር፡- ‹‹ጉዳያችሁ በፍርድ ቤት እየታየ ነው፤ ስለዚህም ክሱ አሁን ባለበት ደረጃ ሊቋረጥ አይችልም፡፡ እናም ክርክራችሁን አቋርጡና ጥፋተኛ ነን በሉ፣ ከዛም ፍርድ ቤቱ ከፈረደባችሁበኋላ ‹ይቅርታ› ጠይቃችሁ እናስፈታችኋለን›› ሆኖም የሙስሊሙ መሪዎች ‹‹ይህንን በጭራሽ አንቀበለውም፣ ጥፋተኛ ነኝም አንልም፣ አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›› ሲሉ በድፍረትና በቁርጠኝነት መልሰውላቸው ወደ እስር ክፍላቸው ተመልሰዋል፡፡ በእርግጥም የኮሚቴው አባላት ትክክለኛ ውሳኔ ነው የወሰኑት፡፡ ምክንያቱም ይህ የሽምግልና ቡድን ቀንደኛ የስርአቱ ደጋፊ ሲሆን፣ መደራደሪያ ብሎ የሚያቀርበው ሁሉም ነገር የአገዛዙን የፖለቲካ ጥቅም የሚያስከብር ነውና፡፡ በድህረ ምርጫ 97 የታሰሩትን የቅንጅት አመራርንም በዚህ አይነት መልኩ መሸወዱ ይታወሳል፡፡(በነገራችን ላይ ሽማግሌዎቹ በተጠቀሰው ዕለት አንዱአለም አራጌን ጠርተው አናግረውታል፤ እስክንድር ነጋን ግን ዘለውታል፡፡ ለምን? ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ደግሞ የሽማግሌ ቡድኑ ለሙስሊሙ መሪዎች ‹‹የመጣነው አንዱአለምን ፈልገን ነው፣ እናንተን እግረ መንገዳችንን ሰላም እንበላችሁ ብለን ነው›› ሲሏቸው፣ ለአንዱአለም ደግሞ የዚህን ግልባጭ ምክንያት ሰጥተውታል፡፡
http://www.ecadforum.com

Thursday, January 3, 2013


Ethnic clash among AAU 4 Kilo students causes damages

Listen to this article. Powered by Odiogo.com


Addis Abeba
3/1/13

A violent ethnic based conflict among Addis Abeba University (AAU) College of Natural Sciences/4 Kilo Campus students that started yesterday afternoon (02-01-2013) 4PM resulted in the damage of properties and injuries of students.
According to De Birhan's sources the violent conflict had reportedly started after "unidentified students posted a poster containing a derogatory message on the College's main Library and two other places about Oromo ethnic students". The conflict continued until mid night when Oromo ethnic students non violently blocked and banned most students from entering or leaving their dormitories. The tension turned out violent when a student was severely attacked around mid night.

The violent clash that continued until early morning had restarted after it was contained several times by the Federal Police who surrounded the Campus and tried to quell the situation. Several students from the conflicting groups that form along ethnic lines were severely wounded and were taken to Zewditu and Yekatit 12 Hospitals. Windows, doors and other properities of the Univeristy and many students' dormitories were damaged in the clash that continued until 3AM this morning.

Students that have been suspected to have had direct involvement in the violence are now under Police custody. Although there is Police presence and calamity in the Campus, students are still barred from either leaving or entering the Campus.

Similarly, De Birhan has learnt that there was a fall out between students and the College's Administration for the past two weeks over grading issues.

The College had introduced a new Grading System/scale, which requires students to score more than 95 out of 100 to get an "A", however students protested the new scale and class representatives had to meet with the College Administration on the matter. Due to disagreement, some representatives had even walked out of the meeting. After tense meeting and talks, the Administration finally agreed to reduce the required score to get an 'A' to 85 points out of 100.

The College was founded on March 20, 1950 by Emperor Haile Silassie I who declared the foundation of the University College of Addis Ababa, including the faculties of Arts and Science. At the time there were only 33 students enrolled. At present, over 5000 undergraduate, 3000 extension, over 1000 MSc and 50 PhD students are enrolled in the College. The Faculty today comprises six departments: Biology, Chemistry, Physics, Earth Sciences,Mathematics and Statistics and four programs namely Biothechnology, Food Science, Computational Science, Matreials Science and Environmental Science.
Breaking News: Protest erupts at Addis Ababa University

Addis Ababa University main campus
Awramba Times (Addis Ababa) – Protest sparked at the College of Natural Sciences, Arat Kilo Campus of the Addis Ababa University. According to our sources in Addis Ababa, The main cause of the protest is due to an ethnic derogatory poster against Oromo-ethnic students placed at the College’s main Library and two other places.
So far, more than 20 students from the conflicting ethnic groups were wounded and were taken to government hospitals. On the other hand Police have accused several students of causing damage to university property, including broken windows and doors. More details to come…
http://www.awrambatimes.com