Friday, December 25, 2015

የ11ኛው ሰዓት ጥሪ እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ይመለከታል!

December 25, 2015
def-thumbየንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ህዝብ ባደረጉት የትግል ጥሪ በ11ኛው ሰዓት ላይ እንደምንገኝ ገልጸዋል ። የ 11ኛው ሰዓት መልዕክት፣ አንደኛ፣ ወደ 12ኛው ሰዓት ወይም ወደ ፍጻሜው እየተቃረብን መሆኑን የሚነገረን ነው። የ11ኛው ሰዓት የትግል ጥሪ የአንድን የትግል ምዕራፍ ለመዝጋት እና አዲስ የትግል ምዕራፍ ለመጀመር የመጨረሻ የሞት ሽረት ትግል የምናደርግበት ጊዜ ላይ መድረሳችንን የሚገልጽ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ጥሪው ከትግሉ ፍጻሜ በሁዋላ ስለሚፈጠረው አዲስ ስርዓት ከአሁኑ ማሰብ መጀመር እንዳለብን የሚያነቃን ደወል ነው። 11ኛው ሰዓት ላይ ቆመን ከ12ኛው ሰዓት በሁዋላ ስለሚፈጠረው ነገር መጨነቅ ካልቻልንና በጊዜ ቤታችንን ካላሰናዳን ፣ ከትግሉ ፍጻሜ በሁዋላ ሊገጥሙን የሚችሉትን ተግዳሮቶች በጊዜና ብቃት ባለው መልኩ ለመፍታት መቸገራችን አይቀርም ። አንድ በእድሜ የገፋ ሰው 11ኛው ሰዓት ላይ መሆኑን ሲያውቅ ከህይወቱ ፍጻሜ በሁዋላ ስለሚኖረው ህይወት ማሰላሰሉ ተፈጥሯዊ ነው። የ11ኛው ሰዓት ጥሪም የአንድን አገዛዝ እርጅናና ፍጻሜ የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ በቦታው የሚወለደውን አዲስ ስርዓት ምንነትም የሚያሳይ ነው።
የ11ኛው ሰዓት ጥሪ ተደራሾች እነማን ናቸው? የጥሪው ተደራሾች በኢህአዴግ ዙሪያ የተሰባሰቡት እና እነዚህን ስብስቦች በማፍረስ አዲስ ስርዓት ለመገንባት የሚታገሉት የነጻነት ሃይሎች ሁሉ ናቸው። የ11ኛው ስዓት ጥሪ ለወያኔ ገዢዎች መገርጀፋቸውን የሚያረዳ የሞት ጥሪ ደወል ነው፤ ወደማትመለሱበት መቃብር ከመወርወራችሁ በፊት በቀራችሁ የአንድ ሰአት እድሜ አሟሟታችሁን አሳምሩ ብሎ የሚመክር ነው። በተለይ በጣት የሚቆጠሩ የሻገቱ ገዢዎችን ደግፋችሁ የቆማችሁ የመከላከያ፣የፖሊስና የደህነት አባላት አሰላለፋችሁን በጊዜ አስተካክሉ የሚል አርቆ ከማሰብ የመነጨ ምክር ነው ። የ11ኛው ሰዓት ጥሪ የሚመክር ብቻ ሳይሆን የሚያስጠነቅቅም ነው። ይህን የገረጀፈ አገዛዝ ደግፈው የቆሙ ሁሉ በጊዜ ከህዝብ ጋር እንዲታረቁ ይህ ካልሆነ ግን በመጨረሻው ሰዓት ከፍርድ እንደማያመልጡ የሚያስጠነቅቅ ነው። ካለፈው የሚመጣው ይበልጣል፤ ወያኔን ደግፋችሁ የቆማችሁ ሁሉ ያለፈ ጥፋታችሁን ለወደፊት በምትስሩት ስራ እንድትክሱ መልእክት ተላልፎላችሁዋል።
የ1ኛው ሰዓት ጥሪ የነጻነት ሃይሎች በአንድነት እንዲሰባሰቡና ትግሉን እንዲያቀጣጥሉም ያሳስባል። አገዛዙ 11ኛው ሰዓት ላይ ነው ማለት በራሱ ጊዜ ይወድቃል ማለት አይደለም። አገዛዙ ከደሃው በዘረፈው ገንዘብ ኪኒኖችን እየዋጠና ምርኩዞችን እየገዛ እድሜውን ሊያራዝም ይችላል። ከገፋነው በቀላሉ ተሰባብሮ ይወድቃል፤ ዝም ካልነው ግን ድዱ ረግፎም በህይወት መቆየቱና ስቃያችን ማራዘሙ አይቀርም። እኛ በዘር፣ በጾታ፣ በትምህርት ወይም በሌሎች ጥቃቅን ነገሮች ሳንለያይ አንድ ሆነን ይህን የሻገተ አገዛዝ እንድናስወግድ ግልጽ ጥሪ ተላልፏል።
የ11ኛው ሰዓት ጥሪ ያረጀውን ስርዓት ወደ መቃብሩ ከከተትነው በሁዋላ ስለሚፈጠረው አዲስ ስርዓት እንድናስብ የሚመክርም ነው። ዛሬ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን እንድንነጋገርና የነገውን ትልም እንድንተልም የሚጠይቅ ነው። አስቀድሞ በጋራ መተለሙ ነገ ሊፈጠር የሚችለውን ችግር ከመቀነሱም በላይ፣ የሻገተውን አገዛዝ በህብበረት ለመጣል ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። በጭሩ የ11ኛው ሰዓት ጥሪ ወያኔን ተባብሮ ለመቅበር ብቻ ሳይሆን፣ በመቃብሩ ላይ ስለሚተከለው አዲስ ችግኝ ለመነጋገር ጥሪ የሚያቀርብ ነው።
ሁላችንም የ11ኛውን ሰዓት ጥሪ ተቀብለን ተግባራዊ ልናደርገው ይገባል። ድሉ የሁላችንም ነው!
አርበኞች ግንቦት7!

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን የመሰጠቱን ጉዳይ ዳግም አረጋገጡ።

December25,2015
ንግግራቸው የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አስመስሏቸዋል።

''በታሪካችን ያላየነው ረሃብ ላይ ነን'' አቶ ኃይለ ማርያም

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ዛሬ ታህሳስ 15/2008 ዓም በኢትዮጵያ ፓርላማ ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ ላይ በተለይ በኦሮምያ ክልል ለተነሳው ሕዝባዊ አመፅ እና በሱዳን እና በኢትዮጵያ መካከል ስላለው የድንበር ጉዳይ ላይ  የተለመደ አወዛጋቢ እና የበለጠ አወሳሳቢ ንግግሮችን ተናግረዋል።

በኦሮምያ የተነሳውን ሕዝባዊ አመፅ ችግሩን፣መነሻውን እና መፍትሄውን የጠቆሙበት አገላለፅ የእራሳቸውን እና የመንግስታቸውን መፍትሄ ቢስነት በአደባባይ በድጋሚ ያጋለጠ ነው።ችግሩ ገበሬው መረጃ አለማግኘቱ ነው ማለታቸው እና በውጭ ኃይሎች ቅስቀሳ ነው የሚለው እርስ በርሱ የተቃረነ አነጋገር በእራሱ ለእራሳቸውም በአግባቡ የገባቸው አይመስልም።ችግሩን መንግስት ስለ ፕላኑ አለመንገሩ ነው ያሉት እና አሁን መንግስታቸው እያናገረ ያለው በጥይት መሆኑን ለሚያስተውለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ንግግራቸው በሕዝቡ ላይ ከመዘባበት ያለፈ አንዳች የሚሰጠው ፋይዳ የለም።በመፍትሄነት ያስቀመጡትም ምንም አዲስ ነገር የሌለው እና አሁንም መልሰን እንነግረዋለን የሚለው አባባል ንግግሩ በጥይት እንደሆነ አመላካች ነው።ሕዝብ የሚባለው እና የሚደረገው ስላልገባው ነው የሚለው አባባል በእራሱ ለሕዝብ ያለን የንቀት ደረጃ አመላካች ነው።በሰላማዊ ሰልፍ እጆቻቸውን ወደ ሰማይ እየሰቀሉ ድምፃቸውን ያሰሙ ታዳጊዎችን በጥይት አረር ከመቱ (እንደ አቶ ኃይለማርያም አነጋገር 'ካናገሩ') በኃላ አሁንም እናናግራለን እያሉ መዘባበት በእራሱ ህዝብን የአላዋቂነት ጥግ ነው።

በሌላ በኩል የሱዳን እና የኢትዮጵያን የድንበር ማካለል ጉዳይ ላይ የጀመሩበት አረፍተ ነገር እና በመካከል እና በመጨረሻ ላይ የደመደሙበት ንግግር ኢትዮጵያ በእዚህ አይነት ደረጃ የባዕዳንን ጉዳይ የሚያስፈፅም መንግስት ኖሯት እንደማያውቅ በግልፅ የሚያሳይ ነው።

''በመሬት ጉዳይ ላይ የተደረገ ድርድር የለም። በኢትዮጵያ እና በሱዳን መሃል ያለው ድንበር በደንብ ስላልተስተካከለ በእርሱ ላይ ነው እየሰራን ያለነው'' ካሉ በኃላ የሱዳን ጠቅላይ ሚንስትር የሚናገሩ እስኪመስል ድረስ የኢትዮጵያን ክብር በሚነካ መልኩ ሱዳንን እየረበሽን ያለነው የእኛ ገበሬዎች ናቸው።አሁን የሚያርሱት መሬት የሱዳን መሬት ነው ብለው ለመከራከር ሞክረዋል።ይህ ማለት ባጭሩ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት ሲያርሱት የነበረው መሬት በእራሳቸው አገር ጠቅላይ ሚኒስትር መሬቱ የሱዳን ነው እየተባሉ ነው ማለት ነው።በተለይ የሱዳን ወታደሮች ለስራ በወሰዷቸው ኢትዮጵያውያን ላይ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ብቻ እጅግ አሰቃቂ በሆነ መንገድ ስለመገደላቸው አንዳች ያልተነፈሱት አቶ ኃይለማርያም ይልቁንም የኢትዮጵያን ገበሬዎች በሱዳን ተገብተው ሲወቅሱ እንዲህ ብለዋል-
''ከእኛ አካባቢ እየሄዱ ሱዳናውያንን እየገደሉ የሚመለሱ'' እንደሳቸው አገላለጥ ''ሽፍቶች''ናቸው ሲሉ ተደምጠዋል።በመቀጠል አቶ ኃይለማርያም እንዲህ አሉ: ''በርካታ ኪሎ ሜትሮች ሱዳን ውስጥ ገብተው የሚያርሱ እኛ የምናውቃቸው ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች እና ባለሀብቶች አሉ''  በማለት እነኝህ መሬቶች ለጊዜው ለሱዳን አይሰጡ እንጂ የሱዳን መሆናቸውን ባረጋገጡበት ንግግራቸው በቀጣዩ የድንበር ማካለልም መንግስታቸው የሱዳን መሆናቸውን እንደሚያውቅ አሁንም እንደ ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሳይሆን እንደ ሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ባጠቃላይ ድንበሩን በተመለከተ ከተናገሩት መረዳት የሚቻለው ሁለት ጉዳይ ነው።አንዱ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ማካለል ሂደት ላይ ናቸው የሚለው ዜና ትክክል መሆኑን።በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አሁንም እንደ ኢትዮጵያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳይሆን በሱዳን ወገን ተገብተው የኢትዮጵያን ገበሬዎች እና ባለ ሀብቶች የሱዳንን መሬት አረሱ እያሉ ይህ መሬት ለሱዳን እንደሚገባ በአንደበታቸው ሲናገሩ ተሰምቷል።በሌላ አነጋገር ለብዙ ትውልዶች መሬቱን ሲያርሱ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከመሬታችን አንነቀልም ካሉ ከሱዳን ወታደሮች ጋር ተባብረው ገበሬዎቹን እና ባለ ሀብቶቹን የማባረር ሥራ እንደሚሰራ እየገለጡ ነው ማለት ነው።ምክንያቱም በአደባባይ መሬቱ የኢትዮጵያን አይደለም።ለጊዜው ነው ሱዳኖች የፈቀዱልን ካሉ በኃላ ይህንንም የሱዳን ውለታ መሆኑን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስረዳት ሲውተረተሩ ተሰምተዋል።

በመጨረሻም አቶ ኃይለማርያም ''በምግብ እራሳችንን ችለናል'' ብለው በተናገሩ በወራት ውስጥ በዛሬው እለት ደግሞ ካለ አንዳች እረፍት ''የገጠመን ድርቅ በታሪካችን ምናልባትም ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ውስጥ አይተነው የማናውቅ በእኔ አመለካከት እጅግ የከፋ ድርቅ ነው'' ሲሉ ተደምጠዋል።ለድርቁ የሰጡት መፍትሄ ግን የበለጠ አስቂኝ ነው።መፍትሄዎቹ የሚመጡ እርዳታዎችን መቀበል እና የውሃ ጉድጓድ በመቆፈር ነው ይላሉ አቶ ኃይለማርያም።ጥያቄው ግን  ከእሩብ ክ/ዘመን አምባገነናዊ እና የከፋፍለህ ግዛ የኢህአዴግ/ህወሓት አገዛዝ በኃላ ኢትዮጵያ በታሪክ ያላየችው ርሃብ ላይ ነች ማለት እና የውሃ እጥረት ችግር ለሆንባት አገር የውሃ ጉድጓድ መቆፈር መፍትሄ ነው ማለት ምን አይነት የአስተሳሰብ ድህነት ነው? የሚል ነው።ባጭሩ አቶ ኃይለማርያም ህወሃቶች ስልጣን እንዲለቁ እና የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት ሿሚዎቻቸውን ቢመክሩ እና የመሸበት ቢያድሩ የተሻለ ነው።

ጉዳያችን GUDAYACHN

Friday, December 18, 2015

የህወሓት የደንነት ቢሮ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን አስጠነቀቀ፡ መፈንቅለ መንግስት ሊደረግ እንደሚችል የቅርብ አዋቂዎች ተንብየዋል

December 18,2015
tigrai

የደንነት መስሪያ ቤቱ በሚንስትሮች ምክር ቤት በኩል ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያ የሰባት ቀን የጌዜ ገደብ የተሰጠው ማስጠንቀቂያ ማስተላለፉ ታውቆአል። የደህንነት መስሪያ ቤቱ በሀገሪቱ ውስጥ ሳይታሰብ የፈነዳውን አመፅ ለመቆጣጠር ምን አይነት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ አልችል ብሎ ሲወዛገብ መሰንበቱ ሲታወቅ ዛሪ ከጥዋት ጁምሮ ሲአካሂድ በዋለው ውይይት ላይ ግን ማንኛውንም አይነት ሀይል ተጠቅሞ አመፁን ለመቆጣጠር ወስኖአል። የውሳኔውን ቅጅ ከ አንድ ሳምንት ማስጠንቀቂያ ጋር በአቶ ካሳ ተክለብርሀን በኩል ለጠቅላይ ሚንስትሩ ልዃል።

የአቶ ሀይለማርያም አስተዳደር አመፁን ለመቆጣጠር መመሪያ ከአሜሪካ መንግስት መቀበሉን በአስቸዃይ አቁሞ የተነሳውን መጠነ ሰፊ አመፅ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ መቆጣጠር የሚያስችል የኦፕሪሽን መርሀ ግብር አውጥቶ ለፊደራል ፓሊስና መከላከያ ማስረከብና ለተግባራዊነቱም ካልተንቀሳቀሰ ሙሉ ሰላም የማስከበሩን ስራ መከላከያ ይረከባል ይላል። በአጭሩ መፈንቅለ መንግስት ይደረጋል ማለት እንደሆነ ምንጮቸ አረጋግጠዋለል።

Thursday, December 17, 2015

ትግላችንን ተጠናክሮ በአንድነት ይቀጥል!

December 17, 2015
def-thumbየኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ በያቅጣጫው መነሳቱ የሚያኮራ ነው። ባለፉት 3 ዓመታት ብቻ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያደረጉትን የመብት ትግል ጨምሮ በደቡብ፣ አማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላና በሌሎችም አካባቢዎች በርካታ የነጻነት ትግሎች ተካሂደዋል። አሁን በኦሮምያ እና በአማራ በተለይም በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉት የነጻነት ትግሎች የአጠቃላዩ የነጻነት ትግል አካሎች ናቸው። በእነዚህ የነጻነት ትግሎች ገዢው ፓርቲ ከህዝብ ጋር ለምንጊዜውም መለያየቱን ለማየት ችለናል። ስልጣኑን ለማስጠበቅ ሲልም፣ አቅሙ ቢፈቅድለትና ማግኘት ቢችል በምድር ላይ ያሉትን ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎችን ሁሉ በገዛ ህዝቡ ላይ ለመጠቀም ወደ ሁዋላ የማይል የአረመኔዎች ስብስብ መሆኑን አረጋግጠናል። በጭካኔውና በፍርሃቱ ብዛት የተነሳ በርካታ ሙስሊሞች፣ ክርስቲያኖች፣ መብታቸውን በሰላም ለመጠየቅ ወደ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ተገድለዋል፤ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ጋዜጠኞች በእስር ተንገላተዋል፤ በእስር ቤትም ማንነታቸውን ከማዋረድ ጀምሮ የተለያዩ አካላዊ ጥቃቶች ተፈጽሞባቸዋል።
የኦሮሞ ህዝብ መብቴ ይከበርልኝ ብሎ መነሳቱን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ከያቅጣጫው ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው። ይህ ለነጻነት ሃይሎች ብስራት ሲሆን ዘርን ከዘር በማጋጨት የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ለሚፈልገው የሽፍታ አገዛዝ ደግሞ ትልቅ መርዶ ነው። ባለፉት 25 ዓመታት ወያኔ አንዱን ዘር ከሌላው ዘር እያጋጨ፣ በወንድማማቾችና እህትማማቾች መካከል መተማመን እንዳይፈጥር መርዙን ሲረጭ ቆይቷል፤ ያሰበው አልሰምርለት ሲል ደግሞ በአገሪቱ አንጡራ ሃብት በሸመተው ጠመንጃ ለመብቱ የተነሳውን ህዝብ ደረት ደረቱን እየመታ ፈጅቶታል። በተለይም የአማራው ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድነት ተሰልፎ በህወሃት አገዛዝ ላይ የነጻነት ክንዱን ለማሳረፍ እንዳይችል ሌት ተቀን የጥላቻ መርዙን በመርጨት ከሌላው ህዝብ ጋር እንዲጋጭ ለማድረግ በእጅጉ ደክሟል። ወያኔ የረጨውን የጥላቻ መርዝ የኦሮሞ እና የአማራ ልጆች በጋራ እያረከሱት መገኘታቸው፣ የሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦች ህዝቦችም እንዲሁ ” አንለያይም” በማለት በጋራ ለመሰለፍና ትግሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነታቸውን መግለጻቸውና በተግባር እያሳዩ መምጣታቸው የ25 አመታት የወያኔ የአፈናና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ እያከተመ መምጣቱን የሚያመላክት ነው። ወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው በመላው ኢትዮጵያውያን ትብብር እንደረከሰበት ሲያውቅ ደግሞ የግድያ አዋጅ አውጥቶ በ-ኢትዮጵያውያኑ ላይ ጥይት አርከፍክፎ ጸጥ ሊያሰኛው መዘጋጀቱን በአዋጅ አስነግሯል። ከታሪክ መማር የማይችለው ጠባቡ ወያኔ፣ ህዝባቸውን አዋጅ አስነግረው የገደሉ ጨቋኝ መንግስታት መጨረሻቸው ምን እንደነበረ እንኳን ቆም ብሎ ማሰብ አልቻለም። ዛሬ የእሳት ላንቃ በሚተፋ ጠመንጃቸው ሊጨፈልቀው የሚያስበው ህዝብ ነገ መልሶ ራሱን እንደሚጨፈልቀው ለአፍታም ቢሆን ለማሰላሰል አልቻለም። የዘረፈው ሃብትና የታጠቀው መሳሪያ አእምሮውን ደፍኖት፣ እየመጣ ያለውን ህዝባዊ ሱናሚ ለማየት ተስኖታል። በጦር መሳሪያ ጋጋታና ድንፋታ ቢሆን ኖሮ ወራሪዋ ጣሊያን እስከዛሬ ድረስ ከአገራችን ለቃ ባልወጣች ነበር፣ በጦር መሳሪያ ጋጋታ ቢሆን ኖሮ እነ ጋዳፊን ዛሬ ቤተመንግስት እንጅ መቃብር ውስጥ አናገኛቸውም ነበር።
የአገራችን ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለነጻነቱ የሚያደርገውን ትግል በጥንቃቄ የሚመራበት ጊዜ ላይ ነን ። የገጠመን ጠላት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ፣ የገዛ ህዝቡን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋው የተነሳ በመሆኑ፣ አገዛዙ እስከዛሬ ካደረሰው ጥፋት ሌላ ተጨማሪ ጥፋት ሳያጠፋ፣ ከአገራችን መሬት ለመንቀል እንድንችል እርምጃችን ሁሉ ጥንቃቄ የተሞላበት ሊሆን ይገባል። ጠላታችን ህዝብን ከህዝብ ለማፋጀት ያለ የሌለ ሃይሉን የሚጠቀም መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ሁሉ ህዝቡን በጅምላ ለመፍጀት ወደ ሁዋላ የማይል ነው። ህዝቡ የጠላቱን አውሬነት ተገንዝቦ እሱ በሚከፍተው ቀዳዳ ዘው ብሎ ላለመግባት መጠንቀቅ አለበት። ሊገድሉን ሲመጡ ዘወር ብሎ በማሳለፍ፣ እንደገና ደግሞ ወደ አደባባይ በመውጣት፣ እንዲሁም የተቃውሞውን አድማስ በማስፋትና የሃይል መከፋፈል እንዲፈጠር በማድረግ ወያኔን አዳክሞና ተስፋ አስቆርጦ ካለሙት ግብ መድረስ ይቻላል። አሁን እየታየ ያለው አንድነት ይበልጥ እየተጠናከረ፣ ከኦሮሞው ጎን አማራው፣ ከአማራው ጎን ጉራጌው፣ ከጉራጌው ጎን ትግሬው፣ ከትግሬው ጎን አፋሩ፣ ከአፋሩ ጎን ጋምቤላው፣ ከጋምቤላው ጎን ሀረሪው፣ ከሃረሪው ጎን ጉሙዙ፣ ከጉሙዙ ጎን አዲስ አበቤው፣ ከአዲስ አበቤው ጎን ጋሞው በአጠቃላይ መላው ህዝብ እጅ ለእጅ እየተያያዘ የነጻነት ባበሩ ወደፊት እንዲሮጥ ማድረግ አለበት። ወጣቱ ራሱን ባለበት ቦታ እያደራጀና አመራር እየሰጠ በያቅጣጫው የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ ይቀጥል።
አርበኞች ግንቦት7 ትግሉን በተለያዩ አቅጣጫዎች አጠናክሮ ቀጥሎአል፤ የአርበኛው ሰራዊት የወያኔን ጀሌዎች በቀኝና በግራ መውጫና መግቢያ እያሳጣቸው ነው። የንቅናቄው አባላት በዳር አገር በአፈሙዝ፣ በመሃል አገር ደግሞ ወጣቱን እያደራጁ ለትግል እንዲሰልፍ እያደረጉት ነው። የንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ “ከነጻነት ትግሎች ጎን አለን” እንዳሉት የአርበኛው ልጆች ፊት ለፊት ተሰልፈው አመራር በመስጠት የነጻነት ትግሉን ለማቀጣጠል እና መከፈል ያለበትን የህይወት መስዋትነት ለመክፈል ተዘጋጅተው በያቅጣጫው እየተንቀሳቀሱ ነው።
ተደጋግሞ እንደተነገረው የአርበኞች ግንቦት7 አላማ በአገራችን የዲሞክራሲያዊ የሽግግር ስርዓት ማስጀመር ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ አላማ ዙሪያ ተሰልፎ ትግሉን ይቀጥል። ይህን አላማ የሚደግፉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ዛሬውኑ ከጎናችን ተሰልፈው ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው የሞት ሽረት ትግል ይሰለፉ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
አገራችን በልጆቿ ነጻ ትወጣለች!
አርበኞች ግንቦት7

“ፕሮፌሰር፣ ጄኔራል” ሳሞራ

December 17,2015
የቻይና ደም-መላሽ!
samoray
ረቡዕ በተሰማው ዜና መሠረት የቻይናው ቲያንጂን የቴክኖሎጂና ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለሳሞራ የኑስ የክብር ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡
ሚያዚያ 1999 የዖጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግምባር በክልሉ በሚገኝ የነዳጅ ፍለጋ ቦታ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከ70 በላይ ንጹሃንን በገደለበት ወቅት ዘጠኝ ቻይናውያን ከሞቱት መካከል ነበሩ፡፡
በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር አዛዥነት በየጊዜው በዖጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሲቃወም የነበረው ኦብነግ ለወሰደው ድንገተኛ እርምጃ በሟቹ መለስ የሚመራው ህወሃት በክልሉ አምስት ቦታዎች ማለትም በፊቅ፣ ቆራሄ፣ ጎዴ፣ ዋርድሄር እና ደጋሃቡር ዘግናኝ የሆነ የመልሶ ማጥቃት ጭፍጨፋ በነዋሪው ሕዝብ ላይ አድርሷል፡፡
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ባወጣው ዘገባ መሠረት ኦብነግ ላደረሰው የአጸፋ መልስ እና ታጣቂዎችን ለመደምሰስ በሚል ህወሃት ያዘመተው ጦር በተደጋጋሚ በሰላማዊው ሕዝብ ላይ ፍጹም ጨካኝና ዘግናኝ ዕልቂት ፈጽሟል፡፡
samorayየመልሶ ማጥቃቱን ዘመቻ ለማካሄድ ጂጂጋ ላይ የክልሉ የደኅንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ባደረጉበት ወቅት የመለስ የጸጥታ አማካሪ አባይ ጸሃዬ እና ሳሞራ የኑስ በጥቃቱ ዕቅድ አወጣጥ ላይ ተገኝተው እንደነበር ታማኝ ምንጮቹን ጠቅሶ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ያስረዳል፡፡
ከዚያም በ1999 ሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ አቶ መለስ መጠነ ሰፊ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ እንዲካሄድ ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ የዖጋዴን ሕዝብ ፍዳውን በላ፤ እንደ ቅጠል ረገፈ፤ ዕድሜያቸው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጃገረዶች፣ ሴቶች አዛውንቶችንም ጨምሮ ተደፈሩ፡፡ ህጻናት ወንዶችም ሳይቀሩ የዚህ ሰለባ ሆነዋል፡፡
የቀድሞው የቻይና መሪ ማዖ ሴቱንግ ሽምቅ ተዋጊዎችን ስለማጥፋት የተናገሩት ቃል በመለስ ፊት አውራሪነት ተፈጸመ፡፡ “ዓሣ በባህር እንደሚዋኝ ሽምቅ ተዋጊም በሕዝቡ መካከል መንቀሳቀስ አለበት፤ (ሽምቅ ተዋጊን ለማጥፋት ካስፈለገ ዓሣው ያለበትን ባህር ማድረቅ ነው)” ያሉት የማዖ ቃል በመለስ ትዕዛዝ በሳሞራ የኑስና ሌሎች የህወሃት አጋፋሪዎች ተፈጸመ፡፡
ውለታ የማይረሱት ቻይናውያን የትምህርት ደረጃው በውል የማይታወቀውን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አሉ ከሚባሉት የጦር አካዳሚዎች ሥልጠና ስለመውሰዱ ምንም ማስረጃ ላልተገኘለት “ቻይናዊ ጄኔራል ደምመላሽ” ባቋራጭ “የላቀ ምሁርነት” አጎናጸፉት፡፡
ውለታን መመለስ ከሆነ አይቀር እንዲህ ነው፡፡
ማዖ ነኝ ከቲያንጂን

“እኛ አማራ ነን እንጂ ትግሬ አይደለንም” የወልቃይት ሕዝብ

December 17,2015

Annexation_Tigray

* “(ችግራችን) ትግሪኛ መናገር፤ ትግሪኛ መጻፍ፤ በትግሪኛ መዝፈን፤ አለብህ የሚል ነው፤ እኛ መሽከርከር አንችልም” የወልቃይት ሕዝብ
“እኛ አሁን የምናቀርበው ምንድነው ማንነት ነው፤ አማራነት በማመልከቻ ለማምጣት አይደለም የተነሳነው፤ አማራ ነን፤ ትላንት አማራ ነን፤ ነገ አማራ ነን፤ ለዘላለም አማራ ነን፤ ይኼ አያሳፍረንም፤ እኛ ስንዘፍን፣ ስናለቅስ፣ ስንፎክር፣ ስንሸልል፣ ለቅሶ ስንደርስ፤ ስናመሰግን ለማንኛውም የምንገልጸው በአማርኛ ነው፡፡ ይህ አማርኛችን ከአያት ቅድመ አያቶቻችን የገኘነው ነው፤ አያሳፍረንም፡፡
“የወልቃይት ሕዝብ አንዲት ጎጆ ተከዜ ተሻግሮ አልቀለሰም፤ ስለዚህ ይህ ምን ማለት ነው፤ የምን ስሜት ነው፤ ሠርጋችንን፤ ሃዘናችንን፤ ደስታችንን የምናወሳውም እንዲሁ ነው፡፡ ለቅሷችንን የሚያውቅ፤ ደስታችንን የሚያውቅ፤ እንጂ በእኛ ላይ አናታችን ላይ መጥቶ አይደለህም፤ አባትህ ሌላ ነው ሊለን አይችልም፤ ማንነት እንደዚሁ ነው የሚገለጸው፤ ማንነት ለቅሶ የምገልጽበት ቋንቋ ነው፤ ማንነት ሳዝን የምገልጽበት ቋንቋ ነው፤ በተለያዩ መልኮ የሚገለጽ ነው፤ እኛ በተለያዩ ሁኔታዎች ከአማራ የሚለየን ምንነት የለም፡፡ ዛሬ ታሪክን የመቶ ዓመት ያደረጉ ሰዎች ሌላ ቋንቋ ሊያወሩ ይችላሉ፤ ታሪክን በትክክለኛ ሁኔታ የገለጹ ምሁራን ግን አማራነታችንን በትክክል ይገልጻሉ፡፡
“24 ዓመት ሙሉ ሕዝባችን እያለቀሰ፤ እንዳይናገር አጎንብሶ እየሄደ ቀና ብሎ እንዳይናገር ያሳፈረው አንድ ኃይል ብቻ ነው፡፡ ይህም ትግሪኛ መናገር፤ ትግሪኛ መጻፍ፤ በትግሪኛ መዝፈን አለብህ የሚል ነው፤ እኛ መሽከርከር አንችልም፤ … አማርኛችን ጥርት ያለ አማርኛ ነው፤ እንደማንኛውም ተናግረን፤ ጽፈን የምንገልጸው ነው፤ … ስለዚህ ዛሬ አማራ መሆናችንን በማመልከቻ ዕርዱን እያልን አይደለም፤ በደማችንና በሥጋችን፣ በማንነታችን፣ በዘራችን የመጣ አማርኛ ነው፤ (ትግሬ አይደለንም) … ይህ የወልቃይት ሕዝብ ድምጽ ነው፡፡”
ሙሉውን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

Saturday, December 12, 2015

የአርበኞች ግንቦት 7 የመጀመሪያ ምክር ቤት ስብሰባ መግለጫ

December 12,2015
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከህዳር 26 ቀን 2008 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ቀን 2008 ዓም ድረስ ሰራዊቱ በሚገኝበት የትግል ቦታ የመጀመሪያውን የምክር ቤት ስብሰባ አድርጎ በስኬት አጠናቋል::
ይህ ስብሰባ የቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርና ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ተዋህደው አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከተሰኘ ወዲህ የተደረገ የመጀመሪያው የምክር ቤት ስብሰባ ነው::
ይህ ስብሰባ፦
1. ውህደት ከተደረገበት ከጥር 2 2007 ዓ.ም ወዲህ የስራ አስፈፃሚውን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አድምጧል፤
2. ከውህደት ወዲህ ንቅናቄው የፈጸማቸውን ተግባራት በጥልቀት መርምሯል፤
3. የንቅናቄውን ህገ-ደንብና አሰራሮችን መርምሮ ማሻሻያዎችን አድርጓል፤
4. የምክር ቤቱ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን አቋቁሟል
5. ተተኪና ወጣት የአመራር አባላት ምክር ቤቱ ውስጥ እንዲካተቱ አደርጓል፤
6. የሃገራችንን የወቅቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሁኔታዎች በጥልቀት መርምሯል፤
7. በወቅቱ ሁኔታዎች ጥናት ላይ ተመርኩዞ የወደፊት የትግል አቅጣጫውን ቀይሷል፣ ግልጽ የሆነ የትግል ስትራቴጅ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፤
8. ከስብሰባው በኋላ መከናወን የሚገባቸውን ተግባራት ቅደም ተከተል አውጥቶ ለስራ አስፈጻሚው መመሪያዎችን አስተላልፏል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የህወሓትን አምባገነን አገዛዝ አስወግዶ በምትኩ ፍትህ የነገሰባት፣ የዜጎች እኩልነት የተረጋገጠባት፣ ዴሞክራሲያዊት አገር ለመገንባት የሚያደርገውን ትግል በግንባር ቀደምትነት ለማስተባበርና ለመምራት ከመቸውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት መነሳቱን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ይገልጻል::
አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ወደ አዲስ ደረጃ ተሸጋግሯል ብሎ ያምናል:: ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችና ድርጅቶች በሙሉ በሚያመቻቸው መንገዶች እየተደራጁ ከንቅናቄያችን ጋር ግንኙነት በመፍጠር በጋራ ትግል አምባገነኑን ወያኔ ከስልጣን እንድናስወግድና በምትኩ ፍትህ፣እኩልነትና የሃገርን አንድነት የሚያረጋግጥ የፖለቲካ ስርዓት እንድናቋቁም ጥሪ ያደርጋል::
ድል ለ ኢትዮጵያ ህዝብ!

ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በህወሓት አገዛዝ የጦር ኃይል ላይ ጥቃት በመሰንዘር ከፍተኛ ድልን ተቀዳጀ!!

December 12.2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ተደጋጋሚ የሽምቅ ውጊያዎችን በማድረግ የህወሓትን መከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ጦር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የህዝብ አለኝታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል፡፡
ባለፈው ሳምንት ህዳር 21/2008 ዓ.ም ጀግናው ሰራዊታችን በዋልድባ በጠላት ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን አሁን ደግሞ ከዋልድባ ወደ አዲ-አርቃይ በመወርወር ማክሰኞ ህዳር 28/2008 ዓ.ም አዲ-አርቃይ ላይ ከወያኔ መከላከያ ሰራዊትና የሚሊሻ ታጣቂ ኃይል ጋር ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1፡00 ለሶስት ተከታታይ ሰዓታት የዘለቀ ከባድ ውጊያ በማድረግ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የጠላት ጦር በመግደልና በማቁሰል ድልን ተጎናፅፏል፡፡
ሰራዊታችን በጦር ሜዳ ውሎው፣ ከጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት በተቀዳ ወኔ፣ እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የህወሓትን መከላከያ ሰራዊትና የሚሊሻ ታጣቂ ኃይል በጦር ሜዳው ላይ በጥይት ቆልቶና አሳሮ አስቀርቶታል፡፡
ፍልሚየው በማግስቱ ረቡዕ ህዳር 29/2008 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ሰዓታት ማለትም እስከ ረፋዱ አራት ሰአት በዚያው አዲ-አርቃይ ላይ የቀጠለ ሲሆን ፣ ወያኔ ከሌላ ቦታ አጓጉዞ ለጦርነት ያሰለፈውን ተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት ጀግኞቹ የአርበኞች ግንቦት ሰባት የነፃነት ፋኖዎች የጠላትን ጦር ድባቅ መትተውታል፡፡
ለነፃነት የሚደረገው ጦርነት አሁንም ቀጥሏል፡፡የወያኔ ባለስልጣናት የሚይዙት የሚጨብጡት አጥተው በተለይ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል የሚገኘውን ድንበር የበለጠ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ሰራዊት ለመዝጋት ቢሯሯጡም ድንበር ላይ የተመደበው ወታደር ከወያኔ እየከዳ የነፃነት ትግሉን ከነትጥቁ እየተቀላቀለ ይገኛል፡፡ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሰራዊት በተቀዳጀው ድል የአካባቢው ህዝብ ጮቤ እየረገጠ እደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ጀግናው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሰራዊት ህዝቡን ከጎኑ በማሰለፍ፣ በህዝብ ድጋፍ ታጅቦ ወደ መሃል አገር እየገሰገሰ ነው፡፡

Wednesday, December 9, 2015

በረሃብ የተጎዳው ወገን ቁጥር በእርዳታ ድርጅቶች ዳታ 13 ሚሊዮን ደረሰ:: ቀየውን ጥሎ የሚሰደደው በርክቷል::

December 12,2015
ተለያዩ የሰሜን እና ምስራቅ ኢትዮጵያ ክፍላተሃገራት የተሰማሩ ከተለያዩ የአለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች የተገኙ ዳታዎች እንደሚያመለክቱት በድርቅ የተጎዳው እና በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ያለው ሕዝብ ቁጥር 13 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት መሰረት በጥር 2016 አስረ አምስት (15 )ሚሊዮን እንደሚገባ ተረጋግጧል::የእርዳታ ድርጅቶቹ ሰራተኞች እንደጠቆሙት በምስራቅ ኢትዮጵያ ሃረርጌ ውስጥ ብቻ ካለፈው ወር ከነበረው የረሃብ ተጎጂ ወገን ቀር በዚህ ዲሴምበር 2015 65% ከፍ ብሌል::የተረጂዎች ቁጥር እና የምግብ አቅርቦቱ እንዳይጨምር የመንግስት ባለስልጣናት ጫና ይፈጥራሉ ያሉት ሰራተኞቹ ሕዝቡ ቀየውን ትቶ ወደ ከተሞች እየዘለቀ መሆኑን ይናገራሉ::
በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ እና በአገው ልዩ ዞን እንዲሁም በአዲስ ዘመን አከባቢ ያለው ሁኔታ ከሌሎች የባሰ ሲሆን ከምስራቅ በለሳ እና ከአገው ምድር ሰቆጣ ቀያቸውን ጥልው በረሃብ ምክንያት የተሰደዱ በጎንደር አዲስ ዘመን ተሰፈሩ መሆኑ ሲታወቅ በትግራይ እንዲሁ እስካሁን እርዳታ ያላገኙ አከባቢዎች እንዳሉ ተጠቁሟል:: በአዲስ ዘመን ያሉ የብኣዴን ባለስልጣናት ከሰቆጣ እና በለሳ ተሰደው የሄዱትን ወገኖች መንግስት በያላችሁበት በጀት እየመደበ ስለሆነ በሚል ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ በማስገደድ ላይ መሆናቸው ታውቋል::ባለፈው ሳምንት በትግራይ በእንደርታ ወረዳ ለሚገኙ በድርቅ ለተጎዱ ተብሎ የመጣው ኣንድ እስካንያ መከኒ ከነተጎታቹ የእርዳታ እህል በወረዳው ባለስልጣናትና ነገዴዎች በመመሳጠር የተራገፈ ኣስመስለው በሌላ መኪና ገልብጠው ጭነው ሲወስዱ የኲሓ ህዝብ እጀ ከፈንጅ ይዞ ለፖሊስ ማስረከባቸው ይታወሳል::

Friday, December 4, 2015

ፈረንሳይ እስከ 160 የሚሆኑ መስጊዶችን ልትዘጋ ነው!

December 4,2015

“ጥላቻ የሚሰብኩ ፈቃድ የሌላቸው መስጊዶች ይዘጋሉ” ኢማም ሃሰን
mosque Paris France
በመጪው ጥቂት ወራቶች ፈረንሳይ እስከ 160 የሚጠጉ መስጊዶችን ለመዝጋት መወሰኗ ተሰማ፡፡ የአገሪቱ ከፍተኛ ኢማም እንዳሉት በሥራ ላይ በዋለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት ጽንፈኛ አመለካከት የሚያራምዱ የእምነት ቦታዎች መዘጋትአለባቸው፡፡
በኅዳር ወር መጀመሪያ አካባቢ በፓሪስ የተከሰተውን ጥቃት ተከትሎ እስካሁን ጽንፈኛ አቋም አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ሦስት መስጊዶች መዘጋታቸውን የአገር አቀፍና የአካባቢ ኢማሞች ለመምረጥ ኃላፊነት የተሰጣቸው ኢማም ሃሰን ኤል-አላዊ ለአልጃዚራ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡ እርሳቸው እንደሚሉት በቀጣይ ወራቶች በርካታ መስጊዶች እንደሚዘጉ አስረድተዋል፡፡
“ከአገር ውስጥ ሚኒስቴር ጋር በምናደርገው ውይይት እና ይፋ በሆኑት መረጃዎች መሠረት ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸው፣ ጥላቻን የሚሰብኩ፣ ታክፊሪ ንግግር የሚደረግባቸው ከ100 እስከ 160 መስጊዶች ይዘጋሉ” በማለት ኢማም ሃሰን ተናግረዋል፡፡ ታክፊሪ ንግግር ማለት በእምነቱ ውስጥ ያሉትን ሌሎች ሙስሊሞችን በከሃዲነት የሚነቅፍ ንግግር ነው፡፡ “እንዲህ ዓይነቱ ንግግር ዓለማዊ በሆነችው ፈረንሣይ ብቻ ሳይሆን በእስላማዊ አገራትም ቢሆን መፈቀድ የለበትም” በማለት የመጀመሪያው የእስርቤት ኢማም (ቻፕሊን) ለመሆን የበቁት ሃሰን ኤል አላዊ ተናግረዋል፡፡
franceይህ በፈረንሳይ አገር በቤተ እምነት ላይ የተወሰደ የመጀመሪያው የተባለለት እርምጃ የተወሰደው “አንዳንድ ሕገወጥ ነገሮች በመገኘታቸው” መሆኑን የጠቀሱት ኢማም ድርጊቱ ባለሥልጣናት ማድረግ የሚገባቸው ሕጋዊ እርምጃ ነው ማለታቸውን አልጃዚራ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
ለ130 ሰዎች መሞት ምክንያት የሆኑትን “አሸባሪዎች” በማለት የጠቀሷቸው ኢማም ሃሰን “እነዚህ የሃይማኖት ልብስ የተጎናጸፉ ሌቦችና አደንዛዥ ዕጽ አዘዋዋሪዎች ናቸው፤ ነገሩ የአሸባሪዎች ጉዳይ ነው እንጂ ከሙስሊሞች ጋር ምንም ግንኑነት የለውም፤ የሁሉንም ሰው ደኅንነት ማስፈን የመለከተ ነው” በማለት ኢማም ሃሰን በጥቃት አድራሾቹ ላይ ያላቸውን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
ሌላው ለአልጃዚራ አስተያየታቸውን የሰጡት የአል-ካዋኪቢ ድርጅት ተባባሪ መሥራች የሆኑት የፋርሱ ሙስሊም ፊሊክስ ማርቃርት የመስጊዶቹ መዘጋት እንዳላስደነቃቸው ተናግረዋል፡፡ ይልቁንም በተለያዩ የፈረንሳይ ከተሞች በተካሄዱ እስላማዊ የጸሎት ሥነ ሥርዓቶች ላይ የሰሙት ነገር በእጅጉ እንዳስደነገጣቸው ተናግረዋል፡፡ “እስልምናን ከፖለቲካ ጋር በማያያዝ እስልምናን አስፈሪ የማስደረግ ሥራ በፈረንሳይ መንግሥት እንደሚሠራ አንዳንድ ቦታዎች በይፋ ሲነገር ሰምቻለሁ” ብለዋል፡፡
ሆኖም ግን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከጥቃቱ በኋላ ፈረንሳይ ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠረ የመብት ጥሰት እየፈጸመች መሆኗን ይናገራሉ፡፡ የቤት አሰሳ፣ እስራት፣ ሙስሊሞች ባለቤት የሆኑባቸው ድርጅቶችን የመዝጋት፣ ወዘተ የመብት ጥሰት ተከስቶባቸዋል የተባለባቸው ናቸው፡፡
“በአሁኑ ጊዜ በፈረንሳይ ሙስሊም ሆኖ መኖር ቀላል አይደለም” ያሉት ማርቃርት “በተለይ የፊት መሸፈኛ የሚያደርጉ ሴቶች የመድልዖ ሰለባ ሲሆኑ ለወንዶች ደግሞ ሥራ ማግኘት እጅግ ከባድ ነው” በማለት አስረድተዋል፡፡
በፈረንሳይ ውስጥ በድምሩ 2,600 መስጊዶች ይገኛሉ፡፡

የወገኖቻችን ስቃይ፣ ችግርና ብሶት በያለንበት ይሰማን፤ ለመፍትሔውም በጋራ እንነሳ!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

December 3, 2015
def-thumbበአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሰበብ በከተማዋ ዙርያ ያሉ ወገኖቻችንን ማፈናቀል በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተፈፀመ ጥቃት ነው። በማስተር ፕላኑ ሰበብ የሚፈናቀሉ ገበሬዎች የሁላችን ወላጆች፣ ወንድሞችና እህቶች ናቸው። በማስተር ፕላኑ ሰበብ የምንፈናቀለው ሁላችንም ነን። ይህን መሰሪ ፕላን በመቃወም ላይ ያሉት የኦሮሞ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።
በዚሁ ወቅት በጎንደር ሌላ አሳዛኝ ጉዳይ ተከስቷል። ህወሓት ከሶስት ሺህ በላይ ዜጎቻችንን ያጎረበት እስር ቤት በእሳት ሲጋይ ዜጎች ተቆልፎባቸው እንዲነዱ ተደርጓል። ከእሳቱ በእድል ያመለጡት በጥይት ታድነዋል። ኢትዮጵያዊያን እንዲህ ዓይነቱን ጭካኔ የሚያውቁት በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ጊዜ ነው። ይህን ጥቃት በመቃወም ላይ ያሉ የአማራ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።
ግፍ ያልተፈፀመበት የኢትዮጵያ ክፍል ባይኖርም ሰሞኑን በአማራና በኦሮሚያ ላይ በርክቷል። በሁለቱም የአገራችን ክፍሎች የንፁሀን ደም እየፈሰሰ ነው፤ በሁለቱም ቦታዎች የእናቶች ዋይታና እሪታ ጎልቶ እየተሰማ ነው። የህወሓት አገዛዝ የትውልድ ቦታ፣ ቋንቋና ዘር ሳይለይ በኢትዮጵያዊያን ሁሉ ላይ የተደቀነ አደጋ መሆኑ ከምንጊዜውም በላይ ዛሬ ግልጽ ሆኗል።
ለዚህ የምንሰጠው ምላሽ ምንድነው? ዛሬም ኦሮሚያ ውስጥ የሚፈፀመው በደል የኦሮሞ፤ አማራ ውስጥ የሚፈፀመው በደል የአማራ ጉዳይ አድርገን እንወስዳለን? መቸ ነው ኦሮሚያ ላይ ለደረሰው ጥቃት አማራዉ፤ አማራ ላይ ለደረሰው ጥቃት ኦሮሞው የሚቆረቆረው?
የሁላችን የጋራ ጠላት የሆነው ህወሓት መኖሩ በዘውግ የተከፋፈለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ አንድነት የሚያመጣ ታላቅ ኃይል ሊሆን ይገባል። ይህ የመከራና የመጠቃት ወቅት የምንቀራረብበት ወቅት ሊሆን ይገባል። ይህ የመከራ ወቅት በህወሓት ላይ በጋራ የምንነሳበት ወቅት ሊሆን ይገባል። ዛሬ በኢትዮጵያ ያሉ የተለያዩ ማኅበረሰቦች በሙሉ በፀረ-ህወሓት ትግል መቀናጀት ይኖርባቸዋል። ይህ ማድረግ ግዴታችን ነው።
ለችግሮቻችን መፍትሄ የምናገኘው ችግሮቹ ከተፈጠሩበት እርከን በላይ ሆነን ስናስብ እንጂ ችግሮቹ በፈጠሩበት ደረጃ ላይ ቆመን መሆን አይችልም። ችግሮቹ ከተፈጠሩበት እርከን በላይ ለመሆን አገር አቀፍ እይታ መኖሩ እጅግ ተፈላጊ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያን ሁሉ በተለይም የአማራና የኦሮሞ ልሂቃን ይህንን ጉዳይ አበክረው እንዲያስቡበት አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያሳስባል።
ግፍ ሞልቶ የፈሰሰበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሆኑት ሕፃናት በፌዴራል ፓሊስ ጥይት የሚገደሉበት አሳዛኝ ወቅት ላይ ነን፤ ዜጎች በር ተዘግቶባቸው በእሳት እየጋዩ ነው። ሰፊ እና ለም የእርሻ መሬት ለሱዳን በስጦታነት ለመስጠት ዝግጁቱ የተጠናቀቀበት ወቅት ላይ ነን። ከአስር ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተርቧል። በፍትህ እጦት እስር ቤቶች በንፁሃን ዜጎች ተሞልተዋል። ውሀ፣ መብራትና የቴሌፎን አገልግሎት ብርቅ ሊሆኑ ነው። ይህ ሁሉ እየሆነ ግን የሥርዓቱ አገልጋዮችና ደጋፊዎች በህንፃ ላይ ህንፃ እየገነቡ በድሀው ላይ ይሳለቃሉ። የህወሓት አገዛዝ ድህነትን፣ ችጋርን፣ ስደትን፣ የእርስበርስ ግጭቶችን እያባባሰ ኢትዮጵያን እየጋጠ የሚኖር አገዛዝ ነው። አገዛዙ በቀደደልን ቦይ ከተጓዝን ችግሮችን ማባባስ እንጂ ማርገብ እንኳን አንችልም። ይህንን ሥርዓት በቃህ ማለት የአማራ ወይም የኦሮሞ አጀንዳ አይደለም፤ ይህ የሁላችንም – የኢትዮጵያዊያን – ጉዳይ ነው።
ለቀምት፣ ሀረር፣ ሱልልታ እና ሌሎች በርካታ የኦሮሚያ ከተሞች ውስጥ ለደረሱ ጥቃቶች ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ሀዋሳ፣ መቀሌ፣ አሶሳ፣ ሁመራ፣ ጋምቤላ ውስጥ ተቃውሞ መሰማት አለበት። በጎንደርና ባህርዳር ለደረሰውም ጥቃት አዳማ፣ ጅማ፣ ሆሳዕና፣ ጅግጅጋ፣ አክሱም ላይ ተቃውሞ መሰማት አለበት። በማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ለሚደርሰው በደል መላዋን ኢትዮጵያ ሊያሳምም ይገባል። መከፋፈላችን መከራችን አብዝቶታል፤ የህወሓት እድሜን አርዝሟል፤ ይብቃ!
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የመከራ ጊዜዓችን እንዲያጥር በዘውግ ሀረግ፣ በብሔርና እና በሀይማኖትና ሳንታጠር የወገናችን ህመም ይሰማን፤ ተሰምቶንም ለጋራ ትግል እንነሳ ይላል።


ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Thursday, December 3, 2015

ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የቀረበውን ይግባኝ ውድቅ አደረገ

December 3,2015
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክር ሆነው እንዳይቀርቡ ያቀረበውን ይግባኝ ዛሬ ህዳር 23/2008 ዓ.ም በዋለው ችሎት ውድቅ አደርጎታል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ተጠይቆ የነበር ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ በተደጋጋሚ ሳያቀርባቸው ቀርቷል፡፡
አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክርነት በተጠሩበት ወቅት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ እንደማይችሉ መቃወሚያ አቅርቦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ይሁንና ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር በመሆኑ ለምስክርነት ሊቀርቡ ይገባል በሚል የፌደራል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ተቃውሞ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
የልደታ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም ቀርበው ምስክርነት እንዲሰጡ ከወሰነ በኋላ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ‹‹ትዕዛዝ አልደረሰኝም፣ የተፃፈው ለቃሊቲ ሳይሆን ለአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት የሚል ነው›› እና ሌሎችም ምክንያቶች በማቅረብ በተደጋጋሚ አቶ አንዳርጋቸውን ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ በስተመጨረሻም ጥቅምት 12/2008 ዓ.ም ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ቃሊቲ እንደሌሉ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ከተከሰሱት መካከል አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) ውጭ ያሉት የፍትህ ሂደቱ እየተጓተተባባቸው በመሆኑ የአንዳርጋቸው ፅጌ ምስክርነት ቀርቶ በሌሎች መረጃዎች ውሳኔ እንዲሰጥላቸው ሲጠይቁ ሁለቱ ተከሳሾች ግን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሊመሰክሩላቸው እንደሚገባ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡
በዚህም መሰረት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይልና አቶ አንዳርጋቸውን ጠይቀውታል ለተባሉት የብሪታኒያ አምባሳደር ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወቃል፡፡ ይሁንና ተከሳሾቹ ለሶስቱ አካላት ደብዳቤውን በፃፉበት ማግስት የፌደራል አቃቤ ህግ ከወራት በፊት ለልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ መመስከር አይገባቸውም ብሎ አቅርቦት የነበረውን መከራከሪያ መሰረት በማድረግ አቶ አንዳርጋቸው ምስክር እንዳይሆኑ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቆ ነበር፡፡
የአቃቤ ህግን ይግባኝ ያየው ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ዛሬ ህዳር 23/2008 ዓ.ም በዋለው ችሎት ‹‹አንድ ሰው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ በሚል ይግባኝ ሊጠየቅበት አይገባም፡፡ ካስፈለገ ግለሰቡ የሰጡት ምስክረነት መረጃው ተመዝኖ የሚሰጠው ፍርድ ላይ ይግባኝ ሊባል ይችላል፡፡ እኛም ጉዳዩን ለማጣራት ምስክርነቱ እንዲቋረጥ አድርገን የነበር ቢሆንም አሁን ግን እንዲቀጥል ወስነናል፡፡ የአቃቤ ህግን ይግባኝም አልተቀበልነውም›› ሲል ይግባኙን ውድቅ አድርጓል፡፡ አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክር መሆን የለባቸውም ብሎ ያቀረበው ክርክር በፍርድ ቤት ውድቅ ሲሆንበት ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከተከሰሱት በተጨማሪ በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል 1ኛ ተከሳሽ አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት ጠርቷቸዋል፡፡ በሌሎች የክስ መዝገቦች ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር ተገናኝታችኋል የተባሉ ተከሳሾችም አቶ አንዳርጋቸውን የመከላከያ ምስክር አድርገው ሊጠሯቸው እንደሚችሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡

የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መገኘት ለኢትዮጵያ ዲሞከራሲ ሀይሎች የጋራ ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው

December 3,2015

ከዚህ ወዲያ አፍ እንዳመጣ “ሽብርተኛ” ማለት የህወሃት መሩ መንግስት እብደት ሆነ!

የፕ/ር ብርሃኑ ነጋን የአውሮፓ ፓርላማ ንግግር በተመለከተ የኢሳት ዘገባን ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ – የቪኦኤ ዘገባ ለማዳመጥ ደግሞ እዚህ ይጫኑ
ቢላል አበጋዝ – ዋሽግተን ዲሲ
ዛሬ ኢትዮጵያ ለህወሃት መሩ መንግስት ተንፈራጦ መግዛት የምትመች አለመሆንዋን ማንም ዜና መከታተል ለሚፈልግ ግልጽ ነው።የህወሃት ባለስልጣናትም ከወትሮው በተለየ መልኩ እርስ በርስ እየተናቆሩ ነው።ተስፋ የቆረጡት ደግሞ ንብረት እያሸሹ ይገኛሉ።በቀይ ባህር አካባቢ አፍሪካ ቀንድን ሊያምስ የሚችል ደመናም ጥሏል ማለት ይቻላል።ሀብታም አረቦችም ልክ እንደ ህወሃት በስጋት ተወጥረዋል።ኢትዮጵያን ማተራመስ ቅር ሳይላቸው ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽሙ ለመሆናቸው የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ይመሰክራል።Professor Berhanu Nega in Eritrea
ከላይ የጠቀስኩት አደጋ ማንጃበቡ ሳያንስ ዛሬ አስራ አምስት ሚሊዮን ወገናችን ለራብ ተዳርጓል።ይህን መከራ በመካድ የጀመረው ህወሃት ህይወት ለማትረፍ የሚጥር አይደለም።በኢትዮጵያ በያለበት እስራትና ግድያው በርትቷል።የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት ስለ ኢትዮጵያ እንዲናገር መጋበዙ ያቀረብኩትን የኢትዮጵያ ሁኔታ ለመንግስታቱ ተወካዮች መግለጽ ብቻ ሳይሆን አጣዳፊ ሁኔታ መፈጠሩንም የማስስጨበጥ ሁኗል። ኢትዮጵያን የፋሺት ኢጣሊያ መንጋጋ ሲያኝካት የተሰደዱ አርበኞች በዓለም መድረክ ጮሆውላት ነበር። ዛሬም በህወሃት መንጋጋ ስትታኘክ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢትዮጵያውያ ወገኖቹ ጋር ሆኖ ድምጹን ከፍ አድርጎ አሰምቶላታል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይህን የፈጸመው በግንባር ሆነው ህወሃት መሩን መንግስት ብርክ እያስያዙ ያሉትን የኢትዮጵያን ጀግኖች ከበረሃ ተለይቶ ነው።
የኢትዮጵያ ሁኔታ ጊዜ የማይሰጥ ነው።ህወሃት መሩ መንግስት በመለስ ዜናዊና ጀሌዎቹ አማካይነት ያፈላው የጥላቻ ጥንስስ ድንገት ሳይፈነዳ አደጋውን ሊገታ የሚችል ዝግጅት ማድረግን ይጠይቃል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሁሉም የሚወከልበት ጊዜያዊ መንግስት ካልቆመ ወያኔ ፈጽሞ የመግዛት ሀይሉን ሊያጣ የሚችልበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም።ህዝቡ በቃኝ ለማለቱ ምልክቶቹ መበራከታቸው ይህን አመላካች ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ሃይማኖትን ተቋማት ጣልቃ በመግባት አዳክሟል።የእስልምና ሃይማኖት ተቋማትን ደፍሮ መሪዎችን ለእስር ዳርጓል።ነጻነትና ዜግነት በየፈጁ ተደፍሯል።
የዓለም መንግስታት በተለይ ሃያላን የኢትዮጵያን ጉዳይ ወደጎን በመተው ህወሃት መሩን መንግስት መወንጀል ሳይሆን በስመ ሽብርተኝነትን መቋቋም አብረውት እየሰሩ ነው።በታሪካችንም የፋሺት ኢጣሊያውን ሙሶሊኒንም አይዞህ ያሉት ነበሩ።ሁሉም ለየራሱ ጥቅም በዓለም ዲፕሎማሲ ሰልፉን ያስተካክላል።በየጊዜውም ይለውጣል።ኢትዮጵያን የምንል አንድ መሆን የግድ የሚለን ጊዜ አሁን ነው።ህወሃት መሩ መንግስትማ ለሙግት፡ለመልስ እንኳን ያቆመው ቅጥረኛ የውጭ አገር ተላላኪን ነው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዋለበት መድረክ።የህወሃት ድንቁርና አንድ መገለጫ ምልክት ነው።የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መግለጫ መስጠት ህወሃት መሩን መንግስት ለሚቃወሙና ለተራበው ከተሜ ገጠሬ ወገናችን ትልቅ ግምት የሚሰጠው ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው።ኢትዮጵያ በዚህ የመከራ ዘመን ለታደጓትን አላህ ለነሱም ይመስክርላቸው።
ድል ለዲሞክራሲያዊ ሀይሎች ሁሉ!
ኢትዮጵያ በአንድነትዋ በነጻነት ለዘለዓለም ትኑር!
አላህ ኢትዮጵያ ይጠብቃት!

Thursday, November 26, 2015

“ረሃቡና ኢህአዴጋዊ እውነታዎች!”

November 26,2015
ኤርሚያስ ለገሰ
ህወሃት መራሹ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ በተከሰተ ቁጥር የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ “የአየር ንብረት መዛባት” በሚል ውጫዊ ምክንያት ማላከኩ የተለመደ ሆኗል። ለአብነት ያህል የዛሬ ዘጠኝ አመት በኢትዮጵያ ረሃብ በተነሳ ወቅት “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” በሚል ረዕስ የውስጥ ድርጀት ሰነድ ተዘጋጅቶ ነበር ደራሲው ጓድ መለስ ዜናዊ ነበሩ። በማስከተልም የፓርቲው ከፍተኛ ካድሬዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት ውይይት እንዲያደርጉበት ተደረገ። በዚህ ሰነድ ገፅ 6 ላይ የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ እንደሚከተለው ይገልጻል።Ermias Legesse of ESAT
“ረሃቡ ከምን እንደሚመነጭ በትክክል ማስቀመጥ መፍትሄውን ለማስቀመጥ ወሳኝ ነው። የረሃቡ ቀጥተኛ ምንጭ ከአየር ንብረት መዛባት ጋር ተያይዞ የተከሰተው ድርቅ ነው። የአየር ንብረቱ መዛባትና ድርቁ እኛ ያልፈጠርነው ልናስተካክለው የማንችለው ነባራዊ ሃቅ ነው። በዚህ ነባራዊ ሁኔታ ማዕቀፍ ድርቁን ተቋቁመን ረሃቡን ለማስወገድ ያስቀመጥነው ስትራቴጂ ተዓምር ሰሪነቱ በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባር ተረጋግጧል። የረሃቡ ዋነና ምንጭም የአየር ንብረት መዛባትና ድርቅ ነባራዊ ሁኔታን መቋቋም ረሃብን ለማጥፋት የቀየስነው ስትራቴጂ በሚፈለገው ፍጥነት በሁሉም አካባቢዎችን ስላልተፈጸመ ነው” ይላል።
እስኪ ይታያችሁ! ከዛሬ ዘጠኝ አመት በፊት (በ 1999 ዓም) የድርቁ መንስዔ የአየር ንብረት መዛባት እንደሆነ ተነገረን። ከዚያ በፊትም ምንጩ ተመሳሳይ ነበር። አሁንማ ልማድ ሆኖብን በኢትዮጵያ ምድር በየሁለት አመቱ ረሃብ የሚከሰት ሲሆን ምንጩ የአየር ንብረት ለውጥ ሆኗል። በነገራችን ላይ በሃገራችን ላይ በተጠቀሰው አመት ድርቁ ወደረሃብ በመቀየሩ ምክንያት በርካታ ህጻናት እና እናቶች ሞተዋል። በአራቱም ማዕዘናት ዜጎች ቀዬአቸውን ለቀው ተሰደዋል። የተፈጠረው አስደንጋጭ ሁኔታ ከህሊና የሚጠፋ አልነበረም።
በዛን ወቅት “በምጥቁ መሪ!” አብዮታዊ አመራር ሰጪነት የተሰራው ወንጀል ዘመን ተሻጋሪና ነገ ከነገ ወዲያ ተጠያቂነትን የሚያመጣ ነው።
እንዲህ ነበር የሆነው፥
በኢትዮጵያ አዲስ ሚሊኒየም ዋዜማ የተከሰተው ድርቅ ወደረሃብ መሸገገሩን የሚያሳይ ረፖርቶች ከመላው ሃገሪቱ መሰማት ጀመሩ። የኢህአዴግ የፕሮፓጋንዳ ማሽን ከዛ አመት በፊት በነበሩት አራት አመታት ኢኮኖሚያችን በሁለት አህዝ አድጓል፥ ሚሊየነር አርሶ አደሮች መፍጠር ችለናል በሚል ቅኝት የሚመራ ስለነበረ ይህን መርዶ ለመቀበል አስቸጋሪ ሆነ። ረሃብን አስወግደናል ብለን ባወጅን ማግስት በረሃብ ተጠቅተን መገኘት በእርግጥም አሳፋሪ ነበር። የአመራርና የማስፈፀም አቅማችን፣ ምርጥ ልምዶች የማስፋት ስትራቴጂያችን ለአለም ተምሳሌት ሆኗል ባልን ጥቂት ቀናት ህዝቡ ረሃቡን መቋቋም አቅቶት እየተሰደደ መሆኑ መመልከት ፕሮፓጋንዳችን “ቢወቅጡት እምቦጭ” እንደሆነ የሚያመላክት ሆነ።
እንደ ተፈራው በዕልፍ አመቱ ዋዜማ የሰው ህይወት በየቦታው መውደቅ ጀመረ፥ ረሃቡን መቋቋም የማንችልበት ሁኔታ ግልፅ ሆኖ ወጣ። የመጀመሪያ ሰሞን እውነታውን አውገርግሮ ከማቅረብ ይልቅ ትክክለኛው መረጃ ተሰብስቦ ወደኢህእዴግ ቢሮ እንዲመጣ ልዩ ውሳኔ ተላለፈ። ለማመን በሚቸግር ሁኔታ የረሃቡ ዋነኛ ሰለባ ከሆኑት አካባቢዎች የሚመጣው መረጃ እጅግ አስፈሪና አስደንጋጭ ሆነ። ከሶማሊያ ጫፍ እስከ አብርሃ አጽብሃ የሚባል የትግራይ ቀበሌ ድረስ ህዝቡ የሚላስ የሚቀመስ ማጣቱ ታወቀ። የከፋ ረሃብ ያጋጠማቸው አካባቢዎች ልጆቻቸውን እየቀበሩ ቀዬአቸውን እየለቀቁ መሰደድ መጀመራቸው እሙን ሆነ።
በሚሊኒየሙ ዋዜማ የችጋሩ ዋነኛ ተጠቂ ከሆኑት አካባቢዎች የመጀመሪያው የሱማሌ ክልል ነበር። የሱማሌ ክልል ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ለስርዓቱ ተገዢ እንዳልሆነ በገሃድ የሚታወቅ እውነታ ነው። በዛ ላይ አካባቢው በጦርነት የሚታመስ መሆኑ የረሃብ አደጋው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አደረገው። በወቅቱ የተፈጠረው ረሃብ በ10ሺዎች የሚጠጉ የቀንድ እና የጋማ ከብቶች መሞታቸው ታወቀ። ከ80 -100 የሚሆኑ ህጻናት በረሃቡ ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ የሚያሳይ መረጃ የስም ዝርዝር ረፖርት ቀረበ።
ይህንን የሱማሊያ የረሃብ ሁኔታ የተቀበለው ጓድ በረከት ከ “ባለራዕዩ መሪ!” ጋር በመነጋገር አንድ ጠንካራ ትዕዛዝ ሰጠ። ጥብቁ ትዕዛዝ “ማንኛውም የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ጋዜጠኛ፣ በመንግስት ክትትል የማይደረግበት በጎ አድርጎት ድርጀት (NGO) ወደሶማሊያ ዝር እንዳይል!” የሚል ነበር። እነሆ ላለፉት 10 አመታት የትኛውም የነጻ ፕሬስ ሆነ የውጭ ጋዜጠኛ ወደሶማሊያ ክልል ልሂድ ብሎ ጥያቄ ቢያቀርብ ኣይፈቀድለትም። ከጓድ በረከት ጋር የቅርብ ወዳጅነት የመሰረቱትም ቢሆን ፍቃድ አያገኙም። የተለያዩ ምክንያቶች እየተሰጣቸው ጥያቄዎች እንዲጥሉ ይደረጋል። በዚህ ምክንያት በሱማሊያ በረሃቡ የሞቱት ህጻናት ከሪፖርቱ ውጪ እንዲሆኑ ተደረገ። እስከ 100 የሚደርሱት ህውየታቸው ያለፉት ህጻናት ማህደር በኢህአዴግ ቢሮ ተቆለፈበት።
በሚሊኒየሙ ዋዜማ ሌላኛው የረሃቡ ተጠቂ አካባቢ ደቡብ ኢትዮጵያ ነበር። ረሃብ ታሪክ ተደርጎበታል የተባለው የደቡብ ኢትዮጵያ በሚሊዮኖች እየረገፉ መሆኑን አስቀድመው መረጃ የመጡት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የውጭ ጋዜጠኞች በመሆናቸው መደበቅ የሚቻል አልነበረም። ከዚህም በተጨማሪ የውጭ ጋዜጠኞች የተፈናቀሉ እና የሞቱ ሰዎች የሚያሳዩት ዘገባዎችን ለዓለም ህዝብ በማስተላለፋቸው ምክንያት መነጋገሪያነቱ ከጫፍ ጫፍ ናኘ። በመሆኑም ነባራዊ ሁኔታውን እንደቅቡል መውሰድ፣ ግን ደግሞ እውነታውን አውረግርጎ ማቅረብ የአቶ መለስ መራሹ የመንግስት የፕሮፓጋንዳ ስትራቴጂ ሆኖ እንዲቀረፅ ተደረገ።
በዚህም ምክንያት የተራበው ህዝብ ከ 14 ሚሊዮን በላይ ቢሆንም ጓድ! መለስ ባዘጋጀው “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” የውስጠ-ድርጅት ሰነድ ጨምሮ የመንግስት ሚዲያ ተቋማት 6.4 ሚሊዮን ብቻ ለረሃብ አደጋ መጋለጣቸው አሳወቁ። በሱማሊያ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ከ500 ያላነሱ ህጻናት በረሃብ ቢሞቱም የፕሮፓጋንዳ ማሽን ከ30 እንደማይበልጡ ይፋ አደረገ። ይህንን አውነታ በማስረጃ ለማስደገፍ ያህል “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” በሚለው የፓርቲ ሰነድ ከገፅ 7-8 የሚከተለውን ይላል፥
“በአንዳንድ የደቡብ አካባቢዎች አደጋውን በወቅቱ ካለማየት ጋር ተያይዞ ባለፈው አመት 26 ያህል ህጻናት ለሞት የተዳረጉበት ሁኔታ ተከስቷል። ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኋላ በረሃብ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች የሉም። አልፎ አልፎ በአፈጻጸም ጉድለት ምክንያት እንደተጠቀሰው የሟች ዜጎች ቢኖሩም በአጠቃላይ በመቶ ሺዎች ቀርቶ በመቶዎች የማይሞቱበት ተፈጥሯል። በተወሰኑ አካባቢዎች የሚታየው የአፈጻጸም ጉድለት ካስተካከልን ምንም ዜጋ የማይሞትበት ሁኔታ መፍጠር እንደምንችልም ጥርጥር የለውም” ይላል።
እንዲህ እውነቱ ተቀናንሶ እና በብዕር ቆንጨራ ተከታትፎ ቢቀርብም በአደባባይ ያለው ሚስጥር ሃቁን መሸፋፈን አልቻለም። ዛሬም ዜጎች በረሃብ ሰቆቃ ውስጥ እየኖሩ ነው። ህይወታቸው እየተቀጠፈ እየተመለከትን “የምጥቁ መሪ!” ተከታዮች ረሃብ የለም ይሉናል። ችግር የተከሰተው “ምናምንቴ” የሚል ስያሜ በተሰጠው አየር መዛባት ምክንያት ድርቅ ስለተከሰተ እንደሆነ ይሰብኩናል። ፍቱን መድሃኒቱም በተግባር የተረጋገጠው “ኪራይ የሚሰበስበው” ስትራቴጂያቸው እንደሆነ ይነግሩናል። ርግጥ ሃቁን በትክክል ቢያስቀምጡ ከትናንትናው ምላሳቸው ጋር ስለሚጣሉ አጣሞ ማቅረብ ግዴታቸው ይሆናል። ምንም እንኳን ያሳምንልናል ብለው የሚያቀርቡት መከራከሪያ ከተጨባጭ ሃቁና መሬት ላይ ካላው እውነታ የትየለሌ በመሆኑ በህዝቡ ትዝብት ላይ ቢወድቁም!….
እዚህ ላይ ማንም አእምሮ ያለውና የአለምን ፖለቲካል ኢኮኖሚ የሚከታተል ሰው የአየር መዛባት፣ የዝናብ እጥረት አልተከሰተም አይልም። ከአገዛዙ ከበለጠ የድርቅ ባህሪያና ትርጉም መረዳት የሚያቅተውም አይደለም። በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በመላው አለም የምግብ ምርት ወይም የውሃ አቅርቦት በመቀነሱ ከፍተኛ ጫና የሚያስከትሉ የእርጥበት እጥረት መከሰቱን የሚክድ የለም። የድርቅ መነሻ ምክንያቱ ከመደበኛ እና ከሚጠበቀው በታች በአየር ጠባይ መለያየት የተነሳ የዝናብ እጥረት መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም። በአለም አቀፍ ደረጃም በአየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት በተለያዩ ዘመናት ሃገሮች በድርቅ ሲጠቁ ተመልክተናል።
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ ባለፈው ክረምት ጓድ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ከውጭ የመጡ የሃገሬ ሰዎች በሚሊኒየም አዳራሽ ሰብስቦ ያሰማው “ኢህአዴጋዊ አውነታ” የኢትዮጵያውያን መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በተለይ በካሊፎርኒያ የአሜሪካ ዜጋ በድርቅ እየተሰቃየ መሆኑ አስረግጦ ሲናገር የተሰማው ጭብጨባ እስከዛሬም ጆሮዬን ይሰቀጥጠናል። የሆነው ሆኖ “ካሊፎርኒያ በድርቅ ተሰቃየች” የሚለው አባባል የትኛውን ግብ ለማሳካት በጭብጨባ እንደታጀበ የሚያውቁት አጨብጫቢዎች ብቻ ቢሆንም የገባንበትን የሰብዕና መላሸቅ አጉልቶ የሚያሳይ ነበር። የአውስትራሊያ አሊያም የካሊፎርኒያ ህዝብ በድርቅ ቢጠቃ ደስ ይለናል ማለት ነው?
የአገጣሚ ነገር ሆኖ የዛሬ ሳምንት እኔና ተወልደ በየነ (ተቦርነ) ለኢሳት የገቢ ማስገኛ ዝግጅት የካሊፎርኒያ እምብርት ወደሆነችው ሎስ አንጀለስ (LA) (ተቦርነ “ላይ አርማጭሆ” ይላታል) ሄደን ነበር። የፕሮግራሙ አዘጋጅ ኮሚቴ የእንኳን ደህና መጣችሁ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ “እንኳን በድርቅ ምክንያት እየተሰቃየች ያለችውን ካሊፎርኒያ በሰላም መጣችሁ!” በሚል ነበር የጀመሩት።
ይህንን የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በአርምሞ ሲያዳምጡ የነበሩት ተሰብሳቢዎች በጭበ አስከትሎም የማያባራ ሳቅ አጀቡት። መቼስ! ተንኮል ካልሆነ በስተቀር ጭብጨባና ሳቅ ምን አመጣው? እንኳንም ጓድ! ሃይለማርያም በስብሰባው አልኖረ! እንኳንም በሚሊኒየም አዳራሽ የተገኙ የካሊፎርኒያ ነዋሪዎች አልሆኑ።
እናማ የስብሰባው አዘጋጆች ፕሮግራም ከተጠናቀቀ በኋላ በያዙልን ዕለታዊ መርሃግብር መሰረት ካሊፎርኒያን ያስጎበኙ ነበር። የድሮ ካድሬ ነገር ሆኖብኝ የምንሄድበት መኪና በቆመ ቁጥር ነጩን፣ ጥቁሩን፣ ስፓኒሹን፣ አፍሪካዊውን ካሊፎርኒያ “ ድርቁ እንዴት ነው? ምን ጉዳት አስከተለ?” የሚል ጥያቄ አነሳ ነበር። ያለማጋነን ጥያቄ ከመለሱልኝ ሰዎች ውስጥ ዘጠና በመቶው ድርቅ መኖሩን አያውቁም። የተቀሩት ውሃ ለመቆጠብ የሻወር ቤታቸውን የውሃ ወንፊት እንዳጠበቡ ነግረውናል። ከፊሎቹ ለውሃ ቁጠባ ሲባል መኪናቸውን በሁለት ሳምንት አንዴ እያጠቡ መሆኑን እያዘኑ አጫውተውናል። ሃዘናቸውንም ተጋርተነዋል። የሻወር ቤት ወንፊት ከማጥበብ፣ መኪናን በሳምንት ሁለት ጊዜ ከማጠብ በላይ ምን ስቃይ አለ? አትክልትን ከሳምንት አምስት ቀን ሁለት ቀን ውሃ እንዲጠጡ ከማድረግ በላይ ምን የሚያበሳጭ ነገር አለ?
የአጋጣሚ ነገር ሆኖ በግዛቱ የመንግስት ተቋም ውስጥ የሚሰራ ሙያተኛ ከአስጎብኚዎች አንዱ ነበር። ግለሰቡ ካሊፎርኒያ ያጋጠማት ችግር ጓድ ሃይለማሪያም ከጠቀሱት በተቃራኒ፣ ከልክ በላይ መብላት የሚመጣ ውፍረት (Obesity) መሆኑን ነገረን። ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ እንዲሉ ወዳጃችን የካሊፎርኒያ ችግር ከመጠን በላይ ምግብ በመብላት እና የአካል እንቅስቃሴ ባለማድረግ የሚመጣ የሰውነት ውፍረት እንደሆነ አጫወተን። በመፍትሄ ደረጃም በግዛቱ በሚገኙ ት/ቤቶች “Child obesity school program” ቀርጸው ተግባራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን ነገረን። በየመቶ ሜትሩ የምናያቸው የተዘረጠጡ ህጻናት ለፕሮግራሙ ተገቢነት የሚያረጋግጡ ነበር። እርግጥም ካሊፎርኒያን ጨምሮ በመላው አሜሪካ ጭንቀትና ስቃዩ የዜጎች የስብ ክምችት መሆኑን ለማወቅ ብዙ መልፋት አይጠበቅም። ለጥቂት ደቂቃዎች ወደኢንተርኔት ጎራ ያለ ሰው ከአሜሪካ አጠቃላይ ህዝብ 78 ሚሊዮኑ (ከዚሁም 12 ሚሊዮን ህጻናት) በውፍረት ግዝፈት መጠቃቱን ይመለከታል። ዘለግ አድርጎ ለተመለከተ ደግሞ የሰውነት ግዝፈት መጠን (obesity rate) በውፍረት በሽታ የግዛቶቹ ተደርድሮ ያያል። ለምሳሌ ካሊፎርኒያ 24.1%፣ ሚሲሲፒ 35%፣ ቨርጂኒያ 35.1% ወዘተ እያለ ይቀጥላል።
እነዚህን የመሳሰሉ ሀገሮች በአየር መዛባት ምክንያት ድርቅ ሲከሰትባቸው ትክክለኛ ፖሊሲ በመቅረፅ ዜጎቻቸውን ታድገዋል። የረጅም እና የአጭር ጊዜ ስትራቴጂካል እቅዶችን ከማውጣት ባሻገር ተስማሚ ቴክኖሎጂ በመምረጥ፣ የውሃ እና አፈር አጠባበቅ ተግባርን በማሻሻል፣ የግብርና ምርት ውጤቶችን ወደውጭ እንዳይወጡ በማገድ፣ የገጠር እና የከተማው ልማት በማቀናጀት… ወዘተ ዘላቂ መፍትሄ አስቀምጠዋል። ከዚህም በተጨማሪ ሰፋፊ ዘመናዊ እርሻዎች በማስፋፋት፣ የግብርና ምርታቸውን በከፍተኛ እጥፍ በማሳደግና፣ የህዝቡን የመግዛት አቃም በማጎልበት በድርቅ ምክንያት የሚከሰተውን አደጋ ከቁጥጥራቸው ውጪ እንዳይሆን አድርገዋል። ድርቅ ተፈጥሯዊ ነውና በማንኛውም ሰዓት ይመጣል፥ ግን ደግሞ እዚህ ግባ የማይባል ጉዳት አያደርስም። በፖለቲካው መስክም ቢሆን የገነቡት ዲሞክራሲያው ስርዓት ሁለንተናዊ ልማት ለማረጋገት የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷል። ያለነጻነት ሁሉን አቀፍ ልማት ማምጣት እንደማይቻል ተገንዝበው ለዜጎቻቸው ነጻነት አጎናጽፈዋል።
እንግዲህ በአለም ያለው እውነታ ይህ ነው። ይሁን እንጂ፣ “ የሞኝ ለቅሶ መልሶ መላልሶ” እንዲሉ ገዢዎቻችን በስልጣን ላይ ከወጡ ጀምሮ በየሁለት አመቱ የሚከሰተውን ከድርቅ የተሻገረ ረሃብ በአየር ጠባይ ለውጥ ምክንያት እንደሆነ ሊያስረዱን ይሞክራሉ። አገዛዙ ስልጣን በያዘ ሁለት አመታት ጀምሮ መጀመሪያ 6 ሚሊዮን፣ ቀጥሎ 10 ሚሊዮን፣ በማስከተል 14 ሚሊዮን ህዝብ በረሃብ ተጋልጦ ነበር። አሁን ደግሞ 15 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊ የረሃብ አደጋ አንዣቦበታል። እነዚህ ጥሬ ሃቆች የሚካዱ አይደሉም። በኢትዮጵያ ቀይ፣ ጥቁር፣ መረሬ አፈር ላይ የተነጠፉ እውነታዎች ናቸው። ዛሬም አገዛዙ በሚከተለው ፖሊሲ ምክንያት ራሳችንን መመገብ አቅቶን አቅማዳችንን ለመጽዋት ክፍት አድርገናል። አገዛዙ ዲሞክራሲያዊ፣ ሰብዓዊና ሌሎች የህዝብ መብቶችን የሚያረጋግጡ ፖሊሲዎችን እስካልቀየረ አሊያም ስርዓቱ እስካልተቀየረ ድረስ የወደፊት እድላችን የከፋ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ሆኗል። የፊተኛው መፍትሄ ኣያለፈበት ይመስላል። የስርዓት ለውጥ የሚለው ደግሞ ይበልጥ ተቀባይነት ማግኘቱ የሚታይበት ሁኔታ ፈጥሯል። ፍጥነቱ በደረሰው መከራ እና አበሳ፣ በደረብን ቁጭት ልክ ባይሆንም። ዞሮ ዞሮ ሃገራችን የገባችበትን የረሃብ አዙሪት ትግሉን ከሚያዘውሩት ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ መሆኑ አልቀረም!

Tuesday, November 24, 2015

በወላይታ ሶዶ ህዝቡን ለትግል የሚያነሳሱ መፈክሮችና ምስሎች በብዛት ተለጠፉ

November 24,2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ
በወላይታ ሶዶ በሦስቱም ክፍለ ከተሞች አርበኞች ግንቦት 7 እያፋፋመው የሚገኘውን የነፃነት አርበኝነት የሚደግፉና ህዝቡን ለትግል የሚያነሳሱ መፈክሮችና ምስሎች በብዛት ተለጠፉ፡፡
ህዝቡ በአርበኞች ግንቦት 7 ሁለገብ የትግል ማዕቀፍ ውስጥ ተሰባስቦ ሁሉም በአንድት ተነስቶ ለተጀመረው ፀረ-ወያኔ፣ ፀረ-አምባገነናዊ የህወሓት አገዛዝ ፍልሚያ የየበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ የሚያስተላልፉት ፅሁፎችና ምስሎች ወላይታ ሶዶን ዳር እስከ ዳር ያጥለቀለቋት እሁድ ዕለት ለሰኞ አጥቢያ ሌሊት ሲሆን ትናንት ከፍተኛ ውጥረትና ግርግር በከተማዋ ሰፍኖ ውሏል፡፡
"የክልሉን አስተዳደር" ጨምሮ የአካባቢው የህወሓት-ደህዴግ ሹሞችን የተቃውሞ ፅሁፎችና ምስሎችን የያዙ ወረቀቶች በሁሉም ቦታዎች ተለጥፈው መታየት በእጅጉ አስደንግጧቸዋል፡፡ 
በአሁኑ ሰዓት ደህንነቶችና የታጠቁ ቡድኖች ያገኙትን ወጣት ሁሉ እያፈሱ ወደ ወህኒ በማጋዝ ላይ ናቸው፡፡
በወላይታ ሶዶ በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች ከተለጠፉት ምስሎች የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀ መንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፎቶ ይገኝበታል፡፡

Saturday, November 21, 2015

በሞት ጥላ መካከል ብሄድ እንኳን ክፉን አልፈራም !!! የሀብታሙ አያሌው መልዕክት ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት

Millions of voices for freedom - UDJ's photo.November 21,2015
የልቤን ምጥ ልፃፈው ብዬ ደጋግሜ ብዕሬን ይዤ ወረቀቱ ላይ ብፅፍም እንደተራበው ወገኔ ሆድ ብዕሬ ባዶ ሆኖ ቀለም አልነጥበው አለ፡፡ በቅሊንጦ ማጎሪያ ቤት ሰማይ ስር ነፍሴ ሀዘን አቆርዝዛ በማይገፉ ቀንና ሌሊቶች ውስጥ ባዘነች፡፡ ለወትሮው ወገኔ እንደከፋው ስሰማ እንደወፍ በርሬ ችግሩን ልጋራው ከመሃሉ እደርስ ነበር፡፡ ዛሬ ግን የህዝቤ ስቃይ ወደ ሰማይ ጉኖ በጠኔ ሲንበረከክ እንደ ጅብራ ተገትረው በማያንቀሳቅሱኝ ወታደሮች ተከብቤ በጭንቀት እየባዘንኩ ከመጠውለግ በቀር አደርገው ነገር አጣሁ ፡፡ ወይ ሀገሬ!!! ወይ ወገኔ!!! 
….. እመነኝ እንዳልኩህ አሁንም እመነኝ … አሁንም እመነኝ !!! እመነኝ ደርግ ወድቋል ኢህአዴግ ይወድቃል፡፡ ዛሬ በአሳሪዎቼ ጡጫ ተደቁሼ፤ ድምፄ በኢትዮዮጵያ ሰማይ ስር ባይሰማም የታገልኩለት እውነት ወደ አደባባይ ወጥቶ ህዝቤ የነፃነት ሻማ እሚጎናፀፍበት ቀን እንደሚመጣ ግን ጥርጥር የለኝም፡፡ 

የልጄ ናፍቆት የሚስቴ ስቃይና እንግልት የእህቶቼ መባከን እና መሳቀቅ አቅሜን ሲፈታተኑት በማዕከላዊ የስቃይ ማማ ስር ጉዳት ያተረፉት ሁለቱ ኩላሊቶቼ የቀን ከሌት ስቃዬን ሲያረዝሙት የነከስኩት ጥርሴ ጉልበቴ አበርትቶ የነፍሴን መዛል ብሸሽግም… ዛሬ ግን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖ የታገልኩለት ህዝብ በረሃብ ጠኔ እየተመታ በሞት ጥላ መንበርከኩን ስሰማ ነፍሴ በውስጤ አለቀች እናም የልቤን ሀዘን እፅፍ ዘንድ ሞከርኩ… ሞከርኩ ግን አቃተኝ….

ጃርት እንደ በላው ዱባ በየቦታው የተፈረካከሰው ፓለቲካችን ዛሬም እርስ በእርስ እየተሸነቋቆጠ ይቀጥላል ወይስ ወገኑን ለመታደግ እንኳ አንድ ይሆናል? ነፍሴ በየእለቱ የምትሟግተኝ ጥያቄ ነው ፡፡ ሳንተባበር ጉልበት አንድ ሳንሆን ኃይል ከወዴት እናገኝ ይሆን ? የአምባገነኖች ጡጫ እየደቆሰን ረሃብ በየዘመኑ የሚቆላንስ እስከመቼ ነው? በእውነቱ በሀሳብ ብዙ ባከንኩ አገኝለት ዘንድ ግን መልስ አጣሁ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር እና የኢትዮጵያ ህዝብ መልስ አጥተው አያውቁም እና ተስፋዬ ፈፅሞ አይመክንም፡፡ 

እናም ያገባናል ለሚሉ ሁሉ እላለሁ የኢትዮጵያ ገፅታ የሚገነባው በየሰርጡ በጠኔ የሚሞቱ የወገኖችን እሬሳ በመደበቅ እንዳልሆነ ካሳለፍናቸው ክፉ ጊዜያት ተምረን ባለን አቅም ተረባርበን ወገኖቻችንን ለመታደግ እንበርታ እላለሁ…!!! በአዲስ አበባ፤ በባህር ዳር፤በአርባ ምንጭ፤ በጎንደር፤ በደሴ፤ በአዳማ፤ በአዋሳ፤ በወላይታ ህዝብ በሚንቀለቀል የለውጥ ፍላጎት ድምፁን ባሰማባቸው ሰላማዊ ሰልፎች… ‹‹ኢህአዴግ ከታሪክ ይማር፤›› ‹‹አምባገነኖች ባሉበት ሀገር የጀግና ሞቱ እስር ቤት ነው ፤›› ‹‹ታጋይ ይታሰራል ትግሉ ይቀጥላል፤ ›› ‹‹ እጃችን ባዶ ነው እነዚህ አምባገነኖች ነገ አሸባሪ ይሉናል›› ፤ ‹‹እመነኝ ደርግ ይወድቃል ኢህአዴግም ይወድቃል›› ማለታችንን ….. በእርግጥም ልክ ነበርን፡፡ ዛሬ አሸባሪ ተብለን ከትግል አጋሮቼ ከዳንኤል ሺበሺ ፤አብርሃ ደስታ ፤ የሺዋስ አሰፋ ፤አንዷለም አራጌ፤ ተመስገን ደሳለኝ ፤እስክንድር ነጋ ፤ ወዘተ…. ስፍር ቁጥር ከሌላቸው ውድ የኢትዮጵያ ልጆች ጋር የነፃነት ቀንን እየናፈቅን በእስር ቤት አለን ፡፡ የፍርድ ቤት ድራማውም ተጠናክሮ ቀጥሏል ፍርድ ቤቶችን ከጀርባ ቆመው የሚዘውሩ በቀጭን ትዕዛዝ ማረሚያ ቤቶችን የሚያሽቆጠቁጡ፤ በፍትህ ስም የሚቀልዱ ፓርቲዬን ያፈረሱ፤ የህዝቤን ተስፋ ለማምከን ቀን ከሌት የሚደክሙ የካዛንቺሱ መንግስቶች እጃቸው የሚያጥርበትን ቀን አብዝተን እንናፍቃለን ፡፡

በእውነት እላለሁ በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ ክፉን አልፈራም !!!

Thursday, November 19, 2015

አሁንም እስረኞች ነን - ከዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የተሰጠ መግለጫ

November 19,2015
ከሚያዝያ 17 2006 ጀምሮ በፓሊስ ቁጥጥር ስርውለን የነበርነው 3 ጋዜጠኞችና እና 6 የዞን9 ጦማርያን ከአንድአመት ከሁለት ወር እና ከአንድ አመት ከ5 ወር የእስር ቆይታ በኋላ ሁላችንም ከእስር አንደተፈታን ይታወሳል፡፡ በሃምሌ ወር መጀመሪያሶስት ጋዜጠኞች እና ሁለት ጦማርያን አቃቤ ህግ ክስ አቋርጦ፣ በማስከተል አራት ጦማርያን ደግሞ ነጻ ተብለው ከእስር መለቀቃችንየሚታወስ ሲሆን ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ በዋስትና ላይ ሆኖ የቀረበበትን “አመጽ የማነሳሳት ክስ” እንዲከላከል መባሉም ይታወቃል፡፡

ይሁን አንጂ የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ከተፈታን ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ነጻ አለመውጣታችንን የሚያሳዩ ተደጋጋሚ ተግዳሮቶች በመኖራቸውእና ሊቀየሩም ባለመቻላቸው ይህንን መግለጫ ለማውጣት ተገደናል፡፡

1.     የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ32 በሚደነግገው መሰረት “ ማንኛውም ኢትዮጲያዊ … በፈለገው ጊዜ ከአገር መውጣት ነጻነትን” በሚጻረር መልኩ “የመንቀሳቀስ መብታችን”አሁንም ተገድቧል፡፡ ለምሳሌ ጦማሪ ዘላለም ክብረት ህዳር 7/2008 በፈረንሳይ አገር በሪፓርተርስ ሳንስ ፍሮንቲየርስ (ድንበርየለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት) ለዞን 9 ጦማር የተበረከተውን 2015 የሲቲዝንጆርናሊዝም ሽልማት የዞን9 ጦማርን ወክሎ ለመገኘት ህዳር 6/2008 ቦሌ አየር ማረፊያ ቢገኝም ባልታወቀ ምክንያት ከአገር መውጣት ተከልክሎ ፓስፓርቱንምተቀምቷል፡፡ በዚህም የተነሳ የሚቀጥለው ሳምንት በሚከናወነው በአለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ የሆነ የሲፒጄ የፕሬስ ነጻነት ሽልማት ላይ መገኘቱን እድልም በጣም አጥብቦታል ፡፡

2.    ጦማሪ አቤል ዋበላ (የኢትዮጵያአየር መንገድ ኢንጂነር) ፣ ጦማሪ ዘላለም ክብረት (የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር) ጦማሪት ማህሌት ፋንታሁን( የጤና ጥበቃሚኒስትር የዳታ ኦፌሰር) እና ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ (በፕላን ኢንተርናሽናል የኮምኒኬሽን እና ኖውሌጅ ማኔጅመንት ሰራተኛ) ወደስራገበታችን መመለስ አልቻልንም ፡፡ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ በሆነው መንገድ ተገደን ከአንድ አመት በላይ እስር ቤት መቆየታችን የእኛ ጥፋትአንደሆነ ተቆጥሮ ከስራ ተባረናል ፡፡ሌሎቻችንም በግል እንሰራቸው የነበሩ ስራዎችንም መቀጠል አልቻልንም ፡፡

3.    ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከክሳችሁሙሉ ለሙሉ ነጻ ወጥታችኋል ብሎ የበየነልን ሶስት ጦማርያን ስንያዝ “ማአከላዊ” ምርመራ የተወሰደብን ፓስፓርታችን እና ሌሎች እቃዎቻችንእንዲመለሱልን ብንጠይቅም “ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባችኋል” በሚል ሰበብ እስካሁን አልተመለሱልንም፡፡

4.    ቢቢሲ አንደዘገበው የኢፌዴሪጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ አሁንም “ ታስረው የነበሩት ጋዜጠኞች እና ጦማርያን የእውነት ጋዜጠኞች አይደሉም ከሽብርጋር ግንኙነት አላቸው” በማለታቸው እንዲሁም የተለያዬ የመንግስት ባለስልጣናት የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ የሚሰጡት አስተያየት ፍርድቤቱ ያወጀልንን ነጻነታችንን ኢ- ህገመንግስታዊ በሆነ መንገድ እየናደው ነው ፡፡

በእነዚህእና በሌሎች ጫናዎች ምክንያት ራሳችንን ሳንሱር አንድናደርግ እና ሁሉም ጉዳያችን በእንጥልጥል ላይ ያለ የቁም እስረኞች የሆንንእንዲመስለን እየተደረገ ነው ፡፡ ስለሆነም

-      ህግ መንግስታዊ መብታችን የሆነውእና ምንም ህጋዊ ገደብ ያልተቀመጠበት በነጻነት የመንቀሳቀስ መብት መብታችን እንዲመለስልን
-      በኢግዚቢት ስም በማእከላዊምርምራ የሚገኙት እና ካለምንም ህጋዊ ምክንያት የተያዙት ፓስፓርት እና ሌሎች የግል እቃዎቻችን እንዲመለሱልን

-      መንግሰት የራሱን ፍርድ ቤትውሳኔ አክብሮ አሁንም ወንጀለኛ ስያሜ የሚሰጠንን ስም ማጥፋት እና የእጅ አዙር ጫና አንዲያቆምልን
-      የፓለቲካ ታማኝነትን ለማሳየትያለህግ አግባብ ወደስራ ገበታችን አንዳንመለስ ያደረጉን አካላት ውሳኔያቸውን መለስ ብለው እንዲያዩልን እንጠይቃለን፡፡

ሕገ መንግስቱ ይከበር
ዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

Wednesday, November 18, 2015

“ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት” ረሃቡን በሚመለከት የስራ እቅዶችን አውጥቷል

November 18,2015

ረሃቡን በሚመለከት የተሰጠ መግለጫ፣ ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት (Global Alliance for the Rights of Ethiopians – GARE)

ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት ከተቋቋመበት ወቅት ጀምሮ ለኢትዮጵያዊያን ወገኖቹ በያሉበት ለሚደርስባቸው ግፍና ችግር ያልተቆጠበ ጥረት በማካሄድ ላይ ይገኛል። በዚሁ መሰረት በሳውዲ አረቢያ፤ በየመን፤ በሊቢያ፤ በኬንያ፤ በሰሜን ሱዳንና በማላዊ ችግር ለገጠማቸው ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የገንዘብ፤ የዲፕሎማሲ፤ የምክርና ሌሎች ድጋፎች አድርጓል። ይኼ ግዙፍ ድጋፍ ስኬታማ ሊሆን የቻለበት ዋና ምክንያት ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በያሉበት የገንዘብ ድጋፍ ስላደረጉ ነው። ድርጅታችን እነዚህን ደጋፊዎች ያመሰግናል።Global Alliance for the Rights of Ethiopians (GARE)
አሁን የተከሰተውን የድርቅ ረሃብ፤ ቢቢሲ የተባለው ድርጅትና ሌሎች ተቋሞች ከዛሬ ሰላሳ ዓመታት በፊት “ከተከሰተው የድርቅ ረሃብ የማያንስና አሳሳቢ ነው” ያሉትን ረሃብ በሚመለከት ድርጅታችን መረጃዎችን ሰብስⶅ የችግሩን ጥልቀትና ስፋት ተገንዝቧል። የስራ እቅዶችን አውጥቷል። የኢትዮጵያ መንግሥት “እኔ ራሴ እወጣዋለሁ” ያለውን ብናውቅም፤ በሌላ በኩል የችግሩን መጠን በመረዳት መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድርጅት፤ ወዘተ እና በያሉበት ለኢትዮጵያዊያን ያቀረበውን የድጋፍ ጥሪ በጽሞና ተመልክተነዋል። የተጎዱት ወገኖቻችን ቁጥር ወደ አስራ አምስት ሚሊየን እንደሚደርስ መታወቁ ብቻ ሳይሆን፤ በእኛ ግምትና ግንዛቤ በድርቅ ረሃብ ምክንያት አንድ ህጻን፤ አንድ እናት ወይንም አንድ አባት መሞት የለበትም።
ድርጅታችን ማንኛውም ከሕዝብ የሚሰበሰብ ገንዘብ፤ ተጠያቂነት፤ ግልፅነትና ሃላፊነት ባለው መልክ፤ መንገድና ድርጅት አማካይነት ለተጠቃሚዎች መድረስ አለበት የሚል መርህ ሲከተል ቆይቷል። ከInternational Organization for Migration (IOM) ያደረግነውና አሁንም የምናደርገው ስራ ምሳሌ ነው። በዚህም መሰረት ትብብሩ አግባብ ያላቸውን፤ በረሃቡ ዙሪያ በኢትዮጵያ ሰብአዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋሞችን ሲያነጋግር ቆይቶ በቅርቡ አጥጋቢ መልስ እንደሚደርሰውና ከስምምነት ላይ እንደሚደርስ ይተማመናል።
ይኼን በሚመለከት ትብብሩን በመወከል በNovember 17, 2015 በኢሳት ሬዲዮ ለታዳሚዎች አንደገለጽነው በሚከተሉት ቀናቶችና ሳምንታት ትኩረት የምንሰጠው በረሃብ ለሚሰቃዩ ወገኖቻችን ድርሻችን ለመወጣት የተቀነባበር የገንዘብ ስብሰባ ዘመቻ ማካሄድና የተሰበሰበው ገንዘብ ለተጠቃሚዎቹ እንዲደርስ ማድረግ ነው። በዚህ አጋጣሚ ከዚህ በፊት በየአካባቢው ያልተቆጠበ ጥረት ላደረጉት፤ ለወገኖቻችን እንደርስላቸው ለሚሉትና ለሌሎች ጥሪ የምናደርገው በያላችሁበት የገንዘብ መሰብሰብ ጥረቱን እንድትቀጥሉ፤ ያልጀመራችሁ እንድትጀምሩና ላልሰሙት እንድታሰሙ ነው።
የትብብሩን ድጋፍ የምትፈልጉ በቴሌፎንና በኢሜይል ለመገናኘትና የተዋጣውን ገንዘብ በትብብሩ ባንክ ለመላክ እንደምትችሉ እናሳስባለን።
4ruleoflaw@gmail.com
Tele: 877-746-4384
www.DefendEthiopians.org

Monday, November 16, 2015

The 2015-16 Ethiopian Famine: Yet Another Avoidable Tragedy is Underway!

November 16,2015
Ethiopiawinnet: Council for the Defense of Citizen Rights
Just as the world’s leading development agencies are vowing to finally make poverty history in the four corners of the globe and they are heaping praises on the Ethiopian Government for its “double-digit” economic growth rates and self-serving rhetoric about “transformation,” Ethiopia is once again under the grips of what appears to be yet another famine of “biblical proportion.” The World Food Program of the United Nations and the Government itself have announced that over 8 million Ethiopians are at the risk of death by starvation. Chronically food-deficit areas have been hit by El Nino-related failures of both the small and the big rainy seasons this year.
We must underscore two things at the outset. First, predictable weather-related or pest-related shocks to the food system should not result in mass starvation or high mortality in the presence of an accountable government with a capacity to feed its people. Drought may be an act of God but famine is surely a political act of man. Second, The Citizens Charter for a Democratic Ethiopia embraces the greatest of all human rights—the right to life. Basic food security for all is, therefore, the most fundamental right to which all Ethiopians are entitled. This is why eliminating famine is the litmus test for all who profess commitment to human rights and democratic accountability.
The world has made a remarkable progress over the past 25 years. Millions of Ethiopians are among the one billion people lifted out of debilitating poverty. National and regional famines that claimed the lives of millions in South Asia and Sub-Saharan Africa are thankfully a thing of the past, save the most an unpredictable natural catastrophe. To understand why Ethiopia remains so vulnerable to chronic hunger even in normal years, one needs to keep the following facts in mind:
  • One out ten rural Ethiopian (or 8 million out of 80 million) suffer chronic hunger (under-nutrition and malnutrition), especially during the hunger season between May and September. This is because the lack of adequate land, water, and income diversification has hopelessly eroded the livelihoods of so many. Entire districts have thereby been rendered highly vulnerable to even moderate shocks let alone a total failure of the rains or significant food-price inflation (which also hits the urban poor hard). In this respect, it is quite telling that about half of the $1 billion U.S. annual aid to Ethiopia is food aid—mostly going to the food-for-work program that alleviates food insecurity rather than eradicating it for good.
  • Many more millions live just above this precarious subsistence line even in years of normal rainfall. Drought, pest invasion or civil strife swell the ranks of the starving in short order, with the negative effects persisting for at least a decade. It is no surprise then that Ethiopia faced regional famines in 1965/66, 2000/01, and 2011/12; and regime-destabilizing national famines in 1972-73 and 1974-85.
  • The 2015-16 famine underway bears the telltale signs a national tragedy and must be averted with decisive action. The current is already being compared in its potential devastation, by the survivors, to the infamous 1984 famine of Live Aid (which claimed over 1 million lives). A good indicator of this impending disaster is its national scope: the chronically food-deficit areas of southeastern Tigray, northeastern Wollo, all of Afar and parts of Somali, the southern lowlands of Sidamo and Bale, and the Enset-dependent areas southwestern Ethiopia.
  • In the fine tradition of unaccountable governments torn between publicly revealing the extent of the famine (terrified by the political fallouts) and their strong incentive to tap into international assistance (the donor practice of feeding the greedy to reach the needy), the Ethiopian Government is currently denying the patently obvious mounting loss of livestock and the rising mortality of the most enfeebled (as attested by BBC TV) while claiming to have allocated half of the relief supplies required from its own resources. While we are encouraged by the improved early warning system and the allocation of domestic funds, we are unimpressed by their inadequacy relative to the needs and to what is being spent on white elephant projects. We are also offended by the shameful insinuation of high government officials that it is ultimately the responsibility of the international community to save the most vulnerable in Ethiopia.
Ethiopiawinnet is compelled to implore:
1. The Ethiopian Government to own up to its sole responsibility to spare all its citizens from starvation and death by devoting all the resources necessary to tide them over to the next harvest. In the medium run, it should reform its land policy by granting ownership rights to farmers and pastoralists, invest in food production for domestic use instead of only exports, fostering off-farm employment opportunities, scrapping the current ethnic homeland system of regional administration that has hamstrung the traditional coping mechanism of seasonal inter-regional migration to work, and accelerating industrial development.
2. The international community to once again provide generous and timely relief aid to avert large losses of lives instead of waiting for large-scale deaths as “proof of need.” We also implore donors to insist on sensible food security policies that would make such recurrent dependency on food aid unnecessary for a country that has a great potential to feed itself.
3. All Ethiopians and friends of Ethiopia in the Diaspora to put politics aside for now and extend a generous helping hand through famine relief organizations with a proven record. Thank you.
Ethiopiawinnet, a rights-based CSO, believes that:
  • Famine is a political act of transgression on the mother of all human rights—the right to live.
  • Drought may be unavoidable, but famine certainly is. In the twenty-first century, this abomination belongs nowhere else but in the dustbin of history!

Sunday, November 15, 2015

የወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ውጤቱ ጦርነት ነዉ! (የጎንደር ሕብረት)

November 15,2015
ልዩ መግለጫ
በጎንደር ክፍለሃገር ፤ በላይ አርማጭሆ ወረዳ፤ ልዩ ቦታው ማዉራ፤ ሮቢት፤ ጫጭቁና፤ ጋባ ጋላገር እንዲሁም ሌላም ብዙ አካባቢወች እና ከዚህ ቀደም ሲል ደግሞ፤ በጭልጋ አካባቢ ወገኖቻችን ላይ የወያኔ ሰራዊት የፈጸመዉን ኢሰባዊ ጭፍጨፋ በጥብቅ እናወግዛለን። ኢትዮጵያዊ ቆዳ ለብሶ፤ በሞሶሎኒ ጭንቅላት የሚያስበው ወያኔ፤ ገና ሲፈጠር ጀምሮ፤ ለዘመናት ሃይማኖት ፤ ቋንቋ ፤ ዘር ሳይገድበዉ አብሮ የኖረ ህዝባችንን፤ ከፋፍሎ እድሜ ልኩን ለመግዛት ሲል፤ በጎሳ ነፃነት ስም አንቀጽ 39ኝን በማር የተለወሰ መርዙን ለመላ ሕዝባችን እየጋተ አገራችንን እያተራመሰ ይገኛል። ይህ የጎሳ ፖለቲካው፤ በየተኛውም አካባቢ፤ ሰላም እና መረጋጋትን እንዳላመጣ በተግባር እያየ እንኳ ከሥህተቱ የማይማረው ግትር መንግሥት፤ በመሽ ሰዓት ወደ ሰሜኗ ክፍለ ሀገራችን ጎንደር ላይ ለመተግበር እየሞከረ ባለው የክልል ጣጣ ምክንያት፤ በጋባ፤ ትክል ድንጋይና እና በጭልጋ አካባቢ በከፈተዉ ጦርነት የንጹህ ወገኖቻችንን ህይወት ማጥፋቱ እጅግ አሳዝኖናል። በጣም የሚያስቆጨውና የሚያሳዝነው ደግሞ የወያኔ መንግሥት ሆን ብሎ አስቦና ተዘጋጅቶ አርሶ አደሩ በሳለም አርሶ ከሚኖርበት ቀየው ድረስ በመሄድ የፈጸመው የግፍ ጭፍጨፋ በመሆኑ ነው።gonder-unity
ይህ መንግሥት ተብዬ የአሸባሪ ቡድን፤ እንዲህ አይነቱን ግፍ ሲፈጸም የመጀመሪያው ባይሆንም የመጨረሻው እንደማይሆን እርግጠኞች ነን። በአሁኑ ሰዓት እየተካሄደ ባለው ጦርነት ህጻናት፤ ከቤት የዋሉ አረጋዊያን፤ እሴቱች ሳይቀሩ መገደላቸውን በአካባቢው የሚኖሩ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። አሁንም የፌደራል ወታደር ከቤት፤ ቤት እየተዘዋወረ ሰላማዊ ዜጎችን እያፈነ ነው። ሕዝቡም ቤቱን እና ንብረቱን ለማስከበር ሳይወድ በግድ ከመጣው ወራሪ ጦር ጋር እየተጋፈጠ ይገኛል። የወያኔ መንግሥት እንዲህ አይነቱን አረመኒያዊ ጭፍጨፋ በጎንደር ህዝብ ላይ የጀመረው ዛሬ ሳይሆን ሥልጣን ከመያዙ በፊት ጀምሮ በወልቃይት ጠገዴ እና በጠለምት ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ የዘር ማጥፋት እርምጃን በመውሰድ ነው። አሁንም ይህንን እኩይ ተግባሩን እንደቀጠለ ነው። ወያኔ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ፤ የህዝብን ጥያቄ በሰላም እና በዴሞክራሲዊ መንገድ የሚያሰተናግድ መንግሥት አለመሆኑን በተላያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እያደረግ ያለውን ጭፍጨፋ መመልከቱ በቂ ነው። ከእባብ እንቁላል እርግብ እንደማይገኝ ሁሉ፤ ከወያኔ መንግሥትም ሰላም እና ዴሞክራሲ ይገኛል ብሎ መጠበቅ እራስን ማታለል ነው።
በመሆኑም፤ ይህ አርመኔያዊ፤ ጨፍጫፊ እና ከፋፋይ ሥራዓት በየተራ በየአካባቢያችን እየዘለቀ በልቶን ከመጨረሱ በፊት፤ የጎንደር ህዝብ ትጥቁን ሳይፈታ በአንድነት ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በመተባበር ከማስወገድ ውጪ፤ ፈጽሞ ሌላ የተሻለ አማራጭ የለዉም። ይህ ካልሆነ መሬት መንጠቁን፤ በዘር እየከፋፈለ ርስ በርስ ማዋጋቱን እና መከፋፈሉን ያለማቋረጥ ይቀጥላል።
ጎንድር የአማራዉ፤ የቅማንቱ፤ የሽናሻዉ፤ የቤተ እስራኤሉ፤ የአገዉ የጋራ ርስት አገሩ ናት። ጎንደርን በጎሳ ለመከፋፈል እየተሞከር ያለው እቅድ፤ ከጥፋት ላይ ጥፋት ከመሆኑም በላይ ለቅድስት አገራችን ኢትዮጳያም የተቀነባበረ የብተና ሞሶሎኒያዊ የወያኔ አደጋ ነዉ።
ወያኔ በአሁኑ ሰዓት በጎንደር ዙሪያ እየሰራ ያለው መሰሪ ተንኮል፤ በአንድ በኩል ለቅማንት ብሄረሰብ የሰጠውን አነስተኛ ቀበሌ ለመከለል፤ ጥቂቶችን ሲያስገድድ፤ በሌላ በኩል የጠየቁትን ሙሉውን ቀበሌ ማግኘት ይገባናል? የሚሉ ካድሬወችን በብዙ ገንዘብ ቀጥሮ ወደ ህዝቡ አሰርጎ በማሥገባት ህብረተሰቡ ዕርስ በርሱ ቅራኔ ውሥጥ እንዲገባ በመገፋፋት፤ ጎንደርን የመገነጣጠል አላማውን ለማሳካት ሌተ ከቀን የጥፋት ስራዉን እየሰራ ይገኛል። የተከበርከዉ ጀግናዉ የጎንደር ህዝብ ሆይ! ከምንጊዜዉም በበለጠ አንድነትህን አጠናክረህ ትጥቅህን አጥብቀህ ታሪካዊ ጎንደርን አድን። ለሃያ ዓምስት ዓመታት የወልቃይት ጠገዴ፤ የጠለምት ሁመራ መሬትህ በትግራይ ነጻ አዉጭ ነኝ በሚሉ ባንዳወች ተወሮ ተዘርፏል፤ የዘር ማጥፋትና አፈናቅሎ የማጽዳት ጭፍጨፋ ተፈጽሞበት ጩሆቱን እያሰማ ይገኛል።
ነጻነት በልመና አይገኝምና ተባብረህ የሰባቱም አዉራጃ ህዝብ በአንድነት ዘረኛ ወራሪዉን ወያኔ ከታሪካዊ መሬትህ ጠራርገህ አስወጣ። በጎንደር የሚኖር የትግራይ ተወላጆች ሁሉ በጎንደር መሬት የመኖር ገደብ የሌለዉ የኢትዮጵያዊነት መብታቸው ነዉ። ካድሬወች፤ ሰላዮች፤ ጦረኛ ወራሪ ታጣቂወች ግን የጎንደር ህዝብ ፍጹም አይፈልጋቸዉም፤ በግፈ ትዉልድ ጨርሰዋልና፤ በአስቸኳይ መዉጣት አለባቸዉ። ዛሬ በአንድ አካባቢ ያለው ወገንህ በግፈኛው ቡድን በወያኔ ሲጨፈጨፍ፤ አሻግረህ እያየህ ተራህን ከመጠበቅ ይልቅ፤ “ሳይቃጠል፤ በቅጠል” እንዲሉ፤ እዚያው ችግሩን ከጫረበት ቦታ ድረስ በመሄድ እና ተባብረህ በመዋጋት ለአንዴና ለመጨረሻ ነፃነትክን ተጎናጸፍ። የጎንደር ሕዝብ ወራሪና ከፋፋይ ሃይልን መሸከም ይብቃው።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! የጎንደር አርሶ አደር ከበደል ላይ በደል ተደራርቦበታል። ሱዳን አዝመራውን እያቃጠለ ፊት ለፊት ሲወጋዉ፤ ወያኔ ከኋላዉ ሃብቱን ይዘርፋል፤ ሚሊሻዉን ወደ ጎንደር ለም መሬቶች ያሰማራል። ይህንን አገራዊ ስሜት የሌለውን የዘረኛ መንግሥት የኢትዮጵያ ህዝብ ተከፋፍሎ ወይም ወኔ በሌለው ስሜት ከዳር ቆሞ ከንፈር መምጠጥ እና በባዶ ቁጭት እራስን ማቃጠል ሳይሆን፤ በቆራጥነት በጋራ ሆ! ብሎ በመነሳት ተባብሮ ማሥወገድ ይገባዋል።
የጎንደር ህብረት በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸዉ ወገኖቻችን መራራ ሃዘናችን እየገለጽን፤ ከርሃቡ በላይ በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባችዉን ለመርዳት ከጎንደር ህዝብ ጎን እንደምንቆም እያረጋገጥን፤ እንዲሁም ለዚህ ጉዳት ዋነኛ ተጠያቂ ወያኔ የሚመራዉ መንግስት ስለሆነ፤ እጁን በአስቸኳይ ከህዝባችን ጫንቃ ላይ እንዲያነሳ እንጠይቃለን። በመጨረሻም፤ በማንኛውም በክፍለ ሀገሩ ላይ የሚደርሱ ችግሮችን አሥመልክቶ መላዉ የጎንደር ህዝብ ተባብሮ እና ተመካክሮ እንደጥንቱ እንዲፈታ ጥሪያችን እናቀርባለን።
ጎንደርን በአንድነት እናድን። ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
ከጎንደር ህብረት

Saturday, November 14, 2015

በረሀብ ለተጠቁ ወገኖቻችን እንድረስላቸው !!!

November 14, 2015
def-thumbበወቅታዊ ሁኔታ ላይ የአርበኞች ግንቦት 7 የአቋም መግለጫ
የኢትዮጵያ ሕዝብ ዳግም ለአስከፊ ረሀብና ችጋር ተጋልጧል፤ ስፋት ጥልቀቱ በ70ዎቹና 80ዎቹ ከነበሩት ጋር ይስተካከላል ተብሎ ተፈርቷል። ከአሁኑ ሰው በረሀብ መሞት መጀመሩ ከአራትና አምስት ወራት በኋላ የሚመጣውን አደጋ ከባድነት መገመት ያስችላል።
ለአስር ተከታታይ ዓመታት ከአስር በመቶ በላይ ዓመታዊ የኢኮኖሚ እድገት በማምጣት ዓለምን እየመራን ነው የሚለው ዓይን ያወጣ ውሸት፤ “ድህነትን ተረት እናደርጋለን” የሚለው ጉረኛ መፈክር፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ራድዮ “የህዳሴ ብስራቶች”፣ የአባይ ግድብና የከተማ ባቡር ግንባታ ዜናዎች ለኢትዮጵያዊው አርሶ አደር ቁርስ፣ ምሳና እራት አልሆኑም።
“አድገናል”፣ “ተመንድገናል”፣ “በምግብ ራሳችንን ችለናል” ሲል የከረመው የህወሓት አገዛዝ የረሀቡ ዜና አፈትልኮ ሲወጣ እና የዓለም መገናኛ ብዙሀን መነጋገሪያ ሲሆን የተራበውን ወገናችንን ለማብላት ከመሯሯጥ ይልቅ ተፈጥሮ ላይ ማላከኩን ተያይዞታል። ከዚህ አልፎ ዓመታዊ ድግሶቹ እና ለባለሥልጣናቱ የሚሰጡ ጥቅማጥቅሞች ጉዳይ ከረሀብ በላይ አሳሳቢ በመሆኑ 15 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ በሞት አፋፍ ላይ እያለ የአገሪቱ ሀብት ለድግስና ፈንጠዚያ እንዲሁም ለእያንዳንዱ ባለሥልጣን ቤተመንግሥት አከል መኖሪያ ቤት ማሠሪያ እየዋለ ነው። መቀሌ ላይ ህወሃት 40ኛ ልደቱን ለማክበር ወደ ግማሽ ቢልዮን ብር ባወጣ ማግስት በአማራ ስም ለወያኔ ባርነት የገባው ብአዴን 300 ሚሊዮን ወጪ በማድረግ በረሃብተኛው ሕዝብ አናት ላይ እየጨፈረ ነው:: ይህ የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቅ ብቻ ሳይሆን ደግሞ ደጋግሞ ከመግደል የሚቆጠር ወንጀል ነው።
ለመሆኑ የአየር ንብረት መዛባት እየተደጋገመ ለሚመጣ ችጋርና ቸነፈር በቂ ምክንያት ሆኖ ያውቃልን? ለምንድነው ፍትህና ነፃነት በሰፈነባቸው አገሮች ውስጥ ዝናብ ጠፍቶ የእርሻ ምርት ቢቀንስ እንኳን ሰው በረሀብ የማይሞተው? አስከፊ የረሀብ ዜናዎች የሚሰማባቸው አገሮች በሙሉ ነፃነት የታፈነባቸው አገሮች መሆናቸውስ የአጋጣሚ ጉዳይ ነው? ለምንድነው ተደጋግሞ ከሚመጣ የረሀብ አዙሪት መውጣት ያቃተን?
የእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ አጭርና ቀጥተኛ ነው። ለችግሮች መፍትሄ መሻት የሚቻለው በነፃነት ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ሲኖር ነው። በባርነት ጨለማ ውስጥ ያለ ጭንቅላት ለችግሮች መፍትሄ የማፍለቅ አቅም የለውም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነቱ ድኩም ጭንቅላት ችግሮችን ማሸነፍ ሳይሆን ተሸናፊነትን ተቀብሎ ከችግሮች ጋር ተስማምቶና ተወዳጅቶ መኖርን ይመርጣል። ለዚህም ነው የአስተዳደር በደልና ረሀብ ምክንያትና ውጤት ብቻ ሳይሆን እጅና ጓንትም ጭምር የሆኑት።
ነፃነት ያለው ሕዝብ ረሀብን እንደሚያሸነፍ ተደጋግሞ የታየ ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው ረሀብን የተፈጥሮ ሚዛን መዛባት ውጤት ብቻ አድርጎ ማቅረብ እውነትን መሸፈጥ የሚሆነው። ረሀብ የብልሹ አስተዳደር ውጤት መሆኑ ያፈጠጠ፣ ያገጠጠ ሀቅ ነው። ከረሀብ መገላገያ መንገድም የተበላሸ አስተዳደር ተወግዶ ኃላፊነት የሚሰማው፣ የዜጎች የማሰብ ነፃነት የሚያረጋግጥ ሕዝባዊ አስተዳደር ሲኖር ነው።
አገራችን ኢትዮጵያን የረሀብ ቀጠና ካደረጉ የ24 ዓመታት የወያኔ “የዘርፈህ ብላ” የኢኮኖሚ ፓሊሲ ውጤቶች መካከል አንዳንዱን ለአብነት ያህል መዘርዘር ይቻላል።
1.ገበሬና መሬት ተለያይተዋል። ኢትዮጵያዊያን አርሶ አደሮች መሬት አልባ ሆነዋል። ለም መሬቶች በኢንቨስትመንት ስም ለህወሓት ጉልተኞችና ምስለኔዎቻቸው ታድሏል፤ እነሱ ደግሞ በተራቸው ለባዕዳን ሽጠውታል። ኢትዮጵያዊው አርሶ አደር በሀገሩ ጭሰኝነት እንኳን አጥቶ ለቀን ሠራተኝነትና ልመና ተዳርጓል። በዚህም ምክንያት ገበሬው እንኳንስ ትልቁን የአየር መዛባት ትንሿንም የዋጋ ንረት መቋቋም እስከማይችልበት ደረጃ ተዳክሟል።
2.ዘርን መሠረተ ባደረገ ክልላዊ ድንበር ሳቢያ ኢትዮጵያዊው ጎበዝ አርሶ አደር አንዱ ቦታ ቢከፋ ወደ ተሻለ ቦታ ተዛውሮ ማረስ አልቻለም። ከሰሜን ወደ ደቡብ ከሄደ የአገራችን አርሶ አደር ይልቅ ባህር ተሻግሮ የመጣ ኤንቨርስተር ነኝ ባይ መሬት ማግኘት ይቀለዋል። እንዲያውም ኢትዮጵያዊው ገበሬ በዱላና በጥይት ሲባረር፤ ከባዕድ አገር የመጣው ብድርና ማበረታቻዎች ይሰጠዋል።
3.የህወሓት ባላሥልጣኖችና በየቦታው ያስቀመጧቸው ምስለኔዎቻቸው ራሳቸውን ባለሚሊዮኖች፣ ከፍ ሲልም ባለ ቢሊዮኖች አድርገዋል። እነዚህ በአንድ ጀምበር ከትቢያ የተነሱ ቱጃሮች ከገንዘብ በተጨማሪም የጄኔራልነት፣ የሚኒስቴርነት፣ የክልል ገዢነት፣ እጅግ ቢያንስ የቢሮ ኃላፊነት ሥልጣንን ኪሳቸው ውሰጥ ከተዋል። የመንግሥት ሥልጣንና ሃብት ይኸን ያህል የተቆራኙበት ሥርዓት በኢትዮጵያ ኖሮ አያውቅም። የጥቂቶች ያለአገባብና ያለቅጥ መክበር በአንፃሩ ደግሞ የብሃኑን ሕዝብ መደህየት ረሀብ እጣ ፈንታችን እንዲሆን አድርጓል።
4.በአቋራጭና በፍጥነት ለመክበር አስተማማኙ መንገድ የገዛ ራስ ጥረትና ታታሪነት ሳይሆን ቅጥፈት፣ አጭበርባሪነትና ሎሌነት ማደር መሆኑን የህወሓት አበጋዞች በተግባር እያሳዩ ሠርቶ፣ ለፍቶ ማደግ ሞኝነት እንዲሆን አድርገውታል። በዚህም ምክንያት በባህላችን ውስጥ ኮትኩተው ያሳደጓቸው አድርባይነት፣ ስንፍናና እና ልመና ችግርን የመጋፈጥ አቅማችንን ሰልበውታል።
5.ደኖቻችን ተጨፍጭፈው፣ ለም መሬታችን ተሸርሽሮ በማለቁ የግብርናችን ምርታማነት በእጅጉ ቀንሷል። በህወሓት የአገዛዝ ዘመን የደን ጭፍጨፋና የመሬት መሸርሸር በአስደንጋጭ ሁኔታ ጨምሯል። አገሪቷ በፍጥነት ወደ ምድረበዳነት እየተቀየረች ነው።
6.ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ድርቅን መቋቋም ስለሚችሉ ሰብሎች ወይም የአስተራረስ ዘዴዎች ማሰብ፣ መመራመርና መፈተሽ አይችሉም። አዲስ ነገር መሞከር “የኢህአዴግ የግብርና ፓሊሲን“ በመቃወም ወንጀል የሚያስቀጣ ተግባር ሆኗል። በዚህም ምክንያት ገበሬው ድርቅን መቋቋሚያ አዳዲስ ዘዴዎች መፈለግ ቀርቶ በተለምዶ የሚያውቃቸውንም መጠቀም አልቻለም።
7.የህወሓት አገዛዝ፣ እንደ ኢኮኖሚው ሁሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ ብዛት ሊቆጣጠር የሚሞክረው ቢሮ ውስጥ ቁጭ ተብሎ በሚደረግ የቁጥር ጨዋታ ነው። አገዛዙ ውጤታማ የስነ ሕዝብ ፓሊሲ የለውም፤ እንኳንስ የቀጣይ ዓመታት የሕዝብ እድገት ምጣኔን ሊቆጣጠር አሁን ያለነው ቁጥራችን ስንት እንደሆነ እንኳን በትክክል ሊነግረን አልቻለም፤ ረሀብ ነው መብዛታችንን እየነገረን ያለው።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እነዚህና የመሳሰሉት ጭብጦችን በማንሳት የረሀቡ መሠረታዊ ምክንያት የህወሓት አገዛዝ ያሰፈነው ብልሹ አስተዳደር መሆኑን በአንጽዖት ይናገራል። ሕዝባችን በነፃነት ማሰብ፣ መመራመር፣ መፈተሽ ቢችል ኖሮ ረሀብን መከላከያ ብልሃት ማግኘት ባላቃተውም ነበር ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል። ረሀብን ለማጥፋት ህወሓትን ከሥልጣን ማስወገድ ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ የሆነ ጊዜ ላይ ተደርሶአል ብሎ አርበኖች ግንቦት 7 ያምናል።
ነገር ግን ረሀብ ጊዜ አይሰጥም። የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ በሞት አፋፍ ላይ ላለ ወገናችን መፍትሄ አይሆንም። ስለሆነም ለረሀቡ መሠረታዊ መፍትሄ የሆነውን ትግላችንን ሳንዘነጋ የወገኖቻችንን ሕይወት ለመታገድ የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል። ሲቪክ ማኅበራት የተራበው ወገናችን የወያኔ መጠቀሚያ ሳይሆን የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ የሚያገኝበት መንገድ እንዲያፈላልጉ እና ወገን ለወገን የሚቆምበትን ዘመቻ እንዲያስተባብሩ ጥሪ ያደርጋል። ለወገኖቻችን የሚላከው እርዳታ ከዚህ በፊት እንደነበረው ሁሉ ወደአገዛዙ ባለሥልጣኖች የግል ኪስ እንዳይፈስ ጥንቃቄ እንዲደረግ ያሳስባል። ለወገኖቻችን ለመድረስ እያንዳንዳችን በግል፤ እንዲሁም በቡድን የተቻለንን ሁሉ እናድርግ።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ኅዳር 3 ቀን 2008 ዓ.ም.