Thursday, June 30, 2016

ህወሃት በሰሜኑ ግንባር ተጨናንቋል ም/መቶ አለቃ ደጀኔ እና ወታደር በኩር ይናገራሉ!

June30,2016
በልኡል አለም
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በምእራብ ትግራይ ሂሞራ በታች የማይካድራ ነዳጅ ማጠራቀሚያ አካባቢና እስከ ሰቲት ሁመራ እንዲሁም ጉናና ኡማህጂር ምስራቅ ትግራይና ዓዲ ግራት ድረስ የተሰማራዉ ከተለያዩ ክፍለ ጦሮችና ልዩ ኃይል እንዲሁም አካባቢ ሚሊሻዎች ተወጣቶ በስምሪት ላይ የሚገኘዉ የጸረ ሽብር ቡድን ወደ ግንባር እንዲሰማራ ባለመ መልኩ እየተበተነና እየተሰባጠረ እንደሚገኝ ታማኝ የመከላከያ ምንጮች ገልጸዋል።Ethiopian Soldiers
ይህዉ የጸረ ሽብር ቡድን በተለይም ከደረሰበትና እየደረሰበት ከሚገነዉ ድንገተኛ ጥቃት ምክንያት እጅግ በመመናመኑና በመዳከሙ ለስምሪት የአካባቢዉ ክፍለ/ጦሮች እንዲተኩ የተወሰነ ሲሆን ከላይ የተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በአካባቢዉ ላይ ከሚደረገዉ ወታደራዊ መሯሯጥ የተነሳ ስጋት ስላደረባቸዉ አካባቢያቸዉን ወደ መልቀቁ ደረጃ ሊሸጋገሩ እንደሚችሉ እማኞች እየተናገሩ ይገኛሉ።
የህወሃት አዲስ ምልምልና ቅጥር ወታደሮች በመክዳት ምክንያት ከፍተኛ አደጋ እያስከተሉ በመምጣታቸዉ ወደ ደጀን ጦር በሚደረገዉ ዝዉዉር ከሰቲት ሁመራ ጀርባ ሲካተቱ ነባሮች ስምሪት እና ጸረ ሽብር ስምሪቱን እንደቆጣጠሩ ሆኗል።
በሰሜን ጎንደርና በምእራብ ትግራይ አካባቢ ተሰማርቶ የሚገኘው 24ተኛ ክ/ጦር ከ 25ተኛ ክ/ጦር ጋር ቅይጥ ብረት ለበስ ሜካናይዝድ በማደራጀት የጥምር ዉህድ የሚመስል ስልታዊ ክንዉን እያደረጉ ሲሆን ለዚህ ያለመረጋጋትና የመበታተን ጦስ ዋነኛዉ ምክንያት በየእለቱ በሰራዊቱ ላይ የሚደርሱ አነስተኛ ጥቃቶች እና የዉስጥ አርበኞች የፈጠሩት ጫና በአንኳርነት ተጠቃሽ ከመሆኑ በተጨማሪ የኢትዮ-ኤርትራ የጦርነት ስጋት የፈጠረዉ ትርምስ በራሱ የተያያዘ መጨናነቅ መፍጠሩን ባሳለፍነዉ ሳምንት ከሰሜኑ ግንባር ተነጥለዉ በጎረቤት ሐገር በተጠለሉ ም/መቶ አለቃ ደጀኔ ጥላሁን እና ወታደር በኩር ገ/ስላሴ ለታማኝ ምንጮቻችን ተናገረዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

Wednesday, June 29, 2016

"ከሁሉ መቅደም ያለበት ሰብዓዊ ልማት ነው" ሃብታሙ አያሌው

June 29,2016
“ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል"
habtamu

ከጥቂት ቀናት በፊት “ሀገር አለኝ!! ወገን አለኝ!!” በማለት በፌስቡክ ገጹ ላይ ይህንን የለጠፈው የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ ሃብታሙ አያሌው በጠና ታምሞ በኮማ ውስጥ ይገኛል፡፡
“እዉነት እዉነት እላችሁአለሁ ስቃይና መከራ የምቀበልላት ብቻ ሳትሆን የምሞትላት ሀገር አለችኝ!!
“ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለዉ” ከሚል ጀግና ህዝብ ተወልጄ በእስካሁኑ ስቃይ ጉልበቴ አይዝልም። እንድበረታ ዛሬም ከጎኔ ላልተለያችሁ ቃሌ ይሄ ነዉ። አመሰግናለሁ” ነበር ያለው!
የትግል አጋሩ ዳንኤል ሺበሺ (Daniel Shibeshi) በጥቂት ሰዓታት በፊት በፌስቡክ ገጹ ላይ ከላይ የሚታየውን የሃብታሙን ፎቶ አድርጎ ያሰራጨው ጽሁፍ እንዲህ ይላል፤
“በሀብታሙ አያሌው ጤና መታወክ፣ እየተረባበሻችሁ ላላችሁ ሁሉ በያላችሁበት ሆናችሁ ፀሎታችሁን ቀጥሉበት። አሁንም በኮማ ውስጥ ነው ያለው። ለውጥ አልታየም። ከትንፋሽ ውጭ ሌላ እንቅስቃሴ የለም። ቤተሰብ በሙሉ ተረባብሿል። ነገር ሁሉ ግራ ገብቶኛል። ወገን ሆይ በክፉዎች እጅ ወድቀናል!!! ከሌሊቱ 8ሰዓት።”
በአንድነት ፓርቲ ውስጥ በነበረው የጎላ ተሳትፎ በህወሃት ዓይን ውስጥ የገባው ወጣቱ ፖለቲከኛ ሃብታሙ በህወሃት “አሸባሪ” ተብሎ ተፈርጆ በእስርቤት ሲማቅቅ በቆየበት ጊዜ ከደረሰበት ግፍና ስቃይ የተነሳ ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከፍተኛ ችግር ደርሶባቸው በሃይለኛ ህመምና ስቃይ ውስጥ ሲማቅቅ ቆይቷል፡፡ በአገር ውስጥ መታከም የማይችል በመሆኑ ወደ ውጪ ሄዶ እንዲታከም ከሃኪሞች ቢነገረውም የህወሃት ሹመኛ የሆነው “ወንጀለኛ ዳኛ” ከአለቆቹ በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ሃብታሙ ወደ ውጪ እንዳይወጣ ከልክሏል፡፡
አሁንም በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ቁርጠኛ እንደሆነ የሚናገረው ሃብታሙ ከጥቂት ቀናት በፊት ከጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ጋር በአዲስ ገፅ መፅሔት ያደረገው ቃለምልልስ ከዚህ በታች ይገኛል፡፡
ጥያቄ፡- የግንቦት 20 ፍሬን በተመለከተ የምታምንበትን ገልጸሃል፡፡ የተቃውሞ ፓርቲ ትግልም በውጣ ወረድ የታጀበ ነው፡፡ ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ራሱ በገደል አፋፍ ላይ ነው የሚገኘው፡፡ ለሀገርና ለህዝብ የሚጣፍጥ ፍሬ ለማፍራት ምን መደረግ አለበት?
ሐብታሙ አያሌው፡- በኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት ከተፈለገ፤ በንጉሱም፣ በደርግም የነበሩ ችግሮች ኢህአዴግ ከ25 አመታት በሁአላም እንዲቀጥላቸዉ መፍቀድ አይገባም። በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ብዙ ያልተመለሱ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ዋናውና መሰረታዊዉ ጥያቄ የሰብዓዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥያቄዎች ናቸዉ፡፡ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች ለነገ የሚባሉ አይደሉም። ፈጣን ምላሽ ይጠይቃሉ። ኢህአዴግ እነዚህን መሰረታዊ የህዝብ መብቶች ለማክበር ዝግጁ እንዳልሆነና አቅሙም እንደሌለዉ ከመቼዉም ጊዜ በላይ ግልፅ የሆነ ይመስላል።
የምትፈልገውን ነገር የማግኘት፣ የመምረጥ፣ በህይወት የመኖር፡ የመናገር፡ የመፃፍ…የመሳሰሉት መሰረታዊ መብቶች በተጣሱበት ምንም አይነት ጣፋጭ ፍሬ ሊገኝ አይችልም። ኢህአዴግ ስልጣን ለማስጠበቅ ብቻ የሚከተለዉ በልማት ስም የህዝብን መብት የማፈን ስርዓት ሊያፈርሰን ካልሆነ በቀር ሊሰራን አይችልም።
ጣፋጭ ፍሬ ለማግኘት ከሁሉ መቅደም ያለበት ሰብዓዊ ልማት ነው፡፡ ከልማቱ ጋር ተያይዞ ከድህነት የመውጣት ጥያቄ ይመጣል፡፡ መጀመሪያ ህሊና… ህሊና ከሆድ መቅደም አለበት፡፡ የህሊና ነጻነት የሚባል ነገር አለ፡፡ ኢህአዴግ ያልገባዉ ወይም እንዲገባዉ ያልፈለገው ይህ ነዉ ። የምን ጊዜዉም መከራከሪያዉ ሆድን በማስቀደም ላይ ነው፡፡ ‹‹ልማት ይቀድማል›› ይለናል፡፡ የህሊና ጥያቄዎች ሳይመለሱ ሆድ መቅደም የለበትም፡፡ የስርዓቱ ሰዎች የገዛ ህዝባቸውን እየዘረፉ በረሃብ የሚቆሉት እና የሚያፍኑት እኮ ለዚህ ነዉ እነሱ ጋር የህሊና ጥያቄ የሚባል ነገር የለም ። በአፋቸዉ ዴሞክራሲና ልማት ተነጣጥለው አይታዩም ይሉሃል በተግባር ግን ከዚህ የተለዩ ናቸዉ መብት የጠየቀን ያስራሉ ያሰድዳሉ ይገላሉ፡፡ ኢህአዴግ ከባድ የቁርጠኝነትና የማስፈጸም ችግር ያለበት ድርጅት ነዉ፡፡ ላለፉት 25 ዓመታት ነገሮች ሲሻሻሉና ትንሽ ዕድል ሲያገኙ አልታዩም ከአመት አመት ወደ ባሰ ጨለማ እያመራን ነዉ። ኢህአዴግ ለመነጋገር እና ለሪፎርም መዘጋጀት አለበት ተቃዋሚዉም እንደዛዉ አለዚያ መጨረሻችን የፈራነው እንደ ሀገር መፍረስ ይመጣል። መነጋገር መደማመጥ የሁሉ መፍትሄ ነዉ ነገር ግን ተስፋ የሚያሳጣዉ ኢህአዴግ በየጊዜው እየባሰበት እንጂ እየተሻሻለ የማይመጣ ድርጅት መሆኑን ነዉ።habtamu a
ጥያቄ፡- እንዴት?
ሐብታሙ አያሌው፡- ለማስታወስ ያህል፣ በ83 እና 84 ዓ.ም ልጅ ነበርኩ፤ ምንም አላስታውስም፡፡ ግን አንብቤ እና ጠይቄ ከተረዳሁት፣ መሬት ላይ የነበረውም ነገር እንደሚያሳየው ከ83-87 ዓ.ም ድረስ የሚዲያው ነጻነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ነበር ይባላል፡፡ የፈለከውን መናገር ትችላለህ፣ የፈለከውን መጻፍ ትችላለህ፣ ኢህአዴግ ለማፈንና ለመቆጣጠር የሚያስችል ስልት አልዘረጋም ዴሞክራሲን ለማስመሰል ወይም ለመሞከር ይፈልግ ነበር፡፡
ጥቂት ቆይቶ ግን ወደ ተፈጥሮአዊ የድርጅቱ ባህሪ ተመለሰ። ስለዚህ ወደ አፈናው ሲሄድ፡ ምሁራኖቹን መጀመሪያ በጠላትነት መፈረጅ፣ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ ያለውን ነገር ማጽዳት፣ ሚዲያዎችን በሙሉ መቆጣጠር፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ወይም ሲቪል ማኅበራትን በመንግሥት ደጋፊዎች በመሙላት መቆጣጠር፣ የሃይማኖት ተቋማትን መቆጣጠር . . . ፖለቲካውን አረጋግቶ ለመምራት ሁሉንም ተቋማት ‹‹በእኔ ቁጥጥር ሥር ማድረግ አለብኝ›› ወደሚል ተግባር ሄደ፡፡ መሆን የነበረበት ግን ይህ ሳይሆን ተቃራኒው ነው፡፡ የዴሞክራሲ ተቋማትን በካድሬ መቆጣጠር ሳይሆን መፍትሄዉ ገለልተኛ ሆነዉ እንዲጠናከሩ ማድረግ ነበር። መንግሥት ሊሔድና ሊመጣ ይችላል፣ ሲስተሙ ግን መቆም ነበረበት፡፡ ስለዚህ ኢህአዴግ ያተኮረው ሲስተም ላይ ሳይሆን የቁጥጥር ዘዴ ግንባታ ላይ ነው፡፡
እምነት የሚጣልበት ተቋም ተገንብቶ ቢሆን ኖሮ ላለፉት 25 ዓመታት ምርጫ ቦርድ አያከራክርም ነበር፡፡ ዛሬም የዴሞክራሲ ጥያቄ ሀገሪቷን ያልሆነ ችግር ውስጥ አይከታትም፡፡ የሰብዓዊ መብት ተቋም ቢገነባ፣ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በሚያወጣው ውጤትና በሚነግረን ነገር ላይ ልዩነት አይፈጠርም፡፡ የሚዲያ ተቋሙ (በመንግስት ቁጥጥር ስር ያለው) አንድን ፓርቲ ከማገልገል ይልቅ ሀገራዊ ሚናውን ሊወጣ የሚችል ነጻ የሚዲያ ተቋም እንዲሆን ማድረግ ቢቻል ይሄ ሁሉ ሀገራዊ ቀዉስ አይፈጠርም ነበር፡፡
ጥያቄ፡- እነዚህ ነገሮች በሌሉበት የምታደርገው ምንድን ነው?
ሐብታሙ አያሌው፡- በኢህአዴግ ፕሮግራም ላይ ነጻ የኢኮኖሚ ሥርዓት የሚል አለ፡፡ በነጻ ገበያ እኩል መወዳደር ሚቻልበት ዕድል ግን የለም፡፡ ይልቁንስ እንደምናየውና እንደምንሰማው የመከላከያው ክፍል ተቆጣጥሮታል፡፡ እርግጥ ነው፣ አንድ መከላከያ ሀገርን ከመጠበቅ ባሻገር በልማት ግንባታ ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዲኖረው ማድረግ ይገባል፡፡ ነገር ግን፣ አጠቃላይ የግሉን ሴክተር በሙሉ ከውድድር በሚያወጣ መልኩ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ወደ መከላከያ መሰባሰቡ ተገቢ አይደለም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አቋም ይዘን ተከራክረናል፡፡ የግል ዘርፉ ነው መንግስትን መቆጣጠር ያለበት፡፡ መንግስት በገበያ ውስጥ ያለው ተሳትፎ ውስን መሆን አለበት፡፡ መንግስት ኢኮኖሚውንና የፖለቲካ ሥልጣኑን ከተቆጣጠረ አንባገነን ለመሆን ሰፊ ዕድል ይሰጣል፡፡ በዚህም የግለሰቦች ሚና ከፍተኛ ይሆናል፡፡ አየህ ኢህአዴግ በሁሉም ነገር ቁልቁል ሂዶአል የምልህ ለዚህ ነዉ ። በጥቅሉ አንድ ፓርቲ ይወለዳል ያድጋል ይሞይሞታል አሁን ኢህአዴግ በዚህ ሂደት አልፎ እድገቱን ጨርሷል።
ጥያቄ፡- ስለዚህ ምን ማድረግ ይጠበቅበታል?
ሐብታሙ አያሌው፡- ከዚህ በኋላ ኢህአዴግ ሪፎርም ሳያደርግ፣ የዴሞክራሲ አብዩት ሳያመጣ፣ በዴሞክራሲ መንገድ ለውጥ ሳያመጣ፣ በልማቱ ጉዳይ፣ በሰብዓዊ መብት ለውጥ ሳያመጣ እስካሁን በመጣበት መንገድ ለመቀጠል የሚችልበት ዕድል የለም፡፡ ይልቁንስ ወደበለጠ ቀውስ ውስጥ ነው የሚገባው፡፡ ሪፎርም የማምጣት ዕድሉን መጠቀም አለበት፡፡ እንደውም አንድ አባባል መጠቀም እፈልጋለሁ፡፡ ኢህአዴግን በተቃዋሚ ጎራ ላይ ወድቀን ነው የጠበቅነው፡፡ ወድቀን ጠብቀን፣ ለምን ደረሱብን እያልን ነው፡፡ ወድቀን ባንጠብቃቸው አይደርሱብንም ነበር፤ ለዚህ ጥቂት ምሳሌዎች ባነሳ፣ አንዱ የተቃዎሚዎች ጎራ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት ሆኖ የቀጠለበት በማይረባ ምክንያቶች፤ የግል ጉዳዩን ለማሳካት የተሰባሰበ ስብስብ፣ ከግል ከፍተኛ ፍላጎት መዝለል ያልቻለ ስብስብ በመሆኑ ነው፡፡
ይህ ሲባል የሚከፋው ሰው ይኖራል፤ ግን የሆነ ሰው ይከፈዋል ብዬ አስተያየት ከመስጠት ወደኋላ አልልም፡፡ አንድነት ፓርቲ በእኔ ዘመን ሊቀ-መንበር ያደረገው ኢንጂነር ግዛቸውን ነበር፤ ኢንጂነር ግዛቸው ከኃላፊነት ሲነሳ ‹‹እኔ ከሄድኩ ፓርቲው ብትንትኑ ይውጣ›› ብሎ አንድነትን በትኖ ሄዷል፡፡ ኢንጂነር ግዛቸው አንድነትን በማፍረስ ከኢህአዴግ የሚለይበትን አንድም ምክንያት የሚጠቅስ ሰው አላገኝም፡፡ ኢህአዴግ አንድነትን ለማፍረስ የሰራውን ያህል ኢንጂነር ግዛቸውም ሰርቷል፡፡ እነትዕግስቱስ አንድነትን ለማፍረስ የተጫወቱት ሚና ከኢህአዴግ የሚለየው በምንድን ነው?! ኢህአዴግ መጥቶ አንድነትን ባያፈርሰው ኖሮ ግዛቸው፣ ትዕግስቱና ሰፊው የሚባሉ ሰዎችን ይዘን ነበር የምንቀጥለው፡፡ ያ ስብስብ በርካታ ችግሮች የነበሩበት ስብስብ ነበር፡፡ ወርቅ በእሳት እንደሚነጠረው የፈተና ቀን ሲመጣ አብዛኛው ተበታትኖ ድራሹ ጠፋ፡፡
በእርግጥ ይህንን ለማድረግ የታወቀ ኢህአዴግ ባህሪ አለ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥም ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ እንዳይፈጠር ፍላጎት አለው፡፡ አንድነትን ማፍረስም ለነገ የሚባል ነገር አልነበረም፡፡ ምክንያቱም አንድነት ውስጥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በደንብ የገባቸውና የተረዱ ምርጥ ምርጥ ኃይሎች ነበሩ፡፡ እኔም ወደአንድነት ስገባ እነዚህን ሰዎች አይቼ ነው፡፡ እነዚህን ጥቂት እርሾ የሆኑ ሰዎችን ይዞ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ውስጥ የኢህአዴግን ሁኔታ ተቋቁሞ ትልቅ ለውጥ ማምጣት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ውስብስብ የሆነው የተቃዋሚው ችግር በቀላሉ የሚለቀን አልሆነም፡፡ በፖለቲካ አቋማቸውና እውቀታቸው አንድም ጥያቄ የማይነሳባቸውን እከሌ እከሌ ብሎ ማንሳት ይቻላል፡፡
እኔና ዳንኤል ወደ እስር ቤት ስንገባ ከአንድነት ፓርቲ በጣም ተስፋ የጣልኩባቸው ምርጥ ምርጥ ሰዎች ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ተክሌ በቀለን የመሰለ ፖለቲከኛ፣ በላይ ፍቃዱን የመሰለ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ በቂ እውቀት ያለው ሰዉ፡ ግርማ ሰይፉን የመሰለ ወሳኝ፡ አስራት አብርሃ፡ አስራት ጣሴ፡ ፀጋዬ አላምረዉ … ነበልባል የሆኑት ወጣቶች እንደነ ዳግም፡ እስማኤል ዳዉድ፡ ስንታየሁ ቸኮል፡ ዳዊት ሰሎሞን፡ ያሬድ አማረ፡ አለነ ማህፀንቱን የመሳሰሉ በርካታ ትንታግ ወጣቶች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እድል ቢያገኙ፣ እንደ ኢህአዴግ በር ዘግቶ የሚያፍን ድርጅት ባይሆን ኖሮ የተሻለ ደረጃ የሚደረስበት እድል ነበረ፡፡ መጨረሻ ላይ እኮ እነ አስራት አብርሃ፣ አናንያ ሶሪ፡ ስለሺ ሀጎስ መሃመድ አሊ፡ ሌሎችም በርካታ ሰዎች ተስፋዎች ወደ አንድነት መጥተው ነበር፡፡ እኛም ከታሰርን በኋላ ፓርቲው ሊቀጥል የሚችልበት ሰፊ እድል ነበር፡፡ በላይ ፍቃዱ ተክሌ በቀለ ግርማ ሰይፉ እውቀትና ክህሎታቸዉን ተጠቅመዉ ምርጥ አመራር እየሰጡ ለዉጥ የሚያመጡበ ብሩህ ዕድል ነበረ፤ ነገርግን ይህንን ኢህአዴግ ጠምዝዞ አክሽፎታል፡፡
የኢህአዴግ አንድነትን ማፍረሱ ታሪካዊ ስህተት ነው፡፡ አንድነትን አፍርሶ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ዳግም ጨለማውን የበለጠ አበረታው፡፡ እኛን አሰረ፤ አንድነትን አፈረሰ፡፡ ዉጤቱ ሺህ እልህኛ ወጣቶችን ፈጠረ እንጂ ትግሉን አልቀለበሰዉም፡፡ አንድነት ‹‹በርታ›› ሊባልና ሊደገፍ የሚገባው ድርጅት ነበር፡፡ ድክመቶችን እንዲያርም እድል ሊሰጠው ይገባ ነበር፡፡ አየህ ኢህአዴግ ፈፅሞ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ብቁም ምቹም እንዳልሆነ ሁሉ የተቃዋሚ ጎራው ስብስብም ባለብዙ ችግር ነዉ፡ ከብዙ ሆድ አደሮች ጋር ተጃምለን ለጉዳት ተጋልጠናል እናም መፍትሄዉ ሰከን ብሎ ወደራስ ማየት ራስን መገምገም ነዉ ።
ከሁሉ በፊት ሀገር እናስቀድም ሪፎርም በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል ባይ ነኝ።
በመጨረሻም እኔ ባሁኑ ወቅት በከባድ የጤና ችግር ዉስጥ እንዳለሁ የምታየው ነዉ። የሀገሬ ጉዳይ ቢያሳስበኝም በደረሰብኝ ግፍ ስቃዬን እንዳዳምጥ ተገድጃለሁ። እናም ከብዙ ከሀዲዎች መካከል የነጠሩ የቀድሞ የአንድነት ሃይሎች እንደ ትላንቱ ዛሬም ስላልተለዩኝ አመሰግናለሁ። ተክሌ፡ በላይ፡ ግርማ፡ ስዩም፡ አስራት ጣሴ፡ አስራት አብርሃ፡ ገበየሁ፡ እስማኤል፡ ሰባህ፡ ፋሲካ፡ እዩኤል፡ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ፡ ናትናኤል ፈለቀ፡ ዮናታን ወልዴ፡ ታታሪዉ ጠያቂዬ ተፈሪ፡ ወዳጄ ማይክ መልዐከ … ከፍ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።
ከሁሉ በላይ ጠበቃ አመሃ መኮንን ከግፍ እስር ብቻ ሳይሆን ዛሬም ሂወቴን ለማዳን እያደረክ ላለህዉ ሁሉ ከቤተሰቤ ጋር ምስጋና እናቀርባለን። ኤልያስ እንደ ወንድም አልተለየህኝም ምስጋና ይድረስህ፡ በስም ያልተጠቀሳችሁ በሀገር ዉስጥ እና ዉጭ ያላችሁ ሁሉ አመስግኛለሁ።
ሰላም ለሀገራችን ይሁን!
(ምንጭ:Elias Gebru Godana ፌስቡክ)

Tuesday, June 28, 2016

አስፋልቱ “አብስትራክት” የሆነው የደምቢዶሎ ኤርፖርት

June 28,2016
“የቀረው በwifi ይሠራል”
d d airport
ህወሃት በግፍ በሚመራት ኢትዮጵያ የማይጠፋ ነገር የለም፡፡ ምናልባት መብራት ብቻ ነው የሚጠፋው ብሎ የሚያስብ የቅርቡን ክስትት ያልተከታተለ ብቻ ሊሆን ይችላል ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡
boy
መሃንዲሱን ተዋወቁ
መብራት፣ ውሃ፣ የስልክ ኔትወርክ፣ ወርቅ፣ … ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ የሥርዓቱ ተቃዋሚዎች … በሚጠፉባት አገር ከሰማኒያ በላይ ኮንዶሚኒየም ይጠፋል፤ ሰሞኑን ደግሞ በኢትዮጵያ የህወሃት ተጠሪ ኃይለማርያም በነቀምቴ ከተማ  አውሮፕላን ማረፊያ ያስቀመጡት የመሠረት ድንጋይ ጠፍቷል ተብሎ የማኅበራዊ ሚዲያውን ሰፈር አድምቆታል፡፡
የነቀምቴው ሳያንስ ደምቢዶሎ ደግሞ ተመረቀ የተባለው የአፈር አየር ማረፊያ ህወሃትን ለከፍተኛ ስላቅና ፌዝ አጋልጦታል፡፡ የሥርዓቱ ደጋፊ የሆኑት ሳይቀሩ “ገንዘቡ ተበልቷል” ያሉበት የዚህ አውሮፕላን ማረፊያ የማኮብኮቢያና የማረፊያ መንገድ ከአፈር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ተሳፋሪዎችንም ከአውሮፕላኑ ሲወርዱ የሚያጠልቁት ጭቃ መከላከያ እንዲኖራቸው የሚያስገድድ ሆኗል፡፡ ከአየር መንገድ ንግድ አንጻር ይህ በራሱ በኢትዮጵያ አየርመንገድ መሸፈን ያለበት ወጪ በመሆኑ ከረሜላ፣ ለስላሳና ጣፋጭ ምግቦችን ከአንዳንድ ቦቲ ጋር አብሮ ለተሳፋሪዎች በበረራ አስተናጋጆቹ ማቅረብ እንደሚገባው ፌዘኞች አላግጠዋል፡፡
ddairportየተለያዩ ፎቶዎችን በመገጣጠምም በርካታ ትችት በማኅበራዊ ሚዲያ የቀረበበበት ይህ ጉዳይ አንዳንዶችም ህወሃት በትግራይና በኦሮሚያ የሚያደርገው “ልማታዊ ሥራ” እንዴት የተለያየ መሆኑን በትግራይ የሚገኙ ኤርፖርቶችን ከደምቢዶሎው ጋር በማነጻጸር ምሬታቸውን የገለጹበት ሆኗል፡፡
በዚህ የዜና ዘገባ፥ እፍረት አያውቅም እንጂ፤ የቀድሞው ኢቲቪ ያሁኑ ኢቢሲ እስካሁን 50ዓመት አገልግያለሁ ከዚህ በኋላ በቃኝ ብሎ “ለሰፊው ሕዝብ ጥቅም ሲል” ራሱን ማጥፋት ነበረበት ተብሏል፡፡
እጅግ ከፍተኛ የሥራአጥ ቁጥር ባለበት አገር ይህ ኤርፖርት የሥራ ዕድል ከፍቷል ብለው የተሳለቁ ይህንን ማስታወቂያ በትነዋል፡-
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
በዚህ ሳምንት የተመረቀው ዘመናዊው የደምቢ ዶሎ አየር ማረፊያ መስፈርቱን የሚያሟሉ ማንኛቸውንም አመልካቾች ያለ ውድድር በቀጥታ ለመቅጠር ይፈልጋል። መስፈርቱን እናሟላለን የምትሉ ደምቢ ዶሎ ግብርና ምርምር በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የቅጥር መስፈርት፡- የ11 በሞቶ እድገታችንን ታሳቢ በማድረግ ለ11 ዓመት የሰመጠ ባቡር በማንጠልጠል የጡንቻ ማዳበርያ የአካል ብቃት መስራቱን የሚያረጋገጥ ማስረጃ ማቅረብ ብቻ።
የስራ ቦታ፡- ደምቢ ዶሎ የታረሰ ማሳ ላይ።dd air port
የስራው አይነት፡- በጭቃ የተያዘ አውሮፕላን መግፋት።
“ይህ የሚታያችሁ አፈር ወይም ጭቃ ሊመስል ይችላል፤ አውሮፕላን ማረፊያው በአስፋልት ነው የተሰራው – አብስትራክት ስለሆነ በደንብ አልታችሁም፤ የቀረው ደግሞ በwifi ይጠናቀቃል፥ እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” ብሏል ብለው የኢቢሲውን ተመስገን “ጋዜጠኛዊ ብቃት” ለማድነቅ አንዳንድ ፌዘኞች ስልክ ቢደውሉ ኔትወርክ ጠፍቷል ተብለዋል፡፡
airport(ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ)

Saturday, June 25, 2016

አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” የህወሃት ነፍጠኞች

June 25,2016
“ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት

ogaden 4
የኢትዮጵያን ሕዝብ በነጻ አውጪ ስም እስካሁን በግፍ እየገዛ ያለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ሥልጣን በኃይል ከመያዙ በፊት ሲፈጽም የነበረውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፤ ሥልጣን ከያዘም በኋላ ላለፉት 25 ዓመታት ቀጥሎበታል፡፡ ህወሃት ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ግፍ ያልተፈጸመበት አካባቢ የለም የሚለው አባባል የተጋነነ አይደለም፡፡
ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት” በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ ግራሃም ፔብልስ በኦጋዴን የሚካሄደውን የሚዘገንን ግፍ ሰኔ 15፤ 2008ዓም (June 22, 2016) ዩትዩብ ላይ ለቋል፡፡ (ዘጋቢ ፊልሙ እዚህ ላይ ይገኛል)
“በዛፍ ላይ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሰቅለውኝ ነበር፤ በርካታ ደቂቃዎች ካለፉ በኋላ አወረዱኝ፤ … ከዚያም ካሁን በኋላogaden 1 የምንልሽን ታደርጊያለሽ አለበለዚያ እንገድልሻለን አሉኝ” የግፍ ዶፍ የወረደባት አናብ ከተናገረችው፡፡
የሚዲና የዕርዳታ ሥራዎችን የሚያካሂዱ ሁሉ ወደ ኦጋዴን እንዳይገቡ በህወሃት ትዕዛዝ ተደርጎባቸው ባለበት ባሁኑ ወቅት በኦጋዴን የሚካሄደው ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፤ እስር፣ እንግልት፣ ወከባ፣ … በድብቅ ቀጥሏል ይላል ጋዜጠኛ ግራሃም፡፡
ዘጋቢ ፊልሙን ለመሥራት መረጃው የተሰበሰበው ከሚሊታሪው የኮበለሉና ሌሎች ለህይወታቸው ያልሳሱ ደፋሮች በሰጡት ምስክርነት ነው፡፡ በተለይም ከኢትዮጵያ ኮብለለው በቅርቡ ኬኒያ ልትዘጋው ወደ ወሰነችው የዳዳብ የስደተኞች ካምፕ የሚገኙ ሦስት ሴቶች የህወሃት ሠራዊት ስላደረሰባቸው መከራ፣ ሥቃይና አስገድዶ መድፈር ተግባራት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ወደ ዳዳብ በግንቦት 2006ዓም የመጣችው ሚሪያም ለሁለት ዓመት ተኩል እንዴት እንደተሰቃየች፣ አስገድዶ መድፈርና ድብደባ እንዴት እንደተፈጸመባት ትናግራለች፤
“እንደ ማሰቃያ ይሆን ዘንድ እስኪደክመኝ ድረስ ሬሣ አቅፌ እንድቆም ተደርጌአለሁ፤ ከዚያም ሚጥሚጣ የሞላበት ላስቲክ በራሴ ላይ አስረውብኛል፤ ገመዱን ሲያስሩት አጥብቀው ከአንገቴ ጋር በማሰራቸው ራሴን ስቼ ወድቄ ነበር፡፡ ከዚያ ለብዙ ሆነ እየተፈራረቁ አስገድደው ደፈሩኝ …”ogaden 10
“ኦጋዴን በሚገኘው እስርቤት 1097 የምንሆን ነበርን፤ ቁጥሩን በትክክል አውቀዋለሁ ምክንያቱም በየቀኑ ማለዳ ላይ እያሰለፉ ከቆጠሩን በኋላ በቡድን በቡድን እያደረጉ ይከፋፍሉን ነበር፤ …
“(የተያዝን ጊዜ) እህቴን ጉሮሮዋን አንቀው መረጃ አምጪ አሏት፤ ምንም እንደማታውቅ ብትነግራቸውም አልሰሟትም፤ ከሌሎቻችን ጋር ተቀላቅላ እንድትቀመጥ አደረጓት ከዚያም ሁላችን እያየን አራት ቤቶቻችን አቃጠሏቸው፤ ቤቱን እያቃጠሉ እህቴን ከመካከል ነጥለው ግምባሯ ላይ በጥይት መቷት፤ እህቴን እስከሞት ስትደማ አየኋት፤ ከእርሷ አጠገብ ሌላ ሴት ልጅ በድብደባ ብዛት ሞታ ነበር፤ ከዚያም እኔን ሬሣ ባለበት ጉድጓድ ውስጥ ጣሉኝ፤ በዚያ ጉድጓድ ውስጥ አራት ቀንና አራት ምሽት አሳለፍኩ፤ ጥፋተኛ መሆኔን እንድናዘዝ ምርመራ ይካሄድብኝ ነበር፤ አለበለዚያ መጨረሻዬ እንደ ሬሣው እንደሚሆን ይነግሩኝ ነበር፤ እኔም ምንም የምናዘዘው የለኝም የምታርዱኝ ከሆነ እረዱኝ አልኳቸው፤ (ጉድጓድ ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ) ከሬሣው መካከል አንዱ ጉሮሮው ታርዶ፤ አንገቱም በዱልዱም ነገር ተቆርጦ ጭንቅላቱ እዚያው የቀረው አካሉ ጎን ነበር፤…”
በመስከረም 2007ዓም ወደ ዳዳብ ካምፕ የመጣቸው አናብ ደግሞ “የኢትዮጵያ ሠራዊት በጅምላ ከገደሉ በኋላ በጅምላ የሚቀብሩበትን ቦታ በመደበቅ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ያደርጋሉ፤ አንዳንዶቹ መቼም አይገኙም፤ አንዳንዶቹ ግን በቁሻሻ ጉድጓዶች ውስጥ ተገኝተዋል” ትላለች፡፡
በእርሷ ላይ የደረሰውን በተመለከተ ስትናገር አናብ እንዲህ ትላለች፤ “ወደ እስር ቤት ተወስጄ በሽቦ ታነቅሁኝ፤ ይህ ዓይነቱን ተግባር በተደጋጋሚ ሲፈጽሙ ቆይተው በኋላ እስርቤት ተዉኝ፤ በተያዝኩ ጊዜ ከፊት፥ ከኋላና ጭኔ ላይ በጎማ ጠፍር ገርፈውናል፤ ከእኔ ጋር የተያዙ አምስት ልጃገረዶች ነበሩ፤ ከተያዙት ውስጥ ትልቋ 19ዓመቷ አካባቢ ነበር፤ ትንሽዋ ደግሞ ወደ 15ዓመት አካባቢ ነበረች፤ በተያዝንበት ወቅት ልጆቹን ክፉኛ ሲደበድቧቸውና በሰደፍ ሲመቷቸው አይቻለሁ፤ ልብሳቸውንም ቀዳድደውባቸው ብጣቂ እራፊ አድርገው ተመልሰዋል፤ ይህንን በየጊዜው የሚያደርጉት ተግባር ነው፤ …Ogaden 11
“መረጃ እንድንሰጣቸው በየጊዜው ይመረምሩን ነበር፤ ሴቶችን ‘አስገድደን እንደፍራችኋለን’ እያሉ ያስፈራራሉ፤ ‘አንደፈርም’ ብለው አሻፈረን የሚሉትን ደግሞ ያንቋቸዋል፤ ሴቶቹ ራሳቸውን ስተው ባሉበት ወቅት እንኳን ይደፍሯቸዋል … እኔ የታሰርኩበት ትንሽ ክፍል ውስጥ ሰባት ሴቶች ነበሩ፤ ከዚያ ክፍል ነጻ የተለቀቀ የለም ማለት ይቻላል፤ ከእኛ በፊት እዚያ ክፍል የነበሩት ታርደዋል፤ ሌሎቹም በረሃብ እንዲሞቱ ተደርገዋል፤ ሬሣቸውንም በየጉድጓዱ ወርውረውታል፤ እኛ የነበርንበት ክፍል ሬሣ ነበር፤ የክፍሉን ሁኔታ ማንም ሊገምት የሚችል አይደልም (መግለጽ አይቻልም)፤ በክፍሉ የነበረው ሬሣ ባብዛኛው የወጣት ወንዶች ነው፤ እስከ አራት ቀናት ሬሣው በክፍሉ እንዲቆይ ይደረጋል፤ ከዚያ አውጥተው በየቦታው፤ በየመንገዱ ይወረውሩታል፤ …”
እንደ ሚሪያም በግንቦት 2006 ዓም ወደ ዳዳብ የመጣችው ፋጡማ “ወታደሮቹ እናንተ የኦጋዴንን ሰዎች እናጠፋችኋለን፤ ምንም ዓይነት ነዋሪ እዚህ አካባቢ አንፈልግም፤ እንጨርሳችኋለን” ይሉናል፡፡ “እስርቤት ሳለሁ አንቀውኝ ነበር፤ በሳንጃም ወግተውኛል፤ በየጊዜው መላ አካላቴን ደብድበውኛል፤ ጭንቅላቴን በኤሌትሪክ ጠብሰውታል፤ የማያደርጉት ዓይነት ስቃይ የለም …” በማለት ምሬት እና ሰቆቃ በተሞላበት ድምጽ ምስክርነቷን ስትሰጥ ትደመጣለች፡፡ ኦብነግ በአካባቢው እንዳለ እና ሠራዊቱ አንድ መቀመጫ ቦታ እንደሌለው፤ በተገኘው አጋጣሚ ወደ ሰፈር እንደሚመጡ እና የሚፈልጉትን እንደሚያገኙ ፋጡማ ትናገራለች፡፡Ogaden 12
ህወሃት በበረሃ በነበረበት ጊዜ ተጋዳላዮቹ በየምሽቱና በየሌሊቱ ወደ መንደራቸውና ሰፈራቸው በሚመጡበት ጊዜ የትግራይ እናቶች ልጆቻቸውን ምግብና መጠጥ እያሲያዙ፤ ስንቅ እንየቋጠሩ ይልኩ ነበር አቶ ስዬ አብርሃ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ እንዲያውም የራሳቸውን እናት ጠቅሰው ብዙዎችን ይመግቡ እንደነበርና ለበርካታ ተጋዳላዮች “እናት” እንደነበሩ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
በህወሃት አዛዥነት ወደ ሥፍራው የተላከው ሠራዊት አስገድዶ መድፈር አንዱ የጥቃት መሣሪያው ነው፡፡ በወታደራዊ ሠፈሮች ውስጥ ሴቶች ለወሲብ መገልገያ ሆነዋል፤ ከሚደርስባቸው ሰቆቃ በተጨማሪ በተደጋጋሚ በበርካታዎች ይደፈራሉ በሚለው የግራሃም የቪዲዮ ዘገባ ላይ የስቃይ እንባ የምታፈሰውን ሚሪያም “በተደጋጋሚ ተደፍሬአለሁ፤ ድርጊቱ መደበኛ እየሆነ ከመምጣቱ የተነሳ ተቀበልነው” ስትል ያሳያል፡፡ “ብዙዎች በጣም አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ፤ አንዳንዶችም የሚጥል በሽታ ይዟቸዋል ሌሎችም እውር ሆነዋል፤ እኔም ራሴ ከደረሰብኝ ስቃይና ድብደባ የተነሳ አሁን እየተሻለኝ ቢሆንም የጡንቻ መኮማተርና የሚጥል በሽታ ይዞኛል፡፡”
የኦጋዴን ጭፍጨፋ መሃንዲሱና ጀማሪው ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ነው፡፡ የሙት ውርስ እንጠብቃለን የሚሉት አወዳሾቹም በሙት መንፈስ እየተመሩ ግፉን ቀጥለውበታል፡፡Ogaden 13
የኢትዮጵያን ስም ይዞ በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ የዘመተው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ሠራዊት ኦጋዴን በደረሰበት ጊዜ የፈጸመውን እማኞቹ በግልጽ ያስረዳሉ፡፡ “የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት ይሁኑ ወይም ልዩ ፖሊስ እኔ አላውቅም” የምትለው ፋጡማ ሰፈሮቻቸው በወራሪው ሠራዊት ከተከበበ በኋላ ከብቶቻቸው፤ ግመሎቻቸው፤ … በአጠቃላይ ንብረታቸው እንደተዘረፈ ትናገራለች፡፡ ከሁለቱ ሴቶች ጋር በመስማማትም ወንዶች እየተነጠሉ እንደተገደሉ ታስረዳለች፡፡ በተለይ የተማሩ የሚባሉ የኦጋዴን ወጣቶችን እየለዩ እንደገደሉ የሟች ቤተሰብ የሆኑት እነዚህ እህቶች በቃለምልልሱ ላይ ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ ሁልጊዜ የሚባሉትም “አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” መሆኑን ግፍ፤ እልህና ሲቃ በሞላው ድምጽ ይናገራሉ፡፡ ዘጋቢ ፊልሙ ላይ በተሰጠው መረጃ መሠረት ይህንን ግፍ የሚፈጽሙት ግዢው ህወሃት በልዩ ሁኔታ ያሰለጠናቸው በትምህርት ያልታነጹ፤ ወታደራዊ ዲሲፒሊን የሌላቸውና ከወሮበላ የማይተናነስ ባህርይ ያላቸው ጨካኝ ፓራሚሊታሪዎች እንደሆኑ ያስረዳል፡፡
ህወሃትንና ሹሞቹን በዚህ የኦጋዴን ዘር ማጥፋትና በሰብዓዊ ዘር ላይ በሚፈጸም ወንጀል ማስከሰስ፤ ለፍርድ ማቅረብ የኦጋዴን ወገኖችንና የመላ ኢትዮጵያ ልጆችን ትብብር ይጠይቃል፡፡ ስቃይ፣ መከራ፣ ሰቆቃ፣ … ካላስተባበረን ሌላ ምን ሊያስተባብረን ይችላል? ሰዎች ደስታን እንደመሰላቸው ሊተረጉሙት ይችላሉ፤ ግፍ ግን ቋንቋውና ስሜቱ አንድ ዓይነት ነው – እስከ አጥንት ይዘልቃል፤ መቅኔን ይቆጠቁጣል፡፡
Ogaden 15ከአዘጋጆቹ፤ ምንም እንኳን በጋዜጠኛነት ተግባር ላይ የምንገኝ ቢሆንም የእነዚህ እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን መከራና ስቃይ ያመናል፤ ያስለቅሰናል፡፡ ከአንዲት እናት የተወለድን ሰብዓዊ ፍጡር እንደመሆናችን የሴቶች ስቃይ ከምንም በላይ ልባችንን ያሳምማል፡፡ እንደ ኢትዮጵያዊ ይህንን ስቃይ ማቅረብ ሌላውን ዜና የመዘገብ ያህል ቀላል አይደለም፡፡ ድርጊቱ አሁን የተፈጸመ ያህል እየተሰማቸው አሁንም ትኩስ እንባ እያፈሰሱ ስቃያቸውን የገለጹት እህቶቻችን ህመም የማያመውና የማያስለቅሰው ህወሃትና በድንቁርና ጭለማ ውስጥ የገቡት ጀሌዎቹ ናቸው፡፡ ህወሃት ይህንን ዓይነቱን ግፍ ሲደርግ ኖሯል፤ አሁንም እያደረገ ነው፤ ኢትዮጵያ ግን አሁንም ከእናንተ የኦጋዴን ግፉአን ጋር ታለቅሳለች፡፡
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Thursday, June 23, 2016

አንዳርጋቸው ጽጌ የታገተበትን ሁለተኛ አመት ስናስታውስ ለነጻነት ትግሉ ያለንን ቁርጠኝነት በማደስ ነው!!!

June 23,2016

የወያኔ አገዛዝ በአቡደራቡህ መንሱር ሃዲ ይመራ ከነበረው የየመን መንግሥት ጸጥታ ሃይል ጋር በመመሳጠር አንጋፋውን መሪያችንንና የትግል ጓዳችንን አንዳርጋቸው ጽጌን ከሰነዓ አውሮፕላን ማረፊያ አግቶ በቁጥጥሩ ስር ካስገባ እነሆ ዛሬ ሁለት አመት ሞላው።
የአለም አቀፉን ህግ በመተላለፍ ህወሃት ድንበር ተሻግሮና ባህር አቁርጦ አንዳርጋቸው ጽጌን ከየመን ሲያግት ቢያንስ ሁለት ውጤቶችን ለማግኘት አሰፍስፎ እንደነበር መገመት አያስቸግርም። አንደኛው ሥልጣን ላይ ተደላድሎ ለብዙ አመታት የመቆየት ምኞቱን አደጋ ላይ የጣለበትን የአርበኞች ግንቦት 7 እንቅስቃሴ አከርካሪ በመምታት ትግሉን አሽመደምደዋለሁ የሚል የተሳሳተ ስሌት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ህወሃትን የሚግደራደር ሃይል የትም ቢሆን ሊያመልጥ እንደማይችል በማሳየት የኢትዮጵያን ህዝብ አንገት ለማስደፋትና በፍርሃት አንቀጥቅጦ ለመግዛት የታለመ የእብሪት ውሳኔ ነው።
በዚህም ስሌት ህወሃት አንዳርጋቸው ጽጌን በእጁ ለማስገባት በአፈናው ተግባር ተባባሪ ለሆነው ለመንሱር ሃዲ መንግሥት ዘጠኝ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደከፈለ በራሱ አንደበት ሳይደብቅ ለደህንነት አባላቶቹ ሲናገር ተደምጧል። ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ከድህነት ወለል በታች ላለቺው አገራችንና የዕለት ህይወቱን ከአለም አቀፍ ህብረተሰብ በሚለገስ የምግብ ዕርዳታ ለሚገፋው ህዝባችን ምን ማለት እንደሆነ ግልጽ ነው። በግዜያዊ ጥቅም አይናቸው የታወረዉ የየመን መንግሥት ባለስልጣኖችም ቢሆኑ ለፍትህ፥ ለእኩልነትና ለነጻነት የሚታገልን አንድ ኢትዮጵያዊ በአገሩ አየር መንገድ ሲጓዝ አግተዉ ለወያኔ ሲያስረክቡ ለረጂም አመታት በዘለቀዉና ለወደፊትም ጸንቶ በሚቆየዉ የሁለቱ አገሮች ወዳጅነት ላይ ጥሎት የሚያልፈዉ መጥፎ ጠባሳ የታያቸዉ አይመስልም። የሰነዓውን ኦፕሬሽን በህወሃት በኩል የመራውና አንዳርጋቸዉ ጽጌ እጆች ላይ ካቴና አጥልቆ ለወያኔ ያስረከበው አብረሃም መንጁስም ቢሆን በሱልጣን ሽኩቻ ከነበረበት ሃላፊነት ተፈንግሎ ዛሬ የት እንዳለ ከሱ ከራሱ ዉጭ ሌላ ሰዉ የሚያዉቅ አይመስለንም።
የህወሃት አፈናና ጭቆና የመረረው ህዝባችን አንዳርጋቸው ጽጌን ለማገት የተሄደበት ርቀትና የተከፈለው ዋጋ በነጻነቱ ላይ የተቃጣ ድፍረት መሆኑን ያሳየው “እኔም አንዳርጋቸው ነኝ” በሚል ቁጣ ሆ ብሎ በመነሳት ነው። አገር ውስጥና ከአገር ውጪ የተቀጣጠለው ይህ ህዝባዊ ቁጣ በአንድ አንዳርጋቸው መታገት እልፍ አእላፍ አንዳርጋቸውን ከማፍራቱም በላይ የህወሃት መሪዎችንና ጋሻ ጃግሬዎቻቸው እንደለመዱት ደረታቸውን ነፍተው በሠላም እንዳይወጡና እንዳይገቡ ወደ ሚያሸማቅቃቸው የተግባር እርምጃ ተሸጋግሮአል።
አርበኞች ግንቦት 7 ከአንዳርጋቸው መታገት በኋላ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ቁጣ የአንዳርጋቸዉ የረጅም ጊዜ ምኞትና ትግል ላይ በነበረባቸዉ አመታት በከፍተኛ ደረጃ የደከመበት የልፋቱ ዉጤት ነው ብሎ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 ይህንን ህዝባዊ ቁጣና ህዝባዊ መነቃቃት አስተባብሮና የሚያስፈልገውን አመራር ሰጥቶ ትግሉን ከዳር ለማድረስ በሙሉ ሃይሉና ጉልበቱ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለወዳጅም ለጠላትም ይገልጻል።
የምንወደውና የምናፈቅረው የትግል ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ የታገተበትን ሁለተኛ አመት ስናስታውስ ይህ ጀግና ሰዉ የጀመረውን ትግል ከዳር ለማድረስ ያለንን ቁርጠኝነት በማረጋገጥ ነው። ለፍትህ ለእኩልነትና ለነጻነት ሲታገሉ የወያኔ ሠለባ የሆኑ ወገኖቻችንን በፍጹም እንደማንረሳቸዉና በየዕስር ቤቱ በዘረኞች እብሪት እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖቻችን ሁሉ ነጻ እስኪወጡ ድረስ እነሱ አንግበው የተነሱትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ቆራጥነት ትግሉን እንደምንቀጥል ቃል እንገባለን።
የትግል ጓዳችን አንዳርጋቸዉ ሆይ ! ያንተና እንዳንተ በወያኔ ሰቆቃ የሚፈጸምባቸው ጓዶቻችን ሁሉ የመከራ ዘመን የሚያበቃው የወያኔ የሥልጣን ዕድሜ ለማሳጠር የጀመርከውን ትግል ከዳር ስናደርስ መሆኑን አንተም ታውቀዋለህና እንደምንታደግህ አትጠራጠር።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታሰር የነጻነት ትግሉን አቀጣጥሎታል ሲል አርበኞች ግንቦት7 ገለጸ

June 23,2016

ኢሳት ዜና :- ንቅናቄው የድርጅቱ ከፍተኛ የአመራር አባል የታሰሩበትን ሁለተኛ አመት ለማስታወስ ባወጣው መግለጫ “ ህወሃት አንዳርጋቸው ጽጌን በእጁ ለማስገባት በአፈናው ተግባር ተባባሪ ለሆነው ለየመኑ የቀድሞ መሪ መንሱር ሃዲ መንግሥት ዘጠኝ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ቢከፍልም፣ አፈናው በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ ህዝባዊ ቁጣ ከመቀስቀስ እና እኔም አንዳርጋቸው ነኝ የሚሉ ታጋዮች ትግሉን እንዲቀላቀሉ እንዲሁም ወደ ተግባር ትግል እንዲገቡ ከማድረግ ውጭ በድርጅቱ ላይ ያሰበውን ድል አላገኘም ብሎአል።
“የሰነዓውን ኦፕሬሽን በህወሃት በኩል የመራውና አንዳርጋቸዉ ጽጌ እጆች ላይ ካቴና አጥልቆ ለወያኔ ያስረከበው አብረሃም መንጁስም ቢሆን በሱልጣን ሽኩቻ ከነበረበት ሃላፊነት ተፈንግሎ ዛሬ የት እንዳለ ከሱ ከራሱ ዉጭ ሌላ ሰዉ የሚያዉቅ አይመስለንም” የሚለው የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ፣ የአንዳርጋቸው መያዝ የፈጠረው ህዝባዊ ቁጣ የህወሃት መሪዎችንና ጋሻ ጃግሬዎቻቸው እንደለመዱት ደረታቸውን ነፍተው በሠላም እንዳይወጡና እንዳይገቡ ወደሚያሸማቅቃቸው የተግባር እርምጃ አሸጋግሮታል ብሎአል።
ከአንዳርጋቸው መታገት በኋላ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ቁጣ የአንዳርጋቸዉ የረጅም ጊዜ ምኞትና በትግል ላይ በነበረባቸዉ አመታት በከፍተኛ ደረጃ የደከመበት የልፋቱ ዉጤት ነው ብሎ እንደሚያምን የገለጸው ድርጅቱ፣ አርበኞች ግንቦት 7 ይህንን ህዝባዊ ቁጣና ህዝባዊ መነቃቃት አስተባብሮና የሚያስፈልገውን አመራር ሰጥቶ ትግሉን ከዳር ለማድረስ በሙሉ ሃይሉና ጉልበቱ እየተንቀሳቀሰ ነው ሲል አክሏል።
ንቅናቄው “የትግል ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ የታገተበትን ሁለተኛ አመት ስናስታውስ ይህ ጀግና ሰዉ የጀመረውን ትግል ከዳር ለማድረስ ያለንን ቁርጠኝነት በማረጋገጥ ነው” ያለ ሲሆን፣  ለፍትህ ለእኩልነትና ለነጻነት ሲታገሉ የአገዛዙ  ሠለባ የሆኑ በየዕስር ቤቱ  እየተሰቃዩ ያሉ ሁሉ ነጻ እስኪወጡ ድረስ ትግሉን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በሌላ በኩል በእንግሊዝ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቀኑን በማስመልከት በእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል። ሰልፉ በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ መሆኑን ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀጸላ ከስፍራው ዘግባለች ።

Wednesday, June 22, 2016

ህወሃት “አምባሳደሮችን” በታማኞቹ ሊተካ ነው

June22,2016
“የማይታመኑ ከሆነ “አለመታመናቸውን” ማሳየት አለባቸው”
ambassadors

በተለያዩ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በወሳኝ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ እንደሆነ ተነገረ፡፡ በህወሃት ውስጥ ያለው ፍርሃቻና አለመረጋጋት ለሁኔታው አስገዳጅነት ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡ ህወሃት ለዓመታት ያገለገሉትን ሎሌዎች የማያምናቸው ከሆነ እነርሱም “አለመታመናቸውን” ማሳየት ይገባቸዋል፡፡
በአሜሪካ፤ በአውሮጳ፤ በአውስትራሊያና በኢትዮጵያ አጎራባች በሆኑ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በቅርቡ ወሳኝ በሆኑ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ መታሰቡን ማንነታቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የጎልጉል መረጃ አቀባይ አስታውቀዋል፡፡ ለመረጃው ቅርብ እንደሆኑና የአገራቱም ዝርዝር እንዳላቸው የተናገሩት መረጃ አቀባይ የሹምሽሩ ምክንያት ይህ ነው ተብሎ በውል ባይታወቅም ህወሃት ከውስጥና ጫና ተጠቃሽ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡
በኢህአዴግ ተለጣፊና ድቃይ ድርጅቶች ታቅፈው የሥርዓቱ ሎሌ የሆኑት አምባሳደሮች በመጪዎቹ ሳምንታትና በሐምሌ ወር ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እንደሚደረግ ታውቋል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚደረግ ዓመታዊ ስብሰባና ግምገማ ተብሎ ሽፋን የሚሠጠው ይኸው አምባሳደሮችን የመጥራት ውሳኔ በህወሃት ሰዎች የተቀነባበረና የትኞቹን አምባሳደሮች በማን ለመተካት እንደታሰበ አስቀድሞ የተወሰነ ነው፡፡ በዓለምአቀፍ የዲፕሎማሲ ህግጋት መሠረት የሚነሱት አምባሳደሮች መረጃ ለየአገራቱ ደርሷል፡፡
ለ25 ዓመታት እጅግ አሰቃቂ ወንጀሎችን በመፈጸም በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን በፍግ እየገዛ ያለው የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር ከፍተኛ ችግር ውስጥ በሚወድቅበት ጊዜ ታማኝ የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ነባር ታጋዮች ላይ አመኔታውን በማድረግ “ክፉ ጊዜያትን” ሲያልፍ ቆይቷል፡፡ የአሁኑም ጉዳይ ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ ነገራል፡፡
በተለይ በሰብዓዊ መብት ረገጣ እያደረሰ ያለው ግፍ ከበቂ በላይ በሆነ ማስረጃ በተደጋጋሚ እየወጣበት ባለበት ባሁኑ ጊዜ የወደፊቱ ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው መመለስ ያለበት ጥያቄ ሆኗል፡፡ ለዚህም ይመስላል በሰሜኑ ኢትዮጵያ ከአማራው ክልል ጋር ተያይዞ ያለውን አደገኛ ሁኔታ ለማምከን የኤርትራ ካርዱን የመዘዘው በማለት አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡ ወራትን ያስቆጠረው የኦሮሞ ወጣቶች ተቃውሞ ከሁሉም በላይ አረመኔነቱንና ለሥልጣኑ ሲል የማይፈጽመው ወንጀል እንደሌለ በግልጽ ያሳየ መሆኑን ሰሞኑን የወጣው የሰብዓዊ መብት ተመልካቹ መ/ቤት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ዘገባ ያሳያል፡፡
በተለይም በያዝነው ዓመት ጥር ወር አካባቢ የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ የሚያስገባ” ባለ 19 ነጥብ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፡ በወቅቱ ውሳኔው ኢህአዴግ “ልክ ሊገባ ይሆን” የሚል አመለካከት መጫሩን ጎልጉል ጠቅሶ በጻፈበት ወቅት “ረቂቁ ለውይይት እንዳይቀርብ የቻሉትን ያህል የጣሩት ቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያቸው” አለመሥራቱን፤ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ውሳኔው “ውስጡ በብረት የተወጠረ የቦክስ ጓንቲ ነው” ማለታቸውን ጨምሮ ዘግቦ ነበር፡፡ ይህ በዝርዝር መረጃ ቀርቦበት ለውሳኔ የበቃው ሰነድ ቀኑን ጠብቆ ህወሃት ላይ ሰይፉን እንደሚመዝ የወንጀሉ ተዋናዮች ከማንም በላይ የሚረዱት እውነታ ሆኗል፡፡
በአሜሪካ፤ ወሳኝ በሆኑ የአውሮጳ ከተሞች (ህብረቱ ያለበትንም ጨምሮ) እንዲሁም በኢትዮጵያ አጎራባች አገራት ያሉ አምባሳደሮች በታማኝ የህወሃት ተጋዳላዮች ለመተካት መታሰቡ የዲፕሎማሲው ተጽዕኖ ያስከተለው ጫና ብቻ ሳይሆን በህወሃት ውስጥ ሌላም ፍርሃቻ ስለአለ ነው በማለት ጉዳዩን ከሌላ አንጻር የሚመለከቱ ይናገራሉ፡፡
አሊ ኦጃሊ
አሊ ኦጃሊ
ምዕራባውያን ኃይላት ትኩረታቸውን ሊቢያ ላይ አድርገው ጋዳፊን ከሥልጣን ለማውረድ እንቅስቃሴ በጀመሩበት ወቅት ዓመጹ እየተፋፋመ ሲሄድ በየአገሩ የነበሩ የጋዳፊ ታማኞች መክዳታቸው ይታወሳል፡፡ ጋዳፊ ህይወታቸው በOctober 2011 ከማለፉ ስምንት ወራት በፊት በዋሽንግተን ዲሲ ታማኝ አድርገው ያስቀመጧቸው አምባሳደር አሊ ኦጃሊ ጋዳፊን መክዳታቸው ይታወቃል፡፡ ለጋዳፊ ታማኝ በመሆን አርባ ዓመት ያህል ያገለገሉት አምባሳደሩ በወቅቱ ከከዱ በኋላ የአማጺውን ኃይል ተቀላቅለው ነበር፡፡ ከዚህ አልፈው በአሜሪካ የአማጺው አፈቀላጤና ተወካይ በመሆን ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ የጋዳፊ መውደቅ እውን እየሆነ ሲሄድ አሜሪካ መልሳ በቦታቸው አስቀምጣቸው ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ህወሃትን ያስፈራው ይህንን መሰል የፖለቲካ ቁማር እንደሆነ ይነገራል፡፡
ከሎሌነት ባላለፈ አገልግሎት የሚሰጡትን “የራሴ፤ ታማኞቼ” ከሚላቸው ጋር ፈጽሞ እኩል ሊያደርጋቸው የማይፈልገው ህወሃት የፖለቲካው ትኩሳት አቅጣጫውን የቀየረ ዕለት የአሊ ኦጃሊን መንገድ ሊከተሉ ይችላሉ ብሎ የጠረጠራቸውን በቶሎ ለመተካት መወሰኑ “ከጋዳፊ ተምረናል” የሚል እንድምታ እንዳለው ይነገራል፡፡ በየትኛውም የለውጥ እንቅስቃሴ ጊዜ በተለይ በጎረቤትና በኃያላን አገራት ያሉ አምባሳደሮች መክዳት አልፎም ንቅናቄውን መቀላቀል የአምባገነኖችን ዕድሜ በማሳጠር በኩል ቁልፍ ሚና ይኖረዋል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ህወሃት ምዕራባውያን በተገኘው አጋጣሚ ፊታቸውን እንደሚያዞሩበት በመገመት ይህንን መሰሉን ጥንቃቄ ማድረጉ ሥልጣኑን እንዴት እንደሚንከባከብ የሚያሳይ ነው፡፡ በተለይ የኦህዴድ መሸርሸርና በክልሉ ያለው ዓመጽ እስካሁን አለመብረድ ከአምባሳደር ጀምሮ እስከ በታች እርከን የቆንስላ ተግባራት ላ የተሰማሩ ኦሮሞ ዲፕሎማቶችንና ሠራተኞችን በዓይነቁራኛ እንዲታዩ እያደረጋቸው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር “ለችግር ጊዜ አትታመኑም” ተብለው እንደሸቀጥ እንዲመለሱ የሚጠሩት አምባሳደሮች ቀን ፊቷን ሳታዞርባቸው ለምንስ በእርግጥ “የማይታመኑ መሆናቸውን” ለህወሃት አያሳዩትም በማለት የዜናው አቀባይ ለዲፕሎማቶቹ ጥሪ አዘል ምክር ለግሰዋል፡፡   (ፎቶ: ያለፈው አመት ሹመኞች)
ምንጭ ጎልጉል

Monday, June 20, 2016

BREAKING: Genzebe Dibaba’s coach arrested in doping raid

June 20,2016
image
BARCELONA, Spain (AP) — The coach of World 1500m champion Genzebe Dibaba and other long-distance runners was arrested near Barcelona after Spanish police raided his hotel room and found traces of EPO and other banned substances on Monday.

Jama Aden, a Somalian, was detained along with one of his unnamed trainers from Morocco, as the IAAF tested 30 athletes who were also guests at the Sabadell hotel, about 25 kilometers from Barcelona, where the coach has established annual training camps since 2013.

Police confirmed Aden and his trainer were under arrest on charges of administering and distributing doping substances and endangering public health. After questioning by law enforcement, both detainees should face prosecution within 72 hours.

Local authorities did not expect further arrests to follow.

The athletes, including Dibaba, at the raided hotel were mainly from Somalia, Sudan, Ethiopia or Djibouti.

Dibaba is a heavy favorite to win the Olympic women’s 1500m in Rio de Janeiro.

A simultaneous police raid in Madrid also yielded 16 arrests related to the trafficking of drugs and anabolic steroids.

Despite coinciding in time, law enforcement officers stressed there was no connection between the Sabadell operation and the bust in the Spanish capital, mainly linked to the bodybuilding underground market for steroid users.

Source: AP

” የኢህአዴግ” እና “ህግደፍ” የሰሙኑ ዉጥረት



June 20,2016
(የግል እይታ) – ዑስማን ካዋጃ
Ethiopiaየዛሬ 25 አመት የዓረቦች ታላቅ ህልም እና አጀንዳ በኢህአዴግ እና ህዝባዊ ግንባር ንዲሞክራሲን ፍትሕን (ህግደፍ) ኣስፈፃሚነት ተግባራዊ ሆነ ፡፡ የኢ/ያ ህዝቦችን በመሳርያ አፈሙዝ በማስገደድ ፡ ኤርትራውያንን የፈጠራ ታሪክ በመጋት እና Mass hallusination በመፍጠር ሁለት አገሮች ተፈጠሩ፡፡ ኤርትራ የግላችን ኢ/ያ የጋራችን የሚል የዝርፍያ እቅድ በ “ህግደፍ” ተነድፎ ሁለቱም ባለግዜዎች ለተግባራዊነቱ ተረባረቡ፡፡ እነ ቀይባህር ኮርፖሬሽን ተመስርተው ኢ/ያ ያለምንም ከልካይ ተዘረፈች፡ እነ Horn international bank በብድር እና እና እርዳታ የተገኘውን የውጭ ምንዛሪ በሰአታት ፍጥነት ህጋዊነትን አላብሰው አስመራ አደረሱት፡፡ ስለ አገር መቆርቆር እንደወንጀል ተቆጠረ፡ ምስጋና ለወቅቱ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪ ለነበሩት አቶ ገብሩ አስራት ይህን የዝርፍያ እቅድ በተቻላቸው መጠን ለመከላከል ሞከሩ በውጤቱም በተለምዶ ኢትዮ ኤርትራ የሚባለውን ግጭት ተቀሰቀሰ፡፡
ከ ሁለት ዓመታት ከባድ ጦርነት በኢትዮጵያ ልጆች ከባድ መስዋዕትነት የሻዕብያ ምሽግና ትዕቢት ተናደ፡፡ የኢ/ያ ጦር አሰብን ለመቆጣጠር ጥቂት ኪሎሜትሮች ሲቀሩት ታላቁ ” ባለራአይ” መሪያችን ራዕያችንን እንዳይሆን አድርገው አኮላሹት፡፡
ሰሙኑን የኢትዮ-ኤርትራ ግጭት እንደ አዲስ ተማሙቋል፡ አፍቃሪ ኢህአዴግ ሚድያዎች እና ትናንሽ ካድሬዎት ግቡ ባይታወቅም የጦርነት ነጋሪት እየጎሰሙ ናቸው፡፡ እኔ በግሌ የሰሙኑን የጦርነት አጀንዳ አጥብቄ እቋወማለሁ ለምን ቢባል:
1)ኢህአዴግ ኤርትራ ላይ ባለው ጭንጋፍ አቋም፡
ገዥው ፖርቲ ምን ግዜም ኤርትራ እና ህጋዊ የባህር በር የማግኘት መብታችን በተመለከተ ምን ግዜም ከኢትዮጵያ ህዝቦች በተፃራሪ እነደቆመ ነው፡፡ታድያ ይህን የገዢው ፖርቲ ፀረ ኢ/ያ አቋም ሳይቀየር ምን ለማግኘት ነው ጦርነት ውስጥ የምንገባው? እዚህ ላይ ሻዕብያን አስወግዶ ለኢ/ያ ችግር የማይፈጥር መንግስት ለመመስረት የሚል ውሃ የማይቋጥር ምክንያት በትናንሽ ካድሬዎች ይቀርባል ግን እንበል እና አዲስ የሚመሰረተውስ መንግስት ፀረ ኢ/ያ እንደማይሆን መተማመኛችን ምን ድነው?
2) ቀይ ባህር ላያ የጦር ሰፈሮቻቸው እየገነቡ ባሉ የኢ/ያ ታሪካዊ ባላንጦች ከዚህ አፍራሽ ተግባራቸው በዘላቂነት መከላከል የሚቻለው አስመራ ቤተመንግስት ላይ የሰው ለውጥ በማድረግ ሳይሆን ቀይ ባህርን በቆዋሚነት በመቆጣጠር ነው፡፡ ይህን ማድረግ የሚችል አርቆ አሳቢ መሪ እና ፖርቲ በሌለበት የሚካየድ ጦርነት ኢ/ያን ከባድ ዋጋ ከማስከፈል አልፎ የሚያመጣው ብሄራዊ ጥቅም የለም፡፡
3) የኤርትራውያን ከእንቅልፋቸው አለመንቃት፡
የሆነ ኤርትራዊ የችግራችሁ ምንጭ ምንድነው ብለን ብንጠይቀው መልሳቸው ተመሳሳይ ነው…..ኢሳያስ ኢትዮጵያዊ የደም ሃረግ ስለው ይሉናል ፡፡ታድያ ችግራችሁ እንዴት ይፈታል? የሚል ጥያቄ ብናስከትል አሁንም ገራሚ መልስ ይነግሩናል…..ኤርትራ በንፁህ ኤርትራዊ(ደቂ አባት) ስትመራ ይሉናል፡፡ከኢትዮጵያ ጋር በደም ያልተሳሰረ ንፁህ ኤርትራዊስ ማነው? ማንም ኤርትራዊ ይችን ጥያቄ መመለስ አይችልም፡፡ ታድያ የችግራቸው ምንጭ ትዕቢት፡ክፋት፡ድንቁርና፡ቅዠት፡አዲስ የተፈበረከ የውሸት መንነት: Mass Hallusination መሆኑን መውል ሳይገነዘቡ እና ስህተታቸው ለማረም ከውስጥ እንቅስቃሴ ባልጀመሩበት የኛን በማያገባን ጥልቅ ማለት ምን ለማትረፍ ነው???
እናም የኢህዴግን ባህሪ ባልተቀየረበት ወይም የኢ/ያ ብሄራዊ ጥቅምን ሳይሸራረፍ ሊያስፈፅም የሚችል ፖርቲ ባልተፈጠረበት የሚካየድ ጦርነት ኤርትራውያንን ከኢሳያስ አገዛዝ ነፃ ከማውጣት እና ኢትዮጵያውያን እናቶችን ዳግም ማቅ ከማልበስ ባለፈ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ስለማያመጣ አጥብቄ እቋወማለሁ፡፡

Ethiopia-Eritrea Wargames of Mass Distraction? – Alemayehu G. Mariam

June20,2016
unnamedthe Global Terrorism Database.
In April 2011, the late TPLF thugmaster Meles Zenawi was talking about war, rumors of war and war with Eritrea and a water war with Egypt.
Here we go again in June 2016.
In the past few days, we are hearing once again talk about war, rumors of war and drumbeats of war signaling a ground war between Ethiopia and Eritrea.
But are we also watching a wargame of mass distraction?
T-TPLF communication minister Getachew “Motor Mouth” Reda said, “There were significant casualties on both sides, but more on the Eritrean side. We used to take precautionary measures against this regime, but this time was much more important in terms of magnitude than the measures that were taken so far.” (Whatever that means!)
Eritrea claimed to have killed 200 Ethiopian soldiers and wounded 300 more.
Hiram Johnson, a famous U.S. Senator from California, long ago said, “The first casualty, when war comes, is truth.”
When the two warring parties agree on the same “truth”, I begin to wonder if truth is the first and only casualty.
I also begin to smell the stench of a rat. I can smell a rat from 10 thousand miles away.
Sniff! Sniff! “Ethiopia- Eritrea War”.
Of course, Johnson’s dictum on the first casualty of war does not apply to wargames.
I have observed over the years that every time the T-TPLF leaders find themselves in a superbad publicity pickle, they conjure up a wargame.
I guess that is the T-TPLF’s way of hard-jamming the bad news and distracting domestic and international attention from their ongoing crimes against humanity, corruption, abuse of power and brutal suppression of all dissent.
There is no question the past few weeks have been all bad news for the T-TPLF.
Last week, the U.S. Securities and Exchange Commission (SEC) slammed the T-TPLF big time and ordered it to cough up $6.5 million it illegally ripped off from its supporters and other favor-seeking and bootlicking Diaspora Ethiopians in the U.S. They have to fork the money over to an independent Administrator appointed by the SEC no later than July 8, 2016.
That has got to be pretty humiliating for the T-TPLF and a big blotch on the memory of the late thugmaster who bragged about building the largest dam in Africa by shaking down the people of Ethiopia and Diaspora Ethiopians.
Imagine building a dam by racketeering in unregistered bonds in the U.S.! Bond protection racket?
I can imagine the T-TPLF leaders chafing over the fact that they got caught with their hands in the cookie jar three years after I had cited to them the chapter and verse the U.S. Code they were violating by selling unregistered bonds in the U.S.
I told them straight up on May 8, 2013. Don’t do it! Don’t sell unregistered bonds. It is a crime under U.S. federal and state laws. Don’t do the crime, it will come back to haunt you in time.
Three years later the crime of selling unregistered bond (It is a crime; See “Securities Act of 1933”, sec. 20 (b)) came back to haunt them.
But the T-TPLF’s snake oil unregistered bond salesmen barely escaped criminal prosecution.
But did they really?
The T-TPLF leaders have been getting away with crimes against humanity for so long that they thought they could also get away thumbing their noses at American laws.
They did not.
On the heels of the SEC revelation and order, Human Rights Watch (HRW) issued a major report entitled, “‘Such a Brutal Crackdown’: Killings and Arrests in Response to Ethiopia’s Oromo Protests.”
That report details the T-TPLF’s “use of excessive and unnecessary lethal force and mass arrests, mistreatment in detention, and restrictions on access to information to quash the protest movement.”
Leslie Lefkow, HRW Deputy Africa Director, said, “Ethiopian security forces have fired on and killed hundreds of students, farmers, and other peaceful protesters with blatant disregard for human life.”
Firing into a gathering of “peaceful protesters with blatant disregard for human life” is a crime against humanity. I just want to say that for the record.
In December 2015, T-TPLF minister Reda said the people killed in the protests were “an organized and armed terrorist force aiming to create havoc and chaos has begun murdering model farmers, public leaders and other ethnic groups residing in the region.”
A bunch of high school and college kids protesting in the streets are “an organized and armed terrorist force”?
It reminds me of Puff the Magic Dragon in the Land of Living Lies where Puff takes a little girl called Sandy, to the Land of the Living Lies. There she meets such famous fibbers as Pinocchio and the boy who cried wolf.
In the Land of Living Lies, Puff and Sandy get to see the famous purple cow that no one has ever seen and pink elephant that some see too often.
In the Land of Living Lies that Ethiopia has become under the T-TPLF, school children and college students are seen as an “organized and armed terrorist force aiming to create havoc and chaos.”
I remember when Ethiopia was known as the “Land of 13-months of Sunshine”.
Anyway, President Uhuru Kenyatta and others were charged in count 2 of the International Criminal Court indictment in 2012 for their involvement in the massacres of nearly 2 thousand innocent and peaceful Kenyans during the 2007 presidential election in Kenya.
HRW called for an independent inquiry into the “Oromo Protest” massacres.
The T-TPLF, as always, has turned a deaf ear.
The T-TPLF has been getting bad publicity for its total incompetence in dealing with the famine situation affecting some 20 million Ethiopians and its shameless efforts to keep news of that devastation from international scrutiny.
In complicity with USAID and the other international poverty pimps, the T-TPLF has succeeded in stonewalling any real time information from the famine-stricken areas and sandbagged journalists from making the effort to discover the truth for themselves.
So far the T-TPLF has been somewhat successful in avoiding accountability for its gross negligence, incompetence and criminality in the famine situation. (See my letter to USAID Administrator Gayle E. Smith.)
It is understandable why the T-TPLF wants to hard-jam all the bad news.
What better strategy is there to hard-jam the news than manufacturing news of war and rumors of war to create mass distraction?
I must confess that I view a “war” between the T-TPLF and its “adversaries” to the north as the equivalent of medieval England’s War of the Roses. It is an in-house fight for power between different members of the same family.
The T-TPLF and their alleged adversaries fought together for years as a band of brothers to dislodge the military regime and seize power. They struggled as comrades-in-arms cooperating and helping each other in military operations and diplomatic offensives. There is ample evidence that various top T-TPLF leaders have family and kinship ties with their “adversaries”.
Once the T-TPLF took over power in 1991, they shared it cheerfully with those they now accuse as adversaries in a curious circus in which the tail wagged the dog. That ended in 1993-94.
Between 1998-2000, the former comrades-in-arms were tangled up in a border war. The Eritreans attacked and captured Ethiopian territory. They were repelled after “an estimated 70,000 to 120,000 soldiers and civilians have died in the conflict.”
The late thugmaster Meles Zenawi declared victory; and in an insidiously calculated act of political capitulation and betrayal agreed to turn over the recaptured territory to Eritrea in international arbitration.
When Zenawi lost in arbitration by conveniently failing to put up a vigorous legal defense, he said the arbitral decision is not worth the paper it is written on.
Now, the former comrades-in-arms say they are fighting a war. They are pointing accusatory fingers at each other.
But are they really fighting a war or just wargaming?
But why are they warring against each other? They don’t say.
A high level Eritrean official alleged that the U.N. report which “accused Eritrean leaders of committing crimes against humanity including torture, murder and enslavement” was orchestrated by Ethiopia: “The gathering of information from ‘witnesses’ organised by Ethiopia allows the latter to advance its propaganda against a country that it aims to destabilize.”
Could the U.N. report be the casus belli (cause for war)?
In his book “Why Nations Fight” (2010), Richard Ned Lebow argues that historically four motives — fear, interest, standing, and revenge – have led states to initiate war. He argues the majority of wars are fought in a quest for standing and for revenge in an attempt to get even with adversary states who had previously made successful territorial grabs.
Is standing, revenge and recapture of territory the cause for “war” between the two states today?
My studies of dictatorships and wars initiated by them suggest an alternative explanation.
Pulling out the “war card” is the oldest trick in the dictators’ handbook.
The “handbook” says, “When the going gets tough, declare war. Declare a real or fake war. It does not matter. Talk about war. Spread rumors of war. Sound the drumbeats of war. Play wargames.”
But why? Because war is a sure and proven method of mass distraction!
From the time of the Roman emperors to the present day, the lords and gods of war have played the war card and stirred up patriotic fever in the population to cling to and prolong their hold on power.
Over the millennia, the technology of war may have changed but the deceit, machinations, sophistry, treachery and modus operandi of war-mongers has remained the same.
Dictators often start with a war of words and flood their population with a propaganda of lies, fabrications and half-truths about the need for war.
The prelude to war launched by dictators follows a predictable pattern. They begin by making grandiose public statements about the necessity of war and demonize their enemies hoping to boost popular support at home.
They magically discover love of country and wrap themselves in their flags and become jingoistic (super-patriotic). They will even promise to reverse territorial losses in an attempt to stoke patriotism.
Dictators brazenly pander to the population using nationalism and chauvinism in an effort to mobilize public support. They manufacture mass hysteria about imminent attacks, invisible enemies, lurking terrorists, loss of sovereignty and the rest of it.
Every chance they get, they try to trigger paroxysms of public anger against the enemy and inflame public opinion with provocative and outrageously concocted stories designed to make themselves look patriotic and their opposition and enemies appear unpatriotic.
When all else fails, dictators openly incite fear and hysteria to distract public attention from their crimes and dictatorial rule.
More often than not, the war of words will not amount to much more than declarations of bravado and hyperbolic accusations and recriminations. It often ends at the stage of skirmishes.
But dictators will often continue to talk about and spread rumors of war long after the guns have been silenced in the battlefield.
But war is a tricky proposition for dictators.
The survival of dictators more often than not depends on whether they win a war they have started.
Defeat in war often means the end of dictators.
Defeated dictators are often ousted in coups or other violent mass upheavals. The likelihood of exile, jail and death for dictators increases geometrically with each war dictators lose.
Some African dictators have remained in power despite losing wars they have launched recklessly. Indeed, they have used defeat as a justification and excuse to brutally suppress their population. They have used their enemies as bogeymen to scare their own population into submission.
Other African dictators have no incentive to win a war they started or joined. They feel so entrenched in power that war becomes a wargame for them; but a war of death and destruction for their population.
No one made the fact of dictator-launched wars more clear than Hermann Goering, Hitler’s right-hand man. He told the following to his interrogator at the Nuremberg Trials in 1945:
Naturally the common people don’t want war. That is understood. But, after all, it is the leaders of the country who determine the policy and it is always a simple matter to drag the people along…Voice or no voice [democratic or non-democratic government], the people can always be brought to the bidding of the leaders. That is easy. All you have to do is tell them they are being attacked, and denounce the peacemakers for lack of patriotism and exposing the country to danger. It works the same in any country.
In April 2011, the late thugmaster Meles Zenawi echoed Goering when he said:
Recently, Eritrea is training and deploying Al Shabab and locally grown destructive forces to terrorize our country. But Egypt is the direct force behind these destructive elements that back them. Until now, our strategy has been defending our sovereignty by speeding up our development. Now, we found that we could not go any longer with passive defense. It’s not possible to take passive defense as the only alternative. Therefore, we have to facilitate ways for Eritrean people to remove their dictatorial regime. We have no intention to jump into their country but we need to extend our influence there. If the Eritrean government tries to attack us, we will also respond proportionally.
In December 2006, Zenawi used the exact same logique de guerre (war logic) at the onset of his unsuccessful 843-day war to dislodge the Islamic Courts Union and crush the Al Shabab in Somalia. He said:
With regard to physical attacks or physical acts of the invasion, what has happened since last summer is that the Islamic courts have been training, equipping and smuggling armed opposition elements into Ethiopia. These elements have been engaged in activities of destabilization in Ethiopia. Hundreds of these have been smuggled and they have been involved in clashes with security forces in Ethiopia. To the extent that the Islamic Courts have trained them, equipped them, given them shelter and transported them to the border for smuggling. To that extent, they are directly involved in an act of aggression on Ethiopia. And that has been going since summer. It is still continuing.
In 2009, after leaving Somalia with his tail between his legs, Zenawi waxed philosophical: “If the people of Somalia have a government, even one not positively inclined to Ethiopia, it would be better than the current situation. Having a stable government in place in Somalia is in our national interests.”
That is the same guy who in December 2006 said he will make mincemeat out of the terrorists in Somalia and be back home in a jiffy.
What Zenawi did was cause the death of tens of thousands of Somalis civilians through indiscriminate shelling and displacement of hundreds of thousands.
How many Ethiopian soldiers died in Zenawi’s war in Somalia?
In 2009, Zenawi told “parliament it does not need to know how many soldiers died in Somalia”.
Dictators can make cannon fodder of their population and tell everyone it is not their business to know how many died in a war.
Now we are told the T-TPLF and Eritrea are banging the drums of war. They are dancing to the drumbeat of war.
Of course, the obligatory warnings against war have come from the usual suspects.
The U.S. State Department issued a statement calling for “cessation of hostilities” and urged “both Ethiopia and Eritrea to cooperate in promoting stability and sustainable peace in the region.”
U.N. Secretary-General Ban Ki-moon called on Ethiopia and Eritrea “to show maximum restraint and abide by the accords that ended their border war seven years ago.”
The bottom line question is whether there is a war between Ethiopia and Eritrea or just wargames?
I do not know!
They are having wargames, methinks.
Both sides claimed to have killed and wounded hundreds.
All that sounds and smells fishy to me. It does not pass my smell test (no pun intended).
What I do know is that I have seen this movie (or is it circus?) before.
In 2011, I saw the political theatre of wargames in a three-ring propaganda circus intended to distract the Ethiopian population and diaspora critics from talking about T-TPLF’s crimes against humanity, corruption, abuse of power and the rest of it.
On the other hand, could it be that all of the talk of war and rumors of war is a cover for another kind of “war” that is deeply troubling the T-TPLF?
In my view, all the pretentious war talk betrays the T-TPLF’s preoccupation with the inevitable loss of power and control as a result of a spontaneous popular uprising. All the war talk reveals the deep anxieties and profound political angst of a regime trapped in a siege mentality.
President Kennedy observed, “In the past, those who foolishly sought power by riding on the back of the tiger ended up inside.”
The prospect of ending up inside an angry and hungry tiger’s belly is what keeps the T-TPLF leaders and supporters from sleeping at night and talking about the nightmare of war all day.
I believe the T-TPLF is deeply concerned about a war, but not a war with Eritrea.
It is concerned about a war with the people of Ethiopia.
The T-TPLF knows I am telling the truth because that is what they talk about to each other all the time. What if the people of Ethiopia….?
I do not know if what we are witnessing in June 2016 is a prelude to war or watching a band of brothers just playing wargames of mass distraction.
Could there be war among those who are on different sides of the same coin? They need each other to remain in power just as Siamese twins need each other to live. They are peas in a pod.
War is one thing neither side needs today; and they know it.
In October 2015, the U.N. Security Council “reaffirmed the arms embargo on Eritrea.”
Prosecuting a war under an arms embargo could prove exceedingly difficult.
The much maligned British Prime Minster Neville Chamberlain said, “In war whichever side may call itself victor. There are no winners. But all are losers.”
In an Ethiopia-Eritrea War, who will be the losers?
There is a familiar old saying about fighting (warring) elephants and the grass.
Why is it not possible for the grass to come out as the real winner in a war among elephants?
In April 2011, I wrote, “Time will show if there will be war or intervention in Eritrea, and a water war with Egypt…. But for now, no one needs to lose sleep over that prospect. The only war being waged today by Zenawi is a war of mass distraction.”
In April 2011, Zenawi threatened to “facilitate ways for the Eritrean people to remove their dictatorial regime.”
The facts of the last 5 years speak for themselves.
Call me naïve. Even say that I was born yesterday and do not understand geopolitics and all that.
It may be true that I am naïve and may have been born yesterday. But I was not born last night!
I will repeat what I said in April 2011 in June 2016. The “Ethiopia-Eritrea War” is a wargame of mass distraction.

Sunday, June 19, 2016

‹‹በኔ አመለካከት ጀነራል ሣሞራ ለመንግስትና ለህዝቡ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው፡፡›› ~ሜጀር ጀነራል አበበ ተ/ሃይማኖት

June 19,2016
Abebe ty

ሜጀር ጀነራል ኣበበ ተክለ ሃይማኖት የታጋይዮች ተወዳጅነት ገና ሳይደበዝዝ ነበር በጥሮታ ሰበብ ከመከላከያው የተገለሉት፡፡በሌላ አባባል ጀነራሉ ወታደር ሳይሆኑ ነበር የታጋይነት መዓርጋቸውን እንደጨበጡ ከድርጅቱ የተሰናበቱት፡፡
ይኸው የታጋይነት ትጥቃቸው አሁንም ድረስ ከርሳቸው ጋር ነው፡፡ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ግዜ ሰጥቶ ማንበብ የግድ ይላል፤ ከጊዜ እጥረት የተነሳ ሙሉውን ማንበብ ለማይችሉት ግን አንኳር አንኳሮቹን እንደሚከተለው አቅርቤያቸዋለሁ፡፡
‹‹
☞በዓለም አቀፍ ህግ የአሰብ ወደብን ማስመለስ እንችላለን
☞ለሕገ መንግስቱ በተሟላ መንገድ መተግበር የአቅሜን ያህል እታገላለሁ፡፡
☞እኔ ከመጀመሪያውኑ ስታገልላቸው ለነበሩ አላማዎች፣አሁንም በፅናት ቆሜያለሁ ነው የምለው፡፡
☞ገዥው ፓርቲ ነው ከትግሉ አላማዎች ወደ ኋላ እየተንሸራተተ ያለው፡፡
☞የፓርቲ አባሎች ሲመለምል ከጥራት ይልቅ ብዛት ላይ በማተኮር በሚልዮኖች መለመለ፡፡ ሲቪል ሰርቫንቱ በብቃት ሳይሆን በአባሎቹ ተሞላ፡፡
☞ከዩኒቨርሲቲ “A” ከማምጣት ከኢህአዴግ “C” ማግኘት ይሻላል ተባለለት፡፡
☞የመልካም አስተዳደር ችግር ፖለቲካዊ ነው፤ የዲሞክራሲ ማጣት ውጤት ነው፡፡
☞ችግሩ የሚጀምረው ከላይኛው አመራር ነው፡፡ እላይ ከተስተካከሉ ከስር ይስተካከላል፡፡
☞ኢህአዴግ ውስጥ መተጋገል የለም፡፡
☞ደርግነት የሚመጣው እንግዲህ ሲቪሉ መግዛት ሲያቅተውና “ወታደሩ እኔ እሻላለሁ” ማለት ሲጀምር ነው፡፡
☞ከዚያ በኋላ እየጨለመ የመጣው ዲሞክራሲ፣ ወደለየለት አምባገነንነት ያመራል ማለት ነው፡፡
☞ዲሞክራሲያዊ ምህዳሩ እየጠበበ ደርግነት እያቆጠቆጠ፣ በመንግስትም ከመንግስት ውጪም ማፍያዎች እየታዩ ነው ስል፡ “ብዙ ሰዎች አንተ አትፈራም እንዴ? ሊገድሉህ ሊያስሩህ ይችላሉ” ይሉኛል፡፡
☞በተዘዋዋሪ መንገድ ግን መታገል አለብህ እያሉኝ ነው፡፡
☞መጀመሪያ በ “ካራክተር አሣስኔሽን”፣ ከዚያም የተለያዩ ጥቃቶች ሊፈፀሙ ይችላሉ፡፡ እንግልት… መሞት… መታሰር ያስፈራል፡፡ ያስጠላልም፡፡
☞እኔ ከሁሉም የምፈራው ፈርቶ በቁም መሞትን ነው፡፡ ፈርቶ የህሊና እስረኛ መሆንን ነው፡፡ በተለይ ወጣቶች ከዚህ የህሊና እስርና በቁም መሞት በላይ ምንም እንደሌለ ተገንዝበው መታገል አለባቸው፡፡
☞“የሀገራችን ችግር በህወሓትና በኢህአዴግ ብቻ ነው የሚፈታው” የሚል የምርጫ ቅስቀሳ ለምን እንደጀመሩ አይገባኝም።
☞የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ኢህአዴግ ከሌለ አይኖርም ማለት እብሪት ነው፡፡ ኢህአዴግንም ህወሓትንም የፈጠረው ህዝብ ነው እንጂ እነሱ ህዝብን አልፈጠሩም፡፡
››
ምንጭ – አዲስ አድማስ