Tuesday, October 4, 2016

​አዲስ አበቤዎች ዛሬ ጡንቻዎቻቸውን ፈታትሸዋል፤ ይኽ ገና ፍተሻ ነው። ( ዶ/ር ታደሰ ብሩ)

Oktober 4,2016
​አዲስ አበቤዎች ዛሬ ጡንቻዎቻቸውን ፈታትሸዋል፤ ይኽ ገና ፍተሻ ነው። ነገ ወደየት እንደሚያመራ መገመት ከባድ ነው። ለማንኛውም የሚከተሉትን ጥቂት ነጥቦች እንዳሰፍር ፍቀዱልኝ። 
1. ከቤት ስትወጡ ወንዶች ኪሳችሁ፣ ሴቶች ቦርሳችሁ ውስጥ ያለው ነገር እወቁ፤ የማታስፈልግ ከሆነ ብጣሽ ወረቀትም ብትሆን አስወግዱ፤

2.ራሳችሁን ለመከላከል የሚረዳችሁ ነገር ብትይዙ መልካም ነው፤

3. ሞባይላችሁን አጽዱ፤ በማትፈልጉበት ሰዓት አጥፉት፤

4. በተለይ ምሽት ላይ ድንገተኛ ፍተሻ  ሊኖር እንደሚችል ገምቹ። ከተቻለ ዋና ዋና መንገዶችን አስወግዳችሁ ውስጥ ውስጡን ሂዱ (እርግጥ ነው ለማጅራት መቺ መጋለጥ ሊኖር  ይችላል ሆኖም መንግሥት ነኝ ባዩ አካል ከማጅራት መቺ በባሰበት አገር ማጅራት መቺ ያነሰ ክፉ ሊሆን ይችላል)፤

5. የወታደር፣ የፓሊስ፣ የመንግሥት መኪና ባገኛችሁትና በተመቻችሁ አጋጣሚ ሁሉ ጎማ ማስተንፈስ፣ መስታወት መስበር፣ ቢቻይልም ማጋየት ተልዕኮዓችሁ አድርጉት፤

6. የህወሓት ሰላዮች ቦንብ ሊያፈነዱ ስለሚችሉ ተጠንቀቁ፤ የማታውቋቸው ሰዎች ሲጠጓችሁ ተጠራጠሩ፤

7. ብልጠት እና ፍጥነት በጣም አስፈላጊ ነገሮች ናቸው። ብልጠት ካለ በቀላል ወጪ ብዙ ጉዳት ማድረስ ይቻላል፤ ፍጥነት ካለ ጉዳት አድርጎ መሰወር ይቻላል።

8. ቶሎ ተሰባብሰው አንዳች ነገር ከከወኑ በኋላ የሚበታተኑ አደረጃጀቶችን ተጠቀሙ፤ ለሥራ የምትፈልጓቸው ቡድኖች ቋሚ አባላት እና ቋሚ መገናኛ አይኑራቸው።

9. የህወሓት ሰላዮችን በማበሳጨት፣ በማደናገር፣ በማሞኘት ተደሰቱ። ትግል የጭንቅላት ጨዋታ ነው፤ የህወሓት ሰላዮች ደግሞ ደደቦች ናቸው።

10. መትቶ መሮጥ (hit and run)፤ ተሰብስቦ መንገድ ዘግቶ፣ በተቃውሞ ድምጽ አበሳጭቶ መበተንን እንልመድ።

11. በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት፣  በጦር ሠራዊቱ፣ በፓሊስ፣ በስለላው፣ በሚኒስት መሥሪያ ቤቶች፣ በፋይናንስ ተቋማትና ሌሎች ድርጅች እንዲሁም በራሱ በኢህአዴድ ጽ/ቤት ውስጥ የምትሠሩ የሕዝብ ወገኖች መሥሪያ ቤቶቻችሁን በሕዝባዊ አሻጥር አሽመድምዱ። በፋሽስት መንግሥት ላይ አሻጥር መሥራት በሰማይ የሚያፀድቅ በምድር የሚያስመሰግን ሰናይ (መልካም) ተግባር ነው።  እኩይ ተግባር ከክፉ አገዛዝ ጋር መተባበር ነው። ህወሓትን የሚረዳ አንዳች ነገር ላለመሥራት ተጠንቀቁ፤ ህሊናችሁ ሲቆረቁረው እንዳይኖር፤ በቢሾፍቱ፣ በጎንደር፣ በባህዳር የወደቁ ወገኖቻችን መንፈስ እንዳይወቅሳችሁ።

12. ዘዴዎችን መቀያየር - ለምሳሌ፣ አደባባይ፣ ቤት፤ ቀን፣ ማታ፤ በሥራ ቀናት፣ በእረፍት ቀናት  -  ከተወሰነ  ጊዜ በኋላ ትግሉ መዳረሻ  (tipping point)  ላይ ይደርሳል፤ ከዚያ መመለሻ አይኖረውም። የአዲስ አበባ ሕዝባዊ እምቢተኝነት የህወሓት አገዛዝ ፍፃሚ አብሳሪ ይሆናል። ያ ደረጃ እስኪደረስ ሊያለፋ እንደሚችል ግን ካሁኑ ግንዛቤ ይወሰድ።

Via - Tadesse Biru Kersmo

No comments: