Sunday, September 25, 2016

የውሸትና የማስመሰል ጸብ በመቀሌ ተጀምሯል። የነ አባይ ወልዱ አንጃ ከተሸነፈ ሳሞራ ዮኑስ ሊባረሩ ወይም በጡረታ ሊሰናበቱ ይችላሉ የሚል ስጋት አለ

September 25,2016
ኣዲስ ኣበባው ኣንጃ “ኣቶ ኣባይ ወልዱ ከትግራይ ክልል ኣስተዳዳሪነታቸውና ከህወሓት ሊቀ መንበርነታቸው ማውረድ የሚል ኣላማ ኣንግበው መጥተዋል።

ይህ ማሳካት ማለት “በጥልቀት መታደስ” የሚል ትርጉም ይሰጡታል ይህ እውን ለማድረግ እንደመጡም እያስወሩ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ የመቐለው ኣንጃ የተፎካካሪው ኔትወርክ ኣፈራርሶ ስልጣኑ የበለጠ ሊያሰፋና ልእልናው ሊያስጠብቅ እየተጣጣረ ነው።

የመቐለው ኣንጃ ኣቶ ኣባይ በስልጣን ማቆየት፣ የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ስልጣን ማዳከም ማሳካት ማለት በጥልቅ መታደስ ነው።
የመቐለው ኣንጃ ዋነጃ ደጋፊ ጀነራል ሳሞራ ከመባረር(የነ ኣባይ ወልዱ ኣንጃ ከተሸነፈ ሳሞራ ዮኑስ ሊባረሩ ወይም በጡረታ ሊሰናበቱ ይችላሉ የሚል ስጋት ኣለ) ማዳን የሚል ግብም ለማሳካት እየታገለ ይገኛል።

የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ኣባይ ሲያወርድ ሊፈጠር የሚችል ግርግርና ኣለመግባባት ለማረጋጋት የሚለምኑና የሚሸመግሉ የድሮ የማእከላይ ኮሚቴ ኣባላት ከያሉበት ኣሰባስበው ኣሳትፈዋል።

የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ወቅታዊ ፕሮፖጋንዳ “ኣዲስ ኣበባው የኢህኣዴግ ግምገማ ኣባይ ወልዱና ገዱ ኣንዳርጋቸው ከስልጣን እንዲወርዱ ተወስነዋል በውሳኔው መሰረት ኣባይ በሌላ ኣመራር መተካት ብቻ ነው” የሚል ወሬ በመንዛት የኣባይ ወልዱ ከስልጣን መውረድ የማይቀር መሆኑ እየገለፁ ይገኛሉ።

የህወሓት በጥልቅ መታደስ ዓላማ ኣቦይ ስብሓት የተነጠቁት የበላይነት ማስመለስ፤ ኣቶ ኣባይ ወልዱ በኣጋጣሚ በእጃቸው የገባው ልዕልና ኣስጠብቆ መውጣት ከሚል ትርጉም የዘለለ ኣይደለም።

በህዝባችን ዓይን የዚህ ጥሎማለፍ (ጥልቅ ተሃድሶ) ውጤቱ “ጉልቻ ቢለዋወጥ ወጥ ኣይጣፍጥም” እንደሚባለው ፋይዳ ቢስ ነው።



No comments: