Saturday, August 20, 2016

አዲስ አበባ በከፍተኛ ውጥረት ላይ ናት – አሜሪካ በኢትዮጵያ ያሉ ዜጎቿን አስጠነቀቀችn

August 20,2016
Members of the Ethiopian army patrol the streets of Addis Ababa in 2005.
Members of the Ethiopian army patrol the streets of Addis Ababa in 2005.ኤፍ (ነሃሴ 14 ፥ 2008) የአዲስ አበባ ህዝባዊ እምቢተኝነት አስተባባሪ ኮሚቴ ለመጭው እሁድ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ መግለጫ ማውጣቱን ተከትሎ በከተማይቱ የፍርሃትና የመረበሽ ድባብ መስፈኑን ከአዲስ አባባ የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በአነስተኛና ጥቃቅን፣ በአንድ ለአምስት ጥርነፋ እና በከፍጠኛ የስለላ መረብ ውስጥ የሚገኘው የአዲስ አበባ ህዝብ ግን የቀድሞ ፍርሃት እንደማይታይበት መረጃዎቹ ይጠቁማሉ። ኢትዮጵያ ከጫፍ እስከ ጫፍ እየተቀጣጠለ ባለ ህዝባዊ እምቢተኝነት ውስጥ በመገኘትዋ አዲስ አበባም የዚህ ለውጥ ንቅናቄ አካል እንድትሆን ውስጥ ለውስጥ ከፍተኛ የማስተባበር ስራ እየተሰራ ነው። የሕምባዊ እምቢተኝነት አስተባባሪ ኮሚቴ ህዝቡ በአብዮት አደባባይ በነቂስ እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል። ምክንያቱም የአዲስ አበባው ህዝባዊ ንቅናቄ ለለውጡ ወሳኝ ስለሆነ።
በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች በተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ ከ700 በላይ ወገኖቻችን መገደላቸው፣ በ10ሺዎች ደግሞ ለእስር እንግልትና መሰወር መዳረጋቸውን አስተባባሪ ኮሚቴው በመግለጫው አመልክቷል።
ትላንት ነሃሴ 13 እለት ቡሄ ነበር። ከቶውንም የቡሄ በአል ድባብ አልነበረውም። በአዲስ አበባ ከፍተኛ ውጥረት አለ። በተለይ በአንዋር መስጊድ አካባቢ ከፍተኛ ፍተሻ በመካሄድ ላይ እንደነበር መረጃዎች ጠቁመዋል። ካድሬዎች ቤት ለቤት እየዞሩ እንዲሁም በየመስሪያ ቤቱ ህዝቡን እየሰበሰቡ በእሁዱ ሰልፍ ላይ እንዳትገኙ በማለት እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
በሰሜን ጎንደር በርካታ ከተሞች ህዝባዊ እንቢተኝነቱ ወደ ጦርነት መሸጋገሩን ከስፍራው የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የህወሃት ባለስልጣኖች እና ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የኢትዮጵያን አንጡራ ሐብት በመዝረፍ ፣ ንብሮቶቻቸውን በመሸጥ እና በማሸሽ ላይ እንደሚገኙም ታማኝ ምንጮች ገልጸውልናል።
ሕዝባዊ አመጹ ያስከተለው የሃገሪቱ አለመረጋጋት በዚህ ከቀጠለ ባለስልጣኖቹ ሀገር ጥለው ለማምለጥ እቅድ መያዛቸው ተነግሯል።
ይህ በዚህ እንዳለ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት በኢትዮጵያ የሚገኙ ዜጎቹ እንዲጠነቀቁ በትናንትናው እለት መግለጫ አውጥቷል። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክልሎች መንግሥትን ላይ በሚካሄዱት ተቃውሞዎች ምክንያት አደጋ ሊኖር እንደሚችል በመግለጽ ዜጎቹን አስጠንቅቋል።
የስልክና የኢንተርነት አገልግሎት መቆራረጥ ምክንያት በኢትዮጵያ ያለው የአሜሪካ ኤምባሲ በሀገሪቱ ካሉት የአሜሪካ ዜጎች ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት እንዳሰናከለበት መግለጫው ጠቅሷል።
የተቃውሞ ሰልፎቹ ካለፈው ዓመት ሕዳር ወር ጀምሮ በተለይም በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት እንዳስከተሉ መግለጫው ጠቅሶ፤ ተቃውሞዎቹ ሊቀጥሉና ሊስፋፉ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳለ አስፍሯል። በዚህም ምክኒያት በኢትዮጵያ የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ፣ ደህንነታቸውን እንዲጠብቁና የተቃውሞ ሰልፎችንና ሰዎች በብዛት የተሰባሰቡባቸው ቦታዎችን እንዲያስወግዱ አሳስቧል።

No comments: