Friday, July 31, 2015

ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ለምን ያስጨንቃቸዋል?

July 31, 2015
ሽብሬ ደሳለኝ
Andargachew Tsige is Ethiopianባለፉት 24 ዓመታት ወያኔዎች በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) ለውጥ ለማምጣት የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካ ድርጅቶች እና ፖለቲከኞች ከማዳከም አልፈው በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት ተጽኖ መፍጠር እንዳይችሉ አድርገዋቸዋል።

አብዛኛዎቹ ፖለቲከኞች የወያኔ አፈና ሲበረታ ከማምረር ይልቅ ፖለቲካውን እርግፍ አድርገው ይተውታል ወይንም ደግሞ ስደት ይወጡና ቀደም ሲል የተሰደደውን የኢትዮጵያ ስደተኛ ተቀላቅለው እንደ አብዛኛው ስደተኛ ቤተሰቦቻቸውን እና እራሳቸውን በኢኮኖሚ የማሻሻል ተግባር ላይ አተኩረው ይቀራሉ። ይህ እየተለመደ የመጣ አካሄድ ወያኔዎቹን ተመችቷቸው ኖረዋል፣ እነ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የጨዋታውን ህግ እስከቀየሩት ድረስ።

በርግጥም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ ወደ ፖለቲካው ሜዳ ያመጡት አዲስ የጫወታ ህግ ሰርቷል!
ወያኔ አዲሱን የጨዋታ ህግ ከጅምሩ አልወደደውም፣ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ኋይት ሃውስ ፊት ለፊት ሻማ ከማብራት ያለፉ እንዳይሆኑ ምኞቱ ነበር። ይህ አልሆነም።

አቶ አንዳርጋቸው እና ጓዶቹ ኢትዮጵያውያን የአሜሪካን ወይንም የእንግሊዝን መንግስት በመለመን ነጻነታቸውን እንደማይቀናጁ ይልቁንም ብረት አንስተው ወያኔን በሚገባው ቋንቋ የማነጋገር አስፈላጊነትን አስተማሩ፣ ወተወቱ፣ የመውጪያ መግቢያ ቀዳዳዎችንም አመላከቱ… ኤርትራ!

ወያኔ በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን ሲያዳፍን፣ ለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን እንደሚያማትር አልጠፋውም፣ ወያኔዎች የለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን በስራ ላይ ለማዋል ተባባሪ/ፈቃደኛ የጎረቤት ሃገሮች እንደሚያስፈልጉት ቀደም ብሎ መተንበዩ አልቀረም (ወያኔ ከደርግ መንግስት ጋር ባደረገው የሃይል ትግል ወቅት ሱዳን እና ሶማሊያ ዋንኞቹ መጠለያው ነበሩ)። ከሃገር ጥቅም ይልቅ ለመንበረ ስልጣኑ ቅድሚያ የሚሰጠው ወያኔ ለኢትዮጵያ አጎራባች ሃገሮች ሁሉ የሚጠይቁትን እየሰጠ (ለምሳሌ ሱዳን ከሃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ ይገባኛል የምትለውን የኢትዮጵያ መሬት ከወያኔ ተቀብላለች) በምላሹም ተቃዋሚዎቹን እንዳያስጠልሉ፣ አልፎ ተርፎም ተቃዋሚዎቹን እያደኑ እንዲያስተላልፉለት አግባባቸው። ይሁንና ይህ አካሄድ በጎረቤት ኤርትራ ሊሰራለት አልቻለም።

አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ አውርተው አልቀሩም፣ ከኤርትራ መንግስት ጋር የተሳካ ግንኙነት ፈጠሩ፣ ጦርም ማደራጀት ቻሉ፣ ቀደም ሲል ጀምሮ በኤርትራ መሬት ይንቀሳቀሱ በነበሩት ሃይሎች መካከልም መልካም እና መተማመን የሰፈነበት ግንኙነት እንዲኖር አስቻሉ።

ወያኔ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረገው የለውጥ እንቅስቃሴ እየበረታ መሄዱን በመገንዘብ እንቅስቃሴውን በእንጭጩ ለማስቀረት መንቀሳቀሱ አልቀረም፣ ይህንን ወያኔን እንቅልፍ የነሳ እንቅስቃሴ ወደ ተግባራዊነት እየቀየሩ ባሉት የግንቦት 7 አመራሮች ላይ አነጣጥሮ በተገዙና የተቃዋሚ ካባ በደረቡ ግለሰቦች አማካኝነት አመራሮቹን ከህዝብ ለመነጠል ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርግም ውጤቱ አመርቂ አልሆነም። ወያኔ ከዚህ በኋላ ነበር አማተር ሰላዮቹን ወደ ኤርትራ በመላክ አርበኛውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመግደል ሙከራ ያደረገው ይህም አልተሳካም እንደውም ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ደረሰበት (ብዙዎች አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጠንቅቀው የማያውቁት ሳይቀሩ የአንዳርጋቸውን ማንነት ለመገንዘብ ቻሉ)።

ወያኔ በመጨረሻ ያደረገው ሙከራ ተሳክቶለት አቶ አንዳርጋቸውን ከየመን አፍኖ ወደ አዲስ አበባ መውሰድ ቻለ።
ለጊዜው ወያኔዎች ከፍተኛ የድል አድራጊነት ሰሜት ተሰምቷቸው ጮቤ ረገጡ ይሁንና ብዙም ሳይቆይ ደስታቸው እንደጉም በኖ እስካሁን በሚያቃዣቸው ስጋት ውስጥ እንዲዘፈቁ ሆነ። ጀግናቸው (አንዳርጋቸው ጽጌ) በወያኔ እጅ መውደቁን የሰሙ ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከጫፍ ተነቃነቁ፣ አንዳርጋቸው የጀመረውን የትግል ጉዞ ከግብ ለማድረስም ቁርጠኝነትቸውን አሳዩ፣ የአንዳርጋቸው ቤተሰቦች ሴት ከወንድ ሳይባል በአንዳርጋቸው ጽጌ እግር ተተክተው አንዳርጋቸው ያቀጣጠለውን ችቦ ተረከቡ።
የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራሮችና የአንዳርጋቸው የትግል ጓዶች ዙሩን አከረሩት፣ በተደጋጋሚ ከወያኔ ጋር ባካሄዳቸው የሽምቅ ውጊያዎች ልምድ ካካበተውና የሰሜኑን የኢትዮጵያ ግዛቶች መግቢያ መውጫ ጠንቅቆ ከሚያውቀው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጋር ውህደትን ፈጠሩ፣ በውጤቱም አርበኞች ግንቦት 7 ተወለደ።

በለስ ቀንቷቸው አቶ አንዳርጋቸውን በእጃቸው ያስገቡት ወያኔዎች ከሚቆጣጠሩት ግዛት ውጪ እየተካሄ ያለው እንቅስቃሴ በአንዳርጋቸው መያዝ ምክንያት መባባሱን ተረድተዋል። የእንቅስቃሴውን ፍጥነት ለመግታት በቁጥጥራቸው ስር ያለውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመጠቀም በማሰብ እየቆረጡ እና እየቀጠሉ የሚለቋቸው የአዳርጋቸው ጽጌ ቪዲዮዎች ምንም ውጤት አላመጡም፣ ይልቁንም በኢትዮጵያውያኑ ዘንድ ከፍተኛ ቁጭትን እየጫሩ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ ቃላቸውን እንዲያድሱ አድርጓቸዋል።

ለዚህም ይመስላል አንዳርጋቸው ጽጌን የስፖርት ቱታ በማልበስ ሰው በሌለበት ጎዳና ላይ ፎቶ አንስተው “ተመልከቱ እባካችሁ አንዳርጋቸው ሰላም ነው” በማለት ኢትዮጵያውያኑን ለማረጋጋት የሞከሩት።
አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት መፈጸም ከጀመረና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ገብቶ በአንዳርጋቸው እግር መተካቱ ከተሰማ በኋላ ደግሞ ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጉዳይ ፍም እሳት ሆኖባቸው የሚያደርጉትን አሳጥቷቸዋል፣ ለዚህም ምልክቱ ቴድሮስ አድሃኖም በቪኦኤ ላይ የተናገረው ነው “አንዳርጋቸው ላፕ ቶፕ ተሰጥቶት መጽሃፍ ጽፎ ጨርሷል፣ አንዳርጋቸው የሃገሪቱን ልማት ማየት ፈልጎ እያዟዟርን አሳይተነዋል ወዘተ…”

እውነታው ግን አንዳርጋቸው ጽጌን የት እንዳሰሩት አይናገሩም፣ አንዳርጋቸውን ቤተሰብም ሆነ ማንኛውም ሰው አይጎበኘውም። በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ወያኔዎች በአንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሚያውቁትን የማሰቃያ መንገዶች ሁሉ በመጠቀም አንዳርጋቸው እነርሱ የሚፈልጉትን አይነት መልእት እንዲያስተላልፍ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። ይሁንና ጀግናው አንዳርጋቸው ጽጌ እስካሁን የሚፈልጉትን አልሰጣቸውም (ይህንንም ለማረጋገጥ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ስቃይ እየፈጸሙ ቀርጸው የሚያሰራጯቸውን ቪዲዮዎችን መመልከት ይበቃል)።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በአካል ተገኝቶ ትግሉን መምራት ባይችልም መንፈሱ ግን ትግሉን በማቀጣጠል ላይ ይገኛል። እንግዲህ ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌን ለመቆጣጠር ነው ቁጭ ብድግ በመስራት ላይ ያሉት፣ ይሳካላቸው ይሆን? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል።

ሁሉም በያለበት የነፃነት ትግሉን ይቀላቀል!!!

July 31, 2015
def-thumbእኛ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የሰውነት መብታችን ተገፎ የዜግነት ነፃነታችን ተረግጦና ተዋርደን የምንገኝበት ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው፡፡ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ እስርና የጅምላ ስደት እንደ ዘመነ ወያኔ የታየበት ዘመን የለም፡፡ ህፃናት በረሀብ ከሚማሩበት ክፍል ውስጥ የሚወድቁበት ፤ ወንድ ልጅ በደህንነት ሀይሎች ታፍኖ የሚደፈርበት፤ ሴት ልጅ በገመድ የታሰረ የባልዋነወ ብልት መንገድ ለመንገድ እንድትጎትት የተደረገበት ዘመን ቢኖር ያሳለፍነው የወያኔ ዘመናት ብቻ ነው፡፡ ባጠቃላይ የሰው ልጅ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ መከራና ሰቆቃ እንድንሸከም የተገደድንበት ዘመን ላይ እንገኛለን፡
በአንፃሩም ስለ ለፃነት ስለ ፍትህና እኩልነት ሲሉ የተሰዉ ዋጋም የከፈሉ፤ አሁንም እየከፈሉ የሚገኙ ጥቂት አይደ ሉ ም፡፡ ከነዚህም አንዱ አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ይህ ለነፃነት ለፍትህና ለ ዲሞክራሲ የሚደረገው ተጋድሎ ውሎ አድሮ ዛሬ ከዋናውና ወሳኝ ከሆነው ምእራፍ ላይ መድረሱ ደግሞ የሁላችንንም ተስ ፋ ያለመለመና የተደፋው አንገታችን ቀና ያደረገ መሆኑና በተቃራኒው የወያኔን ካንፕ ያሸበረ መሆኑ በገሀድ እየታየ የሚገኝ እውነት ነው፡፡
እንግዲህ ይህን ወራዳ ስርአት አስወግዶ በምትኩ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመተካት የሚደረገው ትግል ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የተደረገው ርብርብ ቀላል ባይሆንም ቀሪውን አጠናቆ ከዳር ለመድረስ ከመቼውም ጊዜ በላይ የእያንዳዱን ኢትዮጵያዊ የተግባር ተሳትፎ የሚጠይቅ፤ ሁሉም ከያለበት ስለ ነፃነት የሚደረገውን የአርነኝነት ትግል በመቀላቀል የድርሻ ውን ሀላፊነት መወጣት ከሚጠይቅበት ወሳኝ ምእራፍ ላይ መድረሳችንን መረዳት ግድ ይላል፡፡
እኛ ኢትዮጵያውያን ያለ ማንም እርዳታና ድጋፍ ዋጋ ከፍሎ ለፃነትን የማሰከበር እንግዳ ሳንሆን በታሪክ የምንታወቅበት መለያችን መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ እንኳን ዛሬ አለም አለም በጠበበችበት ዘመን ቀርቶ ትናንት በጨለማው ዘመን እንኳ እነ ዶ/ር መላኩ በያን ከአኛ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት ፈር ቀዳጅ ሆነው የተገኙበትን ታሪክ ማስታወስ ይገባል፡፡
እናም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኟውም ስፍራ የሚገኝ ሁሉ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል እውቀት ያለው በእውቀቱ፤ ጉልበት  ያለው በጉልበቱ፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ለመደገፍ ዛሬ ነገ ሳይል አሁኑኑ ከአርበኝነቱ ትግል መቀላቀል ይጠበቅበታል፡፡ ኢትዮጵያዊነታችንን ብቻ ሳይሆን ሰው መሆናችን የሚረጋገጠው ነፃነታችንን አስጠብቀን በነፃነት መኖር ስንችል ብቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡
ስለዚህ ዛሬ አርበኞች ግንቦት ሰባት የለኮሰው የነፃነት ቀንዲል ከነጻነት አደባባይ ለመትከል የጀመረውን ጉዞ በሰው ሀይል፤ በገንዘብና በቁሳቁስ በማገዝ ሁላችንም የድርሻችንን እንድንወጣ ጥሪ ስናደርግ ለእኛ ኢትዮጵያውያን ከእኛ ኢትዮጵ ያውያን ውጭ ማንም እንደሌለ በማስገንዘብ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

Wednesday, July 29, 2015

ከአምስት በላይ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች እና የሸዋሮቢት ነዋሪዎች በእስር ላይ መሆናቸው ተገለጸ

July 29,2015
በሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ሸዋሮቢት ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች እና ወጣት የለውጥ አራማጅ የፓርቲው አቀንቃኞች በመንግስት ሃይል ታፍነው ወደ እስር ቤት ከተወረወሩ ከወር በላይ መሆናቸውን ከክልል ሶስት ሰሜን ሸዋ ዞን የሸዋሮቢት ከተማ አስተደር ነዋሪዎች የሆኑ እና የፓርቲው አባሎች እና አመራሮች ለማለዳ ታይምስ የአባሎቻቸውን መታሰር ጠቁመዋል ።
እነዚህ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች በየትኛው ቦታ እና እንዴት እንደታሰሩ ለመጠየቅ ቢሄዱም የመንግስት ሃይሎች ምንም አይነት መረጃም ሊሰጧቸው እና ያሉበትንም ሁኔታዎች ሊያሳውቋቸው ባለመቻላቸው በከፍተኛ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ የሚገኘውን የሰማያዊ ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት ለማግኘት እና ስለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መግለጫ እንዲያወጡ ለመጠየቅ በደጋግሚ ቢጥሩም ምንም ምላሽ ሊሰጧቸው አለመቻሉ እራሱ አሳሳቢ ከመሆኑም በልይ በክልሉ ለሚገኙት አባሎች እራስ ምታት መሆኑን ገልጸዋል ።
የፓርቲው አመራር ምላሽ መስጠት ሲገባቸው እንደ ወያኔ መንግስት ለአባሎቻቸው ዝምታን መፍጠሩ ለለውጥ የተዘጋጁ ሳይሆኑ ለጥቅሞቻቸው የተነሱ ሃይሎች መስለው ነው የታዩን ብለው የተናገሩት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት እና የቀወት ወረዳ የሰማያዊ ፓርቲ የወጣት መልማዮች ዋና ሃላፊ በዛሬው እለት ይህንን መግለጭ ወደ ግል መገናኛ ብዙሃን ልናመጣው የቻልነው ሰሚ አካል ብናገኝ ጥሩ ነው በሚል ምክንያት ነው ሲሉም አክለው ገልጸዋል ። ከአንድ ወር በፊት የታሰረውን ወጣት ቴዎድሮስ ሃብቴ እስካሁን ያለበትንም ሁኔ ካለማወቃችን የተነሳም ለፍርድ እንኳን አቅርበው ጥፋተኝነቱንም ህነ የተከሰሰበትን ሁኔታ ለመረዳት አልቻልንም የሌሎችንም ወጣት የዘርፍ ክፍሎቹንም ለመከታተል አልቻልንም ሲሎ ገልጸዋል ።

Monday, July 27, 2015

ፕ/ት ኦባማ «ኤርትራ ያለ ተቃዋሚ ድርጅትን በአሸባሪነት ለመፈረጅ» የሚያስችል በቂ መረጃ የለንም አሉ፤

July 27,2015
ኢሳት ዜና ፦ የአሜሪካው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት ” በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ ፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ምክትል ሃላፊ ዌዲ ሸርማን አርበኞች ግንቦት7ትን በአሸባሪነት እንዲፈረጅ ያቀረቡትን ጥያቄ፣ ለፕ/ት ኦባማም ማቅረባቸውን የሚያመለክት ነው። ፕ/ት ኦባማ በመልሳቸው «ፖሊሲያችን መንግስትን በሃይል ከስልጣን ማውረድን አይደግፍም፣ ይህ ፖሊሲያችን በዲሞክራሲያዊ ሁኔታ የተመረጠውን የኢትዮጵያን መንግስትንም ያካትታል» ካሉ በኋላ፣ «በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩብኝ ነው በማለት የሚፈርጃቸው ድርጅቶች እንዳሉ እናውቃለን፣ ይሁን እንጅ በመንግስት ላይ ተቃውሞ ቢያሰሙም የሽብር ዝንባሌ እንደሌላቸው የእኛ የመረጃና የደህንነት መረጃዎች ያሳዩናአል» በማለት በኢህአዴግ መንግስት በኩል የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ተናግረዋል። «ይህንን በመገምገም በኩል ግልጽ የሆነ መስፈርት አለን ያሉት ኦባማ፣ ለወደፊቱ እነዚህ ድርጅቶች የሽብር ጥቃት ይፈጽማሉ አይፈጽሙም የሚለውን ለወደፊቱ የምናየው ይሆናል ብለዋል።
.
«አንድ ድርጅት የፖለቲካ ተቃውሞውን ቢገልጽ ፣ ከአስተሳሰቡ ጋር ባንስማማም እንኳ ከለላ እንሰጠዋለን፣ ይሄ በአሜሪካ በሌላም ቦታ የሚሰራበት እውነታ ነው፤ ይህን ማድረግ ለዲሞክራሲ እድገት አስፈላጊ ነገር ነው» ያሉት ኦባማ ፣ ድርጅቶቹ ወደ ሃይል ሲያዘነብሉና በህገመንግስት የተቋቋመን መንግስት ለመገልበጥ ሲሞክሩ፣ ድርጊቱ ያሳስበናል።» በማለት መልሰዋል። የውጭ አገር ጋዜጠኞች ፣ በእስር ላይ ስለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እንዲሁም ስለኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ ጉዳይ ለፕ/ት ኦባማና ለአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ፕ/ት ኦባማ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥበቃ እና በዲሞክራሲ ዙሪያ ከአቶ ሃይለማርያም ጋር ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን፣ አሜሪካ በቅርብ ሁና እገዛ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልጸዋል። የኢህአዴግ መንግስት ከፕ/ቱ ጉብኝት በዋናነት የሚጠብቀው ለስልጣኑ ስጋት የሚፈጥሩ ድርጅቶች በሽብረተኝነት እንዲፈረጁለት ቢሆንም፣ ይህንን ሳያገኝ ቀርቷል። ይሁን እንጅ ባራክ ኦባማ የኢህአዴግን መንግስት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችን ሳያስቆጣ አይቀርም። ኦባማ በአንድ በኩል በኢትዮጵያ እየጠበበ ስለመጣው የፖለቲካ ምህዳር ሲናገሩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ የሚል ካባ ማልበሳቸው፣ የአሜሪካ የውጭ ፖሊሲን ተቃርኖ የሚያሳይ ነው።
.
በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል ለፕሬዝደንት ኦባማ በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታውቀዋል። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት መንግስት ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገውን የእራት ግብዣ ያልተቀበሉት፣ «አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ፣ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም» ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም «የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ» ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸውም ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ «ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው» ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ኢ/ር ይልቃል

July 27,2015
ኢ/ር ይልቃል መንግስት ለፕሬዝደንት ኦባማ ያዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታወቁ
• ‹‹ኦባማ ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ ውሃ የሚቸልስ ነው››
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ ለነገረ ኢትየጵያ ገልጸዋል፡፡ የራት ግብዣው ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥሪ የተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል ‹‹ አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም›› ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም ‹‹የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው›› ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል በነገው ዕለት የአሜሪካ ኤምባሲና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የወያኔ ታጣቂዎች በታህታይ አድያቦ ወረዳ እርስ በራሳቸው ተዋጉ

July 27,2015
በታህታይ አድያቦ ወረዳ አካባቢ የሚገኙ የገዢው የኢህአዴግ ስርዓት ወታደሮች እርሰ በራሳቸው እየተገዳደሉ እንደሚገኙ ተገለፀ። በትግራይ ሰሜናዊ ምእራብ ዞንEthiopian dictatorial regime troopsታህታይ አድያቦ ወረዳ ተሰማርተው የሚገኙ የኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት በመካከላቸው አንድነትና ፍቅር እንደሌላቸው የገለፀው መረጃው በተለይ ደግሞ በአባላትና በአዛዦች መሃል በተከሰተው ያለመስማማት ምክንያት ወታደር ታዘዘ ደበበ የተባለ ግለሰብ መቶ አለቃ አስራት ባዩና አምሳ አለቃ ካሳ አለሙ የተባሉን በጥይት ገድሎ ለራሱም ህይወቱን እንዳጠፋ የተገኘው መረጃ አስረድቷል።
በተመሳሳይ- በአዲ ሃገራይ አካባቢ የሚገኙ የኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት አንድ ወታደር 3ት ኮነሬሎችን ከነ አጃቢዎቻቸው ገድሎ ራሱን ህይወቱን እንዳጠፋ ባላፈው የዜና ዘገባችን መግለፃችን ይታወሳል።
ምንጭ – ትህዴን

የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት ነው

July27,2015

(ወለላዬ ከስዊድን)


አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል።
“ወደ ሰፈር፣ ወደ ሰፈር እየወረድኩ ነው ንጉሥ ሆይ!”
“ምነው ደህናም እማይደለህ?”
“ጣቴን ድንጋይ ቀርጥፎኝ ነው ንጉሥ ሆይ!”፤ ትንሽዋን ጣቱን በጨርቅ ነገር ጠቅሎ አንከርፏል።
“ና እስቲ! ቀረብ በልና የተጎዳኸውን አሳየኝ”፤ ሰውየው ንጉሡ ጋ ቀርቦ የቋጠራትን ጨርቅ ፈቶ ጣቱን ሲያሳይ ንጉሡ ትንሽ ጭረት ቢጤ ብቻ ያያሉ።
“ሌላ ቦታም ተጎተሃል እንዴ?”
“የለም! ይሄው ብቻ ነው።”
“እና! ይቺን ቁስል ናት! ብለህ ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ?”
“ይችኑስ ቢሆን በማን ልላካት ጌታዬ?” ብሎ ንጉሡን እንዳሳቃቸው ይነገራል። እኔም ለሌላ ሰው የሚላከክ ቢሆን የአቶ መለስን ሙት መንፈስ እዚህ ጋ ባልሸነጎርኩ ነበር። ሆኖም የሳቸው ቁስል ምንም እንኳን አነስተኛ ባይሆንም በማንም ልላክከው ስለማልችል ማንሳት ሊኖርብኝ ነው። አንድ ጊዜ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሁራንን ሰብስበው ንግግር አደረጉ። ምሁራኑ በአንክሮ ሰሟችው። የአነጋገራቸውን አካሄድ ተንኮልና ክፋት እንዳዘለ ቢያውቁም ብዙዎቹ ሊናገሩ አልፈለጉም። በኋላ ግን አንድ እጅ ከመሃል ተቀሰረች። አቶ መለስ ምሁሩ እንዲናገሩ ዕድል ሰጡ። ሰውዬው ከማንም ይበልጥ የአቶ መለስ ንግግር አንገብግቦአቸዋል። ማንገብገብ ብቻ አይደለም በእንዲህ አይነቱ መሪ አገሪቷና ህዝቡ ወደፊት የሚደርስበት ውርጅብኝ የበዛ እንደሚሆን በደልና ስቃዩም አስከፊ ደረጃ እንደሚደርስ ተሰምቷቸዋል።
ምሁሩ ዕድሉን ተጠቀሙበት፤ ማለት የሚገባቸውን አጠቃለው እስኪጨርሱ አንዳችም ፍርሃትና መደናገር ሳይታይባቸው “… አሁን ለሁሉ ነገር ጊዜው አልፏል። እርስዎ እያሉ ገበሬው ውስጥ ገብቶ አደራጅቶ ፋይዳ የሚያመጣ ፓርቲ ይኖራል ተብሎ አይገመትም። ስለዚህ ኳሷ በርስዎ ቁጥጥር ስር እስከዋለች ድረስ ከምንም ነገር በላይ ቅንነትዎን ብቻ እንፈልጋለን። ቅንነትዎ አይለየን ቅን ሆነው ይምሩን ይሄን ብቻ ነው የምንጠይቅዎ …” ነበር ያሉት።
ምሁሩ አቶ መለስ እስከወዲያኛው ቀና እንደማይሆኑና በቀናነት ሊመሩ እንደማይችሉ አላጡትም። ነገር ግን ቀና ማድረግ ባይቻል እንኳን ቀና እንዳልሆኑ ለማሳወቅ ፈልገዋል። ሆኖም አቶ መለስ ቀና ባይሆኑ አይገርምም ከሚሰሩት ተንኮል አንጻር ቀናነት ኪሳራ እንጂ ትርፍ ሊያስገኝላቸው አይችልም። ተፈጥሮአቸውም ቢሆን በቀናነት ተቃኝቶ በሥነ ምግባር ጎልብቶ የቀናነትን ጎዳና የተከተለ ስላልሆነ ቀና ልሁን ቢሉ እንኳን አይችሉም። ይህ ብቻ አይደለም ከአመራራቸው ግብና ዓላማም ጋር ቀናነት አብሮ አይሄድም።
ገና ከትምህርት ቤት ጀምሮ የመሰሪነት ባህሪ እንደነበራቸው የሚመሰክሩ ብዙዎች ናቸው። ስንት ታጋይ ጓደኞቻቸውን ወደ እማይመለሱበት እየላኩ ለሥልጣን የበቁም ናቸው። ከሥልጣን በኋላም ሞት እጃቸውን እስከሰበሰበው ድረስ አለ እረፍት ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያን ያዋረዱ፤ ህዝብ የናቁ፣ የከፋፈሉ፣ ያሰሩ፣ የገደሉ፣ ባንዲራን ያቃለሉ፣ ያገር ክብር የደፈሩን ሰው በምንም አይነት ቅንነት ልንመኝላቸው አንችልም።
እንግዲህ ስለአቶ መለስ ቀና አለመሆን ከተፈጥሮቸውና ከዓላማቸው አንጻር ነው ብለናል። ነገር ግን አቶ መለስን የሚያወግዝ፣ ለዲሞክራሲ ለሠላምና ለእኩልነት መከበር የቆመ፣ የተጣመመን ፍትህ አቃናለሁ የሚል፣ በሰው ልጅ እኩልነት የሚያምንና ይህንንም ለማስከበር የተነሳ ለአገሩ ብልጽግናና ነጻ መውጣት የሚያስብ ቅንነት ከጎደለው ከዓላማና ግቡ ጋር የተቃረነ መሆኑ አያጠራጥርም። አቶ መለስ የጣሏትን ቅንነት አንስቶ በጉያው ካልያዘ ልዩነታቸው ብዙም የተራራቀ አይሆንም። ለሳቸው ቅንነት ይጎዳቸዋል እሱ ደግሞ አለቅንነት ምንም አይነት የነጻነት ጉዞ ሊጓዝ አይችልም።
እንደውም ቀና ልቦና የሌለው ታጋይ ጊዜውና ሁኔታው ሲገጥመው አንዳንዴ ብልጭ እያለች የምታሳጣውን መጥፎ ባህሪ ሰው ጥላቻና ክፋት እፊት ለፊት አውጥቶ እማይጠቀምበት ምንም ምክንያት የለውም። ያንን እስከሚጠብቅና ድብቅ ፍላጎቱን እስኪያሟላ ድረስ ተፈጥሮው እያወከው ለትግል ጓዶቹ የማይመች የትግል እንቅፋት ሆኖ መቆየቱ አይቀሬ ነው።
ጎኑ ያለውን የትግል ጓዱን ያልወደደ ለዲሞክራሲ ቆሜያለሁ፣ ለነጻነት እፋለማለሁ፣ ለነፍትህ እዋደቃለሁ፣ … ቢለኝ አላምነውም፤ ባህሪው የገባበትን ዓላማ እንዳያሳካ አንቆ ስለያዘው የሱን ታጋይነት እጠራጠራለሁ። እውነቴን ነው ይህ ሰው ጫፍ ድረስ አይዘልቅም ይሰናከላል። ተሰናክሎም ያሰናክላል።
እናም የኢትዮጵያ ህዝብ ከገባበት የእጅ አዙር የባርነት አገዛዝ፣ ከነፃነት እጦት፣ ከእስር፣ ከንግልት፣ ከስደትና ከረሃብ ለማላቀቅ የተነሳህ፤ ፍትህ እንዲከበር፣ ዲሞክራሲና ሰላም፣ እድገትና ብልጽግና እንዲገኝ የምትፈልግ ሁሉ የትግልህ መጀመሪያ የቀና ልቦና ባለቤትነት መሆንን በማመን በቀናነት ከትግሉና ከታጋዩ ጋር ተቀላቀል። ቀና ልቦና ያለው መንገዱ ሁሉ ክፍት ይሆንለታል፣ በቀላሉ አይሰናከልም፣ ልቡ አያውከውም፣ አቀራረቡ ግልጽ ነው። አይፈራም፣ አይዋሽም፣ አያታልልም፣ አይጠራጠርም፣ ለቂም አያደባም፣ ለዝና አይናውዝም፣ ለሥልጣን አይዳክርም …
ይህ ካልሆነ ግን፤ እታገልልሃለሁ በምትለው ህዝብ ፊት ለመቆም ጉልበትህ አይጠናም። ህዝብ የምታደርገውን የትግል እንቅስቃሴ ቢያይም የአስተሳሰብህን ሸካራነት፣ የልቦናህን ክፋት ለመረዳት ብዙ ስለማይፈጅበት ክብርና ፍቅር ሊሰጥህ ይቸገራል፣ አይከተልህም። አይዞህ ልጃችን በማለት አያበረታታህም። እንደውም ልታታልለው እንደተነሳህ፣ ልታሞኘው እንዳደባህ ስለሚቆጥርህ ልቡን ከፍቶ አያሳይህም፤ ስለዚህ ቀና ሁን።
የፖለቲካን ትርጉም ከክፋት ጋር አትቀላቅል። ሌላም የምመክርህ አለኝ፣ የትግል ጓዶችህን አክብር፣ ጓደኛህ ስህተት ካለበት በድብቅ ከማማት ይልቅ ስህተቱን ፊት ለፊት ነግረህ እንዲመለስ አድርግ። ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ አሲረህ አሳድመህ አጥቂ አትሁን፤ ቂመኛ ሀሚተኛ አትሁን፤ መልካምነትን አሳንሰህ ስህተትን አታጉላ፤ የኔ ሃሳብ ይበልጣል፣ የምናገረውና የምሠራው ሁሉ የኔ ልክ ነው አትበል። ለቡዙሃን ድምጽና ሃሳብ ተገዛ፤ ሌላውን ደካማ አድርገህ አትይ፤ ለመወንጀል አትፍጠን፤ ልብህን ለንጹህ ወንድምነት ክፍት አድርግ። መቻቻልን፣ በጋራ መሥራትን አዳብር፤ የትግል ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን ለሥልጣንና ለሀብት አትጓጓ፤ ድርሻና ኃላፊነትን ከፍ አድረገህ በመመልከት ሌሎችን አትጫን፤ መልካም ሥነምግባር በማሳየት ሌሎችም አንተን እንዲከተሉ አድርግ። አትወላውል! ለተነሳህበት ዓላማ እስከመጨረሻው ተጓዝ። ወዳጄ ሆይ! ምክር ቢበዛ ባህያ አይጫንምና ይበቃኛል። ለማንኛውም የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት መሆኑን አትዘንጋ።

የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት ባደረጉት ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ብዛት ያላቸውን የኢህአዴግ ሰራዊት ደመሰሱ

July27,2015
arbegnoch g7 በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ማይ-ሰገን በተባለው አካባቢ የሚገኙትን የኢህአዴግ የሰራዊት አባላት በግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በደረሰባቸው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ምክንያት ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውን ተገለፀ።
ባለፈው ቀናት በሑመራ አካባቢ ማይ ሰገን በተባለው ቦታ ላይ የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በኢህአዴግ ሰራዊት ላይ ባደረሱት ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ብዛት ያላቸው ታጣቂዎች ከጥቅም ውጭ ማድረጋቸውን የገለጸው መረጃው በውጊያው ከተገደሉት ታጣቂ አመራሮችም።….
ኮማንደር ወልደሚካኤል ገብረእዝጊአብሄር የሃይል አዛዥ የነበረ፤ ካሕሳይ ነጋሽ በባዕኸር የሚልሻ አዛዥ የነበረ፤ ለግዜው ስሙ ያልታወቀው የሻምበል ማእርግ ያለው በ24 ክፍለጦር የሓይል አዛዥ የሆነውና ሌሎች የሚገኙባቸው እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
እነዚህ የስርዓቱ ታጣቂዎች- በአካባቢው ሰላማዊ ህዝብ የተለያዩ ግፍ ሲፈፅሙ የቆዩ በመሆናቸው የተነሳ የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በላያቸው ላይ እርምጃ መውሰዱን የተገኘው መረጃው አስረድቷል።

Saturday, July 25, 2015

Ethiopian Opposition Group Threatens Armed Resistance

July 25, 2015
(VOA News) Ethiopia’s opposition Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy has decided to use armed resistance in addition to peaceful resistance against the government in Addis Ababa. This follows the move of the group’s leader from the United States to Eritrea.Dr. Berhanu Nega
Berhanu Nega travelled to Ethiopia’s northern neighbor following the merger of his Ginbot 7 with the Ethiopian People’s Patriotic Front. “It’s true he travelled to Eritrea, he went on July 17, 2015,” said the spokesman for the group, Dr. Tadesse Biru.
“He is the leader of an organization that strives to bring about democratic order in Ethiopia, and he went to fulfil his leadership role,” he explained in reference to Dr. Berhanu, who was sentenced to death in absentia while living in the US.
Ethiopia’s government classes Ginbot 7 as a terrorist group. It comprises former members of the Coalition for Unity and Democracy, an opposition grouping that made unprecedented gains against the ruling Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front in 2005 elections.
Tadesse confirmed the merger of Ginbot 7 with the Ethiopian People’s Patriotic Front this year. On armed resistance, he said: “We do have a kind of blended strategy to challenge the government in Addis Ababa. We have been trying to stage civic disobedience; we tried peaceful resistance starting in 2005.”
But, a non-violent solution, he said, has been closed by the government in Ethiopia, and the group has been forced to consider all possible avenues including civic disobedience and armed resistance.
Tadesse emphasized, however, that the group is still open to a non-violent settlement. “We are always open to possibilities of a peaceful resolution. The group emerged from a peaceful movement but now we are forced to consider armed resistance. It’s not our choice but there is no other feasible option to challenge the government in Addis Ababa.”
He said civil disobedience will continue, but will be complemented by ‘non-peaceful resistance, like it was done in South Africa’.
Some observers say the move of the group to Eritrea could renew tensions between the Horn of Africa nations, which fought a two-year war that ended in 2000.
The spokesperson dispelled such fears, saying nothing will happen since the two countries had no friendly relationship anyway. “Eritrea has provided us an opportunity to organize our movement there, that’s all. I don’t think it will in any way affect the relationship – it has not been good.”
As to the strength of the group’s armed force, Tadesse said: “yes, there is a small group that has been training in Eritrea, and there is a movement developing.”
Officials in Addis Ababa have dismissed the group’s move. A special adviser to the Prime Minister was reported saying Ginbot 7 is militarily weak and Berhanu’s move to Eritrea is a “publicity stunt.”

TPLF Security Forces Terrorist Plot in Addis Ababa Leaked

July 25, 2015
def-thumbPatriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy has received credible reports that the fascist regime in Ethiopia has made intricate plans to detonate explosives and blame Patriotic Ginbot 7 for its own terrorist acts.
While we had received the leaked information of the sinister plans being hatched by the TPLF politburo members a few weeks ago, the pending visit of the U.S. President to Ethiopia have made it imperative for the TPLF regime to carry out the heinous crimes in the next few days.
We would like to inform the Ethiopian people and the international community that TPLF has finalized plans to carry on terrorist acts at Bole International Airport, along the major highway leading to the airport, at the headquarters of the African Union and the U.S. Embassy.
The TPLF minority regime is, of course, no stranger to planting bombs in Ethiopia’s capital Addis Ababa in a bid to frame its real and perceived political enemies and brutally murder innocent Ethiopians.
Massive leaks of secret files by WikiLeaks has exposed the late Prime Minister Meles Zenawi as the terrorist-in-chief. In a report from 2006 marked “Secret; Subject: Ethiopia: Recent Bombings Blamed on Oromos Possibly the Work of Government of Ethiopia” “Classified By: Charge [d’Affairs] Vicki Huddleston”, “An embassy source, as well as clandestine reporting, suggests that the bombing may have in fact been the work of the Government of Ethiopia security forces.” (Cable reference id:#06ADDISABABA2708.)
Patriotic Ginbot 7 strongly condemns the senseless brutality and the unconscionable use of terror by the rogue regime in Ethiopia to garner international support. Its utter disregard for the sanctity of human life and the Ethiopian people’s well known reputation as a peaceful and cultured people who abhor violence is truly horrifying.
The very fact that this dying regime is willing to kill, maim and cause mayhem in Addis Ababa to maintain power at any cost and in the face of a shrinking political base is a clear indication that it has lost any legitimacy to rule Ethiopia.
Patriotic Ginbot 7 would like to remind the deeply traumatized people of Ethiopia who are knowledgeable of the sinister motives of the fascist regime to be ever so vigilant and take every precaution for their individual and collective safety.
It is also time for the United States and the international community to realize that a terrorist regime willing to use violence to cling to power will never be a credible partner in the “war against terror.”

ኦባማ፡ “በንግግር (ወሬ) A፣ በተግባር D” ኦባንግ ሜቶ

July 25,2015
“በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን”
obang voa4

ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ውጤት ቢሰጥ በእስካሁኑ የአፍሪካ ፖሊሲያቸው በንግግር (በወሬ) ደረጃ A በተግባር ግን D እንደሚሰጧቸው ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ፡፡ አፍሪካውያንም ሆኑ ኢትዮጵያውያን ለነጻነት በሚያደርጉት ትግል ምዕራባውያን ዕንቅፋት ከመሆን እንዲቆጠቡ አስረዱ፡፡
በአሜሪካ ድምጽ የStraight Talk Africa አዘጋጅ ሻካ ሳሊ የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን የአፍሪካ ጉብኝት በተመለከተ ከሁለት ቀናት በፊት ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ሦስት አፍሪካውያንን ተጋብዘው ነበር፡፡ ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ የሴራሊዮኑ ፕሮፌሰር አብዱል ካሪም ባንጉራ፣ የአፍሪካ ስደተኞች ስብስብ ኃላፊ ጋናዊው ኒ አኩቴ እና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር ኢትዮጵያዊው ኦባንግ ሜቶ ነበሩ፡፡
በእስካሁኑ የአፍሪካ ፖሊሲያቸው ለፕሬዚዳንቱ ምን ውጤት ትሰጣላችሁ በማለት ሻካ ላቀረበው ጥያቄ ዶ/ር አብዱል D እሰጣቸዋለሁ፡፡ ይህም በተለይ ከአፍሪካ ጋር ስላለላቸው ግንኙነትና እንዴት የአፍሪካ ፖሊሲያቸው ውጤት አልባ እንደሆነ በመመልከት ነው ብለዋል፡፡ ይህንን ያሉበትም ምክንያት በርካታ ሰዎችን በመጠየቅ ባደረጉት ጥናትና ምርምር እንደሆነ ሆኖም አሜሪካ ከኩባ ጋር ያላትን የሻከረ ግንኙነት በማለዘብደረጃ የተጫወቱ ሚና ከዚህ የወረደ ነጥብ እንዳያገኙ እንደረዳቸው ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል፡፡
ጋናዊው  አኩቴ ግን ለኦባማ A እንደማይሰጡ ከተናገሩ በኋላ በዝርዝር ሳይጠቅሱ ፕሬዚዳንቱ ላከናወኑት ተግባራት ግን ተመጣጣኝ ነጥብ ሊሰጣቸው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በላይ ግን የትኛውም ነጥብ ይህ ነጥብ ወይም ደረጃ ለምንድነው የሚሰጣቸው ብሎ መጠየቅ ተገቢና አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡obang voa2
ኢትዮጵያዊው ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ውጤት ስጡ ቢባሉ “በንግግር (በወሬ) A በተግባር ግን D” እንደሚሰጧቸው ተናግረዋል፡፡ ይህንንም ሲያስረዱ ከዓመታት በፊት ጋናን በጎበኙ ወቅት “አፍሪካ የሚያስፈልጋት ጠንካራ መሪዎች ሳይሆን ጠንካራ ተቋማት” ነው ማለታቸውን ከጠቀሱ በኋላ “በአሁኑ ወቅት በአገሬ ያለው አገዛዝ በምርጫ መቶ በመቶ አሸንፌአለሁ” የሚል መሆኑን አውስተዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተቋማት መቀጨጭ ወይም መምከን ምን ደረጃ እንደደረሰ ሲያስረዱም “በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብት፣ ለሴቶች መብት፣ ለህጻናት መብት፣ ለዕርቅ፣  መሥራት ሕግን እንደ መጣስ ተቆጥሮ” ለእስር እንደሚዳርግ አስረድተዋል፡፡ አሜሪካ የተመሠረተችባቸው እነዚህ እሴቶች በኢትዮጵያ ዋጋ የሌላቸው መሆኑን ሲገልጹ ዋንኛው ምክንያት ጠንካራ ተቋማት በኢትዮጵያ እንዳይኖሩ አገዛዙ የመያዶች ሕግ በመባል የሚታወቀውን በማወጅ ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖርና ሊቃወሙት የሚችሉትን ሁሉ በሕገወጥነት በመፈረጁ መሆኑን አውስተዋል፡፡
ከዚህ ሌላ በአገራቸው ጠንካራ ተቋም እንዳይመሠረት ዕንቅፋት የሚሆን የጸረ አሸባሪነት ሕግ በሥራ ላይ መዋሉን “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ የፕሬዚዳንቱን ጉብኝት በተመለከተ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን እንደተናገሩት ዋናው ዓላማ የአሸባሪነት ጉዳይ ተብሎ መጠቀሱ ኦባማ ለአፍሪካ ያላቸውን አመለካከት ያሳያል ብለዋል፡፡ ይህም ማለት ማንኛውም የአፍሪካ መሪ ሕዝቡን እያሸበረ የአሜሪካንን ጥቅም እስካስከበረ ድረስ የዜጎች መብት መረገጥ ነገር ለአሜሪካም ሆነ ለምዕራባውያን ከጉዳይ እንደማይቆጥሩት የጋራ ንቅናቄው መሪ ኦባንግ አስረድተዋል፡፡ “ለዚህም ነው በአሁኑ ጊዜ ጠንካራ ተቋማት መመሥረት የሚችሉ ብሩህ ኅሊና ያላቸው ጦማሪያንና ጋዜጠኞችና የነጻነት ድምጾች በአሸባሪነት ተፈርጀው በእስር የሚማቅቁት” በማለት ኦባማ በንግግር ደረጃ ለጠንካራ “ተቋማት መመሥረት ቢያወሩም በተግባር ግን የከሰሩ ናቸው፤ (የአፍሪካ ኅብረትን ሰብስበው ሲያናግሩም) የሚናገሩት ከጠንካራ መሪዎች ጋር ነው” ብለዋል፡፡
ኦባንግ ቀጠሉ “ዛሬ ኢትዮጵያ የምትተዳደረው በአፓርታይድ ዓይነት ዘረኛ አገዛዝ ነው፤ (ወደ አዘጋጁ ሻካ ሳሊ በመጠቆም) ለምሳሌ እኔና አንተ እዚህ አሜሪካ አገር በመጀመሪያ ሰዎች ነን፤ ወንድማማች ነን እንጂ ኢትዮጵያዊ ወይም ዑጋንዳዊ ተባብለን በዘርና በአካባቢ የተለያየን አይደለም፤ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ግን ይህ አይደለም፤ አንዲያውም በቅርቡ ከአሜሪካ የኔብራስካ ጠቅላይ ግዛት ወደ ኢትዮጵያ የሄደች አንዲት እህት መታወቂያ ካርድ ለማውጣት ስታመለክት ዘርሽ (ብሔርሽ) ምንድነው ተብላ ስትጠየቅ የሁለት ቅልቅል በመሆኗ ይህ ነው ብላ መናገር እንደማትችል፤ ኢትዮጵያዊ መሆኗን ብታስረዳም የግድ እንደሆነ ከኃላፊዎች ሲነገራት በማመልከቻው ቅጽ ላይ አማራ + ኦሮሞ = ______ በማለት እናንተው ሙሉት በሚል ክፍት አድርጋ ትታዋለች፤ (በኢትዮጵያ ሰው ከመሆንህ በፊት ዘርህ ይቀድማል) የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት የሚባለው ከደርግ ለመታገል በረሃ ወረደ፤ ደርግ ከተወገደ በኋላ ኢህአዴግ በማለት ራሱን የቀየረ በመምሰል አሁንም (ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም) እየገዛ ይገኛል፤ ዛሬ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት በህወሃት ቁጥጥር ሥር ውሎ ዜጎች ይበረበራሉ፤ ሚሊታሪው፣ ኢኮኖሚው፣ ደኅንነቱ፣ በሙሉ በህወሃት ቁጥጥር ሥር ነው፤ በመሆኑም ኦማባ እስካሁን በኢትዮጵያ ላይ የተከተሉት ፖሊሲ ይህንኑ የሚደግፍና ከሕዝቡ ያልወገነ ነው” በማለት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር አስረድተዋል፡፡
ጠያቂው ሻካ ሳሊ “እርስዎ ከበርካታ የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎችና ከፍተኛ የፖለቲካ ኃላፊዎች ጋር በየጊዜው ይገናኛሉ፤ ከእነዚህ ሰዎች ጋር በሚያደርጉት ንግግር ወቅት እነዚህ ባለሥልጣናት አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ስላላት አቋም በተመለከተ ምንድነው የሚሉት” በማለት ለኦባንግ ላቀረቡላቸው ጥያቄ ሲመልሱ “በየጊዜው የሚሉት በኢትዮጵያ ጠንካራ ተቃዋሚ የለም ነው፤ እኔ የማስረዳቸው ደግሞ አገዛዙ ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖር በስልት እንዴት እንዳደረገ ነው፤ ኢንተርኔቱን ተቆጣጥረውታል፤ ከሃያ ዓመታት በላይ መንግሥት የሌላት ሶማሊያ በኢትንተርኔት አጠቃቀም ኢትዮጵያን ትበልጣለች፤ በየጊዜው የሚነሱ የነጻነት ድምጾች ታፍነዋል፤ ታስረዋል፤ ኢትዮጵያውያን በውጪ መደራጀት ይችላሉ ሆኖም በአገር ውስጥ (ህወሃት) ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖር አድርጓል” በማለት በየጊዜው ለሚያገኟቸው የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንደሚያስረዱ ጠቁመዋል፡፡
ፕ/ር አብዱል በተራቸው በሙያቸው ባደረጉት ጥናት ኦባማ ለአፍሪካ እጅግም የበጀ ወይም በዋንኘነት የሚጠቀስ ተግባር አለመፈጸማቸው ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር አብዱል ማመጣጠን እንዳለባቸው አዘጋጁ ሻካ ሳሊ በመጥቀስ ለአብነት ያህል በራሳቸው በፕ/ሩ የትውልድ አገር ሴራሊዮን የተከሰተውን የኢቦላ ቫይረስ በመከላከል ኦባማ ያደረጉት አስተዋጽዖ ታላቅ እንደሆነ የሴራሊዮኑ ፕሬዚዳንት መናገራቸውን፣ እንዲሁም በላይቤሪያ ኦባማ የፈጸሙት ተግባር ተጠቃሽ እንደሆነ ፕሬዚዳንት ሰርሊፍ የመሰከሩ መሆኑን ከዚህም ባሻገር ወጣት አፍሪካውያንን ወደ አሜሪካ እየመጡ እንዲማሩ በማድረግ ለአህጉሪቱ የወደፊት ራዕይ የሚበጅ Young Africans Leadership Initiative (YALI) ፕሮግራም መመሥረታቸው ሊጠቀስ እንደሚገባው በቃለምልልሱ ወቅት አውስቷል፡፡
ፕ/ር አብዱል ከበፊቱ ጠንከር ባለ ሁኔታ እንዲያውም ፕሬዚዳንት ኦባማ በኬኒያም ሆነ በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ጉብኝት የደመቀ አከባበርም ሆነ ዳንስና ጭፈራ እንደማያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ምክንያቱም ፕሬዚዳንቱ ለሥራ የመጡ ከሆነ ያላቸውን ጊዜ ሁሉ ምን መደረግ እንዳለበት በዝርዝርና ነጥብ በነጥብ ከአፍሪካውያን ጋር ጊዜያቸውን በሙሉ ማዋል ይገባቸዋል፡፡ ጊዜው የጭፈራና የዳንስ ሳይሆን የሥራና ተግባራዊ ለውጥ የሚታቀድበት ሊሆን እንደሚገባ ፕ/ር አብዱል አስረድተዋል፡፡
obang voa5“ፕሬዚዳንት ኦባማ ይህንን ፕሮግራም ቢመለከቱ ለእርሳቸው የሚነግሩት መልዕክት ምንድነው? ካሜራውን እየተመለከቱ መልዕክት አስተላልፉ” በማለት ሻካ ለኦባንግ ሜቶ ላቀረበላቸው ጥያቄ ጥቁሩ ሰው “ከሥልጣን ከለቀቁ በኋላ ስለሚቀጥለው ሌጋሲዎ የሚያስቡ ከሆነ እና መታወስ፣ መታሰብ የሚፈልጉ ከሆነ ሲታወሱ ሊኖሩበት የሚችልበት አንዱ መንገድ ለአምባገነኖች በሠሩት ተግባር ሳይሆን ለሕዝብ በሚያከናውኑት ሥራ ነው፤ የአፍሪካ ኀብረት 50ዓመታት እለፎታል በአኅጉሪቷ (ፖለቲካ) ላይ ያመጣው ይህ ነው የሚባል ለውጥ የለም፤ ስለዚህ በሕዝብ ላይ ኢንቨስት ያድርጉ፤ (ከሕዝብ ጋር ይቁሙ)፤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማነቆ የሆኑት የጸረ አሸባሪነት ሕግ እና የመያዶች ሕግ እንዲሻሻሉ ወይም እንዲሻሩ ማድረግ ይችላሉና በዚህ ላይ ይሥሩ፤ በቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት አሜሪካ እንዳደረገችው በኢትዮጵያም የሲቪክ ማኅበረሰቦች (መያዶች) በነጻነት እንዲንቀሳቀሱና ሕዝብን በማንቃት ረገድ ተግባራቸውን እንዲወጡ እርስዎም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ይቁሙ” በማለት በቀጥታ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ሲቀጥሉም “የኢኮኖሚ ዕድገት አለ ይባላል፤ የሚታይ እንቅስቃሴ አለ፤ መንገድ ይሠራል፤ ፎቅም ይገነባል፤ ሆኖም የኢኮኖሚን ዕድገት በፎቅና መንገድ ሥራ መለካት አይቻልም፤ ኢኮኖሚው በእርግጥ እያደገ እየተመደገ የሄደ ከሆነ ለምንድነው ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን መስዋዕት በማድረግ ቀይባህርን አቋርጠው የተሻለ ኑሮ ፍለጋ የሚሰደዱት፤ ከአጠቃላዩ ሕዝብ 6 በመቶ በማይበልጥ አናሳ ብሔረተኞች ቁጥጥር ስር ስለሆነ አድጓል የሚባለው ኦኮኖሚ ይህ ነው የሚባል ለውጥ በሕዝቡ ኑሮ ላይ ሊያመጣ አልቻለም” በማለት ኦባንግ ሜቶ በመላው ዓለም ፕሮግራሙን ለሚከታተሉ የአገራቸውን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም የጋራ ንቅናቄው ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ “አፍሪካውያንም ሆነ ኢትዮጵያውያን ኦባማን ወይም አሜሪካንን ወይም ምዕራባውያንን ነጻ እንዲያወጡን እየለመንን አይደለም፤ ራሳችንን እንዴት ነጻ እንደምናወጣ እናውቃለን፤ ነገር ግን (ከአምባገነኖች ጋር በማበር) በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን” በማለት ግልጽ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Friday, July 24, 2015

ዝዋይ እስር ቤት

July 24,2015
ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም
temeprison

ሐምሌ 16/2007 ዓ.ም. ለአሥር ወራት በእስር ላይ የቆየውን ጋዜጠኛ፣ ተመስገን ደሳለኝን (ከኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ዝምድና የለውም፤) ለመጠየቅ ወደዝዋይ ወህኔ ቤት ሄጄ ነበር፤ የወሕኒ ቤቱ ባለቤቶች ማረሚያ ቤት ይሉታል፤ ማረሚያ ቤት ማለት ሀሳቡን በነጻነት የሚገልጽና በሀሳቡም ከወያኔ ጋር በሎሌነት ለመተዳደር የማያመች ሲሆን የቀናውን በጉልበት የሚያጎብጡበት ማለታቸው ነው፤ ማረም ማለት ቀጥታውን ማጉበጥ ነው፤ እንዴት እንደሚያጎብጡት ላሳያችሁ፤–
1. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ እስረኞች ሰዎች በመሆናቸው ሰብአዊ ደኅንነታቸውና ክብራቸው ሁልጊዜም እንዲጠበቅላቸው ያስፈልጋል፡፡
2. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ እስረኞች ሁሉ ከመሰቃየትና ከመጉላላት በጸዳ አያያዝ እንዲጠበቁ ይደነግጋል፤
3. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ አንድ እስረኛ ዘመዶቹና ወዳጆቹ ከሚኖሩበት በጣም ርቆ አይታሰርም፤
4. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ የታመመ እስረኛ ሙሉ ህክምናና አስፈላጊውን መድኃኒት ሁሉ ማግኘት አለበት፤
5. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ እስረኞች በአእምሮና በመንፈስ የሚያድጉበት ትምህርትን የማግኘት፣ መጻሕፍትን የማግኘት መብቶች አሏቸው፤
6. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ማንኛውም እስረኛ በእምነቱ መሠረት አምልኮቱን የመፈጸምና የሃይማኖቱን መጻሕፍት የማንበብ መብት አለው፤
7. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ማንኛውም እስረኛ ዘመዶቹና ወዳጆቹ እንዲጎበኙት መብት አለው፤
8. እስረኞች የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ከወህኒ ቤት ሲወጡ ትክክለኛ የማኅበረሰቡ አባሎች ሆነው እየሠሩ ለማኅበረሰቡ እድገት ድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ማሰናዳት ያስፈልጋል፤
በዝዋይ እንዳየነውና እንደተነገርነው የእስረኞች ሁኔታ በጣም የሚያሳዝንና ከላይ የተዘረዘሩትን የሰብአዊ መብቶች የሚጥስ ነው፤ ጤንነት ዋና ነገር ነውና በሱ እንጀምር፤ ተመስገን ደሳለኝ ወንጀል የተባለበት የፖሊቲካም ሆነ የማኅበረሰብ እምነቱን እያፍረጠረጠ በመጻፉ ነው፤ (በ1992 ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባደረግሁት ንግግር ‹‹አትፍሩ›› ብለሃል ተብዬ ተከስሼ ነበር!) እንዲያውም ክሱን አስቂኝ የሚያደርገው መንግሥትን ነቅፈሃል የሚል መሆኑ ነው፤ ሦስት ዓመት እስራት ተፈረደበት፤ ይግባኝ ተከለከለ፤ አሁን ከታሰረ አሥር ወራት ሆኑት፤ ተመስገን በጣም ከታመመ ጥቂት ቆየ፤ አንደኛ አንዱ ጆሮው በጭራሽ አይሰማም፤ ሁለተኛ ከባድ የወገብ ሕመም ስላለበት መተኛትና መቀጥም በጭንቅ ሆኖበታል፤ ሆኖም አሳሪዎቹ ወደሀኪም ቤት ሊወስዱት ፈቃደኛ አይደሉም፤ ከዚያም በላይ መድኃኒት ከውጭ ሲመጣለት ይከለክላሉ፤ እኔም የወገብ ሕመም ስላለብኝ የወገብ ሕመሙን የሚያቀልለትን መድኃኒት ወስጄለት ነበር፤ አንድ አሥር አለቃ መድኃኒቱን አየና ከለከለ፤ መልሼ ይዤው መጣሁ፤ እንዲህ ያለውን ውሳኔ የሚያደርጉ ሁሉ ወያኔዎች ናቸው፡፡
ከተመስገን ጋር ትንሽ ጊዜ ቆይተን በዚያው በዝዋይ የታሰሩ ሌሎች ጋዜጠኞችን ለመጠየቅ መጀመሪያ ተፈቅዶልን ስለነበረ ወደዚያ ስናመራ አንድ ሹም መሳይ መጥቶ ወታደሮቹን ለብቻ ለብቻ በስም እየጠራ በመንሾካሾክ ትእዛዝ ይሰጣል፤ እየተንሾካሾከ ለአንዱ ትእዛዝ ሰጥቶ ሌሎቹን እንዳናይ ከለከለንና ተመለስን፤ ምክንያቱን ብንጠይቅ በአንድ ጊዜ መጠየቅ የሚቻለው አንድ እስረኛ ብቻ ነው ተባልን፤ ቅን መንፈስ ለጎደለውና ለሙስና ለተጋለጠ አሠራር ጥሩ ምሳሌ ነው፤ በመንሾካሾክ የሚሰጠውም ትእዛዝ ዓላማው ያው ይመስላል፤ ወያኔ በሰዎች ላይ እንዲህ ያለ ጭካኔ ማሳየት የሚፈልገው ለምንድን ነው?
በዝዋይ እስር ቤት ትምህርትም እንደመድኃኒት የተጠላ ነገር ነው፤ ለተመስገንም ሆነ ለሌሎች መጻሕፍት አይገቡላቸውም፤ ለምን? ብዬ ስጠይቅ አንዱ ጠባቂ ‹‹ለእውቀት የሚሆን መጽሐፍ ይገባል፤›› አለኝ፤ የእውቀትን ፍቺ ለመጠየቅ ስሞክር ቶሎ ግራ መጋባቱን አየሁና ተውሁት፤ እሱም እንዳያውቅ ስለሚፈልጉ፣ አለቆቹ የእውቀትን ፍቺ ጠበብና ቀለል አድርገው አስተምረውታል፤ ሎሌ ትእዛዝን በሹክሹክታ እየተቀበለ ማስፈጸም እንጂ፣ እውቀት አያስፈልገውም፤ እዚህ ላይ ምናልባት በደርግ ጊዜ በእስር ቤቶች የነበረውን የትምህርት መስፋፋት ማንሣት ይጠቅም ይሆናል፤ በደርግ ዘመን ብዙ የተማሩ ሰዎች ታስረው ስለነበረ እረስበርሳቸው እየተማማሩ አንዳንድ ሰዎች ጀርመንኛና ፈረንሳይና ቋንቋዎች፣ ግእዝና ታሪክ እየተማሩ ወጥተዋል፤ በተለይ በሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ወህኒ ቤቶች አንደኛ ሲወጡ እንደነበረ አስታውሳለሁ፤ ዛሬ በወህኒ ቤቶች ትምህርት ክልክል ነው፤ በቃሊቲ ሁለት የትምህርት ሙከራዎች ከሽፈውብናል፤ አንድ ጊዜ ኦሮምኛ ለመማር የፈለግን ሰዎች ተሰባስበን ተከልክለናል፤ ሕግ ለመማርም ጀምረን ታግደናል፤ እንዲሁም ጂምናስቲክ በቡድን መሥራት ክልክል ነበር፤ ማናቸውም እውቀት አደገኛ ነው! ታዲያ ማረሚያ ቤት የሚሉት ማንን ለማታለል ነው? ማረሚያ ቤት እንዲሆን በመጀመሪያ አሳሪዎቹ መታረም አለባቸው!
እንደተመስገን ደሳለኝ፣ እንደአብርሃ ደስታ፣ እንደእስክንድር ነጋ፣ ከዞን ዘጠኝም በፈቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ወበላ፣ አጥናፉ ብርሃኔ ገና አልተለቀቁም፤ በተጨማሪም ከእስልምና በኩል የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባሎች ዛሬም እንደታሰሩ ነው፤ የመፍትሔ አፈላላጊዎችን ማሰር ነገሩም ግራ ነው፡፡
በመጨረሻም መነሣት ያለበት አንድ አደገኛ አዝማሚያ አለ፤ ፖሊስ የሚባለው ፍርድ ቤት ከሚባለው ጋር ያለው ግንኙነት ሕግ የሚባለውን ከጨዋታ ውጭ አድርጎታል፤ ፍርድ ቤት የሚባለው እስረኛ እንዲፈታ ፖሊስ የሚባለውን ሲያዝ እንደማይፈጸም በተደጋጋሚ ታየ፤ ይህ የመጨረሻው የውድቀት ምልክትይመስለኛል፤ቆም ብሎ ማሰብና አስፈላጊውን የለውጥ እርምጃ መውሰድ የሚያስፈልገው አሁን ነው፡፡
ሐምሌ 17/2007

Thursday, July 23, 2015

AG7, TPDM, and ADFM to form a coalition; OLF and ONLF excluded

July 23,2015
Image
Arbegnoch Ginbot 7 (AG7), Tigray People's Democratic Movement (TPDM), and Amhara Democratic Force Movement (ADFM) have been directed by the Eritrean regime to form a coalition, according to ER sources in Eritrea.

Two senior leaders of AG7, Dr Berhanu Nega and Ato Neamin Zeleke, are currently in Asmara.

The AG7-TPDM-ADFM coalition's political wing will be headed by Dr Berhanu while the military wing will be headed by Ato Molla Asgedom, ER sources report.

AG7 and ADFM combined have less than 100 members on the ground, while TPDM has over 40,000 armed and well-trained members.

AG7 has been pushing for Oromo Liberation Front (OLF) and Ogaden National Liberation Front (ONLF) to be included in the coalition, but the Eritrean regime (Shabia) has refused.

ER sources added that Shabia is preparing to launch a guerrilla-style and asymmetrical warfare with TPDM and its own forces before the rainy season is over. Shabia believes that it can cripple Woyanne's military during the next few months when it is able to respond only by air. Woyanne tanks and artillery will be useless during the rainy season, according to military analysts. Targets will include lightly protected factories, bridges, and key supply routes. More details later...

Q&A: Professor Berhanu Nega – Bucknell University

July 23, 2015
dr-berhanu-NegaIn December, an Ethiopian court sentenced Professor of Economics Berhanu Nega to death in absentia for terrorism.
Q: Your colleagues and friends understand that this charge is bogus, but do you hear from others who don’t?
A: I haven’t heard from any one who takes this as a serious judicial decision. Only the Ethiopian government and its blind supporters take this decision seriously. Even the government knows that the decision of the court is nothing but a reflection of the regime’s desires rather than based on any reasonable evidence. It sends a message to the public — there is no court to save you, you live by our rules, if you question our rules, we will do what we want, and no one will stop us.
Q: The death sentence is real, and you were jailed under the Zenawi government. Are you afraid?
A. One of the reasons that you struggle for freedom and liberty is because you feel that life isn’t meaningful without liberty. I don’t want to think about this in a way that would affect my day-to-day existence. I am not worried not because the government would not try to harm me, but I now live in a society of laws that will protect me. You can’t live in fear. If you allow this kind of fear to determine your actions, dictatorships will exist forever.
Q: What sustained you when you were imprisoned?
A: First, the Ethiopian people and their yearning for freedom. While I was incredibly disappointed by U.S. and European policy makers and diplomats at the time, while I was in prison, I also was hearing about Bucknell, my colleagues, students and people at other universities supporting freedom. People who love liberty and stand by your side — that’s the more endearing attachment. This connection at the human level, that people love and support freedom everywhere, recognizing that freedom is a human condition, is the hope for humanity that keeps you going. It was a source of hope for me when I was in prison, and I suspect for all people fighting for liberty around the world.
Q: What is your hope for Ethiopia?
A. Unless the international community takes the position of outrage as it did in Guinea, the government will not change. The brutality of this regime is mind boggling. This is a government that is known for committing genocide against its people. This is a most hated government because it is not only undemocratic, it is ethnocentric. Its basic strategy is to stay in power by terrorizing people and by dividing them on primordial grounds. There are several groups fighting against the government. Unless there is a serious intervention, the whole region will blow up. I encourage Western policymakers to recognize what is happening and adjust their policy before it is too late to make a difference. The only credible and durable solution for the region, in my view, is the democratization of Ethiopia.

Tuesday, July 21, 2015

የወያ ኔ ኢህአዴግ ስርዓት ልማታዊ መንግስት ሊሆን አይችልም!!

July 21,2015
editorail amharic
ከአሰልቺ የወያኔ ኢህአዴግ ካድሬዎች ፕሮፖጋንዳ አንዱ በአሁኑ ግዜ በአገራችን ውስጥ ፈጣን ልማት ሊያመጣ የሚችል ስትራቴጂ መቀየሱና ተአምራዊ ለውጥ እንዳመጣ ተደርጎ የሚነገረው ነጭ አሉባልታ መሆኑን አጠቃላይ የአገሬው ህዝብ ፍንትው አድርጎ የሚያውቀው ጉዳይ ነው።
ኢህአዴግ በአገራችን ላይ ላሰፈነው አገዛዝ ተቀባይነት ዋነኛ መከራከሪያው “ለኢትዮጵያ ልማትን ያመጣሁና አሁንም በማምጣት ላይ ያለሁ መንግሥት ነኝ፤ ለወደፊቱም ኢትዮጵያን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የሚመራና ቀልጣፋ ልማትን ማረጋገጥ የሚችል ሃይል ባለመኖሩ ለኢትዮጵያ  ሲባል  እኔ  ለረዥም ጊዜ  በስልጣን መቆየት አለብኝ በሚል ማደናገርያ ቃል መልዕክቱን ሲያስተላልፍ በተደጋጋሚ አየሰማነው ነው።
በዛሬቷ ኢትዮጵያ መብራት ሲቋረጥ፤ ውሃ ሲጠፋ፤ እህል ሲወደድ፤ መንደሮች ሲፈርሱ፤ የመኪና አደጋ ሲበዛ፤ ገበሬዎች ሲፈናቀሉ፤ ሰበቡ ልማት ነው? ለረሀብ፤ ለጥማት፤ ለበሽታ እና  መሰል መጥፎ  ነገሮች ልማትን እንደ ምክንያት ሆኖ  ሲቀርብ፤ “መብቴ ይከበርልኝ ብሎ መጠየቅ “በፀረ-ልማትነት” ሲያስከስስ። ባገራችን ልማት ያረጋገጠ ዴሞክራሲያዊ ስርአት መኖሩን የሚያመለክት ነው? ፍፁም አይደለም! የኢኮኖሚ ልማት። … በሰው ልጅ ሁለንተናዊ እድገት፤ በዋና ዋና መሠረተ ልማት አቅርቦቶች፤ በአካባቢው ገበያ በሚኖር ተወዳዳሪነት፤ በምቹ የተፈጥሮ አካባቢ፤ በማኅበራዊ መስተጋብር፤ በጤና፤ በደህንነት፤ በትምህርት’ና በመሳሰሉ ነገሮች እድገት ማምጣትን ያካትታል።
የኢኮኖሚ ልማት የአንድ ሕዝብ ኢኮኖሚያዊ፤ ፓለቲካዊና ማኅበራዊ ደህንነት የሚሻሻልባቸው ሂደቶችና ፖሊሲዎችን ያካትታል። ልማት በቁጥር የሚለካ ብቻ ሳይሆን። በቁጥሮች መለካት የሚቸግር ገጽታ  አለው። እንዲያውም የልማት ዋነኛ ግብ በቁጥሮች ለመለካት አስቸጋሪ የሆነውን “ደስተኛ  ማኅበረሰብን” መፍጠር ነው።
ልማት ማለት የአብዛኛውን ሕዝብ የዛሬ ኑሮ እና የነገ ተስፋው ላይ ተጨባጭ አዎንታዊ  ለውጥ መፍጠር ነው። ይህም በአመጋገባችን፤ በጤናችን፤ በአለባበሳችን፤ በምናገኘው ትምህርት መጠንና ጥራት፤ በሚሰማን የራስ መተማመን ስሜት፤ በምናገኘው ፍትሃዊ ዳኝነት፤ በማኅበረሰቡ ባለው የመግባባት መጠን፤ በሚሰማን የነፃነት ስሜትና ባጠቃላይ የልማት መጨረሻው ግቡ የህብረተሰቡን ድህነት መቀነስ እንጂ ሀብታሙን ይበልጥ ቱጃር ማድረግ አይደለም።
የልማት ትክክለኛው ትርጉም ያልገባው ገዢ የኢህአዴግ መንግስት! ልማት ማለት እንጀራ መጋገር ብቻ ሳይሆን የጋገሩትን እንጀራ የመብላትንም መብት ያጠቃለለ፤ የነገ እንጀራ የማግኘት ተስፋ አሻግሮ የሚመለከት በቁሳዊ ሃብቶች ብቻ ሳይሆን ቁሳዊ ባልሆኑ ሃብቶችም ጭምር የሚለካ መሆኑና፤ ልማት ማለት የዛሬ ነፃነትና የነገንም ተስፋ እንደሆነ  ጠንቅቆ የተረዳው አይመስልም።
የወያኔ-ኢህአዴግ ነጋ ጠባ አስመሳይ “የልማት ጋጋታና የማደናገርያ ቃላቶች ሃቅን ለማድበስበስ ታስበው በተፈበረኩ አሃዞች የሚገለፁ መሆናቸው የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቋል። በአገራችን ውስጥ ዛሬ ድህነትና ስራ አጥነት በዝቷል፤ ፍትህና ነፃነት የለም፤ የህዝቡ ክብርና ስብዕና አልተረጋገጠም፤ የትምህርት ጥራት አሳፋሪ ደረጃ ላይ ወድቋል፤ ስደት ተሰምቶ ወደማይታወቅ ደረጃ ደርሷል፤ ሙስና ተቀባይነት ያለው አሠራር ሆኗል ወ.ዘ.ተ….. ስፍር ቁጥር የሌለው ችግሮች ማንሳት ይቻላል።

የመብት ጉዳይም ቢሆን በጥቂት ፀረ ህዝብ አገዛዝ መሪዎች ምክንያት ሕዝቦች በግፍ የሚሰቃይበትና በባዶ ውንጀላዎች እስር ቤት ውስጥ ገብቶው የሚማቅቁበት ሁኔታ ላይ መሆኑን ይታወቃል። ስለዚ ወያኔ ኢህአዴግ ከኔ የተሻለ መንግስት አታገኙም እያለ በህዝቡ ላይ እየቀለደና ህዝቡን እያደናገረ የስልጣን ቆይታውን ለማስረዘም ላይና ታች እያለ ባለበት ሰዓት ስርዓቱ ትርጉም ያለው ልማት ማረጋገጥ ይችላል ብሎ ማሰብ የሚቻል አይደለም።

Sunday, July 19, 2015

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ወደ ጦር ግንባር!

July 19,2015
Bilderesultat for berhanu nega
ከቃሊቲ እስር ቤት ከተፈታ በሁዋላ ወደ አሜሪካ በመመለስ በተማረበት ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር በመሆን ሲያገለግል ከቆየ በሁዋላ ከጥቂት ወራት በፊት የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማእረግ ተሰጥቶት በበክኔል ዩኒቨርሲቲ በስራ ላይ ቆይቷል። ሙሉ የፕሮፌሰርነት ማእረግ እንደ ተሰጠው የሰሙ ጋዜጠኞች ደስታቸውን ገልጸው ዜናውን ለመዘገብ ሲጠይቁት "ፕሮፌሰርነት ተራ ነገር ነው። የእኔ ስራ ማስተማር ሳይሆን በአስከፊ ጭቆና እና ዘረኝነት ስር ወድቆ የሚማቅቀውን ህዝቤን ነጻ ማውጣት ነው" ሲል ጋዜጠኞቹ ተደምመው ነበር። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚህ በአሜሪካን ሃገር የፕሮፌሰርነት ህይወቱን ትቶ በረሃ የወረደው ምንም ጎሎበት አይደለም።

 የኢትዮጵያ ህዝብ እንባና መከራ፣ ህመምና ሰቆቃ እንቅልፍ ስለነሳው ብቻ ነው ዛሬ ያፈራውን ሃብትና ንብረት ሽጦ ህዝቡን ነጻ ሊያውጣ ከፊት ሆኖ ሊመራ ከድካሙ አረፍ ብሎ በመኖሪያ እድሜው በረሃ የወረደው። የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ወደ ግንባር መሄድ ያለው ትልቅ እንድምታ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም። የቆረጠ ለውጥ ማምጣቱ አይቀርም። ፕሮፌሰር ብርሃኑ የሚሞላው አንድ ታላቅ ክፍተት ህዝባችን የሚከተለው መሪ በአስተማማኝ ሁኔታ ማግኘቱ ነው። 

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በተግባር እና በእሳት የሚፈተን መሪ ለመሆን ወስነህ ሁሉን ትተህ ወደ ግንባር መውረድህ የሚያመጣው ለውጥ ቀላል እንዳልሆነ እኛ ብቻ ሳንሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላቶችም ጠንቅቀው ያውቃሉ። ታላቅ መሪ በተግባር ይፈተናል። እስከ መጨረሻው የነጻነት መዳረሻ ከጎንህ እንሰለፋለን። ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!


አበበ ገላው

ሊቀመንበራችን ትግል ሜዳ ውስጥ ነው!- መግለጫ

July 19, 2015
ሐምሌ 12 2007 ዓ.ም.
ህወሓት በኢትዮጵያዊያን እና በኢትዮጵያ ላይ ያሰፈነው ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ እንዲያበቃ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑበት የፓለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲመሠረት እና የሀገራችን አንድነት በጠንካራ መሠረት ላይ ለማኖር አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ተገዶ የገባበት የመረረ የአመጽ ትግል መጀመሩን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በጀግነትና በጽናት እየታገሉ ነው።
ይህ ትግል በባርነትና በነፃነት መካከል የሚደረግ ወሳኝ ትግል ነው። የዚህ ትግል ውጤት የእኛ የዚህ ዘመን ትውልድ ሕይወት ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የወደፊት ታሪክ፤ የልጅ ልጆቻችንን ሕይወት ይወስናል። በዚህም ምክንያት ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ለነፃነት ግድ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከጎናችን ሊቆም ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7 አመራሩን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን እና ትግሉ በሚጠይቀው ቦታ እንዲገኙ የሚያደርግ መሆኑ ሲገልጽ ቆይቷል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ የአመራሩ በትግሉ ሜዳ ውስጥ መገኘት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ሊቀመንበሩን ጨምሮ አመራሩን ወደ ትግሉ ሜዳ አንቀሳቅሷል። በዚህም መሠረት የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግል ሜዳ ወርዷል።
ትግሉ መሯል። ወሳኝ የሆነ ትግል ውስጥ ገብተናል። የትግሉ መሪዎች የሕይወት መስዋዕትነት እሚከፈልበት ቦታ ይገኛሉ። በአሁኑ ሰዓት የንቅናቄው አመራር በተሟላ ሁኔታ በትግሉ ሜዳ ውስጥ እንዲገኝ ማድረግ ተችሏል። ኢትዮጵያዊያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘረኛው የህወሓት አገዛዝን ከጫንቃችን ለማስወገድ ቆርጠን እንድንነሳ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
ኢትዮጵያን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ የሚያወጣው አርበኞች ግንቦት 7 ብቻ አይደለም። ስለሆነም ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚደረገው ትብብር ቀዳሚ ትኩረት ከተሰጣቸው ሥራዎች አንዱ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ለድል እንዲበቃ ይታገላል። ኢትዮጵያዊያንም በያሉበትም በተመሳሳይ ልዩነቶቻቸውን አቻችለው በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ላይ ክንዳቸውን እንዲያነሱ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
እነሆ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በአካል ትግል ሜዳ ውስጥ ይገኛል። የሚችል ሁሉ እንዲከተል፤ መከተል የማይችል በያለበት ሁኖ ሁለገብ ትግሉን እንዲያጧጥፍ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

አንድ ወታደር 3ት ኮነሬሎችና ሌሎች በርከት ያሉት ወታደሮች በመግደል ራሱን እጠፋ

July 19,2015
በአዲ ሃገራይ አካባቢ  የሚገኝ ለግዜው ስሙ ያልታወቀው ወታደር 3ት ኮነሬሎችና ሌሎች በርከት ያሉት ወታደሮች በመግደል ራሱን እንዳጠፋ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ገለጸ።ከሰሜን የደረሰን መረጃ እንዳስረዳው- በገዢው የኢህአዴግ ስርአት መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ታስረው የሚገኙ ወታደሮች የሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዦች በሚከተሉት ከፋፋይ አሰራር ምክንያት ተማርረው የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ መሆናቸውን የገለጸው መረጃው አሁንም በአዲ ሃገራይ አንድ ወታደር ለ3ት ኮነሬሎች ከነ አጃቢዎቻቸው በኡርምታ ቶክስ በመግደል ለራሱም ህይወቱን እንዳጠፋ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በያዝነው ሳምንት በ3ት የኢህአዴግ ኮነሬሎች ላይ የተውሰደው እርምጃ ለብዙዎቹ በላያቸው ልይ ግፍ ሲፈፀምባቸው የነበሩ ወታደሮች እርካታ የሰጠ መሆኑና ሌሎች አዛዦችም በላያቸው ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እንዳይወሰድባቸው ስጋት መግባታቸውን የተገኘው መረጃ አክሎ አስረድቷል።
adi hageray millitary killing

Saturday, July 18, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት መፈጸም ከጀመረ ወዲህ የወልቃይት ሕዝብ በስርዓቱ አንገዛም ብሎ በአንድነት መነሳቱ ተዘገበ

July 18,2015
አርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ እንደዘገበው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ስርዓት ክልል 1 እና ክልል ሦስት ብሎ የከፈለው የወልቃይት ህዝብ በስርዓቱ አንገዛም ብሎ በአንድነት ተነስቷል፡፡
የወልቃይት ህዝብ “ክልል 1 እና ክልል 3 የሚባል አናውቅም እኛ የጎንደር በጌ ምድር ተወላጆች ኢትዮጵያዊያን ነን” ሲል በአንድነት “ሆ” ብሎ በመነሳት ከእንግዲህ ወዲህ ህወሓት በዘረጋው የፌደራሊዝም ጭምብል ያጠለቀ የጎሳ አስተዳደር እንደማይመራ እንደ ብረት የጠነከረ አቋሙን በመግለፅ ላይ ነው፡፡

የወልቃይት ህዝብ እስካሁንም ድረስ እትብቱ የተቀበረበት መሬቱ ከሁለት ተሰንጥቆ ከፊሉ ክልል 1 ከፊሉ ደግሞ ክልል 3 ተብሎ በህወሓት ዘረኛ ቡድን መቆረሱንና አንድነቱን ሸርሽሮ ለማዳከም የተቀነባበረውን ስውር ደባ እጆቹን በማጣጠፍ ቆሞ አልተመለከተም ነበር፡፡

ከ1992 ዓ.ም አንስቶ እልህ አስጨራሽ ትግል በማድረግ ከፍተኛ መሰዋዕትነት ሲከፍል ኖሯል፡፡ ዘረኛው የህወሓት ቡድን የወለቃይትን የአንድነትና የነፃነት ጥያቄ ያነሱትን ልጆቹን በየጊዜው በመረሸን ህዝቡንም በጅምላ መጨፍጨፍና ዘር በማጥፋት ጥያቄውን በኃይል አዳፍኖት ሊቀር ብዙ ጥረት አድርጓል፡፡

ነገር ግን ዛሬ ህወሓት በወልቃይት መሬት ላይ ያዳፈነው ረመጥ ውስጥ ለውስጥ ሲቀጣጠል ቆይቶ ሳያስብው ግር ብሎ ነዶ ራሱን እየለበለበው ነው፡፡በህወሓት የዘር አገዛዝ በእጅጉ የተማረረው የግፍና በደል ገፈትን ሲጎነጭ የኖረው የወልቃይት ህዝብ የህቡና ይፋዊ አስተባባሪ ኮሚቴዎቹን በመምረጥ በሚገባ ተደራጅቶ ህወሓትን በማንኛውም መስክ ሊፋለመው በአንድነት ተነስቷል፡፡

በመሆኑም ከአዲ ረመፅ 3፣ ከጠገዴ 3 እና ከቃፍታ 1 በድምሩ 7 ይፋዊ ኮሚቴዎችን መርጦ “ክልል 1 እና ክልል 3 አላውቅም፤ እኔ የጎንደር በጌምድር ኢትዮጵያዊ ነኝ” በማለት ከእንግዲህ ወዲህ የህወሓትን የጎሳ አስተዳደር ፈፅሞ የማይቀበለው መሆኑን እንዲያስታውቁለት ወደ አዲስ አበባ ልኳል፡፡

የቀድሞ የ‹‹አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ›› ፓርቲ የአዲስ አበባ ወጣቶች አደረጃጀት የፋይናንስ ኮሚቴ አባል ፍቃዱ በቀለ ታሰረ

July 18,2015
ዛሬ ጥዋት ሌላ የእስር ዜና ሰማን፡፡ የታሰረው፣ የቀድሞ የ‹‹አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ›› ፓርቲ የአዲስ አበባ ወጣቶች አደረጃጀት ውስጥ የፋይናንስ ኮሚቴ አባል እና የወረዳ 15 ሰብሳቢ የነበረው ፍቃዱ በቀለ ነበር፡፡ አጋጣሚ ከወዳጄ አናንያ ሶሪ ጋር ስለነበርን ‹‹በምን ይሆን ደግሞ?›› ብለን ራሳችንን መጠየቃችን አልቀረም፡፡ ወላጅ እናቱና እህቱን በአካል ጠይቀን እንደተረዳነው፣ አንድ ጓደኛው ‹‹አሸባሪ ነው›› ብሎ ጠቁሞበት መሆኑን ነው፡፡ እኛም ካዛንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ልንጠይቀው ሄደን ‹‹እሱን ማግኘት አይቻልም›› ብሎ አንድ ፖሊስ ቢነግረንም በአጋጣሚ ከርቀት አይተነው ሰላም ልንለው ችለናል፡፡
እንግዲህ፣ በየዕለቱ የዜጎችን እስር መስማት የተለመደ ሁነት ሆኗል፡፡ የባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለትየ‹‹ቀዳሚ ገጽ›› ሥራ አስኪያጅ እና የቀድሞ የ‹‹ሚሊየኖች ድምጽ›› ሪፖርተር የነበረው ሃብታሙ ምናለም ‹‹የአልሸባብ ሴል ነህ፤ ኦባማ በሚገኝበት ስብሰባ ላይ የቨብር ተግባር ልትፈጽም አሲረሃል›› ተብሎ ተጠርጥሮ መያዙንና ፍርድ ቤት ቀርቦም ለድጋሚ ቀጠሮ ለሐምሌ 20 ቀን 2007 ዓ.ም መቀጠሩ ይታወሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከቀናቶች በፊት ሌላ የቀድሞ አንድነት ሴት አባል ከታሰረች በኋላ መፈታቷም የሚታወቅ ሲሆን አበበ ቁምላቸው የሚባል የቀድሞ አንድነት በአሁን ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባልም ‹‹ወደኤርትራ ሰው ትመለምል ነበር፣ አንተም ወደዚያ ልትሄድ አስበሃል›› ተብሎ አሁንም ድረስ በካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ይገኛል፡፡
Elias Gebru Godana's photo.

ኢትዮጵያ ከ184 አገራት 171ኛዋ ደሃ አገር!

July 18,2015

“ኢኮኖሚ በመንገድና ፎቅ ሥራ አይለካም”
women carrying

ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የአምስት ዓመታት አኻዝ ያካተተ የዓለማችንን ሃብታምና ደሃ አገራት ዝርዝር ሰሞኑን አውጥቷል፡፡ የዓለም የፋይናንስ መጽሔት ላይ የታተመው ይኸው ዘገባ እንደሚያሳየው በሃብታምና ደሃ አገራት መካከል ያለው ልዩነት በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ነው፡፡ በዚህ የአምስት ዓመት አኻዛዊ ዘገባ መሠረት ከ184 አገራት መካከል ኢትዮጵያ 171ኛ ተራ ላይ የምትገኝ ስትሆን ይህም በድህነት ከሚጠቀሱት ቀዳሚ አገራት ቁጥር ውስጥ አስገብቷታል፡፡ ዘገባውን የተመለከቱ የኢኮኖሚ ባለሙያ የአንድ አገር ኢኮኖሚ በከተሞች ውስጥ በሚሰራ ፎቅ ብዛት እና የመንገድ ሥራ አይለካም ይላሉ፡፡ ሌላ የኢኮኖሚ ባለሙያ ደግሞ “ኢኮኖሚ ከቁጥር ሌላ ሥነ ልቦናዊ ጉዳይም ነው፡፡ የኑሮ ጉዳይም ነው፡፡ የጉሮሮ ጉዳይም ነው፡፡ በቁጥር ብቻ አይለካም፡፡ … የሕንፃ መሐንዲስ ቢሳሳት ሕንፃ ይደረመሳል፡፡ የሰው ኑሮ መሐንዲስ ሲሳሳት ግን ሕይወት ይጠፋል፣ ሕዝብ ያልቃል፣ ትውልድ ይረግፋል፣ አገር ይበጠበጣል፡፡ በዓይናችን እያየነው ነው” ይላሉ፡፡
ይፋ በሆነው ጥናት እንደተገለጸው ደረጃው የወጣው በተለይ ሁለት የኢኮኖሚ መለኪያዎችን በማቆራኘት ነው፡፡ እነዚህም የአገር ውስጥ ምርት (GDP) በካፒታል የሚባለውንና የመግዛት ኃይል ንጽጽር (purchasing-power-parity (PPP) በማጣመር ነው፡፡ በቀላል አገላለጽ PPP ማለት ኅብረተሰቡ የሚጠቀምባቸውን የተወሰኑ የተለመዱ ሸቀጦችን (ለምሳሌ ዳቦ፣ እርሳስ፣ የብርቱካን ጭማቂ፣ ወዘተ) ሰብስቦ በአንድ ቅርጫት ውስጥ በማድረግ ዋጋቸውን መተመን ነው፡፡ እነዚህ በአንድ ቅርጫት ውስጥ የተካተቱት ሸቀጦች አጠቃላይ ዋጋ ኢትዮጵያ ውስጥ 50 ዶላር ቢሆን ኬኒያ ደግሞ 100 ዶላር ቢሆን በኢትዮጵያና በኬኒያ መካከል ያለው የመግዛት ኃይል ንጽጽር 1፡2 (አንድ ለሁለት) ነው ማለት ነው፡፡ ይህንን ቀመር ከአጠቃላይ የዓለም አገራት ጋር በማነጻጸር የአንድን አገር ሕዝብ የመግዛት አቅም ከመላው ዓለም አገራት ጋር ማነጻጸር ይቻላል፡፡ ጥናቱ ያደረገውም ይህንኑ ነው፡፡
በኢኮኖሚክስ ጥናት መሠረት የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒን) መለኪያዎች በርካታ ናቸው፡፡ አንዱ ምርቱን ለማምረት በወጣው የመለካት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከዋጋ ንረት ጋር በማገናዘብ የመለካት ስልት ነው፡፡ ይህ ጥናት የተጠቀመበት መለኪያ ደግሞ ጂዲፒን በካፒታል መለካት ሲሆን ይህም የአንድ አገር ገቢ በነዋሪው ሕዝብ ተካፍሎ የሚመጣው ነው፡፡ የጥናቱ አቅራቢዎች ይህንን የጂዲፒ ውጤት ከመግዛት ኃይል ንጽጽር ጋር በማካፈል ነው መረጃውን ይፋ ያደረጉት፡፡ ይህ ዓይነቱ የመግዛት ኃይል ንጽጽርን ግምት ውስጥ ያስገባ የጂዲፒ አለካክ በኅብረተሰቡ ውስጥ የሚታየውን የኑሮ ውድነት በስሌቱ ውስጥ የሚያካትት በመሆኑ ከሁሉም የጂዲፒ መለኪያዎች የተሻለ ነው የሚል አስተያየት ይሰጥበታል፡፡
economic map
Darkest red: highest GDP per capita (PPP) Medium red: medium-high GDP per capita (PPP) Light red: medium-low GDP per capita (PPP) Lightest red: lowest GDP per capita (PPP)
በእነዚህ የኢኮኖሚ ስሌቶች መሠረት የተደረገው የአምስት ዓመታት ጥናት (እኤአ 2009-2013) እንዳመለከተው በዝርዝሩ ከተካተቱት አገራት ኢትዮጵያ 171ኛ ተራ ላይ ነው የምትገኘው፡፡ ኳታር በአንደኛነት ስትገኝ ሉግዘምበርግ ሁለተኛ፣ ኖርዌይ ሦስተኛ፣ ብሩናይ አራተኛ፣ ሲንጋፖር አምስተኛ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ስድስተኛ፣ አሜሪካ ሰባተኛ፣ ሆንግ ኮንግ ስምንተኛ፣ ስዊትዘርላንድ ዘጠነኛ፣ ኔዘርላንድስ አስረኛ ተራ ላይ ሰፍረዋል፡፡ በዘገባው ላይ እንደተጠቀሰው የእነዚህ አገራት በካፒታል ላይ የተሰላው የ2013 ዓም ጂዲፒ ከመግዛት ኃይል ንጽጽር ጋር ተካፍሎ የተገኘው ውጤት በአሜሪካ ዶላር የሚከተለው ነው፡፡ ኳታር $105,091.42፣ ሉግዘምበርግ $79,593.91፣ ኖርዌይ $56,663.47፣ ብሩናይ $55,111.20፣ ሲንጋፖር $61,567.28፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ $49,883.58፣ አሜሪካ $51,248.21፣ ሆንግ ኮንግ $53,432.23፣ ስዊትዘርላንድ $46,474.95፣ ኔዘርላንድስ $42,493.49፡፡ ይህ ማለት አንድ አገር የምታመርተውን አምርታ፣ የኑሮው ውድነት ተሰልቶ እና በዚያች አገር ውስጥ ያሉት ሸቀጦች የሚያወጡት ዋጋ ከሌሎች የዓለም አገራት ጋር ተነጻጽሮ አንድ ሰው ሊኖረው የሚችለው የገንዘብ መጠን ተብሎ በግርድፉ ሊወሰድ ይችላል፡፡ (ማሳሰቢያ፡ እዚህ ላይ ለማሳያነት የ2013 ዓም ብቻ በማውጣታችን የቁጥርና የደረጃ ልዩነት ይታያል፡፡ ይህም የሆነው የአንዳንዶቹ አገራት ዘገባ የተወሰደበት ዓመት ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ባለመሆኑ ነው፡፡ ሙሉውን ዘገባ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል)
በድህነት ከሰፈሩት አገራት ተራ የምትመደበው ኢትዮጵያ (171ኛ $1,258.60) በበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቀድማለች፡፡ ሴራሊዮን 170ኛ ($1,559.95)፣ ማሊ 168ኛ ($1,136.77)፣ ጊኒ ቢሳው 166ኛ ($1,268.46)፣ ኮሞሮስ 164ኛ ($1,296.77)፣ ሩዋንዳ 162ኛ ($1,591.71)፣ ዑጋንዳ 160ኛ ($1,459.62)፣ ታንዛኒያ 159ኛ ($1,670.21)፣ ዛምቢያ 158ኛ ($1,841.64)፣ ኬኒያ 156ኛ ($1,884.57)፣ ቻድ 155ኛ ($2,061.63)፣ ሱዳን 144ኛ ($2,550.10)፣ ናይጄሪያ 141ኛ ($2,883.44)፣ ጂቡቲ 139ኛ ($2,778.25)፣ ጋና 137ኛ ($3,501.53)፡፡
ኮከቡ ያልሰመረለት ትሪሊየን ጂዲፒ በሚል ርዕስ (June 14, 2015) በታተመው ሪፖርተር ላይ ጽሁፍ ያቀረቡት የኢኮኖሚ ባለሙያ ጌታቸው አሰፋ በኢትዮጵያ ያለውን የኢኮኖሚ ሁኔታና መጪውን እንደሚከተለው ይገልጹታል፡፡
“ገንዘቡ ዋጋ ያጣው ገቢ አሁንም ቢሆን ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ቢሆንም፣ የገቢ ዕድገት ከምርታማነት ዕድገት በላይ ስለሆነ ነው፡፡ ምርታማነት የቀነሰው የመንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ዕድገት፣ የሥልጠና ዕድል፣ ሙያዊ ክህሎትን መገንባት፣ ወዘተ የሚቻለው አለቃን በማምለክ እንጂ ችሎታን አዳብሮ ውድድር ውስጥ በመግባት ስላልሆነ ነው፡፡ … ሥራ ፈጠራ በብሎኬት ምርት፣ መስኮትና በር መግጠም፣ አልባሳት፣ ቦርሳና ቀበቶን የመሳሰሉ የግል መጠቀሚያዎችን ማምረት ጀምሮ አሁን ወደ ጀበና ቡና፣ ቦርዴ (ሻሜታ) ጠመቃ፣ የዓረብ ሱቅ፣ በቆርቆሮ ግድግዳ ደሳሳ ጎጆ የሆቴል ኪዮስክ ወርዷል፡፡ ከዚህ በታች ወዴት እንደሚወርድ አይታወቅም፡፡ …
“ምርታማ ሆኖ ገንዘብ ማግኘት ካልተቻለ አጭበርብሮም፣ ቀምቶም፣ ሰርቆም፣ የሰው አካልንም ቢሆን ደልሎ ገንዘብ ለማግኘት ይሞከራል፡፡ ውድድር ሳይሆን ሽሚያ ይፈጠራል፡፡ በኢትዮጵያ እያደገ የመጣው ይህ አጉል የመስገብገብ፣ የመሻማት፣ የመሻሻጥ ባህሪይ ነው፡፡ ሁላችንም በባህሪይ፣ በአስተሳሰብና መስሎ በመታየት ደላላ እየሆን ነው፡፡ በመንግሥት ድጋፍ በሦስት ሺሕ ብር የፈጠራ ሥራ ጀምሮ በዓመቱ ሦስት ሚሊዮን ብር ካፒታል ማስመዝገብ፣ መቶ ሺሕ ብር ለደላላ ከፍሎ ወደ ሞት ለመሄድ መደራደር፣ ለጥቂት ደቂቃዎች መዝናኛ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ማውጣት፣ ቅጥ ላጣ የውጭ አገር ጉዞ የቅንጦት ወጪ ማድረግ፣ ምልክት የጥሬ ገንዘብ ከጓሮ የሚሸመጠጥ ቅጠል መምሰል ነው፡፡ …
“አምና በመቶ ሺሕ ብር መነሻ ካፒታል የከተማ ሥራ ጀምሬ ዘንድሮ ሦስት ሚሊዮን ብር ካፒታል አለኝ፣ በግማሽ ሔክታር መሬት የግብርና ሥራ አሥር ሚሊዮን ብር ካፒታል አለኝ፣ የሬድዮና የቴሌቪዥን ፕሮፓጋንዳ የወጣቱን ሥነ ልቦና ሰለበ፡፡ የሥራ ባህል ጠፋ፡፡ ገንዘብ ተሠርቶ የሚገኝ ሳይሆን ከሜዳ የሚታፈስ ወይም ጓሮ ከበቀለ ዛፍ የሚሸመጠጥ መሰለ፡፡ መቶ ሺሕ በትኖ ሚሊዮን ለማፈስ የተሰናዳ ትውልድ ተፈጠረ፡፡ ከሠርቶ በሌው አውርቶ በሌውና ዘሎ በሌው በዛ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ትምህርትን አቋርጦ ጊታር ማንሳት ተለመደ፡፡ …
“የጋራ በሆነ መሬት ላይ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ መሥራት የሚቻለው በጋራ ብቻ ነው፡፡ የጋራ የሆነም የግል አይደለም፡፡ የግል ያልሆነም ገበያ አይወጣም፡፡ ገበያ ያልወጣም የገበያ ዋጋ የለውም፡፡ የገበያ ዋጋ የሌለውም በገበያ ዋጋ በገንዘብ አይተመንም፡፡ ስለዚህም በሪፖርት ከምናየውና ከሚነገረን የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) መጠን ገሚሱ የገበያ ዋጋ የሌለው ምናባዊ ስሌት ነው፡፡ የኑሮ መሐንዲሱ ኢኮኖሚያዊ ኑሮን ወደ ምናባዊ ሥሌት ከወሰደው የሕዝብ ገቢ መጠንና ኑሮም በገበያ ተለክቶ እውነቱ የሚታወቅ ሳይሆን ምናባዊ ይሆናል፡፡ አመለካከቱና አስተሳሰቡም የኑሮው ነፀብራቅ ነውና ኑሮውን ተከትሎ ምናባዊ ይሆናል፡፡ ሲያገኝም ሲያወጣም በምናባዊ ሥሌት ነው፡፡ ሳይበላ የበላ መስሎ፣ ሳይጠጣ የጠጣ መስሎ፣ ሳይደላው የደላው መስሎ፣ ያላመነውን ያመነ መስሎ፣ ያልተቀበለውን የተቀበለ መስሎ፣ የናቀውን ያከበረ መስሎ፣ የጠላውን የወደደ መስሎ በመታየት በምናባዊ ዓለም ውስጥ ይኖራል፡፡…poor
“ሕዝቡ ከምናባዊ ዓለም ወጥቶ ገሃዱን ዓለም እንዲቀላቀል የኑሮ መሐንዲሱ ኢኮኖሚስት አለ ብሎ በወረቀት ላይ የሚጽፈውን የምርት መጠን ለሽያጭ ወደ ገበያ አውጥቶ፣ በበያ ዋጋ አስተምኖ እውነተኛውን በገበያ ዋጋ የተለካ የምርት መጠን ያሳየን፡፡ ያለበለዚያም የገንዘብ አቅርቦቱ ለገበያ በቀረበው ምርት መጠን ልክ ሆኖ በዋጋ ግሽበት ስቃይ እንዳን፡፡ እኔ እንኳ በሩቁ ከማውቀው ወደ ገበያ ከማይቀርቡና ማገበያያ ገንዘብ ከማያስፈልጋቸው ምርቶች ውስጥ ከጠቅላላ ጂዲፒው አንድ ሦስተኛው የሚሆነው፣ ገበሬው ከራሱ እንደገዛ ተቆጥሮ በምናባዊ ሥሌት በገንዘብ የሚለካው የግብርና ምርት ይገኝበታል፡፡ በወረቀት ላይ የሚመለከቱ የአገር ውስጥ ምርት መጠን ቁጥርና ለፕሮፓጋንዳ የሚያገለግሉ ጥንስስ ፕሮጀክቶች ስም ጋጋታ ሳይሆን፣ የአጠቃላዩ ሕዝብ ምርታማነት ብቻ የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ወሳኝ ነው፡፡…
“አንጀት ላይ ጠብ የሚለው ሺዎች ለሚሊዮኖች አስበውና ተደራጅተው ሲሠሩ ሳይሆን፣ የአጠቃላዩ ሕዝብ ሚሊዮኖች ለራሳቸው አስበው በገበያ ውስጥ ተወዳድረው እንዲሠሩ የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ሁኔታዎች ሲመቻችላቸው ነው፡፡ ‹‹ጧት ጧት ዳቦአችንን ጠረጴዛችን ላይ የምናገኘው በዳቦ ጋጋሪው የፅድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ለራሱ ገንዘብ ለማግኘት ሲል በሚሠራው ሥራ ነው›› አዳም ስሚዝ፡- ነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ሥርዓት ጠንሳሽ፡፡ ‹‹ልማት ማለት አንድ ሰው ሊሆንና ሊያደርግ የሚፈልገውን ሕጋዊ ነገሮች የመሆንና የማድረግ ነፃነትና አቅም ሲያገኝ ነው›› አማርተያ ሴን፡- በ1998 በልማት ኢኮኖሚክስ የኖቤል ተሸላሚ፡፡”
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በፋይናንስ መጽሔት ላይ ያወጣውን ይህንን መረጃ የተመለከቱ በኢትዮጵያ የግል ትምህርት ተቋም የኢኮኖሚክስ ባለሙያ የሆኑ ለጎልጉል እንዳሉት የዴሞክራሲን መንገድ የተከተለችው ጋና ከሌሎቹ የሰሃራ በታች አገራት በከፍተኛ ፍጥነት የማደጓ ምክንያት ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደሚጠቀስ ጠቁመዋል፡፡ የዕድገቷ መጠንም ዘገባው በተጠናቀረበት ባለፉት አምስት ውስጥ ያልተዛባ ነገር ግን ሥርዓት ያለው ዕድገት እያሳየች መሆኗን ጨምረው ተናግረዋል፡፡ አክለውም ሲናገሩ “አንድ የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ያልሆነ ሰው ይህንን ዘገባ በመመልከትና የኢትዮጵያን ደረጃ ከሌሎቹ የአፍሪካ አገራት ጋር በማነጻጸር ብቻ ለምን ኢትዮጵያውያን ለተሻለ ኑሮ ወደሌሎች አገራት እንደሚኮበልሉ መናገር ይችላል፤ የአገራችን ሕዝብ ያለው አቅም እጅግ የወደቀ በመሆኑ በአቅም ከምትበልጠን ጂቡቲ መሰደድ እንደ አማራጭ ሊወሰድ ይችላል” ብለዋል፡፡ በመጨረሻም “እንደ ባለሙያ ለመንግሥት አካላት የኢኮኖሚውን ጉዳይ ስናስረዳ የሚሰማን የለም፤ ከዚያ ይልቅ እንደ ካድሬ ፕሮፓጋንዳ እንድንናገር፣ ኢኮኖሚው በድርብ አኃዝ እንዳደገ እንድንደሰኩር፣ ወዘተ ነው የሚፈለግብን፡፡ ሃቁ ግን ይኸው በገሃድ የሚታይ ነው፤ የአንድ አገር ዕድገት በበርካታ የኢኮኖሚ መመዘኛዎች በሳይንሳዊ መንገድ የሚለካ ነው እንጂ በዘጋቢ ፊልም በታጀበ የመንገድ ሥራና የፎቅ ብዛት ጨርሶውኑ ሊሆን አይችልም፤ ምናልባትም ካልተሳሳትኩ በዓለም ላይ ኢኮኖሚዋን በመንገድ ሥራና በፎቅ ብዛት የምትለካ አገር ኢህአዴግየሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አትቀርም” ብለዋል፡፡ethio poor
የኢኮኖሚ ባለሙያው ጌታቸው አሰፋ ሪፖርተር ላይ ያወጡትን ጽሁፍ ሲያጠናቅቁ እንዲህ ይላሉ፤ “የአገር ውስጥ ምርት በግሳንግስ ምርቶች ማበጡ የምርታማነት ማደግ አይደለም፡፡ ያበጠ ነገርም ይፈርጣል፡፡ ኢኮኖሚ ሲፈርጥ ደግሞ ማኅበራዊ ቀውስ ያመጣል፡፡ ‹ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል› ተረት እንዳይተረትብን፡፡ የብሔራዊ ገቢ ሒሳብ ባለሙያው በተቀመጠለት የማዕከላዊ ዕቅድ የጊዜ ገደብ አገሪቱን በእጁም በእግሩም ገፍቶ መካከለኛ ገቢ ደረጃ ለማድረስ አስቦ፣ በነፃና በጋራ የሚሠራውን የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ በምናባዊ ሒሳብ የአገር ውስጥ ምርት ሥሌት ውስጥ አካቶ ሊሆንም ይችላል ምርቱን ያሳበጠው፡፡ ኢኮኖሚ ከቁጥር ሌላ ሥነ ልቦናዊ ጉዳይም ነው፡፡ የኑሮ ጉዳይም ነው፡፡ የጉሮሮ ጉዳይም ነው፡፡ በቁጥር ብቻ አይለካም፡፡ እንደ ዶሚኖ ጨዋታ ቁጥር በመገጣጠም ብቻም የሚገነባ አይደለም፡፡ የሕንፃ መሐንዲስ ቢሳሳት ሕንፃ ይደረመሳል፡፡ የሰው ኑሮ መሐንዲስ ሲሳሳት ግን ሕይወት ይጠፋል፣ ሕዝብ ያልቃል፣ ትውልድ ይረግፋል፣ አገር ይበጠበጣል፡፡ በዓይናችን እያየነው ነው፡፡”
ይህንን ዓለምአቀፍ የደረጃ ዘገባ በመመርኮዝ እኤአ እስከ 2020 ድረስ ይህ የደረጃ ስሌት እምብዛም ለውጥ ሳያሳይ እንደሚቀጥል በርካታ ትንበያዎች አሉ፡፡ በሌሎች ደግሞ ምናልባትም በዝቅተኛው ተራ ላይ የሚገኙት አገራት እጅግ እየደኸዩ በሃብታምና በደሃ መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ ለከፍተኛ የማኅበራዊ ቀውስ እየተጋለጡ ይሄዳሉ የሚል ሙያዊ ስሌትም ይሰጣል፡፡ (ፎቶ: ከኢንተርኔት የተገኙ በጎልጉል የተገጣጠሙ)
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Thursday, July 16, 2015

አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጠ (የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ይዘናል)

July 16,2015
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
andargachew new picture
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር በአካል ተገናኝታችኋል›› የሚል ክስ የመሰረተባቸው ተከሳሾቹ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝታችኋል ከተባለ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ታስረው የሚገኙ በመሆናቸው መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ይታዘዝልን›› የሚል ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
የፌደራል አቃቤ ህግ በበኩሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ አይችሉም ብሎ ተቃውሟል፡፡ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህዝባዊ መብት በመሻሩ ለፍርድ ስራ ልዩ አዋቂ ወይንም ነባሪ ሆነው መስራት አይችሉም ያለው የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በተጨማሪ ምስክርነት ቀርበው መመስከር አይገባቸውም ሲል የተከሳሾቹ ጥያቄ ውድቅ እንዲሆን ለፍርድ ቤቱ አመልክቶ ነበር፡፡
ሆኖም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር ለምስክርነት በመሆኑ፣ ምስክርነትም ግዴታ እንጅ መብት በመሆኑ ሰኞ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ለተከሰሱት ተከሳሾች ልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲመሰክሩ ወስኗል፡፡ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው የት እንደሚገኙና ማዘዢያው የት ተብሎ ሊፃፍላቸው እንደሚገባ ተጠይቀው ለቃሊቲ ማረሚያ ወይንም ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ሊጻፍላቸው እንደሚገባ፣ ካልቀረቡላቸውም ክሳቸው ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር የተገናኘ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ አቤቱታ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡


ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡላቸው በጠየቁበት ወቅት በዳኞችና በአቃቤ ህጎች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ መፈጠሩንና ከአቶ አንዳርጋቸው ይልቅ ሌሎች መከላከያ ምስክሮችን ማቅረብ እንደሚችሉ፣ አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት ለማቅረብ መሞከር እንደሌለባቸው እንደገለፁላቸው ታውቋል፡፡ ዳኛው በድንጋጤ ‹‹እኛ እዚህ ጉዳይ ላይ የለንበትም›› ማለታቸውን ተከሳሾቹ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ውስጥ ላነጋገራቸው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ገልጸውለታል፡፡
andargachew