Saturday, January 31, 2015

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

January 31,2015
የገዢውን ፓርቲና መንግስትን ሽፍትነት ያጋለጠው አንድነትን የማፍረስ የምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኢትዮጵያዊን ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም!!!
ጥር 21/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ የምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም ያለበትን ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በዚህ ደረጃ እንዲዋራድ ከጀርባ ሆኖ አመራር የሚሰጠው ገዢ ፓርቲም ሆነ መንግሰት በዚያው ልክ የሚገባቸውን የተዋረደ ደረጃ የያዙበት ዕለት ነው ብለን እናምናለን፡፡ አንድነት ፓርቲ አንድም የህግ ጥሰት ሳይፈፅም የሚያደርጋቸውን ሁሉ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በሀገሪቱ ህግ እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ በህግ ሽፋን የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና ሬዲዮ፣ የመንግሰት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር የከፈቱት ዘመቻ የመጨረሻ የሆነውን አንድም ህጋዊ መሰረት የሌለውን ህገወጥ ውሳኔ በአንድነት ፓርቲ እና አባላት ላይ አሰተላልፈዋል፡፡
ገዢው ፓርቲና መንግሰት በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲነበብ ያደረጉት የፖለቲካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከወረቀት አልፎ በተግባር እንዳይታይ ግብዓት መሬቱን ፈፅመዋል፡፡ በዚህ ፀያፍ ተግባር ከፊትም ሆነ ከጀርባ ሆነው የተሳተፉ ግለሰቦችም ሆኖ ተቋማት በታሪክ ተገቢው የውርደት ቦታ እንደሚይዙ እምነታችን ነው፡፡ ይህ ህገወጥ አካሄድ ህጋዊ መሰመር እንዲከተል የበኩላቸሁን ድርሻ የተወጣችሁ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በሀገር ውሰጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ሁሉ በተለይ በገዢው ፓርቲ እኩይ ሴራ በሀስት ተወንጅላችሁ በወህኒ ቤት ለምትማቅቁ ታጋዮች ታሪካችሁ በወርቅ ቀለም ተፅፎዋል፡፡ በቀጣይም ያለምንም መዘናጋት እና ተሰፋ መቁረጥ በምናደርገው ሰላማዊ ትግል በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት ትንሳኤ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለንም፡፡
የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በህገወጥ መንገድ ለሆዳቸው ባደሩ ጥቂት አንድነት ፓርቲ አባላት እና በአንድነት አባልነት በማይታወቁ የገዢው ፓርቲ ጥርቅሞች ለተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ  ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት ያነገብነው የነፃነት መንፈስ በምርጫ ቦርድ በሚሰጥ ሰርተፊኬትና ዕውቅና ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኝ ስለአልሆነ ለነፃነት የምናደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የምንቀጥል ሲሆን፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የአንድነት መዋቅሮች እና የአንድነት አባላት ለዚህ ህገወጥ ቡድን በግልፅ እውቅና እንዲነሱ እንጠይቃለን፡፡
ፓርቲያችን በመጨረሻ ሰዓት እንኳን ተፈትነው ለወደቁ ተቋማት እድል ለመስጠት ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ወሰኖ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ ቢሆንም፤ በዛሬው ዕለት ጥር 22/ 2007 ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የፓርቲያቸን ፅ/ቤት በፖሊስ ተወሮ የፓርቲው ንብረት ያለምን ህጋው ርክክብ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎዋል፡፡ በአሰተዳደር የተሰጠን ውሳኔ በፍርድ ቤት የማሰለወጥ ህጋዊ ሰርዓት እንዳለ ቢታወቅም ህገወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔን በፖሊስ ወረራ ለማሰፈፀም የተሄደበት መስመር ገዢው ፓርቲና መንግሰት አሁንም ከጫካ አሰተሳሰብ ያለመውጣቸውን እና የአውራ ፓርቲ ፍልስፍናቸውን በማናለብኝነት ለመተግበር መቁረጣቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂው ትእዛዙን ያስተላለፈው ክፍል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡
ሰለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች፣ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት እንዲጎለብት ፍላጎት ያለችሁ ሁሉ ይህን እኩይ ተግባር በማውገዝ ተጨባጭ እርምጃ እንድትወሰዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!!!
ጥር 22/ 2007 ዓ.ም
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)                                                      
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
UDJ




ደላሎች ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳያከራዩ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

January 31, 2015
‹‹ለአሸባሪ ፓርቲ ቢሮ ብታከራዩ ተጠያቂነቱን ትወስዳላችሁ›› የቂ/ክ/ከ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ
የቤት ደላሎች ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳያከራዩ ከቀበሌ ባለስልጣናት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ተደራጅተው በመስራት ላይ የሚገኙት ደላሎች የቂ/ክ/ከ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ከበደ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ አሸባሪ ፓርቲ ነው፡፡ ለአሸባሪ ፓርቲ ቢሮ ብታከራዩ ተጠያቂነቱን ራሳችሁ ትወስዳላችሁ›› ብለው ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደሰጧቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ለማከራየት ተስማምተው የነበሩ አንድ ግለሰብ በቀበሌ ካድሬዎች ትዕዛዝ ቤቱን እንዳያከራዩ ተደርገዋል፡፡ ማስጠንቀቂያ የደረሳቸው ደላሎች ግለሰቧን ‹‹መጀመሪያ ቀበሌ ሄደሽ ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ልታከራይ መሆኑን አሳውቂ›› ብለው በመከሯቸው መሰረት ቀበሌ ሄደው ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ላከራይ ነበር፡፡ ምን ችግር ይኖረዋል?›› ብለው ሲጠይቁ የቀበሌ ካድሬዎች ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ህገ ወጥና አሸባሪ ፓርቲ ነው፡፡ ለእሱ ቢሮ ማከራየት በህግ ያስጠይቅሻል›› ብለው ስላስፈራሯቸው ለማራየት ሳይደፍሩ ቀርተዋል፡፡
የየካ ክፍለ ከተማና የቂርቆስ ክፍለ ከተማ በጋራ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳይከራይ ደላሎቹና አከራዮችን እያስጠነቀቁ ሲሆን ሰማያዊ ፓርቲ ካሳንቺስ የሚገኘው ጽ/ቤቱን እንዲለቅ በቤቱ ባለቤቶች ላይ ከፍተኛ ግፊት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ አከራዮቹ በቀበሌ ባለስልጣናትና በደህንነቶች በደረሰባቸው ጫና ምክንያት ፓርቲው ቤታቸውን እንዲለቅላቸው፣ ካልለቀቀም አሁን ከሚከፍለው 3 እጥፍ ገንዘብ እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል፡፡

አንድነት ታገደ፣ ጽ/ቤቱ ተወረረ ፣ ከዚህ በኋላስ

January 31,2015
ግርማ ካሳ
Girma Kassa's photo.
ይህ ሳምንታ በጣም አሳዛኝ ሳምንት !!!! በዚህ ምርጫ አንጻራዊ መረጋጋትና ብሄራዊ መግባባት መጥቶ ፣ የጋራ የልማት ኮሚሽን ተቋቁሞ በጋራ አባይን እንገነባላን፣ የባቡር መስመሮችን እንዘረጋለን፣ አገራችንን ከዉጭ ኃይሎች ከቻይናዎች ከመሳሰሉ ጥገኝነት እናወጣለን የሚል ተስፋ ነበረኝ።
ሆኖም በዚህ ሳምንት በኃይል፣ በጭካኔ የዚህን ፓርቲ ሕጋዊነት ሕወሃቶች ጨፍልቀዋል። በሐሳብ ማሸነፍ ሲያቅታቸው የኃይልና የጡንቻ እርምጃ ወስደዋል። በጠራራ ጸሃይና በአደባባይ ወንበዴዎችን ሽፎቶች መሆናቸውን አሳይተዋል። የ2007 ምርጫ በደምና በጭካኔ፣ ከመደረጉ ከአራት ወራት በፊት ተጠናቋል።
ፖለቲካዉን ከተቀላቀልኩ ከዘጠና ሰባት ጀምሮ በሰላም ለዉጥ ይመጣል ብዬ ስከራከር እንደነበረ ይታወቃል። ስለሰላማዊ ትግል ብዙ ጽፊያለሁ። አሁንም በሰላማዊ ትግል አምናለሁ። ወደ ጦርነት የሚሉ ወገኖቼ ስሜት ብረዳም፣ ዉሳኔያቸውን ባከብረም፣ የጦርነትን አስከፊነት ከግምት በማስገባት፣ አሁን የሰላማዊ ትግሉን ብቻ ነው የምደገፈው። (ይሄን ስል የትጥቅ ትግል እቃወማለሁ ማለት አይደለም። አለመቃወምና መደገፍ የተለያዩ ነገሮች ናቸው)
የሰላማዊ ትግልን እደግፋለሁ ስል፣ ህጋዊ የሰላማዊ ትግልን ማለቴ አይደለም። ሕጋዊ የሰላማዊ ትግል ከአሁን በኋላ በኢትዮጵያ ሞቷል። ተቀብሯል። የምርጫ ፓርቲ የሚባል ነገር ከአሁን በኋላ የለም። እርግጥ ነው እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ያሉ አሉ። እነርሱም ቢሆኑ በዚህ ሁኔት ይቀጥላሉ ብዬ አላስብም። ምናልባትም በአደባባይ የምርጫ ካርዶቻቸውን ቀዳደው ሊያቃጥሉም ይችላሉ። ምርጫዉን ከተሳተፉ የሚያመጡት ለውጥም አይኖርም። ለምን አንድ አስጊ ደረጃ ሲደርሱ በጉልበት መጨፍለቃቸው አይቀሬ ነው።
ትንሽ ላብራራ። ሕጋዊ ስል አገዛዙ ያወጣዉን ሕግ በመከተል የሚደረግ ትግልን ማለቴ ነው። በፈለጉ ጊዜ ሕጋዊነትን ሕግ ወጥ በሆነ መልኩ የሚረግጡ ከሆነ፣ ሕግን ተጠቅመው ዜጎችን የሚያፍኑ ከሆነ፣ እንዴት ተደርጎ ነው ሕጋዊ ትግል የሚደረገው ?
ለሕወሃት ሕግ አልገዛም የሚል የእምቢተንኘት ሰላማዊ ዘመቻና ትግል ነው የሚቀጥለው ምእራፍ። ሰላማዊ፣ የእምቢትኝነት ዘምቻ ስል፣ ጠመንጃ ከማንሳት ዉጭ የሚደረጉ ተግብራት ሁሉ ያጠቃልላል። ሕወሃትን ስናከብረው፣ እርሱ ባወጣው ሕግ ተገዝተን ስንቀሳቀስ፣ የሚጨፈልቀን ከሆነ፣ ታዲያ መብታችንን በራሳችን መንገድ ለምን አናስከበርም ?
ይህ አይነቱ ትግል አንደኛ ጥንቃቄ ይጠይቃል። ሁለተኛ ራስን አጋልጦ መሆን የለበትም። ሶስተኛ የምናደርገውን አስቀድመን እየነገርንና ወያኔዎች እንዲጠነቀቁ እያደረግን አይደለም። አራተኛ ዲሴንትራላይዝ መሆን አለበት። አምስተኛ ዲሲፕሊን እና ተጠያቂነት መኖር አለበት። በስሜት፣ ባልተጠና መልኩ አንድ ነገር አድርገን ብዙ ሰው እንዲጎዳ ማድረግ የለብንም። አንርሳ ለሕዝብ የሚያስብ "ኢትዮጵያው ነኝ" ቢልም ኢትዮጵያው ያልሆነ፣ ከግራዚያኒ የማይተናነስ አገዛዝ ነው ያለን። ስለዚህ በምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ለዜጎቻችን መጠንቀቅ አለብን።ስድስተኛ የምናደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች ከተደረጉ በኋላ ለሕዝብ እናሳወቅ። ሰባተኛ ገዢውን ፓርቲ ፍሊትሬት እናድረግና ሚስጥራቸውን እናወጣ። ስምንተኛ ሜዲያ በጣም አስፈላጊ ነው። በዚህ ረገድ እንደ ኢሳት ያሉ ትልቅ ሚና ሊጫወቱ ይገባል። ይጫወታሉምም።
አንድ ነገር ግን ግልጽ ላደርግ። ሕወሃት ይወድቃል። ይሄን እርግጠኛ እንሁን። በዚህ ሳምንት የወሰኑት ዉሳኔ እንደዉም የበለጠ እንድቆርጥና እንድንጨክን ነው ያደረጉን። አሁን አንዱን በር በኃይል ቢዘጉብንም፣ ሌሎች በሮች አሉ። ይህ ስርዓት ከሕዝቡ ጋር የተጣላ ስርዓት ነው። የበሰበሰ ስርዓት ነው።
ዉድ በገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ያላችሁ ወገኖቼ፡
ነጻነት ከሰማይ አይመጣም። ነጻነትን የምናመጠው እኛው ራሳችን ነን። ሕጋዊ ሆነው የሚንቀሳቀሱ የምርጫ ፓርቲዎች ፣ እግዚአብሄር ይባርካቸዉና፣ ተደብድበው፣ ታስረው ትልቅ ዋጋ ከፍለው መድረስ የሚችሉበት ጫፍ ላይ ደርሰዋል። ሕጋዊነታቸው ይኸው ተነጥቀዋል። ከአሁን በኋላ ተራው የእያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊያን ነው። በራሳችን ተደራጅተን፣ የምንቀሳቀስበት ሰዓት ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት ወደፊት እመለስበታለሁ።

Friday, January 30, 2015

አንድነትን “እናኝከዋለን፤ እንገድለዋለን” – ምርጫ ቦርድ

January 30,2015
ትዕግስቱ አወሉ እንደ አየለ ጫሚሶ
tplfs election board

የዛሬ አስር ዓመት “የሕዝብ ሱናሚ” እያለ ሲምል ሲገዘት የነበረው ህወሃት ሱናሚው ወደ እርሱ እየጎረፈ ሲመጣ በረገገ፡፡ መፍትሔ በጠብመንጃ አፈሙዝና በብረት ብቻ እንደሆነ የሚያምነው ህወሃት በረሃ የለመደውን በትሩን አነሳ፤ ንጹሃንን ጨፈጨፈ፤ ደም አፈሰሰ፤ ኢትዮጵያን ወደ እስርቤትነት ቀየራት፡፡ ትዕዛዙን በቀጥታ የሰጡት “ባለራዕዩ” ለፍርድ ሳይቀርቡ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” ያሉትን ሰፊውን ሕዝብ ሳይጨርሱት እንደ ክዳን ቆርኪ ተስፈነጠሩት፤ ላይመለሱ ሄዱ፡፡
የዛሬ አስር ዓመት የቅንጅት አካሄድ ያስፈራው ህወሃት ጉዳዩን ለራሱ ለፓርቲውና ለሕዝብ ከመስጠት ይልቅ ደም መቃባት ውስጥ ገባ፡፡ ፓርቲው የነበረበት የውስጥ ችግር እንዳለ ሆኖ የፈሪ በትር የዘረጋው ህወሃት የገደለውን ገድሎ ከጨረሰ እና የኢትዮጵያን መሬት በደምና በእናቶች እምባ እንደገና ካጨቀየ በኋላ ቅንጅትን የማፍረስ ተግባሩን በዕቅድ ይዞ በይፋ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ግምባር ቀደም ተሰላፊው የተቋም ባንዳ “ምርጫ ቦርድን”፤ በግለሰብ ደረጃ ደግሞ በተለይ ሁለት ግለሰቦችን አሰለፈ፡፡ ዘመቻ “ቅንጅትን መግደል” ተጀመረ፡፡
በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ምንም በማያሻማ ሁኔታ በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ዶናልድ ያማሞቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (ስቴት ዲፓርትመንት) ለሚገኙት አለቆቻቸው THE ETHIOPIAN GOVERNMENT CHEWS THE CUD” (የኢትዮጵያ መንግሥት ቅንጅትን አኘከው) በሚል ርዕስ የጻፉት እንዲህ ይነበባል፤
Over the course of the week of January 7, the National Electoral Board of Ethiopia (NEB) hammered what appear to be the final nails in the coffin of the opposition Coalition for Unity and Democracy (CUD) party. Since their surprise showing in the 2005 elections, gaining enough seats to become the second largest political party in Ethiopia, the CUD has virtually disintegrated as a result of internal power struggles and interference from the Ethiopian Government (GoE). In the latest setback, the NEB awarded the famous victory sign — the CUD symbol widely recognized by voters — to former ally turned foe, Lidetu Ayalew of the United Ethiopian Democratic Party-Medhin (UEDP-Medhin).  The NEB followed this later in the week by finally awarding registration of the reformed Coalition for Unity and Democracy Party (CUDP) party name to yet another former CUD ally turned foe Addis Ababa city council member-elect Ayele Chamisso.  Though Ayele, who is broadly viewed as having been co-opt by the GoE, has invited all faction of the former CUD to join his party, few will likely take his offer.
In a meeting with Ambassador on January 11, NEB board chairman Dr. Merga Bekana and vice-chairman Dr. Addisu Gebre-Egziabhier said that the Board still had not decided on the CUDP’s registration and would continue to consider the matter in coming weeks. Almost immediately following the meeting, however, the NEB publicly announced that it had decided that morning to award the party license to Ayele. This followed their controversial decision earlier in the week to give the CUD’s famous victory symbol to the CUD’s despised adversary Lidetu Ayalew (another person believed to have been co-opted by the GoE during the CUD’s post-2005 election struggles), and his UEDP-Medhin party.
The opposition fiercely accused the NEB of being under the influence of the GoE and of delivering votes to the ruling Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Forces (EPRDF) party after the opposition’s surprisingly strong showing. Since then, a new Board has been put in place, but the opposition have not altered their criticism. The NEB’s recent decisions to award the CUD party symbol and name to politicians, who are at best undeserved and at worst proxies of the GoE, has done much to reignite lingering suspicions regarding the NEB’s independence. As if to prove these suspicions, NEB vice-chairman Dr. Addisu (a Tigrayan political scientist widely believed to be the “enforcer” at the NEB) recently commented to USAID’s Senior Democracy Advisor — a former Stanford University Political Science Professor ) (strictly protect) that the NEB had decided to “kill the CUD.” The NEB decisions of the last week have effectively done exactly that.
በጃኑዋሪ 7 ሳምንት ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ (ቅንጅት) ፓርቲ የሬሣ ሳጥን ላይ የመጨረሻ የሚባለውን ሚስማር መትቷል፡፡ በ2005 (1997) ምርጫ በአገሪቱ ሁለተኛው ትልቁ የተቃዋሚ ፓርቲ ለመሆን የሚያስችለውን አስደናቂ ድልና በቂ መቀመጫ ካገኘ በኋላ ቅንጅት በውስጡ በነበረው የኃይል (የሥልጣን) ሽኩቻና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይደርስበት በነበረው ጣልቃ ገብነት ምክንያት አለሁ ቢልም እየተፈረካከሰ ነበር፡፡ በቅርቡ በተደቀነበት ሌላ ደንቃራ ደግሞ ምርጫ ቦርድ ዝነኛውንና በብዙሃን መራጭ ዘንድ ዕውቅና የነበረውን የቅንጅትን (V) ምልክት ቀድሞ (የቅንጅት) ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ፓርቲ – ኢዴፓ-መድህን ልደቱ አያሌው ሸልሞታል፡፡ በመቀጠልም ምርጫ ቦርድ ይህንን ተከትሎ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የስም ምዝገባ ቀድሞ የቅንጅት ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የአዲስ አበባ ምክርቤት እጩ ተመራጭ አየለ ጫሚሶ ሸልሞታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ቅጥረኛ እንደሆነ በሰፊው የሚታመነው አየለ ጫሚሶ ከቀድሞው ቅንጅት ተሸራርፈው ለወጡት ሁሉ የእርሱን ፓርቲ እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቢደርግም ጥቂቶች ብቻ ጥሪውን ይቀበላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ . . .
addisu  g of neb
አዲሱ ገብረእግዚአብሔር
የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔርከአምባሳደሩ (ያማሞቶ) ጋር ጃኑዋሪ 11 ቀን ባደረጉት ስብሰባ የቅንጅትን ምዝገባ በተመለከተ ገና ውሳኔ ላይ እንዳልደረሱ እና በመጪዎቹ ሳምንታት ጉዳዩን እንደሚመለከቱት ነበር የተናገሩት፡፡ ነገር ግን ወዲያውኑ ስብሰባው እንዳበቃ ማለት ይቻላል የዚያኑ ቀን ጠዋት የቅንጅትን የስም ምዝገባ ለአየለ ለመስጠት መወሰኑን ምርጫ ቦርድ ለሕዝብ ይፋ አደረገ፡፡ ይህ የቦርዱ ውሳኔ በሳምንቱ መጀመሪያ አካባቢ የቅንጅትን ዝነኛ (V) ምልክት በቅንጅቶች ለተናቀውና የፓርቲው ጠላት ለሆነው ልደቱ አያሌውና ለኢዴፓ-መድህን ፓርቲው ለመሸለም የተደረገውን አከራካሪ ውሳኔ ተከትሎ ነው፡፡ (ልደቱ አያሌው ከምርጫ 1997 በኋላ ቅንጅት ውስጥ በነበረው ትግል ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥት የተመደበ ሌላው ቅጥረኛ እንደሆነ ይታመናል)፡፡ . . .
ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ መንግሥት ሥር እንደሆነ እና ተቃዋሚዎች አስገራሚ ውጤት በምርጫው ላይ ካሳዩ በኋላ (የመራጮችን) ድምጽ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢህአዴግ) እንዳስረከበ ተቃዋሚ (ፓርቲዎች) አጥብቀው ይከስሳሉ፡፡ ከዚያ ወዲህ አዲስ ቦርድ የተሰየመ ቢሆንም ተቃዋሚዎች ግን አሁንም ትችታቸውን አላቆሙም፡፡ የቅንጅትን ስም እና ምልክት ፍጹም ለማይገባቸውና ለኢትዮጵያ መንግሥት የቅርብ ወዳጆች ለሆኑት ፖለቲከኞች ማስረከቡ ምርጫ ቦርድ ከአድልዎ የነጻ አለመሆኑ ላይ ያሉትን ጥርጣሬዎች እንደገና እንዲቀጣጠል አድርጓል፡፡ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር አዲሱ በቅርቡ ለዩኤስኤይድ ከፍተኛ የዴሞክራሲ አማካሪና የቀድሞ የስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር (ስሙ እንዳይወጣ በጥብቅ የተከለከለ) ምርጫ ቦርድ “ቅንጅትን ለመግደል” ወስኖ እንደነበር መናገሩ እነዚህን ጥርጣሬዎች እርግጠኛ ያደርጋቸዋል፡፡ (የአዲግራት ተወላጅ የሆነው) (ዶ/ር አዲሱ የትግሬ የፖለቲካ ሳይቲስት ሲሆን የምርጫ ቦርድ “ፈጣሪና አድራጊ” እንደሆነ በሰፊው ይታመናል)፡፡ ባለፈው ሳምንት ምርጫ ቦርድ የወሰደው ውሳኔ (የቅንጅትን ስምና ምልክት ለቅጥረኞቹ መስጠቱ) ይህንኑ (ቅንጅትን የመግደሉን ዕቅድ) የሚያረጋግጥ ነው፡፡ . . . (ሹልክዓምድ (ዊኪሊክስ) ላይ የወጣውን ሙሉ መረጃ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
አሁንስ ማነው ባለሳምንት? በዚህኛው የምርጫ ድራማ አየለ ጫሚሶን የሚጫወተው ትዕግስቱ አወል እንደሆነ ይፋ ሆኗል፤ ልደቱንስ ማን ይተውነዋል?
ከዚህ በፊት በሰማያዊና በሌሎች ፓርቲዎች ላይ የደረሰውና አሁንም እየደረሰ ያለው እንዲሁም ሰሞኑን በአንድነት ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ላይ የደረሰው ሰቆቃ የዘንድሮውን ሁኔታ የተለየ እያደረገው እንደሆነ ጎልጉል ከተለያዩ ምንጮች የሚደርሱት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ስለዚህም ነው “ምርጫ ቦርድ” ቅንጅትን በዕቅድ እንደገደለው አሁንም አንድነትንና ሌሎቹን ተቀናቃኞች “አኝኮ ለመግደል” ውሳኔው የሆነው፡፡
ከሕዝብ በኩል የሚሰማው የሰላማዊ ትግል ቁርጠኝነት ግን የህወሃትን የልመና ኮሮጆ በሚሞሉት ምዕራባውያንም ዘንድ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው እንደሆነ ጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ሰልፍ በተካሄደበት ወቅት በተለያዩ የማኅበራዊ ገጾች ላይ ተሰራጭቶ ያገኘነውን መረጃ መጥቀሱ የቁርጠኝነቱን መጠን በተወሰነ መልኩ የሚያመለክት ነው፡፡ “በዕለቱ የደረሰበትን ጉዳት አስመልክቶ ለቢቢኤን ሬዲዮ የተናገረው የአዲስ አበባ ወጣቶች ጉዳይ አንድነት ፓርቲ ኃላፊ ስንታየሁ ቁስሉ ሳይደርቅ በወኔ እንዲህ ነበር ያለው “ወያኔ ላጠፋው ጥፋት የሚያወራርደው ሒሳብ እንዳለ ማወቅ አለበት፡፡ ለትግላችን እንሰዋለን፤ በዋዛ አንላቀቅም”፡፡

Boycotting Ethiopian National Elections: Damn if You Do, Damn if You Don’t!

January 30, 2015
by Messay Kebede
I maintain that the upcoming elections will be a turning point for Ethiopia, not because they will result in a major change of policy subsequent to a renovation of the ruling elite but because the absence of change will compel opposition groups to reassess their strategies and the country as a whole will plunge further into the abyss of despair. While most reasonable people and opposition parties never contemplated the possibility of wining the elections and becoming the new ruling majority, nevertheless the expectation was—since the death of Meles Zenawi—for some opening, however narrow, to accommodate opposition groups. In light of the prevailing heightened repression and disqualification of some opposition parties from the competition by concocting bogus charges, the expectation proved utterly naïve. It is now patently clear that the EPRDF will use all available means to preserve the status quo indefinitely.
Opposition parties are already variously reacting to the perceived decision to exclude them once again. Some areBoycotting Ethiopian National Elections making their participation conditional on the change of policy of the National Election Board toward a neutral stand guaranteeing a level of playing field. Others have decided to participate regardless of the prevailing conditions because they believe that nothing can be achieved by shunning the elections. Still others seem undecided or are waiting for the development of the situation before taking a definitive stance. This article analyzes the cons and pros of participating in the upcoming elections with the view of showing the realistic alternative that emerges from taking part in the elections or boycotting them.
Let us state plainly the emerging quandary. Admittedly, the goal of participation is not to win, not because the regime is popular and has the allegiance of the majority of voters, but because it will use threat, harassment, deceit, and even violence to retain its present position, which is that only one parliament member is representing the opposition. The opposition may even lose this one seat or add some more, but the retention of an overwhelming majority will be the inevitable outcome of the elections. If so, why then participate when there is no the slightest opportunity to perform better?

Expected Gains from Participation

Those who opt for participation argue that winning has many forms. Indeed, elections, even if they are unwinnable, provide a good opportunity to denounce the regime. They supply a convenient platform to openly expose the failures and injustice of the regime at a time when popular attention and expectations are activated by the government’s own propaganda and its desire for renewed legitimacy. Exposing the regime is a vital component of nonviolent opposition. It is inconsistent to stay away from elections because the regime in place does not allow a fair playing field even as the purpose of peaceful struggle is, precisely, to mobilize voters to protest against the unfair conditions of political competition. Only such protests can bring about change, not boycott.
Parties that participate in elections find a good opportunity to promote themselves and make their program known to the public. Not only does participation help the recruitment of new members, but it also engages the party in the typical task of organizing and mobilizing the people. A party that is absent from the battle field on the pretext that conditions are highly unfavorable does not deserve to be called an opposition party, all the more so as it came into existence primarily to fight for the democratic opening of the political system.
To encourage people to oppose the regime, it is imperative to show the availability of an alternative program. If people are not exposed to the ideas of a viable organization and alternative policy, their legitimate fear of the unknown, including the possibility of a chaos, will prevail over their frustrations and make them stick to the status quo. Nothing extends more the life of unpopular governments than the lack of an alternative: such governments will always claim that the opposition is fearful to participate because it is too weak or has no viable rival program. And nothing shortens more their existence than the presence of a party that continues to fight against all odds. So that, in willingly participating in elections that are decided in advance, the opposition party demonstrates its full commitment, thereby changing its alleged weakness into the strength of steadfastness.
There is no telling in advance whether participation does not result in the gain of some seats. However limited, seats in the parliament offer the opportunity of voicing opposition from within the system, not so much to change the ongoing policy as to give more credibility to the availability of an alternative path. Parliamentary representation officializes opposition in the eyes of the people as well as of the government, forcing the latter to respond to criticisms instead of simply dismissing them as the views of outcasts.
To sum up, participation in elections, even when they are completely unfair, is not devoid of appreciable gains. In addition to being consistent with the choice of nonviolent opposition, it provides a much needed forum for opposition parties to convey their messages, mobilize voters, and strengthen their standing. By contrast, the rejection of elections until acceptable conditions emerges is defeatist and inconsistent with peaceful opposition, not to mention that it obtains and change nothing.

Expected Gains from Non-Participation

Naturally, those who favor boycotting the elections are not without some expectations of gains as well. To the extent that their decision is a political one, it must contain the possibility of advancing their cause in some way. So what do they expect to achieve in shining the elections?
Their main argument is that non-participation of opposition parties deprives the government of the legitimacy that it seeks by organizing these elections. Participating without the chance of winning even one seat is nothing but a free gift to the government. In advertising the pitiful result of the opposition, the government will have the easy game of declaring a crushing victory and portraying the opposition as irrelevant, nonexistent.
To take part under the existing conditions is to encourage the government to continue the same electoral policy. The only leverage that opposition parties have is that the government wants popular legitimacy by all means so that it is suicidal to give it up for what is nothing but a staged show to fool the Ethiopian people as well as the international community. Since opposition parties cannot expect anything unless existing conditions change, the kind of pressure liable to yield some results is precisely to make their participations conditional on some concessions on the part of the government. For this pressure to succeed, there is one and only one condition: the boycott must be unanimous and firm.
Experience teaches us that taking part in the elections under existing conditions will not result in any gain of parliamentary seat. Recall what happened to the All Ethiopian Unity Party in the 2010 elections: it broke away from the rest of the opposition by agreeing to participate without any tangible reforms of the electoral process only to find out that it was unable to secure even one seat despite its undeniable popularity in the Amhara region. What is more, opposition parties that already had some seats were completely wiped out. Obviously, the refusal of the government to make changes in the electoral process is motivated by a deliberate policy of expulsion of the opposition, and not by the precaution of having a sizeable majority.
As to exposing the anti-democratic nature of the regime, what else is more resoundingly revealing it than the refusal to participate in fake elections? By openly stating that participation depends on the creation of a level playing field, opposition parties do their primary job, namely, the presentation of reasonable and expected demands that normally go along with the very idea of holding elections. If elections do not have a minimum of fairness, they cease to be elections and turn into an exercise of canonization. The least that opposition parties can do is to put an end to this quinquennial farce.

Critical Assessment

What is striking about the above position is the belief that the refusal to participate puts pressure on the government. It would have been so if the opposition were united and the boycott unanimous. But to expect unity and a unanimous position is to assume solved the very problem that keeps the TPLF in power. Those who speaks of pressure put the cart before the horse by forgetting that the persistence of the hegemony of the TPLF is due to the success of its divide-and-rule policy, essentially manifested by the ethnicization of Ethiopia. Moreover, I do not remember a case where this government changed its opinion because of popular protests, let alone because of complaints from opposition parties. In other words, as hard as it may seem to accept, opposition parties have no leverage on this government.
True, the government wants legitimacy, but it can obtain it in various ways. For instance, it can force people to vote in great number so as to compensate the lack of opposition parties with a massive popular endorsement. Dictatorial regimes have practiced and refined this method for quite some time. If at all costs the presence of an opposition is required, the government can create fake opposition parties or divide existing parties by means of threats and bribes. This should not come as a surprise since the government has already given us the taste of such methods, just as it is presently doing it by prohibiting two major opposition parties, namely, Unity for Democracy and Justice Party and All Ethiopian Unity Party.
Given these available recourses, we can say that the government wants legitimacy, but not to the point of making concessions to the opposition. All the more reason for saying so is that legitimacy is essentially sought to shore up its international reputation, especially in the eyes of donor countries. Unfortunately, we have seen time and again that foreign countries, including democratic countries, are more interested in doing business than in denouncing and punishing undemocratic regimes.
To demand repeatedly for something and repeatedly obtain nothing, to the extent that it reveals the absence of leverage on the government, is easily construed as a demonstration of insurmountable weakness and inability to emerge as an alternative. What else can the people conclude from this constant failure to put pressure on the government but the utter weakness and irrelevance of the opposition? Since the opposition cannot extract the slightest concession from the government, there is no reason for the people to side with the opposition and become the target of government retaliation. Voting for the government may not bring change but at least it protects against retaliation.
As a matter of fact, neither participation nor boycott adds anything to the goal of denunciation for the simple reason that the anti-democratic nature of the regime has long ceased to be a mystery to foreigners or natives. If we still find Ethiopians who are not aware of its real nature, such people are better left alone since they are either irremediably apolitical or indifferent to what is going around them.
What about mobilization and organization? Does participation, as claimed by those opposing boycott, serve to strengthen opposition parties? It would have been so if the government would allow freedom of expression and organization. Such disposition would mean that the government is ready to face opposition in a level playing ground. But the very dilemma over participation stems from the knowledge that the government will not allow a condition of fair competition, that it will paralyzed the opposition by restrictions, harassments, and imprisonments, not to mention the silencing of the free press. To expect the strengthening of the opposition as a result of participation is just a wishful thinking.
The likely outcome being that participation will not bring any result, it removes the grounds for complaint about the lack of democracy. Your participation was a defiance intent on showing that you can pierce the barrier of exclusion. Your failure to do so only exposes your weakness and irrelevance. The aim of the government is not to show its strength by winning elections; rather, it is to display overtly that it has no real rivals worthy of that name. It does not want to win majority votes; it wants to ridicule the opposition by a crushing victory, thereby showing that there is no alternative to its rule. The proper analogy expressing Ethiopian elections is two soccer teams competing with the players of one of the teams being blindfolded.
In fact, a clear pattern emerges from the manner the government deals with opposition parties. Plainly, the government steps up its repressive power when it confronts unitary parties, such as the Unity for Democracy and Justice Party and All Ethiopian Unity Party, while being more tolerant of opposition parties with an ethnic banner. In ruthlessly repressing unitary parties, the government wants to bring about their final demise. The relative tolerance of the government to ethnicized opposition parties is, for sure, due to the perception of some affinity with its own policy; more importantly, however, it originates from the conviction that ethnic parties, fragmented as they are, can never become a threat to the hegemony of the TPLF. Add to this that it is simply easy to create hostility between these parties and reduce them to the permanent status of a negligible opposition.
The real threat, if fair elections were held, comes from unitary parties, as demonstrated by the success of Kinijit in 2005. In the eyes of the TPLF, Ethiopian nationalist parties cannot be allowed to grow, for the real enemy to its hegemony–which rests on the efficient implementation of divide-and-rule policy–is none other than Ethiopian nationalism. It is amazing that more than 20 years of uninterrupted attack and stifling have not succeeding in weakening Ethiopian nationalism. It has become the forbidden fruit: the more you want to muffle it, the more people want it.

Who Wins?

What springs from all is clear enough: opposition parties, whether they participate or not, lose in that none of the projected goals ascribed to participation or boycott is achievable. Neither participation nor boycott affects the standing of the government or the state of opposition parties in any meaningful way. Does this mean that the government win?
One thing is sure: after the elections, the government will not be better off. Not only will it face the same problems, but also its intransigence and repressive policy will heighten popular frustration and instill the sense of a political deadlock in the county. In other words, there is no winner, but only a huge loser, namely, nonviolent, peaceful opposition. Seeing the complete ineffectiveness of participation or boycott, people, especially the young, are increasingly bound to question the wisdom of peaceful opposition. The more repression continues, the more the deadlock over the possibility of change thickens, and the higher becomes the disposition toward uprising as the only alternative left. This is the iron law of all social blockage: Ethiopia will not be an exception.
When uprising becomes the only way out, young activists go underground or join armed struggle. Exciting nonviolent parties, too, to the extent that they are serious about the struggle for change, will be compelled to have a hard look at their strategy. Even if they continue to operate in a legal manner, it is no longer to win seats in the parliament. Instead, they anticipate uprising and hope to take its leadership when it erupts. Without doubt, the present attitude of the TPLF gives Ethiopians no other choice than revolution with, alas, the unpredictable but certainly severe and uncontrollable consequences that confrontation or civil war will have in present-day Ethiopia. Ethiopians, gear up for the worst!

Thursday, January 29, 2015

BREAKING NEWS - PEACEFUL POLITICAL ENVIRONMENT IN ETHIOPIA IS ABOUT TO END!

January 29,2015

The press conference held at Addis Ababa Hilton Hotel by Pro-TPLF (Tigray People Libration Front) Electoral board chairman Prof.Merga, states as it has suspended two prominent strong opposition parties in Ethiopia.These are ''Unity party'' (Unity) and ''All Ethiopian Unity party'' (AUP). Addis Ababa Hilton's press conference states as acknowledgement is given by the electoral board to operate legally with in the nation is taken by force and given to the regime's  'Poppets' parties'.These two TPLF-duplicated parties will get green light to operate with an identical name of the suspended ones.

It is quite clear that the two TPLF-poppets parties, introduced by Electoral board, do not have even formal office, council and even members are not yet disclosed. Many believe TPLF is creating its own 'loyal party' in the name of the prominent one.It was another surprise, when the electoral board chair person confirms  the major pre-condition to continue as opposition party is ''to be loyal'' to his Pro-TPLF board.

''Ethiopian Unity party'' (Unity) and ''All Ethiopian Unity party'' (AUP) were legally operating in all part of the nation with in strong controversy with TPLF cadres. Both parties were expecting to participant with the coming May 'stress-full' election.It is recalled that they were also active participant in 2005 controversial election that TPLF was beaten seriously by the peoples voice. In 2005, Independent commission confirmed over 200 people were killed by the regime's armed soldiers and security men which were under direct command post of the late Meles Zenawi.

The ''Blue party'' (ሰማያዊ ፓርቲ), the youngest but challenging the regime party may also host the same act from TPLF. Last month the party chairman and many of council members were beaten and send to prison during their peace-full demonstration in the capital demanding ''transparent election process'' on the coming May,2015.

At the result of such Un-lawful act of the regime, there is high tension in all part of the country. The two prominent parties response following to the decision is not yet known. ESAT, Ethiopian Satellite Television based on Washington DC announces on its social media page it will have detail report in this evening's broadcasting service.

There is strong believe as peaceful political environment in Ethiopia is about to end.It is about weeks that armed opposition parties Ginbot 7 Freedom and Justice movement and Ethiopian Patriotic Front (EPF) based on vast Eritrean deserts are united and created one front called ''Arbegnoch-Ginbot7 for Unity and Democracy Movement” (አርበኞች-ግንቦት7 የአንድነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ)

የምርጫ ቦርድ የአንድነት ፓርቲን ህጋዊነት አሳልፎ ለተለጣፊዎቹ ለእነ ትእግስቱ አወሉ ሰጠ

January 29,2015
የኢህአዴግ ምርጫ ቦርድ አንድነት በተለጣፊዎቹ በእነ ትግስቱ አወሉ እየተመራ ወደ ምርጫ እንዲገባ ወሰነለት። ሕጋዊው አንድነት በተለጣፊው መተካቱ ተረጋገጠ።
አንድነት ዛሬ ተላለፎ መሰጠቱን ተረጋገጠ! የኢህአዴግ ምርጫ ቦርድ አንድነት በእነ ቱግስቱ እየተመራ ወደ ምርጫ እንዲገባ ተወሰነበት፤ እንዲህ ነው ጨዋታ ሆደ ሰፊ ነኝ የሚለው የወያኔ ምርጫ ቦርድ በተደጋጋሚ በ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ እያሳረፈ ያለውን ሸፍጥ በመቀጠል ጭራሽ ህጋዊ ላልሆኑና ከአንድነት ና ከመኢአድ ፓርቲ ለተገነጠሉት ገንጣይ ወንበደዎች አሳልፎ ሰቷቸዋል ሙልውን ዘገባ ከታች ያገኙታል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጽህፈት ቤት በአመራር ውዝግብ ውስጥ በነበሩት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲና በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ዙሪያ ውሳኔ አሳለፈ።

አንድነትን በተመለከተ አቶ ትዕግስቱ አወሎ የፓርቲው ህጋዊ ሊቀመንበር ናቸው ብሏል። በመኢአድ በኩል ለአቶ አበባው መሃሪ የፓርቲው የህጋዊ ፕሬዚዳንትነት ዕውቅናም ሰጥቷል። አንድነትም ሆነ መኢአድ ቦርዱ ዕውቅና በሰጣቸው መሪዎች እየተመሩ በምርጫው መሳተፍ እንደሚችሉም ነው የተወሰነው። መግለጫውን የሰጡት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ፀሃፊ አቶ ነጋ ዱፌሳ ቦርዱ ለሁለት የተከፈሉትን የሁለቱንም ፓርቲዎች አመራር ችግራቸውን ለመፍታት የተሰጣቸውን ጊዜ ለመጠቀም ያከናወኗቸውን ተግባራት በጥልቀት መመርመሩንም ተናግረዋል።

ቀደም ሲል የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነትና መኢአድ በውስጣቸው የተከሰተውን ችግር ፈትተው እንዲመጡ የ14 ቀናት ጊዜ ሰጥቶ የነበር ሲሆን፥ ቦርዱ የጊዜውን መጠናቀቅ ተከትሎ በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት የመጨረሻ ውሳኔ ለማሳለፍ በዛሬው ዕለት ቀጠሮ መያዙ ይታወሳል።

በአቶ በላይ ፈቃዱ የሚመራው አንድነት የምወያየውም ሆነ የማካሂደው ጠቅላላ ጉባኤ የለም በማለት ባለፈው አርብ በሰጠው መግለጫ ሲያስታወቅ፣ በአቶ ትዕግስቱ አወሉ የሚመራው የአንድነት ቡድን ደግሞ ቅዳሜ እለት ባካሄደው ጉባኤ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ ሌሎች አመራሮቹን መምረጡም አይዘነጋም።

Tuesday, January 27, 2015

የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ!!!

January 27,2015
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ አማካይነት እየደረሰበት ያለውን በደል ለሕዝብ ለማሰማት ጥር 17 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ጂንካና ሸዋ ሮቢት የተቃውሞ ሰልፎችን ጠርቶ ነበር። በተለይ በአዲስ አበባው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወገኖቻችን ለህወሓት ፍጹም ታማኝ በሆነው የፓሊስ ክፍል ያለርህራሄ መደብደባቸው እና የተቃውሞ ሰልፉም በጉልበት መበተኑ ነፃነትና ፍትህ ናፋቂውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳዘነ ብቻ ሳይሆነ ያስቆጨ ጉዳይ ነው። በመላው ዓለም በሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ የተለመደውን ድንጋይ ውርወራ እንኳን ሳይከጅሉ፤ የፓሊሶችን ሰብዓዊ ርህራሄ ለማግኘት “ፓሊስ የኛ ነው” እያሉ እየዘመሩ በፓሊስ ተደበደቡ። ሴቶችና አዛውንት ብቻ ሳይሆን ተላላፊ መንገደኞች እንኳን ከፓሊስ ዱላ አላመለጡም። ከሁሉም በላይ የሚዘገንነው ደግሞ የ 7 ወራት ነብሰ ጡር ሴትም በፓሊስ መመታትዋና ሆዷ መረገጡ ነው። ይህ እኩይ ተግባር የሚፈጥረው ቁጭት በህወሓት ላይ ብቻ አያበቃም። ትዝብቱ ለፓሊስም ተርፏል። ይህ የጭካኔ ተግባር ለፍትህና ለነፃነት በሚደረገው ትግል የሕዝብ አጋር ይሆናል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የፓሊስ ሠራዊትን የሚያዋርድ ነው። ደካማ እናቶችን፣ አረጋዊያንን፣ ባዶ እጃቸውን ተቃውሞ እያሰሙ ያሉትን ወጣቶችንና ነፍሰጡሮችን በጭካኔ መደብደብ ለራሱና ለሥራው ክብር ለሚሰማው ፓሊስ ውርደት ነው፤ የሞት ሞት ነው። የኢትዮጵያ የፓሊስ ሠራዊት አባላት ተግባራቸው ያሳፍራቸዋል፣ ይቆጫቸዋል፤ ቁጭታቸውንም ይህን ትዕዛዝ በሰጡ አለቆቻቸው ላይ በግልም ሆነ በተደራጀ መንገድ በሚወስዱት እርምጃ እናያለን ብሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ ያደርጋል።
የጥር 17 ቀን 2007ቱ ሽብር በአንድ ወቅት የተፈጠረ፤ በአንድነት ፓርቲ ላይ ብቻ ያነጣጠረ፣ የተናጠል ክስተት ሳይሆን ህወሓት ደግሞ ደጋግሞ ሲፈጽመው የነበረ ነው። ከዚህ በፊት በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ፈጽሞታል። የአዲስ አበባ ከተማ ማስተር ፕላንን በተቃወሙ የተለያዩ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎች በተለይም በአምቦ ላይ የብዙዎችን ሕይወት የቀጠፈ ሽብር ነዝቷል። በቅርቡ ደግሞ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ተመሳሳይ አረመናዊ ድርጊት ፈጽሟል።
አርበኞች ግንቦት 7: ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የህወሓት ታጣቂዎች በወገኖቻችን ላይ ያደረሱትን ድብደባ፣ ህገወጥ እስር፣ እና የተቃውሞ ሰልፍ ክልከላን አጥብቆ ይቃወማል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው ህመም ህመሙ፣ ቁስላቸው ቁስሉ ነው።
ባለፉት ሃያ ሶስት ተከታታይ ዓመታት፣ በአምቦ፣ በጅማና በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞችና ገጠሮች፣ በባህዳር፣በጎንደርና በበርካታ የአማራ ከተሞችና ገጠሮች፣ በጋምቤላ፣ በሶማሊ፣ በአፋር፤ በአጠቃላይ በመላው ኢትዮጵያ በየአስፋልቱ፣ በየሜዳውና በየጥሻው በህወሓትና ተላላኪዎቻቸው የፈሰሰው የኢትዮጵያውያን ደም በከንቱ ፈሶ መቅረት የለበትም ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች መሰል ድርጅቶች ጋር በመተባበር የህወሓትን እድሜ በማሳጠር የእናቶቻችን እምባ ሊያብስ ዝግጁ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ኢትዮጵዊያን እንደከብት እየተደበደቡ ወደ ማጎሪያ የሚያጋዙበት እና በጠገቡ ሰላዮችና ፓሊሶች እየታነቁ የሚታረዱበት ጊዜ ማብቃት አለበት ይላል።
የቱን ያህል ቢለመንም ሆነ ቢወገዝ ህወሓት ለነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒን ምርጫ ዝግጁ ሊሆን ቀርቶ በምርጫ የሚወዳደሩት ፓርቲዎች እነማን እንደሆኑና እነማን በእጩ ተወዳደሪነት መቅረብ እንዳለባቸው ሳይቀር የሚወስን ዓይን አውጣ አጭበርባሪ ድርጅት ነው። ይህንን ከዚህ በፊት አይተነዋል፤ አሁንም በአንድነትና በመኢአድ ላይ እየተደገመ ነው። ህወሓት፣ በየአምስቱ ዓመታቱ በሚያደርጋቸው የሴራ ምርጫዎች በሚቀጥሉት አርባና ከዚያም በላይ ለሆኑ ዓመታት በሥልጣን ላይ የሚቆይበትን ስልት ቀይሶ የሚንቀሳቀስ፤ ኢትዮጵያን ለብዙ ዓመታት ለመግዛት ማድረግ የሚችለውን ክፋት ሁሉ ከማድረግ የማይመለስ አገር በቀል ቅኝ ገዥ ነው። ህወሓት የዘረጋው ሥርዓት ህገ-አልባነት፣ ፀረ-ሕዝብነት እና አምባገንነት ለማጋለጥ በሚል ርህራሄን በማያውቁ የሥርዓቱ አገልጋዮች ፊት ባዶ እጅ መጋፈጥ የሚፈጥረው የሞራል የበላይነትና የመንፈስ ጀግንነት ባያጠራጥርም የሚያስከፍለው ዋጋ ከሚገኘው ውጤት ጋር ማመዛዘን ግን እጅግ ተገቢ የሆነ የማይታለፍ ሥራ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ከህወሓት የሴራ ምርጫ ፋይዳ ያለው ውጤት ይገኛል ብሎ አይጠብቅም። ከምርጫው የሚፈልገው ውጤት አንድ ነገር ብቻ ነው፤ እሱም የመንግሥት ለውጥ ነው። ምርጫው በምርጫነቱ ወደ መንግሥት ለውጥ አያደርስም፤ ወደ መንግሥት ለውጥ ወደሚያመራ ሕዝባዊ አብዮት ሊያሸጋግር ግን ይችላል። ይህም ቢሆን የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ በተለይም የሠራዊቱን ዓይነትና አደራጀጀት እግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ መታቀድ ይኖርበታል።
አርበኞች ግንቦት 7 የራሱን ጥናት አድርጎ ለኛ አገር ተጨባጭ ሁኔታ እና ህወሓትን ለመሰለ ጠላት የሚመጥን የትግል ስልት ሁሉንም የትግል ስልቶች እንደሁኔታው ያዳቀለ – ሁለገብ – መሆን ይኖርበታል ብሎ ወስኖ ለተግባራዊነቱ እየተንቀሳቀሰ ነው። ሁለገብ የትግል ስልት ሕዝባዊ ተቃውሞን፣ ሕዝባዊ እምቢተኝነትንና ሕዝባዊ አመጽን እንደወቅቱ ተጨባጭ ሁኔታ ማፈራረቅና ማደባለቅን ይፈልጋል። ሰላማዊ ትግል በተለይም ሕዝባዊ እምቢተኝነት ሲባል ደግሞ ህወሓት ያወጣቸው አፋኝ ህጎች እያከበሩ የሚደረግ አለመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ ይረዳል። ሁለገብ ትግል በተቻለ መጠን የወገን ኃይል ራሱን ፈጽሞ መከላከል በማይችልበት ሁኔታ እንዳይገኝ ለማድረግ ይጥራል። በአርበኞች ግንቦት 7 እምነት ሁለገብ የትግል ስልት ሰፊ ተቀባይነት የሚያገኝበት ወቅት ደርሷል። ከዚህ በፊት “የሰላም በሮች ሲዘጉ የአመጽ በሮች ይከፈታሉ” ተብሎ በአንድ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ታጋይ የተነገረው “የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ” በሚል እንዲሻሻልና በዚህ ወለል ብሎ በተከፈተው በር ሁላችንም እንድንገባ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል። በሁለገብ የትግል ስልት በሰላማዊ መንገድ የሚደረጉ የትግል ዓይነቶች አሉ፤ በሌላም መንገድ የሚደረጉ አሉ። ስለሆነም በሁለገብ ትግል እያንዳንዳችን እንደየዝንባሌዓችንና እንደየችሎታዎቻችን አስተዋጽኦ ልናበረክት የምንችልበት ሰፊ እድል ይከፍትልናል።
ስለሆነም፣ በዚህ አጋጣሚ አርበኞች ግንቦት 7፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለጦር ሠራዊትና ፓሊስ አባላት ወገናዊ ጥሪ ያደርጋል።
በህወሓት ዘረኛ አገዛዝ በሚደርስብን ውርደት፣ እንግልት፣ ስደት፣ ሥራ አጥነትና ድህነት የተማረራችሁ እና እኩልነቷ የተረጋገጠ፣ የበለፀገች ኢትዮጵያን ማየት የምትመኙ ሁሉ የሁለገብ የትግል ስልትን አዋጪነት እንድታጤኑ የዚሁ ስልት አካል ሆናችሁ እንድትታገሉ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
የኢትዮጵያ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት በግል ከሚደርስባችሁ ግፍ በተጨማሪ የገዛ ራሳችሁን ወገኖች መግደላችሁ፣ ማቁሰላችሁ፣ ማድማታችሁና መደብደባችሁ የህሊና እረፍት ሊነሳችሁ ይገባል። ህሊናችሁ እረፍት የሚያገኘው የሥርዓቱ እድሜ ሲያጥር መሆኑን በመገንዘብ ለገዛ ራሳችሁ ክብር፣ ለወገናችሁና ለአገራችሁ ስትሉ ፋሽስቱን ወያኔ ከድታችሁ ከአርበኞች ግንቦት 7 ኃይል ጋር ተቀላቀሉ።
እነዚህን ጥሪዎች ተግባራዊ ካደረግን ወገኖቻችን መሠረታዊ መብቶቻቸውን በመጠየቃቸው በመወደስ ፋንታ በፓሊስ ዱላ ሲደበደቡ የማናይበት ዘመን ይመጣል። ይህ ካልሆነ ግን “ውሀና መብራት አጣን” ብሎ አቤቱታ ማሰማት እንኳን በጥይት የሚያስገድልበት ቀን ይመጣል። ያ ከመሆኑ በፊት እንወስን፤ ራሳችንና አገራችን ከህወሓት ዘረኛ አገዛዝ ነፃ እናውጣ።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Sunday, January 25, 2015

United Nations Review Should Condemn Crackdown – Human Rights Watch

January 25,2015
(Geneva) – United Nations member countries should call on Ethiopia to stop targeting activists and the media under draconian laws. The UN Human Rights Council will review Ethiopia’s human rights record under the Universal Periodic Review (UPR) procedure on May 6, 2014.
A Human Rights Watch submission to the UN on Ethiopia highlights its ongoing suppression of the media and nongovernmental organizations, and the lack of accountability for torture and other serious abuses by its security forces. The arbitrary arrest of nine bloggers and journalists on April 25 and 26, just 10 days before the review, reflects Ethiopia’s blatant disregard for fundamental rights and should be strongly condemned by UN members.
“The UN review is taking place just as Ethiopia is renewing its crackdown on free speech,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “To make this review meaningful, UN member countries should forcefully tell Ethiopia that its attacks on the media and activist groups are a blight on its human rights record.”
Since Ethiopia’s first UPR review in 2009, the human rights situation has deteriorated substantially. The authorities have shown harsh intolerance of any criticism of government actions and have sharply restricted the rights to free expression and association.
Despite Ethiopia’s commitment during the 2009 review to take “measures to provide for free and independent media,” Ethiopia now has one of the most repressive media environments in the world. Numerous journalists languish in prison, independent media outlets have been closed down, and many journalists have fled the country.
Critics of government policy – including journalists, rights activists, and opposition party supporters – risk harassment, arbitrary detention, and politically motivated prosecutions. Many prosecutions are carried out under repressive laws that have dramatically curtailed the ability of independent Ethiopian and international organizations to investigate and report on human rights violations and other concerns.
Critics are also subject to illegal surveillance of telephone communications, and the contents of these communications are sometimes used during unlawful interrogations. Government censors routinely block websites of opposition parties, independent media sites, blogs, and several international media outlets.
During the 2009 review Ethiopia rejected recommendations to amend two draconian laws – the Charities and Societies Proclamation (CSO law) and the Anti-Terrorism Proclamation – to comply with international human rights standards.
“Ethiopia’s membership in the Human Rights Council should make it a leader in respecting rights, not repressing them,” Lefkow said. “UN members should press Ethiopia to amend the laws it uses to decimate independent media and civil society.”
The Ethiopian government has failed to conduct credible investigations or prosecutions of members of the security forces implicated in torture and other rights violations, war crimes, and crimes against humanity. This includes security force abuses in Gambella, the Somali regionOromia, and inSomalia.
In an October 2013 report, Human Rights Watch documented the use of torture by police and investigators against detainees in Maekelawi, the main investigation center in Addis Ababa, the capital.
At the Human Rights Council, countries should stress the need for Ethiopia to address torture and other serious crimes by security forces, and to investigate and prosecute security personnel responsible for serious crimes.
“Ethiopia’s refusal to address serious crimes by security forces is a major obstacle to human rights progress and deeply distressing for the families of the victims,” Lefkow said. “UN members need to push Ethiopia to meaningfully investigate grave violations and to hold those responsible to account.”

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

January 25, 2015
የፍትህና የነፃነት ጥያቄያችን ደም በማፍሰስ አይቀለበስም!!!
ፓርቲያችን አንድነት ገዥው ፓርቲ፣ ምርጫ ቦርድና የገዥው ፓርቲ ልሳን በመሆን እያገለገሉ ያሉ ሚዲያዎች በመተባበር ከምርጫ ለማስወጣትና ተለጣፊ አንድነት ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ መጥራቱ የሚታወቅ ነው፡፡UDJ/Andinet party logo
የተቃውሞ ሰልፉን ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም እንደምናከናውን ለአዲስ አበባ መስተዳድር ብናሳውቅም መስተዳድሩ በ12 ሰዓት ውስጥ በፅሁፍ ምላሽ መስጠት ባለመቻሉ ሰልፉ እውቅና አለው፡፡ መስተዳድሩ ግን የተጣለበትን ሃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ወደ ጎን በመግፋት የተወሰኑና የማይታወቁ ግለሰቦች ፔቲሽን ተፈራርመው አምጥተዋል በማለት ብዥታ ለመፍጠር ሞክሯል፡፡ ፓርቲያችን ህጉን ጠብቆ ህጋዊ የሆነ ሰልፍ ለማካሄድ ቢሞክርም አሁንም ሃላፊነት በጎደለው ሁኔታ የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል፡፡ በተደጋጋሚ እንዳየነው ፖሊስ ደንብ ማስከበር ሲገባው አድሎ ለፈፀመው አካል በመወገን ድብደባ መፈፀሙ ከወገንተኝነት ያልፀዳ መሆኑን እንድናረጋግጥ አድርጎናል፡፡
ጥያቄያችን አሁንም የፍትህ፣ የእኩልነትና ህግ እንዲጠበቅ የማድረግ ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ የመንግስትነት ስልጣኑን በመጠቀም የስልጣን ዘመኑን ለማስረዘም እየከወነ ያለውን ሴራ ማስቆም ነው፡፡ ጥያቄያችን የነፃነትና ያልተሸራረፈ ዴሞክራሲ ይረጋገጥ የሚል ነው፡፡ ጥቄያችን ምርጫ ቦርድ የገዥው ፓርቲ አጋር መሆኑ ቀርቶ ገለልተኛ ሚናውን ይወጣ የሚል ነው፡፡ እነዚህ ጥያቄዎቻችን ደግሞ ደም በማሰስ፤ በድብደባም ሆነ በእስር ፈፅሞ አይቆሙም፡፡ ትግላችን የአንድ ፓርቲ የበላይነት አገዛዝ እስከሚያበቃ ድረስ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
በሚቀጥለው ሳምንትም በተለያዩ ከተሞችና በአዲስ አበባ የሰላማዊ ተቃውሞ ድምፃችንን ከፍ አድርገን እናሰማለን፡፡ ትግሉ ይቀጥላል፡፡
ድል የህዝብ ነው!!

UK diplomats clash over Briton on death row in Ethiopia: Officials’ fury after Foreign Secretary claims he couldn’t ‘find time’ to help father-of-three facing execution

January 25,2015
  • Andargachew Tsege was snatched by officials at Yemen airport last June
  • The 59-year-old was transferred to Ethiopia where he is thought to remain
  • Father-of-three moved to London in 1979 from native African country
  • He was dubbed ‘Ethiopian Mandela’ after exposing government corruption
  • Leaked emails revealed British officials’ frustration at political inaction
  • Philip Hammond said he could not ‘find time’ for phone call on issue
Foreign Secretary Philip Hammond said he could not ‘find time’ for a phone call to raise the issue and did not want to send a ‘negative’ letter
An explosive row has erupted between diplomats and Ministers over their reluctance to help a British man on death row in Ethiopia.
A series of extraordinary emails, obtained by The Mail on Sunday, reveal officials’ increasing frustration at political inaction over Andargachew Tsege.
Tsege, 59, a father-of-three from London, was snatched at an airport in Yemen last June and illegally rendered to Ethiopia. There are concerns he may have been tortured.
Yet Foreign Secretary Philip Hammond said he could not ‘find time’ for a phone call to raise the issue and did not want to send a ‘negative’ letter.
In one email, an exasperated official asks: ‘Don’t we need to do more than give them a stern talking to?’
Tsege, who has lived in the UK since 1979, has been called Ethiopia’s Nelson Mandela. Tsege fell out with his university friend ex-Prime Minister Meles Zenawi, after he exposed government corruption and helped establish a pro-democracy party.
In 2009, he was sentenced to death in his absence for allegedly plotting a coup and planning to kill Ethiopian officials – claims he denies.
He was abducted on June 23 while en route to Eritrea, emerging two weeks later in Ethiopia, where he has since been paraded on TV. It is not known where he is being held.
The diplomatic exchanges disclose how officials were dismayed when British Ministers rejected requests to raise the case with Ethiopia.
‘I feel so shocked and let down,’ said Tsege’s wife Yemi Hailemariam. ‘I thought Britain was a nation driven by fairness but it seems my husband’s life is simply not valued.’
The series of emails begins on July 1, with Foreign Office officials confirming his capture: ‘His detention in Yemen is significant news, and could get complicated for the UK.’
Diplomats noted that neither Yemen nor Ethiopia informed Britain about the rendition of its citizen. ‘It feels a bit like I’m throwing the kitchen sink at the Yemenis but I want them to think twice before they do this again,’ wrote one senior figure at the British Embassy in Addis Ababa. 
He also noted that a prominent Ethiopian minister had given assurances over Tsege’s treatment –‘but I wouldn’t take them with complete confidence’.
Ethiopia has claimed Tsege tried to recruit other Britons to become involved in terrorism. But the regime has used anti-terror laws to jail journalists and silence political rivals, and UK officials had not seen credible evidence. 
One diplomatic cable says: ‘All we have seen are a few pictures of him standing in an Eritrean village – hardly proof that he was engaged in terrorist training.’
Three weeks after Tsege’s kidnap, the Foreign Office’s Africa director wrote that Ministers ‘have so far shied away from talking about consequences… their tone has been relatively comfortable’.
On July 21, Hammond’s office was still reluctant to talk to his Ethiopian counterpart on the phone.
‘I don’t think we are going to be able to find time for that at the moment,’ wrote his private secretary. He also turned down sending a ‘negative’ letter, asking for it to be rewritten ‘setting out areas of co-operation. It can end with a paragraph on the Tsege case.’
Despite concerns over Ethiopia’s human rights record, the nation receives £376 million a year in UK aid. One farmer there is suing Britain, claiming the money was used to usurp him from his land.
Hammond is believed to have finally called his counterpart at the end of July, one month after the kidnap. It is understood he focused on requesting consular access rather than condemning the capture.
Reprieve, which campaigns against the death penalty said: ‘These shocking emails show the Foreign Secretary appears to have blocked any meaningful action that could potentially bring this British father home to his family, unharmed.’
The Foreign Office said they were ‘deeply concerned’ by Tsege’s detention and were lobbying for further consular access as well as seeking confirmation the death penalty would not be carried out.

የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ባለቤት ስለሺ ሃጎስ በሕወሓት ፖሊሶች ክፉኛ ተደበደበ

January 25,2015
(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ አንድነት በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ያስደነገጠው የሕወሓት መንግስት በዜጎች ላይ አሰቃቂ ድብደባ ሲፈጽም መዋሉን ቀደም ብለን መዘገባችን ይታወሳል:: አሁንም ከሰልፉ በኋላ በአንድነት አመራሮችና አባላት ላይ የመንግስት ተላላኪዎች እጅጅ አሳዛኝ ጭፍጨፋ ማድረጋቸውን የቀጠሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል የጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ባለቤት በዚህ በምስሉ ላይ የምታዩት ጋዜጠኛ ስለሺ ሀጎስ እጅግ አሳዛኝና አሰቃቂ ድብደባ ተፈፅሞበታል::
አሁን ባለው ሁኔታ የአንድነት አመራርና አባላት በሰላማዊ ትግሉ እራሳቸውን አሳልፈው እየሰጡ፤ በኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል እንደማያዋጣ እያሳዩን ያለበት ሁኔታ ነው ያለ ሲሆን በዚህም በደማቸው ደማቅ ታሪክ እየጻፉ ይገኛሉ::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ የሚሊዮኖች ድምጽ እንደዘገበው በአንድነት ሰልፍ የተገኙ ዲፕሎማቶች በሆነው ነገር በጣም አዝነዋል። የተጎዱትን ሁኔታ ለመከታተል ወደ ሆስፒታልም ሄደዋል።የተጎዱ ወገኖቻችን ፣ «ከዚህም የበለጠ ዋጋ ለነጻነታች እንከፍላለን። እነርሱ ያላቸውን የመጨረሻ ዱላ ነው የተጠቀሙት፣ እርሱም ኃይል” ያሉ ተጎጂዎች ይህ የትግል ወኔያቸውን የበለጠ የሚያጠናከር እንጂ የሚቀንሰው እንዳልሆነ እያረጋገጡ ነው። ታጣቂዎቹ በተለይም በአቶ ስለሺ ሐጎስ እና በአቶ አሰራት አብርሃ ላይ፣ ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመዉባቸዋል። የሰባት ወር ነፍሰ ጡር ሴት ሆዷ ላይ ተመታለች። የሰባ አመት እናት፣ አባት ሽማግሌ ተደብደበዋል።
ጋዜጠኛ ስለሺ የተደበደበው ሰውነቱ በፋሻ ተጠቅልሎ ይታያል
ጋዜጠኛ ስለሺ የተደበደበው ሰውነቱ በፋሻ ተጠቅልሎ ይታያል

Saturday, January 24, 2015

በነትግስቱ ቡድን ጠቋሚነት የአንድነት አመራሮችን ማሰር ተጀምሯል

January 24,2015
1. አቶ አስራት አብርሃ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ
2. አቶ ሰለሞን ስዩም የፍኒትና ሚሊዮኖች ድምጽ ኤዲቶሪያል ሃላፊ
3. አቶ ስንታዩ ቸኮል የአዲስ አበባ ምክር ቤት የወጣቶች ክፍል ሃላፊ
4. አቶ ንዋይ ገበየሁ የህዝብ ግንኙነት ረዳት ሃላፊ እንዲሁም ሌሎችም ወደ አልታወቀ ቦታ በፖሊስ ተይዘው ተወሰደዋል።
ወያኔ/ኢሕአዴግአወል ጋር ከምርጫ ቦርድ ጋ የኃይል የአዲስ አበባ ሰልፍ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት የኃይል እርምጃ መዉሰድ ጀምሯል። የአንድነት አመራሮች ፖሊስ እየጎተተ በማሳሰር እየሰራ ያለው፣ ከአቶ ትግስቱ ር አብሮ እየሰራ ያለው የማነ አሰፋ እንደሆነ ታወቋል።
በዚህ ሰዓት ትግሉ ወደ አንድ ምዕራፍ ተሸጋግሯል አአስራት፤ ነዋይ ፤ስንታየሁና ሰለሞን ቢታሰሩም እንኳ የሶሻል ሚዲያውን ከሀገር ውጪ ያሉ የአንድነት ምዕራፍ 2 ሶሻል ሚዲያ ቡድን አባላት እየመሩት ነው ምዕራፍ 3 እና 4 ከሰዓታት በኋላ የተጀመረው ትግል ግቡን እስኪመታ እረፍት አይኖራቸውም፡፡

የነፃነት ቀን ቀርባለችና ወደ አደባባይ ውጡ!!!

እሁድ ጥር 17 ደብርማርቆስ ንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ በመገኘት
ለአንድነት ፓርቲ አጋርነታችንን እናሳይ!!!
አንድነት አንድ ነው!!!

የሰልፍ ትብብር ጥሪ ለእውነተኛ ተቃዋሚዎች በሙሉ!

አንድነት እሁድ ጥር 17 በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የሚያካሄደው ሰላማዊ ስልፍ ላይ እውነተኛ ተቀዋሚዎች ሁሉ በፈለጉት መልኩ በሰልፉ ላይ ትሳተፉ ዘንድ ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን። በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ በሚካሄደው ታላቅ ሰላማዊ ስልፍ ላይ የሰማያዊ፣ የመኢአድ፣ የመድረክ እና የዘጠኙ ፓርቲዎች አመራሮች እንድትሳተፉ በዚህ አስቸጋሪና ታሪካዊ ወቅት ከጎናችን እንደምትሆኑ እምነታቸን ነው።
የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ
udj 67
10947240_407366432761047_2187322177615197122_n
10269525_407366416094382_8678569693027599769_n


1545601_407366336094390_5858335905222877108_n