Tuesday, November 24, 2015

በወላይታ ሶዶ ህዝቡን ለትግል የሚያነሳሱ መፈክሮችና ምስሎች በብዛት ተለጠፉ

November 24,2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ
በወላይታ ሶዶ በሦስቱም ክፍለ ከተሞች አርበኞች ግንቦት 7 እያፋፋመው የሚገኘውን የነፃነት አርበኝነት የሚደግፉና ህዝቡን ለትግል የሚያነሳሱ መፈክሮችና ምስሎች በብዛት ተለጠፉ፡፡
ህዝቡ በአርበኞች ግንቦት 7 ሁለገብ የትግል ማዕቀፍ ውስጥ ተሰባስቦ ሁሉም በአንድት ተነስቶ ለተጀመረው ፀረ-ወያኔ፣ ፀረ-አምባገነናዊ የህወሓት አገዛዝ ፍልሚያ የየበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ የሚያስተላልፉት ፅሁፎችና ምስሎች ወላይታ ሶዶን ዳር እስከ ዳር ያጥለቀለቋት እሁድ ዕለት ለሰኞ አጥቢያ ሌሊት ሲሆን ትናንት ከፍተኛ ውጥረትና ግርግር በከተማዋ ሰፍኖ ውሏል፡፡
"የክልሉን አስተዳደር" ጨምሮ የአካባቢው የህወሓት-ደህዴግ ሹሞችን የተቃውሞ ፅሁፎችና ምስሎችን የያዙ ወረቀቶች በሁሉም ቦታዎች ተለጥፈው መታየት በእጅጉ አስደንግጧቸዋል፡፡ 
በአሁኑ ሰዓት ደህንነቶችና የታጠቁ ቡድኖች ያገኙትን ወጣት ሁሉ እያፈሱ ወደ ወህኒ በማጋዝ ላይ ናቸው፡፡
በወላይታ ሶዶ በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች ከተለጠፉት ምስሎች የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀ መንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፎቶ ይገኝበታል፡፡

No comments: