Tuesday, April 14, 2015

የህወሃት በቀቀኖች ሚሚ ስብሃቱና ባለቤቷ ዘሪሁን ተሾመ በዲሲ – አርአያ ተስፋማሪያም

April 14,2015

mimi
ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱና ባለቤቷ ዘሪሁን በዲሲ እንደሚገኙ ታውቋል። ባላፈው ቅዳሜ ከዲሲ ከሚተላለፈውና ንጉሴ በተባለ “ጋዜጠኛ” ከሚሰናዳው ራዲዮ ጋር ቃለምልልስ ያደረገው ዘሪሁን በዲሲ በሚገኙ የሃበሻ ሬስቶራንቶች ከባለቤቱ ጋር ሲዝናና ኢትዮጵያውያን እየሰደቡት፣ እያስፈራሩትና አንዳንዶች ደግሞ ስልክ እየደወሉ በሱማሊኛ ቋንቋ ተቃውሟቸውን ከመግለፅ ባሻገር “ኢህአዴግ አባረራችሁ እንዴ?” እያሉ በፌዝ የጠየቁት እንዳሉ ተናግሯል። መሳደብና ማስፈራራት በህግ እንደሚያስጠይቅና አግባብም እንዳልሆነ አያይዞ ተናግሯል።

በእርግጥም ስድብ የሚደገፍ አይደለም። ነገር ግን «ዛሚ» የተባለውና በእሱና ሚሚ ስም የሚታወቀው ራዲዮ የሚለቀው የስድብ ውርጅብኝ አግባብ ነው?..በሚሚ ያልተሰደበ፣ ያልተዘለፈ፣ ያልተንቋሸሸ ግልሰብና የህብረተስብ ክፍል አለ ይሆን?…”በራስህ ሊደረግብህ የማትሻውን በሌሎች አታድርግ” የሚባለው ለዚህ ነው። በተለይ በአንዲት የተቃዋሚ አመራር አባል ላይ ሚሚና ዘሪሁን የፈፀሙት እጅግ አስነዋሪ የወሲብ ቅንብር ድርጊት (ቪዲዮ) የሚረሳ አይደለም።…በነገራችን ላይ ሁለቱ ባለሃብቶቹን ተከትለው ነው የመጡት።

ቱጃሮቹ ተመልሰዋል። ከነሱ ስር አልጠፋ ያሉበት ምስጢሩ ምን ይሆን?….ዘሪሁን ዲሲ ለሚገኙ ወዳጆቹ – ገዢው ፓርቲ በአውስትራሊያ አምባሳደር አድርጐ ሊሾመው እንደሆነ መናገሩ ታውቋል። ሌላው የሚሚና ዘሪሁን አስገራሚ ድርጊት ሳይጠቀሳ አይታለፍም፤ ቀን ከአረንጓዴዋ ቅጠል ጋር በሰላም ካሳለፉ በኋላ ማታ ውስኪ ሲጐነጩ ድብድብ መከተሉ ነው። አንዳንዴ ጠርሙስ እስከመወራወር እንደሚደርሱ ለሁለቱ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ገነነ አሰፋ ማሸማገሉ እንደሰለቸው ጭምር የሚናገረው ነው።

No comments: