Monday, April 13, 2015

በቤተመንግስት አካባቢ አለመተማመኑ በገሃድ እየታየ ነው * የቤተመንግስቱ ጠባቂዎች በሙሉ ወደ ቤንሻንጉል ተላኩ

April13,2015
(ዘ-ሐበሻ) ሕወሓት በሚያስተዳድረው መንግስት ውስጥ እርስ በ እርስ በባለስልጣናቱ መካከል ያለው አለመግባባት እና አለመተማመን እያየለ መሄዱ ቤተመንግስትም መድረሱ ተሰማ:: በተለይም የመለስን ራዕይ ገደል ይግባ የሚለው የአቶ አርከበ ቡድን ሃይለማርያም ደሳለኝን ይዞ እያየለ መሄዱና በሌሎች የሕወሓት አባላት ላይ ያለው አለመግባባት ወደ አለመተማመን ደርሶ የቤተመንግስት ጠባቂዎችን እንዳስቀየረ የዘ-ሐበሻ ምንጮች አጋለጡ::

ቤተመንግስቱን ሲጠብቁ የነበሩ የሕወሓት ተላላኪ ወታደሮች በጠቅላላ ወደ ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ጉባ ወረዳ መላካቸውን ያጋለጡት የዘ-ሐበሻ ምንጮች እነዚህ ጠባቂዎች ደግሞ የአየር ሃይል አባላት መሆናቸው ጉዳዩን ከረር አድርጎታል:: ሕወሓት በሚመራው አየር ኃይል ውስጥ ያለው መታመስና በርካታ የአየር ሃይል አባላትም እየከዱ ወደ ጎረቤት ሃገራት መሰደድና ተቃዋሚዎችን መቀላቀል ያስደነገጠው መንግስት የአባይን ግድብ ትጠብቃላችሁ በሚል ሰንካላ ምክንያት መሳሪያቸውን በጠቅላላ አስቀምጠው ወደ ቤንሻንጉል እንዳዘዋወራቸውና በምትካቸውም ጆሮዋቸውን ቢቆርጧቸው ያለውን መከፋፈል የማያውቁ ወታደሮችን በቤተመንግስቱ አካባቢ አስፍሯል::

በገዢው ፓርቲ ውስጥ ያለው መከፋፈል ወደ እርስ በ እርስ መበላላት ሊያደርስ እንደሚችል ከውስጣቸው የሚወጡ መርጃዎች ይጠቁማሉ::

No comments: