Friday, December 12, 2014

አስራ አንዱን የማዕከላዊ ገራፊዎችን እወቋቸው

December 12,2014
ከዳዊት ሰለሞን
በማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ጋዜጠኞችን፣ፖለቲከኞችን፣የሀይማኖት ምሁራንና ያለ ምንም ተሳትፎ ኦሮሞዎች በመሆናቸው ብቻ በኦነግነት ተጠርጥረው ታስረው የነበሩ መተኪያ አልባ ዜጎችን በማሰር ቃላት ሊገልጸውና የሰው ልጅ ሊሸከመው አይችልም ተብሎ የሚታሰብን ሰቅጣጭ ድርጊት በመፈጸም ረገድ ወደር የሌላቸው ገራፊዎች ስም ዝርዝር ይፋ ተደርጓል፡፡እነዚህ ሰዎች አሁንም በዚሁ ድርጊታቸው ጸንተው ወንድሞቻችንን እያሰቃዩ የሚገኙ በመሆናቸው ህዝብ ሊያውቃቸውና ቀን ሲወጣም ፍትህ ሊጠይቅባቸው ይገባዋል፡፡

ስማቸው የተጠቀሱትን ሰዎች የምታውቁ አልያም በእነዚህ ሰዎች በማዕከላዊ ምርመራ ወቅት ስቃይ የደረሰባችሁ ዜጎች መረጃውን ልታዳብሩት ወይም ሊጨመሩ የሚገባቸውን ገራፊዎች ልታጋልጡ ትችላላችሁ፡፡
ethiopia-torture-620ገራፊዎቹ ነጭ ወረቀት በማቅረብ ተጠርጣሪዎች ፊርማቸውን እንዲያኖሩ የሚያስገድዱ፣ገልብጠው የሚገርፉ፣በወንድ ብልት ላይ ውሃ የተሞላ ላስቲክ በማንጠልጠል የሚያሰቃዩ፣ሴት እስረኞችን ጡታቸውን በበትር የሚደበድቡ፣ሰውን ካልደበደቡ ስራ ያልሰሩ የሚመስላቸው ቃሉ ከገለጻቸው ‹‹አረመኔዎች››ናቸው፡፡ምናልባት የፍትህ ጸሀይ ወጥታ ህዝብ አሸናፊ ሲሆን እነዚህ ሰዎች ይፈጽሙ የነበሩትን ግፍ በአደባባይ እንዲመሰክሩ ይደረጉ ይሆናል፡፡
ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ወዳጆቻቸውም ስማቸውን ተመልክተው የህሊና ዕዳ ይፈጥሩባቸው ይሆናልና ስማቸውን ይፋ ማድረጉ ብዙ ጥቅም ይኖረዋል ባይ ነኝ፡፡
1. ታደሰ መሰረት የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ኃላፊ
2. ዩሀንስ ኢንስፔክተር
3. ተዘራ ቦጋለ ኢንስፔክተር
4. ብርሃነ ኢንስፔክተር
5. ከተማ ኢንስፔክተር
6. ሰይድ አሊ ኢንስፔክተር
7. ገብረመድህን ኑር ኢንስፔክተር
8. ሙልጌታ ኢንስፔክተር
9. አሰፋ ትኩት ምክትል ኢንስፔክተር
10. ታደሰ አያሌው ኢንስፔክተር
11. በለጠ ኢንስፔክተር

No comments: