Tuesday, December 16, 2014

በኦሞ ስምጥ ሸለቆ ለሽርሽር የሄዱት በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች 12 ስዊድናውያን የተኩስ እሩምታ ወረደባቸው

December 16,2014

ኢሳት ራድዮ ታህሳስ 6/2007 ዓም እንደዘገበው በግድያ ሙከራው ላይ የስዊድን የመገናኛ ብዙሃን በብዛት እየዘገቡበት መሆኑን ያብራራል።እንደ ዘገባው በኦሞ ስምጥ ሸለቆ ለሽርሽር የሄዱት በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች 12 ስዊድናውያን የነበሩ መሆኑን እና የተኩስ እሩምታ እንደወረደባቸው ይገልፃል።አቶ ሞላ ይግዛው በስዊድን የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፎረም ምክትል ሊቀመንበር በጉዳዩ ላይ በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል -

''አስራ ሁለት የስዊድን ዜጎች አምባሳደሩን ጨምሮ ይላልእዛ ላይ አራት ሰዎች የጫነው መኪና ላይ ስዊድናውያንን ለመግደል ያለመ እና ያነጣጠረ ተኩስ ነው የተከፈተው።ከእዚህ ጋር በጥያየዘ ባለፈው ጊዜ H&M የተሰኘው ድርጅትን ያጋለጠ አንድ ጋዜጠኛ በእዛ አካባቢ ወይም ደቡብ ኢትዮያ የሚደረገውን ግፍ ለዓለም ማጋለጡ እና በዓለም የሌለ ዲክታተር መባሉ ይታወቃል።ከእዛ በፊት አንድ ቀን የስዊድን የጦር ፍርድቤት ያቀረብነውን የወንጀል ክስ ተቀብሎ ክስ እንደሚመሰርት አስታውቆ ነበር።በመሆኑም ይህንን ያደረገው ወያኔ ነው ሌላ ሊሆን አይችልም'' ብለዋል።

ኢሳት ራድዮ በመጨረሻ ላይ እንደገለፀው ጉዳዩን የስዊድን ጋዜጦች፣ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ሌሎች የመገናኝ ብዙሃን ሽፋን ቢሰጡትም ኢህአዲግ ም ሆነ የሚቆጣጠራቸው ራድዮ እና መገናኛ ብዙሃን እስካሁን ምንም ያሉት ነገር እንደሌለ ይገልፃል።

No comments: