Saturday, September 13, 2014

(ድብቅ ስትራቴጂ) የህወሓት ሥርዓት የአፋር ህዝብን መሬት የትግራይ ነው አለ

September 13,2014
(በአኩ ኢብን አፋር )
በሰሜናዊው የአፋር ክልል የሚገኙ የአፋር ክልል ወረዳዎች ዳሉልን ጨምሮ «የትግራይ መሬት ነው!» በማለት አፋቸው ሞልተው የሚናገሩ የህዋሓት መሪዎች ይደመጣሉ!! እሱም አብዓላ፣ ደሉል፤ ኮናባ፣ ባራህሌ፣ የትግራይ መሬት ነው ከሚባሉ ቦታዎች ይጠቀሳሉ። በኮናባ ወረዳ ከሁለት ሳምንታት በፊት በትግራይ ነዋሪዎችና በአፋር ነዋሪዎች መካከል ግጭት ተፈጥሮ አንድ የአፋር ወጣት ሲሞት 3 ደግሞ መቁሰላቸው ዘግበን ነበር። ችግሩ በሁለት ነዋሪዎች መካከል የሚፈጠር ግጭት አይደለም! የህዋሓት መንግስት የአፋር መሬትን ለመቀራመት የሚያደርገው ሆን ተብለው የሚደረጉ ትንኮሳዎች መሆናቸው ግልፅ ነው! «የኮናባ ወረዳ እና የአፅቢ ወረዳ የድምበር ወዝግብ የቆየ ቢሆንም የዛሬው በመንግስት ሆን ተብሎ የተፈጠረ በመሆኑ አሳስቦናል።» ይላሉ የኮናባ ነዋሪዎች።
afar region
የህዋሓት መንግስት ባለስልጣናት «መሬቱ የእኛ ነው እስከ ዳሉል የትግራይ መሬት ነው ብትፈልጉም ባትፈልጉም መንግስት እርምጃ ይወስዳል» ብለው ይናገራሉ። የአፋር የአገር ሽማግሌዎችን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች በነገሩ በመገረም «በመሬታችን እየሞተን ነው! ገና አሁንም እንሞታለን!» በማለት ባለፈው ሳምንት በውቅሮ የተደረገው ስብሰባ ያለ ምንም መፍተሄ ተበትኗል! በስብሰባው የትግራይ ክልልን ወከለው የተገኙት የውቅሮው የዞን አስተዳደር የዞኑ የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የአፅቢ ወረዳ መስተዳደርና የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ በአፋር በኩልም እንደዛው። ለእነርሱ ታማኝ የሆኑት የዞን 2 የመንግስት ባለስልጣናትና በርካታ የአገር ሽማግለዎች ተገኝተዋል!! በዚህ ስብሰባ በባለፈው ውግያ የንፁሃን ሰዎችን ህይወት ያጠፉትን ሰዎች የአፅቢ ወረዳ የፀጥታ ኃይሎች ለህግ እንዲያቀርቡ በአፋር ሽማግሌዎች የተጠየቁ ቢሆንም ሰሚ አላገኙም!! «ካሁን በኋላ» ይላሉ የኮናባ ወጣቶች «ካሁን በኋላ ሁላችን በተጠንቀቅ እንቆማለን እንሞታለን!»
ከመንግስት የምንጠብቀው ፍትህ የለም!!

No comments: