Saturday, July 19, 2014

አቶ አንዳርጋቸው ታፍኖ የተወሰደበት ቦታ እስከአሁን አልታወቀም ነገር ግን በደህንነት ሰዎች በደረሰበት ድብደባ ራሱን በመሳቱ ለህክምና ከአዲስ አበባ ውጪ ይዘውት ወጠዋል የሚሉ አስተያየቶች እየተበራከቱ ነው።

July 19, 2014
አባይ ሚዲያ 
አቶ አንዳርጋቸው ታፍኖ የተወሰደበት ቦታ እስከአሁን አልታወቀም ነገር ግን በደህንነት ሰዎች በደረሰበት ድብደባ ራሱን በመሳቱ ለህክምና ከአዲስ አበባ ውጪ ይዘውት ወጠዋል የሚሉ አስተያየቶች እየተበራከቱ ነው።
ዛሬ የአዲስ አበባ ምንጫችን ብዙ ቦታዎችን ለማካለል ሞክሬ ነበር ነገር ግን የአንዳርጋቸው ይኖርበታል ተብሎ የሚገመቱ ቦታዎችን ማግኘት እንዳልቻለ ይሁን እንጂ ከደህነነት ሰዎች አንዱ በሆነ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሊኖርም እንደሚችል የግል አስተያየቱን ልኮልናል።
ዘጋቢያችን አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በማናገር አቶ አንዳርጋቸው በአሁኑ ሰአት ከሰውነት ክፍሉ ውስጥ አንዱን ሰብረዉት ወይም ቆርጠውት እንደሚሆን  ስቃዩን በማብዛት ነገር ግን  እንዳይሞትባቸው ከአዲስ አበባ ውጪ ለህክምና ይዘውት ወጥተው ይሆናል የሚል በርካታ አስተያየቶች  መሰብሰቡን ዘግቦል።
አዲስ አበባ ላይ ሊያክሙት አይችሉም እንዴ ብለን ላነሳንለት ጥያቄ ሲመልስ፡ ይህን በአዲስ አበባ ሆስፒታሎች ሊያደርጉት አይችሉም 1ኛ መረጃው ይወጣባቸዋል የራሳቸውን ሆስፒታል እንኮን አዲስ አበባ ላይ አያምኑትም። በወያኔ ውስጥ ውጥረት አለ! ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሰውየውን ምን ማድረግ እንደሚገባቸው ግራ የገባቸው ይመስላል። ስለዚህ እውነትም በአካሉ ላይ ጉዳት ደርሶበት ከሆነ ወደ ማይታወቅበት ስፍራ ወስደው ሊያሳክሙት ይችላሉ የሚለው ገዢ ሃሳብ ያመዝናል።
ይሁን እንጂ አቶ አንዳርጋቸው በሚያደርሱበት ጭካኒያዊ ድብደባ ሂወቱ በድንገት ሊያልፍ የሚችልበት አጋጣሚም ከፍተኛ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ ኢቲቪ ድብደባውን በመደበቅ በደረሰበት አደጋ  ሂዎቱ በእስር ቤት አለፈ የሚል ዜና ሊያሰማን ይችላል የሚል ስጋት አለኝ ሲል አያይዞ ስጋቱን ገልጾልናል።
በዚህ አጋጣሚ አቶ አንዳርጋቸውን የታፈነበትን አካባቢ እና ቦታ ለድህረ ገጻችን ከሀገር ውስጥ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን መረጃ ለምትሰጡን አባይ ሚዲያ ማበረታቻ እንደሚሰጥ ማሳወቅ እንፈልጋለን፡፡

No comments: