Thursday, July 17, 2014

ስካርና ለቅሶ

July 17/2014
አርአያ ተስፋማሪያም
( በፎቶው ሰመሃል መለስ ከጥቁር አፍሪካዊ ወጣት ጋር…)
የአዜብ መስፍንና የመለስ ዜናዊ ልጅ የሆነችው ሰመሃል መለስ በየቀኑ ከልክ በላይ አልኮል እንደምትጐነጭ የቅርብ ታማኝ ምንጮች አስታውቀዋል። የ27 አመት ወጣቷ ሰመሃል አቅሏን እስክትስት ከጠጣች በኋላ እየተነፋረቀች እንደምታለቅስ ታውቋል። ቦሌ በሚገኘውና የቀድሞ ስዩም መስፍን መኖሪያ ቤት ውስጥ ከወላጅ እናትዋ ጋር የምትኖረው ሰመሃል የሚያስለቅሳት ነገር አስገራሚ ሆኖዋል። ሰመሃል በአባትዋ ሞት አሊያም በእናትዋ መታመምና በደረሰባት የፖለቲካ ኪሳራ እንዲሁም ብዙ ባለስልጣናት ስለማይጠይቋቸው “ተበሳጭታ” ይሆን የምታለቅሰው?..የሚሉት ዋናዎቹ ናቸው።

ሰመሃል ማወቅ ያለባት ነጥብ አለ። በሺህ የሚቆጠሩ ወገኖች እስር ቤት በማጐር፣ በመግደልና ቤተሰብ በመበተን፣ በማሰቃየትና ከአገር እንዲሰደዱ እንዲሁም በስደት እንዲያልቁ በማድረግ ወንጀል የፈፀሙት አባትዋ መለስ ዜናዊ እንደነበሩ ልታውቅ ይገባል። የ3 አመቱ ህፃን ናፍቆት አባቱን እስክንድር ነጋን ከጉያው እየደበደቡ ሲወስዱት ስቅስቅ ብሎ ሲያለቅስ አንቺ ምናልባት ከአባትሽ ጋር ትሳሳቂ ነበር። የ10 እና 13 አመት ታዳጊ ወጣቶች በምርጫ 97 በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ ቀጥታ ትእዛዝ የሰጡት (ያውም በቲቪ ወጥተው) አባትሽ መለስ ዜናዊ ናቸው። የነዛ ሕፃናት ወላጆች ዛሬም ያለቅሳሉ። በ10ሺዎች የሞቱለት የባድመ ጦርነት አስመልክቶ መሬት እንስጥ ያሉት መለስ ዜናዊ ፓርላማ ቀርበው « ቁራሽ መሬት ሄደ ብለን ሃዘን አንቀመጥም፤ ሙሾ አንወርድም» ብለው በጀግኖቹ መስዋእትነት የተሳለቁ ናቸው። የጀግኖቹ እናት ዛሬም ታለቅሳለች። አባትሽ ትተውት የሄዱት የዘርና ጐሳ ፖለቲካ አገሩን እያመሰው ይገኛል። መለስ አስፋፍተውት በሄዱት እስር ቤቶች ዛሬም ዜጐች በጅምላ እየተሰቃዩ ይገኛሉ። ስንቱን ልዘርዝረው!?...እኩል እናልቅስ!?

No comments: