Monday, July 7, 2014

ስብሃት ነጋ ከአሜሪካ መንግስት በወር 10.000 ዶላይ ደምወዝ ይከፈለዋል።

July7/2014
ምንሊክ ሳልሳዊ
ሕወሃት በኢትዮጵያ ውስጥ የትግራይ አይሁድ ስርአትን የመዘርጋት ምስጢራዊ እቅድ አለው።

በአሁን ወቅት ስብሃት ነጋ የያዘውን ስልጣን የቀድሞው የኢንስቲትዩቱ ፕረዝዳት የነበረው ዶክተር ክንፈ አብርሃ እንደሞተ ወያኔ ዶክተሩን የሚተካ ሰው በማጣቱ በትም ተቸግሮ ስለነበር ቦታውን እንዲይዝ የተፈለገው የትግራይ ተወላጅ ስለነበር አቶ መለስ ዜናዊ በዘር ቆጠራ ሲያጠያይቁ አንድ በሃይለስላሴ ጊዜ ወደ ካናዳ ለትምህርት ሂደው ደርግ ሲመጣ በዛው በጥገኝነት የቀሩ ህይወታቸውን ሙሉ ወርልድ ባንክ የሰሩ እና የተማሩ በጡረታ የሚኖሩ ዲያስፖራ አዛውንት ኢትዮጵያን በዘረኝነት ሳይሆን በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ብቻ የሚያውቛትን ዶክተር የትግራይ ተወላጅ አስጠርቶ ሊሾማቸው አስቦ አልተሳካለም። ለምን ?

እኚህ ካናዳ በጡረት የሚኖሩ አዛውንት በጊዜው የመለስ ዜናዊን ጥሪ ተቀብለው ወደ አዲስ አበባ መጥተው ነበር ። ገና ከአይሮፕላን ወርደው ወደ ኤርፖርቱ ከገቡ ጊዜ ጀምሮ እንዲሁም በሆቴሎች በመንገዶች ላይ የተመለከቱት በዞሩባቸው መስሪያ ቤትች ያሉ ነገሮችን በመታዘብ አስደንጋጭ ገተመኝ ሆኖባቸው ነበር ። ሁሉንም ሲያዩት ከአንድ ብሄር እና ከአንድ ቤተሰብ የተሳስረ ሃገሪቷ የአንድ ሰው ንብረት በሚመስል መልኩ ብሰንሰለት አደጋ ውስጥመሆኗን ሲናገሩ ተደምጠዋል። የአገሪቱ ተቋማት በአንድ ቋንቛ ተገጣጥመው እንደተሰሩ አላቂ ምርቶች አዲስ አበባ በመሰለ ሜትሮ ፖሊቲይን ከትማ ውስት መመልክታቸው እጅግ አስደንግጧቸው ነበር።

እኚህ ለጊዜው ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት ካናዳ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ በጥሪው መሰረት ከመለስ ዜናዊ ጋር በአካል ተገናኝተው በነበረ ጊዜ መለስ ዜናዊ የዶክተር ክንፈን ቦታ እንዲይዙልኝ ፈልጌ ነበር ያስመጣዎት ምክንያትም ይህ ቦታ እንደርሶ ያለ ልምድ ያለው ሰው እንዲይዘው ስለተፈለገ ስለሆነ እርሶን መሾም በ እጅጉ ያስፈልገናል ሲላቸው... ዶክተሩ ነገሩ ስለገባቸው የተጠሩት በ እውቀታቸው ሳይሆን የትግራይ ተወላጅ ብቻ ስለሆነ እንደሆነ ስለተደረዱ የገመቱትም ሆኖ ስለገጠማቸው መለስ ዜናዊን አንድ ጥያቄ ጠየቁት ... ለመሆኑ አገሩን ሁሉ ከላይ እስከ ታች በአንድ ጎሳ አዋቅራችሁ እስከመች መዝለቅ ትችላላችሁ ? በዚህ ዘመን በተለይ ፕራክቲክል ነው? ባላንስ ኦፍ ፓውር / የሃይል ሚዛኑ / ሽፍት ባይደረግ ምን ይውጣቹሃል ? ወዘተ የሚል ጥያቄ አንስተውበት ነበር፡፤

የመለስ መልስ ግን በወቅቱ አጭር ነበር " ይህ ነገር የትም እንደማያደርሰን እንውቀዋለን ።ነገር ግን በተቻለን መጠን ስልጣናችንን ሉዝ (ከማጣታችን) በፊት የትግራይ አይህድ ፈጥረን ማለፍ አለብን ብለን ወስነናል፡፤ ቁርጥ ያለ መልስ ነግሯቸዋል። በጥሪያቸው መሰረት ወደ አዲስ አበባ የመጡት አዛውንት ሃገሪቷ በአደገኛ የጎሳ ቫይርስ ውስጥ መሆኗን ተገንዝበው ከደሙ ንጹህ ነኝ ብለው መልሰውለት ወደ መጡበት ካናዳ ተመልሰዋል።

የትግራይ ይሁድ ለመፍጠር ማለት ልክ እስራኤላውያን በአለም ተሰራጭተው ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ እይስፈራሩ እንደሚኖሩት ሁሉ የትግራይ ተወላጆችም በህወሃት ውሳኔ መሰረት በአገሪቷ ቁልፍ ቦታዎችን በምያዝ ኢትዮጵይውያንን እያስፈራራ ለማኖር እና ለመግዛት እቅድ እንዳለው እኚሁ አዛውንት ተናግረዋል፤፡

እኚህ ምሁር አዛውንት አልቀበለውም ብለው ጥለው የሄዱትን ስልጣን ለስብሃት ነጋ ተሰጥቶት ደምወዙም 10.000 ዶላር ሲሆን ደሞዙንም የምትከፍለው አሜሪካ መሆኗን መረጃዎች ጠቁመዋል። 

No comments: