Monday, March 17, 2014

ኢትየጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ አንድ የኩዌት መንግስት ባለስልጣንን ልጅን ገደለች።

march 17/2014


ኢትጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የኩዌት የህዝብ ፣ የወጣቶች እና የስፖርት ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ሃሙድ ፉሊታ ልጅ የሆነችውን የ19 ዓመት ወጣት ነው ደረቷን እና ሆድዋን በቢላ 4 ቦታ በመውጋት የገደለቻት ።

ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ ስሟ ያልተጠቀሰ ቢሆንም የ22 አመት እድሜ እንዳላት ግን ተዘግቧል። ኢትዮጵያዊቷ ግድያውን ከፈጸመች በኋላ ለፖሊስ እጇን እንደሰጠች ለማወቅ የተቻለ ሲሆን አቃቢ ህግም ጉዳዩን እንደያዘው ታውቋል።

በተያዘው አመት ብቻ 13 የኪዌት ዜጎች በቤት ሰራተኞቻቸው መገደላቸውም ተጠቁሟል። በኩዌት የውስጥ ጉዳይ ሚንስቴር የህዝብ ጉዳዩቸ እና የደህንነት መረጃ ዳይሬክተር እንዳሉትት በኪዌት 81 ሺህ ኢትዮጵያዊያ ን ሰራተኞቸ የሚገኙ ሲሆን 45 ሺህ የሚሆኑት በቤት ሰራተኝነት የሚተዳደሩ ናቸው። ዳይሬክተሩ አክለውም በሃገሪቱ ለሚገኙ ህገወጥ ኢትዮጵያውያንን የሚየስጠልሉ ዜጎች ህጋዊ እርምጃ እንመሚወሰድባቸው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያዊያን የቤት ሰራተኞች በኩዌት ገብተው እንዳይሰሩ የታገደ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን አሁን ደግሞ የኪዌት አንድ የፓርላማ አባል በሃገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ከሃገር እንዲወጡ ፓርላማው እንዲወስን ጥያቄ አቅርቧል።

ለበለጠ መረጃ ➤➤➤ http://diretu.be/865737

No comments: