Friday, August 23, 2013

ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ ወደ ሃገሯ ለመመለስ በተዘጋጀችበት ወቅት እራሷን በገመድ አንቃ ገደለች

በትላንትናው እለት በሳኡዲ አረቢያ አስደንጋጭ የሆነ ትእይንት ተፈጥሮአል ፡ይሄውም በቤት ሰራተኝነት ለሁለት አመት አገልግሎት ወደ ሳኡዲ አረቢያ ሄዳ ሁለት አመቷን አጠናቃ ወደ ሃገሯ ለመመለስ ጊዜዋን በጨረሰችበት ወቅት እና እንዲሁም አሰሪዎቿ የሰራተኝነት ቪዛዋን ፣የጊዜ ገደቡን እንዲጨርስ አድርገው ጨርሰውላት ለመሄድ በተዘጋጀችበት ወቅት እራሷን ለማጥፋት በመወሰን በመኝታ ቤቷ በመግባት በገመድ እርሳሷን አጥፍታለች ሲሉ አሰሪዎቿ ለመገናና ብዙሃኖች ተናግረዋል ::
 
ምን እንደነካት አናውቅም እኛንም አስገርሞናል አስደንግጦናል ለሁለት አመታት ከእኛ ጋር ስትሰራ ምንም ችግር የለባትም ያለ ጊዜ ገደቡ የቪዛዋን ጉዳይ ጨርሰን በጠየቀችን መሰረት ልንሸኛት ሁላችንም በተዘጋጀንበት ሰአት እርሷን አጥፍታለች ያሉት አሰሪዋ ከሚኖሩበት ደቡባዊ ሳኡዲ አረቢያ ከሃሚስት ሙሽህቲ ከተማ አካባቢ ነው ።እስካሁን የማንነቷ ጉዳይ አልታወቀም !

No comments: