Wednesday, August 28, 2013

የግንቦት7 አባላት ናቸው የተባሉ ሰዎች ክስ ተመሰረተባቸው

ነሃሴ ፳፩(ሃያ አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከተለያዩ የአማራ አካባቢዎች ተያዙ የተባሉ 10 ሰዎች ዛሬ በአቃቂ 4ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል።
ዘመኑ ካሴ ከተባለው ሰው በስተቀር ሌሎች 9ኙ ተከሳሾች ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ለህዳር 2 ቀን፣2006 ዓ/ም ቀጠሮ ተሰጥቶአቸዋል።
ፍርድ ቤት ከቀረቡት መካከል የባህርዳር ከተማና ዙሪያዋ ነዋሪዎች የሆኑት አሸናፊ አካሉ፣ ደህናሁን ቤዛ፣ ምንዳየ ለማ፣ አንሙት የኔዋስ፣ ሳለኝ አሰፋ ፣ የክልሉ የማረሚያ ቤት ረዳት ምክትል ኢንስፔክተር ሙሉየ ማናየ ፣ ጸጋው ካሳ ፣ የአለም አካሉና ሙሉ ሲሳይ ይገኙበታል።
በግለሰቦች ላይ የተመሰረተው ክስ አሸባሪ ከሆነው ግንቦት 7 ጋር ግንኙነት በመፍጠር ጥቃት ለማድረስ ተንቀሳቅሰዋል ሚል ነው።
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የግንቦት7 ሊ/መንበር ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ መንግስት መብቱን የጠየቀውን ሁሉ ግንቦት 7 እያለ መወንጀሉ የተለመደ ባህሪው ነው ብለዋል
ገዢው ፓርቲ በመጪው እሁድ በሀይማኖት ጉዳይ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን በተመለከተ ምን አስተያየት አለዎት የተባሉት ዶ/ር ብርሀኑ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ህዝቡን በሀይማኖት ለማጋጨት ላቀደው እቅድ በተመለደ ትእግስቱ እንዲያከሽፈው ጠይቀዋል።

No comments: